Tag: News in Amharic
የዘጠኝ ፓርቲዎች ትብብር ምርጫዉን ያለ ቅድመሁኔታ ለመሳተፍ መወሰናቸው የሚገልጹ ዘገባዎች እየወጡ ነው

በቅርቡ የአንድ ወር መርሃ ግብር አዉጥቶ ሲንቀሳቀስ የነበረው የሰማያዊ ፓርቲና የዘጠኝ ድርጅቶች ስብስብ፣ ፓርቲዎች ትብብር፣ ያለ ቅድሜ ሁኔታ በመጪው የ2007 ምርጫ እንደሚሳተፍ አሳወቀ። ትብብሩ ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡን የምገልጹ አንዳንድ ዘገባዎች በተለይም በዳያስፖራ አካባቢ የሚሰሙ እንደሆነ ቢታወቅም፣ የትብብሩ ዋና ጸሃፊ አቶ ግርማ በቀለ በፌስ ቡክ በግልጽ በሰጡት አስተያየት፣ ትብብሩ ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ አለማስቀመጡን ገልጸዋል።
“NO Precondition is set by members of Tibibir. We decided to be part of the election and advised all members to take their election Sign. Believe me, it is all the decision of Tibibir that is under action by its members and Blue is not an exception to present and decisions are being made in participatory process.” ሲሉ የትብብሩ አባል ድርጅቶች ለምርጫ የሚያስፈልገውን የምርጫ ምልክት በአስቸኳይ ለመዉሰድ መስማማታቸውንም አቶ ግርማ በቀለ ገልጸዋል።
በዚሁም መሰረት፣ የሰማያዊ ፓርቲንም ጨምሮ ሌሎች የትብብሩ አባል ድርጅቶች የምርጫ ምልክት ከሌሎች ድርጅቶች ቀድመው እንደወሰዱም የሚገልጹ መረጃዎች እየደረሱን ነው። ምርጫ ቦርድ ከአንድ ሳምንት በኋላ የድርጅቶቹን ምልክት ይፋ የሚያደርግ ሲሆን፣ የሰማያዊን ጨመሮ የሌሎች ድርጅቶች የምርጫ ምልክትም ምን እንደሆነ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ የትብብሩን ዉሳኔ አስፈላጊና ጠቃሚ ዉሳኔ ሲሉት፣ ሰማያዊ/ትብብሩ ወደ ምርጫ ያለ አንዳች ቅድሜ ሁኔታ ለመሳተፍ በመወሰኑም፣ በምርጫው ረገድ ከአንድነት ፓርቲ ተመሳሳይ አቋም እንደያዘ በግልጽ ያመላከት እንደሆነም አስረድተዋል።
“ያለ ቅድመ ሁኔታ ወደ ምርጫ ለመግባት ሰማያዊ/ትብብር ከወሰኑ፣ ለምርጫው መዘጋጀት አለባቸው። ድርጅታዊ ሥራ ላይ ማተኮሩ የድግ ነው። ተመሳሳይ ፕሮግራም ካላቸው ከነ አንድነት ጋር በምርጫው ረገድ መተባበር ያስፈልጋቸዋል” ሲሉ እኙ ተንታኝ ትብብሩ ወደ ምርጫ ከገባ ዘንዳ የምርጫ ዘመቻውን አብሮ ከሌሎች ጋር ለማቀናጀት እንዲዘጋጅም ጠይቀዋል።
በተያይዘ ዜና የአንድነት ፓርቲ የምርጫ ታዛቢዎች በማስመረጥ ዙሪያ በተቻለ መጠን ገለልተኛ የሆኑ የሕዝብ ታዛቢዎች እንዲመረጡ ለማድረግ በየዞኖቹና በየወረዳዎች ስምሪት እንደጀመረም ለማወቅ ችለናል።
አቡጊዳ
የኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናትን በጨረፍታ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ሲጠቀሱ በቅድሚያ የሚታወሱት በላስታ አውራጃ፣ በ“ሮሃ” (ላሊበላ) ከተማ አጠገብ ከአንድ-ወጥ ድንጋይ ተፈልፍለው የተሰሩት አስራ አንድ ቤተ ክርስቲያናት ናቸው፡፡ የአስራ አንዱ ቤተ ክርስቲያናት ስም እንደሚከተለው ነው፡፡አቡጊዳ – ሰማያዊ/ትብብሩ ምርጫዉን ያለ ቅድመ ሁኔታ ለመሳተፍ መወሰናቸው ታወቀ
በቅርቡ የአንድ ወር መርሃ ግብር አዉጥቶ ሲንቀሳቀስ የነበረው የሰማያዊ ፓርቲና የዘጠኝ ድርጅቶች ስብስብ፣ ትብብር፣ ያለ ቅድሜ ሁኔታ በመጪው የ2007 ምርጫ እንደሚሳተፍ አሳወቀ። ትብብሩ ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡን የምገልጹ አንዳንድ ዘገባዎች በተለይም በዳያስፖራ አካባቢ የሚሰሙ እንደሆነ ቢታወቅም፣ የትብብሩ ዋና ጸሃፊ አቶ ግርማ በቀለ በፌስ ቡክ በግልጽ በሰጡት አስተያየት፣ ትብብሩ ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ አለማስቀመጡን ገልጸዋል። “NO Precondition […]
የኢቦላ ዘማቾች ተሸኙ
ኢቦላን ለመዋጋት ወደ ምዕራብ አፍሪካ ይጓዛሉ ለተባሉት ከ200 በላይ ሐኪሞችና ሌሎችም ባለሙያዎች አሁን በአዲስ አበባ ሂልተን አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል፡፡
የኢትዮጵያን የኢቦላ ምላሽ የሚያስተባብረ ው የማኅበረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አቤል የሻነህ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ ሽኝቱ የተዘጋጀው ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዘማቾች ነው፡፡
ኢትዮጵያዊያኑ ባለሙያዎች ወደ ምዕራብ አፍሪካ የሚጓዙት የአፍሪካ ኅብረት ፀረ-ኢቦላ ምላሽ አካል ሆነው እንደሚሆን ተገልጿል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ እስከአሁን የኢቦላ ተጠርጣሪም ሆነ የወረርሽኙ ምልክት ኢትዮጵያ ውስጥ አለመታየቱ በአይሮፕላን ጣቢያዎች ላይ እየተካሄደ ያለው ፍተሻና ክትትልም እንደቀጠለ መሆኑን ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የሱዳን ባለሥልጣናት የአልበሽርን “ንፁህነት” እየተናገሩ ነው
ዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት – አይሲሲ አቃቤ ሕግ ዳርፉር ውስጥ የሚያካሄዱትን ምርመራ ለጊዜውም ቢሆን እንደሚያቋርጡ ከገለፁ በኋላ የሃገሪቱ “ፕሬዚዳንት ኦማር ሃሰን አልበሽር ንፁህ ሰው ስለመሆናቸው ማረገገጫ ነው” ሲሉ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አሕመድ ቢላል አስታውቀዋል፡፡
የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አልበሽርን “የሰላም ሰው” ብለዋቸዋል ዛሬ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ፡፡
ዳርፉር ላይ ሲያካሂዱ የቆዩትን ምርመራ እንደሚያቆሙ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ፋቱ ቤንሱዳ ያሳወቁት “ለጊዜውም ቢሆን” በሚል ቢሆንም የማስታወቂያ ሚኒስትሩ ግን ይህ የቤንሱዳ ውሣኔ ከኦማር ሁሴን አል በሽር የሚገኝ “አንዳች ጥፋት ላለመኖሩ ማረጋገጫ ነው” ሲሉ የድል ብሥራት ከማውጣት አልቦዘኑም፡፡
አቃቤ ሕጓ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ባለፈው ሣምንት ሲናገሩ…
የኢቦላ ዘማቾች ተሸኙ – ዲሴምበር 16, 2014
Ethiopia – Ebola – medics – farewell
የሱዳን ባለሥልጣናት የአልበሽርን “ንፁህነት” እየተናገሩ ነው – ዲሴምበር 16, 2014
Sudan – Vindication – ICC
የመድረክ የተቃውሞ ሰልፍ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራስያዊ አንድነት መድረክ ትላንት በአዲስ አባባ ባካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በመጪው ግንቦት የሚካሄደው ምርጫ ነጻና ፍትሀዊ እንዲሆን ጠየቀ።
የታሰሩ የፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጣኞችና የሙስሊሙ ህብረተሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እንዲፈቱም ጥሪ አቅርቧል። የዘገባውን ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ፤
የ‹‹መድረክ›› ሰልፍ እንድምታ
(ቢልልኝ ሀብታሙ አባቡ) የተቃዋሚዉ ጎራን በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት አብይት ፖለቲካዊ ክስተቶችን አስተናግዷል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ትግል ሲኮላሽ የመድረክ ደግሞ ቀዝቀዝ ያለ በሚመስል መልኩ ተስተናግዷል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ ፕሮግራም በተስተጓጎለ በሳምንቱ የመድርኮቹ መሳካቱ ምን ሊያመላክት ይችላል የሚለውን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የመድርኩን ሰልፍ ከራሱ ከመድርክ፣ ከመንግስትና ከህዝብ አንፃር ሊኖረው የሚችለውን እንድምታ አጠር ባለ መልኩ ለማየት እንሞክራለን፡፡ ሀ) ከመድረክ አንፃር መድርክ ከሌሎችና ፓርቲዎችና ከራሱም ያለፈ የትግል ልምድ የተማረው ነገር ያለ ይመስላል፡፡ ፓርቲው ቀድሞ ከነበረበት ጽንፍ ይዞ የመታገል አቅጣጫ በተወሰነ መልኩ ለዘብ እያለ መምጣት የሚያሳዩ ሁሄታዎችን መታዘብ ይቻላል፡፡ መድረክ ከሌጋሲው የተማረው ጉዳይ ቀድም ሲል በነበው ፅንፍ ይዞ የመታገል አቅጣጫ የመንግስትን የቁጥጥር ጫና እንዲሚያጠብቀው ሳይማር እንዳልቀረ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ባልተለመደ መልኩ ሌሎች ተቃዋሚዎች ክፉኛ የሚጥሉትንና መንግስት እየተጠቀመበት ያለውን ባንዲራ በሰልፍ ውስጥ መጠቀሙ በተወሰነ መልኩ ከአክራሪነት ለዘብ ያለ አቋም እያሳየ ለመምጣቱ ማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡ ፓርቲው ወዶም ይሁን ተገዶ በወሳኝ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከኢህአዴግ ጋር መመሳሰል ባይችል እንኳን መንግስት ከሚፈልገው የአቋም መለሳለስ ደረጃ ላይ ሊደርስ እንደሚችል የሚጠቁሙ ፍንጮች እንዳሉ መውሰድ ይቻለላል፡፡ በሌላ መልኩ መድረክ የሰላማዊ ሰልፉን ዉጤት ተከትሎ መንግስት የሚሰጋባቸውን ችግሮች እንዳይከሰቱ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ ለማድርግ ከመንግስት ጋር ስምምንት ላይ ሳይደርስ እንዳልቀረ የሚያመላክቱ ነገሮች አሉ፡፡ በአቋም እየተለሳለሰ መምጣቱና ለሰልፉ ኃላፊነቱን ከመንግሰት ጋር መጋራቱ ሰልፉን ስኬታማ ለማድረግ ሳይግዘው እንዳልቀረ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በ2002 ምርጫ ከኢህአዴግ ጋር […]
የሳምንቱ የስፖርት ዜናዎች!
ኤርትራዊው አትሌት ሣሙኤል ፀጋዬ በQuantinar አገር አቋራጭ አሸነፈ።
አቶ ሽመልስ ከማል ከአቶ ሬድዋን ሁሴን ጋር በመጋጨታቸው አኩርፈው ቤት መቀመጣቸው ተሰማ
አቶ ሽመልስ ከማል ከአቶ ሬድዋን ሁሴን ጋር በመጋጨታቸው አኩርፈው ቤት መቀመጣቸው ተሰማ
የመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል ከ ሚኒስትሩ ሬድዋን ሁሴን ጋር መግባባት ባለመቻላቸው አኩርፈው ቤት በመቀመጥ መደበኛ ሥራቸውን እያከናወኑ አለመሆኑን ምንጮች ገልጸዋል።
አቶ ሽመልስ ከደባል ሱስ ጋር በተያያዘ በመደበኛ የስራ ሰዓታቸው ሊገኙ ባለመቻላቸው ሚኒስትሩ ይህን ባህሪያቸውን እንዲያስተካክሉ ቢነግሩዋቸውም ሊያስተካክሉ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የተፈጠረ መሆኑን ምንጮች ይገልጻሉ።የአቶ ሽመልስን ሃላፊነት ደርበው እየሰሩ ያሉት በቅርቡ ከዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዳይሬክተርነት ተነስተው የመንግስት ኮምኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን የተሾሙት አቶ እውነቱ ብላታ ናቸው።
አቶ ሽመልስ በቅርቡ የታዩት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ ሊቀመንበር በመሆናቸው በድርጅቱ ስብሰባ ላይ ብቻ ነው፡፡ የፕሬስ ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሰብስቤ ከበደ ከአቅም ማነስና የመልካም አስተዳደር ችግር ጋር ተያይዞ በድርጅቱ ጋዜጠኞች እየቀረበባቸው ያለውን ግልጽ ትችትና ቅሬታ በተደጋጋሚ ስብሰባዎች ላይ በመገኘት ከማስተባበላቸውም በተጨማሪ ጥያቄውን የሚያነሱ ጋዜጠኞችን እስከማስፈራራት የደረሰ ንግግር ሲያደርጉ የተሰሙት አቶ ሽመልስ፣ መደበኛ ስራቸውን መተዋቸው በኮምኒኬሽን መ/ቤቱ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖአል፡፡
አቶ ሽመልስ ከማል በአቶ በረከት ስምኦን ደጋፊነት የብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ስራአኪያጅ የነበሩ ሲሆን፣ የ97 ምርጫን ተከትሎ የቅንጅት አመራሮችና ጋዜጠኞች በተከሰሱ ወቅት አቃቤ ሕግን ወክለው ሐሰተኛ መረጃዎች እንዲቀርቡና ሐሰተኛ ምስክሮችን በገንዘብ በመግዛትና በመደለል ለኢህአዴግ ውለታ ለመስራት የጣሩ ሰው መሆናቸው ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጅ አቶ በረከት ከጤና ጋር በተያያዘ ስራቸውን እየተዉ በመምጣታቸው አቶ ሽመልስ ብቸኛው ደጋፊያቸውን አጥተዋል። አቶ ሽመልስ አቶ በረከትን የመተካት ህልም ቢኖራቸውም ሳይሳካላቸው አቶ ሬድዋን ቦታውን እንዲወስዱ ተደርጓል። በሁለቱ ባለስልጣኖች መካከል ባለው ልዩነት የተነሳ፣ አቶ ሽመልስ ከስራቸው የሚባረሩበት ቀን እሩቅ ላይሆን እንደሚችል ወይም በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን በመልቀቅ ከአገር ለመውጣት ሙከራ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ታዛቢዎች ይገልጻሉ። የአቶ ሽመልስ የስልጣን ቆይታ በከፍተኛ ህመም ከሚሰቃዩት ከአቶ በረከት ስምኦን ህልውና ጋር የተያያዘ መሆኑን ታዛቢዎች ይናገራሉ።
ታኀሳስ ፮(ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና
ታህሳስ 4,2007 የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም(December 13,2014) – ዲሴምበር 15, 2014
የዛሬው የሙዚቃ ቃና ፕሮግራም በአሜሪካ የቢል ቦርድ ሰንጠረዥ ላይ ከመቶዎቹ ምርጥ ዜማዎች መካከል በዚህ ሳምንት ከአንድኛ እስከ ሶስትኛ ደረጃ የወጡትን ምርጥ ዜማዎች እና የ Taylor Swift ን ዜማዎች ያካትታል፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 15, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
መድረክ በአዲስ አበባ የተሳካ የተቃውሞ ሰልፍ አካሄደ
ታኀሳስ ፮(ስድት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመድረክ የህዝብ ግንኙነት ሃለፊ አቶ ጥላሁን እንዳሻው የገዢው ፓርቲ የጸጥታ ሃይሎች ሲያደርሱት ከነበረው ጫና አንጻር ሲታይ የተሳካ የሚባል ሰላማዊ ሰልፍ መደረጉን ገልጸዋል። መጪው ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ እንዲሆን፣ የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች እረገጣ እንዲቆም፣ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እንዲፈቱ በመፈክሮች መጠየቃቸውን ገልጸዋል። በሰልፉ ላይ …
አየር መንገድ የሰማያዊ ፓርቲ የፋይናንስ ክፍል ሃላፊን ከስራ አባረረ
ታኀሳስ ፮(ስድት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአየር መንገድ ውስጥ ሱፐርቫይዘር አፒራንስ በሚል የሃላፊነት ቦታ ላይ ሲሰሩ የነበሩት አቶ ወረታው ዋሴ ሃላፊነታቸውን በአግባቡ አልተወጡም በሚል በፈረንጆች አቆጣጠር ከዲሰምበር 8፣ 2014 ጀምሮ ከስራቸው እንደተባረሩ የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሶአቸዋል። አቶ ወረታው በበኩላቸው ውዝግቡ የቆየ መሆኑን በማንሳት ፣ አየር መንገዱ የወሰደው እርምጃ ከፖለቲካ አቋማቸው ጋር የተያያዘ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ …
አቶ ሽመልስ ከማል ከአቶ ሬድዋን ሁሴን ጋር በመጋጨታቸው አኩርፈው ቤት መቀመጣቸው ተሰማ
ታኀሳስ ፮(ስድት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል ከ ሚኒስትሩ ሬድዋን ሁሴን ጋር መግባባት ባለመቻላቸው አኩርፈው ቤት በመቀመጥ መደበኛ ሥራቸውን እያከናወኑ አለመሆኑን ምንጮች ገልጸዋል። አቶ ሽመልስ ከደባል ሱስ ጋር በተያያዘ በመደበኛ የስራ ሰዓታቸው ሊገኙ ባለመቻላቸው ሚኒስትሩ ይህን ባህሪያቸውን እንዲያስተካክሉ ቢነግሩዋቸውም ሊያስተካክሉ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የተፈጠረ መሆኑን ምንጮች ይገልጻሉ። …
ሁለትም አንድም ናቸዉ
ሁለቱ፤ በአንዱ-ዓለም አቀፍ አስተሳሰብ አንድ የሆኑበት ሰበብ ምክንያት አንድም አጋጣሚ-አለያም «ትንኝም ለሆዷ፤ ዝሆንም ለሆዱ —-» እንዳለዉ ኢትዮጵያዊዉ ባለቅኔ ካልሆነ በስተጠቀር ብዙም ትንታኔ የለዉም።
የሲድኒው የእገታ ጥቃት ማብቃት
በኦስትሬሊያ የሲድኒ ከተማ አንድ ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ ዛሬ ንጋት ላይ በርካታ ሰዎችን ያገተበትን አንድ ቡና ቤት የከተማይቱ ፖሊስ ከጥቂት ጊዜ በፊት ማጥቃቱ እና በዚሁ ጊዜም ሁለት ሰዎች፣ መገደላቸውን፣ እንዲሁም ፣ ሶስት በጠና መቁሰላቸው ተገለጸ። ከተገደሉት መካከል አንዱ አጋቹ ነው።
የክርስትናና የእስልምና ጥንታዊ የእጅ ጽሑፍ ጥናት
ከ 12 ተኛዉ እስከ 20ኛዉ ክፍለ ዘመን በብራና ላይ የተፃፉ የኢትዮጵያ የክርስትናና የእስልምና ጥንታዊ የእጅ ጽሑፎች ላይ የተደረጉ ጥናቶችን በንጽጽር ያቀረበና የታሪክ ምሁራን የተሳተፉበት ዐውድ ጥናት
የቤልጅግ የ24 ሰዓት አጠቃላይ የሥራ ማቆም አድማ
በቤልጅግ ፤ ሶስት ሚሊዮን ገደማ አባላት ያሏቸው ሶስት ትላላቅ የሠራተኞች ማሕበራት በጠሩት የ 24 ሰዓት የሥራ ማቆም አድማ መሠረት፤ መዲናይቱን ብራሰልስን ጨምሮ አገሪቱ በመላ የሥራ እንቅሥቃሤዋ ተገትቶ ውሏል።
በዩናይትድ ስቴትስ የተጠናከረዉ ተቃዉሞ
ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ በተከታታይ መሣሪያ ያልያዙ ጥቁሮች በነጭ ፖሊሶች መገደላቸዉ ያስነሳዉ ተቃዉሞ እንደቀጠለ ነዉ።
የ«አይ ሲ ሲ» ዉሳኔና የፕሬዚዳንት ኦማር ኧል በሽር ድል
ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት «አይ ሲ ሲ» በሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ኧል በሽር ላይ የጣለዉን የጦር ወንጀልነት ክስ ለተወሰነ ጊዜ ማቋረጡን አስታዉቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራርን ከስራ አባረረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰማያዊ ፓርቲ የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ የሆኑትን አቶ ወሮታው ዋሴን ከስራ አባረረ፡፡
ከሁለት አመት በፊት በኢሜል ለህዳሴው ግድብ ገንዘብ እንዲያዋጡ በተጠየቁበት ወቅት ለተላከው የኢሜል መልዕክት አልከፍልም ብለው በመመለሳቸው ‹‹ሰራተኛ በማሳመጽ፣ የኢንዱስትሪ ሰላም በማናጋት›› በሚል ተከሰው ተባርረው በፍርድ ቤት ወደ ስራ መመለሳቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡አቶ ወሮታው ከስራ የተባረሩት ጥፋት ያጠፋን ሰራተኛ አልቀጣህም በሚል ሲሆን በእሳቸው ስር የነበረውና አጠፋ የተባለው ሰራተኛ ጉዳይ ተመርምሮ ወደ ስራ መመለሱ ታውቋል፡፡
አቶ ወሮታው ከእሳቸውም በላይ ጉዳዩ የሚያገባው የማኔጅመንት አባል በተመሳሳይ ጉዳይ የአምስት ቀን ደመወዝ ብቻ ሲቀጣ እሳቸው ከስራ መባረራቸው በፖለቲካ አመለካከታቸው ላይ የተመሰረተና ፖለቲካዊ ውሳኔ እንደሆነ ያሳያል ብለዋል፡፡ ከስራቸው ይሰራ የነበረው ሰራተኛ ጥፋተኛ አለመሆኑን የገለጹት አቶ ወሮታው ‹‹በፖለቲካ አመለካከቴ ምክንያት ሁልጊዜም እኔን ማባረር ይፈልጋሉ›› ሲሉ የተባረሩት በፖለቲካ አመለካከታቸው እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
አቶ ወሮታው ዋሴ ከሁለት አመት በፊት በኢሜል ለህዳሴው ግድብ ገንዘብ እንዲያዋጡ በተጠየቁበት ወቅት ለተላከው የኢሜል መልዕክት አልከፍልም ብለው በመመለሳቸው ‹‹ሰራተኛ በማሳመጽ፣ የኢንዱስትሪ ሰላም በማናጋት›› በሚል ተከሰው ተባርረው ከሁለት አመት በኋላ በፍርድ ቤት ወደ ስራ መመለሳቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በወቅቱ አየር መንገድ አቶ ወሮታው ዋሴ ካሳ ተከፍሏቸው እንዲለቁ ይግባኝ ጠይቆ የነበር ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለሁለት አመት ካራዘመ በኋላ ወደ ስራ እንዲመለሱ አዝዞ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ ጥፋተኛ ነው ብሎ ያባረራቸው አየር መንገድ ወደ ስራ በተመለሱ በ15 ቀናት ውስጥ ሰርተውበት ወደማያውቁት ክፍል በማዘዋወር እድገት አግኝተው የማኔጅመንት አባል እንደሆኑ እንደገለጸላቸው የሚናገሩት አቶ ወሮታው እድገቱ ሰራተኛ ሲባረር የመክሰስ መብት ስላለው፣ በተቃራኒው ግን ሳይፈልጉት በእድገት የማኔጅመንት አባል እንዲሆኑ የተደረገው የማኔጅመንት አባል የሆነ ግለሰብ ቢባረርም የመክሰስ መብት የሌለው በመሆኑ ሆን ተብሎ ለማባረር የተደረገ ስልት ነው ብለዋል፡፡ አቶ ወሮታው በወቅቱ ይህን እድገት አልቀበልም ብለው እንደነበርም ገልጸውልናል፡፡
አቶ ወሮታው ዋሴ አሁን ከስራ ባባረራቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ለ14 ዓመታት ያህል ማገልገላቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ትግራይ ትናፍቃለች!
ፍኖተ ነጻነት ቁጥር 88
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
የአንድነቱን ጉባዔ በወፍ በረር – ከዳንኤል ተፈራ
እንደ መነሻ ከሁለት ወር በፊት አንድነትን እንዲመሩ በጠቅላላ ጉባዔ የተመረጡት ኢ/ር ግዛቸው ሺፈራው ጥቅምት ሁለት ቀን 2007 ዓ.ም ካቢኔያቸውን በትነው ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለብሔራዊ ምክር ቤቱ አስረከቡ፡፡ የቀድሞው ፕሬዘዳንት ኢ/ር ግዛቸው ለምክር ቤቱ ባሰሙት ንግግር በአመራራቸው ያልተደሰቱ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎችን የ‹‹ልቀቅ›› ጫና መቋቋም እንዳልቻሉና ከህሊናቸው ጋር ተማክረው ለፓርቲው ጥቅም ሲባል በፈቃዳቸው ሃላፊነታቸውን […]
በውንብድና መብታችንን ለድርድር አናቀርብም! ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

በአፈና፣ በኃይል እርምጃና በውንብድና መብታችንን ለድርድር አናቀርብም!
ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ #Ethiopia #NegereEthiopia #Miniliksalsawi
• ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
እኛ 9 ፓርቲዎች በትብብር ለመሥራት በፈጸምነው ስምምነት ያወጣነውን የጋራ ዕቅድ ለማስፈጸም ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ስንገባ ህገ መንግስቱ፣ የምርጫና የሰላማዊ ሠልፍና ህዝባዊ ስብሰባ አዋጆች በሚፈቅዱት መሰረት ያቀረብናቸውን ጥያቄዎች በቢሮክራሲያዊ ሴራና ማስፈራራት ለማፈን የአዲስ አበባ መስተዳድር የተከተለውን ህገወጥ አካሄድና ይህንኑ ተከትሎ የተወሰዱትን የኃይል እርምጃዎች በሚመለከት ፡-
1ኛ/ ‹‹በቢሮክራሲያዊ ሴራ የዜጎችን ህገመንግሥታዊ መብት ማፈን ሠላማዊ ትግሉን አያቆመውም !!››በሚል ርዕስ ሕዳር 08 ቀን 2007 ዓ.ም.
2ኛ/ ‹‹ማስፈራራትና አፈና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችንና ሠላማዊ ሕዝባዊ የለውጥ ንቅናቄዎችን አይቀለብስም!!›› በሚል ርዕስ ሕዳር 17 ቀን 2007 ዓ.ም. መግለጫዎች ማውጣታችን፣ እንዲሁም በአባል ፓርቲዎቻችንን አማካኝነት –
1. ‹‹ የህገ መንግሥቱ የበላይነትና የዜጎች ህገ መንግሥታዊ መብት እንዲረጋገጥ ›› ለተከበሩ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ፣
2. ‹‹በአገሪቱ ህገመንግሥትና ህጎች የተረጋገጡ የዜጎች መብቶች እንዲተገበሩ ›› ለተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ህዳር 24/2007 ዓ.ም ጥያቄ ማቅረባችንና በግልባጭ ለ- ኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብት ኮሚሽን፣- የህዝብ እንባ ጠባቂና -ሰብዐዊ መብት ጉባኤ ማሰማታችን ይታወሳል፡፡
የእነዚህ መግለጫዎችም ሆነ ደብዳቤዎች ይዘት ሲጠቃለል ‹‹የአገሪቱ ህገመንግሥት ይከበር ›› የሚል ጥያቄና መስተዳደሩ በሚወስዳቸው ህገወጥ እርምጃዎች ከያዝነው ህጋዊና ሠላማዊ ትግል የማናፈገፍግና የትኛውንም መስዋዕትነት በመክፈል ለህገመንግሥታዊ መብታችን መከበር የጀመርነውን የጋራ ትግል እንደምንገፋበት፣ የአዲስ አበባ መስተዳድር ከህገ ወጥ ድርጊቱ እንዲታረም፣ ጥሪ ማቅረብና ግልጽ አቋማችንን ማሳየት ነበር፡፡ በዚሁ ሂደት ያጋጠሙንን ህገወጥ ድርጊቶች በሙሉ በዝርዝር ለህዝባችንና ለባለድርሻ አካላት በሙሉ በፕሬስ ሬሊዞችና ዕለታዊ የውሎ ዘገባና ዜናዎች አድርሰናል፡፡ ግን ሰሚ ጆሮ ሊናገኝ አልቻልንም፡፡ የአዲስ አበባ መስተዳድር የመረጠው መንገድ ለጥያቄዎቻችንና ጥሪዎቻችን ተገቢውን ህጋዊ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በህገ ወጥ ድርጊቱ መግፋትና ጥያቄዎቹን በኃይል እርምጃ ማፈን ነው፡፡ አፈ ጉባኤውም ሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምንም ባለማለታቸው መስተዳድሩ ‹‹በያዝከው ግፋበት ፈቃድ›› በማግኘቱ ለበለጠ ህገወጥነትና የኃይል እርምጃ በመበረታታት ለህዳር 27 እና 28 ቀን 2007 በጠራነው ህጋዊ ሠላማዊ ሠልፍ ሂደት ላይ በሰጠው ከመንግሥት የማይጠበቅ የቅጥፈት መግለጫ ፣ በዕለቱ በሠላማዊ ዜጎች ላይ በተወሰደው አረመኔኣዊ እርምጃና ጥይት እራሱ ገሎ እራሱ ይጮኃል እንዲሉ በንጹኃን የመብት ጠያቂ ዜጎች ላይ የተለመደውን የፈጠራ ክስ ለመፈብረክ በተጠቀመው ነጭ ውሸት አረጋግጧል ፡፡ የአብነት ማሳያዎችም–
1. ኢቲቪ/ኢብኮ/ ሰሚ ባላገኘው የ‹‹ማስፈራሪያ›› ማስጠንቀቂያው ‹‹በሌላ ቦታ እንዲያደርጉ›› የቀረበላቸውን አማራጭ ባለመቀበልና እዚያው ካልሆነ ሞተን እንገኛለን በማለት ‹‹አሉ›› ያለው እኛ ዓርብ(26/03/07) ከሰዓት በኋላ እስከ ቀኑ 10፡30 ድረስ ውሳኔ ከማይሰጡ (ሥልጣኑ ከሌላቸው) የመስተዳድሩ ሹማምነት ጋር ቆይተን ‹‹የማሪያም በር›› ልንሰጣቸው ከሞከርነው ጋር የማይጣጣምና መግለጫው ‹‹ ባይበላስ ቢቀር›› የሚያስብል መሆኑ፤
2. ከ80 በላይ ንጹኃን የመብት ጤቂ ዜጎች ላይ የተፈፀመው እስራትና ከ50 በላይ በሆኑት ላይ የ ለማመንና መቀበል የሚያስቸግርና (በተለይ በሴት እህቶቻችን ላይ)አረመኔያዊ ድብደባ (ፖሊስ ጣቢያ ግቢ ውስጥ ጭምር) በተፈጸመበት የተሞከረው ‹‹ ከባድ የኮንስትራክሽን መሣሪያ በኪሳቸው ደብቀው›› ልማቱን አደናቀፉ ዓይነት የፈጠራ ውንጀላና ክስ ማቅረባቸውን፤ መጥቀስ ብቻ ይበቃል፡፡
በመሆኑም መስተዳድሩ ከሠልፉ ዕለት በፊትና እስከዛሬ እነዚህን ዓይን ያወጡ ህገመንግሥቱን የደፈጠጡ የአደባባይ እውነታዎች ለመሸፈን በፓርቲዎች ላይ በተለመደው መንገድ በህዝብ ሃብት የሚተዳደሩትን የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን በተለይም ኢቲቪ/ኢብኮ/ በመጠቀም በሰራው የበሬ ወለደ ፕሮፖጋንዳ ማንነቱን ፍንትው አድርጎ ለህዝብ አሳይቷል፣ ራቁቱን አስቀርቶታል፣ተጋልጦበታል፡፡
በእኛ በኩል ከሂደቱም ሆነ ከተወሰደው እርምጃና ከተሞከረው ርካሽ ፕሮፖጋንዳ ለቀጣዩ የጋራ ትግላችን ብዙ ተምረንበታል፤ አስተምረናል፣አትርፈንበታል እንጂ ከዓላማችን አልተገታንም፣ ቃላችንን አላጠፍንም፡፡በመሆኑም
1. ከዚህ በኋላ ለሰልፍም ሆነ ስብሰባ ገዢው ፓርቲ በዘመናት በማለማመድ ፈቃጅ ሆኖ ለመታየት ያደረገውን ጥረት ሰብረን ዕውቅና ከመስጠት ያለፈ ህጋዊ ሥልጣን የሌለው መሆኑን እንዲያውቅ/እንዲማር አድርገናል፤
2. በማስፈራራት ትግሉን መግታት እንደማይቻልና ለዚህም ለነጻነታቸውና ክብራቸው የቱንም መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ታጋዮች በተለይም ወጣቶች መኖራቸውን አሳይተናል፤
3. የህዝቡ የለውጥ ፍላጎት የደረሰበትን ደረጃና የንቃተ ኅሊና መዳበር ከክልል ጭምር በመምጣት በጋራ ትግሉ በመሳተፍና የትግል አጋርነታቸውን በመግለጽ ባደረጉት አስተዋጽኦና በመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ፕሮፖጋንዳ ያለው እምነት መሟጠጡን ፣እንዲሁም የገዢው ፓርቲ በሠላማዊ ትግል ያደረበትን የፍርኃትና ሥጋት ደረጃ ለክተንበታል፤
4. ህዝቡ ለፈጠራ ወንጀሎች እንዳይፈራና ይልቁንም በመንግሥት አሠራርና አመራር ላይ ያለው እምነት ከጥያቄ እንዲወድቅ፤ፖሊስንና ፍርድ ቤቶችን ጨምሮ አስፈጻሚ አካላት ያለባቸውን ተጠያቂነት እንዲረዱና ራሳቸውን እንዲጠይቁ የሚያስችል ስሜት ፈጥረናል፤
በአጠቃላይ የገዢውን ፓርቲ እየባሰ የመጣውን አምባገነናዊ ባህሪይ አጋልጠን ፣ኢትዮጵያዊያን ለተባበረ የጋራ ትግል ያላቸውን ድጋፍ በተግባር ተመልክተን፣ የጀመርነው የ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› ፕሮግራማችንን ትክክለኛለትና ተቀባይነት ለክተን ትግሉ ወደማይቀለበስበት የላቀ ደረጃ መሸጋገሩን አረጋግጠናል፡፡ስለሆነም የጋራ ትግላችንን አጠናክረን በበለጠ ጽናትና የኃላፊነት መንፈስ በጥበብ በመምራት እንደምንቀጥል እያረጋገጥን የሁለተኛውን ዙር ፕሮግራም ዕቅድ በቅርብ ጊዜ እንደምናሳውቅ እየገለጽን –
1ኛ/ በአገር ቤትና በውጪ የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ከጎናችን በመቆም ላደረጋችሁት ሁለንተናዊ ድጋፍ፣ በአምባገነኑ ሥርኣት የተወሰደብንን አረመኔያዊ እርምጃ በመቃወም በሰልፍ፣ በመግለጫ፣በታሰርንበት አስፈላጊውን በማቅረብና ተመላልሳችሁ በመጠየቅ … የትግሉ ባለቤትነታችሁን ላረጋገጣችሁና አጋርነታችሁን ለገለጻችሁና ላኮራችሁን ክፍ ያለ ምስጋናችን እያቀረብን፣በዚህ ረገድ ድምጻችንን ከህዝባችንና ከዓለም ህዝብ ዘንድ በማድረስ ፣ከወገኖቻችን ጋር በማወያየት ከፍተኛውን ሚና ለተጫወታችሁ በአገር ቤትና በውጪ ለምትገኙ መገናኛ ብዙኃን አድናቆታችንን እየገለጽን በቀጣዩ ፕሮግራማችንም ከጎናችን እንድትቆሙ ፣
2ኛ/ገዢው ፓርቲ/መንግሥት የወሰደውን ኢህገመንግሥታዊና ህገወጥ እርምጃና አሰራር አጥብቀን እየተቃወምን፣ይህ ዓይነቱን ለማንም የማይበጅ አካሄድ መርምሮና የህዝቡን የለውጥ ፍላጎት ተረድቶ ቆም ብሎ ራሱን እንዲፈትሽ፣ከገባበት ፍርኃትና ሥጋት ተላቆ ለህዝብ ጥያቄዎች ተገቢውን ወቅታዊ ምላሽ በመስጠት ህገመንግሥቱን አክብሮ እንዲያስከብር፤
3ኛ/ የዓለም አቀፉ ማኅበረ ሰብ አባላትም ተገቢውን አዎንታዊ ተጽዕኖ በገዢው ፓርቲ/መንግሥት ላይ በማሳረፍ ለሰብዐዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች መከበርና ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታበረክቱ፤ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ያለመስዋዕትነት ድል የለምና ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ተደራጅ 2007 ለለውጥ – አንድነት
አንድነት በነገው ዕለት ተደራጅ 2007 ለለውጥ የሚል ዘመቻ በሶሻል ሚዲያና መዋቅሩ በዘረጋባቸው የሀገሪቱ አከባቢዎች ሁሉ ይጀምራል! የዚህ ዘመቻ ዓላማ በቀጣዩ ምርጫ ፓርቲው አሸናፊ ሆኖ አንዲወጣ የሚያደርጉት ህዝባዊ ንቅናቂዎች ለመፍጠር ያለመ ሲሆን፤ ህዝቡ በምርጫው ሂደት ከመጀመሪየው ጀምሮ ተሳታፊ እንዲሆን በፓርቲው በአባልነትና በደጋፊነት እንዲደራጅና በንቃት እንዲሳተፍ ያደርጋል። ህዝቡ ተደራጅቶ ታህሳ 12 በሚደረገው የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ ላይ ቤቀበሌው […]
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 14, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
ኢትዮጵያ እና ዪሮ ቦንድ የመሸጥ ዕቅዷ
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአሥር ዓመት አንድ ቢልዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ በ6,6% በሆነ ወለድ ለዓለም አቀፉ ገበያ እንደምታቀርብ ሰሞኑን ይፋ አድርጋለች። የዚሁ ውሳኔዋ ትርጓሜ፣ ጥቅሙን እና ተፅዕኖውን በተመለከተ ከባለሙያዎች ጋር ውይይት አካሂደናል።
መድረክ በአዲስ አበባ ያዘጋጀው ሠልፍ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ በአዲስ አበባ ያዘጋጀው ሠልፍ ዛሬ ከግንፍሌ አካባቢ ተነስቶ 22 አካባቢ በሚገኘው ወረዳ 8 ሜዳ ላይ መጠናቀቁ ተገለጠ።
‹‹በአፈና፣ በኃይል እርምጃና በውንብድና መብታችንን ለድርድር አናቀርብም!›› የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሁለተኛ ዙር መርሓ ግብሩን በቅርቡ እንደሚጀመር አስታወቀ

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሁለተኛ ዙር መርሓ ግብሩን በቅርቡ እንደሚጀመር አስታወቀ
‹‹ገዥው ፓርቲ ከፍርኃት ተላቆ ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት አለበት!››
ከህዳር ወር 2007 ዓ.ም ጀምሮ የአንድ ወር መርሓ ግብር ነድፎ ሲንቀሳቀስ የቆየው የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በዛሬው ዕለት ታህሳስ 5/2007 ዓ.ም ‹‹በአፈና፣ በኃይል እርምጃና በውንብድና መብታችንን ለድርድር አናቀርብም!›› በሚል ባወጣው መግለጫ ሁለተኛ መርሓ ግብሩን በቅርብ ቀን ይፋ እንደሚያደርግ ገልጾአል፡፡
መግለጫው ለህዳር 7/2007 ዓ.ም ታቅዶ የነበረው ህዝባዊ አደባባይ ስብሰባ፣ እንዲሁም ለህዳር 27/28 2007 ዓ.ም ታቅዶ የነበረው የአዳር ሰልፍ በገዥው ፓርቲ የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች እንደተበተነ የሚታወቅ ሲሆን ትብብሩ መርሓ ግብሮቹን ለማስፈጸም ህጋዊ መንገድ ቢከተልም በወቅቱ ስርዓቱ የወሰደውን ህገ ወጥ እርምጃ በዝርዝር አስቀምጧል፡፡
ትብብሩ በመግለጫው በአንዱ ወር መርሓ ግብር ወቅት ስርዓቱ አፋኝ እርምጃዎችን ቢወስድም ገዢው ፓርቲ በዘመናት በማለማመድ ፈቃጅ ሆኖ ለመታየት ያደረገውን ጥረት ሰብሮ ዕውቅና ከመስጠት ያለፈ ህጋዊ ሥልጣን የሌለው መሆኑን እንዲያውቅ ማድረጉን፣ በማስፈራራት ትግሉን መግታት እንደማይቻልና ለዚህም ለነጻነታቸውና ክብራቸው የቱንም መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ታጋዮች በተለይም ወጣቶች መኖራቸውን እንዳሳየበት ገልጾአል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የህዝቡ የለውጥ ፍላጎት የደረሰበትን ደረጃና የንቃተ ኅሊና መዳበር፣ ህዝቡ ለፈጠራ ወንጀሎች እንዳይፈራና ይልቁንም በመንግሥት አሠራርና አመራር ላይ ያለው እምነት ከጥያቄ እንዲወድቅ፣ ፖሊስንና ፍርድ ቤቶችን ጨምሮ አስፈጻሚ አካላት ያለባቸውን ተጠያቂነት እንዲረዱና ራሳቸውን እንዲጠይቁ የሚያስችል ስሜት ፈጥሬበታለሁ ብሏል፡፡
‹‹የገዢውን ፓርቲ እየባሰ የመጣውን አምባገነናዊ ባህሪይ አጋልጠን፣ ኢትዮጵያዊያን ለተባበረ የጋራ ትግል ያላቸውን ድጋፍ በተግባር ተመልክተን፣ የጀመርነው የ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› ፕሮግራማችንን ትክክለኛለትና ተቀባይነት ለክተን ትግሉ ወደማይቀለበስበት የላቀ ደረጃ መሸጋገሩን አረጋግጠናል፡፡›› ያለው ትብብሩ የጋራ ትግሉን በበለጠ ጽናትና የኃላፊነት መንፈስ በመምራት የሁለተኛ ዙር እቅዱን በቅርብ ቀን ይፋ እንደሚያደርግ ገልጾአል፡፡
ትብብሩ በአንድ ወሩ መርሓ ግብር ወቅት በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላደረጉለት ሁለንተናዊ ድጋድ፣ በስርዓቱ እርምጃ በመቃወም በሰልፍ፣ በመግለጫ፣ በታሰርንበት አስፈላጊውን በማቅረብና በመጠየቅ ላደረጉት ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ በተመሳሳይ የወሩ መርሓ ግብር ከተጀመረ አንስቶ ጉዳዩን ለህዝብ ለማሳወቅ የጣሩትን በአገር ቤትና በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፤ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ በማመስገን በቀጣዩ ፕሮግራም ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
በሌላ በኩል ገዥው ፓርቲ ‹‹ለማንም የማይበጅ አካሄድ መርምሮና የህዝቡን የለውጥ ፍላጎት ተረድቶ ቆም ብሎ ራሱን እንዲፈትሽ፣ ከገባበት ፍርኃትና ሥጋት ተላቆ ለህዝብ ጥያቄዎች ተገቢውን ወቅታዊ ምላሽ በመስጠት ህገ መንግሥቱን አክብሮ እንዲያስከብር›› ሲል ጥሪ አቅርቧል፡፡
የመድረክ ሰለማዊ ሰልፍ ተጠናቀቀ::

የመድረክ የወጣቶች ክንፍ ከፖሊስ እና ከፀጥታ አካላት እጅና ጓዋንት ሆኖ የክትትል፤ የኢንተለጀንስ እና የቁጥጥር ስራውን በአግባቡ እንዲሚወጣ ለመግለፅ እንፈልጋልን፡፡ የሚል የህዝብ ግንኙነት ስራ ትዝብት ውስጥ የጣለው የመድረክ ፓርቲ ከገንፍሌ ተነስቶ፣ በኣዋሬ ኣልፎ በየካ ክፍለ ከተማ የሚገኝ ኳስ ሜዳ መጨረሻው ያደረገው ሰለማዊ ሰልፍ ተጠናቀቀ።
በዘጠኙ ፓርቲ ላይ የደረሰውን እስር ድብደባ እና እንግልት እንዳላወገዘ የሚነገርለት መድረክ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ሁለት ሺህ የሚጠጋ የኣዲስ ኣበባ ኑዋሪ የተሳተፈበት ሰልፍ በወጣቶች የመድረክ ኣመራር፣ የሴቶች ተወካይ፣ ኣቶ ቡልቻ ሚደቅሳና የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ዼጥሮስ ባሰሙት ንግግሮች ተጠቃሏል።
ሰለማዊ ሰልፉ የኢህኣዴግ መንግስት ሊያርማቸው የሚገቡ፣ መመቻቸት ያሉባቸው ፖለቲካዊ ምህዳር፣ መወገድ ያለበት የፀረ ሽብር ህግ ፣ ምርጫው ፍትሃዊ እንዲሆን ሊያደረጉ የሚገቡ ስራዎች እንዲሰሩ፣ በየቦታው እያጋጠመ ያለው ዓፈና፣ እስርና እንዲሁም ግድያዎች እንዲቆሙ ጥሪ ቀርበዋል።
የመድረክ ኣመራሮችና ወጣቶች እየመሩት የተካሄደው የሰለማዊ ሰልፉ ዓላማዎች የምያንፀባርቁ መፈክሮች በወጣቶች ኣባላት ተነበዋል። ከመፈክሮቹ
1- ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንጂ በአስመሳይ ፕሮፓጋንዳ፣ በኃይልና በተጽኖ አይገነባም!!
2- የሀገራችን ችግሮች በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ በሚገለጽ የሕዝብ ውሳኔ እንጂ በኃይል እርምጃ አይፈቱም!!
3- ከምርጫ በፊት የምርጫ ውድድር ሜዳው የሚስተካከልበት ውይይትና ድርድር እንዲካሄድ አጥብቀን እንጠይቃለን!!
4- በማስመሰያ ምርጫ በየአምስት አመቱ ሕዝብን ማታለልና ሀብቱን ማባከን ይቁም!!
5- የማስመሰያ ምርጫ ለማካሄድ ለሚባክነው የሀገርና የሕዝብ ሀብት ኢህአዴግ ተጠያቂ ነው!!
6- ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ በሌለበት ሁኔታ የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት እውን ሊሆን አይችልም!!
7- ሕዝባችን በ1ለ5 መረብ አፈናና ቁጥጥር ከሚካሄድ የምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ነፃ እንዲሆን እንጠይቃለን!!
8- ያለገለልተኛ የምርጫ አስተዳደርና ያለገለልተኛ የምርጫ ታዛቢ ታአማንነት ያለው ምርጫ ሊኖር አይችልም!!
9- ገለልተኛ የምርጫ ቦርድ በፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ ይቋቋም!!
10- በካድሬዎች የሚከናወን የምርጫ አስፈጻሚነትና ታዛቢነትን አንቀበልም፣ እናወግዛለን!!
11- ነፃ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ታዛቢዎች ምርጫውን በነፃነት የሚከታተሉበትና የሚታዘቡበት ሁኔታ
እንዲመቻች እንጠይቃለን!!
12- በምርጫ ወቅት በታጠቀ ኃይል በሕዝባችን ላይ የሚፈጸም ማስፈራሪያና ወከባን እናወግዛለን!!
13- በሰላማዊ ተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ የሚካሄድ እስራትና ወከባ በአስቸኳይ ይቁም!!
14- ኢህአዴግ በመንግሥት ሀብትና ንብረት የሚያከሄደውን ሕገወጥ የምርጫ ዘመቻ እናወግዛለን!!
15- የጸጥታ ኃይሎች የሕዝብ አገልጋዮች እንጂ ሕዝብን ማስፈራሪያና ማሸማቀቂያ መሆን የለባቸውም!!
16- ያልተሟላ የምርጫ ሥነምግባር ኮድ ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ለማካሄድ አያስችልም!!
17- ከድምጽ መስጫ ጣቢያዎች የተቃዋሚ ፓርቲ ታዛቢዎችን ማባረር የሕዝብን ድምጽ ለመስረቅ ስለሆነ በአስቸኳይ
እንዲቆም እንጠይቃለን!!
18- የሕዝብን ድምጽ መዝረፍ ዴሞክራሲን መገንባት ሳይሆን መቅበር ነው!!
19- የምርጫ ጣቢያዎች ከአስተዳደር አካላትና ከታጣቂ ሠራዊት ተጽኖና አፈና ነፃ ይሁኑ!!
20- በምርጫ ወቅት በምርጫ ጉዳዮች ፈጣን ውሳኔ የሚሰጡ ነፃና ገለልተኛ ዳኞች በየደረጃው እንዲኖሩ እንጠይቃለን!!
21- ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ማሰር፣ ማሰቃየትና መግደል ሕዝባችን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሥልጣን ባለቤት ለመሆን
የሚያካሄደውን ትግል አይገታም!!
22- ሀሳብን የመግለጽ ሕገመንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀማቸው የታሰሩ የሕልና እስረኞች በሙሉ በአስቸኳይ ይፈቱ!!
23- በግፍ የታሰሩ ሰላማዊ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት፣ ጋዜጠኞችና የሙስሊሙ ማሕበረሰብ መፍትሔ አፈላላጊዎች በአስቸኳይ ይፈቱ!!
24- የፀረ-ሽብር ሕጉን ለፖለቲካ ዓላማ መጠቀሚያ ማድረግን እናወግዛልን!! ሕገ-መንግሥታዊ መብትን በማይጥስ
ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲሻሻልም እንጠይቃለን!!
25- የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ለገዥው ፓርቲ የሚያሳዩትን ወገንተኝነት በአስቸኳይ ያቁሙ!!
26- ሁሉም ፓርቲዎች በሕጋዊና ፍትሐዊ አግባብ ከመንግሥት በጀት ድጋፍ የሚያገኙበት ሥርዓት እንዲኖር አጥብቀን እንጠይቃለን!
27- በነፃነት የመሰብሰብና የመደራጀት መብታችን ይከበር!!
28- የአንድ አምባገነን ፓርቲ ሳይሆን ትክክለኛ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እንሻለን!!
29- ኢህአዴግ ለሕገመንግሥትና ለሕግ ተገዥ በመሆን ለነፃ ምርጫ እራሱን እንዲያዘጋጅ እንጠይቃለን!!
30- የሕግ የበላይነት ባልተከበረበት ሁኔታ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት አይቻልም!!
31- የኑሮ ውድነቱና የተጎሳቆለው የሕዝባችን ሕይወት የኢህአዴግ የኢኮኖሚና ማሕበራዊ ፖሊሲ ውጤቶች ናቸው!!
32- በወገንተኝነትና በአድልኦ በሕዝባችን ላይ የሚጫን ግብር በአስቸኳይ ይስተካከል!!
33- በልማት ስም በሕገወጥና ግብታዊ በሆነ መንገድ ሕዝብን ማፈናቀልና ለችግር ማጋለጥ እንቃወማለን!!
34- የመሬት ወረራ ይቁም!!
35- በሙስና የተዘረፈው የሕዝብ ሀብት ለሕዝቡ ይመለስ!! ሙሰኞችም ለፍርድ ይቅረቡ!!
36- የውኃ፣ የማብራት፣ የትራንስፖርትና የስልክ አገልግሎቶች ችግሮቻችን በአስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጣቸው እንጠይቃለን!!
37- የአህአዴግ አገዛዝ በሐይማኖቶች የውስጥ ጉዳዮች የሚፈጽማቸውን ጣልቃ ገብነቶች እናወግዛለን!!
እነዚህ መፈክሮች ለመላ ዓለም ይሰራጫሉ ተብለው ይጠበቃል።
የአዜብና የደህንነቱ ሹም እቅድ ክሽፈት(ከኢየሩሳሌም አርአያ)

አዜብ መስፍን ከባለቤታቸው ህልፈት በኋላ የፓርቲው ሊቀመንበርና የጠ/ሚ/ር ስልጣን ለመረከብ አቅደው እንደነበረ ታማኝ ምንጮች አጋለጡ። የደህንነት ዋና ሹም የነበረው ወ.ስላሴ ወ/ሚካኤልን ከፊት በማስቀደም ወ/ሮ አዜብ የሞከሩትና በፓርቲው አንዳንድ አመራሮች “መፈንቅለ ድርጅት ሙከራ” ሲሉ ፈረጀውታል።
ከምንጮቹ የተገኘው ዝርዝር መረጃ ተከታዩን ይመስላል። አቶ መለስ ዜናዊ መሞታቸውን ተከትሎ በሕወሐት ውስጥ ሁለት አይነት ቡድኖች ብቅ አሉ። ወ/ሮ አዜብ የድርጅቱ ሊቀመንበር በመሆን የጠ/ሚ/ር ስልጣኑን ለመረከብ ካልሆነም ምክትል ጠ/ሚ/ርነትን ለመቆናጠጥ ከፍተኛ ፍላጐት አሳደሩ። ከአዜብ ጐን የቆሙት በረከት ስሞኦን “የመለስን ራዕይ የማስፈፅመው እኔ ነኝ” ሲሉ ለካድሬዎቻቸው ቀሰቀሱ።
በአንፃሩ እነስብሃት ነጋ ከጀርባ የሚመሩትና ፀጋይ በርሄ፣ ጌታቸው አሰፋ፣ አርከበና ደብረፂዮን ያሉበት ቡድን በተቃራኒው ቆሞ በውስጥ አድፍጦ የፖለቲካ መስመሩን እያስተካከለ ነው። አዜብ ከጐናቸው ያሰለፏቸው የደህንነት ሹም ወ/ስላሴ፣ ገ/ዋህድን እንዲሁም ሚሊየነሩ ነጋ ገ/እግዚያብሄር መቀሌ ድረስ ኔትዎርክ ዘረጉ። አዜብን የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጐ ለማስመረጥ አዜብ የመደቡት በ10ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በአቶ ነጋ በኩል ወጪ እየተደረገ በነወ/ስላሴ አማካይነት ለበርካታ ካድሬዎች ይታደል ጀመር። አዜብ ያንን ሁሉ ገንዘብ ያለምንም ጠያቂ ፈሰስ ማድረጋቸውና ያለመጠየቃቸው አስገራሚ ነበር። ለካድሬዎች በነፍስ ወከፍ ከ3 እስከ 8 ሚሊዮን ብር ተከፋፈለ።
ካድሬው ድምፅ ለአዜብ በመስጠት የሕወሐት ሊ/መንበር ማድረግ እንዲሁም ወ/ስላሴን በፓርቲው ማ/ኮሚቴ አባልነት ለማስመረጥ በተጨማሪ ጌታቸው አሰፋን እንዳይመረጥ ማድረግ የሚሉ መመሪያዎች ገንዘቡን ለሚቀበሉ ካድሬዎች ጥብቅ መመሪያ ከነወ/ስላሴ ተላለፈ። ካድሬው እነወ/ስላሴ የሰጡትን ገንዘብ በመቀበል ትእዛዙን ተፈፃሚ እንደሚያደርግ ነገራቸው። ጉዳዩን ሰምተው እንዳልሰሙ የሆኑት እነጌታቸው አሰፋ በጐን ካድሬውን እያስጠሩ « የሚሰጧችሁን ገንዘብ ተቀበሉ። የሚሏችሁን እሺ በሉ። በጉባኤው ላይ ግን ከእኛ ጐን ትቆማላችሁ» ሲሉ በማስጠንቀቂያ መልክ ነገሩ። ካድሬው ከነጌታቸው ጐን እንደሚቆም ቃል ገባላቸው። እነወ/ስላሴ፣ አባይ ወልዱ፣ ገ/ዋህድ..እንዲሁም በባለሃብት ሽፋን የአዜብን ተልእኮ ለማስፈፀም ሲሯሯጡ የከረሙት ነጋ ገ/እግዚያብሄር ጉባኤው ሳምንት እየቀረው በመቀሌ “ቡቡ ሂልስና አክሱም” በመሳሰሉ ሆቴሎች ካድሬውን በግብዣ ሲያንበሸብሹ ሰነበቱ።
የጉባኤው እለት ደረሰ። ለሕወሐት ሊቀመንበርነት እጩዎች ሲጠቆሙ ወ/ስላሴ እጅ በማውጣት “አዜብ መስፍን” ሲል ጠቆመ። ተሰብሳቢው ድጋፍና ተቃውሞ ሲጠየቅ 12 ጣቶች (ድምፆች) ብቻ ሲደግፉ የተቀረው አዜብን በመቃወም ውድቅ አደረገው። አባይ ወልዱ፣ ወ/ስላሴ፣ ቴዎድሮስ ሃጐስ፣ ትርፉ፣ በየነ፣ ገ/ዋህድ…ለአዜብ ድጋፍ ከሰጡ 13 ድምፆች ይጠቀሳሉ። አዜብ « የመለስ ራዕይ ሳይበረዝ ሳይከለስ ለማስቀጠል..» አልጨረሱም የመድረኩ መሪ ጣልቃ ገብተው « ስነ ስርዓት ..አሁን የእጩዎች ምርጫ እያካሄድን ነው» ሲል አርከበ ቀበል አድርግው « የመለስ ራዕይ የሚባል የለም። የፓርቲው ራዕይ ነው ያለው» ሲሉ አዜብ በግልምጫ እያዩ ተናገሩ። ካድሬው እንደካዳቸው ያወቁት አዜብ ንዴት በገፅታቸው ላይ ይነበብ ነበር። ብሽቀት የገባው ወ/ስላሴ እቅዳቸውን ጌታቸው እንዳኮላሸው የተረዳ ይመስላል። እጁን በማውጣት « ጌታቸው አሰፋ ለማ/ኮሚቴ አባልነት አይመጥንም። ሰካራም ነው፣ ሴሰኛ (ሴት በማማገጥ) ነው። ውሎና አዳሩ ሸራተን ነው። እንዳውም አቶ መለስ ዜናዊ በጌታቸው ዙሪያ ማጣራት እንዲካሄድ ያስጀመረው ምርመራ ነበር። ውሳኔ ሊሰጥበት ጫፍ ሲደርስ እንዳጋጣሚ ሞት ቀደመው። ስለዚህ ጌታቸው ለፓርቲው ማ/ኮሚቴ አባልነት አይመጥንም» በማለት በእልህ ስሜት ይናገራል።
አስመላሽ ወ/ስላሴ (በቅፅል ስማቸው አባይ ነብሶ- በፓርላማ ከመለስ ዘናዊ ኋላ አዘውትረው የሚቀመጡና ጥቁር መነፅር የሚያጠልቁ አይነስውር) እጃቸውን በማንሳት በዚህ ዙሪያ መናገር እንደሚፈልጉ ይጠይቃሉ። ሲፈቀድላቸው እንዲህ አሉ፥ « አሁን ወ/ስላሴ እንዳለው በጌታቸው ዙሪያ ማጣራት ስናካሂድ ከነበርነው ሶስት ሰዎች አንዱ እኔ ነኝ። እንድናጣራ ያዘዘን መለስ ነው። የቀረበልን ጥቆማ “ጌታቸው ቪላ ቤት ገንብቷል፣ ሙስና ውስጥ ገብቷል” የሚሉ ነበሩ። ረጅም ጊዜ ስናጣራ ቆየን። ነገር ግን የተባለውን ቤትም ሆነ በሙስና ያፈራው አንዳች ነገር ልናገኝ አልቻልንም። ከዚያ በጌታቸው ላይ ጥቆማውን ያቀረበው ወይም ያመጣው ማነው?.ብለን ስንጠይቅ ወ/ስላሴ መሆኑን አወቅን።
በወ/ስላሴ ዙሪያ ለምን ማጣራት አናካሂድም ብለን ጀመርን። በስሙ፣ በወንድምና እህቱ እንዲሁም በቤተሰቡና በሌሎች ግለሰቦች በሙስና መበልፀጉን አረጋገጥን» በማለት የሙስናውን ማስረጃ በዝርዝር አባይ ነብሶ ለጉባኤው አቀረቡ። ለማ/ኰሚቴ የተጠቆመው ወ/ስላሴ 2 ድምፅ ብቻ በማግኘቱና ከጨዋታ ውጭ በመሆኑ ኩም አለ። ጉባኤው በነጌታቸው አሰፋ ድል አድራጊነት ተጠናቀቀ። የሙስናዋን ፋይል የያዙት ጌታቸው አሰፋ በቅድሚያ ያደረጉት ወ/ስላሴን ከስልጣን ማባረር ነበር። ከዛም እነገ/ዋህድን ጨምሮ ለአዜብ ገንዘብ ሲረጩ የነበሩትን እነነጋ ገ/እግዚያብሄርን በሙስናው ፋይል እስር ቤት መክተት የሚለውን እቅድ ተግባራዊ አደረጉ። የደህንነቱን ቢሮ እንዳሻው ይፈነጭበት የነበረውና የአቶ መለስና አዜብ ቀኝ በመሆን አገሪቱን በአፈና መዋቅር ሲያሰቃያት የከረመው ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል በበርካታ የደህንነት አባላት ጥርስ የተነከሰበት ጭምር ነበር። ይህን የሚያውቁት ጌታቸው አሰፋ በደህንነቶች ለተከታታይ ቀናት ወ/ስላሴ እንዲደበደብ ማድረጋቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።
ሕወሐት ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ለማድረግ አቅዷል (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

የጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣን ወደ ሕወሐት ለመመለስ የፓርቲው ቁልፍ አመራሮች በምስጢር ሲመክሩ መስንበታቸውን የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። በአቶ ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል፣ አባይ ፀሐዬ፣ ጌታቸው አሰፋ፣ ጄ/ል ሳሞራ የኑስ፣ ፀጋይ በርሔ፣ አርከበ እቁባይና ስብሃት ነጋ የሚመራው የሕወሐት ከፍተኛ አመራሮች ከዚህ ቀደም ሲካሂዱት በነበረውና ህወሀት የጠ/ሚ/ ርነት ስልጣን መልሶ መያዝ ይኖርበታል፣ የሚለውን ምክክር ከዳር ለማድረስ አቋም መያዘያቸውን ያስታወቁት ምንጮቹ በተለይ በቅርቡ የተካሄደው የአራቱ ፓርቲዎች ጉባኤ ላይ በብአዴንና ኦህዴድ በኩል ቅሬታና ተቃውሞ እየበረታ በመምጣቱ የሕወሐት አመራሮች ስልጣኑን በእጃቸው ለማስገባት ቆርጠው መነሳታቸውን አስረድተዋል።
በብአዴን በኩል የአቶ በረከት ስሞን ከስልጣን መገፋት በደጋፊዎችቻቸውና አመራሩ በኩል ቅሬታ መፍጠሩን የጠቆሙት ምንጮቹ በረከት ስሞን የጠ/ሚ/ር ሃ/ማርያም አማካሪ ተብለው ቢሾሙም ነገር ግን በጠ/ሚ/ር ፅ/ቤት ቢሮ እንዳልተሰጣቸውና የተሰጣቸው ካዛንቺስ አካባቢ የሚገኘው የቀድሞ የደህንነት ቢሮ መሆኑን ምንጮቹ ገልፀው በዚህ ቢሮ ኩማ ደመቅሳ እንደሚገኙና በጠ/ሚ/ር ፅ/ቤት አዲስ ቢሮ ተገንብቶ ይሰጣችኋል የተባለው ተግባራዊ እንዳልሆነ አያይዘው አስረድተዋል።
በጠ/ሚ/ር ፅ/ቤት ቢሮ የተሰጣቸውና ከአቶ ሃ/ማርያም እያንዳንዷ እንቅስቃሴ ያልተለዩት አርከበ እቁባይ፣ አባይ ፀሐዬና ፀጋይ በርሄ ሲጠቀሱ በም/ጠ/ሚ/ር ቦታ ደብረፂዮን መኖራቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል። ለሕወሐት አመራሮች ሌላው ራስ ምታት የሆነባቸው የኦህዴድ ፓርቲ ከሕወሐት እኩል መገዳደር እያሳየ መምጣቱ ነው ያሉት ምንጮቹ በተለይ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ኦህዴድ የተለያዩ የስልጣን ጥያቄዎች በማንሳት ድፍረት እያሳየ መጥቷል ብለዋል።
ሕወሐት የጠ/ሚ/ርነት ስልጣኑን መቆጣጠር የፈለገበት አንዱ ምክንያት ይህ መሆኑን ምንጮቹ አልሸሸጉም። በኦህዴድ በኩል የጠ/ሚ/ር ስልጣን ለኦሮሞ ይገባል በሚል ከዚህ ቀደም የነበረው የሕወሀት ስልጣንን አንሰራፍቶ የመያዝ አካሄድ መገታት አለበት የሚል አቋም እንደተያዘ ያስረዱት ምንጮቹ በተለይ የህወሀት አመራር የኦህዴድ አካሄድ እንዳልተዋጠለትና ከዚህ ቀደም ማን ጠ/ሚ/ር ስልጣን ይያዝ የሚለው የህወሀት ምክክር በእንጥልጥል ቆይቶ በቅርቡ ግን ዶ/ር ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል ስልጣኑን መያዝ አለበት የሚል ውሳኔ ላይ መድረሱን ምንጮቹ አስገንዝበዋል። የደብረፂዮን ወደ ጠ/ሚ/ር ስልጣን የማምጣት እቅድ በተመለከተ አርከበ እቁባይ ተቃውሞ አሰምተው መከራከራቸውንና በመጨረሻ ግን ኦህዴድና ብአዴን ለመጨፍለቅ ሲባል አርከበ መቀበላቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል። የህወሀት አመራሮች ከስምምነት የደረሱበትን ጉዳይ ከቀጣዩ ምርጫ በኋላ ጠ/ሚ/ር አቶ ሃ/ማርያም ደሳለኝን ከብቃት ማነስ ጋር በማያያዝ ከስልጣን ለማውረድና በምትካቸው የጠ/ሚ/ርነቱን ቦታ ለደብረፂዮን ለመስጠት መወሰናቸውን ምንጮቹ አጋልጠዋል።
ወዛደር እና ወታደር ይለይለት! – ከዳንኤል ፈይሳ
(ጨዋታው ተጀምረ፡፡ ይህ ጨዋታ ለሕዳሴው ግድብ ድጋፍ ሲባል የሚደረግ መሆኑን ያለማሳወቅ አያስፈልግም፡፡ ያለእንደዚህ ያሉ የድጋፍ ሰጪ ጨዋታዎች የህዳሴው ግድብ ፕሮጄክት አይጠናቀቅም ሲሉ ቃል አቃባዩ እንጂነር ስመኘው ገልፀዋል፡፡) በሃገራችን ኢትዮጵያ እንደ ውሃ ወለድ በሽታዎቻችን ብዛት ሁሉ ሁኔታ-ወለድ የሆኑ ብዙ ክስተቶች ያጋጥማሉ፡፡ከነዚህ መሃል በተለይ በፖለቲካው መስክ ሰዎች የሚያገኙት ስፍራ ከማንነታቸው ጋር የማይገጥም እየሆነ ተቸግረናል፡፡ አሁን ባለው ነባራዊ […]
አንድነት ጠቅላላ ጉባኤውን በድል አጠናቀቀ!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ እጅግ ደማቅ በሆነ ሁኔታ ያካሄደ ሲሆን፤ በጠቅላላ ጉባኤው ሶስት ዋና ዋና ተግባራት ተካሄደዋል፤ የመጀመሪው አጀንዳ ኢር ግዛቸው በራሳቸው ፍቃድ ስልጣናቸውን በለቀቁ ጊዜ የአንድነት ብሄራዊ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤው በሰጠው ስልጣን መሰረት አዲስ የፓርቲው ፕሬዚደንት መምረጡ ጉባኤው ተቀብሎ ያፀደቀ ሲሆን፤ በዚህ መሰረትም አቶ በላይ ፍቃዱ የፓርቲው ፕሬዚደንት ሆነው […]
ሕወሐት ደ/ፂዮንን ጠ/ሚ/ር ለማድረግ አቅዷል * የአዜብና የደህንነቱ ሹም ያልታሳካ እቅድ – ኢየሩሳሌም አርአያ
የጠ/ሚ/ር ስልጣን ወደ ሕወሐት ለመመለስ የፓርቲው ቁልፍ አመራሮች በምስጢር ሲመክሩ መስንበታቸውን የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። በአቶ ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል፣ አባይ ፀሐዬ፣ ጌታቸው አሰፋ፣ ጄ/ል ሳሞራ የኑስ፣ ፀጋይ በርሔ፣ አርከበ እቁባይና ስብሃት ነጋ የሚመራው የሕወሐት ከፍተኛ አመራሮች ከዚህ ቀደም ሲካሂዱት በነበረውና ህወሀት የጠ/ሚ/ ርነት ስልጣን መልሶ መያዝ ይኖርበታል፣ የሚለውን ምክክር ከዳር ለማድረስ አቋም መያዘያቸውን ያስታወቁት ምንጮቹ በተለይ በቅርቡ […]
“ኦሮማይ” እና በዓሉ ግርማ
መጽሐፉ የብዙዎቹን አትኩሮት የሳበው ታሪኩ እውነት ነው ስለተባለ እና በመጽሐፉ ሳቢያም የደራሲው ህይወት ለአደጋ በመጋለጡ ይመስለኛል፡፡ ከመጽሐፉ ዐቢይ ገጸ-ባህሪያት አንዱ የሆኑት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ “የደም እምባ” በተሰኘው መጽሐፋቸው ተመሳሳይ እይታ አንጸባርቀዋል፤ እንደ ሻለቃ ዳዊት አባባል ኦሮማይ ባይታገድ ኖሮ ተወዳጅነቱ ይሄን ያህል አይገዝፍም ነበር፡፡ ሆኖም እኔ በዚህ አባባል አልስማማም፡፡ ደራሲው ባይሞት እና ታሪኩ እውነተኛ ባይሆን እንኳ “ኦሮማይ” ተደናቂ የመሆንን እድል አያጣም ነበር ብዬ አምናለሁ፡፡ ለዚህም በርካታ አብነቶችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ የኮማንደር “አያልነሽ” ወጎች
————-
The writer, Afendi Muteki, is a researcher of the Ethnography and History of the peoples of East Ethiopia. He is an author of “Harar Gey”, an Ethnography book about the historical city of Harar. You can read some of his articles on his facebook page.
Facebook https://www.facebook.com/afendimutekiharar
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 13, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
ሱዳን፤ አይ ሲ ሲ ዳርፉር ውስጥ ምርመራውን አቋረጠ
ኔዘርላንድ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት በእንግሊዘኛ ምኅፃሩ ICC ዳርፉር ላይ የሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን አስመልክቶ ከፍቶት የነበረውን ክስ ማቋረጡን አስታወቀ።
የርዋንዳ የመረጃ አቀራረብ ነፃነት እና ፈተናዉ
በምሥራቅ አፍሪቃዊትዋ ሀገር በርዋንዳ የፕሬስ ሕግጋትች ነጻ ሆነዉ ቢቀመጡም፤ በሀገሪቱ የሚገኙ ጋዜጠኞች በነጻነት መሥራትና መፃፍ እንዳልቻሉ ለጋዜጠኞች የሚሟገቱ ድርጅቶች ዘግበዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ገመና – ተመስገን ደሳለኝ (ከዝዋይ እስር ቤት)
መሐሙድ የሱፍ የተወለደው በ1980ዓ.ም ከሶማሌ ክልል ርእሰ-መዲና ጅጅጋ 500 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውዶሀን ከተማ ነው፡፡ ለቤተሰቡ ሰባተኛ ልጅ ሲሆን፤ አምስት እህቶችእና ሦስት ወንድሞች አሉት፡፡ በጅጅጋ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ መዝለቁቢሳካለትም፤ ከዚህ በላይ ግን ሊቀጥል አልተቻለውም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኢትዮጵያመንግስት የደህንነት ሠራተኞች የ1999ዓ.ም የግንቦት ሃያ በዓል በጅጅጋ ከተማ ስታዲዬም በተከበረበት ዕለት፣ የኦጋዴን ነፃአውጪ ግንባር […]