ሰማያዊ ፓርቲ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደረገ ባለው ፖለቲካዊ ትግል በፍርሀት ድባብ ውስጥ ተውጦ የነበረውን ህዝብ የጨለማ ድባብ እየገፈፈው ይገኛል፡፡ በዚህ ስራውም የብዙ ታላላቅ ምሁራንን እና ወጣቶችን ቀልብ መሳብ ችሏል፡፡ በመሆኑም ፓርቲው ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን ያሳካ ዘንድ ብሎም አሁን ካለበት የተሻለ ተንቀሳቅሶ ተፎካካሪና ተወዳዳሪ ፓርቲ ይሆን ዘንድ ገንዘብ ያስፈልገዋል፡፡ ገንዘቡን ሊያገኝ የሚችለው ደግሞ ከአበላትና ደጋፊዎች መሆኑ ሀቅ ነው፡፡ በመሆኑም ግንቦት 23 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ ቪው ሆቴል ታላቅ የእራት ግብዣ ፕሮግራም ደግሶ ይጠብቅዎታል፡፡የእራት ግብዣው መግቢያ ካርዶችም የተዘጋጁ ሲሆን እነዚህም ባለ አምስት መቶ ባለ አንድ ሺህ፤ባለ ሶስት ሺህ፤ባለ አምስት ሺኅ እና ባለ አስር ሺህ ብር ናቸው፡፡እርስዎም የእራት ግብዣውን ካርድ በመግዛት ሰማያዊ ፓርቲን እያገዙ ወደ ነጻነት ይጓዙ፡፡ ባለ አስር ሺህ ብር ካርድ በቁጥር ጥቂት ስለሆነ ባለ አምስት ሺህና ሶስት ሺህ አማራጭ መኖሩን እንዳይዘነጉ፡፡ በእራት ግብዣው ላይ የተከበሩና ታላላቅ ሰዎች፤ተጋባዥ እንግዶች፤ታላላቅ ፖለቲከኞች፤ገጣሚያንና ጋዜጠኞች ይገኛሉ፡፡እንዲሁም የተለያዩ አዝናኝ ፕሮግራሞች፤ጨረታዎችና ታዳሚን ሊያዝናኑ የሚችሉ ለየት ያሉ ጨዎታዎች ይቀርቡበታል፡፡ በዚህ የእራት ግብዣ ላይ በመገኘት እየተዝናኑ፤በኢትዮጵያዊ ጨዋነት እየተጎራረሱ ስለ ሀገርዎ እጣ ፈንታ በመሶብ ዙሪያ ይነጋገሩ፡፡ የመግቢያ ካርዶችን ከአስተባባሪዎች፤ከአባላትና ከአመራሮች ማግኘት የሚችሉ ሲሆን ከሀገር ውጭ የምትኖሩ ወገኖቻችን የመግቢያ ካርዱን ለወዳጅ ዘመድ መግዛት የሚቻል በመሆኑ ይህን በአይነቱ ለየት ያለና ለነጻነት የሚከፈል ውድ ስጦታ ወዳጅ ዘመድዎን እንዲጋብዙ ስንል ጥሪ እናቀርባለን፡፡ አያይዘንም የእራት ግብዣው ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ክፍት መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ለበለጠ መረጃ፡-ሰማያዊ ፓርቲ
ስልክ ቁጥር-+251 911 679223
+251 931 153809
+251 11 8 592950
አቢሲኒያ ባንክ አራዳ ቅርንጫፍ የባንክ ሂሳብ ቁጥርC/619
E-mail [email protected]
www.semayawiparty.org

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች መድረክ በጠራው ሰልፍ ተገኝተው መፈክር ሲያሰሙ እንደነበረ የሚገልጽ ቪዲዮ በሰማያዊ ፓርቲ ፌስ ቡክ ገጽ ተለቀቀ። ሊቀመንበሩን ኢንጂነር ይልቃልን ጨምሮ፣ ሰማያዊዎች የሰማያዊ ፓርቲ ከኔተራዎችን ለብሰውና የድርጃታቸው አርማ ይዘው ሳይሆን፣ እንደ ሌላው ህዝብ ሰልፉ እንደተቀላቀሉ ቪዲዮው ያሳያል።

·የሠሞኑ የአክራሪ ኦሮሞዎች እንቅስቃሴ የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ የነደፈውን የአዲስ አበባ ከተማን የማስፋፋት ዕቅድ ለመቃወም ሣይሆን ዐማራን ከምድረ-ገፅ ማጥፋት መሆኑን ያረጋግጣል። ሠሞኑን በዓለማያ፣ በአምቦ፣ በነቀምት እና በሮቤ (መዳወላቡ) ዩኒቨርስቲዎች በሚማሩ የዐማራ ተማሪዎች ላይ በአክራሪ የኦሮሞ ተማሪዎች እና በኦሕዴድ ካድሬዎች ትብብር ዘርን መነሻ እና መድረሻ አድርጎ የሚፈጸመው ጥቃት፣ ማቆሚያ የሌለው እና የዐማራን ነገድ ከምድረ-ገፅ ለማጥፋት በትግሬ-ወያኔዎች እና በተባባሪዎቻቸው […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የበጎ ሰው ሽልማት መርሐ ግብር ግንቦት 30 ቀን 2006 ዓም በኢሊሊ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ ‹‹በጎ ሰዎችን በመሸለምና በማክበር፣ ሌሎች በጎ ሰዎችን እናፍራ›› በሚል ሐሳብ የተጀመረው መርሐ ግብር ወደ ማጠናቀቂያው እየተጓዘ ነው፡፡ በሰባቱ ዘርፎች የሚወዳደሩት 35 ዕጩዎች የታወቁ ሲሆን ማክሰኞ ግንቦት 19 ቀን 2006 ዓም በኢሊሊ ሆቴል ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ በሚሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ ይሆናሉ፡፡
መርሐ ግብሩን ለማገዝ አያሌ ድርጅቶችና ባለሞያዎች ከኮሚቴው ጎን ቆመዋል፡፡ ዳሽን ቢራ ለዝግጅቱ የሚሆነውን ወጭ ለመሸፈን ግንባር ቀደሙን ቦታ የያዘ ሲሆን ሸገር ሬዲዮና ኢ ቢ ኤስ ቴሌቭዥን የዝግጅቱ አጋር በመሆን ማስታወቂያዎችንና የዝግጅቱን መርሐ ግብሮች በነጻ ለማስተላለፍ ወስነዋል፡፡ ኢሊሊ ሆቴል ደግሞ አዳራሹን በነጻ በሚባል ዋጋ በመስጠት ትብብሩን ለግሷል፡፡ የሽልማቱን ምስል ታዋቂው ሰዓሊ እሸቱ ጥሩነህ አዘጋጅተውታል፡፡

መርሐ ግብሩን ለመሳተፍ ለሚፈልጉ 100 የዚህ ጦማር ተከታታዮች ካርድ ተዘጋጅቷል፡፡ ካርዱን ለማግኘት በሚከተለው የኢሜይል አድራሻ ይመዝገቡ፡፡ [email protected] 
ሥራው የሁላችሁንም ጸሎትና እገዛ ይጠይቃል፡፡ 

በአዲስ አበባ እና በሐረር ከተሞች ከ310 ያላነሱ የተወረሱ የቤተ ክርስቲያኒቱ ቪላ ቤቶችና ሕንፃዎች አልተመለሱም፤ ለተመለሱት ቤቶችና ሕንፃዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ለማውጣት የተያዘው ዕቅድ በተሟላ ኹኔታ ተሳክቷል፡፡ ለቤተ ክርስቲያኒቱ የተመለሱት 16 ሕንፃዎች፣ 12 መጋዘኖች፣ 110 ቪላ ቤቶች ዓመታዊ የኪራይ ገቢ ከ23 ሚልዮን ብር በላይ ደርሷል፤ የኪራይ ተመን ማስተካከያ ለማድረግ ጥናት እየተካሔደ ነው፡፡ የኢሕአዴግ ዋና ጽ/ቤትን ጨምሮ …

በ10 ሺዎች የሚቆጠር ህዝብ የተሳተፈበት ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ አዲስ አበባን አጥለቅልቋታል። ስላማዊ ሰልፉን የጠራው በፕሮፌሰር መራራ ጉድና የሚመራው መድረክ ፓርቲ ነው። ሃሳባችንን በነጻነት መግለጽ እንፈልጋለን ! ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታችን ይከበር!!! ተቃውሞ ባሰም የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ እናወግዛለን !!! መድረክ ለኦሮሞ ተማሪዎች ያለውን አጋርነት ይገልጻል !! ቪቫ መድረክ !!! መድረክ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ የተወሰደውን […]

‹‹ቪዛ ይሰጠንና ወደ ሱማሌያ ቢሆንም እንሂድ›› ቤታቸው የፈረሰባቸው በኮልፌ ቀራኒዮ አለም ባንክ አካባቢ ህገ ወጥ የመሬት ወረራ በማድረግ ቤቶችን ሰርታችኋል የተባሉ ዜጎች ቤቶቻቸው በላያቸው ላይ በሀይል ፈርሶ ንብረታቸው መወረሱን አመለከቱ፡፡ ከ15.000 የሚልቁ ነዋሪዎች በሚገኙበት አለም ባንክ አካባቢ ሰዎቹ አነስተኛ መጠለያ ያረፉባቸውን ቤቶች ከገበሬዎች ላይ በመግዛት መኖር ከጀመሩ አመታት መቆጠሩን ያስረዳሉ፡፡ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት ልከውና ወደ ስራ […]

የአንድነት የድጋፍ ማህበር በሰሜን አሜሪካ በቅርቡ የተካሄደውን የንፁሐን ዜጐች ግድያና ማሰቃየት እንዲሁም ዜጎችን አገራችሁ አይደለም ተብለው ከቅያቸው የማፈናቀሉን ተግባራት በእጅጉ ያወግዛል፡፡ የአምቦ እና የተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች አገዛዙ ያወጣውን የአዲስ አበባ ማስተር ኘላን በመቃወም ሠላማዊ ተቃውሞ በማሰማታቸው የአካባቢው ባለስልጣናትና የመንግስት ታጣቂዎች ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል በመጠቀም በንፁሐን ዜጐች ላይ የጦር መሣሪያ በመተኮስ የብዙ […]

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

ወያኔ ለትግራይ ሕዝብ ሀብትንና ብልጽግናን አመጣ ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ወያኔ የሥልጣን ወንበሩ ላይ በመውጣቱ ትግሬዎች ሁሉ አልፎላቸዋል ተብሎ ይታመናል፤ በተለይ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ ላይ የጠነከረ እምነት አላቸው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ ይደረጋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን የተፈራ ርእስ ነው፤ ውስጥ-ውስጡን እንጂ አደባባይ አይወጣም፤ ይህንን ጉዳይ በኢትዮጵያ ውስጥ አደባባይ ለማውጣት ጊዜው የደረሰ ይመስለኛል፤ አረጋዊ በርሄ፣ ገብረ መድኅን አርአያ፣ አስገደ ገብረ ሥላሴ፣ አብርሃ ደስታ (አሥር ቢሞሉልኝ ደስ ይለኝ ነበር!) እየደጋገሙ ቢያነሡትም ሌሎች በቁም-ነገር የተቀበሉት አይመስልም፤ ሕዝቡ ግን በራሱ መንገድ እየተናገረና ምስክርነቱን እየሰጠ ነው፤ በመቀሌ የተሠራውን የመኳንንት መንደር ሕዝቡ አፓርቴይድ ብሎ ሲሰይመው፣ በአዲስ አበባ የተሠራውን መንደር መቀሌ ብሎ ሲሰይመው እየመሰከረ ነው፤ ‹‹የለሁበትም!›› እያለ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ጀነራል አለምሸት፣ በባለቤታቸው ወ/ሮ አንሻ ሰይድ ስም፣ በቅርቡ ያሰሩት ፎቅ፣ ግምሹ በወር 500000 ብር፣ ለአንድ ባንክ፣ ለበርካታ የቻይና ኩባንያዎችና አንድ ሬስቶራንት ተከራየ። በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች እየተጓተቱ ባለበት ወቅት የአገዛዙ ቱባ ባለስልጣናት ግንባታዎቻቸውን በተቀላጠፈ መንገድ ማጠናቀቅ መቻላቸው፣ አገዛዙ ምን ያህል በስልጣን ብልግና የተጨማለቀ መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ።

መግቢያ፤ በጥንቱ ዘመን፤ የአባይ ወንዝ ዋናዋ ምንጭ ኢትዮጵያ መሆኗና ባለቤትነቱዋ ታውቆ፤ የግብጽ መሪዎች በየዓመቱ ለሚጎርፍላቸው ውሀ ይከፍሉ ነበር። ባሁኑ ጊዜ ግን፤ በተለይ ግብጽ የአባይን ወንዝ እንደ ግል ንብረቷ በመቁጠር ኢትዮጵያ በገዛ ወንዟ ለመጠቀም የምታከናውነውን ጥረት መቃወም ብቻ ሳይሆን ማስፈራራትም ይቃጣታል። እንደሚታወቀው፤ ሰሞኑን በየድህረ-ገጹ በስፋት ከሚቀርቡት ሐተታዎች፤ ትችቶችና አስተያየቶች ውስጥ ሰፊ ስፍራ ይዞ የሚገኘው በኢትዮጵያ በመገንባት […]


ያለ በቂ ማስረጃ በሕገ ወጥ መንገድ ከአራት ሳምንት በፊት ከተያዙት ስድስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን በተጨማሪ በአንድ ጦማሪ አባል መኖሪያ ቤት ላይ ፖሊስ 7 ሰዓታት የቆየ ብርበራ አካሄደ፡፡
በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ በዞን ዘጠኝ ጦማሪና መስራች ሶልያና ሽመልስ ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ፖሊስ ብርበራ ያካሄደ ሲሆን የጸረሽብር ሕጉ ይፈቅድልናል የሚል ምክንያት ሰጥተው ያለ ፍርድ ቤት የብረበራ ማዘዣ ከካሜራ ቀራጭ ጋር የተገኙት ሰባት ፖሊሶች በጦማሪዋ ክፍል እና ሌሎች አስፈላጊ ነው ባሉዋቸው ክፍሎች ሲያካሂዱ ነበረውን ብርበራ ጨርሰው ይጠቅመናል ያሉትን የዶ/ መረራ ጉዲና የመጨረሻ መጽሀፍ እና ሌሎች ወረቀቶች ወስደው ቤት ውስጥ የነበሩትን የጦማሪዋን ወላጅ እናት አስፈርመው ከጠዋቱ 4 ሰአት አካባቢ ቤቱን ለቀው ወጥተው ነበር፡፡ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ተመልሰው በመምጣት ተጨማሪ ፍተሻ በዋናው መኖሪያ ቤት መካሄድ እንፈልጋለን ብለው ሁለተኛ ዙር ብርበራ በምግብ ማብሰያ ክፍል ውስጥ እናካሂዳከን በሚል ሰበብ ትንሹ ክፍል ውስጥ የጦማሪዋን እናት እነዲወጡ በማግለል ከማቀዝቀዛውን አንቀሳቅሰው አፍታም ሳይቆዩ 19 ገጽ የግንቦት ሰባት ፕሮግራም አግኝቻለሁ ሲል አንዱ ፈታሽ ተናግሯል፡።
የጦማሪዋን ወላጅ እናት እነዲፈርሙ ያግባቡ ቢሆንም ወላጅ እናትዋ ከክፍሏ እና ሌላም ቦታ በመፈተሽ ስታገኙ ያየሁት ወረቀት ላይ ፈርሜያለሁ ይህ ግን ምግብ ማብሰያ ክፍል ውስጥ ያልነበረ እና እዚህ ያልተገኘ ሌላ ወረቀት ነው ሲገኝም አላየሁም በማለት አልፈርምም ብለዋቸዋል፡፡ በመሆኑም ፈታሾች ተጨማሪ የሰው ሃይል ደውለው በማስጠራት ለማግባባት ቢሞክሩም ስላልተሳካላቸው ይዘዋቸው የመጡትን የራሳቸውን ሁለት ምስክሮች ብቻ አስፈርመው ባለቤትዋ ለመፈረም ፍቃደኛ አይደሉም ብለው ቤቱን ለቀው ሄደዋል፡፡ ከፓሊስ ጋር የመጡት ምስክሮች አንደኛው አድራሻቸው በብርበራ ምስክርነት ዶክመንቱ ላይ ያልተጻፈ መሆኑንም ለመረዳት ችለናል ፡፡
በብርበራው ወቅት በነበራቸው 7 ሰአት ቆይታ የጦማሪዋን መጸሃፍት የጉዞ ትኬቶች የስልጠና ማንዋል እና የመሳሰሉትን ጥቃቅን ወረቀቶች የወሰዱ ሲሆን ማብሰያ ክፍል ከፍሪጅ ጀርባ አገኘነው ካሉት ወረቀት ግን ቤት ውስጥ ያልነበረና ፓሊሶች ራሳቸው ያመጡት በመሆኑ እናትዋ ተናግረዋል፡፡
የዞን ዘጠኝ ጦማሪ አባላት ከየትኛውም በፓርላማ በአሸባሪነት ከተፈረጀ የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆኑና ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው እነዲሁም አነዚህ ድርጅቶች ላይ በተለያየ አጋጣሚ ትችቶቻቸውን ሲያቀርቡና ሲቃወሙ የሚታወቁ ቢሆንም ሲሆን በተያዙት አባሎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው አስገድዶ ለሃሰተኛ መረጃ እንዲፈርሙ የማድረግ ተግባር ሳያንስ ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር ለማያያዝ ማስረጃን እንደተገኘ አድርጎ የማቅረቡ ተግባር መንግሰት ይታማበት የነበረውን የፓለቲካ ውንጀላን በሽብር የመቀየር ክስ በተግባር እንድናይ ያስቻለን ነው ፡።
በመሆኑም አሁንም ቢሆነ ጦማሪ ጓደኞቻችን ሃሳባቸውን በነጻነት ከመግለጻቸው ውጪ ምንም አይነት የወንጀልም ሆነ ሽብር ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው እያስታወስን መንግስት ያሰራቸውን ጦማርያን እና ጋዜጠኞች አንዲፈታ አሁንም አንጠይቃለን፡፡

በድጋሚ ሽብር፣ በድጋሚ ግድያ፤ ናይጀሪያ ውስጥ የተከሰተው ፍንዳታ በሙስሊሞች እና ክርስቲያኖች መካከል ያለውን ግንኙነት እንዲበላሽ እያደረገው ነው ተብሏል። በርካታ ናይጄሪያውያን መንግሥት በአፋጣኝ ከቦኮ ሐራም ጋር መነጋገር ያስፈልገዋል ሲሉ ተደምጠዋል።

ሱዳን በምሥራቅ ከምትዋሰናቸው ጎረቤቶቿ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጋር ግንኙነቷን ለማመጣጠን እየጣረች መሆኑ ተገለጠ። የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ዖመር ኧል በሽር የኤርትራ መዲና አስመራን በጎበኙ በጥቂት ወራት ውስጥ የኤርትራው አቻቸው ኢሳያስ አፈወርቂ ከሁለት ሣምንታት በፊት ሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ተገኝተው ተነጋግረዋል።

በደቡብ ሱዳን የኢጋድ አጣሪና ተቆጣጣሪ ቢሮ የበላይ ሐላፊ አምባሳደር ተፈራ ሻዉል እንዳሉት የኦስሎዉ ጉባኤ ከሠብአዊ ርዳታ በተጨማሪ የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ሐይላት የተፈራረሙትን የሠላም ዉል ገቢር እንዲያደርጉ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ግፊት ያደረገበትም ነበር

«በአገራችን ኢትዮጵያ የደራስያን፤ የሙዚቀኞች ማኅበር ከተቋቋመ እጅግ ረጅም ግዜ ቢሆንም እስከ ዛሬ ሰዓልያን እና ቀራፅያን ማኅበር አቋቁመዉ ልምዶቻቸዉን ሲለዋወጡ ባለማየታችን፤ ይህን ማህበር አቋቋምን» ያለን ወጣት ሰዓሊ የዛሬዉ የወጣቶች ዓለም ዝግጅታችን እንግዳ ነዉ።

ኑና አብረን ድምጻችንን እናሰማ!! የአንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የመሀል ቀጠና ፅ/ቤት ለግንቦት 10 ጠይቆትየነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በገዢው ፓርቲ የተለያዩ ሰበቦችና ምክንያቶች ሲድበሰበስ ከርሞ ለሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም መተላለፉን የመሀል ቀጠና ጽ/ቤቱ በጠራው የአስቸኳይ ስብሰባ መወሰኑንናይህንኑ ውሳኔውንም በቀን መወሰኛ ደብዳቤው ላይ ገልጾ ለአዳማ መስተዳድር ከንቲባ አቶ አብረሐም ማስረከቡን በመረጃ አያይዞ ገልጧል፡፡በመሆኑም ሰኔ አንድ የአንድነት […]

አረና ትግራይ ለሉአላዊነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ በዛሬው ዕለት በሀውዜን ከተማ ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ሕዝባዊ ስብሰባ ለማድረግ በዝግጅት ላይ እንዳለ ከመቀሌ የመጡ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ደርሰው እኛ ሰላማዊ ሰልፍ ስለምናደርግ ስብሰባ የሚባል ነገር የለም በማለት ወደ አዳራሹ የሚመጣውን ሰው ድንጋይ በመወርወር ስብሰባው እንዳይካሄድ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ስብሰባውን እንዲታደም ሲቀሰቅሱ የነበሩ አንድ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና ሁለት አባላት ታርጋ በሌላቸው ሞተር […]

ከጸጋዬ ገብረመድኅን አርአያ

ወያኔዎች አዲስ አበባን ከተቆጣጠሩ በኋላ የነበሩትን ዕለታት ክንውኖች በሥርዓት የመመዝገብ ልምድ ያለው ሰው የሚያሰፍራቸው ልዩ ልዩ ሁኔታዎች ይኖሩታል። ከመጀመሪያው ዕለት አንስቶ። የእኔን የመጀመሪያ ዕለት አጭር ማስታወሻ ልንገራችሁ። በማለዳ ተነስቼ ጋቢዬን አጣፍቼ ከበሬ ላይ ቆሜ ሥፍር ቁጥር የሌላቸው አህዮች ወደ መሐል ከተማው (አዲስ አበባ) ሲጓዙ አያለሁ። ያንኑ ያህል ባራባሶ ጫማ የተጫሙ፣ የአካል ዝለት የሚታይባቸውና ከእህል ጋር ከተለያዩ አያል ቀን የሆናቸው የሚመስሉ “ሰብአዊ ፍጥረቶች” አብረዋቸው ይሮጣሉ። ሲያሳዝኑ! ቆይ ቆይ…ከፓስተር ኢንስቲቱት በር ላይ አንድ ጥይት ተተኰሰ። ሌላ ጥይት- ሌላ ጥይት! ሰዎቹ ካለፉ በኋላ ወጣ ብለን ያየነው ሟች በሰፈሩ እንደ ሕሊና ሕመምተኛ የሚታወቅ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነቢዩ ሲራክ

በለጋ እድሜዋ ትዳር መስርታ ሁለት ትጉህ መንታ ልጆች የታደለች እህት ከትዳር ጓደኛዋ ችግር ገጠማት። የ “ተበዳይ ነኝ!” ባይ ወዳጀን ምሬት ደጋግሜ ብሰማም ከቀናት በፊት “በደለኝ!” ያለችው የትዳር አጋሯ በኮሚኒቲው ሽምግልና ኮሚቴ በኩል ክስ መስራቱን እና የክስ ጥሪ እንደደረሳት ሰማሁ። ከአሰር አመት በፊት እድሜዋ ገና የ17 አመት እያለ የዛሬ የ12 አመት እድሜ የሆነውን ትልቁን ልጀን ያሳደገችውን እህት የቆየ አብሮነት ትውስታ እያሰብኩ የአለመግባባቱን ሽምግልና ወደሚከወንበት የጅዳ ኮሚኒቲ ሽምግልናውን ለመታዘብ መጓዝ ጀመርኩ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ባለፉት ሳምንታት ለ 59ኛ ግዜ የተካሄደዉ፤ የአዉሮጳ ሀገሮች የሙዚቃ ዉድድር መድረክ፤ ደማቅ በሆነ የሙዚቃ ዉድድር የኦስትርያዉ ከያኒ 290 ነጥብን በማግኘት፤ እስከ ዛሪ በዉድድሩ ከተመዘገቡ የአሸናፊነት ነጥብ በአብላጫነት፤ የአራተኛ ደረጃን መያዙ ተነግሮለታል።

የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ስራ አስፈጻሚ አባልና የወጣቶች ጉዳይ ሰብሳቢ አቶ ስንታየሁ ቸኮል ትናንት ለምሳ ወደ መኖሪያ ቤቱ ሲያቀና ማንነታቸውን ባልለያቸው ሰዎች በድንጋይ መፈንከቱ ታውቋል፡፡ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ኳስ ሜዳ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 8፡00 እንደደረሰ ሁለት ሰዎች ወደ እርሱ በመቅረብ ምንም ሳያነጋግሩት በድንጋይ ፈንክተውት መሰወራቸውን አቶ ስንታየሁ ለፍኖተ […]

በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ሰብሳቢነት የተመራው ኮሚቴ በ80 አንቀጾችና በ99 ገጾች አዘጋጅቶ ያቀረበው የ፲፱፻፺፩ ዓ.ም. ሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ ረቂቅ የተጠናቀቀው፣ ምልዓተ ጉባኤው በሰጠው አስተያየትና ባደረገው ማስተካከያ መሠረት ከአርቃቂ ኮሚቴው ጋራ ሠርቶና አሟልቶ ለቀጣዩ ስብሰባ የሚያደርስ የሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና የሕግ ምሁራን ኮሚቴ በማቋቋም ነው፡፡ *** የፓትርያርክ እንደራሴ ምደባ እንዳስፈላጊነቱ ሲሠራበት የቆየ መኾኑን በመጥቀስና ለወደፊቱም …

ከሰሞኑ ወያኔ መራሹ የአዲስ አበባ አስተዳደር ያወጣው አዲስ አበባ ዙርያ የኦሮሚያ ዞን ያካተተ ማስተር ፕላን እና የእዝ አስተዳደር ተግባራዊነትን በመቃወም በብዙዎች የኦሮሚያ ክልል ተወላጆችና ሃገር ወዳዶች ሰፊ ህዝባዊ የመብት ማስከበር ንቅናቄ ተቀስቅሶ በመንግስት ቅጥ ያጣ ግድያና እስር ለጊዜው ጋብ ቢልም አሁንም ቢሆን በህዝቡ ውስጥ ሞልቶ ሊገነፍል የደረሰ ቁጣ አለ፡፡ በሌላ በኩል በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ለረጅም ጊዜ […]

መግቢያ፤ በጥንቱ ዘመን፤ የአባይ ወንዝ ዋናዋ ምንጭ ኢትዮጵያ መሆኗና ባለቤትነቱዋ ታውቆ፤ የግብጽ መሪዎች በየዓመቱ ለሚጎርፍላቸው ውሀ ይከፍሉ ነበር። ባሁኑ ጊዜ ግን፤ በተለይ ግብጽ የአባይን ወንዝ እንደ ግል ንብረቷ በመቁጠር ኢትዮጵያ በገዛ ወንዟ ለመጠቀም የምታከናውነውን ጥረት መቃወም ብቻ ሳይሆን ማስፈራራትም ይቃጣታል። እንደሚታወቀው፤ ሰሞኑን በየድህረ-ገጹ በስፋት ከሚቀርቡት ሐተታዎች፤ ትችቶችና አስተያየቶች ውስጥ ሰፊ ስፍራ ይዞ የሚገኘው በኢትዮጵያ በመገንባት […]

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ህዳር 29 ቀን 2006 ዓ.ም ለማድረግ ያሳወቀው ሰልፍ ተከለከለ፡፡ መድረክ ሰልፉን ለመጥራት በሀገራችን መሰረታዊና ወቅታዊ የሆኑ ችግሮችን እንዲሁም በሳውዲና በአለም ዙሪያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው ሰቆቃ መሰረቱ የስደት መንስኤው ላይ በመሆኑ፣ መንግስትን በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ እንደነበር ለማወቅ ችለናል፡፡ ሰልፉን ለማድረግ የታቀደው ስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ አምስተኛ በር ፊት ለፊት ከሚገኘው የመድረክ […]

ኢትዮጵያ የደቡብ ሰዳን ግጭት ከተጀመረ ካለፈው ታኅሣስ ወዲህ ባለፈው ጊዜ ውስፋ 130 ሺህ ደቡብ ሱዳናዊያን ስደተኞችን መቀበሏንና እስከ ያዝነው የአውሮፓ ዓመት መጨረሻ በሚቀሩት ሰባት ወራት ውስጥ ይህ ቁጥር እስከ 350 ሺህ ሊደርስ ይችላል ብሎ እንደሚጠብቅ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ የሚገኙት የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር – የዩኤንኤችሲአር የኢትዮጵያ ቢሮ ቃል አቀባይ አቶ ክሱት ገብረእግዚአብሔር ለቪኦኤ በሰጡት ቃል በአሁኑ ጊዜ በቀን ከ800 እስከ 1000 ስደተኛ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
 

ኢትዮጵያ ውስጥ በሁሉም ድንበሮቿ አቅራቢያ ባሉ የስደተኞች መጠለያዎች ውስጥ ከ550 ሺህ በላይ ከሶማሊያ፣ ከኤርትራ፣ ከሱዳንና ከኬንያ የገቡ ስደተኞች መኖራቸውን አቶ ክሱት አመልክተው ከግማሽ…

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በአሁኑ ዘመን ፤ በኢንዱስትሪ እጅግ ደርጅተው የሚገኙ ሃገራት እዚህ ደረጃ ለመድረስ የበቁት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ምርምር አማካኝነት ሳይንስንና ቴክኖሎጂን የሙጥኝ በማለት እንደሆነ የሚያጠያይቅ አይደለም። ከምዕራባውያኑ ሃገራት መካከል የኢንዱስትሪው

በጥቁር ዐባይ ወንዟ ላይ ኢትዮጵያ ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በመገንባት ያለችውን ግዙፍ ግድብ ጉዳይ በተመለከተ ለመነጋገር ፣የግብፅ ው ጭ ጉዳይ ሚንስትር ነቢል ፋኼሚ ወደ አዲስ አበባ ሳይጓዙ እንደማይቀሩ ታዋቂው የመንግሥት ጋዜጣ ኧል አህራም

አፍሪቃ፣ የዐረቡ ዓለም እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት እያጠናከሩት ያሉትን የንግድ ምክር ቤት ወደ አንድ የንግድ ቀጣና ለማሳደግ በሚያስችላቸው ዘዴ ላይ ከጥቂት ጊዜ በፊት ተስማምተዋል። የዛሬው የከኤኮኖሚው ዓለም ዝግጅት ትኩረት ምክር ቤቱ በሁለቱ ቡድኖች መካከል ያለውን የንግድ ግንኙነት በማሳደጉ ላይ በያዘው ሚና ላይ አድርጓል።