የጥምቀት በዓል አከባበር በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ በክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች ዘንድ ዛሬ የጥምቀት በዓል በደማቅ ተከብሮአል። የጥምቀት በዓል ከጊዜ ወደ ጊዜ የዓለም አቀፉን ሕብረተሰብ ቀልብ እየሳበ በመምጣቱ የአከባበር ሥነ-ስርዓቱን በተመ የትምሕርት፤የሳይንስና የባሕል ድርጅት «UNESCO» ጥበቃ ስር በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተመልክቶአል።