የጀርመንና የቻይና ልዩ ግንኙነት

የጀርመን መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል በያዝነዉ ሳምንት መጨረሻ ቻይናን ይጎበኛሉ። ሜርክል የጀርመን ከፍተኛ የንግድና ባንክ ባለስልጣናትን አስከትለዉ ለአራት ቀናት በቻይና በሚያደርጉት ጉብኝት ከፕሬዝደንት ሺ ቺ ፒንግና ከጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪጂንግ ጋ ይነጋገራሉ።