ተቃዋሚ ሃይሎች ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ሰብረው በመግባት ስርአቱን ማፍረስ ያለባቸው ወቅት ነው:: ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን የፖለቲካ የምጣኔ ሃብት እና የማሕበራዊ ቀውስ እና ውጥረት ተከትሎ የባለስልጣናት አረመረጋጋት ታክሎበት በገዢው መደብ የተዋቀረው የደሕንነት ተቋም መናጋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ የላኩት መረጃ ጠቁሟል::እንደውስጥ አዋቂ ምንጮች ዘገባ ከሆነ የደህንነት አባላቱ ቡድን እና ብሄር በመለየት በሃላፊዎቻቸው ላይ ያላቸውን ጥላቻ […]

ሃሳብን ለመግለፅ መቻል መታደል ነው፡፡ የመናገር ነፃነት፣ ሃሳብን የመግለፅ ነፃነት፣ የመሰብሰብና የመደራጀት ጉዳዮች ሁሉም የዲሞክራሲ ልጅ-ልጆች ናቸው፡፡ የከፋው ኢ- ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት “ኦሆሆ አሃሃ!” ማለትንም እንደማይፈቅድ ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ አንዳንዴ የተከለከለውን በማየት የተፈቀደውን የማየት እድል ይገኛል፡፡ ተበታትኖ ማሰብ የሃሳብ ልዩነትን ለማየት የሚያግዘንን ያህል፤ አንድ ላይ ሆነን ማሰብ የአንድነትን ጉልበት ያሳውቀናል፡፡ ዞሮ ዞሮ አንድነትም ልዩነትም በህብር መያዝ […]

ተቃዋሚ ሃይሎች ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ሰብረው በመግባት ስርአቱን ማፍረስ ያለባቸው ወቅት ነው:: ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን የፖለቲካ የምጣኔ ሃብት እና የማሕበራዊ ቀውስ እና ውጥረት ተከትሎ የባለስልጣናት አረመረጋጋት ታክሎበት በገዢው መደብ የተዋቀረው የደሕንነት ተቋም መናጋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ የላኩት መረጃ ጠቁሟል::እንደውስጥ አዋቂ ምንጮች ዘገባ ከሆነ የደህንነት አባላቱ ቡድን እና ብሄር በመለየት በሃላፊዎቻቸው ላይ ያላቸውን ጥላቻ […]

The post የኢሕአዴግ የደህንነት መዋቅር መናጋቱን ምንጮች ጠቆሙ:: appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

Image

ተቃዋሚ ሃይሎች ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ሰብረው በመግባት ስርአቱን ማፍረስ ያለባቸው ወቅት ነው::
Minilik Salsawi : ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን የፖለቲካ የምጣኔ ሃብት እና የማሕበራዊ ቀውስ እና ውጥረት ተከትሎ የባለስልጣናት አረመረጋጋት ታክሎበት በገዢው መደብ የተዋቀረው የደሕንነት ተቋም መናጋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ የላኩት መረጃ ጠቁሟል::እንደውስጥ አዋቂ ምንጮች ዘገባ ከሆነ የደህንነት አባላቱ ቡድን እና ብሄር በመለየት በሃላፊዎቻቸው ላይ ያላቸውን ጥላቻ እና ተቃውሞ እያሰሙ ሲሆን ለአንድ ብሄር ብቻ ተለይቶ የሚደረገው የበላይነት አድሎአዊ አሰራር ፍትሃዊነትን ሳይሆን የበታችነታችሁን ያሳብቅባቹሃል የሚሉ ጠንካራ ቡድኖች ከኢሚግሬሽን እና ደህንነት መምሪያ አከባቢ መከሰታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል::

የደህንነት አባላቱ በዜጎች መካከል በሚደረግ አድሏዊ አሰራር ለሃገር ይጠቅማሉ የተባሉ አባላትን በየክፍለ ሃገሩ በማዘዋወር ከችሎታቸው እና ከሰለጠኑት የደህንነት ሙያ ጋር የማይገናኝ ስራ ላይ በመመደብ መረጃ አምጡ ማለት የስርአቱን ዝቅጠት ከማሳየቱም በላይ በቀበሌ ካድሬዎች እና በመንደር ጆሮ ጤቢዎች የሚሰበሰቡ መረጃዎችን አሜሪካ እና እስራኤል ሰልጥነው በመጡ የአማራ እኦሮሚያ እና የደቡብ ክልል የደህንነት አባላት ማሰለል ስር አቱ ምን ያህል መዋቅሩን እንደሳተ እና በሰለጠኑ ዜጎች ላይ ሃገራዊ እምነት እንዳሌለው ያሳያል ሲሉ ምንጮቹ ተናግረዋል::

በውጭ አገር ሰልጥነው የመጡ የደህንነት አባላት ወደ ሃገራዊ የደህንነት መረጃ ሃይሎች እና ጉዳዮች እንዳይጠጉ የሚደረግ ሲሆን በቦታው ከዚህ ቀደም የተመደቡም ቢሆኑ በመረጃ መውር ውስጥ እንዳይሳተፉ ሲደረግ የአንድ ብሄር ተወላጆች በዚህ ላይ እንዲቀሳቀሱ መደረጉ ለስር አቱ ሰዎች አደጋ እና የመዋቅር መናጋት የፈጠረ ሲሆን አንዳንድ የሕወሓት አባላት አብረውን ውጪ አግር ሰልጥነው የመጡ አባሎቻችን የት ሄዱ ለምን አብረውን አይሰሩም በማለት በመዋቅሩ ውስጥ አደጋ ሆነው በመገኘት መናጋቱን እንዳጦዙት ታውቋል::

እንደ ምንጮቹ ከሆነ በአሁኑ ውቅት በሰራዊት ውስጥ እና በደህንነቱ ውስጥ የመዋቅር መናጋት አለመተማመን እና የእርስ በርስ ፍትጊያዎች በስፋት እየታዩ በመሆኑ በሃገር ውስጥ እና በውጭ አገር ያሉ ተቃዋሚዎች ይህንን ክፍተት እና የመዋቅር መናጋት እንዲሁም የውስጥ ሽኩቻን ተገን በማድረግ ሰርገው በመግባት ለስርአቱ መውደቅ ተጨማሪ ሃይል ሊሆኑ ይገባል ሲሉ ምክራቸውን ለግሰዋል::

ጥር ፲፩(አስራ አንድ ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጎንደር በፋሲል ግንብ አጠገብ በተከበረው በዓለ-ጥምቀት ከትናን የከተራ እለት ጀምሮ በርካታ ቱሪስቶች መገኝታቸውን ወኪላችን ከስፍራው ዘግቧል። በዓሉ በአዲሰ አበባ ጃን ሜዳም – እንደ ወትሮው ሁሉ እጅግ በደመቀ ሁኔታ መከበሩ ታውቋል። በላሊበላ እጅግ በርካታ ቀሳውስት ተገኝተው በወረብና በዝማሬ ማክበራቸውንም በስፍራው ያለችው ወኪላችን የላከችው መረጃ ያመለክታል። እንዲሁም በተለያዩ የውጪ …

ጥር ፲፩(አስራ አንድ ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወይዘሮ የምስራች በተለይ ለኢሳት  ሲናገሩ፤ አቶ አንዳርጋቸው ካልታወቀ እስር ቤት ሆነው ልጆቻቸውንና የቤተሰቡን አባላት ድንገት ሲያናግሩ ደንግጠው እንደነበር በመጥቀስ፤ ድንገት የተደወለውን ስልክ ሲያነሱ በድምጻቸው ወዲያው እንደለዩዋቸው ግልጸዋል። ሰላምታ ከተለዋወጡ በሁዋላ ጤንነታቸውን በተመለከተ እንደተጠያየቁና   አቶ አንዳርጋቸው በደህና ጤንነት ላይ መሆናቸውን እንደገለጹላቸውም ወዘይሮ የምስራች ተናግረዋል። <<ድምጹን ሥንሰማው  ደስታም፣ድንጋጤም …

ጥር ፲፩(አስራ አንድ ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በባህር ዳር ከተማ  ለከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች  መምህራን ሲካሄድ የቆየው ስብሰባ የታሰበለትን ዓላማ ሳያሳካ መጠናቀቁን በስፍራው የሚገኘው የኢሳት ወኪል ያጠናቀረው መረጃ ያመለክታል። መንግስት  ሰሞኑን ትምህርት ቤቶችን ለአንድ ሳምንት በመዝጋት ለግልና ለመንግስት መምህራን ሲሰጠው የቆየው ስልጠና በሚጠናቀቅበት ጊዜ መምህራን  በተሰጡት በሁሉም ርዕሶች ላይ ስምምነት ላይ …

ጥር ፲፩(አስራ አንድ ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጎንደር ዙሪያ ወረዳ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) አስተባባሪ  የሆነው ወጣት ዘመነ ምረተአብ ትናንት ጥር 10 ቀን  11:00  አካባቢ  በማክሰኝት ከከተራ በዓል ላይ ባልታወቁ ሰዎች ተወስዷል። አፋኞቹ ዘመነ ምረተአብን ወዴት እንደወሰዱትና በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ እስካሁን አልታወቀም። ቀደም ሲል የታሰሩት  የመኢአድ የቀድሞ  ዋና ጸሃፊ አቶ ተስፋየ ታሪኩ፣ የድርጅቱ …

ጥር ፲፩(አስራ አንድ ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካራቱሪ በበኩሉ መንግስት አስፈላጊውን ነገር አላመቻቸልኝም ባይ ነው። የህንዱ ግዙፍ ኩባንያ <<ካሩቱሪ ግሎባል ሊሚትድ>> በኢትዮጵያ ሲያደርግ በቆየው የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ መንግሥት እምነት እንዳጣበት መግለጹን ሪፖርተር ዘግቧል። አቶ አበራ ሙላት ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፣ ኩባንያው ይጠበቅበት የነበረውን ሥራ ማከናወን ሳይችል ቀርቷል፡፡ በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንትና መሬት አስተዳደር …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በኢትዮጵያ በክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች ዘንድ ዛሬ የጥምቀት በዓል በደማቅ ተከብሮአል። የጥምቀት በዓል ከጊዜ ወደ ጊዜ የዓለም አቀፉን ሕብረተሰብ ቀልብ እየሳበ በመምጣቱ የአከባበር ሥነ-ስርዓቱን በተመ የትምሕርት፤የሳይንስና የባሕል ድርጅት «UNESCO» ጥበቃ ስር በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተመልክቶአል።

በምጸታዊ ካርቱኖቹ የሚታወቀው የፈረንሳዩ ሻርሊ ኤብዶ ጋዜጣ ከተፈጸመበት ጥቃት ማግስት ለህትመት የበቃው እትም በዓለም ዙሪያ ቁጣን ቀስቅሷል። በድጋሚ በነብዩ መሐመድ ላይ የሚሳለቅ ምስል ይዞ ብቅ ያለው የፈረንሳይ ጋዜጣ በእስያ፤መካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪቃ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል።

የአይቮሪኮስቱ አጥቂ ዊልፍሬድ ቦኒ በ32,3 ሚሊዮን ዩሮ ከስዋንሲ ሲቲ ወደ ማንቸስተር ሲቲ ተዛውሯል። የክሮሺያው ግብ አዳኝ ወጣት አንድሬ ክራማሪችም የእንግሊዙ ሌስተር ሲቲን ተቀላቅሏል። በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ ውጤቶች የሚንደረደረው የዛሬው የስፖርት ጥንቅራችን ዝውውርን የሚመለከቱ እና ሌሎች ስፖርት ነክ ዜናዎችን አካቷል።

ከ30በላይ የዓለም ቋንቋዎች ዝግጅቶችን የሚያሰራጨዉ ዶይቼ ቬለ ራድዮ እና የጀርመን የባህል ተቋም በመተባበር ባዘጋጁት መድረክ በአዲስ አበባ ከሚገኙ ሦስት ትምህርት ቤቶች ለተዉጣጡ ተማሪዎች በሙዚቃ የተደገፈ የጀርመንኛ ቋንቋ ትምህርት ተሰጠ።

ኩሊባሊ የኮሸር የገበያ አዳራሽ ሺያጭ-ሸማቾችን አግቶ ጥያቄዉ ካልተሟላለት ታጋቾቹን እንደሚገድል ሲዝት፤ ሲፎክር፤ ባቲሌይ እቅርቡ ያሉትን ገበያተኞች ይዞ-ከምድር በታች ወደሚገኘዉ ሸቀጥ ማከማቻ ክፍል ወረደ።

Hiber Radio: የአፋር ነፃ አውጭ ግንባር ማስጠንቀቂያ… የኤርትራና የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች በአስመራና በአዲስ አበባ… አንድነትና መኢአድ ምርጫ ቦርድን መክሰሳቸው… ኢሳያስ አንድ የሱዳን ጀነራል ኢትዮጵያን አጥፋ ብሎኝ ነበር ስለማለታቸው… ሌሎችም   የህብር ሬዲዮ ጥር 10 ቀን 2007 ፕሮግራም ለክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለጥምቀት በዓል አደረሳችሁ <…ለሶስተኛ ጊዜ ጉባኤ አንጠራም ምርጫ ቦርድ ህገወጥ ተግባር እየፈፀመ ነው መኢአድ ላይ […]

The post Hiber Radio: የአፋር ነፃ አውጭ ግንባር ማስጠንቀቂያ… የኤርትራና የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች በአስመራና በአዲስ አበባ… አንድነትና መኢአድ ምርጫ ቦርድን መክሰሳቸው appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

ሉባልታዊና ሐሜተኛ ማህበረሰብ የጥርጣሬና የሟርት ዘመን ምልኪዎች – ህዝብን ማታለል ክፉ እርግማን ነው፡፡‪  ‬ፍላጐታችንን ያከበሩ በመምሰል ፍላጐታቸውን የሚያሟሉ ሰዎች አደገኞች ናቸው፡፡ ፀሐይ የሚሞቅ ውሻ ሁሉ ሞኝ አይደለም፡፡  

The post ምንሊክ ሳልሳዊ የሳምንቱ መልዕክት appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

በውስጥ መስመር ህወሃቶች የሚያሰሙኝን ድንፋታ ወድጎን ልተወውና ፕሮፈሰር ቆንስጣንጢኖስ በስም ማጥፋት እንደሚከሱኝ ተደጋጋሚ መልእክቶች እየደረሱኝ ነው። ህወሃቶች አለምን በጠባቡ አእምሯቸው እየቃኙ በየሄዱበት ሁሉ የሃሰት ክስ የሚያዳምጥ ፍርድ ቤት ያለ ይመስላቸዋል። ለማንኛውም ከፕሮፌሰሩ ብቻ ሳይሆን እዚህ አሜሪካን አገር ለፕሮፌሰርነት ካበቃቸው የዲግሪ ወፍጮ ቤት የፍርድ ቤት ጥሪ ከደረሰኝ በደስታ እንደ ምቀርብ ላረጋግጥ እወዳለሁ። ለክሱ ተጨማሪ ወረጃ ካስፈለገ […]

The post አበበ ገላው ከፕሮፈሰር ቆንስጣንጢኖስ የሃሰት የዲግሪ ባለቤት ጋር ያደረገው አጠር ያለ ውይይት appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

ከአንድነት ጋር የሚሟገቱትን አካላት ባፈላልግ በድብቅ ከተነሳው ”የቃለ ማህላ” ፎቶግራፋቸው ውጪ ላገኛቸው አልተቻለኝም ነበር። ዛሬ በኢቲቪ መስኮት ግን በአቶ በላይ የሚመራው አንድነት ሀገወጥ ነው ሲሉ አፋቸውን ሞልተው…(አፋቸውን ሞለተው ለማለት እንኳ አያስደፍርም…) ብቻ ግን የሞሉትን ሞልተው ሲናገሩ አይቻቸዋለሁ። እንዲህ ያልኩት ከመሬት ተነስቼ አይደለም፤ ቪዲዮውን ጠቅ አድርጋችሁ ስትመለከቱት አቶ ትግስቱም ሆኑ ጎረምሳው ጸሃፊያቸው የሚናገሩት የራሳቸውን ሳይሆን እነደ […]

The post ፈልጌ አስፈልጌ ያን ሰሞን አጣኋት… አቤ ቶኮቻው appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

(ከኢየሩሳሌም አርአያ) ልኡል ገ/ማርያም የተባለ የሕወሐት አባልና ዳኛ በከፍተኛ ወጪ በመንግስት እየታከመ መሆኑ ታውቋል። በዶ/ር ታዬ ወ/ሰማያት፣ በቅንጅት አመራሮችና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ እድሜ ልክና ሞት የፈረደ ነው። ዙቤር የተባለ ሃብታም የገዛ ጓደኛውን በውሻ እያስነከሰ በጥይት ደብድቦ ከገደለው በኋላ ጉዳዩ የቀረበው ልዑል ዘንድ ነበር። የፈርደበት 6 አመት በማለት ሲሆን ከፍተኛ ገንዘብ ተቀብሎ ይህን ፍርድ ተብዬ እንዳስተላለፈ […]

The post መንግስት የሕወሓት አባሉን ዳኛ ልኡል ገ/ማርያም በከፍተኛ ወጪ እያሳከመ ነው – ከኢየሩሳሌም አርአያ appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ

——

ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ያስተማሩት ትምህርት ዘመናዊነትን ይከለክላል?…. በዘመን አፈራሽ የቴክሎኖጂ ትሩፋቶችና በተቀላጠፉ አሰራሮች መጠቀምን እርም ያደርጋል?… መልሱ “አያደርግም” ነው፡፡ የነቢዩንና የተከታዮቻቸውን የህይወት ታሪክ በወጉ ከፈተሽን ነገሩን በቀላሉ መረዳት እንችላለን፡፡ እስቲ አንዳንድ ምሳሌዎችን እንውሰድ፡፡

·        ነቢዩ በዘመናቸው ለነበሩት ነገሥታት ደብዳቤ መጻፍ አስፈለጋቸው፡፡ አንዱ ባልደረባቸው “ደብዳቤው ከርስዎ የተላከ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማኅተም ያስፈልግዎታል፤ ማኅተም ቢያስቀርጹ መልካም ይመስለኛል” አላቸው፡፡ ነቢዩ የማኅተም አስፈላጊነት ሲነገራቸው እምቢ አላሉም፡፡ ሃሳቡን ወዲያውኑ ተቀብለው አዲስ ማኅተም አስቀረጹ፡፡

·        ከሂጅራ በኋላ በስድስተኛው ዓመት የቁሬይሽ ተዋጊዎች በመዲና ከተማ ላይ ሶስተኛ ዙር ወረራ ሊፈጽሙ ተነሱ፡፡ ከቁሬይሾች ጋር በርካታ ማህበረሰቦች ማበራቸውም ተሰማ፡፡ ይህም ወሬ ለነቢዩ ደረሳቸው፡፡ ነቢዩም በጉዳዩ ላይ ከባልደረቦቻቸው ጋር መወያየት ጀመሩ፡፡ በውይይቱ ላይ ከነበሩት ባልደረቦቻቸው መካከል “ሳልማን አል-ፋርሲ” የሚባለው “በከተማችን ዙሪያ ምሽግ ብንቆፍር ጠላቶታችንን በቀላሉ መመለስ እንችላለን” አላቸው፡፡ ሳልማን የፋርስ (ኢራን) ተወላጅ ነው፡፡ በሀገሩ ሲደረግ ያየውን ነው ለነቢዩ የነገራቸው፡፡ እስከዚያ ጊዜ ድረስ “ምሽግ” በዐረቦች ዘንድ አይታወቅም ነበር፡፡

ነቢዩ ከሳልማን በሰሙት ምሽግ የመቆፈር ብልሃት ተገረሙ፡፡ በተግባር ላይ ሊያውሉትም ተነሱ፡፡ የመዲና ከተማን ከዳር እስከ ዳር በምሽግ ቁፋሮ አጠሯት፡፡ የመካ ቁረይሾች እየፎከሩ ወደ መዲና ሲመጡ ምሽጉ ገደባቸው፡፡ በፈረስና በእግር እየዘለሉ ምሽጉን ለማለፍ ቢሞክሩም ምንም አልተሳካላቸውም፡፡ ይህ ሁኔታ ሌሊቱን ከጣለው ከባድ ዝናብ ጋር ተዳምሮ በጣም አስፈራቸው፡፡ በመሆኑም እቃቸውን እንኳ በወጉ ሳይሰበስቡ ወደመጡበት ፈረጠጡ፡፡ ነቢዩ አንድም ጦር ሳይሰብቁ በእጥፍ የሚበልጣቸውን የጠላት ሃይል ከሳልማን አል-ፋርሲ በሰሙት ዘዴ አባረሩት፡፡

·        በዚያ ዘመን በርካታ መልዕክተኞች ወደ ነቢዩ ዘንድ ይመጡ ነበር፡፡ ታዲያ አንዱ የነቢዩ ባልደረባ “ንጉሦችና የጦር መሪዎች የውጪ መልዕክተኞችን በሚቀበሉበት ጊዜ የአዘቦት ልብሳቸውን አይለብሱም፤ ለየት ያለ ልብስ ለብሰው በርሱ ላይ ካባ ይደርባሉ” አላቸው፡፡ ነቢዩም ምክሩን ተቀብለው በተግባር ላይ አውለውታል፡፡

·        ነቢዩ አይጽፉም፤ አያነቡምም፡፡ ደብዳቤም ሆነ ሌላ ጽሑፍ የሚጽፉላቸው ተከታዮቻቸው ናቸው፡፡ ከጸሐፊዎቻቸው መካከል እጅግ በጣም የተከበረው ዘይድ ኢብን ሣቢት የሚባለው ወጣት ነው፡፡ ነቢዩ የላኳቸው ደብዳቤዎች በአብዛኛው በርሱ እጅ ነበር የተጻፉት፡፡

ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በደብዳቤ የሚገናኟቸው የማህበረሰብ መሪዎችና ነገሥታት በሙሉ ዐረብኛን ማንበብ የሚችሉ አልነበሩም፡፡ ዐረብኛን የሚያነቡት በዐረቢያ ልሳነ-ምድር (Arabian Peninsula) እና በዙሪያው ባሉት መሬት ላይ የነገሡ መሪዎች ብቻ ነበሩ፡፡ በመሆኑም ነቢዩ ከዐረብኛ በተጨማሪ በሌሎች ቋንቋዎችም ደብዳቤዎችን መጻፍ እንዳለባቸው ተገነዘቡ፡፡ ዘይድ ኢብን ሣቢትንም በዘመኑ ሰፊ ተናጋሪ የነበራቸውን የእብራይስጥ (Hebrew) እና የአረማይስጥ (Aramaic/ Syriac) አጻጻፍ እንዲያጠና በመዲና ይኖሩ ከነበሩት አይሁዶችና ክርስቲያኖች ዘንድ ላኩት፡፡ ዘይድም ሁለቱንም አጻጻፎች በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጥናት የጸሐፊነቱን ስራ በሶሥት ቋንቋዎች ቀጥሎበታል፡፡

·        ነቢዩ ለዕውቀት የነበራቸው ከበሬታ ሲወሳ በዓለም ከሚኖሩት ሙስሊሞች ግማሽ ያህሉ የሚያውቁት አንድ ሐዲስ አለ፡፡ ሐዲሱ እንዲህ ይላል፡፡

“ዕውቀትን ቻይና ድረስ እንኳ ቢሆን ሄዳችሁ ፈልጉት”

ከላይ ከተገለጹት ታሪኮች እንደምትረዱት ነቢዩ ጠቃሚ የሆነ ዕውቀትን ያበረታቱ ነበር፡፡ “የተቀላጠፈ አሰራር መጠቀም ሀገርን ያጠፋል” በማለት በተከታዮቻቸው ላይ በሩን አልዘጉም፡፡ የርሳቸው ተከታዮችስ?… ባልደረቦቻቸውም ቢሆኑ በዘመናዊነት ላይ በነበራቸው እይታ የነቢዩን ፈለግ ተከትለዋል፡፡ አንዳንድ ምሳሌዎችን እንጥቀስ፡፡

·        ኸሊፋ ዑመር ቢን ኸጣብ (ረ.ዐ) ከነቢዩ የቅርብ ረዳቶች አንደኛው ነበሩ፡፡ ከነቢዩ ህልፈት በኋላ የሙስሊሙን ኸሊፋዊ መንግሥት ለአስር ዓመታት መርተዋል፡፡ የነቢዩን ሐዲሶችን ጨምሮ በርካታ ታሪኮችን መመዝገብ የተጀመረው በርሳቸው ጊዜ ነው፡፡ ታዲያ ታሪክ ሲመዘገብ የዘመን መቁጠሪያ መጠቀም የግድ ይላል፡፡ ይሁንና በዚያ ዘመን ራሱን የቻለ የቀን መቁጠሪያ በዐረቢያ ምድር አይታወቅም ነበረ፡፡ በመሆኑም ዑመር ነቢዩ ከመካ ወደ መዲና ያደረጉት ስደት (ሂጅራ) እንደ መነሻ ሆኖ እንዲያገለግል ውሳኔ አስተላለፉ፡፡ ይህም ተግባራዊ ሆኖ እስከ አሁኑ ዘመን ድረስ እየተሰራበት ይገኛል፡፡

·        አምስተኛው ኸሊፋ ሙአዊያ ኢብን አቡ-ሱፍያን (ረ.ዐ) ደግሞ በተማከለ አሰራር ደብዳቤዎችን ከግለሰቦች ተቀብሎ የሚያከፋፍል ተቋም በመመስረት በዓለም ታሪክ አዲስ አሰራር አስተዋውቀል፡፡ ዛሬ “ፖስታ ቤት” የሚባለውን ተቋም የፈጠሩት ኸሊፋ ሙአዊያ ናቸው (ባለፈው ነሐሴ ወር ይህንን ጉዳይ በጻፍኩበት ወቅት በርካታ ሰዎች የግኝቱ ባለቤት ሙአዊያ መሆናቸውን እንደማያውቁት ተገንዝቤአለሁ፤ ሆኖም ነገሩ ሐቅ ነው፤ እውነትነቱን ለማረጋገጥ ካሻችሁ በመጽሐፍ፣ በኢንተርኔትም ሆነ በሲዲ የተሰራጨው “ኢንሳይክሎፒዲያ ብሪታኒካ” ስለሙአዊያ የጻፈውን ታሪክ አንብቡት፡፡ በሁሉም ቦታ እንዲህ የሚል ነገር ተጽፎ ታገኛላችሁ፡፡

“Early Arabic sources credit two dīwāns in particular to Muʿāwiyah: the dīwān al-khatam, or chancellery, and the barīd, or postal service, both of which were obviously intended to improve communications within the empire”
የኢንሳክሎፒዲያ ብሪታኒካን ጽሑፍ በኢንተርኔት ለማንበብ ካሻችሁ ይህንን ሊንክ ተጠቀሙ፡፡

·        በአሁኑ ወቅት የዓለም ህዝብ በሙሉ የሚጠቀምበት “የሂንዱ-ዐረብ” የቁጥር ዘዴ የመጨረሻ ቅርጹን ያገኘው በሙስሊሞች አማካኝነት ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር ለሂሳብ አቆጣጠር የሚያመቸው “የዜሮ ጽንሰ ሃሳብ” የተፈለሰፈው በ8ኛው ክፍለ ዘመን በባግዳድ ከተማ ነው፡፡

·        የሳይንስና የምርምር ዘርፍ ከፍተኛ እመርታ እንዲሳይ ያደረጉትን አል-ጀብራ እና አልጎሪዝም የተሰኙ የሂሳብ ስልቶችን የፈጠረው ሙሐመድ ኢብን ሙሳ አል-ኸዋሪዝሚ የተባለ ሙስሊም ሳይንቲስት ነው (ዜሮንም የፈጠረው አል-ኸዋሪዝሚ ነው)፡፡

·        ሌላም ብዙ ብዙ መዘርዘር ይቻላል፡፡

ከነዚህ ምሳሌዎች ለመረዳት እንደሚቻለው የጥንቱ ሙስሊሞች በአዳዲስ ፈጠራዎች ከመጠቀም አልፈው ለራሳቸውም ልዩ ልዩ ፈጠራዎችን አስተዋውቀዋል፡፡ በአዳዲስ ፈጠራዎች መጠቀም “ውግዝ” ቢሆን ኖሮ ነቢዩና ባልደረቦቻቸው “እርም፤ ነው አትጠጉት” በማለት ክልከላ ያስቀምጡበት ነበር፡፡ ስለዚህ ዘመን ባስገኘልን ትሩፋት ከመጠቀም ወደኋላ ማለት የለብንም፡፡

ይሁንና ይህ በፈጠራዎች የመጠቀም ጉዳይ ሲነሳ አንድ ነገር መታወቅ አለበት፡፡ ይኸውም በጥቅም ላይ የሚውለው አዲስ ፈጠራና አሰራር የሰዎችን ኑሮ በማቃለል ረገድ አስፈላጊነቱ የሁሉም ተጠቃሚዎች ምስክርነት ሊኖረው የተገባ መሆኑ ነው፡፡ እስልምና ከጉዳት በስተቀር አንዳች ጥቅም የሌለውን ፈጠራ ይከለክላል፡፡

 በሌላ በኩል ደግሞ በፈጠራና በዘመናዊነት ስም አላህ እርም ያደረጋቸውን ድርጊቶች መፍቀድ አይቻልም፡፡ ለምሳሌ ማንኛውም የእስልምና ሙፍቲ “አስካሪ መጠጥ ለጤና ይጠቅማችኋል፣ ድንበር ሳታልፉ ጠጡ” በማለት ውሳኔ መስጠት አይችልም፡፡ ቁማርን ህጋዊ ማድረግም በፍጹም አይቻልም፡፡ በሰብዓዊ መብት ስም ግብረ-ሰዶምን ህጋዊ ማድረግም ተቀባይነት የለውም፡፡ እነዚህ ድርጊቶች የሰዎችን ኑሮ ከማቃወስ በስተቀር አንዳች ጠቀሜታ የላቸውም፡፡

ነቢዩ በዘመናዊ እውቀት መጠቀምን ከልክለዋል የሚል የተቀዣበረ ወሬ የሚነዙት ነቢዩን የማያውቁት ጠላቶቻቸው ብቻ አይደሉም፡፡ “የነቢዩን ትክክለኛ ትምህርት የምንከተለው እኛ ብቻ ነን” ማለት የሚቃጣቸውና ሰዎችን “አዛ” ማድረግ ልማዳቸው የሆነ ከሙስሊሙ ዓለም የበቀሉ አንዳንድ ጽንፈኛ አንጃዎችም ጭምር ናቸው፡፡ ለምሳሌ የ“ጣሊባን” አንጃ አፍጋኒስታንን በሚያስተዳድርበት ጊዜ “በእስልምና የተከለከሉ ናቸው” በሚል በርካታ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን እርም አድርጎ ነበር፡፡ ይሁንና ነቢዩ እንዲህ ዓይነት ጽንፈኝነትን አላስተማሩም፡፡ አላህ ነቢዩን የላከለው ለራሕመት (እዝነት) ነው እንጂ ጽንፍ በወጣ አስተምህሮ ሰዎችን እግር ተወርች ቀፍድደው ለሰቀቀን ኑሮ እንዲዳርጓቸው በሚል አይደለም፡፡ ነቢዩም ተከታዮቻቸውን ሲያስተምሩ “አግራሩ፤ አታክርሩ” (“የሲሩ፤ ወላ ቱዐሲሩ”) ነበር ያሉት፡፡ በመሆኑም የነዚህን ጽንፈኞች አድራጎት በማየት የነቢዩን አስተምህሮ በተዛነፈ ሁኔታ መረዳት ተገቢ አይደለም፡፡

የአላህ ሶላትና ሰላም በነቢዩ ላይ ይስፈን (ሰልላሁ ዐለይሂ ወሰለም)

——

አፈንዲ ሙተቂ

ጥር 9/2015

—–

በእኔ እምነት ምርጫ ቦርድ ልጓሙን በጥሶ መፈርጠጥ ጀምሯል፡፡ አዎ ምርጫ ቦርድም ሆነ ኢህአዲግ በህግ የበላይነት ሊያምኑና ህግን ሊያከብሩ ብሎም በተሰጣቸው ገደብ መሰረት ሊንቀሳቀሱ ይገባል፡፡ ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ዴሞክራሲ፣የህግ የበላይነት ….ወዘተ እያሉ መደስኮሩ ጉንጭ ከማልፋት በተዘለለ ለዜጎች ጠብ የሚልላቸው ነገር አይኖርም፡፡ መንግስታት አንባገነን በሆኑበት አግባብ ገለልተኛ ተቋማትን መገንባት አስቸጋሪ ነው፡፡ ….በሀገራችንም እየሆነ ያለው ይህ ሀቅ ነው፡፡ […]

ይህ የተገፋ ህዝብ እንዳጎነበሰ አይኖርም ቀና ያለ እለት …!!! ወህኒ የጀግና እንጂ የወያኔ እብሪተኞች ቤት አይደለም!! ባለስልጣናት የጸረ አሸባሪነት ህግን ለማስፈጸምም ይሁን ለመተግበር ሞራላቸው ምን ድረስ እንደሆነ ሊመልሱልን ይገባል:: ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያልተመዘገቡ ሀገወጥ እና አሸባሪ ከሆኑ የተወነጀሉበት ተቀባይነት ያለው ክራይቴሪያ ይነገረን እና እናውግዘው:: አጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝቦች ጥያቄያቸው ግልጽ እና ግልጽ ነው ካልሆነ የሚዋከቡበት ምክንያት የለም […]

ተቃዋሚዎች ሆይ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የሚባለውን የወያኔ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በወያኔ መንግስት የተሾመ ለወያኔ ማፊያ ቡደን የሚያገለግል እንደሆነ በረጅም አመት የማጭበርበር የስራ ልምዱ አስመስክሯል ። ይህ ድርጅት ገለልተኛ እንዳልሆነ እየታወቀ በኢትዮጵያ የሚገኙ ከ 34 በላይ የሚሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወያኔን በማይገባው ቛንቛ በሰላማዊ ትግል ታግሎ ወያኔን ለማስወገድ ውጤታማ ያልሆነ ልፋት እየለፉ ይገኛሉ […]

የአንድነት ፓርቲ አባል የሆነው ወጣት እስማኤል ዳውድ ዛሬ ከጠዋቱ በ12፡30 ገደማ ሁለት ታጣቂ ፖሊሶች እና ሁለት የደህንነት ሰዎች መኖሪያ ቤቱ መጥተው ጃንሜዳ ፊት ለፊት በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ መታሰሩ ተገለጸ፡፡ እስማኤል ዳውድ በአንድነት ፓርቲ በኩል በምትታተመው የሚሊዮኖች ድምፅ ጋዜጣ በ …

የአንድነት ፓርቲ አባሎች ጃንሜዳ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ታሰሩ Read more »

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ከጀርመን ከተሞች፤ እንደ ድሬስድን እስልምና እንዳይስፋፋ የሚታገል ከተማ የለም። ባለፉት የሰኞ ሳምንታት ድሬስድን ውስጥ እስልምና እንዳይስፋፋ የሚታገሉ የፔጊዳ ደጋፊዎች ድሬስድን ከተማ ሰልፍ ሲወጡ ሰንብተዋል። የነገው ሰልፍ ግን የሽብር ጥቃት ሊሰነዘር ይችላል በሚል ፍራቻ ፖሊስ በከተማዋ ማንኛውም አይነት የአደባባይ ሠልፍ እንዳይደረግ አገደ።

ጋዜጠኛ ዮሐንስ ደሳለኝ – (ጀርመን)

Ethiopia Zare ቅዳሜ ጥር 10 ቀን 2007 ዓም January 17, 2015:- ባሳለፍንው ሰኞ በፍራንክፈርት የሚገኙ ኢትዩጽያዊያን በአሁኑ ሰዓት በአገራቸው የሚደረገውን የመብት ጥሰት ለተለያዬ ተቁማት ለማሳወቅ ሁለት ሰዓት የፈጀ ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ። መነሻውን ከዋናው የባቡር ጣቢያ አንድ ጣቢያ (station)አልፉ በሚገኘው ታውንስላገን አካባቢ ከዋናው ደች ባንክ አጠገብ ያደረገው ሰልፍ፣ ረፈዱ 11፡00am ላይ ተጀምሮ የእንግሊዝ ኤምባሲን አካሎ ምሳ ሰዓት ላይ (1፡00pm) ፍራንክፈርት የሚገኘው ኢትዬጽያ ቆንጽላ ጽ|ቤት በመገኘት በተለመደው ኢትዬጵያዊ ጨዋነት ተጠናቁል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጋዜጠኛ ዮሐንስ ደሳለኝ – (ጀርመ)

Ethiopia Zare ቅዳሜ ጥር 10 ቀን 2007 ዓም January 17,2015:–  ባሳለፍንው ሰኞ በፍራንክፈርት የሚገኙ ኢትዩጽያዊያን በአሁኑ ሰዓት በአገራቸው የሚደረገውን የመብት ጥሰት ለተለያዬ ተቁማት ለማሳወቅ ሁለት ሰዓት የፈጀ ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ። መነሻውን ከዋናው የባቡር ጣቢያ አንድ ጣቢያ (station)አልፉ በሚገኘው ታውንስላገን አካባቢ ከዋናው ደች ባንክ አጠገብ ያደረገው ሰልፍ፣ ረፈዱ 11፡00am ላይ ተጀምሮ የእንግሊዝ ኤምባሲን አካሎ ምሳ ሰዓት ላይ (1፡00pm) ፍራንክፈርት የሚገኘው ኢትዬጽያ ቆንጽላ ጽ|ቤት በመገኘት በተለመደው ኢትዬጵያዊ ጨዋነት ተጠናቁል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በአሁኑ ጊዜ የኖርዌይ ዜግነት ያላቸው ቀድሞ የጋምቤላ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ኦኮሎ አኳይ ላይ ተሰምተው የነበሩ የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች ቃል ሳይቀረፅ በመቅረቱ፣ ከሳሽ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በድጋሚ እንዲያሰማ ታዘዘ፡፡ ጉዳዩን እየመረመረው የሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የክስ መዝገቡን ለጥር 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጥሮ የነበረው፣ ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ በአቶ ኦኬሎ፣ የደቡብ ሱዳን ዜግነት […]

The post ዓቃቤ ሕግ በቀድሞ የጋምቤላ ፕሬዚዳንት ላይ በድጋሚ ምስክሮቹን ሊያሰማ ነው appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

ስሜነህ ታዘበው/ ከአዲስ አበባ የ2007 ምርጫ ሊደረግ የቀረው ሶስት ወራት አካባቢ ብቻ ነው። ምርጫ ቦርድ ባወጣው ሰለዴ መሰረት የታዛቢ ምርጫዎችን ያደረግ ሲሆን፣ ለተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችም የምርጫ ምልክታቸውን ሰጥቷል። የዲሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ ባልሆኑበት ሁኔታ ምርጫዉን መሳተፍ የማይታሰብ ነው የሚል አቋም በሊቀመንበሩ ኢንጂነር ይልቃል ጌትነትና ሌሎች የአመራር አባላት ሲያንጸባርቅ የነበረው የሰማያዊ ፓርቲ፣ የዣንጥላ ምልክት የተሰጠው ሲሆን፣ በተለያዩ ወረዳዎችም […]

The post የሰማያዊ ፓርቲ ለ2007 ምርጫ ተወዳዳሪዎች እያስመዘገብ ነው ! – ስሜነህ ታዘበው appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.

የአንድነት ለዴሞክራሲ እና  ለፍትህ ፓርቲ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኢንጅነር ግዛቸው ሽፍራው የአንድነት አባለት ለፓርቲው ህልውና ሲሉ የተፈጠረውን ችግር በሰከነ መንፈስ እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ:: የፓርቲው የቀድሞ ፕሬዝዳንት በእነ አቶ በላይ ፈቃዱ በሚመራው ቡድን ምክትል ፕሬዝዳንት ግርማ ሰይፉ በኩል ከፓርቲው  መሪነት የተነሱት ፓርቲውን የመምራት እና ጫናን የመቋቋም አቅም ስላልቻሉ ነው መባላቸውን በታህሳሱ ምርጫ ፕሬዝዳንታዊ ውድድር አቶ ግርማን  በከፍተኛ የድምፅ ልዩነት ማሸናፋቸውን በማንሳት ኃሳቡን አጣጥለውታል። በፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ቀን ተሸናፊው አቶ ግርማ ራሴን ያየሁበት ውድድር ነው። ውጤቱም እንኳንስ ፓርቲ ወረዳ  መምራት የማልችል መሆኔን የሚያሳይ ነው ማለታቸውን ያስታወሱት ኢንጅነር ግዛቸው ስልጣኔን ያስረከብኩት ፓርቲው በቡድን ፓለቲካ እንዳይፈርስ ለህልውናው በማሰብ ነው ብለዋል። አሁን ፓርቲውን እያመሰው ያለው የቡድን እና ዝምድና ፓለቲካ ነው የሚል አስተያየት የሰነዘሩት ኢንጅነር ግዛቸው የፓርቲው አባላትም የአንድነትን የቀደመውን ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመፍታት ስልት ተጠቅመው በሰከነ መንፈስ ችግራቸውን መፍታት የፓርቲውን ህልውና እንዲታደጉት ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁለት የከፈሉት አመራሮች ችግራቸውን በጋራ በውይይት እንዲፈቱ የሁለት ሳምንት ግዜ መስጠቱ ይታወሳል። ********* ምንጭ፡- ፋና፣ ጥር 09-2007 More from Horn Affairs Amharic‘የእነበላይ ፍቃዱ አንድነት’ መግለጫ:- ‹‹የምርጫ ቦርድ ታሪካዊ ወንጀል እየፈፀመ ነው››ሰንደቅ ጋዜጣ:- ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ በሠነዘሩት አሉባልታ ሊከሰሱ ነውAudio| የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ አመራር በአዲሱ ማስተር ፕላን ላይ የሰጡት መግለጫበኦሮሚያ ክልል በዩንቨርስቲዎች ስለተከሰቱት ግጭቶች ከመንግስት የተሰጠ መግለጫየመኢአድ ውዝግብ በድጋሚ አገረሸበመጪው ምርጫ ከፖለቲከኞቻችን፣ ከፖለቲካቸው እና ከህዝቡ ምን ይጠበቃል?

የመድብለ ፓርቲ ስርዓት እንዳይፈጠር የምርጫ ቦርድ ታሪካዊ ወንጀል እየፈፀመ ነው፡፡ ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ/አንድነት/ የተሰጠ መግለጫ የአንድንታ ፓርቲ በኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲፈጠር በምንም መለኪያ በገለልተኝነት የማንጠብቃቸውን የዲሞክራሲ ተቋማት በተግባር ለመፈተን እንዲቻል የሁለት ሺ ሰባት ምርጫን በሁሉም ሂደቶች ህዝቡን በማሳተፍ እንደሚወዳደር እና ህዝብን የስልጣን ባለቤት ለማድረግ እና የኢህአዴግ አገዛዝ የመጨረሻ እንዲሆን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ይህን ስንወስን እነዚህ ተቋማት ገለልተኝነታቸውን አረጋግጠው ታሪክ የሚሰሩበት እድልም ያገኛሉ የሚል ተሰፋ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ምርጫ ቦርድ ይህን እድል ከመጠቀም እና በህግ የተሰጠውን ኃላፊነት በብቃት ከመወጣት ይልቅ ለገዢው ፓርቲ ያለውን ወገንተኝነት በምርጫው ሂደት ዋዜማ በይፋ እያረጋገጠ ይገኛል፡፡ አሁንም ቦርዱ ወሰነ ተብሎ በሚዲያ የተገለፀው እንዲሁም ለፓርቲያችን በፅሁፍ የተሰጠው “በአስራ አምስት ቀን ውስጥ በጋራ ጉባዔ አድርጉ” የሚል ትዕዛዝ፤ ቦርዱ በተደጋጋሚ ፓርቲያችንን ደንብ እንዲያከብር እየጠየኩ ነው በማለት ከደንብ ውጭ እንድንሰራ የአዛኝ ቂብ አንጓች ሆኖዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔ የመጥራት ኃላፊትን ያለበት የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት ወይም ደግሞ በአባላት ጥያቄ የጠቀላላ ጉባዔ አባላትን አንድ ሶስተኛ ፊርማ አስባስበው በኦዲትና ኢንስፔክሽን ትዕዛዝ መሆኑ በግልፅ እየታወቀ ከፓርቲያችን መተዳደሪያ ደንብ ውጭ በ15 ቀን ውስጥ ጉባዔ ጥሩ የሚል ትዕዛዝ፤ ቦርዱ ከገዢው ፓርቲ ጎን ተሰልፉ እየተጫወተ አንድነትን ከጫወታ ለማስወጣት ካለሆነ ሌላ ምንም ትርጉም ልንሰጠው አንችልም፡፡ ይህ ደግሞ ቦርዱ እየሰራ ያለውን ታሪካዊ ወንጀል ይፋ የሚያደርግ ነው፡፡ ይህ በማን አለብኝ ሰሜት የተሰጠ ውሳኔ ሳይታረም ቢቀርና ገዢው ፓርቲ […]

(ፋኑኤል ክንፉ) ታህሳስ 28 ቀን 2007 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሳባ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፈጸማቸውን የሕግ ጥሰቶች በመመርመር እስከ ጥር 4 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ በሕጉና እና በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት አሟልቶ እንዲያቀርብ በደብዳቤ ማሳወቁ ይታወቃል። ይህን የቦርዱ ጥያቄ ባይሟላ ቦርዱ የመጨረሻ ሕጋዊ እርምጃ በፓርቲው ላይ እንደሚወስድ በደብዳቤ ቁጥር አ/573/ፓ4/ጠ405 በተፃፈ ደብዳቤ መግለጽን ለማወቅ ተችሏል። የቦርዱን ማሳሰቢያ ከግምት በመውሰድ አንድነት ፓርቲ ጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ የሕግ እና የውስጥ ደንብ ሁኔታዎችን የመመርመር ሥልጣን ያለው ጠቅላላ ጉባኤ መሆኑን ጠቅሶ፣ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን ጥር 3 ቀን 2007 ዓ.ም ቀበና መድሐኒዓለም አጠገብ በሚገኘው ጽ/ቤት ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ለማድረግ መወሰኑን ለምርጫ ቦርድ በደብዳቤ አስታውቋል። በሌላ መልኩ ምርጫ ቦርድ ግልባጭ እያለ ለሚያሳውቃቸው “የእነአቶ አየለ ስሜነህ” የአመራር ቡድን በበኩላቸው፣ ታህሳስ 30 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ጥር 3 ቀን 2007 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በሳሬም ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንደሚያደርጉ በደብዳቤ ለቦርዱ አስታውቀዋል። ከላይ የሰፈሩት ሁለቱ አካሎች በተለያየ ቦታዎች ጉባኤ እንደሚያካሂዱ ማሳወቃቸውን አግባብነት የሌለው መሆኑን ገልፃ፣ ምርጫ ቦርድ በሁለቱም ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ታዛቢ ሳይልክ ቀርቷል። ዝግጅት ክፍላችን ከላይ የሰፈረው ውዝግብ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በመገኘት ያጠናከረውን ዘገባ እና በእነአየለ ስሜ ጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡትን ፕሬዝደነት ቃለ ምልልስ ይዞ ቀርቧል። ዘገባው […]

ኣቶ ገብሩ ኣስራት ´ሉዓላዊነትና ዲሞክራሲ በኢትዮጵያ´ በሚል ርእስ ትልቅ መፅሓፍ ፅፈዋል፤ ትልቅነቱ ሃገርን ያክል ዓብይ ስብስብ የሚንዱ ወይም የሚገነቡ ርእሰ ጉዳዮች – ማለት ሉዓላዊነትና ዲሞክራሲ- በኢትዮጵያችን የደረሱበትን ኣሳሳቢ ደረጃ ኣስመልክቶ እንድንመክርበት በጥልቀት መርምሮ ስላስቀመጠልን ነው። ከዚህም ኣልፎ ላሳሳቢው ችግር መፍትሄ ይሆናሉ ያላቸውን ኣንኳር ፍሬነገሮች ግልፅ ኣድርገዋል። ከዚህ በመነሳት ይህ ትላልቅ ርእሶችን ያነገበ መፅሓፍ እንዴት መታየት […]