Tag: News in Amharic
" ህልም አንደሆነ አይታሰርም " ጦማሪ አቤል ዋበላ
Commit to the paper the suffering in that dark chamberAnnounce to the world all the unbearable torture
በአዲስ አበባ በኑር (በኒ) መስጅድ ህዝበ ሙስሊሙ ድንገተኛ ተቃውሞ በማድረግ አስገራሚ ተቃውሞውን ገልጽዋል (photos and video)

የተለያዩ መፈክሮችን የያዙ ፊኛዎች ወደ ተውለብለበዋል :: ፊኛዎቹ የተለያዩ መፈክሮች የተጻፈባቸው ሲሆን ከነዚህም መካከል : – ትግሉ ይቀጥላል ፍትህ ነጥፏል ፤ሂጃብ መለያችን፤ኒቃብ ውበታችን ፤ትግላችን ቀጥሏል
ፍትህን ማዘግየት ፍትህን መንፈግ ነው ፤ትግላችን እንደቀጠለ ነው ::
ፍትህ ፍትህ ፍትህ ;We Need Justice ፤Hijab Is Beauty ፤ justice Is Denied የሚሉት መፈክሮች ይገኙበታል፡፡ በርካታ ፊኛዎች የተውለበለቡና ወደ ሰማይ የተለቀቁ ሲሆን ተቃውሞው በከፍተኛ ድምቀት ተከናውኗል፡፡ መንግስት በሴኩላሪዝም ሽፋን እየፈጸመ ያለውን የሂጃብ ገፈፋ የሚያወግዝ ሲሆን በተጨማሪም በህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ እጸፈጸመ ያለውን የፍትህ መዛባት ፤ በማረሚያ ቤቱ የሚፈጸሙ ግፎችን ለማውገዝ ነው፡፡ መንግስት ሙሉ በሙሉ ተቋሞውን በሃይል አስቁሚያለሁ ሲል የነበረ ሲሆን ህዝበ ሙስሊሙ ግን ድንገተኛ ተቃውሞ በማድረግ አስገራሚ ተቃውሞውን ገልጽዋል፡፡
የባህር ዳር ህዝብ አደባባይ ወጣ፤ ባህር ዳር በህዝባዊ ጥያቄዎች እየተናጠች ነው::
የባህዳር ነዋሪ በነቂስ በመውጣት በክልሉ ም/ቤት ፊት ለፊትና በአዲሱ ም/ቤት(ቀበሌ 10) መስቀል አደባባይ የቤተክርስያን የታቦት ማደሪያ ፣ ንብረትነቱም የቤተ-ክርስቲያን ነው ልትነጠቅ ወይም መንግስት እንደሚለው ለባለሀብት ሊሰጥ አይገባም በማለት ቁጣቸውን በማሰማት ላይ ናቸው፡፡ የባጃጅ ሾፌሮችም በየቦታው ትላክስና ጩኸት እያሰሙ ነው፡፡ የመስቀል አደባባይን መፍረስ በመቃወም በባህርዳር ከተማ የነበረው ሰልፍ ጥያቄውን አሰምቷል:: ሆኖም በአሁኑ ሰዓት በባህርዳር ከተማ በሕዝበ […]
Letter to the former ETV ይድረስ ለቀድሞው ኢቲቪ – የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ ያለው ማን ነበር?
ለሶደሬ
ሰሞኑን አዲስ ስያሜ ይዘህ የወደፊት መለያዮን/ፈረንጆች ሎጎ ይሉታል/ ስሩልኝ፤ የጣቢዬንም መርህ /ሞቶ/ ሰይሙልኝ ብለህ ያስነገርከውን ማስታወቂያ ተመልክተናል፡፡ እርግጥ ነው ገና ስያሜህን ቀይረህ በኢቲቪ መስኮት ብቅ ባልክበት ሰሞን አንድ ጦማር በዚሁ ገፅ ላይ መፃፋችንን…
ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ስርአት መገለጫ ብቻ ሳይሆን የሰላማዊ ትግል ስልት አካል ጭምር ነው! – Dave Teshome
ምርጫ በአንባገነን መንግስት ውስጥ? ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ስርአት መገለጫ የሚሆነው ነጻ፣ ፍትሃዊና ተወዳዳሪ (free, fair and contested) ባህሪያትን የተላበሰ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ በኢ-ዴሞክራሲዊ መንግስት ውስጥ የሚደረጉ ምርጫዎች በምንም መመዘኛ የዴሞክራሲ ስርዓት መገለጫዎች አይሆኑም፡፡ በሀገራችን በአጼው፣ በደርግ እና በኢህአዴግ ዘመነ-መንግስታት ተደርገው የነበሩ ምርጫዎች የአጼውን፣ የደርጉንና የኢህአዴግን የአገዛዝ ስርዓቶች የስልጣን ዘመን ለማራዛም የተደረጉ (“mechanism of regime maintenance”) ምርጫዎች […]
የሜሮን ጌትነት ግጥምና ውዝግቡ
ቁም ነገር መፅሔት ቁጥር 193 ታህሣስ 2007
ለሶደሬ
ስለ ሜሮን ጌትነት ግጥምና ውዝግቡ
መቼም ሰሞኑን በማህበራዊ ድረ ገፆች ላይ ህዝቡ እየተቀባበለው ያለውን ‹አትሂድ› የሚለውን የሜሮን ጌትነት ግጥም አልሰማሁም አትለኝም? ወር በገባ በመጀመሪያው ረቡዕ በራስ ሆቴል በሚቀርበው የግጥም ምሽት ላይ ያቀረበችው ግጥም የመንግስት ደጋፊና ተቃዋሚዎችን የጦፈ ውዝግብ…
ልዩነትን በማቻቻል በጋራ መታገል ችላ የማይባል ሃገራዊ አጀንዳ ነው።
Minilik Salsawi – ባሳለፍነው የትግል አመታት ውስጥ የተቃዋሚዎች እርስ በ እርስ መፈራረጅ መወነጃጀል መናናቅ ለስልጣን ጥመኝነት መሮጥ እንዲሁም ለስም እና ለዝና መትጋት ያለመደማመጥ እና ያለመከባበር ፖለቲካ ተቀራርቦ ያለመነጋገር እና ያለመመካከር ፖለቲካ ሃገራኢ ሆደሰፊነት እና መቻቻልን ያላዘለ ፖለቲካ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተረፈው ነገር ቢኖር ከጭቆን ወደ ጭቆና ማቅ ውስጥ ከመዘፈቅ ውጪ ምንም የናፈቀውን የነጻነት አየር እንዲተነፍስ አላደረግነውም። የተቃዋሚ ሃይሎች ጥንካሬ እንዲጎለብት በየድርጅቱ ውስጥ ያሉትን እንከኖች በማጥራት በጋራ እና በተመቻቸ የሃሳብ መግባባት ተቻችሉ እና ተግባብቶ የትግል ስትራቴጂን ግብ ለማድረስ ለአንድ ወጥ ህዝባዊ እና ሃገራዊ አጀንዳ ተግቶ መስራት ይጠበቅብናል።
ወያኔ የተቃዋሚዎችን እና የለውጥ ሃይሎችን እርስ በእርስ መፈነካከት በማየት አርጩሜውን ተስፋ በሚጣልባቸው ግለሰቦች እና ፓርቲዎች ላይ እያወናጨፈ ባለበት እንዲሁም የውስጥ አሰራራቸውን በመሰለል በትግሉ ውስጥ ያላቸውን ሚና እንዲኮላሽ በመስራት የውስጥ ድክመቶቻቸውን በመጠቀም እርስ በርስ እንዲፋጁ እና ተቃዋሚዎች እንዲከስሙ ጥንካሪያቸውን እንዳያገኙ ሲሰራ ይህንን እንዴት አድርገን በማሻሻል የወያኔን ሴራ ማክሸፍ አለብን የሚል አመኔታ የሚያስገኝ ሕዝባዊ ስራዎችን በመስራት ጥንካሬን ማግነት እንዲሁም ሕዝባዊ ድጋፎችን ማግኘት ግድ የሚልበት ጊዜ ላይ መሆናቸውን ተቃዋሚዎች ሊያውቁት ይገባል::ተቃዋሚዎች ካለፈው ድክመቶቻችን ተምረን ከዘለፋ እና ከስድብ እንዲሁም ከመፈራረጅ የሴራ ፖለቲካ በመውጣት ጥንካሬዎቻችንን የምናሳይበት ለውጥ የምናመጣበት አመት እንዲሆን በጋራ ጠንክረን መስራት አለብን።አንድነት ሃይል ነው የሚለው ብሂል ለሃገራዊ አጀንዳ መተግበር ትልቅ አስታውጾ አለው::ከኛ በላይ ላሳር ከኛ በላይ አዋቂ የለም የሚል አመለካከት ይዞ ከመክነፍ የህዝብን ጥያቄ መሰረት አድርጎ ተቀራርቦ በመነጋገር እና በመወያየት ሃገራጂ ማኒፌስቶ በማምጣት የጋራ ሃገራዊ አጀንዳ በመቅረጽ ለለውጥ መትጋት ግዴታ ነው::
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ይህ ሳይታለም የተፈታ እና የሁሉም የነጻነት ፈላጊ ሃይሎች ጥያቄ ነው። በሃገር ውስጥ ያሉትን ፓርቲዎች መዋቅሮቻቸውን በማጠናከር የውስጥ ድክመቶቻቸውን በመቅረፍ እንዲጠነክሩ የማድረግ ግዴታ ከለውጥ ፈላጊ ሃይሎች ይጠበቃል። መመካከር መተራረም ግድ ይላል። በውጪው አለም የሚገኙ የነጻነት እና የለውጥ ሃይሎች እንዲጠናከሩ እና ከጥልፍልፎሽ ፖለቲካ ወተው ጠንካራ ሃይል እንዲሆኑ የዲያስፖራው ሃይል ከበፊቱ በበለጠ መልኩ ሊሰራ ግድ ይለዋል። የወያኔ የጎን ውጋት እና የራስ ምታት የሆነው ዲያስፖራው የጀመረውን የትግል ስልት እና ትጋት በማስፋት ሚዲያዎችን በማጠናከር እና የነጻ አውጪ ፓርቲዎችን በመርዳት በማግባባት ጠንካራ ሰንሰለት ከሃገር ቤት ጋር በመፍጠር ሕዝብን ከጨቋኞች ነጻ ማውጣት አለበት።ዲያስፖራው በየቀኑ ወያኔ የሚፈጥረውን ተራ የቤት ስራ እና የማደናገሪያ ማዘናጊያ አሉባልታ ፊት ሳይሰጠው በለውጡ ጉዳይ ላይ በማተኮር በሃገር ቤት ያለው ሃይል እንዲስማማ የፖለቲካ ጡዘቶች ክፍተት እንዳይኖር ተቀራርቦ እንዲሰራ ትልቁን ሚና መጫወት አለበት::
የሚዲያ ተቋማት እና የድህረገጽ ውጤቶች ሕዝብን በማስተማር ሕዝብን መብቱን እና ነጻነቱን አውቆ ለሌላው እንዲያስተምር በማድረግ ረገድ አስፈላጊውን ወቅታዊ መረጃ እና መነሳሳትን በማስረጽ ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል። ያለፉ እና የከሰሙ ወሬዎችን እና አሉባልታዎችን ከመርጨት የወያኔ የፈጠራ አደናባሪ እና አዘናጊ አጀንዳዎችን እኝኝ በማለት ከማውራት ብሄር ተኮር ክፋፋይ ሃሳቦችን ከማርከፍከፍ አዛኝ መሳይ መርዝ ሃሳቦችን ከመናገር ተቆጥበን ሕዝቡን ስለመብቱ እና ነጻነቱን በማስተማር ረገድ መትጋት ከተያዘ ለውጥ የማይመጣበት ምንም ምክንያት የለም። ትችትን እና ሂስን ላለመዋጥ እውነትን ላለመቀበል የሚደረጉ ሩጫዎች ታጥቦ ጭቃ እንጂ የትም እንደማያደርሱ እንዲሁም ፓርቲዎችን እና ሰዎችን መፈረጅ እና መወንጀል ሃሳቦችን ማጣጣል ምንም ለውጥ እንደማያመጣ ካለፈው ተምረናል ። ያሳልፍነው የትግል ሂደት ከጭብጨባ እና ስብሰባ ያለፈ ፋይዳ እንዳሌለው ተገንዝበን የወሬ እና ሆይሆይ ትግል ስለማያዋጣ ጥንካሬን እና ለውጥን የምናመጣበትን የትግል ስልት በመመካከር እና በመወያየት ሃሳብን በማቻቻል መረጃ በመለዋወጥ ሃገራዊ የጋራ አጀንዳ ሊኖረን ይገባል እላለሁ።
አምር ኢብን ኣስ እና “ፉስጣጥ” (ክፍል አንድ)
![]() |
| Mosque of Amr in Old Cairo in 19th Century |
አምር ግብጽን በሚያስተዳድርበት ጊዜ በክርስትያኖቹ ላይ ይደርስ የነበረውን ጭቆና ሙሉ በሙሉ አስወግዷል፡፡ በህዝቡ ላይ በየምክንያቱ ይጣሉ የነበሩትን ልዩ ልዩ የታክስ ዓይነቶች በማስቀረት ሁሉም ዜጎች ዓመታዊውን “ዑሽር” (አስራት) እና “ዘካት” ብቻ እንዲከፍሉ አድርጓል፡፡ በመንግሥቱ ቢሮክራሲ ውስጥም ክርስትያኖቹን አሳትፏል፡፡ የቤተ-ክርስቲያኖች ይዞታ የሆኑ መሬቶችና ንብረቶች እንዲከበሩም አድርጓል፡፡
የኃይለማርያም ‘የወራቤ ንግግር’ ለያዙት ሥልጣን ደቂቅነታቸውን አጋለጠ፤ የሔርሜላ ምስክርነት በከፍያለው ግ/መድህን
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ፣ ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ በስንት ውጣ ውረድ ያገኙትን ሥልጣን ጥርሳቸውን ነክሰው ከያዙ ሁለት ዓመት ከሁለት ወርና 26 ቀን አስቆጥረዋል። በእነዚህ ወራት ውስጥም፡ ኃይለማርያም ሥልጣን የረገጡ ቀን ስለራሳቸው ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሰጡት ምስክርነትና ግምት ከዛሬው ኃይለማርያም በአያሌው የተለያዩ ናቸው። ገና መጀመሪያ ላይ ከመለስ ጀርባ ከጦር አዝማችነታቸው ወጥተው (በካድሬነታቸው) በሙቱ ማግሥት የሥልጣንን በር ሲይንኳኩ፣ […]
በእውቀት ላይ የተመሰረተ እንጂ የስሜት ፖለቲካ አያዋጣንም – ናኦሚን በጋሻው
ከ250 አመታት በፊት ፣ 13 ኮሎኒዎች፣ ተብለው የሚታወቁት የአሜሪካ ግዛቶች በእንግሊዝ ሥር ነበሩ። አሜሪካኖቹ የግብር ጫና ስለበዛባቸው ለነጻነት መታገል ጀመሩ። በአሜሪካኖች እና በእንግሊዞች መካከል ጦርነት ተጀመረ። የአሜሪካኖች መሪ ጀነራል ጆርጅ ዋሺንግተን ነበሩ። እንግሊዞች ብዙ ጦር አሰልፈው ያመጹ አሜሪካዉያንን ለማስገበር ተንቀሳቀሱ። በኑዮርክ አሜሪካኖች ትልቅ ሽንፈት ደረሰባቸው። የእንግሊዝን ጦር መቋቋም አልቻሉም። ጆርጅ ዋሽንግተን፣ በሌሊትና በጉም ወደ 9 […]
የህንድ ፊልም ትዝታ
ሶኒ፤ አሜሪካና ሰሜን ኮሪያ – ዲሴምበር 19, 2014
Sony, US, North Korea
ባካባቢ ጉዳይ የመንግሥት ባለሥልጣናት እንዲጠየቁ ተጠየቀ – ዲሴምበር 19, 2014
COP20, Lima, Kerry
2014 አም ለፍልሰት የከፋ አመት እንደነበር ተገለጸ
IOM በሚል አህጽሮት የሚታወቀው አለም አቀፍ የፍልሰት ድርጅት በያዝነው ወር የሚያበቃው 2014 አም ግጭትን፣ የፖለቶካ ወከባንና የኢኮኖሚ ችግርን በመሸሽ ለሚሰደዱት ሰዎች አደገኛ አመት ሆኖ እንደቆየ አስታውቋል።
በከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ የተገዙ የማምረቻ መሳሪያዎች በኤሌክትሪክ ሃይል ችግር ከአገልግሎት ውጭ እየሆኑ ነው ሲሉ ሚኒስትር አለማየሁ ገለጹ
ታኀሳስ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የውሃ፣ የመስኖና የኢነርጂ ሚኒስትር አለማየሁ ተገኑ ህዳር 26 ቀን 2007፣ በቁጥር ውመአሚ 1/01/67 በጻፉት ደብዳቤ ” በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች በከፍተኛ ወጪ ተገንብተው ለበርካታ ኢንተርፕራይዞች የመስሪያና መሸጫ አገልግሎት የሚውሉ ህንጻዎችና ሼዶች በኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት ችግር ምክንያት ለታለመላቸው አላማ ለማዋል ” አልተቻለም ብለዋል። “በእነዚህ ማእከላት ውስጥም በከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ የገቡና …
በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው የተከሰሱት በድጋሜ ተቀጠሩ
ታኀሳስ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት ቤት ቢቀርቡም ሌላ ቀጠሮ እንደተሰጣቸው ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ …
ንግድ ባንክ ከባንክ ውጭ የሚደረግ የገንዘብ ሽግግርን ለማስቀረት በውጭ አገራት ቅርንጫፍ ባንኮችን ሊከፍት መሆኑን አስታወቀ
ታኀሳስ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባንኩ እንደሚለው በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚኖሩባቸው አገሮች ቅርንጫፎችን በመክፈት በአመት እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚሆነውን፣ ከባንክ ውጭ የሚደረገውን ገንዘብ የማስተላለፍ ዘዴ ለመቆጣጠር አስቧል። አሜሪካ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስና ሳውድ አረቢያ በመጀመሪያው ዙር የንግድ ባንኮች ቅርንጫፎች ከሚከፈትባቸው አገራት ተርታ ተመድበዋል። ባንኮቹ መከፈታቸው ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የሚልኩትን ገንዘብ ለመጨመር እንደሚረዳም …
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 18, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
“ካላገዝከን ወዮልኽ!” ብሎ ትግል የለም
የፖለቲካ እንቅስቃሴ፣ ሰላማዊም የትጥቅም፣ በባህሪው ትብብርን ይጠይቃል። ሕብረተሰብ በማሳትፍ የሚደረግ የትብብር ሥራ ነውና። የኢትዮጵያ ገዥ ጥምር ድርጅት አንድ አካል የኾነው ህወሓት የፈር ቀዳጅነት ሚናውን ወስዶ የዛሬ አርባ ዓመት በትግራይ በረኻዎች የትጥቅ ትግል ጀምሮ በሚያካሂድበት ጊዜ፣ “ተወዲቡ ብጽንዓት ዝተቓለሰ ይዕወት” (ሲተረጎም፣ ተደራጅቶ በጽናት የታገለ ለድል ይበቃል) የሚል መፎክር ከአነገባቸው መፎክሮች አንዱ ነበር። በነገራችን ላይ የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም ኢህአዴግ እንደ መንግስት ሀገር ሲመራ የተከተለው ህዝብን አደራጅቶ እና አስትፎ የመስራት ባህልም ከዚኽ መፎክር የተወረሰ ሳይኾን አይቀርም። ለዚህም ነው ኢህአዴግ ነጥሮ በመውጣት በትጥቅ ትግሉም ሀገር በመምራቱም ወቅት ውጤታማ ሊኾን የበቃው። አሁን በፖለቲካው ተደራጅተው ሳይደራጁም እየተንቀሳቀሱ ያሉ የተቃውሞ፣ ሕጋዊ የኾኑትም ያልኾኑትም በዋናነት የዚኽ የተባብሮ መስራት ድክመት ስላለባቸው ነው ለውጤት ያልበቁት። ሲጣመሩ፣ ሲቀናጁም ኾነ ሲያብሩ፣ የአብሮ መስራት ምክንያታቸው የመላው ህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ በፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና ፖለቲካዊ ፕሮግራም ነጥሮ የወጣ ፖለቲካዊ አቋም ይዘው መስዋእት ለመክፈል ተዘጋጅተው ሳይኾን በጥላቻ እና የስልጣን ጥም ብቻ መሰረት አድርገው ነው ወደ አንድ የሚሰባሰቡት። በዚኽ አካሔድ ደግሞ ጠብ የሚለ ውጤት አላገኙም። በተለይ ለመስዋዕትነቱ የሚመርጡት ሌላ አካል እንዲኾንላቸው ይፈልጋሉ። እነሱ በአቋራጭ ስልጣን ላይ ለመፈናጠጥ እንዲያስችላቸው። ከዚኽ አንጻር የሀገራችን ተቃዋሚዎች ትጥቅ ትግል አውጀው በሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩት እና በስመ አክቲቪዝም የሚከትሏቸው (ሁለቱንም መንገድ የሚያጣቅሱ ቡድኖች) እንዲኹም በሰላማዊ ሕጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱት በተደጋጋሚ የመተባበር እና ለህዝብ መስዋዕት የመኾን መሰረታዊ ባህሪ ስለሚጎድላቸው እና የስልጣን […]
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እስር እና «ሲ ፒ ጄይ»
ኢትዮጵያ ውስጥ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የአምደ መረብ ጸሓፍት ቁጥር ከአምናው በእጥፍ ማደጉን CPJ በሚል ምኅፃረ-ቃል የሚጠራዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ገለጠ። የCPJ የምሥራቅ አፍሪቃ ተወካይ ቶም ሮድስ ኢትዮጵያ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ምርጫው ከመድረሱ አስቀድሞ ተቺዎች ድምፃቸው እንዳይሰማ እያፈናቸው መሆኑን ተናግረዋል።
በሳኡዲ አረቢያ ያሉ አንዳንድ ኢትዮጵያውን ስሞታ
ሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ቢኖራቸውም በግልጽ በማያውቁት ምክንያት ታስረናል ይላሉ።ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ተገቢውን ድጋፍ አላገኙም።
የዩኤስ አሜሪካና የኪዩባ አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ
ዬኤስ አሜሪካና ኪዉባ ከሃምስ ዓመታት በላይ ያቋረጡትን ዲፕሎማስያዊ ግንኙነት ማሻሻል እንደሚፈልጉ ከገለፁ በኋላ የዓለም መንግሥታት ዉሳኔዉን በደስታ ተቀበሉት።
የታህሳስ ወር ሃገራዊ እና ባህላዊ ትርጓሜ
«አርሶ አደሩ እያጉረመረመ ሲለዉ ከረመ፤ አርሶ በሌዉ መጣ ጠላ ሊጠጣ፤ አርሶ በሌዉ ካለ ምን ችግር አለ፤ አርሶ በሌዉ ጎፈር ማረስ መቆፈር፤ ላለዉ መንገዱን አለስልሶ ከርሞ ይመጣል ያልሞተ ሰዉ፤ እመቤቴ ያደረችበቱ እጣን ይሸታል መሬቱ» እያለ ሆ ይላል ያዜማል ፤ የኢትዮጵያ ገበሬ የዘራዉን ሰብል በታህሳስ ሲሰበስብ።
በሳኡዲ አረቢያ እስር ቤት የሚማቅቁት ኢትዮጵያውን
ሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ቢኖራቸውም በግልጽ በማያውቁት ምክንያት ታስረናል ይላሉ።ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ተገቢውን ድጋፍ አላገኙም።
የሩስያ ብሔራዊ ሸርፍ «ሩብል» ዋጋ መውደቅ
የሩስያ ማዕከላይ ባንክ የሀገሩ ገንዘብ «ሩብል» ዋጋ እያሽቆለቆለ የተገኘበትን ሁኔታ ለማከላከል በአሁኑ ጊዜ የሚቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ ይገኛል፣ ይሁንና፣ የእስካሁኑ ጥረቱ አንድም የረባ ውጤት አላስገኘለትም። የሩብል መውደቅ ሩስያን ወደ ከፋው የኤኮኖሚ ቀውስ ወስጥ ይጥላት ይሆን?
የኤቦላ ተፅዕኖ በምዕራብ አፍሪቃ
የኤቦላ ተኀዋሲ በምዕራብ አፍሪቃ ፣ በተለይ በሶስቱ በበሽታው በጣም በተጠቁት ሀገራት፣ ላይቤርያ፣ ጊኒ እና ሲየራ ልዮን ላይ እያደረሰ ስላለው ማህበራዊ እና ኤኮኖሚያዊ ተፅዕኖ የተመድ በአፍሪቃ አዳራሽ ባካሄደው ጉባዔ ላይ ዝርዝር መግለጫ ሰጠ።
የአሜሪካና የኪዩባ አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ
ዬኤስ አሜሪካና ኪዉባ ከሃምስ ዓመታት በላይ ያቋረጡትን ዲፕሎማስያዊ ግንኙነት ማሻሻል እንደሚፈልጉ ከገለፁ በኋላ የዓለም መንግሥታት ዉሳኔዉን በደስታ ተቀበሉት።
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እስርና CPJ
ኢትዮጵያ ውስጥ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የአምደ መረብ ጸሓፍት ቁጥር ከአምናው በእጥፍ ማደጉን CPJ በሚል ምኅፃረ-ቃል የሚጠራዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ገለጠ። የCPJ የምሥራቅ አፍሪቃ ተወካይ ቶም ሮድስ ኢትዮጵያ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ምርጫው ከመድረሱ አስቀድሞ ተቺዎች ድምፃቸው እንዳይሰማ እያፈናቸው መሆኑን ተናግረዋል።
በአዳር ሰልፍ ወቅት ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው የመአሕድ ም/ጸሃፊ ህይወታቸው አደጋ ላይ ነው

በአዳር ሰልፍ ወቅት ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) ምክትል ፀኃፊ መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ ራሳቸውን ስተው ሆስፒታል እንደገቡና ሕይወታቸው አደጋ ውስጥ እንደሆነ የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ ሽዋንግዛው ገ/ስላሴ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በአዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው ሲሆን ለአምስት ቀናት ቀዝቃዛና ጨለማ ቤት ውስጥ ታስረው ቆይተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ የስኳር በሽታ መድሃኒታቸውን በመቀማታቸውና ህክምናም ባለማግኘታቸው ታመው እንደነበር ለማወቅ መገለጹ ይታወሳል፡፡
መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በድብደባውና በስኳር በሽታ ምክንያት በአሁኑ ወቅት ዘውዲቱ ሆስፒታል የሚገኙ ሲሆን ሆስፒታል ከገቡበት ቅዳሜ ታህሳስ 4/2007 ዓ.ም ጀምሮ ሰው ማናገር አለመቻላቸውን የፓርቲው ፕሬዝዳንት አክለው ገልጸዋል፡፡
ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራርን ከስራ አገደ

የሰማያዊ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ አቶ እያስፔድ ተስፋዬ ከሚሰራበት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአዳር ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ በደረሰበት እስር ምክንያት ከስራው ታገደ፡፡ እያስፔድ ተስፋዬ በሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ጨለማና ቀዝቃዛ ክፍል ታስረው ከነበሩት አመራሮች መካከል አንዱ ሲሆን ከእስር ከተፈታ በኋላ ታስሮ ስለመቆየቱ ማስረጃ ቢወስድም ለ15 ቀን ከስራ ታግዶ እንዲቆይ ተደርጓል፡፡
‹‹ታስሬ መቆየቴን የሚያሳይ ማስረጃ ወደምሰራበት ቅርንጫፍ ስወስድ ከእኛ አቅም በላይ ስለሆነ ወደ ዲስትሪክት ውሰድ ተባልኩ፡፡ ዲስትሪክት ስወስድ የንግድ ባንክ ዳይሬክተር የሰው ኃይል አስተዳደር ማመልከቻና ታስረህ የቆየህበትን ማስረጃ አስገባና እነሱ ወደ ስራ ገበታህ ተመለስ ካሉህ ነው የምትመለስ፤ እነሱ ተመለስ እስኪሉህ ድረስ ግን ወደ ስራ ገበታ መመለስ አትችልም አሉኝ፡፡ ባሉኝ መሰረትም ለሰው ኃይል አስተዳደር ደብዳቤና ከፖሊስ ጣቢያ የተሰጠህን ማስረጃ ወሰድኩ፡፡ እሱ እስኪያየው ድረስ ተብሎ አንድ ቀን ቀጠሮ ተሰጠኝ›› የሚለው እያስፔድ በቀጠሮው መሰረት ሲሄድ ጉዳዩ ለቅሬታ ሰሚ ኮሜቴ እንደተላከ፣ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ አባሎች ስልጣና ላይ በመሆናቸው ለ15 ቀን ስራ መግባት እንደማይችልና ለታገደበት ቀናትም ደመወዝም እንደማይከፈል እንደተገለጸለት ለነገረ ኢትዮጵያ አስረድቷል፡፡
ቀደም ሲል የሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ አቶ ወሮታው ዋሴ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተባረሩ መሆናቸው ይታወሳል፡፡
የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በካንጋሮ ፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት እነአብርሃ ደስታ ለታህሳስ 15 ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው ::

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች ለታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ተከሳሾቹ የክስ መቃወሚያ አቅርበዋል
ዛሬ ታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት የቀረቡት የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ እንዲሁም አንደኛ ተከሳሽን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች በጠበቆቻቸው አማካኝነት የክስ መቃወሚያቸውን ይዘው ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
ሆኖም ግን 7ተኛ ተከሳሽ አቶ አብርሃም ሰለሞን የሰጠው የተከሳሽነት ቃል ከክሱ ጋር ተያይዞ ለጠበቃው አለመቅረቡን ተከትሎ ጠበቃው የክስ መቃወሚያ ለማዘጋጀት ባለመቻላቸው የተከሳሽ ቃልን የያዘውን ዶክሜንት ከጽ/ቤት ወስደው መቃወሚያቸውን እንዲያስገቡ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን የክስ መቃወሚያ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል ተከሳሾች በእስር ላይ ባሉበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሊጎበኟቸው የሚሄዱ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ወደ እስር ቤቱ ሲገቡ በተለየ መዝገብ እንዲመዘገቡ እየተደረጉ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው በተለየ መዝገብ በመመዝገባቸው ከሌላው በተለየ ማሸማቀቅ እየተፈጸመባቸው ነው፡፡
ይህን በተመለከተ ለማረሚያ ቤቱ አቤት ቢሉም ሊሻሻል አለመቻሉን ተከሳሾቹ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ለማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታቸውን ተቀብሎ በቀጣይ ቀጠሮ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ስለጉዳዩ ቀርቦ እንዲያስረዳ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
አክራሪ … አሸባሪ … የሰለቸን መንግስታዊ መዝሙር … የፖለቲካ የበላይነት የፈጠረው አክራሪነት/አሸባሪነት የህዝቦች ስጋት ነው፡፡ – ምንሊክ ሳልሳዊ
ሃገሪቱን የሚያሰጋት የሃይማኖት አክራሪነት/አሸባሪነት ሳይሆን የፖለቲካ የበላይነት የፈጠረው አሸባሪነት ጽንፈኝነት እና አክራሪነት ነው:: ጥላችሁን እንዳታምኑ እየተባለ ሃይማኖት መንግሥታዊ ቅርጽ ይዞ እንዲወጣ ለማድረግ መሞከር አክራሪነት ነው፡፡
«መጾም፣ መጸለይ፣ ሥርዓተ-አምልኮን መፈጸም ሃይማኖታዊ አልባሳትን መልበስ ለሃይማኖቱ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንጂ አክራሪነት ሊባል አይችልም፤»…የአክራሪ ክርስትና ወይንም እስልምና ቡድን መኖር የክርስትና እና እስልምና ተከታዮችን በሙሉ «አክራሪ» አስብሎ ሊያስፈርጃቸው አይችልም::አክራሪ ተብሎ የሚፈረጀው የሚራመዱ የፖለቲካ ጡዘቶች በሰዎች ላይ ሌላ እምነትን በመጫን በግዳጅ እና በሃይል ሊያስገድዱ ሲሞክሩ ይህ ማለት አህበሽን እና ተሃድሶን በጥንታውያኑ እስልምና እና ተዋህዶ ላይ በኢትዮጵያ እንደተሞከረው ማለት ነው::
አክራሪነት አሉታዊ ትርጉም ሲኖረው የራስን እምነትና አመለካከት በሌሎች ላይለመጫን መሞከር ነው፡፡ ሃይማኖት መንግሥታዊ ቅርጽ ይዞ እንዲወጣ ለማድረግ መሞከር ራሱ አክራሪነት ነው፡፡ አክራሪነት የፖሊቲካ ገጽታ ያለው ነው፡፡ ኾኖም ግን ሃይማኖትን ማጥበቅ አክራሪነት አይደለም፡፡ሃይማኖት ፍጹም እውነታን በፍጹም እምነት ስለሚቀበል ከሌሎች ግላዊ አስተሳሰቦች የተለየ ነው፡፡ የሃይማኖት መገለጫዎችን መጠቀም የዚያን ሃይማኖት ጥልቀት የሚያሳይ እንጂ እንደ ችግርም የሚወሰድ ወይም አክራሪነት ሊኾን አይችልም፡፡ «መጾም፣ መጸለይ፣ ሥርዓተአምልኮን መፈጸም ሃይማኖታዊ አልባሳትን መልበስ ለሃይማኖቱ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንጂ አክራሪነት ሊባልአይችልም፤» ይላሉ የዘርፉ ምሁራን፡፡
የአክራሪነትና የአጥባቂነት ፅንሰ ሐሶቦች በጥሩ ኹኔታ ተለይተው ተገልጸዋል፡፡ አንዳንድ ሰነዶች ወያኔም ለይስሙላ የገለበጣቸው ሰነዶቹ አክራሪነትንና አጥባቂነትን በአግባቡ ለይተውና ተንትነው ያስቀምጣሉ፡፡ በዚሁ መሠረት አጥባቂነትን፣ ‹‹የግል ሃይማኖትን ሃይማኖቱ በሚያዘው መሠረት ሳይንጠባጠብ ሁሉንም ትእዛዛት መፈጸም ነው፤» በማለት ሲፈታው አክራሪነትን ደግሞ፣ «ከራስ እምነት ወጥቶ ሌላውን መተንኮስና የሌሎችን ሃይማኖት መኖር አለማመንና አለመፍቀድወይም ሌሎቹን አስገድዶ የራስ እምነት ተከታዮች ለማድረግ መጣር ነው፤» ይላል፡፡ በተግባር ላይ አለመዋሉ እና በጣልቃ ገብነት መተርጎሙ ጉዳት አመጣ እንጂ::
ከዚህ ብያኔ ስንነሣ ክርስቲያንም ሆነ ሙስሊም ከርሱ ውጭ የኾኑትን የሌሎቹን መኖር የማይቀበልና ከግለሰቦቹ ፈቃድ ውጭ አስገዳጅ እስከኾነ ድረስ እርሱን አክራሪ ማለት ይቻላል፡፡መብትን መጠየቅ ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት መሸሽ አክራሪነት አይደለም:: በዚህ መልኩ አክራሪው ይህንኑ ድርጊት ሊፈጽም የተነሣውን ቡድን ብቻ እንጂ «አክራሪው ቡድን» የወጣበትን/የተገኘበትን ቤተ እምነት ሊወክል አይችልም፡፡ ስለዚህ በአለማቀፍ ደረጃ የአክራሪ ክርስትና እና እስልምና ቡድን መኖር የክርስትና እና እስልምና ተከታዮችን በሙሉ «አክራሪ» አስብሎ ሊያስፈርጃቸው አይችልም፤ ለሌላው ቤተ እምነትም እንዲሁ፡፡ ሃገሪቱን የሚያሰጋት የሃይማኖት አክራሪነት ሳይሆን የፖለቲካ የበላይነት የፈጠረው አሸባሪነት ጽንፈኝነት እና አክራሪነት ነው:: #ምንሊክሳልሳዊ
ምርጫ የሰላማዊ ትግል ስልት ሳይሆን የዲሞክራሲያዊ ስርዓት መገለጫ ነው! ዮናታን ተስፋዬ ረጋሳ ከሰማያዊ ፓርቲ
(ይህ የግሌ አስተያየት ነው!)
ምርጫ ካልተገባ ሌላኛው አማራጭ ትጥቅ ትግል ብቻ ነው ያለው ማነው? ሲጀመርስ ምርጫ የዲሞክራሲ መገለጫ ነው እንጂ ከመቼ ወዲህ ነው የሰላማዊ ትግል አካል ሊሆን የሚችለው፡፡ ሰላማዊ ትግል ዲሞክራሲ በሌለበት የሚደረግ ትግል ከሆነ ዘንዳ የዴሞክራሲ መገለጫ የሆነው ምርጫ ሰላማዊ ትግል ነው ማለትስ ምን ማለት ነው?
ሰላማዊ ትግል እኮ ሰላማዊ ትግል ያስባለው መሳሪያ የሚያስነሳ ጭቆና መኖሩ ነው፡፡
ግልፅ በሆነ መንገድ ለማስቀመጥ
በምርጫ የሚደረግ ትግል ህዝቡ የስልጣኑ ባለቤት በሆነበት ሀገር እንጂ ሁሉም ነገር በአገዛዙ መዳፍ ስር በሆነበት ሁናቴ አይደለም፡፡
ሰላማዊ ትግል ዲሞክራሲ ጨርሶውኑ በሌለበትና እየሞቱ ማሸነፍ ግድ የሆነበት የትግል አካሄድ ነው፡፡
የትጥቅ ትግልም ዲሞክራሲ ፈፅሞ በሌለበት ሀገር ውስጥ እየገደሉም እየሞቱም ለማሸነፍ የሚደረግ ትግል ነው፡፡
ከዚህ በመነሳት
1- አሁን ባለንበት ሁናቴ ምርጫ ማካሄድ የዴሞክራሲ ሂደት ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ማለት ሲሆን
2- ኢህአዲግን በፈቃዳችን እንደ መንግሰት እውቅና መስጠት ነው
ስለዚህ፡- ትግሉ ሰለማዊ ትግል ነው የምንለው ምርጫ ማድረግ የሚቻልበትን ምህዳር መፍጠር፤ ህዝቡን የስልጣኑ ባለቤት ማድረግ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በመሁኑ ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ማቸውንም የፖለቲካ ስራ በነፃነት መስራት በማይቻልበት ሁናቴ ነፃነት እንዲኖር መታገል ከሁሉ በፊት መሆን ያለበት ትግል ነው፡፡ ይህ ትግል በባህሪይው እልህ አስጨራሽ፣ ተስፋ አስቆራጭ፣ ብዙ ዋጋ የሚያስከፍል … ፍሬው ግን ዘላቂና እጅግ አስደሳች ነው፡፡ ለዛ ነው ደጋግመን ህይወታችንንም ቢሆን እስከመስጠት ድረስ ፍፁም ሰላማዊ ሆነን እንታገላለን የምንለው፡፡
ሰለማዊ ትግል ከነፍጥ ትግል የሚለየውም በዚሁ ባህሪይው ነው፡፡ በመውደቅ በመነሳት ውስጥ ማሸነፍ፤ ሳይገድሉ በመሞት ማሸነፍ፡፡ ይህ መንገድ በምርጫ ከሚደረግ የስልጣን ትግልም ሆነ መሳሪያ አንስተው በሀይል ስልጣን ለመያዝ ከሚደረግ ትግል ፍፁም የተለየ ነው፡፡ ነፃነት ትግል ይፈልጋል፡፡ ፍፁም ሰላማዊ ሆነን እናሸንፋለን!
አክራሪ … አሸባሪ … የሰለቸን መንግስታዊ መዝሙር … የፖለቲካ የበላይነት የፈጠረው አክራሪነት/አሸባሪነት የህዝቦች ስጋት ነው፡፡ – ምንሊክ ሳልሳዊ
ሃገሪቱን የሚያሰጋት የሃይማኖት አክራሪነት/አሸባሪነት ሳይሆን የፖለቲካ የበላይነት የፈጠረው አሸባሪነት ጽንፈኝነት እና አክራሪነት ነው:: ጥላችሁን እንዳታምኑ እየተባለ ሃይማኖት መንግሥታዊ ቅርጽ ይዞ እንዲወጣ ለማድረግ መሞከር አክራሪነት ነው፡፡ «መጾም፣ መጸለይ፣ ሥርዓተ-አምልኮን መፈጸም ሃይማኖታዊ አልባሳትን መልበስ ለሃይማኖቱ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንጂ አክራሪነት ሊባል አይችልም፤»…የአክራሪ ክርስትና ወይንም እስልምና ቡድን መኖር የክርስትና እና እስልምና ተከታዮችን በሙሉ «አክራሪ» አስብሎ ሊያስፈርጃቸው አይችልም::አክራሪ ተብሎ […]
ኢራን፣ “ሩሚ” እና “መስነቪ”
የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰቦች ይዞታ ሁለት ገጽታ፤
ኢትዮጵያ ውስጥ በልማትና አገልግሎት ላይ የተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕድገት ሲያሳዩ በመብቶች ጉዳዮች ላይ ሲሠሩ የነበሩት ግን መዳከማቸውን አንድ ጥናት አመልክቷል፡፡
በሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች አማካይነት በዚህ ዓመት ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል፡፡
ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን ተጠቃሚ ሆነዋል – ተብሎም ተገምቷል፡፡
የዘገባውን ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ፤
ሕዝብን ያላስከተለ ትግል ዉጤት አያመጣም – ግርማ ካሳ
ሕዝብን ያላስከተለ ትግል ዉጤት አያመጣም – ግርማ ካሳ
“ምርጫው ላይ ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠናል።በምርጫው ልንሳተፍም ሆነ ላንሳተፍ ውሳኔ የምናሳልፈው እኛ ሳንሆን ሂደቱ ነው” ብለዋል። ” እኛ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጥነው ምርጫ ላይ ሳይሆን የምርጫ ሂደቱ ላይ ነው” ሲሉ ደግሞ አቶ ግርማ በቀለ የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፀኃፊ፣ ቀደም ሲል ለምርጫው ቅድመ ሁኔታ አላቀመጥንም የሚለው ለማሻሻል ሞክረዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የትብብሩ አመራሮች መልስ ለመስጠት የተቸገሩ፣ እርስ በርሳቸዉም አንድ አቋም ያልያዙ መሰለኝ። አቶ ዮናትን ቅድመ ሁኔታ ለምርጫው አስቀምጥናል እያሉ፣ የትብብሩ ዋና ጸሃፊ ለምርጫው ቅድመ ሁኔታ አላስቀመጥንም የሚሉ ከሆነ የቱ ነው ትክክለኛ የትብብሩ አቋም ? ? ? አቶ ዮናትን ወይስ አቶ ግርማ በቀለ ያሉት። በዚህ ጥያቄ ላይ “Honesty is the best policy” ይላሉ ፈረንጆች። ሰማያዊም ሆነ ትብብር በዚህ ረገድ አቋማችሁን በግልጽ ማስቀመጥ አለባችሁ። መቃረን የለባችሁም።
ሌላው ወደ ምርጫ ለመግባት ሂደቱ ይወስነዋል ይላሉ አቶ ዮናታን። ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል። አንዱ ቅድመ ሁኔታ ይመስለኛል የምርጫ ቦርድ ነጻ መሆን አለበት የሚል ነው። በዚህ ረገድ አሁን ባለው ሁኔታ ገዢው ፓርቲ ፈቀቅ ያለበት ሁኔታ የለም። ካልተገደደ በቀር አሁን ያለው ምርጫ ቦርድ ነው የሚቀጥለው።
ትዝ ይለኛል ከምርጫ ቦርድ ሰብሰባ ሰማያዎች ረግጠው ወጥተው ነበር …ምርጫ ቦርድ ግን ኢግኖር ነው ያደረጋቸው። ስራዉንም ቀጥሏል። የአንድ ወር መርሃ ግብር ብለዉም ከፖሊሶች ጋር ተጋጩ፥ ብዙዎች ለሁለት ሶስት ቀናት ታሰሩ። አሁንም ምንም ለዉጥ የለም በምርጫ ቦርድ አካባቢ።
ሁለት ሶስት መቶ ሰዎች ይዞ ሰልፍ መዉጣት አገዛዙን አያስገድድም። ይልቅ መቶ ሺሆች፣ ሚሊዮን ሕዝብ እንዲወጣና ለመብቱ እንዲጮህ ነው ማድረግ የሚያስፈለገው። ለዚህም በጋራና በትብብር መስራት ያስፈልጋል። ጠንካራ ከሚባሉ ድርጅቶች ጋር ከነ አንድነት፣ መድረክ ጋር አብራችሁ ሰላማዊ ሰልፎችን ሰማያዎች ቢጠሩ፣ አብረው መሰረታዊ የዲሞክራሲ ጥያቄዎችን ቢያነሱ ብስለትና እውቀት ባለበት መልኩ ቢንቀሳቀሱ፣ ትልቅ ቫይብሬሽን መፍጠር ይቻል ነበር።
እርግጥ ነው እዚህ በዉጭ ያሉ እንዳንድ ጽንፈኞቹ ከረን አፌር ክፍል ያሉ ሰማያዎችን ፣ ሆይ ሆይ እያሏቸው ነው። ምናልባት ሁለት፣ ሶስት ቀናት በመታሰራችሁ “ጀግኖች፣ አንበሶች” ሲሏቸው፣ ያለ እነርሱ ሰው የሌለ ሊመስላቸው ይችላል።
ሆኖም ግን እዚህ በዉጭ ያሉ ጽንፈኖች ችግር ዉስጥ ነው ሰማያዎዎችን የሚከቷችሁ። አዎ ከዉጭ ድጋፍ ማግኘት ጥሩ ነው። ዉጭ ያለው ወገን የትግሉም አካል ነው። ሆኖም ዉጭ ያለው ማህበረሰብ የሚፈልገውን ሳይሆን በአገር ቤት ያለው ሕዝብ የሚፈለገውን በማዳመጥ ነው መንቀሳቀስ የሚገባው። የሰላማዊ ትግል የራሱ የሆነ ሰራዊት አለው። እርሱም ሕዝብ ነው። ሕዝብን ያላሰለፈና ያላንቀሳቀሰ ትግል ዋጋ አይኖረዉም።
አንድ ነገር ብዬህ ላቁም። ከአንድ አመት በፊት ሰማያዊ ሰልፍ ሲጠራ ወደ 70 ሺህ ሕዝብ ተገኝቶ ነበር። ከሶስት ወራት በኋላ ሰልፍ አንድነት ሲጠራ አብረው አእንዲያደረጉ ትልቅ ተማጽኖ ቢቀርብላቸውም፣ እምቢ ብለው፣ ተሽቀዳድመው ሰልፍ ጠሩ። ሰልፉ ጃን ሜዳ ነበር ግን መስቀል አደባባይ መሄድ አለብን ሲሉ ከፖሊስ ጋር ዉዝግብ ፈጠሩ። ጥቂት ፖሊሶች አፈኗችሁ።
ስድስት ወራት በኋላ፣ ሚያዚያ ላይ አንድነት ሰልፍ ጠርቶ ከአስተዳደሩ ጋር እየተነጋገረ ባለበት ጊዜ ፣ እንደ ጎህ ዝንብ ጣልቃ ገብተው፣ ሰልፍ ጠሩ። ለአንድነት አይሆንም በተባለ ቀን፣ እውቅና አገኙ። ለሰልፉም ቅስቀሳ አደረጉ። የተገኘላችሁ ሰው ሶስት መቶ አካባቢ ብቻ ነበር። ከሰባ ሺህ ወደ ሶስት መቶ መዉረድ ማለት ትልቅ የፖለቲካ ኪሳራ ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ የሰማያዊን ስትራቴጂ እንደማያደገፍ ሰልፉ ላይ ባለመገኘት ገለጸ።
ለምንድን ነው ይሄ የሆነው ብለው መጠየቅ አልቻሉም። አሁን በአንድ ወር መርሃ ግብር እንቅስቃሴያቸውም የተለየ ነገር አላየንም። እንደ ኢሳት ባሉ ሜዲያዎች ሁሉ ሳይቀር ለሌለ ማንም ድርጅት ያልተደረገ ትልቅ ቅስቀሳ ተደረገላቸው። በሶሻል ሜዲያዉም እንደዚሁም። ከአምስት ሚሊዮን የአዲስ አበባ ህዝብ፣ መቶ አይሞላም የወጣላቸው። ለምን የአዲስ አበባ ህዝብ ጥሪያቸዉን ሰምቶ እንቅስቃሴያቸዉን አልተቀላቀለም ? ይሄ መመለስ ያለበት መሰረታዊ ጥያቄ ነው።
ገዢው ፓርቲን ማስገደድ የሚቻለው ህዝቡ በነቂስ ሲወጣ ብቻ ነው። ሰማያዊቾ ትኩረት ሰጥተው መንቀሳቀስ የነበረባቸው ሕዝቡ እንዲወጣ ማድረግ የሚቻልበትን ስትራቴጂ በመንደፍ ላይ መሆን ነበረበት። ደግሜ እላለሁ ….ሰማያዊች የያዙት መስመር በጣም አደገኛና ትግሉን የሚጎዳ ነው። አላስፈላጊ ኮንፍሮንቴሽን አስወግደው፣ ሕዝቡን በማደራጀት ላይ፣ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር አብሮ በመስራት ላይ ቢያተኩሩ ጥሩ የሚሆን ይመስለኛል። አለበለዚያ የሁለተኛ መርሃ ግብር ብለዉም የሚያወጡት ከአንደኛው የሚለይ አይሆንም።
የአንድነት ፓርቲ በፖለቲካ ፕሮግራም ተመሳሳይነት ካላቸው ጋር ፣ ሰማያዊን ጨምሮ፣ ያለ አንዳንች ቅድመ ሁኔታ በጋራ ለመስራት ዝግጁ እንደሆነ እየገለጸ ነው። ሆኖም የሰማያዊ አመራሮች ከአንድነት ጋር ለመስራት አለርጂክ ለምን እንደሆነባቸው ደጋፊዎቻቸው መጠየቅ ያለባቸው መስለኝ።
የሰማያዊ አቅጣጫ ስህተትና የማይጠቅም ነው – ግርማ ካሳ
የሰማያዊ አቅጣጫ ስህተትና የማይጠቅም ነው – ግርማ ካሳ
አቶ እያስፔድ ተስፋዬ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚ አባልና የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ ናቸው። “አቧራን ለማጥራት – ነጻነት ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ ነው” በሚል ርእስ አንጹ ጽሁፍ አቅርበዋል። በሚከተለው ሊንክ ያገኙታል። የእኝህ ወጣት አቀራረብ በጣም ተመችቶኛል። በነጻነት ነጥባቸውን በማስቀመጥ ለምርጫ ከመገባቱ በፊት መሟላት ያለበት ቅድመ ሁኔታ እንዳለ ይከራከራሉ።
የድርጅት አባል ባልሆነም፣ የምደገፈው ድርጅት አለ። እርሱም የአንድነት ፓርቲ ነው። ይህ ፓርቲ፣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለምርጫ እንደሚሳተፍ በይፋ ለህዝብ አሳዉቆ፣ «2007 ለለውጥ»፣ «ተደራጅ ለምርጫ» በሚል መርህዎች በአገሪቷ ሁሉ መጠነ ሰፊ የምርጫ እንቅስቃሴ ጀመሯል።
የአንድነት አቋም ለምን ትክክለኛ እንደሆነ፣ በአንጻሩም ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ አቋም ለምን የወቅቱን ሁኔታ ያላመዛዘነ የተሳሳተና በ እወቀት ሳይሆን በስሜት ላይ የተመሰረተ አቋም እንደሆነ ለማሳየት እሞክራለሁ። የአንድነት አባል እንዳለመሆኔ፣ ከዚህ በታች የምጽፈው የግል አስተያየቴ እንደሆነ ከወዲሁ ለአንባቢያን አሳውቃለሁ።
ብዙዎቻችን በምርጫ በመግባትና ባለመግባት ዙሪያ የሚደረገው ዉይይት አካል ሆነን ሐሳቦችን ሰንዝረናል። አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫ መገባት የለበትም የሚሉ ወገኖች ፣ ከምን ተነስተው እንደዚያ እንደሚሉ እረዳለሁ። ሆኖም የነርሱን አቋም ተቃዉሜ ስጽፍ፣ ምርጫ ባለመግባት የሚገኝን ጥቅም ሊያሳዩን ባለመቻላቸው ነው።
እዚህ ዉጭ አገር ያሉ አንዳንድ በጠመንጃ ትግል እናምናለን የሚሉ ቡድኖች፣ ምርጫ እንዲገባ አይፈልጉም። (እነርሱ ዉጊያቸውን ትተው ለምን በሰላማዊ ታጋዮች ዙሪያ እንደሚጨነቁ ባይገባኝም) ምናልባት ምርጫ ከተደረገና አንጻራዊ መሻሻል ከመጣ የነርሱ ፖለቲካ ዜሮ ስለሚገባ ሊሆን ይችላል ምርጫዉን የሚቃወሙት። በመሆኑም ከነዚህ ቡድኖች በምርጫ ዘመቻ ላይ ተቃውሞ ቢሰማ ልንገረም አይገባም።
አገር ቤት በሰላም የሚታገሉ ወገኖች ግን ፣ ምርጫዉን ቦይኮት ሲያደርጉ ፣ በተመሳሳይ ሁኔታ ደርጅታቸውን ወይንም ሕዝቡን የሚጠቅም መሆኑን በማስላት መወሰን ያለባቸው መሰለኝ። ይሄን ካደረጉ የቦይኮት ጥሪው ችግር ይኖረዋል ብዬ አላስብም። ነገር ግን ትንሽ ያልተመቸኝ ፣ እነ አቶ እስያስፔድ እንዲያስረዱን የምፈልገው ፣ ቦይኮት ማድረጉ ምን ጥቅም ለትግሉም ሆነ ለሰማያዊ ፓርቲ እንደሚያስገኝ ነው። ቦይኮት ተደረገ፤ ከዚያስ ? ? ትልቅ መመለስ ያለበት ጥያቄ።
እስከሚገባኝ ድረስ የሰማያዊ ፓርቲ ሆነ ትብብር በቀዳሚነት አቋማቸው በግልጽ አይታወቅም። አንዳንድ አመራሮች ያለ ቅድመ ሁኔታ ወደ ምርጫው እንገባለን ይላሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ ተቃራኒዉን ይናገራሉ። ስለዚህ በቅድሚያ የሰማያዊም ሆነ ትብብሩ አቋም ግልጽ መሆን አለበት። አንድ የአመራር አባል ፌስ ቡክ ላይ በመጻፉ ሳይሆን፣ ደርጅቶቹ በኦፊሴል ለሕዝብ አቋማቸዉን ግልጽ ማድረግ አለባቸው።
ለዉይይት ያህል.፣ ቅድመ ሁኔታ ሳይሟላ ወደ ምርጫው አይገባም ከተባለ፣ ቀጣዩ ጥያቄ የሚሆነው ቅድመ ሁኔታዎቹ ምንድን ናቸው የሚል ነው። ከዚያ ገዚው ፓርቲ ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲያሟላ ምን እየተደረገ ነው ? የተደረገውስ ምን ዉጤት አመጣ ? የሚሉ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
የሰማያዊ ፓርቲ አገዛዙ ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲያሟላ፣ ጫና ለማድረግ የአንድ ወር መርሃ ግብር አጠናቋል። ዉጤቱን ሁላችንም የምናወቀው ነው። ካለፈው የአንድ ወር መርሃ ግብር የተለየ ነገር በሚቀጥሉት መርሃ ግብሮች ምን ሊፈጠር እንደሚችል በርግጠኝነት መናገር ቢያስቸግረም፣ መገመቱ ግን ይከበዳል ብዬ አላስብም።
የሰማያዊ ፓርቲ ቅድመ ሁኔታዎች አልተሟሉም ብሎ ከምርጫው ቢወጣ፣ ገዢው ፓርቲ የሚፈራው ወይም የሚጎዳበት ሁኔታ የሚፈጥር ቢሆን ኖሮ «ቦይኮት አደርጋለሁ» በሚል ማስፈራራትና ቅድመ ሁኔታዎች ማስቀመጥ ያስኬዳል ብዬ ልቀበል እችል ነበር። ሆኖም ያደረች ባቄላ እንደሚባል፣ ገዢው ፓርቲ ሰማያዊ ምርጫ ዉስጥ ገባ፣ አልገባ ግድ አይሰጠዉም። የሰማያዊ ምርጫውን አለመሳተፍ ለነርሱ ኢንሲግኒፊካንት ነው። በመሆኑም ምርጫ አንገባም ማለት ፖለቲካ ፋይዳ አይኖረዉም።
ሌላው ቦይኮት በሚደረግበት ጊዜ ፣ ሕዝቡም ቦይኮት እንዲያደርግ ማስተባበር ያስፈልጋል። ህዝቡ ወደ ምርጫ ሄዶ ፣ ሰማያዊ ግን ብቻዋን ቦይኮት ቢያደረግ፣ እንደ ቢራቢሮ አየር ላይ የሚንሳፈፍ ድርጅት ነው የሚሆነው። ድርጅቶች በሙሉ ተባብረው፣ ተነጋግረው፣ በተቀናጀ መልኩ ቦይኮት እንዲደረግ ዘመቻ ቢያደርጉ፣ ህዝቡም የቦይኮቱ አካል እንዲሆን ቢያደራጁ፣ ከቦይኮቱ ጎን ለጎን ሰላማዊ ሰልፎችን የሥራ ማቆም አድማዎችን ቢጠሩ …ቦይኮት ሊሰራ ይችላል። ከዚያ ዉጭ ግን ቦይኮት የሚያመጣዉ አንዳች ፋይዳ አይኖርም። (እስከሚገባኝ ድረስ የሰማያዊ ፓርቲ ከነ አንድነት ፓርቲ ጋር አብሮ መስራቱ እንደ አለርጂክ እየሆነበት ነው። ከተመሰረቱ ጊዜ ጀመሮ ከአንድነት ጋር ፉክክር እንጂ የያዙት፣ በቁም ነገር፣ «በአንድ ላይ መሰባሰባች የአገርና የሕዝብ ጥያቄ ነዉ» በሚል ሂሳብ ለመንቀሳቀስ ሲሞክሩ አይታዩም)
በመጨረሻ የማነሳው ነጥብ የፕራክቲካሊቲ ነጥብ ነው። ሰማያዊ «አገዛዙ ላይ ጫና አሳድሬ፣ ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሟሉ አደርጋለሁ» ይላል። በአራት ወራት ጊዜ ዉስጥ ምን ያህ ይሄ ግብ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ? እዉነት እንነጋገርና በአራት ወራት ዉስጥ አገዛዙ ምርጫ ቦርድን ይለውጣልን ? ለነዚህ ጥያቄዎች መልሱ « አይችልም፣ አይሆንም» የሚል ነው።
ምርጫ ቦርድ ላይ በየምርጫ ጣቢያ ጫና ሊያደረግ የሚችለዉን ህዝብ፣ ድምጹን እንዲያስከበር ከማደራጀትና በየሜዳው ሄዶ ከመንቀሳቀስ ዉጭ ሌላ አማራጭ አይኖርም። የሰላማዊ ትግል ሰራዊት ሕዝቡ ነው። ወታደሮች ከኋላው ያላሰለፈ ጀነራል የትም እንደማይደርስ፣ ህዝቡን ከበስተኋላ ያላሰፈ የሰላማዊ ትግል መሪም ሆነ ድርጅት ሩጫ ከንቱ ነው።
«አንድነት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በምርጫው እሳተፋለሁ» ብሎ መግለጫ መስጠቱን አልቃወምም፡፡ አባላቶቼን ከወዲሁ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ይረዳኛል ብሎ ይሆናልና፡፡ ልክ እንደዚሁም ሁሉ ሌላውም የእኛን አቋም እንዲያከብርልን እሻለሁ፡፡» ሲሉም አቶ እያስፔድ ጽሁፋቸውን ያጠቃልላሉ። በመርህ ደረጃ ትክክል ናቸው። ሆኖም በዚህ ወሳኝ ወቅት የሰማያዊና የአንድነት ስትራቴጂዎች የተለያዩ በመሆናቸው ሕዝቡን የማደናገር ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። አንድነት በአንድ በኩል ለምርጫ ተመዝገቡ እያለ ለምርጫ ሲቀሰቀስ፣ ሰማያዊ ደግሞ በሌላ በኩል ቦይኮት ይደረግ እያለ የሚቀሰቅስ ከሆነ፣ በተቃራኒ ወገን ቆሙ ማለት ነው። የግድ አንድነቶች የሰማያዊ አማራጭ ትክክል እንዳለሆነ የማስተማርና የመቀስቀስ፣ በሐሳብ የማሸነፈ ሃላፊነት ይኖርባቸዋል።
ስለዚህ መከባበሩ፣ እንደተጠበቀ፣ ቢቻል ሁለቱም ወደ አንድ አቋም እንዲመጡ ቢነጋገሩና በጋራ ቢሰሩ፣ ካልሆነም ግን የግድ አንዱ ሐሳብ አሸናፊ ሆኖ መውጣት ስላለበት የፖለቲካ ክርክሮቹ በሰለጠነ፣ ከስሜትና ከስድብ በጸዳ መልኩ ቢደረጉ ጥሩ ሊሆን ይችላል።
ከዚህ በፊት እንደጻፍኩት፣ ሰማያዊ የወሰደው ቅድመ ሁኔታ የማስቀመጣ ፖለቲካና አቋም ስህተተ ነው ብዬ ነው የማምነው። አንዳንዶች በምርጫው መሳተፉን «ተለጣፊ» እንደመሆን እና ለአገዛዙ ሌጂቲመሲ(እውቅና) እንደመስጠት አድርገው የሚቆጥሩ አሉ። እነዚህ ወገኖች አንድነት ወደ ምርጫ በመግባቱ «ተለጣፊ» ሆኗል የሚል አስተሳሰብ ካላቸው፣ መለስ ብለው የሚሊዮኖችን ንቅናቄ እንዲመለከቱ እጋብዛቸዋለው። በአሁኑ ጊዜ የሕዝብን ትርታ የያዘ፣ በሆያ ሆዬ ላይ ሳይሆን፣ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ የሚያራምድ ፣ በሁሉም ክልሎች መዋቅር ያለው የፖለቲካ ድርጅት አንድነት ብቻ ነው። ሂዱ አርባ ምንጭ፣ ሂዱ ጂንክ፣ ሂዱ ወሊሶ፣ ሂዱ ጊምቢ፣ ሂዲ ጎንደር፣ ሂዱ አሳሶ፣ ሂዱ አዳማ፣ ሂዲ ሶዶ፣ ሂዱ ደሴ …አንድነትን በዚያ ታገኛላችሁ።
ለአገዛዙ ሌጂቲመሲ መስጠት ነው ለሚሉት ደግሞ ሌጂቲመሲ ሰጭው ማን እንደሆነ ቢነገሩን ጥሩ ነበር። በዉጭ ኃይሎች ዘንድ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሌጂቲሚስ ያገኛል የሚል ፍርሃት ከሆነ ያላቸው፣ በጣም የዲፕሎማሲ እወቀት ዴፊሸንሲ አለባቸው ማለት ነው። እነአሜሪካ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴጎች አምባገነን፣ በሕዝብ ያልተመረጡ፣ ድምጽ ሰርቀው ስልጣን ላይ ጠመንጃ ስለያዙ ብቻ፣ እየገደሉና እያሰሩ እንደሚገዙ ያውቃሉ። ሆኖም እውቅና ሰጥተዋቸው ዋይት ሃዉስ ድረስ ጠርተው እያስተናገዷቸው ነው። ለምን ሌላ፣ የተሻለ፣ ጥቅማቸውን የሚያስጤብቅ ኃይል ስለሌለ። እቅጩን እንወቅ፣ ቦይኮት ተደረገም አልተደረገም፣ ምርጫ ተገባም አልተገባም፣ አሜሪካም ሆነ አዉሮፓዉያን በአገዛዙ ላይ ያላቸውን አቋም አይለዉጥም። እነ አሜሪካ የፖሊሲ ለዉጥ የሚያደርጉት፣ ፊታቸውን ከሕወሃት/ኢሕአዴግ የሚያዞሩት፣ ተቃዋሚዎች ምርጫዉን ቦይኮት በማድረጋቸው ሳይሆን፣ ሕዝቡን አደራጅተው በሚሊዮኖች የሚቆጠሩትን ማነቃነቅ ከጀመሩ ብቻ ነው። ለዚህም ነው ምርጫ ከተገባ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሌጂቲማሲ እንዲያገኝ እናደርገዋለን የሚለው አስተያየት ዉህ የማይቋጥርና በእወቅት ላይ ያልተመሰረተ ነው የምለው።
ለጊዜው አበቃሁ !
የማለዳ ወግ …አስገራሚው ትዕይንት “በተስፋዋ” የአረብ ምድር በሳውዲ! – ነቢዩ ሲራክ
* የገቡት ይወጣሉ ፣ የወጡት ተመልሰው ይመጣሉ * የሳውዲ መንግስት “ህገ ወጦችን” የማጽዳቱ ዘመቻ ቀጥሏል * ስፍር ቁጥር የሌላቸው ዜጎች ከሞት ጋር ተፋጠው እየተሰደዱ ነው * የሳውዲ መንግስት ማስጠንቀቂያና እርምጃ … የሳውዲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውንና ህጉ በማይፈቅደው መንገድ የመኖሪያ ፈቃዳቸው ካለው ሙያ ውጭ የሚሰሩ የማናቸውንም ሀገር ዜጎች በመላ ሀገሪቱ ለማጽዳት የተደራጀ ዘመቻ ከተጀመረ ወር […]
አዲሱ የአዋሽ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ሆነ Awash Bridge Opens to Traffic
አዲስ አበባ ህዳር 26/2007 አዲሱ የአዋሽ ወንዝ ድልድይ ግንባታ በመጠናቀቁ ዛሬ ለትራፊክ ክፍት መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮ-ጅቡቲ መስመር 90 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ገቢና ወጪ ንግድ የሚስተናገድበት መንገድ ሲሆን በቀን ከ20 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችንም…
በሰላማዊ ሰልፈኛ ላይ ዱላ መሰንዘር ሽንፈት ነው›› እስክንድር ነጋ
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሰማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች በትብብሩ ውስጥ የታቀፉ ፓርቲዎች በጠሩት የአዳር ሰልፍ ላይ የወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የተወሰደውን አሳፋሪ እርምጃ ሰምቻለሁ፡፡ እርምጃው ሁለት ነገሮችን በጉልህ ያሳዬ ነበር፡፡ አንደኛ የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ሽንፍትን ያሳየ ነው፤ ሁለተኛው ደግሞ ሰላማዊ ትግሉ እየተጠናከረ መምጣቱን ያመላከተ ነው፡፡ አንተ ባዶ እጅህን መብትህን ለመጠየቅ ስትንቀሳቀስ፣ መሳሪያ ወደታጠቀ አካል በሰላም ስትገሰግስ […]
ህወሃት በመንግስት ወጪ 40ኛ አመቱን ለማክበር ሸርጉድ እያለ ነው
ታኀሳስ ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በከፍተኛ ዝግጅት ይከበራል የተባለው የህወሃት 40ኛ አመት በአል ወጪ የሚሸፈነው ከመንግስት ካዝና መሆኑ በአባል ድርጅቶች መካከል መነጋገሪያ አጀንዳ እየሆነ መምጣቱን የሚናገሩት የኢህአዴግ ምንጮች፣ ከመንግስት ካዝና ለሚወጣው ገንዘብ የተሰጠው ሰበብ ገጽታ ግንባታ የሚል መሆኑን ገልጸዋል። ህወሃት በአሉን ከድርጅቱ ካዝና በተለይም የአገሪቱን ሲሶ ሃብት ከተቆጣጠረው ኢፈርት ካዝና መጠቀም እየቻለ፣ ወጪውን …
በሃረር ከ10 ሺ በላይ ህገወጥ ቤቶች ይፈርሳሉ
ታኀሳስ ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ መንግስት የሃማኖት፣ የእድር፣ የአፎቻ መሪዎችን፣ የአገር ሽማግሌዎችንና ታዋቂ ግለሰቦችን በራስ መኮንን የህዝብ አዳራሽ ታህሳስ 5 ቀን 2007 ዓም ሰብስቦ ባወያየበት ወቅት ፣ ከ1990-2004 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰሩ ቤቶች በሰነድ አልባ ቤትነት የተመዘገቡ እና ከከተማው ማስተር ፕላን ጋር የማይጋጩ ከሆነ ህጋዊ ይደረጋሉ፣ ከ2004 ዓም እስካሁን ካርታና ፕላን …






