በዩጋንዳ ለምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ!!!
በሳውዲ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍና ሰቆቃ በማውገዝ የሳውዲ መንግስት ለዓለም አቀፉ የሠብዓዊ መብቶች መከበር የፈረመውን ስምምነት እንዲያከብርና ዜጎቻችን ላይ እያደረሠ ያለውን ኢሞራላዊ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲያቆምና ለሠው ልጆች ሰብዓዊነት እንዲያሳይ ለመጠየቅና በቀጣይ በምስራቅ አፍሪካ ያለውን የስደተኞች ሁኔታ ለመምከር የወገኖቻችን መከራና ስቃይ ነግ በኔ ሊሆን ይችላል ብሎ በማሠብ በአንድነት ሆነን ለመምከር አንዳንድ ቅድመ ዝግጅቶች ለማድረግ ከጎናችን እንዲቆሙ እንጠይቃለን።
ቀጣይ እንቅስቃሴያችንን በ<efjaehrco>ፌስ ቡክ ላይ ማስታወቅያችንን ይከታተሉ።
በህዝባዊ ተቃውሞ ለመሣተፍ በ<[email protected]>ይመዝገቡ።
በዩጋንዳ ነግ በኔ የወገን ለወገን ደራሽ የጋራ ድምፅ አስተባባሪ ኮሚቴ
[email protected]>

አንዳንዶች በድሎትና በምቾት ላይ ያገኙትን የሰላም ዘመን ምንም ሳይጠቀሙበት ‹ተወለዱ- ሞቱ› ተብለው ያልፋሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ስደታቸውን፣ እሥራቸውንና ግዞታቸውን፣ መከራቸውንና ሕመማቸውን የሀገርንና የወገንን ታሪክ ለመለወጥ፣ በሰው ልጅ ታሪክም ውስጥ ጉልሕ ቦታ ለመያዝ ሲጠቀሙበት ይታያሉ፡፡ እኛ ‹የመከራ በረከት› ፈረንጆች ‹blessing in disguise› የሚሉት ማለት ነው፡፡ ሰውን የሚጎዳው የደረሰበት ችግርና መከራ አይደለም፡፡ በዚያ ችግና መከራ ውስጥ ሆኖ የሚያየው ነገር ነው፡፡ ገነት ውስጥ ሆነው ሲዖልን ከሚያዩ ሰዎች ይልቅ ሲዖል ውስጥ ሆነው ገነትን የሚያዩ ሰዎች ይበልጣሉ፡፡ አንዳንዶች በመታመማቸው ምክንያት ታሪክ ሠርተዋል፡፡ አንዳንዶች በመታሠራቸው ምክንያት ታሪክ ሠርተዋል፤ አንዳንዶች በመሰደዳቸው ምክንያት ታሪክ ሠርተዋል፤ አንዳንዶችም በመቸገራቸው ምክንያት ታሪክ ሠርተዋል፡፡
ችግር ሁለት ነገሮችን ትወልዳለች፡፡ ጠቢባን ሲያዋልዷት ብልሃትን፣ ሞኞች ሲያዋልዷት ድህነትን፡፡

ችግርን ቀምሰዋት፣ በጥበብም አዋልደዋት ብልሃትን እንድትወልድ ካደረጓት የሀገራችን ሰዎች አንዱ ደጃዝማች ኃይሉ እሸቴ ናቸው፡፡ ዘመነ መሳፍንት ተብሎ በሚጠራው የሀገራችን ዘመን አብዛኛውን ዘመናቸውን ያሳለፉት የአስተዳደር፣ የጦርና የቀለም ሰው ደጃዝማች ኃይሉ እሸቴ የተወለዱት በ1746 ዓም አካባቢ ጥር 12 ቀን ነው፡፡ አባታቸው ደጃዝማች እሸቴ እናታቸውም ወ/ሮ ወለተ ራጉኤል ይባላሉ፡፡

ደጃዝማች ኃይሉ በዘመኑ እንደነበሩት የኢትዮጵያ የመኳንንት ልጆች ፈረስ ግልቢያውንና አደኑን እየተማሩ፣ የቀለም ትምህርቱንም ጎን ለጎን እያስኬዱ አደጉ፡፡ በዚህ መካከል ግን መጋቢት 11 ቀን 1760 ዓም አባታቸው ደጃዝማች እሸቴ በጦርነት ላይ ሞቱባቸው፡፡ ያኔም እድሜያቸው ወደ አሥራ አራት ዓመት ያህል ሆኗቸው ነበር፡፡ ወላጅ እናታቸው በ1755 ዓም የሞቱባቸው ኃይሉ እንደገና የአባታቸው በልጅነታቸው መሞት ኀዘኑን አጸናባቸው፡፡

ዘመነ መሳፍንት ግም ግም ሲልና ከትግራይ የመጡት ራስ ሚካኤል ስሑል መንግሥቱን እየጠቀለሉት ሲመጡ፤ በጎንደር ከተማም በቋረኞቹና በኦሮሞዎቹ መካከል ንጉሡን ኢዮአስን ይዘው መንግሥቱን ለመቆናጠጥ የፖለቲካው ትግል ሲያይል፣ ኃይሉ እሸቴ የራስ ሚካኤል ስሑልን ልጅ ወለተ ተክለ ሃይማኖትን አግብተው የራስ ሚካኤልና የቋረኞቹ ደጋፊ መሆናቸውን አሳዩ፡፡ ራስ ሚካኤል ስሑል በጎንደር ቋረኞችን ይዘው ሥልጣን ሲያደላድሉ፣ ደጃች ልቦ እና ደጃች ፋሲል ከተባበሯቸው ከይልማና ዴንሳ፣ ከሜጫ፣ ከዳሞትና ከወሎ ተወላጆች ጋር ሆነው ሸፈቱ፡፡ የተወሰኑት ቋረኞችም ተከተሏቸው፡፡ ራስ ሚካኤልም አስገብራለሁ ብለው፣ ደጃዝማች ኃይሉም የአባታቸውን ሞት ለመበቀል አብረዋቸው ዘመቱ፡፡ የመጀመሪያውን የታወቀ ጀብዷቸውንም በዚህ ጦርነት ላይ አሳዩ፡፡ የዘመኑ ገጣሚም

ጎራዴማ ወትሮ እንዲመታ ዐውቃለሁ፣

እኔ ኃይሉን እንጂ አመሰግናለሁ፤

ብሎ ገጠመላቸው፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ደጃዝማች ኃይሉ ተፈሪነታቸውና ተሰሚነታቸው እየጨመረ፤ በግዛትም ላይ ግዛት እየተሾሙ ኖሩ፡፡ በተደጋጋሚ በየጦርነቱ ባሳዩት ጀብዱ እየተገጠመላቸው፣ ግዛትም እየተጨመረላቸው፤ የራስ ሚካኤል ስሑል ዘመን ሲያልፍም ከመጭዎቹ ኃያላን ጋር እየተስማሙ እስከ ዐፄ ተክለ ጊዮርጊስ ዘመን እየተወደዱና እየተሞገሱ ቀጥለው ነበር – ደጃዝማች ኃይሉ፡፡

በአንድ በኩል የዐፄ ተክለ ጊዮርጊስ ዘመን በ1771 ዓም ሲጀምር የደጃዝማች ኃይሉ የተወዳጅነትና የተከባሪነት ዘመን በሌላ በኩል ማዘቅዘቅ ጀመረ፡፡ በተክለ ጊዮርጊስና በሰሎሞን መካከል በቤተ መንግሥት የሥልጣን ሽኩቻ ተፈጠረ፡፡ በመጨረሻም ደጃች ክንፉ የሰሎሞንን ዋና ደጋፊ ራስ ኃይሉን ወግተው ንጉሥ ተክለ ጊዮርጊስን አነገሡ፡፡ በዚህ ጊዜ ደጃዝማች ኃይሉ የዘመነ መሳፍንት ሁከትና ውጊያ ሲሰለቻቸው ካልመጡብኝ አልሄድም ብለው ዐርፈው ተቀምጠው ነበር፡፡ ደጃች ክንፉ ራስ ኃይሉን ለመውጋት ሲዘምቱ ደጃዝማች ኃይሉ አብረዋቸው እንዲዘምቱ ልከውባቸው ነበር፡፡ ደጃዝማች ኃይሉ ግን ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ ይህም በአሸናፊዎቹ በእነ ደጃች ክንፉ ዘንድ ጥርስ አስነከሰባቸው፡፡

ከጦርነቱ በኋላ በንጉሥ ተክለ ጊዮርጊስና በደጃች ክንፉ ታዝዘው ደጃዝማች ኃይሉ ወደ ጎንደር መጡ፡፡ የጠበቃቸው ግን ጎጃም ቡሬ ላይ በቁም እሥር መቀመጥ ሆነ፡፡ እርሳቸውም ቡሬ ላይ ጥቂት ከቆዩ በኋላ ጠፍተው ሲሄዱ ደጃች ክንፉ ፈረሰኛ ልከው አቸፈር ላይ አስያዟቸውና በሠንሠለት ታሥረው ጎንደር ገቡ፡፡ እርሳቸው ታሥረው ጎንደር ሲገቡ የጎንደር ሕዝብ በእጅጉ ማዘኑን ታሪከ ነገሥቱ ይነግረናል፡፡ የዋልድባ መነኮሳትም ኃይሉን ለማስፈታት ምልጃ ገብተው ነበር፡፡ ንጉሡም ከዛሬ ነገ እፈታለሁ እያሉ ዝም ብለው አስቀመጧቸው፡፡

የጎንደሩ የቁም እሥር ያልተመቻቸው ደጃዝማች ኃይሉ በሌሊት ጠፍተው ማኅደረ ማርያም ገቡና የተማጽኖ ደወል መቱ፡፡ ኃይሉ በደኅናው ዘመን ከታላላቅ ገዳማትና አድባራት አባቶች ጋር በጎ ግንኙነት ነበራቸው፡፡ እርሳቸውም የዘመኑን ትምህርት የተማሩ ነበሩና በእነዚህ ታላላቅ አባቶች ዘንድ ተሰሚነት ነበራቸው፡፡ ደጃዝማች ኃይሉ በእቴጌ ማርያም ሥና በተደበረችው ማኅደረ ማርያም ለአራት ዓመት ከሦስት ወር ነበር በግዞት የተቀመጡት፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ በሰላሙ ዘመናቸው በጦርነትና በአስተዳደር ካበረከቱት አስተዋጽዖ ይልቅ ኃይሉን ሲያስጠራቸው የሚኖረው በዚህ በግዞትና በመከራ ዘመናቸው ለሀገራቸው የሠሩት ተመን የማይገኝለት ሥራቸው ነበር፡፡

ራስ ኃይሉ በማኅደረ ማርያም ሲቀመጡ ከሁካታውም ከጦርነቱም ጋብ አሉ፡፡ ሀገር ለሀገር ከመዞር ዐርፈው ወደ ልባቸው ተመለሱ፡፡ በደብሩ የሚከናወነው ጸሎትና ትምህርትም ጽሞናን ሰጣቸው፡፡ በዚያ ዘመን ማንም ሊታየው ያልቻለውን ዘመን ተሻጋሪ ራእይም አዩ፡፡ ሀገሪቱ በግራኝ አሕመድ ጊዜ ከገጠማት የርስ በርስ ጦርነት ወጥታ ወደ ሌላ የርስ በርስ ጦርነት ገብታለች፡፡ በጎንደር ከተማ የሚደረገው የሥልጣን ትግል ከምንም በላይ የጎዳው ሕዝቡንና የሕዝቡን ታሪክ ነው፡፡ በተለይም ደግሞ ለብዙ ዘመናት በየቤተ መንግሥቱ፣ በየገዳማቱና አድባራቱ የተከማቹ መዛግብት በጦርነቱ ምክንያት ይቃጠላሉ፤ ይቆነጻጸላሉ፡፡ ኃይሉ በንሥር ዓይናቸው ይህንን ነበር ያዩት፡፡

‹በሰንበት ላይ ደብረ ዘይት፣ በእራት ላይ ዳረጎት› እንዲሉ ኃይሉ ይህንን ሲያስቡ የሸዋው ተወላጅ ጽሕፈት ዐዋቂው አቤቶ አበጋዝ ወደ ማኅደረ ማርያም መጣ፡፡ ደጃዝማች ኃይሉ እሥርና ግዞቱን ወደ ታላቅ የጥናትና ምርምር ተቋምነት ቀየሩት፡፡ ከየገዳማቱና ከየሊቃውንቱ እየተላላኩ የታሪክ መዛግብትን እያስመጡ፣ እያመሳከሩና እየጠየቁ ስማቸውን እስከ ዓለም ፍጻሜ የሚያስጠራውን፣ ዛሬ በፓሪስ ቤተ መጻሕፍት በቁጥር 143 ተመዝግቦ የሚገኘውን፣ በአራት አዕማድ ተጽፎ፣ በ370 ገጽ በብራና የተዘጋጀውን ‹ታሪከ ነገሥት ዘደጃዝማች ኃይሉ እሸቴ› የተባለውን የኢትዮጵያ የታሪክ መጽሐፍ አዘጋጁ፡፡ ለሦስት ዓመታት ያህል መረጃዎችን ሲያሰባስቡ፣ መጻሕፍቱን ሲያመሳክሩ ቆይተው፣ ለአንድ ዓመት ያህል ተጽፎ በ1778 ዓም መስከረም ሰባት ቀን ተጠናቀቀ፡፡

ደጃዝማች ኃይሉ ከማኅደረ ማርያም ግዞት በኋላ እንደ ጥንቱ ባይሆንም እየተሾሙ ለጥቂት ጊዜ ቆይተዋል፡፡ በተለይ በራስ ዓሊ ጊዜ  ስሜንንና በጌምድን እየተሾሙ በደስታ ኖረዋል፡፡ ራስ ዓሊ ሲሞቱ ግን ከቀጣዩ ባለ ሥልጣን ከራስ ወልደ ገብርኤል ጋር መስማማት ባለመቻላቸው በስደት ወደ ጎጃም ወደ ራስ መርእድ ዘንድ ሄዱ፡፡ በዚያ ሆነው ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበትን ዘመን ሲናፍቁ መርዕድና ወልደ ገብርኤል ሐምሌ 15 ቀን 1791 ዓም ባደረጉት ውጊያ ሁለቱም ራሶች ሲወድቁ የድሉ ሚዛን ወደ ራስ ወልደ ገብርኤል ሰዎች ዞረ፡፡ደጃዝማች ኃይሉም ወደ ርስቴ እመለሳለሁ የሚለው ተስፋቸው ተቆረጠ፡፡

ደጃዝማች ኃይሉ የሕይወታቸውን ፍጻሜ ያሳለፉት ጎጃም ሞጣ ነው፡፡ እዚያ ምናልባት እስከ 1810 ዓም አካባቢ የቆዩ ይመስላል፡፡ ሞጣ እያሉ ታላቁ የውጊያና የታሪክ ሰው ታምመው ሞቱ፡፡ ወገኖቻቸውም ሬሳቸውን ይዘው ራሳቸው ወዳሠሩት ወደ እስቴ መካነ ኢየሱስ ለመቅበር መጡ፡፡ ዘመነኞቹ የራስ ጉግሣ ሰዎች ግን ሬሳውን አናሳልፍም ብለው እምቢ አሉ፡፡ በዚህ ጊዜ ልጃቸው ወ/ሮ ምርጪት ፡-

እግዚኦ አቤት አቤት

እግዚኦ አቤት አቤት

አፈር ይለምናል የሀገሩ ባለቤት፤

ብለው ወደ ራስ ጉግሣ ደብዳቤ ጻፉ፡፡ ራስ ጉግሣም ነግ በእኔ ብለው ፈቅደው የታላቁ የውጊያና የታሪክ ሰው የደጃዝማች ኃይሉ መጨረሻ በእስቴ መካነ ኢየሱስ ተፈጸመ፡፡ በክፉ ዘመን ሰብስበው በማጻፍ ለዘመናችን ያበረከቱልን ታሪከ ነገሥት ግን ዘመንን እየተሻገረ እስከ ዘመናችን ዘልቋል፡፡ ለነገም ይኖራል፡፡ በችግራቸው የሚቆዝሙ፣ በመከራቸው የሚተክዙ፤ ከግንብ ባሻገር ብርሃንን ለማየት ያልታደሉ ሰዎችንም ይወቅሳል፡፡ እኛም ዜናውን ከታሪከ ነገሥታቸውና ተክለ ጻድቅ መኩሪያ ከጻፉላቸው አጭር ታሪክ አግኝተነዋል፡፡

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

ህዳር 7 ቀን 2006 በመላው ዓለም ለምትገኙ የኢሳት ድጋፍ ኮሚቴዎችና አድማጮች ሁሉ ባለፉት ጥቂት ቀናት በሳዑዲ አረቢያ ነዋሪ በሆኑ የኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ እየደረሰ የሚገኘውን እጅግ ዘግናኝ ድብደባ፣ ግድያና ሴቶችን አስገድዶ መድፈር በከፍተኛ ቁጭትና ሃዘን ተከታትለናል። የኢሳት የዝግጅት ክፍልም ይህንኑ ልዩ ትኩረት ስጥቶ መረጃዎችን እግር በእግር ሲያቀርብ ቆይቷል። የተሻለ ሕይወት ለመኖር በሚል ተስፋን ሰንቀው በስደት ሀገር […]

ኢትዮጵያዊ ባልሆነ መንግስት መገዛት ይብቃን! ጌታቸው ሽፈራው

አንድ የኢህአዴግ ታጋይ አሊያም ሲቪል ካድሬ ሲሞት በቴሊቪዥን ሳይቀር ይለፈፍለታል፡፡ በሳውዲ እየሞቱ ለሚገኙት ኢትዮጵያውያን ግን አንድም ነገር አልተደረገም፡፡ ሌላው ይቅርና መሰሎቹ አጭበርብረው ‹‹ምርጫ አሸነፍን›› ሲሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ለማጉረፍ ማንም የማይቀድማቸው እነ ኃ/ማሪያም አሁን ምንም አላሉም፡፡ በተቃራኒው ድምጽ ለማሰማት የወጡትን በጨካኝ ፖሊሶቻቸው አስደበደቡ፡፡

ወደ ጣሊያን ሲያቀኑ ያለቁት የአፍሪካ ስደተኞችን ሞት አስመልክቶ ሰንደቅ አላማው ዝቅ ብሎ ተውለብልቧል፡፡ የኢትዪጵያውያንን ነፍስ ምን ያህል አርክሰው ቢያዩት ነው? ለአንድ ቀን ሀዘን፣ ለአንድ ቀን ሰንደቅ አላማውን ዝቅ ለማድረግ አልፈቀዱም፡፡ ስለዛ አምባገነን መሪያቸው ግን ሁሌም ይቆዝሙብናል፣ ይለምኑብናልም፡፡ ኢትዮጵያን እንደነጠቁን ሰላማዊ ሰልፉን በመከልከል ዳግመኛ አረጋግጠውልናል፡፡ በተቃራኒው ከኤስያ፣ እስከ አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ የእኛዎቹ ወገኖች እንደልባቸው ሰላማዊ ሰልፍ እያደረጉ ነው፡፡

እንዲያውም ድጋፍ እየተደረገላቸው፡፡ ትናትና ፌስ ቡክ ላይ እንዳነበብኩት አንድ የአውሮፓ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ሲያሳውቁ የድምጽ ማጉያ የመሳሰሉ መሳሪያዎች ከሌሏቸው ማዘጋጃ ቤቱ ሊያውሳቸው እንደሚችል አረጋግጦላቸዋል፡፡ እንደ ሳውዲ ካሉት ውጭ ለኢትዮጵያውያን አገራቸው ካለው ይልቅ የተሰደዱበት መንግስታት ደግና ርሁሩሆች ናቸው፡፡ ለእኔ ኢህአዴግ ኢትዮጵያዊ ላለመሆኑ ከዚህ ውጭ አስረጅ አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡ የግድ እንደ ግራዚያኒ በየ ቤታችን ገብቶ በቆጨራ እስኪቆርጠን መጠበቅ የለብንም፡፡ ካድሬ ሆነ ተቃዋሚ፣ አማራ ሆነ ኦሮሞ፣ ትግሬ ሆነ ወላይታ ኢህአዴግ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን እስካለሰበ ድረስ ከስቃዩ ሊያመልጥ አይችልም፡፡ መለስ ከሞተበት ጊዜ ጀምሮ ኢህአዴግ ገንዘብ ሲያሰባስብ የነበረው እንደ ሳውዲ ባሉ አገራት ከሚገኙት ዜጎቻችን ጭምር ነው፡፡ የልመና ጊዜ በሮ የደረሰው የውጭ ጉዳይ አሁን በቲውተር ከሚቀልደው ያለፈ ሊፈይድ አልቻለም፡፡ ካድሬም ብትሆን አይቀርልህም፡፡

Image
በጊዜያዊ ጥቅም ከሆነማ ጣሊያንም ለባንዳዎቹ ከፍተኛ ጥቅም ሰጥታለችኮ፡፡ እነ ራስ ሀይሉ በወር 175 ሺህ ሊሬ ይከፈላቸው ነበር፡፡ የፋሽስቱን ስርዓት ያልተቃወመ ወጣት አሁን ኢህአዴግ ከሚያደርገው በላይ ተከፍሎታል፡፡ እናቶች፣ ካድሬ ቄሶችና ሌሎችም ኢህአዴግ አሁን ከሚያደርግላቸው በላይ ጣሊያንን እንዳይቃወሙ ጥቅማጥቅም ተሰጥቷቸዋል፡፡ በኋላ ግን በጅምላ ተጨፍጭፈዋል፡፡ እናም ይህን ኢትዮጵያውይ ያልሆነ መንግስት ኢትዮጵያዊ ማድረግ አይቻልም፡፡ በቃ! ከዚህ በላይ በደል መሸከም አንችልም፡፡ ከዚህ በላይ ባይተዋር መሆን አንፈልግም፡፡ ከዚህ በላይ ማንባት አንሻም፡፡ ኢህአዴግን በግልጽ በቃህ የምልበት የመጨረሻው ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ አዎ! ኢትዮጵያዊ ባልሆነ መንግስት መገዛት ይብቃን! Getachew Shiferaw.

Image
Ethiopian migrants sleep out in the open near a transit centre where they wait to be repatriated in the western Yemeni town of Haradh, on the border with Saudi Arabia, (REUTERS/Khaled Abdullah) dailystar.com
********************************************************************************************************************

በአብዛኛው የኢህአዴግ ድርጅቶችን ብቻ በማሳተፍ የምዝገባ ዘመቻው ቀጥሏል
ዛሬ መልካም ዜናን ከሪያድ መጠለያዎች ሰማሁ !
* 66 በሚደርሱት መጠለያ የሚገኙት ኢትዮጵያን ይዞታ መሻሻል ጀምሯል
* የምግብ የውሃና የህክምና አገልግሎቱ ሽፋን አበረታች ነው ፣ አቅርቦቱ ሙሉ በሙሉ በሳውዲ መንግስት የሚሸፈን ነው
* ለህጻናትና ለአቅመ ደካማ ሴቶች ትኩረት እየተሰጠ ነው
* የተሻለ መጠለያ ለማስተላለፍ የተደረጉ ሙከራዎች በተጠላዮች ፍርሃቻ ከሽፈዋል
* ተጠላዩ ግን ፍርሃት አለበት ፣ ከመጠለያው ውጭ ያሉ ዜጎች በሚሰጡት ነዋሪው ሊያረጋገው አልቻለም

የጅዳው አስጊ ሁኔታና የቆንስል መስሪያ ቤቱ የሽሜሲ ዘመቻ፡-

* የጅዳ ቆንስል ላልተወሰነ ጊዜ ተዘግቷል
* የመረጃ እጥረት አሁንም አለ
* በጅዳ አንዳንድ አካባቢዎች ህገ ወጥ ወገኖች በመረጃ እጥረት ወደ ሁከት እንዳይሸጋገሩ ያሰጋል
* መኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ነዋሪዎች እንዲታገሱ ህጋዊ ነዋሪዎች እየተማጸኑ ነው
* የቆንስላው ሃላፊዎች ትኩረት ወደ ሽሜሲ ጊዜታዊ እስር ቤት ሆኗል
* በአብዛኛው የኢህአዴግ ድርጅቶችን ብቻ በማሳተፍ የምዝገባ ዘመቻው ቀጥሏል
* በቆንስሉ መዘጋት ብዙዎችን አስቆጥቷል ” የታመመ ቢሞት እንደጰት እንቅበር? ፖስፖር ቢታደስ ማስተካከል ቢያስፈልግ ምን እናድርግ? የጋብቻ ወረቀት ማረጋገጫና እና ተመሳሳይ ግልጋሎት ስንፈልግ የት እንሂድ? ” ሲሉ በማጠየቅ በአስቸኳይ ቆንስሉ እንዲከፈት ነዋሪዎች መንግስትን ተማጽነዋል

* የሰው ሃይል እጥረት አለ፣ ሶስት ኢኒስፔክተሮች ከሃገር ቤት ጅዳ ገብተው ስራቸውን ጀምረዋል
* በጎ እናድርግ የሚሉ ነዋሪዎች ተበራክተዋል ፣ የቆንስሉን መልስ እየጠበቁ ነው

አይኖቼ በደም ቀሉ። ልቤ ተሰበረ። ከሳዉዲ አረቢያ፣ ከባህር ማዶ፣ የወገኖቼ ጩኸትና ሮሮ፣ ከጣራዬ በታች የመነጨ ይመስል፣ በጆሮዬ በቅርበት ያቃጭላል። በርግጥ እንደ አገር፣ እንደ ሕዝብ ፣ እንደ ኢትዮጵያዊ መዋረዳችንን አየሁ። በተለይም ደግሞ በአሁኗ ሰዓት፣ እንደ ወገን ምንም ማድረግ ባለመቻሌ ዉስጤ ደበነ። የማድርገዉን ሳጣ መሬት ተንበረከኩ። አይኖቼን ወደ ላይ አንስቼ፣ እጆቼን ዘረጋሁ። «ሄሮድስ ሊገድልህ ፈልጎ በነበረ ጊዜ፣ […]

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሥራ አስኪያጁ ላይ የተላለፈውን የስንብት ርምጃ ውድቅ በማድረግ ወደ ሓላፊነታቸው እንዲመለሱ ለሊቀ ጳጳሱ ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡ ይኹንና ትእዛዙ በ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ዘንድ ተቀባይነት አግኝቶ ተፈጻሚ ባለመኾኑ በአሜሪካ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋራ በሐዋርያዊ ጉብኝት ላይ የሚገኙት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ እየተጠበቁ ነው፡፡ ራሳቸውን ‹‹የሊቀ ጳጳሱ የግል አማካሪ›› ብለው …

የኢትዮጵያ መንግሥት የሶማሊያዉ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አሸባብ እና አሸባሪዎች ያላቸዉ ሌሎች ቡድናት ኢትዮጵያ ዉስጥ አደጋ ለመጣል መዘጋጀታቸዉን የሚጠቁም መረጃ ደርሶኛል በማለት ሕዝቡን አስጠንቅቋል።

የኬንያ እና የሶማልያ መንግሥታት በኬንያ ከለላ ያገኙ ከ500,000 የሚበልጡ የሶማልያ ስደተኞችን ወደ ትውልድ ሀገራቸው ለመመለስ ከተመድ የስደተኞች ጉዳይ ተመልካች መሥሪያ ቤት፣ በምሕፃሩ «ዩ ኤን ኤች ሲ አር» ጋ አንድ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።

Image

በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው መከራ መስማት ህሊና መሸከም ከሚችለው በላይ ሆኗል። ኢትዮጵያዊን እህቶቻችን ወንድሞቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ እየተገደሉ፤ አካሎቻቸው በስለት እየተቆራረጠ፤ እየተደበደቡና እየተደፈሩ ነው።

ይህ ሁሉ የሚፈፀው በሪያድ፣ ጂዳና አዲስ አበባ የሚገኙ የወያኔ ዲፕሎማቶች መልካም ፈቃድና ሙሉ ተባባሪነት መሆኑ ደግሞ ይበልጥ የሚያንገበግብ ነው። ወያኔ ለአረብ ሀብታም ሸሪኮቹ ለም መሬቶቻችንን ሰጥቶ ኢትዮጵያዊ በአገሩ ሠርቶ የእለት ጉርሱን መሸፈን የማይችልበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ አደረገው። ቀጥሎ ደግሞ በሺዎች የሚቆጠሩ ልጃገረዶችና ወጣት ኢትዮጵያንን እየደለለ ከባርነት ላልተሻለ ግርድና አሳልፎ ሰጣቸው። ይህ ሁሉ ግፍ አልበቃ ብሎ “በሏቸው፤ ቀጥቅጧቸው፤ ህገወጦች ናቸው” እያለ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ በአጋፋሪነት እያስተናገደ ነው።

በኩየት በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ ተመሳሳይ ሰቆቃ ሊደርስ የሚችል መሆኑ ምልክቶች እየታዩ ነው። በኩዌት ያለአንዳች ምክንያት ቁጥራቸው በአንድ ሺህ በላይ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን በድንገት ከሥራ ተባረዋል። እዚህም የወያኔ እኩይ እጆች እንዳሉት መረጃዎች አሉ። በሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም ሕይወታቸው በዘወትር ስጋት ላይ ወድቋል።

የኢትዮጵያዊያን እጣ ፈንታ በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም ሰቆቃና እንግልት መሆኑ የሚያሳዝን ብቻ ሳይሆን የሚያስቆጭ፤ ለመራራ ትግል የሚያነሳሳም ነው። ለአገሩ ሕዝብ የሚቆረቆር መንግሥት ኑሮን ቢሆን ኖሮ ሕይታችን እንዲህ የተመሰቃቀሰ ባልሆነም ነበር።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሳውዲ አረቢያ እና ሌሎችም የመካከለኛ ምሥራቅ አገራት መንግሥታት ለኢትዮጵያዊያን እህቶቻንና ወንድሞቻችን ሰብዓዊ ክብር እንዲሰጡ አበክረን እናሳስባለን። ሰብዓዊ መብቶችን መድፈር ዓለም ዓቀፍ ወንጀል መሆኑን ልንነግራቸው እንፈልጋለን። በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ አሁኑኑ ይቁም!!! ሰቆቃ ፈፃሚዎች ለፍርድ ይቅረቡ!!!

በተቻለው ፍጥነትና ባገኘነው እድል ሁሉ ተጠቅመን ሕይወታቸው አደጋ ላይ ላሉት ወገኖቻችን እንድንደርስ ግንቦት 7 ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ያደርጋል።

በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ በዘላቂነት የሚወገደው ወያኔ ከሥልጣን ተባሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የመረጠው መንግሥት ሲያስተዳድር በመሆኑ ለዚህ ታላቅ ግብ በኅብረት እንነሳ።

በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ ይቁም!!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ህዳር ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሳውድ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ ተባብሶ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ የሳውዲን መንግስት ለመቃወም በሳውድ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ተቃውሞዋቸውን ለመግለጽ የወጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በፌደራል ፖሊሶች ተደብድበዋል። ከ100 በላይ ሰዎች ታስረው የነበረ ሲሆን እስከ ምሽት ድረስ 40 የሚሆኑት ተለቀዋል። ሰልፉን ያዘጋጀው የሰማያዊ ፓርቲ 15 የአመራር አካላትም በእስር ላይ …

ላለፉት ሰባት ዓመታት በዐረብ ሀገር የኖረችና ከአራት ወራት በፊት ነዋሪነቷን በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገች ወጣት ኢትዮጵያዊት፣ ከኢትዮቲዩብ ጋር ባደረገችው ቃለምልልስ በዐረብ ሀገር የነበራትን ቆይታ፣ በሀገር ቤትም ያለውን ችግር፣ የኢትዮጵያን ኤምባሲ በተመለከተ በግሏ የደረሰባትን ስትገልጽ ልብ ትሰብራለች። ትናንት ኅዳር 5 ቀን 2006 ዓ.ም. (ኖቨምበር 14፣ 2013 እ.ኤ.አ.) ዋሽንግተን ዲሲ በሳዑዲ ዐረቢያ ኤምባሲ በርካታ ኢትዮጵያውያኖች የተቃውሞ ሰልፍ ባደረጉበት ወቅት ነበር ኢትዮቲዩብ ያናገራት። 

 

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ ሣዑዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን ላይ “ተፈፅሟል፣ እየተፈፀመም ነው” ያለውን ግፍ በመቃወም ዕሁድ፤ ኅዳር 8/2006 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡

የሰልፍ ዕውቅና የሚሰጠው ክፍል ግን በቃል አሉታዊ መልስ እንደሰጠው አስታውቋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ሳዑዲ አረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር በመቃወም የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ፡፡

አዲስ አበባ በሚገኘው የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አቅራቢያ በተሰባሰቡት ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ “ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እሥር ተፈፅሟል” ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ድርጊቱን አውግዟል፡፡

የአዲስ አበባ አስተዳደር በበኩሉ ለቪኦኤ በሰጠው ቃል ሰልፉ “ሕገወጥ ነው” ብሏል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ አዘጋጆቹ “ከሚመለከተው ክፍል ፍቃድ…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከፍበኛ መሻሻል ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ፈባጠን አካሄድ አፍሪካን አልፎ በቀሪውም ዓለም መድረክ ሊያሣትፈው የተቃረበ ይመስላል፡፡

ነገ፣ ቅዳሜ ኅዳር 7/2006 ዓ.ም ከናይጀሪያ አቻው ጋር በሚያደርገው የመልስ ግጥሚያ አስፈላጊውን ሁሉ አሟልቶ ካሸነፈ በመጭው ሰኔ ብራዚል በምታስተናግደው የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ አህጉሪቱን ከሚወክሉ አምስት የአፍሪካ ብሔራዊ ቡድኖች አንዱ ይሆናል ማለት ነው፡፡

ለዚህ ወሣኝ ፍልሚያ ቡድኑ “ብቃት ያለው ዝግጅት አድርጌአለሁ” ይላል፡፡

ሰሎሞን ክፍሌ የነገው የመልስ ጨዋታ ወደሚካሄድባት የናይጀሪያ ከተማ ካላባ ደውሎ የቡድኑን ዋና አሠልሐኝ ሰውነት ቢሻውንና ሌሎችም የቡድኑን አባላት አነጋግሯል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ፌደራል አቃቢ ሕግ “የግንቦት ሰባት አባል በመሆን” ና “የሽብር ወንጀል ፈፅመዋል” ሲል በሃያ ሰዎች ላይ ክሥ መሥርቷል፡፡

ሰዎቹ መቼ እንደታሠሩ ግን አልገለፀም፡፡

ጉዳዩ እየታየ ያለው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት ሲሆን ተከላካይ ጠበቃ ያቀረበው የክሥ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ውድቅ ሆኗል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የአንዳንድ ተከሣሾች ጉዳይ በሌሉበት መታየት ጀምሯል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የመለስካቸው አምኃ ዘገባ ያዳምጡ፡፡

ሐኪሞቹና ረዳቶቻቸዉ አዲስ አበባና ደብደረ ብርሐን ከተሞች በሚገኙት ሆስፒታሎች ዉስጥ በማሕፀን፥ በኩላሊትና በአይን ሕመም ይሰቃዩ ለነበሩ በሺሕ ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን የቀዶ ሕክምና ርዳታ አድርገዋል

አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበዉ ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል።

SHARE:

ማምሻውን በደረሰን መረጃ
ሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ የደረሰውን በድል እና ስቃይ ለመቃወም አዲስ አበባ በተጠራው ሠላማዊ ሠልፍ የኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሶች አሰቃቂ ድብደባና እሰር መፈፀማቸው ቀደም ተብሎ መገለፁ የሚታወቅ ነው፡፡ አሁን በደረሰን መረጃ ቁጥራቸው ወደ 100 የሚጠጉ እስረኞች የተለቀቁ ሲሆን ፤ከነዚህም መካከል ጋዜጠኞች እንደሚገኙበት ለማወቅ የተቻለ ሲሆን የተቀሩት ማለትም፡-
1ኛ. ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የፓርቲው ሊቀ/መ
2ኛ. አቶ ስለሺ ፈይሳ የፓርቲው ም/ት ሊቀ/መ
3ኛ. አቶ ወረታው ዋሴ የፓርቲው የፋይናስ ጉዳይ አላፊ
4ኛ. አቶ ጌታነህ ባልቻ የፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ አላፊ
5ኛ. አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት አላፊ
6ኛ. አቶ ዮናታን ተስፋዬ የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ አላፊ
7ኛ. አቶ አብታሙ ደመቀ የብሔራዊ ም/ቤት አባል
8ኛ. አቶ ዮናስ ከድር የብሔራዊ ም/ቤት አባል
9ኛ. ዮሴፍ ተሻገር የብሔራዊ ም/ቤት አባል
10ኛ. ወጣት አቤል ኤፍሬም አባል
11ኛ. ሰለሞን ወዳጄ አባል
12ኛ. ፋሲካ ቦንገር አባል
13ኛ. መርከብ ሀይሌ አባል
14ኛ እመቤት ግርማ አባል
15ኛ. አስራት አብርሃም ደራሲና ጻአፊ (በግል)
16ኛ. ዳዊት ፀጋዬ ደራሲና ጻአፊ (በግል)
17ኛ. እየሩስ ተስፋ አባል
18ኛ. ንግስት ወንድኢፍራው አባል
ከላይ በስም ዝርዝ የተገለፁ እስካሁን መስቀል ፍላወርና ፒያሳ ማዘጋጃ አካባቢ በሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ ሲሆን ከፍተኛ ደብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሎአል፡፡ እንዲ አይነቱን ድርጊት ፓርቲው ያስቆጣው መሆኑን እየገለፀ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እንጠይቃለን፡፡

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል እና ስቃይ መጠኑ ከመጨመር አልፎ ሕይወትን እስከማሳጣት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን በደል እና ስቃይ ለመቃወም እና ሀዘናችንን ለመግለፅ በዛሬው ዕለት ማለትም ህድር 6 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራ ቢሆንም በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ በአሰቃቂ እርምጃ ሰልፉ ሊካሄድ አልቻለም፡፡

እኛ ኢትዮጵያን በውጭ በሚገኙ ዜጐቻችን ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ እንዲቆም፣ ይህንንም ድርጊት የፈፀሙት ለሕግ እንዲቀርቡና የተጐዱ ዜጐች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በዜጐቹ ላይ ያሳየውን ቸልተኝነት በአስቸኳይ በማቆም ተገቢ የሆነውን የመንግሥት ኃላፊነት እንዲወጣ ቢጠየቅም፤ ሰልፉ በተቃራኒው በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ ተጠናቋል፡፡
በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ቢሆኑም እኛ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራችን ድምፃችንን እንኳን እንዳናሰማ ታፍነናል፡፡ በዚህም እንቅስቃሴ ላይ የተሳተፉ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እስር ተፈፅሞባቸዋል፡፡

Image

የመንግሥት ፖሊሶች የራሳቸውን ዜጋ በመደብደብና በማሰቃየት ብሎም በማሰር በሳውዲ በሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን በደል ሀገር ውስጥ በሚገኙ ንፁሐን ወገኖቻቸው ላይ ደግመውታል፡፡
ይህ በውሸት ዲሞክራሲ ስም የተደበቀው አምባገነን መንግሥት ሕዝብን ለማሸማቀቅ የወሰደውን እርምጃ ወደ ጐን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅድም አያቶቹን በማስታወስ ያስረከቡትን ክብር ከማስመለስ ወደ ኋላ እንደማይል እርግጠኛ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡
ፓርቲያችን እንዲህ አይነቱን የለየለት የመንግሥት ሕገ ወጥ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ የሚመለከተው መሆኑን እየገለፅን፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጐናችን እንዲቆም በአፅንኦት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም

SHARE:

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል እና ስቃይ መጠኑ ከመጨመር አልፎ ሕይወትን እስከማሳጣት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን በደል እና ስቃይ ለመቃወም እና ሀዘናችንን ለመግለፅ በዛሬው ዕለት ማለትም ህድር 6 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራ ቢሆንም በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ በአሰቃቂ እርምጃ ሰልፉ ሊካሄድ አልቻለም፡፡
እኛ ኢትዮጵያን በውጭ በሚገኙ ዜጐቻችን ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ እንዲቆም፣ ይህንንም ድርጊት የፈፀሙት ለሕግ እንዲቀርቡና የተጐዱ ዜጐች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በዜጐቹ ላይ ያሳየውን ቸልተኝነት በአስቸኳይ በማቆም ተገቢ የሆነውን የመንግሥት ኃላፊነት እንዲወጣ ቢጠየቅም፤ ሰልፉ በተቃራኒው በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ ተጠናቋል፡፡
በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ቢሆኑም እኛ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራችን ድምፃችንን እንኳን እንዳናሰማ ታፍነናል፡፡ በዚህም እንቅስቃሴ ላይ የተሳተፉ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እስር ተፈፅሞባቸዋል፡፡
የመንግሥት ፖሊሶች የራሳቸውን ዜጋ በመደብደብና በማሰቃየት ብሎም በማሰር በሳውዲ በሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን በደል ሀገር ውስጥ በሚገኙ ንፁሐን ወገኖቻቸው ላይ ደግመውታል፡፡
ይህ በውሸት ዲሞክራሲ ስም የተደበቀው አምባገነን መንግሥት ሕዝብን ለማሸማቀቅ የወሰደውን እርምጃ ወደ ጐን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅድም አያቶቹን በማስታወስ ያስረከቡትን ክብር ከማስመለስ ወደ ኋላ እንደማይል እርግጠኛ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡
ፓርቲያችን እንዲህ አይነቱን የለየለት የመንግሥት ሕገ ወጥ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ የሚመለከተው መሆኑን እየገለፅን፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጐናችን እንዲቆም በአፅንኦት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም

Image

Getachew=Shiferaw-
በጧቱ ነበር ወደ ወሎ ሰፈር ለማቅናት መንገድ የጀመርኩት፡፡ መሃል ላይ አንድ ስልክ ደረሰኝ፡፡ ‹‹የሰማያዊ ፓር አመራሮችና አባላት ታግተዋል›› የሚል፡፡ ለማረጋገጥ ወደ ቢሮ መሄድ ነበረብኝ፡፡ ቢሮ ስደርስ የአካባቢው ሰዎች ሰብሰብ ሰብሰብ ብለው ስለ ታሳሪዎቹ፣ ሳውዲ ውስጥ ስለሚሰቃዩት ኢትዮጵያውያን፣ ስለሰላማዊ ሰልፉ ያወራሉ፡፡

በርካታ ፖሊሶች በቢሮው አካባቢ ተሰባስበዋል፡፡ ግቢው ውስጥ ግን ማንም የለም፡፡ ቢሮው በር ላይ ሳውዲ ውስጥ ለሚሰቃዩት ወገኖች በምልክትነት የተሰቀለው ጥቁር ምልክት እንዳልተነሳ ስመለከት ፖሊሶቹ ስለ ጉዳዩ እውቀት እንደሌላቸው ገባኝ፡፡ አመራቹን በአንዳች ነገር ከሰው ብቻ እርምጃ እንዲወስዱ ተነግሯቸዋል ማለት ነው፡፡

ከሰዎች መረጃ እያሰባሰብኩ እያለ ሌላ ስልክ ደረሰኝ፡፡ ‹‹ወደ ጃን ሜዳ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸዋል›› የሚል ነው፡፡ ወደዛው መሄድ አለብኝ፡፡ አንድ ጓደኛየን አግኝቸው ከእሱ ጋር አመራሁ፡፡ ኤምባሲው ጋር የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀላቀል እየረፈደብን ቢሆን ስለ ታሳሪዎቹ መረጃ ማግኘት ነበረብን፡፡

ጃን ሜዳ ፖሊስ ጣቢያ ስንደርስ ኢንጅነሩንና ሌሎች ጥቂት አመራሮችን ከርቀት አየናቸው፡፡ ሌሎቹን አስገብተው እየደበደቧቸውም ይሁን ለሌላ ጉዳይ ውስጥ ገብተው አይታዩም፡፡ ፖሊሶቹ ወደ እኛ ሲመጡ ሳውዲ ኤምባሲ ያለውን ጉዳይ ከመታሰር ብለን ታሳሪዎቹን ከእርቀት ሰላም ብለን ወደ ኤምባሲው እየተቻኮልን አቀናን፡፡

ሰዓቱ እየሄደ በመሆኑ ላንደርስ እንችላለን ብለን ሰግተናል፡፡ በእርግጥ የኢህአዴግ አንዱ ስልትም እንዲህ በተለያዩ ጉዳዮች በመወጠር ዋናውን ነገር ማሳት ነው፡፡ ወሎ ሰፈር አካባቢ ወደ 6 ሰዓት አካባ ስንደርስ ጥቁር የለበሱ ሰዎች ከኤምባሲው አቅጣጫ እየተመለሱ ነው፡፡ ሌላው ህዝብ ደግሞ በየ መንገዱ ዳር ቆሞ ይመለከታል፡፡

ይበልጥ እየቀረብን ስንሄድ የምናውቃቸውን ሰዎች አገኘን፡፡ እስካሁን አልተደበደብኩም የሚል ሰው አላጋጠመንም፡፡ አንዲት ምን አልባትም ሳውዲ ውስጥ የምታውቀው ሰው ጥቃት የደረሰበት ዘመድ ያላት የምትመስል ሴት ስቅስቀስ ብላ ታለቅሳለች፡፡ ሙሉ ጥቁር ልብስ ለብሳለች፡፡ ይህች ሴት እንዲህ የምታለቅሰው ከድብደባው ይልቅ ለዜቾቻችን ክብር ያልተሰጣቸው መሆኑ ነው፡፡

ሌላኛዋ ደግሞ የምታለቅሰው በጣም በመደብደቧ ነው፡፡ አንድ ሌላ ወጣት (ጓደኛየ ጋር ይተዋወቃሉ) ሰላም ካለን በኋላ በየ ቦታው ይቀመጣል፡፡ ምኑን እንደመቱት ስንጠይቀው ኩላሊቱ አካባቢ የተገመደለ አዲስ ቁስል አሳየን፡፡ ልጁ በንዴት ይቁነጠነጣል፡፡

በርካቶች መታሰራቸውን ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የነበሩት ነግረውናል፡፡ አብዛኛው የተበተነው ወጣት እያማረረ ነው፡፡ አንደኛው ‹‹ሰላማዊ ትግል አያስፈልግም›› ይላል፡፡ ለጎኑ ካሉት ክርክር ይገጥመዋል፡፡ ሌላኛው ‹‹ ነገ ኳስ ላይም ቢሆን ይህን ጮከታችን እናሰማለን››፣ ሌላኛው ‹‹እኔ የተደበደብኩት አገሬ ውስጥ ነው ወገኖቹ ሳውዲ ውስጥ እየሞቱ ነው፡፡››፣ ሌላኛዋ ‹‹እሁድም መጥተን መደብደብ አለብ›› ……

እኔም ቢሆን ኢህአዴግ ይፈቅዳል የሚል ተስፋ አልነበረኝም፡፡ ሰማያዊዮች ሲታሰሩም ማረጋገጥ የቻልኩት ይህን ነው፡፡ ግን መታሰርም ሆነ መደብደብ አንድ ነገር ነው፡፡ ይህ ለዜጎቻችንም ሆነ ለራሳችን ያለንን ክብር የምናሳይበት ነው፡፡ ኢህአዴግ ዳግመኛ ከገዳዮቻችን፣ ከጠላቶቻችን ጎን ቆሞ፡፡ ጸረ ህዝብነቱንም አስመሰከረ፡፡
አንዳንዴ ስትደበደብ ወይንም ስትሰታሰር ይወጣልሃል፡፡ እኔ እየዞርኩ ሳይ የዋልኩት የዜጎችን ሰቆቃ ብቻ ነው፡፡ እናም ቅጥል ብያለሁ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ለመሳተፍ የወጡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ታሰሩ፡፡ ከጽ/ቤታቸው ተነስተው ወደ ሰላማዊ ሰልፉ ቦታ ሲሄዱ 4 ኪሎ የኦሮሚያ ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ጎን በሚገኘው ወታደራዊ ገራዥ መታሰራቸውን ዘጋቢያችን ከቦታው አድርሶናል፡፡ ከመታሰራው ቀደም ብሎ ከፖሊስ ጋር እንሂድ አትሄዱም በሚል ጭቅጭቅ ላይ እንደነበሩ ሰምተናል፡፡ ሌሎች የፓርቲው አባላትና አመራሮች ተበታትነው ወደ ሳውዲ አረቢያ […]

ጥላቻው እያደገ ሔዷል ፣ ሳውዲ አሰሪዎች ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞቻቸውን ድሮ ድሮ በአረቦች ዘንድ የተከበርን ፣ የታፈርን የእኛን የሃበሻ ልጆች “ጨካኞች ፣ የማይታመኑ !” እያሉ ጥላቻቸውን መገልጽ ጀምረዋል። November 14,2013 የወጣው አረብ ኑውስ Recent clashes make Saudis wary of Ethiopian maids በሚል ርዕስ ስር ሳውዲ አሰሪዎች ኢትዮጵያን ሰራተኞችን ለማባረር እየዛቱ ነው ! ይህ የአረብ ኒውስ ዘገባ […]

የህግ ባለሙያው ዶ/ር ሸክስፒር ፈይሳ ንግግር ያደርጋል

አሁንም የኢትዮጵያዊያኖች የድረሱልኝ ጥሪ እየተሰማ ነው(ቪድዮዎችን ይመልከቱ)

Ethiopia Zare (ሐሙስ ኅዳር 6  ቀን 2006 ዓ.ም. November 30, 2013)በካናዳ የንግድ መናገሻ በሆነችው ቶሮንቶ ከተማ በሳኡዲት አረቢያ በኢትዮጵያዊያኖች ላይ የሚፈጸመውን ግፍ በመቃወምና በአሰቃቂ ሁናቴ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች የሻማ ማብራት ስነስርአት ነገ አርብ እንደሚካሄድ ይፋ ተደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ህዳር ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአውሮፓና አሜሪካ የሚገኙ ኢትዮያውያን በሰልፍ ተቃውሟቸውን ሲገልፁ ውለዋል። በሳዑዲ ዐረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈፀመ ያለው ግፍ ተባብሶ መቀጠሉን ተጠቂዎቹ ለኢሳት ገለፁ። በሪያድ  ወደማጎሪያ ካምፕ ውስጥ  የተወሰዱ ኢትዮጵያውያን ካሉበት ስፍራ ሆነው ለ ኢሳት በስልክ እንደገለፁት፤ በትናንትናው ዕለት ብቻ  በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በከባድ መኪናዎች እየተጫኑ ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። ስደተኞቹ-ለሳዑዲ ፖሊሶች፦” ወደ …

ህዳር ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህዳር እና የታህሳስ ወራትን  በሙሉ በጾም በጾሎት ምእመኑ እግዚኦታ እንዲያሰማ ቄስ አለሙ ሺጣ የኢትዩጵያውያን ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ዋና ጽሓፊ በአምላክ ስም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በኢትዩጵያ በአሁኑ ስዓት እየተሰተዋለ ላለው ችግር ፣በምስራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ሐገራት እንዲሁም በአለም ለሚታየውና ለሚሰማው በደል- ሀይማኖቱ በሚጠይቀው ስርዓት እጆችን ወደ አምለክ እንድናነሳ እና እንድናለቅስ …

ህዳር ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሸንጎው ከፍተኛ የአመራር ምክርቤትቅዳሜ ጥቅምት 29፣ 2006 ባደረገው ስብሰባ በሳዑዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ በሀገሪቱመንግስት የጸጥታ ሀይሎችእየደረሰ ያለውን ህገወጥ እስራት፣ድብደባና ስቃይ በታላቅ ሀዘንና አንክሮ እንዳጤነው ገል ል። ሸንጎው  ለዚህ ግፍ ሰለባዎችና ለቤተሰቦቻቸው የተሰማውን ሀዘን  በመግለጽ  ከጎናቸው እንደሚቆምምአረጋግጧል። በተመሣሳይ የ ኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ ( ኢህአፓ) ሳውዲ አረብያ በዜጎቻችን ላይ …

በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎቹ ወደሀገራቸው እየተመለሱ መሆኑን የገለፀው የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናቱም ከሳዑዲ አቻዎቻቸው ጋር እየተነጋገሩ መሆናቸውን አስታውቋል።

በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ አምባሣደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ የተመራ የልዑካን ቡድን ወደ ሪያድ መጓዙ ተገልጿል፡፡

ሰሞኑን መግለጫ እያወጡ ያሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግን መንግሥት ለእርምጃው ዘግይቷል፥ የበለጠ ሥራም ይጠብቀዋል ይላሉ።

በጉዳዩ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት ለነገ ጥሪ የበተነው መኢአድ የሌሎች አንዳንድ ሃገሮች ዜጎች መብቶች ከኢትዮጵያዊያኑ በተሻለ ሁኔታ እንደሚጠበቅና በኢትዮጵያዊያን ላይ ግፍ ሲደርስ ግን የአሁኑ የመጀመሪያ አለመሆኑን የድርጅቱ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ አመልክተዋል፡፡

ዛሬ መግለጫ ያወጣው ሰማያዊ ፓርቲ ደግሞ ነገ ዐርብ፣…

“የወገን ደራሽ ወገን ነው” በሚል መሪ ቃል የተጠራ የኢትዮጵያዊያን ሰልፍ ዛሬ፣ ኅዳር 5 / 2006 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የሣዑዲ አረቢያ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ ተካሂዷል፡፡

በሰልፉ ላይ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የተገኙ ሲሆን ሣዑዲ አረቢያ ለሚገኙ ወገኖቻቸው ጥበቃ እንዲደረግ፣ ሰብዓዊ መብቶቻቸው እንዲከበሩ፣ በአፋጣኝ ወደ ሃገራቸው የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠይቀዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡