ሶሪያ የኬሚካል የጦር መሳሪያዎቿን ለማስፈተሽ መስማማቱዋን ፕሬዚዳንት አሳድ አስታወቁ
መስከረም ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከምእራባዊያን አገራት በተለይም ከአሜሪካ ድብደባ ለጊዜውም ቢሆን የተረፈችው ሶሪያ በአገሯ ያሉ የኬሚካል የጦር መሳሪያዎችን በሙሉ ለማውደም ፈቃደኛ መሆኑዋን ፕሬዚዳንት በሽር አላሳድ ተናግረዋል። ከሩሲያ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት አላሳድ፣ አገራቸው ስምምነቱን የምትፈርመው ሩሲያ ስላግባባቻች እንጅ የአሜሪካን ጥቃት ፈርታ አይደለም። የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን በኒውዮርክ ታይምስ ላይ ለአሜሪካ ህዝብ …
