የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ኢህደግ በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደውን ምርጫ ነጻና ሰላማዊ ከማድረግ ጋር በተያያዘ የአስልጣኞች ስልጠና ለከፍተኛ አመራሮቹ እየሰጠ ነው።

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የየመን አገር ውስጥ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ኢትዮጵያውያኑ  ሞቻ በሚባለው የወደብ ከተማ አቅራቢያ  ሲደርሱ የተሳፈሩበት ጀልባ በመስጠሙ 24ቱም አትዮጵያውያን አልቀዋል። የሁሉም አስከሬን መገኙቱን ባለስልጣኑ ሲናገሩ፣ የተረፉ ካሉም በማፈላለግ ላይ መሆኑን አስታውቋል። ባለፈው ወር ከ79 ያላነሱ ኢትዮጵያውያን ባህር ላይ ማለቃቸው ሲታወስ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ባህር ላይ የሞቱ ኢትዮጵያውያንን ቁጥር …

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ተማሪዎች ኢህአዴግን እንዲመርጡ በሚል በግዳጅ በተዘጋጀው የፖለቲካ ስልጠና ላይ ተማሪዎች ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን አስተያየቶችን ሰጥተዋል ። ኢህአዴግ እነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን የመሰሉ ሰዎችን አሸባሪዎች ማለቱ ትክክል አለመሆኑን የሚገልጹት ተማሪዎች፣ ኢህአዴግን የሚበልጡት በመሉ  አሸባሪ እያለ እንደሚፈርጃቸው ተናግረዋል ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የሚኖርበት ቤት 400 ሺ ብር እንደሚከፈልበት የተናገሩት ተማሪዎች፣ …

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ከመላው አገሪቱ ለተውጣጡ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች መጪውን ምርጫ በተመለከተ ስልጠና እየሰጠ ሲሆን፣ ከስልጠናው በፊት ማንኛውም ባለስልጣን ስልክ ይዞ መግባት እንደማይችል ጥብቅ የሆነ መልእክት በመተላለፉ፣ ሁሉም ባለስልጣናት ስልካቸውን መኪናቸው ውስጥ እየተዉ ወይም ለሹፌሮቻቸው እየሰጡ መግባታቸው ታውቋል። ወደ ስብሰባው የሚገባ ሰው ማንኛውንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን መያዙንና አለመያዙን ለማረጋገጥ  …

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ጥቅምት ወር በጎንደር፣ በትግራይና በጎጃም አካባቢዎች የተያዙ የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮች ፍድር ቤት ቀርበው የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል። ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው የሰማያዊ፣ የአንድነትና የመኢአድ ፓርቲዎች የዞን አመራሮች  ታህሳስ 21 ቀን 2007 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት ቀርበው ፣ አመራሮቹ ለ3ኛ ጊዜ የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል፡፡ “ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም፣ …

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል  በተለይም በአምቦ፣ በአለማያና በሌሎችም ዩኒቨርስቲዎች ለተፈጸሙ ግድያዎችና  በሌሎች  አካባቢዎች ለደረሱ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተጠያቂ የሆኑት ኮማንደር ፣ ታህሳስ 17 ቀን 2007 ዓም ሲያሽከረክሩት የነበረው መኪና ተገልብጦ ከ3 ጠባቂዎቻቸው ጋር በሂርናና አሰበ ተፈሪ መካከል በሚገኝ አንድ ገደላማ ቦታ ላይ ገብተው ህይወታቸው ወዲያውኑ አልፎአል። ኮማንደሩ የተሳፈሩበት …

የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ኢሀደግ በመጪው ግንቦት ውር የሚካሄደውን ምርጫ ነጻና ሰላማዊ ከማድረግ ጋር በተያያዘ የአስልጣኞች ስልጠና ለከፍተኛ አመራሮቹ እየሰጠ ነው።

(አቶ እያስፔድ ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚና የወጣቶች ክፍል ሃላፊ ናቸው። በቅርቡም ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት/ባንክ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ምክንያት ተባረዋል። በነገረ ኢትዮጵያ ብዙ ጊዜ ጽሁፎችን የሚያቀርቡ ወጣት ፖለቲካኛ ናቸው። በጋራ ህዝቡን ማታገል እንደሚገባ በመገልጽ በተለትም ለሰማያዊና ለአንድነት ፓርቲ ጥሩ ያቀረቡበት ጽሁፍን ያንብቡ) ለውጡ ይመጣል! ጥያቄው ግን ተዘጋጅተናል ወይ? ————————————————- ስለ 1966ቱ ለውጥ ብዙ ተብሏል፡፡ በለውጡ ወቅት […]

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የአንድነት፣ የሰማያዊና የመኢአድ አባላት ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ! ለጥር 19/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው! በሽብር ክስ ተጠርጥረው የመኢአድ፣ የሰማያዊና የአንድነት አመራሮች በዛሬው እለት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን የአንድነት ፓርቲ ጠበቃ አቶ ገበየሁ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም በነበረው ሰነድ፣ አሻራ እና ቃላቸውን ወስደዋል እንዲሁም አስረላጊ ምርመራም አካሂደዋል፡፡ ተጨማሪ ምንም ምርመራ ያደረጉት ነገር ስላልተገኘ ደምበኞቼን የዋስትና መብታቸው […]

አምና ሊባል አንድ ቀን የቀረዉ ጎርጎሪዮሳዊዉ 2014ዓ,ም በጤናዉ ረገድ ዓለም ያደናገጡ በሽታዎች የተከሰቱበት ነበር። በዚህ ዓመት ከታዩት በሽታዎች ሳርስ፣ ማርቡርግ እና የወፍ ጉንፋን በየተቀሰቀሱበት አካባቢ ሲወሰኑ፤ ኤቦላ ግን መነሻዉ ምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት ቢሆንም የተሐዋሲዉ ስርጭት በርካታ ቦታዎችን ነካክቷል።

ጥር
በልዩ ቅናሽ የመጻሕፍት ሽያጭ ወር
አግዮስ ኅትመትና ጠቅላላ ንግድ ሥራ ሐላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያሳተማቸውን
የዲያቆን ዳንኤል ክብረትና የሌሎችንም መጻሕፍት፤ የንባብ ባህላችንን ለማሳደግ እና አንባብያንን ለማበረታታት፤ ከ25% እስከ 50% (ከሃያ አምስት እስከ ሃምሣ በመቶ) ቅናሽ በማድረግ፤
ከጥር 1 እስከ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ባሉት ቀናት ውስጥ ለአንድ ወር
የሚቆይ ልዩ የመጻሕፍት ቅናሽ ሽያጭ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል፡፡
ቦታ፡- አግዮስ መጻሕፍት መደብር
አድራሻ፡- መገናኛ ለም ሆቴል አጠገብ፣ ማትያስ ሕንፃ ምድር ቤት (G – 06)
             ስልክ ቁጥር፡- 011 663 9902 / 0930098254
በተለይ ‹አራቱ ኃያላንን ላልገዛችሁ ይኼ መልካም አጋጣሚ ነው

ውድ አንባብያን መጻሕፍቱን በአዲስ አበባ ሌሎችም አካባቢዎች በወኪሎቻችን አማካኝነት በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ፤
      ለጉርድ ሾላ፣ ሲ ኤም ሲ ሚካኤል እና አካባቢው፤
መዝገቡ መጻሕፍት መደብር፤ ጉርድ ሾላ ቴሌ ፊት ለፊት፣ ዲ ኤም መንጃ ፈቃድ ት/ቤት ሕንፃ ሥር፤
                               ስልክ ቁጥር፡- 0912 951732
      አራት ኪሎ / ቅድስት ማርያም / አካባቢ፤
ፍሬው መጻሕፍት መደብር፤ ዐፄ ናዖድ ት/ቤት አጠገብ ስልክ ቁጥር፡- 0911 685232

      ፒያሳ አራዳ ጊዮርጊስ አካባቢ፤
ጌታቸው መጻሕፍት መደብር፤ አራዳ ጊዮርጊስ ጤና ጣቢያ ፊት ለፊት፤ ስልክ ቁጥር፡- 0911 469954
መኮንን መጻሕፍት መደብር፤ ስልክ ቁጥር፡- 0913 108312

ከትምህርት ቤትና ከመጻሕፍት ያገኙት ዕውቀት አራት ዓይና ያደረጋቸው ሊቁ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታዬ በተጠያቂነት ደረጃ የሚገኙና አገልግሎታቸውም ሙሉ ነበር፡- ቀዳሽና መዘምር፤ ጋዜጠኛና ሰባኬ ወንጌል፤ ጸሐፊና ተርጓሚ፤ አስተዳዳሪና መምህር፤ የአውራጃ አብያተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ፤ ኤርትራን ጨምሮ የአህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የስምንት መምሪያዎች ምክትልና ዋና ሓላፊ፡፡ ሊቁ በሓላፊነት በተመደቡባቸው ቦታዎች …

ለውጡ ይመጣል! ጥያቄው ግን ተዘጋጅተናል ወይ? ነው፡፡
————————————————-
ስለ 1966ቱ ለውጥ ብዙ ተብሏል፡፡ በለውጡ ወቅት የነበሩትን ሰዎችም ሆነ ሌሎቹን የሚያስማማ አንድ ነገር ቢኖር የለውጡ ግብታዊነት እና ለውጡን ሊሸከም የሚችል ድርጅት በወቅቱ አለመኖሩ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ቆመን ለውጡ ገና ነው ብለን ብንዘናጋ እንደ ኃይሌ ፊዳ ልንሳሳት የምችልባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ይመስሉኛል (ሀይሌ ፊዳ ከብርሀነ መስቀል ጋር ባደረጉት ውይይት ለውጡ ገና ነው ብዙ አመታትንም ይፈልጋል ብሎ ነበረ)፡፡ ከዚያ ይልቅ ለውጡን ለመቀበል በሚያስችል ተክለ ሰውነት ላይ ለመገኘት ምን እናድርግ የሚለው ላይ መዘጋጀት አስፈላጊ ነው፡፡

ብዙዎች በመኢሶን እና በኢህአፓ መካከል የነበረው ልዩነት ያለፈውን ትውልድ ዋጋ እንዳስከፈለው ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡ አንዳንዶች የሁለቱ ልዩነት የእናቸንፋለን እና የእናሸንፋለን የቃላት ጨዋታ ነበረ ሲሉ በሚያነሱት ሀሳብ ባልስማማም (ልዩነታቸው መሰረታዊ ነበር ብዬ ስለማምን) የሁለቱ ልዩነት ግን ትውልዱን ዋጋ ማስከፈሉን የማይቀበል ማንም ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡

ስለሁለቱ ልዩነት ሲነሳ ቢያንስ በሁለት ወቅቶች ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡
የመጀመሪያው ከለውጡ በፊት የነበረው እና ከለውጡም በኋላ እስከተወሰነ ድረስ አብሮ የዘለቀው የሁለቱ ፓርቲዎች የመደጋገፍ ጊዜ ነው፡፡ በአልጀርስ የነበረው የኢህአድ/ኢህአፓ መስራች ቡድን ከሀይሌ ፊዳው የመኢሶን መስራች ቡድን ጋር በአንዳንድ ነጥቦች ሳይስማሙ ቢለያዩም ልዩነታቸው ሰፊ የሚባል አልነበረም፡፡ ለዚህም ማሳያው የኢህአፓ ልሳን የነበረችው የዴሞክራሲያ የመጀመሪያ ዕትሞች እና የመኢሶን ልሳን የነበረችው የሰፊው ህዝብ ድምፅ ጋዜጣ የመጀመሪያ ዕትሞች በይዘት መመሳሰል እና በሀሳብ መደጋገፍ ነው፡፡ ይህ ሂደት እነ ሀይሌ ፊዳ ከውጪ ወደ ሀገር ቤት እስኪገቡ ድረስ የቀጠለ እንደነበርም ታሪክ መዝግቦ ያስቀመጠው ሀቅ ነው፡፡

ሁለተኛው ወቅት ደግሞ ለውጡ ከመጣ በኋላና እነ ሀይሌ ፊዳ ሀገር ቤት ከገቡ በኋላ ያለው እና በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለው ልዩነት መሰረታዊ እየሆነ የሄደበት እና በጣም የተለጠጠበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ወቅት በመኢሶን እና በኢህአፓ አመራሮች መካከል ግንኑነት ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም (ለአብነትም ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ከዶ/ር ሀይሌ ፊዳ ጋር፤ ነገደ ጎበዜ ከአለማየሁ ሀይሌ(ደርግ ውስጥ ሰርጎ የገባ የኢህአፓ ሰው ነው ይባል ነበር) ጋር ተገናኝተው አውርተዋል) ከረፈደ በኋላ የተደረገ ውይይት በመሆኑ ያመጣው ለውጥ አልነበረም፡፡

በእኔ እይታ ለሁለቱ ድርጅቶች አለመስማማት አቢዩ ምክንያት ከለውጡ በኋላ ኢህአፓ ሰፊ ህዝባዊ መሰረት (ማስ ቤዝ) ማግኘቱ በመኢሶን በኩል ለደርግ ሂሳዊ ድጋፍ እየሰጡ መቀጠል ይሻላል ወደሚለው ሀሳብ እንዲሄዱ የገፋቸው ይመስለኛል፡፡ ከመነሻው የነበራቸውን አነስተኛ ልዩነት አጥብበው በጋራ ቢሄዱ ኖሮ አንዳቸው ተለይቶ ህዝባዊ መሰረት የሚገነባበት እና ሌላኛቸው ህዝባዊ መሰረት ለመያዝ ከወታደሩ ጋር የሚሰለፍበት ሁናቴ አይኖርም ነበር፡፡

ለማንኛውም ይህን ያነሳሁት በታሪኩ ላይ ለመነታረክ ሳይሆን ዛሬም ከታሪክ ሳንማር ያለፈውን ስሀተት እንዳንደግም ካለኝ ፍርሀት ነው፡፡
ዛሬ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለይም ሰማያዊ እና አንድነት በጋራ ሆነው ለሚመጣው ለውጥ ራሳቸውን ካላዘጋጁ በስተቀር ከለውጡ በኋላ ልዩነታቸውን አጥብበው ለውጡ ተፈጥሯዊ ይዘቱን ጠብቆ ለሀገር በሚጠቅም መልኩ ለማስቀጠል ይችላሉ ማለት ዘበት ነው፡፡ ልዩነታቸውን አሁን ላይ ማጥበብ እና በጋራ መቆም ካልቻሉ ከለውጡ በኋላ እንደ ጠላት የሚተያዩበትም እድል እጅግ በጣም የሰፋ ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ፡፡ በተለይም ደግሞ ለውጡን ተከትሎ ከሁለት አንዳቸው ከፍ ያለ መስዋዕትነት የከፈሉ እንደሆነ፡፡

የተቃዋሚዎች በአንድ መቆም ለለውጡ ተዘጋጅቶ ለመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለውጡን ለማምጣትም የተሻለው እና አጭሩ መንገድ ነውና የየፓርቲዎቹ አመራሮች(በተለይም የሰማያዊ እና የአንድነት) ዛሬ ነገ ሳይሉ ቁጭ ብለው በመነጋገር ወደ አንድ የሚመጡበትን እና በጋራ ህዝቡን የሚያታግሉበትን መንገድ እንዲፈጥሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ ፡፡
Image

በደብረማርቆስ፣ ባሶ ሊበንና ሞጣ መረር ያለ ተቃውሞ ተነስተዋል::
በጎጃም የመሰናዶ ተማሪዎች የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ተቃውሙ አሰሙ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ሁሉም ትምህርት ቤቶች የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል መሰናዶ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቁመው እንዲወስዱ የተደረገውን የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ተቃውሞ ማሰማታቸውን ምንጮን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ወቅት የህዝቡ አስተሳሰብ፣ የግል ሚዲያ፣ ተቃዋሚዎች ለኢትዮጵያ እድገት ጠንቅ ተደርገው የቀረቡ ሲሆን ተማሪዎች ይህንን አቀራረብ ተቃውመውታል፡፡ በአንጻሩ ከወራት በፊት ስልጠናውን የወሰዱት መምህራንም ዳግመኛ ስልጠናውን እንዲወስዱ ተደርገዋል እየጠደረጉ ሲሆን ዝምታን መምረጣቸው ተገልጾአል፡፡

ተማሪዎቹ ‹‹የምርጫ ቅስቀሳ ከሆነ ለተቃዋሚዎችም ይፈቀድ፣ ለምን ለግጭት የሚጋብዙ ቅስቀሳ ትቀሰቅሳላችሁ፣ የኢህአዴግ ፖሊሲ ምሁራንንም ጭምር ለስደት የዳረገ ነው፣ ከቻይና እና ከኮሪያ የሚያስተሳስረን የታሪክም ሆነ የባህል መሰረት የለንም፣ ኢህአዴግ 23 አመት ያልተገበረውን ዴሞክራሲ ሊያስተምረን አይችልም›› የሚሉ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል፡፡

በስልጠናው ወቅት ተቃውሞዎች እየተነሱ ሲሆን በተለይም ደብረማርቆስ፣ ባሶ ሊበንና ሞጣ ላይ ተማሪዎቹ ‹‹ኢህአዴግ ሌላ፣ ኢህአዴግ ሌባ›› የሚል ጩኸት በማሰማታቸው ሲሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ 20፣ 20 ሆነው በየክፍሉ እንዲሰለጥኑ ተደርገዋል፡፡ በተለይ በደብረማርቆስ ከተማ በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹ የካድሬ ስልጠና አንሰለጥንም በማለት መረር ያለ ተቃውሞ እያሰሙ እንደሚገኙ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡


ታኅሣሥ 19 ቀን 2007 ዓም በቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታወቁት ሊቃውንት መካከል አንዱን አጥተናል፡፡ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየን፡፡ ስለ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በመቆርቆር፣ በማስተማርና በመጻፍ የምናውቃቸው፤ ቤተ ክርስቲያኒቱን ከጫፍ እስከ ጫፍ ያገለገሉ፤ በተለይም ለወጣቱ ትውልድ ጥያቄዎቹን በመመለስና አስረግጠውም በማስረዳት የምናደንቃቸው ነበሩ፡፡
ዜማ፣ አቋቋም፣ የአማርኛ ሰዋስው፣ ቅኔና የግእዝ አገባብ፣ ብሉይ፣ ሐዲስ፣ ነገረ መለኮት፣ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ በዘመናዊ ትምህርት እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የተማሩ መሆናቸውን ስናይ፤ በአንባቢነታቸው ጥንታውያንና ዘመናውያን መጻሕፍትን የሚያገላብጡ ብቻ ሳይሆኑ በላዔ መጻሕፍት እንደነበሩ በሌሎቹ ሊቃውንት ሲመሰከርላቸው፤ በምሥራች ድምጽ ሬዲዮ ትምህርት በመስጠት፣ በታሪክና ድርሰት ክፍል ለዐሥር ዓመታት በማገልገል፤ የመዝሙር ክፍልን በመምራት፣ የዜና ቤተ ክርስቲያንን በምክትልና በዋና አዘጋጅነት  በማገልገል፣ እንዲያውም ጋዜጣውን የጋዜጣ መልክ በማስያዛቸው በ1962 ዓም መሸለማቸውን  እያዘከርን የተጓዙበትን የዕውቀት ጎዳና ስንመረምር ያጣነው አንድ ሰው ብቻ ባለመሆኑ፡-
አራት ሰው ሞተ ተቀበረ ዛሬ
ድጓ ጾመ ድጓ መዋሥዕት ዝማሬ
ተብሎ ለሊቁ የተገጠመው ሙሾ ለእርሳቸውም ይስማማቸዋል እንላለን፡፡ 

የየረርና ከረዩ አውራጃ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ፣ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ዋና ጸሐፊ፣ የቀበና አቦ አስተዳዳሪ፣ የካህናት አስተዳደር መምሪያ ጸሐፊ፣ የኤርትራ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ የከፋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ የትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ ኃላፊ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ የአስተዳደር መምሪያ ኃላፊ፣ የቁጥጥር አገልግሎት ኃላፊ፣ የበጀትና ንብረት መምሪያ ኃላፊ፣ የስብከተ ወንጌል መምሪያ ኃላፊ፣ የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህት ቤት ምክትል ዲን፣ እየሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱን ማገልገላቸው ስንመለከት፡-
ቀባሪዎቹን
አፈር መልሱ እንጂ ድንጋይ ለምናችሁ
የቀለም ቀንድ ነው ትሰብሩታላችሁ
እንላቸዋለን፡፡
በ1977 በምዕራብ ጀርመን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ያሬዳዊ ዜማ ለማሳየት ከተጓዘው ልዑክ አንዱ ነበሩ፤ በ1995 የዓለም አብያተ ክርስቲያናት በእስክንድርያ ከተማ ባደረገው ጉባኤ ቤተ ክርስቲያንን ወክለው ነበር፣ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ በአዲስ መልክ ሲዘጋጅ በብርቱ ካገለገሉት ሊቃውንት አንዱ ነበሩ፣ የመንና ጅቡቲ የሚገኙ ምእመናንን ለማስተማር በየዓመቱ ይጓዙ ነበረ፡፡ የሊቃውንት ጉባኤ አባል ሆነው ለብዙ ዓመታት አገልግለዋል፡፡ ይህንን ስንመለከትም
እንግዲህ መቃብር ጠንክረህ ተማር
ዕውቀት ተሸክሞ መጣልህ መምር
እንለዋለን፡፡
ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በሚያዘጋጁት ጉባኤ ልጆችን ሳይንቁ፣ ክፍለ ሀገር በሚዘጋጅ ጉባኤ ለመንገዱ ሳይሰቀቁ በመጓዝ ያስተማሩ የዘመናችን ሐዋርያ ናቸው፡፡ ክህነትን፣ ትምህርትንና ጽሕፈትን አንድ አድርገው የያዙ፤ በተለይም ‹‹ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን›› እንደ አንድ የትምህርት ዘርፍ ሆኖ እንዲወጣ በብርቱ የደከሙ ሊቅ ናቸው፡፡ ድካማቸው ፍሬ አግኝቶ በየጊዜው ያዘጋጇቸው መጣጥፎችና መጻሕፍት ዛሬ ከኮሌጆች እስከ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ድረስ የማስተማርያ ዋና መሣሪያዎች ሆነዋል፡፤ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አንድ የትምህርት ዘርፍ ሆኖ እየተሰጠ ይገኛል፡፡
ሚያዝያ 19 ቀን 1929 ዓም  ይፋት ውስጥ  ደብረ ምሥራቅ ሾተል አምባ በኣታ አጥቢያ ተወልደው፣ በ1941 ዓም ከብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ዲቁና፣ በ1959 ዓም ቅስና ተቀብለው፤ አራት ወንዶችና አራት ሴቶች ወልደው፣ አሥር የልጅ ልጆች አይተው በ78 ዓመታቸው የተለዩን ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየ በዕለተ ዕረፍታቸውና ቀብራቸው ብዙዎችን ያስደነቁ ሁለት ነገሮች ተከስተዋል፡፡ የመጀመሪያው ክንፈ ገብርኤል ተብለው ተጠርተው በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል(ታኅሣሥ 19 ቀን) ወደ ፈጣሪያቸው መጠራታቸው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ሲከናወን የሕይወት ታሪካቸው በሚነበብበት ጊዜ ከትልቅ ዋርካ ላይ ማንም ሳይነካው አንድ ትልቅ ቅርንጫፍ ተገንድሶ መውደቁ ነው፡፡
ቦታው የነበሩ፣ ይህንንም ነገር የተመለከቱ ሁሉ ታሪኩን በካሜራቸው ሲቀርጹና ከታላቋ ዋርካ ከቤተ ክርስቲያን ብዙዎችን የያዘው አንዱ ታላቅ ቅርንጫፍ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል ዛሬ መሰናቱን በኀዘን ሲተረጉሙ ነበር፡፡ የቅርንጫፉን ቅጠልም ብዙዎቹ ተሻምተው ወስደውታል
በረከታቸው ይደርብን፡፡  


(አፈንዲ ሙተቂ)
—-
     ጎንደር ካፈራቻቸው ሰዎች መካከል አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የሚያውቀው እኝህ ሰው ይመስሉኛል፡፡ እኔ ጸሐፊው ስለርሳቸው የሰማሁት የቋራው መይሳው ካሳን ከማወቄ በፊት እንደሆነ አስታውሳለሁ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በአለቃ ገብረሃና ስም የሚነገሩ ቀልዶችን የነገረን ደግሞ ማን መሰላችሁ….? ከዚህ በፊት ያስተዋወቅኳችሁ የሁለተኛ ክፍል አለቃችን የነበረው አያሌው አብነት  ነው፡፡ ሆኖም እርሱ ያኔ የነገረንን እዚህ መጻፍ አይመችም፡፡ ስለዚህ የአያሌውን ቀልዶች ትተን ስለአለቃ ገብረሃና ከመዛግብት ያገኛቸውን ወጎች እንጨዋወታለን፡፡ ከዚያ በፊት ግን “ዐረፈ ዐይኔ ሐጎስ” “አለቃ ገብረሃ እና አስቂኝ ቀልዶቻቸው” በሚል ርዕስ ካሳተሙት መጽሐፍ ያገኘነውን የአለቃ ገብረሃናን ታሪክ አጠር አድርገን እናወሳለን፡፡
  
አለቃ ገብረሃና በሙሉ ስማቸው “ገብረሃና ደስታ ተገኝ” ይባላሉ፡፡ የተወለዱት በ1814 በጎንደር ክፍለ ሀገር በደብ ታቦር አውራጃ ፎገራ ወረዳ (አሁን ደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ) ውስጥ ነው፡፡ በተወለዱበት አካባቢ የቤተ ክህነት ትምህርት ተምረው በሃያ ስድስት ዓመታቸው የሊቀ-ካህናት ማዕረግ አግኝተዋል፡፡ በዚህ ሹመት ለሰባት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ በፍትሐ ነገሥት አዋቂነታቸው ተመርጠው ጎንደር ውስጥ በዳኝነት ተሾሙ፡፡
  አለቃ በካህንነትም ሆነ በዳኝነት ሲያገለግሉ እንደ ሌሎች የዘመኑ መኳንንት ቁጥብ አልነበሩም፡፡ ከተራው ህዝብም ሆነ ከመንግሥት ባለስልጣናት ጋር ይቃለዱ ነበር፡፡ ይህ ቀልደኝነታቸው እየገነነ ሄዶ በትንሹ ራስ ዓሊ ዘንድ ተሰማላቸው፡፡ በመሆኑም ወደ ቤተ መንግሥት ተጠርተው የራስ ዓሊ አጫዋች በመሆን ተሰየሙ፡፡ እንግዲህ ከዚህን ጊዜ ጀምሮ ነው አለቃ ገብረሃና የመኳንንቱና የመሳፍንቱ አጫዋች በመሆን ህይወታቸውን የገፉት፡፡
 
   አለቃ ገብረሃና በአጼ ዮሐንስም ሆነ በአጼ ምኒልክ ዘንድ ክብርና ሞገሥ አግኝተው እንደ ታላቅ ሰው ይታዩ ነበር፡፡ በአጼ ቴዎድሮስ ዘመን ግን ከፍተኛ ችግር ደርሶባቸው ነበር፡፡ ቴዎድሮስ አለቃን ያገኟቸው በቤተ መንግሥቱን ከራስ ዓሊ በተረከቡ ጊዜ ነው፡፡ ቴዎድሮስ አለቃን በዝና ቢያውቋቸውም ቀልድና ባልቱን አልወደዱላቸውም፡፡ ቴዎድሮስ ቀልዱን እንዲያቆሙና በዳኝነቱ እንዲቀጥሉ ቢገስጿቸውም አለቃ በጄ የሚሉ አልሆኑም፡፡ በመሆኑም አለቃን ከዳኝነታቸው ሽረው ትግራይ ውስጥ የሚገኘው የጨለቆት ሥላሤ ገዳም አስተዳዳሪ አድርገው ሾሟቸው፡፡ 
  
የደብሩ ቆይታ የቤተ መንግሥት ኑሮ ለለመዱት አለቃ ገብረሃና የሚመች አልሆነም፡፡ በዚያ ላይ አጼ ቴዎድሮስ ቤተ ክህነትን ርስት አልባ ለማድረግ መሞከራቸው ከሀገሬው ህዝብ ጋር አጣላቸው፡፡ በመሆኑም ካህናቱ ቴዎድሮስን ለመገልበጥ ማሴር ጀመሩ፡፡ አለቃ ገብረሃናም ዱለታውን ተቀላቀሉ፡፡ ይህም ወሬ ለአጼ ቴዎድሮስ ደረሳቸው፡፡ አጼውም አለቃ ገብረሃና ታስረው እንዲቀርቡ አዘዙ፡፡ ሆኖም አለቃ ገብረሃና ሸሽተው ጎጃም ውስጥ ከሚገኘው ዘጌ ገዳም ተደበቁ፡፡
   ከሁለት ዓመት በኋላ አጼ ቴዎድሮስ በመቅደላው ጦርነት ራሳቸውን ገደሉ፡፡ አለቃ ገብረሃናም ከተደበቁበት ወጥተው ወደ ጎንደር ተመለሱ፡፡ በ1864 አጼ ዮሐንስ አራተኛ ሲነግሡ በጎንደር ከተማ የነበራቸውን የቀድሞ ሹመታቸውን አጸደቁላቸው፡፡ በምኒልክ ጊዜ ደግሞ ወደ አዲስ አበባ መጥተው በእንጦጦ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን የአቋቋም እና የመርገድ አስተማሪ ሆኑ፡፡ ከጥቂት ቆይታ በኋላም የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ሆኑ፡፡
  አለቃ ገብረሃና በአዲስ አበባ ኑሮአቸው ከአጼ ምኒልክ ጋር ተዋድደው ይኖሩ ነበር፡፡ ነገር ግን እቴጌ ጣይቱ ቀልዳቸውንና ተረባቸውን አልወደዱላቸውም፡፡ በዚህም የተነሳ ሁለት ጊዜ ተጣልተው ወደ ደብረ ታቦር ሄደዋል፡፡ በሶስተኛው ዙር ግን ከአጼ ምኒልክም ጋራ ተቀያይመው ኖሮ እስከ መጨረሻው ተሰነባብተው ወደ ትውልድ ቄየአቸው ከሄዱ በኋላ እዚያው ኖረው በሰማኒያ አራት ዓመታቸው አርፈዋል፡፡
  አለቃ ገብረሃና መልከ መልካም ቢሆኑም አጭር ሰው ነበሩ፡፡ በዚህ ቁመታቸውም ከሌሎች ጋራ ብዙ ጊዜ ተቋስለዋል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ በእግራቸው መንሻፈፍ ሊቀልዱ ሲሞክሩ አለቃ ያልጠበቋቸውን መልሶች እየሰጧቸው “ኩም” ያደርጓቸው ነበር፡፡
   አለቃ ወይዘሮ ማዘንጊያ ከተባሉት ባለቤታቸው ተክሌ የተባለ ልጅ ወልደው ነበር፡፡ ይህ ልጃቸው በትምህርት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ የደብረ ታቦር እየሱስ ጉባኤ ቤተ ክርስቲያን ካህን እስከ መሆን ደርሷል፡፡ ሆኖም ጠላቶቹ ተመቀኝተውት መድኃኒት በጥበጠው በማጠጣት ገድለውታል፡፡
   *****
    በአለቃ ገብረሃና ስም የሚነገሩ ብዙ ጨዋታዎችና ቀልዶች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ በርሳቸው የተነገሩ መሆናቸው የተጻፈ ቢሆንም አንዳንዶቹ በጊዜ ሂደት የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ለበረካ ያህል በርሳቸው ስም የሚነገሩ ጥቂት ጨዋታዎችን እንቋደስ፡፡
   አንድ ጊዜ አለቃ ለግብዣ ተጠሩ፡፡ በግብዣው የቀረበው ጎመን ሆዳቸውን ቆዝሮአቸው ኖሮ ወደ እሳት ዳር ተጠጉና ሆዳቸውን ማሻሸት ጀመሩ፡፡ ጋባዣቸው ነገሩ ገርሞት “ምነው አለቃ! ሆድዎትን ምን ሆነው ነው” ሲላቸው “ረ ምንም አይደለም! ጎመኑን እያበሰልኩት ነው” በማለት መለሱላቸው፡፡
  በሌላ ጊዜ ደግሞ አለቃ የታመመ ሰው ሊጠይቁ ይሄዳሉ፡፡ የቤቱ ባለቤት ጠላ ትሰጣቸውና ታቀርብላቸዋል፡፡ አለቃ ጠላውን ፉት እያሉት ሳሉ ሴትዮዋ አመለጣት፡፡ አለቃ ጠላቸውን አገባደው ሲጨርሱ ሴትዮዋ ወደርሳቸው መጣችና “ልድገምዎት እንዴ አለቃ” በማለት ጠየቃቸው፡፡ አለቃም “አዎ! ግን እንደ ቅድሙ ጠረር አታድርጊው” አሏት፡፡
    አለቃ ስንቃቸውን በአገልግል ይዘው ከጥቂት ነጋዴዎች ጋር የዐባይ በረሃን በማቋረጥ ላይ ሳሉ ሽፍቶች በአካባቢው እንዳሉ ይሰማሉ፡፡ ነጋዴዎቹም ለገንዘባቸው አለቃም ለነፍሳቸው ተጨነቁ፡፡ “ምን እናድርግ” እያሉ በመመካከር ላይ ሳሉ አለቃ አንድ ዘዴ ትዝ ይላቸውና ነጋዴዎቹ ገንዘባቸውን እንዲሰጧቸው ይጠይቁአቸዋል፡፡ ነጋዴዎቹም የተጠየቁትን አደረጉ፡፡ አለቃም ገንዘቡን ከአገልግላቸው ውስጥ ከተቱት፡፡
    ጥቂት እንደተጓዙ ሽፍቶቹ ከጫካ ውስጥ ወጥተው “ያላችሁን ቁጭ አድርጉ” ይሏቸዋል፡፡ ነጋዴዎቹ ምንም የለንም ይላሉ፡፡ ሽፍቶቹ ወደ አለቃ ዞረው “በአገልግሉ ውስጥ ያለው ምንድነው” ብለው ጠየቋቸው፡፡ ብልሃተኛው አለቃ “ወላሂ! ወላሂ! ክሽን ያለች የዶሮ ወጥ ናት! ከፈለጋችሁ እዚሁ እንብላ” ብለው መለሱ፡፡ ሽፍቶቹም “በስመ አብ! እኛ የእስላም ስጋ አንበላም” እያሉ በማማተብ ለቀቋቸው፡፡
——
አፈንዲ ሙተቂ)
ታሕሳስ 2007


(አፈንዲ ሙተቂ)
—–አንድ–ኡምዱርማን (ሱዳን)—
አሕመድ ያ ሐቢቢ ሰላም ዐለይከ
ያ ሚስኪ ወጢቢ ሰላም ዐለይከ
ሰላም ዐለይከ ዘይነል አንቢያእ
ሰላም ዐለይከ አትቀል አትቂያእ
ሰላም ዐለይከ አስፈል አስፊያእ
ሰላም ዐለይከ ሚን ረብቢ ሰማእ
ሰላም ዐለይከ ዳኢማን ቢላ ኢንቲሃእ
——ሁለት–ገለምሶ—
1.      ሙሐመድ ሰላሙን ዐለይኩም
ሰይዲ ሰላም ዐለይኩም
ሰለዋቱላህ ዐለይኩም
2.     አላሁመ ሰሊ ዐላ ሰይዲና ሙሐመዲን ወዐላ ኩልሊ ነቢዪን
ወሰልሊ ዐላ አቢበክሪን ወዐላ ኩልሊ ወሊዪን
ወሰልሊ ዐላ ጂብሪለን ወዐላ ኩሊ መለክ
—-ሶስት– ጅማ—
አላህ አላህ ላኢላሀ ኢልለላህ
 ሙሐመዱን ረሱሉላሂ ሐቢቡ ዒንደላህ
ዐለይሂ ሰላቱ ወሰላሙ ሚነልላህ
—-አራት– ጅቡቲ—-
ሰላዋቱልላህ ዐለይከ ያ ሙሐመድ
ሰላሙልላህ ዐለይከ ያ ሙሐመድ
ሰላሙልላሂ ያ ኑረል ቁሉቢ
ያ ኑረል ቁሉቢ
—-አምስት– ሐረሪ—–
ሰሊ ያ ረብቢ ዐላ ሙሐመዲን
ሰሊም ያ ረብቢ ዐላ ሙሐመዲን
ባሪክ ያ ረብቢ ዐላ ሙሐመዲን
ኩሉ የውሚን ወለያሊን አልፈ መር
—-ስድስት– ወሎ—– 
ሰላቱ ወተስሊሙ ወ አዝካ ተሒቲን
ዐለል ሙስጠፈል ሃዲ ጣሃ ያ ሙሐመዲን
——————————————–

በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክንበመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡
የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት ሚዲያውን የሚመለከት ነው፡፡ በዚህ አዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የአንተርኔት ድረገጾች ፈቃድ ማውጣት የግድ መሆኑን ደንግጎአል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል የመረጃ መረብ አማካኝነት ለስርጭት የሚቀርብ ማንኛውም ፕሮግራም በአገር አንድነትና ሉአላዊነት ላይ አደጋ የሚጥል ፣በአገር ደህንነት፣ ክብርና ጥቅም ላይ ጉዳት የሚያደርስ ፣የአገር ሚስጢርን የሚገልጽ ፣ አመጽና ጦርነትን የሚቀሰቅስ፣ የሰው ልጆችን ስብዕና ፣ነጻነት ወይንም ስነምግባር የሚጻረር ፣የሌሎችን እምነት የሚያንኳስስ መሆን እንደሌለበት ደንግጎአል፡፡
በተጨማሪም ሥራዎቹ ማንኛውንም የህብረሰተብ ክፍል፣ ብሔር፣ጎሳ፣ቀለም፣ጾታ፣ዘር፣ቋንቋ፣ሃይማኖት፣ማህበራዊ አመጣጥ፣ ወይንም ሌላ መሰል አቋምንና ክብርን የሚነካ ወይም የሚያዋርድ፣ በህዝቦችና በሃይማኖቶች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይንም ጥላቻ የሚያስፋፋ፣ የግለሰብን ስም የሚያጠፋ፣፣ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆችን አመለካከት ስሜት የሚጎዳና ወደአልተፈለገ አቅጣጫ እንዲያዘነብሉ የሚገፋፋ፣ የህብረሰተቡን ሞራል የሚጥስ ወይንም በሕግ የተከለከለ ማንኛውንም ድርጊት የሚፈጽም መሆን የለበትም ይላል፡፡
ተጠያቂነትም በተመለከተ ረቂቅ አዋጁ እንዳሰፈረው በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራም ለሚያስከትለው ማንኛውም የወንጀል ድርጊት ወይም የፍትሐብሄር ጉዳት የፕሮግራሙ ሃላፊና የብሮድካስት አገልግሎት ሰጪው በአንድነት ተጠያቂ ይሆናሉ ይላል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራምን ቁጥጥርን በተመለከተ ከህብረተሰቡ በቅሬታ መልክ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የመመርመር፣ተቆጣጣሪ የመመደብ ስልጣን ወደፊት ለሚቋቋመው ባለስልጣን መ/ቤት ሃላፊነቱን ይሰጣል፡፡
ረቂቅ አዋጁ የቴሌቪዥንን ከአናሎግ ወደዲጂታል ሽግግርን ለማቀላጠፍና የግል ቴሌቪዥን ለመፍቀድ ይረዳል ተብሎአል፡፡ በዚህ ረቂቅ አዋጅ መሰረት ተጠሪነቱ ለጠ/ሚኒስትሩ የሆነ የኢትዮጵያ የሚዲያ ባለስልጣን የሚባል መ/ቤት ይቋቋማል፡፡
የብሮድካስት አግልግሎት የሚመራበትን ሥርዓት ለመደንገግ ከ15 ዓመታት በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 178/1991 የግል ቴሌቬዥን ጣቢያ ፈቃድ ለግል ባለሃብቶች የፈቀደ ቢሆንም ይህ ተግባራዊ ሳይሆን አዋጁ በቁጥር 533/1999 የተሻሻለ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተሸሻለውም አዋጅ ቢሆን የግል ቴሌቭዥን ጣቢያ የተፈቀደ ቢሆንም ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ኢትዮጵያ ለዚህ ደረጃ ገና አልበቃችም በማለት አዋጁ እንዳይፈጸም እስካሁን ድረስ መከልከሉ የሚታወቅ ነው፡፡

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው እሮብ ጀምሮ ለ3 ቀናት በተካሄደው የመሰናዶና የመምህራን የፖለቲካ ስልጠና ላይ የገዚውን ፓርቲ ካድሬዎች በጥያቄ ከማፋጠጥ ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ በሚታየው ዘረኝነት፣ የፍትህ እጦትና ሙስና ላይ አስተያየቶችን የሰጡ ተማሪዎች ከስብሰባው መጠናቀቅ በሁዋላ ተማሪውንና ህዝቡን ለአመጽ ለማነሳሳት አስባችሁዋል በሚል ማስጠንቀቂያና ባስፈራሪያ እንደደረሳቸው ዘጋቢያችን ገልጻለች። ለተማሪዎች በሚሊኒየም ትምህርት ቤት በፕላዝማ የተደገፈ …

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት ባወጣው የ2014 ሪፖርት ኢትዮጵያ ለግዳጅ ሥራ፣  ለወሲብ ንግድና  ለሕገወጥ የሰዎች ዝውውር የተዳረጉ ወንዶች፣ ሴቶች እና ሕፃናት መነሻ፤ በተወሰነ ደረጃም መዳረሻ አገር ናት ብሎአል። አዲስ አበባ የሚገኘው ዋና የገበያ ማዕከል ከአፍሪካ ቀዳሚው የወሲብ ንግድ ቤቶች መገኛ ነው የሚለው ሪፖርቱ፣  ዕድሜያቸው እስከ 8 ዓመት የሚሆኑ ልጃገረዶች በነዚህ …

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክንበመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን  ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡ የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት …

(ወልደብርሃን ስሁል) የዛሬ መቶ ሰባ ዓመት አካባቢ አንዲት “ሚጢጢየ” አውሮፓዊት ሃገር ማንም ሳይቀድማት ኢትዮጵያን በጉልበት ይዛ ቅኝ ለመግዛት “ክተት ሰራዊት ምታ ነጋሪት ብላ” ቆርጣ ተሰናዳች። በቆዳ ስፋቷ አንድ ትልቅ ወረዳ እምታክል ናት። አፍሪካ ውስጥ ግን የራሷን መቶ እጥፍ የሚያክል ግዛት መቆጣጠር እሚያስችል አቅምና እብሪት ነበራት። ህልሟን ለማሳካት ፕሮጀክት ቀርፃ feasibility study አካሄደች። እቅዷና ጥናቷ ያነጣጠረውም በዘመነመሳፍንቷ ኢትዮጵያ ላይ ነበር። የቀይ ባህር አካባቢ ደከም ባለ አውሮፓዊ ሃይል እንዲያዝ ትሻ የነበረችው ታላቋ ብሪታንያም ይሁንታ ሰጠቻት፤ በወርራ ቅኝ ልትገዛን ቆርጣ ለተነሳችው ቤልጅየም! ቤልጅየም ለኢትዮጵያ ያሰበችው ፕሮጄክት ብሎንዲል ከሚባል እብሪተኛ ሰው የጀብድ ልክፍት ጋር የተቆራኘ ነበር። ግብፅ በወርኔር ሙዚንጀር፤ ጣልያን በፔትሮ አንቶኖሊ ምን እንዳደረጉን ጠንቅቀን እናውቃለን። ከነሱ በፊት ቀድሞ ስለተሰናዳልን የብሎንዲል Humanitarian Mission ግን ብዙ አናውቅም። ነገሩ ያስገርማል እንጂ አያስቅም። “ገድለ‐ብሎንዲል” በጥቂቱ እንዲህ ነበር፦ የቤልጂግ መንግስት መጀመርያ በ1841 ከፍተኛ በጀት መድቦ ብዛት ያላቸው የስለላ ወኪሎቹን ወደ ግብጽ አሰማራ። ወኪሎቹም “ለሳይንሳዊ ጥናት እና ለሰብአዊ ተልእኮ” በሚሉ ሽፋኖች ካይሮ ላይ ከትመው ስለ ኢትዮጵያ ጥናት ጀመሩ። ማንኛውንም ዓይነት መረጃ በዝርዝር እየቀራረሙ ከሚያቀርቡት ሪፖርት የቤልጂየም ንጉስ ቀዳማዊ ሊዮፖልድ “በውስጧ ሁከት የነገሰባት ኢትዮጵያን” በቀላሉ መውረርና መቆጣጠር እንደሚችል አመነ። ለወረራም ቋመጠናም የሰላዮቹ አስተባባሪ በአካል ወደ ኢትዮጵያ ሂዶ “ሰብዓዊ ተልእኮ” የሚል ስም ያለው ጉብኝት እንዲያካሂድ አዘዘው። ዋናው ተልእኮው ግን ለወረራ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጥር እና ባስቸኳይ እሚተገበር የድርጊት መርሃ ግብር እንዲያዘጋጅ ነበር። […]

ትናንት በ19/04/07 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ የኮምቦልቻ ጽ/ቤት መከፈቱን ተከትሎ የማስተዋወቅ ስራ ሲሰሩ ከነበሩት የአንድነት አመራሮች መካከል አቶ ተማም መሀመድ በከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ተጠርተው ተጠይቀዋል፡፡ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎቹ ‹‹እናንተ ያለጊዜው የምርጫ ቅስቀሳ እያደረጋችሁ ነው፤ የፀጥታ ችግር ለመፍጠር እያሰባችሁ ነው፤ሳታሳውቁ ነው የምትሰሩት›› የሚሉ ጥያቄዎች ያቀረቡባቸው ሲሆን፤ አቶ ተማም እኛ ቢሯችንን ስንከፍት ተገቢውን የማሳወቂያ ደብዳቤ ለሚመለከታቸው […]

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

«ዓለም ከሁለተኛዉ ያዓለም ጦርነት ወዲሕ የዘንድሮን ያክል ሕዝብ ተሰዶ፤ተፈናቅሎባት አያዉቅም።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለበርካታ ሕዝብ አስቸኳይ እርዳታ እንዲያቀርብ የዘንድሮን ያክል ተጠይቆ አያዉቅም።»

የአፋር ነፃ አዉጪ ግንባር (ALF) ከአፋር መስተዳድር ገዢ ፓርቲ ከአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ)ጋር ያካሄደዉ ዉህደት ህገ ወጥ ነዉ በሚል በዶቼ ቬለ የተላለፈዉ ቃለ መጠይቅ ከሃቅ የራቀ ነዉ ሲል አስተባበለ።

የሶማልያ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አሸባብ የመረጃ ኃላፊ እንደሆኑ የተነገረላቸዉ ግለሰብ ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ ቅዳሜ በሶማልያ ለሚገኝ የአፍሪቃ ሕብረት ሰላም አስከባሪ ኃይልና ለሶማልያ መንግሥት ጦር እጃቸዉን ከሰጡ በኋላ ግለሰቡ ከዓመት በፊት ቡድኑን ጥለዉ መዉጣታቸዉን አሸባብ ዛሬ አስታወቀ።

Image
ከአውሮፓ ወደ ኤርትራ ለውህደቱ ስብሰባ እንዲሄድ የተወከለው በጀርመን የሚኖረው አቶ ካሳዬ መርሻ ወደ አስመራ እንዳይገባ በሻእቢያ መከልከሉ ሲታወቅ ከፊል ኤርትራዊ እንደሆነ የሚታወቀው እና ከአውስትራሊያ የተወከለው የወልቃይት ተወላጅ አቶ አለልኝ ከሻእቢያ ፈቃድ ማግኘቱ ታውቋል:: ነዋሪነት በጀርመን የሆነው እና ለአርበኞች ግንባር ትግል ታላቅ አስታውጾ እንዳበረከተ የሚነገርለት አቶ ካሳዬ መርሻ በግንባሩ አባላት አስፈላጊዉን ወጪ ተሸፍኖለት ለጉዞ ሲንደረደር በሻእቢያ መከልከሉ በውጪ የሚኖሩ የግንባሩ አባላትን ያሳሰበ ቢሆንም ሁኔታውን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑ ታውቋል::

በዚህ ምክንያት በውጪ የሚኖሩ የአርበኞች ግንባር አባላት እና ደጋፊዎች የተወከለው አቶ ካሳዬ እንዳይመጣ በሻእቢያ መከልከሉን በተመለከተ ያላቸውን ተቃውሞ በደብዳቤ መላካቸው ሲታወቅ በአስመራ የሚገኙ የግንባሩ አመራሮች ሁኔታውን እንዲፈቱ በደብዳቤያቸው ያሳውቁት አባላቱ በአግባቡ የተወከለው ሰው በውህደቱ ጉባዬ ላይ እንዲገኝ ሲሉ አቋማቸውን ገልጸዋል::የወከሉት ሰው በመከልከሉ በውህደቱ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬም አስምረውበታል::በቂ ሃይል እና ተንካራ መዋቅር እንዳለው የሚነገርለት አርበኞች ግንባት አባላቱ በኢትዮጵያ ለሚመጣው ለውጥ ተግተው እንደሚሰሩ እና ማንም እንደማያስቆማቸው ተናግረዋል::

አንድ አስተያየት ሰጪ እንደተናገሩት በሃገር ቤት ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃገራዊ አቋም እንዳይኖራቸው ሕወሓት/ኢሕ አዴግ በሰርጎ ገብነት እየገባ እንደሚያፋልሳቸው ሁሉ በውጪ የሚኖሩ ድርጅቶችንም እንዲሁ ሻእቢያ በውስጥ ጉዳያቸው እየገባ እሱ በሚፈልገው መልኩ እንዲሽከረከሩ ያደርጋል ሲሉ ተደምጠዋል::

ከጀርመን የተወከሉት አቶ ካሳዬ ወደ አስመራ እንዳይገቡ ካልተፈለገበት አንዱ ምክንያት ከዚህ ቀደም በግንባሩ ላይ በሻእቢያ የሚፈጸሙ ግፎችን ለማስቀረት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ ሲሆን የግንባሩ አባላት እና ታጋዮች ይህንን በደንብ ስለሚያውቁ በውህደቱ ላይ እንዲገኝላቸው ፍላጎቱ ቢኖራቸውም ሻእቢያ ግን አንድ ጊዜ ጥርስ ስለነከሰበት እንዳይመጣበት ከልክሏል::እንዲሁም በውጪ የሚኖሩ አባላት ውህደቱ ላይ ችግር ካለ እንዲወገድ ወደፊትም ችግሮች እንዳይፈጠሩ አመራሩን ለማስተካከል እና አማራጮችን መጠቀም በሚል ስልት አቶ ካሳዬ የራሱን የፖለቲካ ልምድ ተጠቅሞ ሊያስተካክል ይችላል እንዲሁም ያሉትን ችግሮች እንዲስተካከሉ በፊትለፊት ይናገራል የሚሉ ፍራቻዎች በሻእቢያ ስላሉ የተወከሉት አባል ወደ አስመራ እንዳይገቡ ከልክለዋል::

አቶ ካሳዬ ወደ አስመራ ሁለት ጊዜ ካሁን ቀደም ሂዶ ካለምንም ፍርሃት ለሻእቢያ ግንባሩን በተመለከተ ያለውን ችግር እና ወደፊት መሆን የለበትን ጉዳይ ካለፍርሃት አፍረጥርጦ ስለተናገረ እንዲሁም አቶ ካሳዬ የአርማጮ ተወላጅ በመሆኑ በአከባቢው ያለውን እና በግንባሩ ታጋዮች ዙሪያ ያለውን ጉዳይ አንስቶ ካለፍርሃት ለሻእቢያ መናገሩ ለአሁኑ መከልከል ምክንያት ቢሆንም ጉዳዩን ለመፍታት አስመራ እና አውሮፓ ያሉ የግንባሩ አመራሮች እየጥሩ መሆኑን ምንጮች ከአስመራ ተናግረዋል:
******************************************************************************
የወያኔ አየር ሃይል ባልደረቦች ይዘውት የገቡትን ሄሊኮፕተር ተከትሎ አቶ ኢሳያስ አፍወርቂ የአዲስ አመትን ጋዜጣዊ መግለጫ አስታከው ይናገራሉ ተብሎ በመጠበቅ ላይ ሲሆን የወያኔ ቃል አቀባዮች ሌመንግስት ታማኝ ለሆነ ጋዜጣ ሄሪኮፕተሩ ለማስመለስ ጥረት አለመደረጉን መግለጻቸው ቢታወቅም የሕወሓት ጦር ጄኔራሎች ግን ካልተመለሰ ምሳችንን አስመራ እንበላለን ሲሉ መደንፋታቸው የወያኔ ባለስልጣናቱን አለመናበብ አመልክቷል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ወያኔ በውጪ ከሚኖሩ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ለመደራደር ማንዣበቡን ፍንጮች ጠቁመዋል:: ወያኔ በስልጣን የመቆየት እድሉ እንደተመናመነ በማወቁ ድርድር የማድረግ ፍላጎት ማሳየቱ እና በታሪክ ልንከስም ነው ያሉት ባለስልጣንን ተከትሎ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ገዢው ፓርቲ የገባበትን አጣብቂኝ ሊወጣው ባለመቻሉ ውንደለመደው በማዘናጋት ጊዜ መግዣ መፈለጉን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል:: ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በወህኒ ቤት ዘረፋ እንደተካሄደባቸው አስታወቁ ‹‹በደምበኞቼ ላይ ዘረፋ ተፈፅሟል›› ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ‹‹በህይወቴ ላይ የደህንነት ስጋት አለብኝ›› አቶ ሀብታሙ አያሌው ‹ከፍተኛ በደል ተፈፅሞብኛል›› አቶ ዳንኤል ሺበሺ በእነ ዘላለም ወርቅነህ የክስ መዝገብ የተከሰሱት አራት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ላይ በወህኒ ቤት ውስጥ በመንግስት የደህንነት አባላት ዘረፋ እንደተካሄደባቸው ለፍርድ ቤት ተናገሩ፡፡ በሽብርተኝነት ተወንጅለው ክስ የተመሰረተባቸው […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጥር 3 በባህርዳር ለሚያደርገው ህዝባዊ ሰልፍ የቅድመ ዝግጅት ስራ የሚያከናውኑ ከፍተኛ የፓርቲው ልዑካን ወደ ስፍራው አምርቷል፤ ቀደም ሲል የሰሜን ቀጠና ሀላፊ አቶ አእምሮ አወቀ የሄዱ ሲሆን አሁን ደግሞ አቶ አስራት ጣሴና አቶ ብሩ በርመጅ ወደ ስፍራው አቅንተዋል። የከተማው አስተዳደር ሰልፉን ላለመፍቀድ አሁንም እያንገላገረ ቢሆንም፤ ህጉ በሚፈቅደው መሰረት የሰልፉን ቦታና ጊዜ አንድነት […]

አንድነት ፓርቲ፣ በወጣቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አማካኝነት በአዲስ አበባ በሚገኙ የተለያዩ ካፌዎች የሻይ ቡና ውይይት በማካሄድ ፓርቲውን በአዲስ መንገድ ማስተዋወቅ መጀመሩን የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ አቶ እንግዳ ወልደፃዲቅ፣ ለፍኖተ-ነፃነት ገለፁ። “ድምፅ አለኝ ምርጫ አለኝ” በሚል መሪ ቃል ታህሳስ 13 ቀን 2007 ዓ.ም የተጀመረው የሻይ ቡና ውይይት ለአንድ ሳምንት የሚዘልቅ ሲሆን የፕሮግራሙ አላማ “ህብረተሰቡ ስለምርጫው እንዲወያይ […]


በላይ ማናዬ

 በታላቁ መጽሐፍ የተጠቀሰ አንድ ታሪክ ላይ አንዲት እናት ልጇን በጓደኛዋ ስለመሰረቋ እናነባለን፡፡ ይህቺ እናት ልጄን ተሰረቅኩ ብላ ወደ ጠቢቡ ሰለሞን አቤት ትላለች፡፡ ጠቢቡ ሰለሞንም ሁለቱን ሴቶች ተሰረቀ ከተባለው ህጻን ጋር ተያይዘው እንዲቀርቡ ያደርጋል፡፡ ጠቢቡ ንጉስ ሰለሞን እውነተኛ እናት የትኛዋ እንደሆነች ለማወቅም የራሱን የምርመራ ዘዴ ሲጠቀም እናስተውላለን፡፡ በዚህም ሁለቱ ሴቶች የተካሰሱበትን ጉዳይ ሰለሞን በጥበብ ትክክለኛ ዳኝነት ሰጥቶ ያሰናብታቸዋል፡፡ ህጻኑም እውነተኛ እናቱን ያገኛል፡፡ ይህ ፍትህ የተሰጠው ከብዙ መመላለስ በኋላ አልነበረም፤ አፋጣኝና ትክክለኛ ፍርድ ነበር የተሰጠው፡፡
 እንደ ጠቢቡ ሰለሞን በአንድ ጀንበር በጥበብ ተከሳሽንና ከሳሽን ሰምቶ ትክክለኛ ውሳኔ የሚሰጥ የዳኝነት አካል እንዲኖረን በባዶ የምመኝ ሰው አይደለሁም፡፡ ነገር ግን ማነኛውም ተከሳሽ የተከሰሰበት ጉዳይ ተጣርቶ በፍጥነት ውሳኔ እንዲሰጠው፣ ፍትህ እንዲያገኝ እፈልጋለሁ፡፡ የዘገየ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራል ይባላል፡፡ ትክክለኛ አገላለጽ ነው፡፡ እውነትም በሀገራችን በዚህ አገላለጽ መሰረት ውሳኔ ተጓትቶባቸው፣ ፍትህ የተነፈጉ ብዙዎች ናቸው፡፡
 ማክሰኞ ጥቅምት 4 ቀን 2007 . በእነ እስማኤል ኑርሑሴን የክስ መዝገብ 1 አመት 6 ወር በላይ በእስር ሲሰቃዩ የቆዩ 12 ተማሪዎች እና 1 መምህር በመጨረሻ ብይናቸው ሲሰማ የሆነው ‹‹የዘገየ ፍትህ እንደተነጠቀ ይቆጠራል›› የሚለውን አባባል ያስረገጠ ነበር፡፡ ምክንያቱም ተከሳሾቹ ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የተበየነው 6 ወር እስር ብቻ ነበር፤ በእስር የቆዩት ግን 1 አመት 6 ወር ነበር፡፡ ይህ የሚያሳየን ተከሳሾቹ አፋጣኝ ፍትህ ባለማግኘታቸው ብቻ ተጨማሪ አንድ አመት እስርን በግፍ አሳልፈዋል ማለት ነው፡፡ በእነ እስማኤል ኑርሑሴን የክስ መዝገብ ያለአግባብ ከተፈረደባቸው ጊዜ በላይ በእስር ያሳለፉት ሰዎች ከጅግጅጋ፣ ከሲቪል ሰርቪስ፣ ከባህር ዳር፣ ከጅማ፣ ከደሴ፣ ከሐዋሳና ከደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲዎች ተለቅመው የታሰሩ 12 ሙስሊም ተማሪዎችና 1 አስተማሪን የተካተቱበት ነበር፡፡ በአጠቃላይ የተጓተተው ክስ ሂደት ብይን ለማግኘት 18 ወራትን ወስዷል፡፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ደግሞ ተከሳሾቹ በእስር ላይ ነበሩ፡፡ በግንቦት 2005 . ክስ የተመሰረተባቸው እነዚሁ ተማሪዎች በተለያዩ ሰበባሰበቦች ምክንያት ችሎቱ እየተጓተተ በመቆየቱና የፍትህ ስርዓቱ የዜጎችን መብት ማስከበር በማይችልበት ደረጃ በመኮላሸቱ ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እንኳ ክሳቸው ከሚያስፈርድባቸው በላይ በእስር እየቆዩ መሆኑን የህግ ባለሙያዎች ሲያሳስቡ ቆይተው ነበር፡፡ ሆኖም ግን ሰሚ ጆሮ አላገኙም ነበር፡፡ እነዚህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ለረጂም ጊዜ ተስተጓጉለዋል፡፡ ሊሰሩት የሚችሉት ነገር ሁሉ ተደናቅፎ መቆየቱም እሙን ነው፡፡ ታዲያ እነዚህ ሰዎች ፍትህ አገኙ ወይስ ተነፈጉ?
በነገራችን ላይ አፋጣኝ ፍትህ ማግኘት መሰረታዊ መብት (The right to speedy trial) ነው፡፡ በህግም ጥበቃ ያለው መሆኑን በተለያዩ ሀገራት ህጎች ተደንግጎ ይታያል፡፡ በአሜሪካ (The Sixth Amendment to the U.S. Constitution) በወንጀል የተከሰሱ ሰዎች አፋጣኝ ፍትህ የማግኘት መብት እንዳላቸው ተደንግጓል፡፡ በእርግጥም አፋጣኝ ፍትህ የማግኘት መብት ከድሮ ጀምሮ የነበረ መሰረታዊ መብት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በእንግሊዝ በንጉስ ሄነሪ ሁለተኛ (1154–1189) ጊዜ እንግሊዛውያን አፋጣኝ ፍትህ ማግኘት እንዳለባቸው በህግ ተደንግጎ ነበር፡፡ 1215 .. ደግሞ ንጉሱ በእጁ የሚገኙ የፍትህ ጥያቆችን ማዘግየት እንደማይችል በማግና ካርታ (Magna Charta) በግልጽ ደንግጎ ነበር፡፡ ይህ ፍትህን በአፋጣኝ የማግኘት መብት በኢፌዴሪ ህገመንግስት ላይ በግልጽ አልተቀመጠም፡፡ በህገመንግስቱ አንቀጽ 37 ላይ ‹‹ፍትህ የማግኘት መብት›› ሲገልጽ እንኳ አፋጣኝ ፍትህ የማግኘት መብትን በተመለከተ የሚለው ነገር የለም፡፡ ብዙ ዜጎች በህግ ጥላ ስር ውለው ክስ ተመስርቶባቸውም ይሁን ክስ ሳይመሰረትባቸውየፍትህ ያለህእያሉ በየእስር ቤቱ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ዜጎች የፍርድ ቤት ውሳኔው ራሱ ፍትሃዊ ነው በማይባልበት ሁኔታ እንኳ አፋጣኝ ብይን (‹‹ፍትህ››) ሲሽቱ ቢታይም የፍላጎታቸው ሲሞላላቸው አይታይም፡፡
 ባለፈው ሚያዝያ 17 ቀን 2006 . ለእስር የተዳረጉት የዞን 9 ጦማሪዎችና ጋዜጠኞች እንሆ ከታሰሩ 8 ወራት አልፈዋል፡፡ እስካሁንም ግን ክሳቸውን በውል አላወቁትም፡፡ ክስ ሳይመሰረትባቸው በምርመራ ሰበብ ወራትን አሳልፈው፣ ክሱ ተመሰረተ ከተባለ ጀምሮ የተመሰረተው ክስ እንዲሻሻል በሚል ሌላ ሰበብ እስካሁን ክሳቸው ምን ላይ እንዳረፈ በግልጽ አልታወቀም፡፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን ጦማሪዎቹና ጋዜጠኞቹ በእስር ላይ ናቸው፡፡ ከቀናት በፊት እስረኞቹ በሚገኙበት ቂሊንጦ እስር ቤት ተገኝቼ በጠየኳቸው ጊዜ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስና ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ በዋናነት አፋጣኝ ‹‹ፍትህ›› ማግኘት እንደሚሹ ነበር በአንክሮ የነገሩኝ፡፡ ናትናኤል ፈለቀ ይህን በተመለከተ፣ ‹‹ትክክለኛ ፍትህ አገኛለሁ የሚለው ተስፋዬ በጣም መነመነ ነው ነገር ግን ቢያንስ አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ እሻለሁ፡፡ ክሳችንን በውል ሳናውቀው ወራት ተቆጥረዋል፤ የሚታይ ጠብ የሚል ነገር እያየን ግን አይደለም›› ማለቱን አስታውሳለሁ፡፡ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስም በተመሳሳይ፣ ‹‹ፍትህ መጠበቁ ሞኝነት አንደሆነ ይገባኛል ውሳኔው ምንም ይሁን ምን ግን አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ እፈልጋለሁ›› ብሎ ነበር፡፡ ዳሩ ግን አሁን ባለው የተንዛዛ አሰራር ፍርድ ቤት መኖሩ፣ ዳኞች መሰየማቸው ብቻ ዜጎች ፍትህ እንዲያገኙ አያደርጋቸውም፡፡ የፍትህ ተቋማት የስርዓቱ አገልጋዮች በሆኑበት ሀገር አፋጣኝ ፍትህ ቀርቶ በተንዛዛው ሂደት ውስጥ አልፎም ቢሆን ትክክለኛ ፍትህን ማግኘት ቅዠት ይሆናል፡፡ ስለሆነም ዜጎች ፍትህ ያገኙ ዘንድ አጠቃላይ ስርዓቱን የመቀየር ወይም የማረቅ ትልቅ ስራ ይጠይቃል፡፡

«ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት ) እና የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ጭቁን ህዝቦች ጋር በመሆን ያካሄዱትን የትጥቅ ትግል በድል ያጠናቀቁት የውጭና የሌሎች ድጋፍ አግኝተው ሳይሆን የጠራ ህዝባዊ መስመር በመያዛቸው ነው» ሲሉ የህወሓት ሊቀመንበር አስታወቁ። ህወሓት የትጥቅ ትግል የጀመረበትን የደደቢት በረሃና ሌሎች ታሪካዊ ስፍራዎች በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገቡ ጥረት እንደ ሚያደርጉ ታሪካዊ ስፍራዎችን የጎበኙ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ገልጸዋል። የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በመጪው የካቲት የሚከበረውን የህወሓት 40ኛው ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በክልሉ የትጥቅ ትግል የተካሄደባቸውን ስፍራዎችና የማዘዣ ጣቢያዎችን ለአንድ ሳምንት ያህል ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የህወሓት ሊቀመንበር አቶ ዓባይ ወልዱ የጉብኝቱን መርሐ ግብር መጠናቀቅ አስመልክቶ ትናንት ማምሻውን በመቀሌ በተዘጋጀው የማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ እንደገለጹት፤ ህወሓትና የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ጭቁን ህዝቦች ጋር በመሆን የትጥቅ ትግሉን በአሸናፊነት ሊወጡ የቻሉት የጠራ ህዝባዊ መስመር በመያዛቸው ነው። የክልሉ ህዝብ ቀደም ሲሉ በነበሩትና በደርግ ሥርዓቶች ሲደርስበት የቆየውን ብሔራዊ ጭቆና ለማስወገድ ህወሓት የትጥቅ ትግሉ መጀመሩን ገልጸው፤ በወቅቱ የተሳሳተ ዓላማ ያነገቡ ኃይሎች ትግሉን ገና ከጅምሩ በእንጭ ጩ ለማኮላሸት ተንቀሳቅሰው እንደነበር አስታ ውሰዋል። «ህወሓት የያዘውን ህዝባዊ ዓለማና ትክክለኛ መስመር የሚደግፉ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎችን ከጎኑ እያሰለፈ ህዝቡን የትግሉ ባለቤት ማድረጉ ትግሉን በአሸናፊነት እንዲወጣ አስችሎታል» ብለዋል። ሊቀመንበሩ እንዳሉት ህወሓት በወቅቱ ሲያጋጥሙት የነበሩትን በርካታ ተግዳሮቶችና እንቅፋቶችን ተቋቋሞ ትግሉን በአሸናፊነት ሊወጣ የቻለው የጠራ ህዝባዊ መስመር በመያዙና ባለው የዓላማ ፅናት ነው። ህወሓትና የትግራይ ህዝብ የትጥቅ ትግሉን ያካሄዱት ይደርስባቸው የነበረውን […]

Image
ጌታቸው ሽፈራው
ያች ስለ መገንጠል የተዶለተባት ደደቢት በዓለም ቅርስነት ትመዝገብ እየተባለ ነው አሉ፡፡ አሜሪካኖች እርስ በእርስ ተዋግተው አገር ገንብተዋል፡፡ ጣሊያንና ጀርመኖች ደም ተፋስሰው አገር አቁመዋል፡፡ ምን አልባት እነዚህ አገራት ለአገር ግንባታ (አንድነት) ደም የፈሰሰባቸው ቦታዎች በራሳቸው ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ይሰጧቸው ይሆናል፡፡ እንጅ ዩኒስኮን መዝግብልን ብለው የተጃጃሉ አይመስለኝም፡፡ ኧረ እንዲያው ቢጠይቁስ ስለ አንድነት አጀንዳ የተነሳበት ቦታ (የግድ ከሆነ) ቅርስስ ቢሆን ምን አለበት?

ደደቢት የጠባብ ‹‹ብሄርተኝነት›› እንጅ የአገር ግንባታ መነሻ አይደለችም፡፡ የዓለም ህዝብ ከህወሓት አላማ ምን ሊማርበት ነው ደደቢትን ዓለም በቅርስነት የሚሸከመው? ከዚህ በተቃራኒ ቢቻል በዓለም አቀፍ ደረጃ ካልተቻለ ደግሞ በአፍሪካ ደረጃ አድዋ የሚከበርና የሚታወስ ቦታ ማድረግ ይቻል ነበር፡፡ ምክንያቱም የአፍሪካ የነጻነት ትግልም የሚፈነጥቀው ከዚህ ታሪካዊ ቦታ ነውና! ግን ይህ ኢትዮጵያና አፍሪካውያን እንጅ ህወሓት እንደ ቡድን ጥቅም አያገኝበትም፡፡ ከአላማው ጋርም ፍጹም የተለያዩ ናቸው፡፡

አሊያም ህወሓት ራሱ ተዋናይ የሆነበትን የሀውዜን ጭፍጨፋ በዓለም ከተደረጉ አስከፊ ጭፍጨፋዎች መዝገብ የሚባል ነገር ካለ ቢገባ ምክንያታዊ ይሆናል፡፡ ወይንም ደግሞ ከደርግ ጋር የተደረገውና በሁለቱም ወገን በርካታ ኢትዮጵያውያንን የጨረሰው የእርስ በእርስ ጦርነትን አስከፊነት ዓለም እንዲማርበት ቢደረግ ችግር ላይኖረው ይችላል፡፡ ቢያንስ ኢትዮጵያውያንም ሌላው ዓለምም ይማርበት ይሆናል፡፡

ደደቢት ምን ባይ ነች በዓለም ቅርስነት የምትመዘገበው? እንዲያው ፈረንጆቹን ‹‹ደደቢትን በዓለም ቅርስነት መዝግቡልን!›› ሲባሉ ምንድን ነው የሚሰማቸው? መቼስ ፈርዶብን በእነሱ ምክንያት ኢትዮጵያውያን ጅሎች ናቸው አይደለም የምንባለው? ሌላውን ነገር ለብቻቸው፤ ስድቡን ግን አብረን እንጋተዋለን፡፡ አይ አገር የመጋራት እዳው! ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር አይደለም የሚባለው?

እነዚህ ሰዎች በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ መለስ ዜናዊ የተቀመጡበት ባርጩማ፣ አልኮል የጠጡበት መለኪያ፣ የለበሱት ፒጃማ….በዚህ ከቀጠለም ሚስታቸው (አዜብ) ሳይቀሩ በዓለም ቅርስነት ይመዝገቡልን ብለው ወደ ዩኒስኮ መንከራተታቸው የሚቀር አይመስለኝም፡፡ ጋሻጃግሬም ይመዝገብ የሚል ድርጅታዊ ውሳኔ ከተላለፈ ደግሞ ለሰውዬው ቀኝ እጅ ሆነው ህዝብ ሲያስበዘብዙ የኖሩት እነ በረከት፣ አባዱላ፣ ሽፈራው ሽጉጡ….በቁማቸው የፖለቲካ ሉሲዎች መሆናቸው ነው፡፡ አይጣልኮነው!

እኔ በበኩሌ ከደደቢት ይልቅ ራሱ ህወሓት በ‹‹ቅርስነት›› ባይሆን ባንዳች አስገራሚ መዝገብ ላይ ቢሰፍር ምክንያታዊ ነው ባይ ነኝ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በዓለም ገዥ ሆኖ ገንጣይነቱን አንጠልጥሎ የሚዞር አስገራሚ ቡድን ህወሓት ብቻ በመሆኑ ነው፡፡ ገዥ ሆኖ ተገንጣይ ዓለም አይታ አታውቅም ነበር፡፡ አሁን ግን ጉዱ ህወሓት አለላት፡፡ በመሆኑም አንድ ቀን ትውልድ አፉን ይዞ ይስቅበት ዘንድ በአንዳች አስገራሚ መዝገብ ጎላ ብሎ ቢጻፍ ክፋት የለውም፡፡

እስከዛው ግን እነ አዜብ የስራ ሂደት ባለቤት ተቋቁሞላቸው በዓለም ቅርስነት የሚመዘገቡበት ሁኔታ እንዲመቻች አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እየጠየቅን ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ያለ አንዳች ተቃውሞ! ያለ አንዳች ድምጽ ታቅቦ! በቃ የባለራዩ ሚስት አዜብ መስፍን በቅርስነት ይመዝገቡ! ከተጃጃሉና ካሰደቡን አይቀር እስከዚህ ድረስ ነው እንጅ!

Image
ወያኔው የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የተከሰተውን አለመተማመን ለመቆጣጠር በድጋሚ እንቅስቃሴ ተጀመረ::
የወያኔ ተባባሪ ባለስልጣናት በውሳኔ ሰጭነት ጉዳዮች ላይ አንሳተፍም ሲሉ አማረሩ ::(ምንሊክ ሳልሳዊ)
የደህንነት አባላት ለጸረ ሰላም ሃይሎች እና ለጠላቶቻችን መረጃ እየሸጡ ነው ሲሉ በሃላፊው ተወንጅለዋል::

የመከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊቱ ከሃገሪቱ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር በማበር አደጋ ሊፈጥር ይችላል ሲል መፈራቱ እንዲሁም ሰራዊቱን እየከዱ የሚሄዱ መበራከታቸው አለመተማመኑን ከማስፋቱም በላይ በሕወሓት የጦር እና ደህንነት ክፍሎች ውስጥ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል ሲሉ ውስጥ አውቂዎች ይናገራሉ::ክዚህ ቀደም ተሞክሮ እንዳልተሳካ እና አሁንም ከባለፈው አካሄድ እና ግምገማ በተሻለ መልኩ በወያኔ መከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ አዳዲስ የሆኑ ውስጣዊ እርምጃዎችን በመውሰድ በተጠናከረ መልኩ በሰራዊቱ መካከል እየተከሰተ ያለውን አለመተማመን ለመቆጣጠር የሚረዱ ግምግናዎች እና የማጣሪያ ስብሰባዎች በስፋት መካሄድ የጀመሩ ሲሆን በፖሊስ ክፍሉ ውስጥ በተለይ በቡድን የሚያሴሩ ሰዎች አሉ እየተባለ ስለሚነገር የወያኔ አንድ ብሄር ሰዎችን በስፋት በመመደብ እንዲሁም ከዚህ ቀደም እንደተደረገው የቢሮ ሰራተኛውን ከደህንነት ቢሮ በሚመደቡ የሕወሓት ደህንነቶች ለመተካት የታቀደ ሲሆን ቀሪውን ከቢሮ ውጭ የሚሰራውን የፖሊስ አካል ለመቆጣጠር አዲስ ሃይል እንደሚመደብ ታውቋል።

የወያኔ ተባባሪ ባለስልጣናት በውሳኔ ሰጭነት ጉዳዮች ባለመሳተፋቸው ማማረራቸው ተሰምቷል በሃገሪቱ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መንግስት እንቅስቃሴ ውስጥ ከወያኔ ባለስልጣናት ውጪ ለበታች ተከታይ ባለስልጣናት ምንም አይነት መረጃ መስጠት እንደቆመ ሲታወቅ ማንኛውም ሃገራዊ ጉዳይ አልቆ እና በአፈጻጸም ደረጃ ላይ ሆኖ እንደማንኛውም ሰራተኛ እንደሚሰሙ ባለስልጣኖቹ በመናገር ላይ መሆናቸው ታውቋል ። በደህንነት ቢሮ ውስጥ በተደረገ ግምገማ የደህንነት አባላት መረጃዎችን በግል ጥቅም በመለወጥ አሳልፋቹ እየሸጣችሁ ናቸው በሚል መገምገማቸውን የውስጥ ምንጮች ተናግረዋል።እንደ ምንጮቹ ከሆነ መረጃን ያለምንም ርሕራሔ መረጃው በአምስት ደቂቃ ውስጥ ጠላት እጅ ገብቶ ያገኘነው ነው ሲሉ አንድ የደህንነት ሹም ተናግረዋል።በዚህ ግምገማ የተከፉት የደህንነት አባላት በመንግስት ባለስልጣናቱ እየተናጡ ቢወረፉም ዝምታን መርጠዋል።

የአንድነት ሰሜን አሜሪካ የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ባዘጋጀው የዛሬው ቴሌኮንፈራንስ የቴሌቭዥኝ ፣ የራዲዮ ጣቢያዎች፣ ድህረ ገጾችና ፓልቶክ ክፍሎች ተጋብዘዋል። በዚህ መሰረት ማህደረ አድነት ( አትላንታ)፣ ሕብር ራዲዮ (ላስ ቬጋስ)፣ መለከተ ራዲዮ ( ቫንኮቨር)፣ የአንድነት ድምጽ ራዲዮ ( ዲሲ)፣ የአዲስ ድምጽ ራዲዮ (ዲሲ)፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች አንድነት ድምጽ ራዲዮ፣ አቡጊዳ፣ ሳተናው እና ዘሃበሻ ድህረ ገጾች፣ የቃሌ፣ የከረንት አፌር […]

(አቶ እያስፔድ ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚና የወጣቶች ክፍል ሃላፊ ናቸው። በቅርቡም ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት/ባንክ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ምክንያት ተባረዋል። በነገረ ኢትዮጵያ ብዙ ጊዜ ጽሁፎችን የሚያቀርቡ ወጣት ፖለቲካኛ ናቸው። በትብብሩና በአንድነት መካካል ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነት የሚከተለዉን ጽሁፍ አቅርበዋል። አንድነት ትብብሩ ውስጥ ለመግባት ያስቀመጣቸው ቅድመሁናዎች ሊሟሉ ይችላሉን? (የሰማያዊ አመራር) የፓርቲዎች መተባበር እና ጋራ መቆም እጅግ በጣም አስፈላጊ […]

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 17፣ 2007 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሁለት ሳውዲ አረቢያዊያን እንስቶች መኪና በማሽከርከራቸው በሽብር ወንጀል ተከሰሱ።

ሎጃን አል ሃትሎል እና ማይሳ አል አሞዲ በሀገሪቱ እንስቶች መኪና እንዳያሽከረክሩ የሚያዘውን ህግ ከመጣሳቸውም ባሻገር በማህበራዊ ድረ ገጾቻቸው ሴቶች መኪና የማሽከርከር መብት ሊኖራቸው ይገባል በማለት ቀስቅሰዋል በሚል ነው ክስ…