ሻምበል ሳሙኤል መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ሪፖርተር :?:

” አብራሪዎቹ ከፖለቲካ ራሳቸውን ገለልተኛ ያደረጉት ባለው መንግስት ላይ ያላቸውን ጥላቻ እና ቂም ያመለክታል::በአንድ ሃገር የደህንነት ህዝባዊ ጥበቃ ስራ ላይ የተሰማራ ወታደር ከአምባገነኖች ፖለቲካ ራሱን ማግለሉ ህዝባዊ ተቆርቋሪነቱን ያሳያል:: ” Minilik Salsawi

ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው ነበረ::
የተጠለፈው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሔሊኮፕተር አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ ::
ሪፖርተር :- የኢትዮጵያ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ባለፈው ዓርብ ተጠልፎ ኤርትራ ግዛት አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ፡፡ የዘወትር የበረራ ልምምድ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሩሲያ ሠራሽ ኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር ይዞ ወደ ኤርትራ የኮበለለው ዋና አብራሪ ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ ይህንን ዓይነት ተግባር ይፈጽማል ብለው እንደማያስቡ ባልደረቦቹ ገልጸዋል፡፡

ከሻምበል ሳሙኤል ጋር በኢትዮጵያ አየር ኃይል አብረው የሠለጠኑና የሠሩ የሥራ ባልደረቦቹ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ግለሰቡ መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ‹‹እጅግ በጣም ጥሩ ሰው ነው፡፡ የመንግሥት ተቃዋሚ አልነበረም፡፡ ራሱን ከፖለቲካ ጉዳዮች የሚያገል፣ ሥራውን ብቻ የሚሠራና ልጆቹን በኃላፊነት የሚያሳድግ ሰው ነበር፤›› ብለው በድርጊቱ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡

አክለውም በትንሽ ነገር የሚከፋና የሚደሰት፣ በቅጽበት የሚለዋወጥ ባህሪ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በግል ሕይወቱም የሚበሳጭበት ጉዳይ እንደነበርና አልፎ አልፎም በዚሁ ጉዳይ ይደበት እንደነበር አልሸሸጉም፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ለሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ አየር ኃይል የገባው በ1994 ዓ.ም. ሲሆን፣ የቅጥር ውል የፈረመው በታህሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ለ12 ዓመታት አገልግሏል፡፡ በ2003 ዓ.ም. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ወደ ዳርፉር ሱዳን ያሰማራው የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል በመሆን ለአንድ ዓመት ያህል እንዳገለገለና በዚያም ተልዕኮ ዳጐስ ያለ ዶላር ይዞ መመለሱን ባልደረቦቹ ተናግረዋል፡፡

ሻምበል ሳሙኤል ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ መሆኑን፣ ወላጆቹ የመቀሌ ነዋሪ መሆናቸውን ባለቤቱና ሁለት ልጆቹ ቢሾፍቱ እንደሚኖሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ባለፈው ዓርብ ማለዳ ከረዳት አብራሪው መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝና የበረራ ቴክኒሺያን ፀጋ ብርሃን ግደይ ጋር በኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር የዘወትር የልምምድ በረራ ለማድረግ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ድሬዳዋ ከሚገኘው የአየር ኃይል ቤዝ እንደተነሱ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ዋና አብራሪው ከአጭር ጊዜ በረራ በኋላ የበረራ ከፍታውን በመቀነስ ወደ ኤርትራ በማቅናት ሔሊኮፕተሩን አሰብ ማሳረፉን ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

መከላከያ ሚኒስቴር ባለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ ተዋጊ ሔሊኮፕተሩን ዋና አብራሪው ይዞ ወደ ኤርትራ መኮብለሉን አምኗል፡፡ ሚኒስቴሩ በመግለጫው ዋና አብራሪው ቴክኒሺያኑንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን አስታውቋል፡፡

ሔሊኮፕተሩ ባለፈው ዓርብ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ጀምሮ በመደበኛ የሥልጠና ልምምድ ላይ እንደነበር ጠቅሶ፣ ሔሊኮፕተሩ ከግንኙነት ውጪ በመሆኑ ሠራዊቱ በአካባቢው ማኅበረሰብና አጋሮች ለተከታታይ ቀናት ፍለጋ ሲደረግለት መቆየቱን አትቷል፡፡ ‹‹ሆኖም ሔሊኮፕተሩ በከሀዲው ዋና አብራሪ አማካይነት ቴክኒሻንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን መረጃዎች ይጠቁማሉ፤›› ብሏል፡፡ ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች ዋና አብራሪው የሔሊኮፕተሩ አዛዥ በመሆኑ የትም ወስዶ ሊያሳርፈው እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

‹‹ረዳት አብራሪው ጀማሪ ነው፡፡ የበረራ ቴክኒሺያኑ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን መከታተል ነው፡፡ ዋና አብራሪው ረዳት አብራሪውና ቴክኒሺያኑ እያወቁም ወይም ያለነሱ ዕውቅና የፈለገበት ወስዶ ሊያሳርፍ ይችላል፤›› ብለዋል፡፡ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው መክረማቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር መትረየስና ተወንጫፊ ሮኬቶች የተገጠሙለት ዘመናዊ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ነው፡፡ ከኋላው ስምንት ወታደሮችን ወይም ሁለት የቁስለኛ አልጋዎችን መያዝ ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኤምአይ 17 እና ኤምአይ 8 የትራንስፖርት ሔሊኮፕተሮች ሲኖሩት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸው በደርግ ጊዜ የተገዙ ኤምአይ 24 ሔሊኮፕተሮችን ነበር፡፡ በግንቦት 1990 ዓ.ም. የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሲጀመር አሥር ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተሮች የተገዙ ሲሆን፣ በጦርነቱ ወቅት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡

የ1997 ዓ.ም. ሦስተኛ ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ የተነሳውን ግርግር ተከትሎ ሁለት የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች (ሻምበል አብዮት እና ሻምበል በኃይሉ) አንድ ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ይዘው ወደ ጐረቤት አገር ጂቡቲ መኮብለላቸው ይታወሳል፡፡ ብዙም ሳይቆይ የጂቡቲ መንግሥት አብራሪዎቹን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግሥት የሰጠ ሲሆን ሔሊኮፕተሩንም መልሷል፡፡ አብራሪዎቹ የጦር ፍርድ ቤት ቀርበው በአሁኑ ወቅት በእስር እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ወቅት በቤላሩስ በሥልጠና ላይ የነበሩ ሰባት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የኤስዩ 27 ተዋጊ ጀት አብራሪዎች ከድተው ጥገኝነት መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ አብራሪዎቹ በተለያዩ የምዕራብ አገሮች ጥገኝነት ማግኘታቸው ይነገራል፡፡

ቀደም ሲል ሻምበል ተሾመ ተንኮሉ የተባለ የአየር ኃይል ባልደረባ በ1995 ዓ.ም. ኤል 39 የተሰኘ የመለማመጃና ቀላል የውጊያ አውሮፕላን ለልምምድ በረራ ከመቀሌ ቤዝ ይዞ እንደተነሳ ወደ ኤርትራ ኮብልሎ ነበር፡፡

እስከ ማክሰኞ ታኅሳስ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ምሽት ድረስ የኤርትራ መንግሥት ስለተጠለፈው ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጠም፡፡
source Reporter ሪፖርተር
Image

ከአርአያ ተስፋማሪያም

ፍቅረኞቹ አሁን የሚኖሩት አሜሪካ ነው። ተማሪ እያሉ ሳያስቡት ልጅ አፈሩ። የሁለቱን ፍቅርና መዋደድ እንዴት እነደነበረ የሚያውቋቸው ምስክር ናቸው። 6 አመት በመዋደድ የዘለቀው ፍቅራቸው በድንገት እሷ ከአገር በመውጣቷ ለጊዜው ተቋረጠ። የምትፅፋቸው ደብዳቤዎች ውብና አስደናቂ ነበሩ። ልክ እንደውጫዊና ውስጣዊ ውበቷ አይነት ነበሩ። በተለይ «..ውድ ፍቅሬ ቅድሚያ ግን እወቅልኝ፤ ዛሬም ልቤ አንድ! ፍቅሬም ዘላለማዊ ወረት የሌለበት እንደሆነ! ..ብቸኝነት ጅራፍ ነው! የእሳት ጅራፍ!…የዚህ አለም ኑሮ አክትሞልኝ ፅዋዬን እስክጐነጭ ፣ ተራ ደርሶኝ አንደበቴ ተሸብቦ እጅና እግሬ እስከሚታሰር ለአንተ ያለኝን ጥልቅ ፍቅርና መውደድ ከመግለፅና ከመተግበር ወደኋላ አልልም። አንተ ከማጣ (ልብ ተነጥቆ መኖር ከተባለ) ሞቴን እመርጣለሁ..» የሚለው አስደማሚ ደብዳቤዋ ይጠቀሳል። ከ4 አመት በኋላ ስትመጣ ግን እሱ በማያውቀውና ባላደረገው ነገር ቤተሰብ በጠነሰሰው ሴራ ለመለያየት በቁ። በተደጋጋሚ ቀርቦ ሊያስረዳት ቢሞክርም ለማዳመጥ እንኳ ፈቃደኛ ሳትሆን ቀረች። ልጃቸው ልታስታርቅ ብዙ ጥራለች፤ ግን አልሆነም ..ሌላ ሰው አፍቅራ አሜሪካ ገባች። እሱም ልጁን ይዞ ሄደ። ልጇን ለማየት እሱ ወዳለበት ከተማ ስትመጣ ሁሉንም ነገር አስረዳት። ታማኝ ሆኖ ለ4 አመት እንደጠበቃት አስረዳት። በጣም ተፀፀተች።..ጊዜው ግን አልፎ ነበር። ..በቅርቡ ልጅ መውለዷን ሲሰማ ሆስፒታል ድረስ በመሄድ ጠየቃት። የልጇን ግንባር ስሞ « እንኳን በሰላም ተገላገልሽ..ደስ ይበልሽ!» አላት። አንገቷን እንዳቀረቀረች ነበር። …እሱ አንድ እመነት አለው፤ ያፈቀርከውን ሰው ስትለያየው መጥፎውን የምትመኝ ከሆነ..መጀመሪያውኑ ፍቅር አልነበረህም ማለት ነው!..ይላል።..ደግሞም ምንም ክፋት የማታውቅ መልካም ሴት መሆኗን ይመስክርላታል።….ይህ እውነተኛ ታሪክ የእኔ ነው፤….ባለቷሪኳ ደግሞ የኢየሩስ እናት…

«..ለአይኔ ማመን ያቃተኝ ታላቅ ነገር ዛሬ ተከሰተ – ደብዳቤህ። ተመስገን አምላኬ!

በስራ የዛለ ሠውነቴ ከእረፍት አስበልጦ ከአንተ ሊያወጋ የተወሰኑ ረድፎችን መጓዙን አይኖቼ አስተዋሉ። ስቀጥል፥ ከምንም በላይ በሀገርህ ላይ ሠላምህን፣ በቤትህ ውስጥ የሠከነ ሕይወትን፣ ከሰዎች ጋር መልካም ግንኙነትን፣ ለፈጣሪህ ቅን ልቦናን፣ ለቤተሰብህ መታዘዝን፣ እምነት ማተብህን ማጥበቅን፣ ለሰውነትህ ምቾትን፣ ለአይምሮህ መረጋጋትን፣ በስራህ አስተዋይነትን፣ በማህበራዊ ህይወትህ ጥሩ ግንኙነትን፣ በሰዎች ዘንድ ተወዳጅነትን፣ እንዲያድልህ ፥ ለፈጣሪዬ – ለፈጣሪህ፣ ለአምላኬ – ለአምላክህ፣ ፃድቅም ባልሆን ለሃጢያተኞች ሲል መከራን ለተቀበለ፣ በበደሉት መጠን ቂም ለማይዝ፣ በጠሩት ጊዜ ለሚሰማ ለሕያው አምላክ – በልኡል መንበሩ ተቀምጦ አዳርህን – አዳሬን፣ ውሎህን – ውሎዬን፣ ለሚቃኝ ለሚመለከት፣ እውነተኛ ሚዛንና ፍርድን በእጁ ለያዘ ፈጣሪ አምላክ የእጁን በረከት እንዲዘረጋልህ የዘወትር ፀሎቴ ነው!!

ውድ ፍቅሬ፥ ቅድሚያ ግን እወቅልኝ፤ ዛሬም ልቤ አንድ፣ ፍቅሬም ዘላለማዊ ወረት የሌለበት እንደሆነ!! በቀዘቀዘና በሰከነ አነጋገር ክንድህን ተንተርሼ….ጠረንህን እያሸተትኩ ..አ. ፈ..ቅ..ር..ሀ..ለ..ሁ…የምልህን! በቀን የሰው አይን፣ በጠፍ ጨረቃ ጋኔን ሳልፈራ ..አንተን እያልኩ ድፍን ሰፈርህን እያሰስኩ « ፍቅሬን.. ውለዱ» እያልኩ ሳስሥህ የምከርመውን፤ ይህን ስፅፍልህም ወደኋላ በትዝታ እየተቃጠልኩ ትርሃስ ላይ ተደፍቼ እያነባሁ መሆኑን ብታየኝ.. “አዝንልሻለሁ” ከምትለኝ በላይ ዛሬ ታዝንልኝ ነበር። የሚያባብለኝ የለ፤ የሚያፅናናኝ። ብቻዬን ልብህን እያሰብኩና እየፈለኩ፣ እንዲያጫውተኝ እየዳሠስኩ – ፍቅርን ከትርሃስ ጋር በእንባ ሌሊቱን በመገላበጥ አነጋለሁ፤ ናፈቅከኝ!!…በካፊያ ዝናብ ከአንተ ጋር መሆን ምን ያህል እንደሚያስደስተኝ አንተም ታውቃለህ፤ ምን ብዬ ልንገርህ!?…ቢያንስ ያንተ ይሻላል- ቤተሰብን አይቶ መፅናናት ቀላል ነገር እንዳይመስልህ!! ብቸኝነት ጅራፍ ነው፤ የእሳት ጅራፍ!!!..ከስራ መልስ አረፍ ባልኩ ቁጥር ቀልቤ አዲስ አበባ….ሰፈር ልቤ ከአንተ ጋር በምናብ ሲጨዋወት ያመሻል።

« …የምወድህ ፍቅሬ፥ አጀማመራችን እኮ ብንተማመን – ልንፋቀር፣ ብንዋደድ ልንዛለቅ፣ ብንተሳሰብ ልንስማማ፣ ብንከባበር ላንናቆር፣ ብንቀያየም ላንለያይ ነበር። ታዲያ ዛሬ ማዶና ማዶ ሆነን እየተሰቃየን ተግባብተን ላንስማማ በየራሳችን ሃሳብ እየተጓዝን የፍቅራችንን መንገድ አጣመምነው። ሃላፊነቱን በእኔ ላይ ብቻ እንደማትጥልብኝ አምናለሁ፤ እንዲሁም የጥፋተኝነትን ፅዋ። ካጠፋሁ ይቅርታ! ግን ጥፋቴ ምን እንደሆነ አልታየኝም። እዚህ ያለሁበትን አጣብቂኝና ፈተና፣ ስቃይ፣ ችግር፣ መከራ ብትመለከት እንኳን ቅያሞት ሃዘን ይገልህ ነበር። እኔ አንተን የማልቀየምህ ለምን መሰለህ?..ሁሉን ነገር ስለማታየው፣ የስደትን ኑሮ በሰው ሃገር ስላልተረዳህልኝ፣ እኔም ኢትዮጲያ እያለሁ እዚህ ችግር ያለ ስለማይመስለኝ፣ አንተም ከእኔ የተለየ አስተሳሰብ ስለሌለህ፥ ለዚህ ነው ብዙም ያላመረርኩብህ። ተስፋ ነበረኝ ከአንድ ከ8 ወራቶች በኋላ አይንህን የማየት፤ ሁሉን ነገር ተወያይተን አምላካችንን በመሃከላችን አኑረን ቃሌን ልሰጥህ፣ ቃልህን ልቀበልህ!! በቃ ተስፋዬ ተሟጠጠ፤ የጓጓሁለትም የመምጫዬ ጊዜ አጠራጠረኝ። ገላዬ እኮ ከምንም በላይ ይናፍቅሃል! እውነተኛ ፍቅር በልቤ ስለመኖሩ መሀላና ምስክር የምትሻ አይመስለኝም። እወድሃለው እኮ! አልተለወጥኩም! ኑሮ አስመርሮኝ፣ ጤና ማጣት ማንነቴን እየተፈታተነ መኖር ስላስጠላኝ እንጂ በአንተም የጨከነ አንጀት ኖሮኝ አይደለም። አንተን ከማጣ ፍቅርህን በልቤ እንደሰነቅኩ ወደ መቃብሬ መውረድን እመርጣለሁ!!..የማይካድ እውነታ ተለያይተን ላንረሳሳ ትልቅ ምሰሶ የብረት ማገር በመካከላችን ጋርደን (ቃልን) በትዝታ እየተንገላታን ማዶና ማዶ ሆነን <ነበረን> መጨዋወት ከጀመርን ሁለት አመታት ተቆጠሩ። ወደ ኋላ ትንሽ ልመልስህ፥ በአብሮነት የፍቅር ጊዜያችን በአንተ ያለወጥኩት ፍጥረት አልነበረም፤ ቢኖር እንኳ አንድ እናቴ ብቻ ነች። ከተጣላኸው ተጣልቼ፣ ከተቀየምከው ተቀይሜ፣ የወደድከውን ወድጄ፣ ያቀረብከውን አቅርቤ፣ አንተን መስዬ ሣይሆን ሆኜህ አብሬህ ዘልቄ ነበር ፍፃሚያችን ያምር መስሎኝ – በተስፋ ጓጉቼ!! ከሁሉ ጋር እንደ ሺህ ዘመን የርስት ባላጋራ የጐሪጥ ስተያይ ኖሬያለሁ። የፍቅር ሃይማኖተኛ ባህታዊ መሆኔና መገዛቴ ጥሩ ባሪያ ተብዬ ያስመሰግነኛል እንጂ አያስንቀኝም! በጥሩ አፍቃሪነቴም እኮራለሁ እንጂ አላፍርም! አንተም ብትሆን እንደማትጠላኝ አውቃለሁ!..»

« .. ውድ የሆንከው ፍቅሬ ሆይ፥ የዚህ አለም ኑሮ አክትሞልኝ ፅዋዬን እስክጎነጭ፣ ተራ ደርሶኝ አንደበቴ ተሸብቦ እጅና እግሬ እስከሚታሰር፣እስትንፋሴ እስከቆመበት፣ በድኔ ወደከርሰ መቃብር ወርዶ የዘላለም እረፍቱን እስካገኘበት እለት የመጨረሻ ደቂቃና ሰኮንድ ድረስ አንተን ከማድነቅና የሕይወቴ እስትንፋስ መሆንህን ከመናገር ወደኋላ አልልም!! እወድሃለሁ! አፈቅርሃለሁና የሚደርስብኝን ችግር፣ የሚገጥመኝን ፈተና አንተን በማስታወስ ፍቅር ትዕግስቱን ሰጥቶኝ በደስታ ለማሳለፍ የቆረጥኩት ዛሬ አይደለም። ወደኋላ ሳስብ “አንተን አፍቅሬ የተሰቃየሁበት፣ በቤተሰቤ የደረሰብኝ የስድብ ናዳ …ሁሉም ትዝታ ሆኖ፥ እንዳያልፍ የለም አለፈ። ያንተ ፍቅር ግን ምንግዜም በልቤ ውስጥ የማይቀልጥ የዘላለም ሻማውን እንዳበራ ይኖራል። መቼም ቢሆን የማይለወጥ ቃል ኪዳኔ ነው!! ከአምላኬ በታች ያመለኩህ አንተን ብቻ ነው!! ብትጠላኝ ላልጠላህ፣ ብትክደኝ ላልከዳህ፣ ብትርቀኝ ላልርቅህ፣ ብትሰድበኝ ብትንቀኝና ብታዋርደኝ፣ ላልሰድብህ ላልንቅህ ላላዋርድህ፣ ከትእዛዝህ ውጭ ላልወጣ “እሺ” ከማለት በቀር መጥፎ ቃላት ላልሰነዝር..ፍቅር ሸብቦ የያዘኝ የአንተው ምርኮኝ ነኝ!! ልቤ ፍቅርህን ከማሽበልበል ውጭ መርዝ አይተፋም። አንደበቴ ፍቅርህን( አንተነትህን) ከማድነቅ በቀር ሬት አይተፋም!! ፍቅርህ ጣፋጭ ነው!! ቁጣህ አስደንጋጭ – ንግግርህ አስፈሪ፣ ቁልምጫህ አጥጋቢ – ፀብህ መራራ፣ ልብህ የዋህ – አስተሳሰብህ ጠንካራ (አስተዋይ)፣ ተክለቁመናህ ማራኪ – ቁም ነገር አዋቂ፣ አላማህ ተወዳጅ – ለችግር ፈጥኖ ደራሽ፣ በአጠቃላይ አምላክ ሲፈጥርህ ከሁሉም ነገር አድሎሃል። እወድሃለሁ! ልቤ ንፁህ ነው፤ ያንተን ፍቅር ብቻ የሚያስተናግድ!! አንደበቴ ቁጥብ ነው፥ አንተን ብቻ የሚያደንቅ!! ለእኔ ምንጊዜም ቢሆን ውድ ነህ!! ከማንም – ከምንም በላይ አፈቅርሃለሁ፤ እወድሃለሁ!! ”አፈቅርሃለሁ” ለሚለው ቃል መተኪያ ባገኝለትና የልቤን ብገልፅልህ ምንኛ ደስ ይለኝ ነበር መሰለህ!?..

ፍቅሬ ሆይ፥ ሁልጊዜ እሰጋለሁ፣ እጨነቃለሁ። አንተ ከእኔ ጋር የመኖር አላማ የሌለህ ስለሚመስለኝ ኑሮዬ የስጋት፣የጭንቀት፣ የብስጭት ይሆናል። ሌላ ምንም አያሳስበኝም። ደግሞም ከአንተ ተለይቼ ከምኖር (ልብ ተነጥቆ መኖር ከተባለ) ሞቴን እመርጣለሁና አደራ የገደል ላይ ሳር የሆነውን ሕይወቴን ነፍስ ዝራበት፤ በደመነፍስ የሚመራ ሕይወቴን፣ አላማቢስ የሆነብኝን ጭንቅላቴን፣ በጭንቀት የሚሸማቀቅ አካላቴን፣ አዝናናው፣ አበረታታው፣ ደባብሰው፣ ነፍሴ በአንተ ትለምልም፤ ካለአንተ ማን አለኝ፤!? አገር ቤት እያለሁ የሰራህልኝን ውለታ እስከ እለተ ሞቴ የማልረሳው ትልቅ ሸክም ነው። < ሸክም ነው ያለኩህ> ከፍዬ ስለማልጨርሰው ነው!! የእኔ ፍቅር አንድ ነገር ልንገርህ?፤ እኔን የአሜሪካ ኑሮ የሚያስደስተኝ፣ እዚህ ያለው ብልጭልጭ ነገር የሚያዘናጋኝ አይደለም። …አንድ ነገር ልብ በል፤ እየፃፍኩልህ ያለሁት ከሌሊቱ 7፡30 በኢትዮ.ሰዓት አቆጣጠር እንደሆነ እወቅ። ከእንቅልፌ ሠአት ላይ ቆጥቤ ነው በድቅድቅ ሌሊት የምፅፍልህ፤ እንጂ ቀንማ ትንፋሽም የለኝ። ምን ያክል ስለፋ እንደዋልኩ ፈጣሪ አይቷል!! የድካሙ ነገር አይነሳ.. እስቲ ተከድኖ ይቀመጥ፤ ስደትን ያየ ይፍረደኝ!?….ግን ዛሬ ደግሞ ደስ ያለኝ ነገር አንተ ማንንም እንዳልተላመድክ ገለፅክልኝ፤ ጥሩ ጌታ ያፅናህ! እኔስ ፀንቻለሁ በአካልም፣ በልብም፣ በመንፈስም። አምንሃለሁ! ባላምንህ ኖሮ መልስ አልፅፍልህም ነበር። አንተስ ታምነኛለህ?..እንደድሮው?..

ውድ ፍቅሬ፥ መኝታዬ ክፍል ጥግ ላይ ተቀምጬ እንባዎቼ በጉንጬ ላይ እየተሽኳለሉ ዱብ.. ዱብ..ዱብ ይላሉ። ፎቶዎችህን አስተውላቸዋለሁ፤ ድብዳቤዎችህን መላልሼ አነባቸዋለሁ፤ ደግሞ እፅፋለሁ። ልቤ ግን ድም -ድልቅታውን አያቋርጥም፤ የመገናኘት ምኞቴን በደውሉ ያስተጋባልኛል!! ያሳለፍነው እኮ እንኳን በነዚህ አመታት ቀርቶ መቼም የሚረሳ አይደለም፤ አይረሳም። አንተ ትረሳለህ ወይ?..ሰሞኑንማ ከመስሪያ ቤትህ ጀምሮ አዘውትረን እናድርበት የነበረው ..ሆቴል ድረስ ጣፋጩ ትዝታ በአእምሮዬ ይመላለሳል። ትዝ ይልህ እንደሆነ በዛ ሰሞን ፍቅር በዝቶ ቅብጥብጥ ሲያደርገን « ውዴ ፍቅር በዛ፤ ልንለያይ ነው መሰለኝ » ስትለኝ እኔም < እባክህ ፍቅሬ እንደዚህ አትበለኝ?> ብዬ አንገትህ ስር ሽጉጥ የምለው፣ በደረትህ የምንፈላሰሰው፣ አትዩብኝ የምለው አይንህ፣ አትንኩብኝ የምለው እጅህ…አረ ስንቱን…ስንቱን ልዘርዝረው!?…ውድ ነህ፣ እንቁ ነህ!

ውድ ፍቅሬ ሆይ፥ ግን አንድ ነገር የማልደብቅህና ከዚህ በፊት ደግሜ ደጋግሜ የፃፍኩልህ፣ በህልሜም ተደጋጋሚ ነገር ስላየሁ ሰጋሁ። አንተን በርግጥ ልመንህ?..እንዴት ነው ልቤ ያምንሃል፤ ህልሜ ግን አስፈራኝ። ስለዚህም ጉዳይ ገልፀህ ፃፍልኝ። ኩርት ያልክ ሁንልኝ!! ልክ እንደቀድሞህ። እንዲያ ከሆንክ ስመጣ አይኔን ለማየት አታፍርም። ከምንም በላይ ደግሞ ሕሊናህ ነፃ ይሆናል!! ካልሆነ ግን ከእኔ ይበልጥ እራስህን ሰላም ታሳጣለህና ጠንቀቅ፣ ሰቅጠጥ በል!! “ምነው ይህቺ ልጅ ጨቀጨቀችኝ” እንደማትለኝ ነው!?..ፍቅር የወለደው የስጋት ጭንቀት ነውና አትፍረድብኝ። ..ቦሌ ላይ ስትሸኘኝ አንድ ጥያቄ ጠይቀኸኝ ነበር፤ < አንቺ ግን ቃልሽን ጠብቀሽ፣ አስችሎች ሌላ ሳትላመጂ እንገናኛለን? > ስትለኝ እኔም “ራሴን የምፈትንበት ጥሩ አጋጣሚ ይሆናል፤” ብዬህ ነበር። አዎ! አንተን ካላሰብኩ በቀር ገላዬ ፈተናውን በቅጡ ተወጥቷል። በፈጣሪ እርዳታ!! …በብዙ ፈተና ተፈትኜ አለፍኩ፤ ማለፍ ያቃተኝ ግን የልቤን ፈተና ነው። ጊዜ ይፈታዋል!!…አሁን ላበቃ ጥቂት መስመሮች ቀርተውኛል። የደስታ ብስራት ላቋድስህ፤ ከ6 ወራት በኋላ ልመጣ ነው..» አበቃ።…..ይህ እውነተኛ ታሪክ ሲሆን የፍቅር ሴረኞች ለያዩዋቸው። ባለታሪኮቹ….

በነ ሀብታሙ አያሌው የክስ ጉዳይ የተሰየመው ችሎት ‹አስገራሚ› ውሎ

∙ተከሳሾቹ ‹‹ዘረፋ›› ተፈጽሞብናል ብለዋል ∙‹‹ለማን አቤት ይባላል?›› ሀብታሙ አያሌው

በላይ ማናዬ : ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት ቀርበው ነበር፡፡ የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ እንዲሁም አንደኛ ተከሳሽን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች ተሟልተው ፍርድ ቤት ተገኝተዋል፡፡

ችሎቱ የተሰየመው ታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ ወቅት ተከሳሾች በቀረበባቸው የሽብር ክስ ላይ የሰጡትን መልስ በተመለከተ 7ኛ ተከሳሽ መልስ በዕለቱ ባለማቅረባቸው አሟልተው እንዲቀርቡ ነበር፡፡ በተጨማሪም ተከሳሾች በእስር ላይ ባሉበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሊጎበኟቸው የሚሄዱ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ወደ እስር ቤቱ ሲገቡ በተለየ መዝገብ እንዲመዘገቡ እየተደረጉ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበው ስለነበር ይህን በተመለከተ ማረሚያ ቤቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ በታዘዘው መሰረት ማብራሪያውን ለመስማት ነበር፡፡
Image
የተከሳሾች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች በጥየቃ ወቅት በተለየ መዝገብ ይመዘገባሉ የተባለውን አቤቱታ በተመለከተ፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በደብዳቤ መልስ መስጠቱ የተገለጸ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ‹‹ማረሚያ ቤቱ በሰጠው መልስ እስረኞች ከሌሎች በተለየ የደረሰባቸው ችግር የለም›› ማለቱን ገልጾ ይህንኑ መልስ ሙሉ ለሙሉ መቀበሉን አስታውቋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በዛሬው የችሎቱ ውሎ ላይ ተከሳሾች ለየት ያለ አቤቱታ በጠበቆቻቸው በኩል አቅርበዋል፡፡ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ለችሎቱ እንዳስረዱት ደንበኞቻቸው ከሌሎች በተለየ መልኩ ከፍተኛ በደል እየተፈጸመባቸው ነው፡፡ አቶ ተማም አባቡልጉ በታህሳስ 12 ለ13 ቀን 2007 ዓ.ም አጥቢያ ሌሊት ስምንት ሰዓት ጀምሮ ደንበኞቻቸው ላይ ድንገተኛ ፍተሻ ተደርጎ የግል ማስታወሻዎቻቸው፣ ገንዘብ እና በተከሰሱበት ጉዳይ ላይ እያዘጋጁት የነበረው መቃወሚያና መከራከሪያ ተወስዶባቸዋል ብለዋል፡፡

‹‹ደንበኞቼ ላይ እየተደረገ ያለው ጉዳይ ለህይወታቸውም የሚያሰጋቸው ነው፡፡ በማረሚያ ቤቱ በሌሊት ፍተሻ ያደረጉባቸው ሰዎች ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ‹ህገ-ወጥ› ተግባራት ሲፈጽሙባቸው የነበሩ የፌደራል ፖሊስና የደህንነት አባላት ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህን ሰዎች ደንበኞቼ ያውቋቸዋል፡፡ ስለሆነም ፍተሻው የተከናወነው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አልነበረም ማለት ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው የተለየ የስም ዝርዝር ተይዞ ከሌሎች በተለየ መልኩ ነው፡፡ ለአብነት ደንበኞቼ አቶ አብርሃ ደስታና በሌላ የክስ መዝገብ የተከሰሰው አብዱራዛቅ አክመድ ላይ የሆነው ከሌሎቹ በተለየ መልኩ ነው፡፡ ፍተሻው ስለት ነገር አልያም ሌላ ህገ-ወጥ ቁሳቁስ ለመያዝ የተደረገ አለመሆኑን ከተወሰዱት ንብረቶች ማየት ይቻላል›› ሲሉ አቶ ተማም ለፍርድ ቤቱ በደንበኞቻቸው ላይ የተፈጸመውን ድርጊት አስረድተዋል፡፡

ይህን በተመለከተ አስተያየት የሰጡት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ በበኩላቸው፣ ‹‹ማረሚያ ቤቱ መንግስት ዜጎች ታንጸው እንዲወጡ ያሰራው ነው፡፡ ይህን አሰራር ለመጠበቅም የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የተለያዩ ስራዎችን ሊሰራ ይችላል፡፡ እየቀረበ ያለው አቤቱታም ከዚህ አኳያ መታየት ያለበት ነው›› ብለዋል፡፡

ጠበቃ ተማም የደንበኞቻቸውን አቤቱታ ከህግ አንጻር ያስረዱ ሲሆን፣ ‹‹በመሰረቱ ፍተሻ ሊካሄድ መቻሉ ላይ አይደለም አቤቱታው፡፡ የተካሄደው ፍተሻ ግን ህገ-ወጥ ነው፤ ምክንያቱም ፍተሻው የተከናወነበት ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ባለው ጊዜ ሳይሆን ሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ነው፡፡ ይህ ህገ-ወጥ ነው፡፡ በሌላ በኩልም ፍተሻው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አይደለም የተከናወነው፡፡ በደህንነቶችና የፌደራል ፖሊሶች ነው ፍተሻው የተደረገው፡፡ ይህም ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎቱም ሆነ ብቃቱ እንደሌለው ያሳያል፡፡ ስለሆነም ፍርድ ቤቱ ይህን መሰል ድርጊት የፈጸሙት አካላትና በማን ትዕዛዝ እንደተፈጸመ ምርመራ እንዲካሄድ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን›› ብለዋል፡፡

ጠበቃ ተማም በተጨማሪ ከደንበኞቻቸው ላይ በፍተሻው ወቅት የተወሰዱባቸው ንብረቶችና ማስታወሻዎች እንዲመለሱላቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው አመልክተዋል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ ‹‹የተለየ ከፍተኛ በደል ደርሶብኛል›› በሚል ለፍርድ ቤቱ እንዲያስረዱ ዕድል እንዲሰጣቸው ጠይቀው የነበሩት 3ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሺ የጠየቁት የመናገር እድል ሳይፈቀድላቸው ቀርቷል፡፡

በጠበቆቹ አማካኝነት የቀረበው አቤቱታን በተመለከተ ችሎቱ አስተያየት የሰጠ ሲሆን በተለይ ጠበቃ ተማም አቤቱታውን ባቀረቡበት ወቅት ‹‹ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎትም ብቃትም የለውም›› ያሉት አገላለጽ ተገቢ ስላልሆነ እንዲታረሙ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በቃል የገለጹት የመሐል ዳኛው፣ ‹‹እንዲህ አይነት አገላለጽ ማረሚያ ቤቱ የበቀል እርምጃ እንዲወስድ የሚገፋፋ እንዳይሆን…›› በማለት ሌላ አስገራሚ መነጋገሪያ ከፍተዋል፡፡

ይህን የዳኛውን ንግግር ተከትሎ 2ኛ ተከሳሽ አቶ ሀብታሙ አያሌው የመናገር እድል ከተደጋጋሚ ጥያቄ በኋላ ለአጭር ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡ እናም፣ ‹‹እርስዎ እያሉት ያለው ነገር ተገቢ አይደለም፡፡ በህይወቴ ላይ የደህንነት ስጋት አለብኝ ነው እያልኩ ያለሁት፡፡ ይህንን ስጋቴን ለችሎት እያስረዳሁ ነው፡፡ ግን እርስዎ ‹የበቀል እርምጃ› እንዲወሰድብን ማሳሰቢያ እየሰጡ ነው፡፡ ይህ ተገቢ አይደለም፡፡ በእርግጥ አሁንም የበቀል እርምጃ እንደማይወሰድብን ማረጋገጫ የለንም፡፡ እሺ ለማን አቤት ይባላል? የደረሰብንን በደል ለፍርድ ቤት ከማስረዳት ውጭ ለማን አቤት እንላለን….አሁን እኮ ፍርድ ቤቱ ከማረሚያ ቤቱ ጋር መወገኑን ነው እያየን ያለነው፡፡ ፍርድ ቤቱ የእኛን አቤቱታ እየሰማ አይደለም፡፡ ከፍርድ ቤት ውጭ ለማን አቤት እንበል?›› ሲል አቤቱታውን በስሜት ውስጥ ሆኖ አስረድቷል፡፡

የሀብታሙን ንግግር አዳምጠው አንደኛ ዳኛ ‹‹እኛ ሳንሆን ህጉ ነው ይህን እንድንል የሚያደርገን›› በማለት አጭር መልስ ሰጥተዋል፡፡

በዚህ መልኩ ቀጥሎ የዋለው ችሎት በተከሳሾች በኩል የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ፍርድ ቤቱ ይህን ጉዳይ የማየት ስልጣን አለው ወይስ የለውም በሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት፣ እና መደበኛ ክሱን ለማየት ለታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተጥቷል፡፡
‪#‎NegereEthiopia‬

ሪፖርተር ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ በዘመነ መንግሥታቸው ለትምህርት ከፍተኛ ትኩረት ይሰጡት እንደነበርና ለዚህም እውን መሆን ራሳቸው የትምህርት ሚኒስትር እንደነበሩ ይወሳል፡፡ ከሕይወታቸው ፍፃሜ በኋላም የእሳቸውን ጅማሬ ለማስቀጠል በስማቸው መታሰቢያ ማኅበር ተቋቁሟል፡፡ ማኅበሩም በሕይወት ዘመናቸው ትኩረት ይሰጡት ለነበረው የትምህርት ዘርፍ በተቻለ መጠን ተጠናክሮ እንዲቀጥል እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙና በአካዴሚክ ዕውቀታቸው በጣም ጠንካራ ሆነው […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከወራት ፀጥታ በኋላ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከሚዲያው ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተዋል፡፡ የሰሞኑ ዋና የመወያያ ርዕስ የሆነውንና አገሪቱ ወደ ዓለም አቀፉ የቦንድ ገበያ ለመግባት ያደረገችውን ጥረት እንደተጠበቀው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያብራሩት ዋናው ጉዳይ ነበር፡፡ ‹‹አገሪቱ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ገበያው ገንዘብ ለማግኘት ብቁ ሳትሆን ቆይታለች…›› በማለት ጉዳዩን ያስረዱት አቶ ኃይለ ማርያም፣ በስኳር […]

እነ ሀብታሙ አያለው ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ የዛሬ ቀጠሯቸው መቃወሚያ ለማቅረብ የነበረ ቢሆንም ታህሳስ 12 ቀን 2007 ዓ.ም በደረሰባቸው ድርጊት ፍርድ ቤቱ ሌላ ቀጠሮ ለመስጠት ተገዷል፡፡ በለቱ ሌሊት 8፡00 ላይ የእስር ቤቱ የስራ ባልደረባ ያልሆኑ የደህንነትና የፖሊስ አባላት ለዛሬው ቀጧሯቸው የሚሆን የመቃወሚያና የመከራከሪያ ሰነዶቻቸውን ወስደውባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ገንዘባቸው እንደተወሰደባቸው ጠበቃቸው ተማም […]


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ                                  
—–
በ7ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ የተጠነሰሰው እስላማዊ ኪነ-ህንጻ በአስራ አራት ክፍለ ዘመናት ውስጥ እያደገ ብዙ ፈርጆች ያሉት የጥበብ  ዘይቤ ሊሆን በቅቷል፡፡ በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ አድናቆት የተቸራቸው ቋሚ ግንባታዎችንም አበርክቷል፡፡ በካይሮ ከተማ የሚገኘው የአል-አዝሃር መስጊድ፣ የደማስቆው “የበኑ ኡመያ” መስጊድ (the Omayyad Mosque)፣ የኢስታንቡል “ሱሌይማኒያ” መስጊድ፣ በኢስፋሓን የሚገኘው የኢማም አደባባይና መድረሳ (Midyyan-e-Imami)፣ የህንዱ ታጅማሃል፣ ታላቂ የቁርጡባ መስጊድ (Great Mosque of Cordoba)፣ የግሪናዳ ከተማ መከላከያ ግንብ (fortress) እና ልዩ ልዩ ግንባታዎች፤ የፌዝ ከተማ የመከላከያ ግንብና ጥንታዊው የቃራዊያን መስጊድ (ሞሮኮ)፣ ከጭቃ የተሰሩት የቲምቡክቱ መስጊዶች ወዘተ… ከተደናቂ እስላማዊ ግንባታዎች ጥቂቶች ናቸው፡፡
እስላማዊ ኪነ-ጥበብ ብዙ ፈርጆች እንዲኖሩት ያደረገው በባህሪው “ሆደ ሰፊ” በመሆኑ ነው፡፡ ይህም ሲባል ከሙስሊሙ ዓለም የተገኙት የኪነ-ህንጻ ጠቢባን በየሀገራቸው የነበሩትን ጥንታዊ የንድፍ ዘይቤዎች ከእስልምና መርሆች ጋር በማጣጣም አዳዲስ የኪነ-ህንጻ ዘይቤዎችን ይፈጥሩ ነበር ለማለት ነው፡፡ ለምሳሌ በኢስታንቡል ከተማ የሚገኙት ታላላቅ መስጊዶች የተሰሩት የጥንቱን የቤዛንታይን ኪነ-ህንጻ ከዐረቢያና ከፋርስ ኪነ-ህንጻ ጋር በማዋሃድ በተፈጠረው የቱርክ ኪነ-ህንጻ ዘይቤ ነው፡፡ የቲምቡክቱ መስጊዶችም የማሊን ጥንታዊ የኪነ-ህንጻ ጥበብ መሰረት በማድረግ ነው የተሰሩት፡፡
ጥንት ከተገነቡት እስላማዊ ቅርሶች መካከል ከፊሎቹ ጠፍተዋል፡፡ ግማሽ ያህሉ ግን ዛሬም ቋሚ ሆነው ታሪክን ይመሰክራሉ፡፡ በእስላማዊ ግንባታዎቻቸው በዓለም ዙሪያ የተደነቁት ከተሞች የሚከተሉት ናቸው፡፡
1.      መካ
2.     መዲና
3.     እየሩሳሌም
4.     ባግዳድ (ኢራቅ)
5.     ሰመራ (ኢራቅ)
6.     ቡኻራ (ኡዝቤኪስታን)
7.     ሰመርቀንድ (ኡዝቤኪስታን)
8.     ደማስቆ (ሶሪያ)
9.     ኢስታንቡል (ቱርክ)
10.    ሂራት (አፍጋኒስታን)
11.     መዘር-ኢ-ሸሪፍ (አፍጋኒስታን)
12.    ቁርጡባ (ስፔን)
13.    ግሪናዳ (ስፔን)
14.    ካይሮ (ግብጽ)
15.    ሰንዓ (የመን)
16.    ዘቢድ (የመን)
17.    ፌዝ (ሞሮኮ)
18.    መራኪሽ (ሞሮኮ)
19.    ቱኒስ (ቱኒዚያ)
20.   ቲምቡክቱ (ማሊ)
21.    ጄኔ (ማሊ)
22.   ሀረር (ኢትዮጵያ)
23.   ዛንዚባር (ታንዛኒያ)
24.   ኒሻፑር (ኢራን)
25.   ኢስፋሓን (ኢራን)
26.   ሺራዝ (ኢራን)
27.   ቴህራን (ኢራን)
28.   ጠብሪዝ (ኢራን)
29.   ዴልሂ (ህንድ)
30.   አግራ (ህንድ)
እስላማዊ ኪነ-ህንጻ ሲጠቀስ በቀዳሚነት ከሚወሱት ጠቢባን መካከል አንዱ ከ1489 እስከ 1588 የኖረው ቱርካዊው “ሲናን” ነው፡፡ ቱርኮች ይህንን ሰው ሲጠሩት “ኮጃ ሚማር ሲናን”፣ ማለትም “ታላቁ አርክቴክት ሲናን” ይሉታል፡፡ ችሎታውን ሲገልጹም “እርሱን የመሰለ የኪነ-ህንጻ ጠቢብ አልተፈጠረም” ነው የሚሉት፡፡ በርግጥም በመቶ የሚቆጠሩ “እጹብ ድንቅ” የተባሉ ስራዎቹን ያየ ሰው በከፊልም ቢሆን የቱርኮችን አባባል መጋራቱ የማይቀር ነው፡፡
 “ሲናን” የተወለደው “አጊርናዝ” በተባለች የቱርክ አነስተኛ ከተማ ነው፡፡ በልጅነቱ በአባቱ ስር የአናጺነትና ድንጋይ የማሳመር ጥበብን ተማረ፡፡ አንድ ቀን ግን ህይወቱን የቀየረ አጋጣሚ ተፈጠረ፡፡ በዚያ ቀን (በ1521) የኦቶማን ቱርክ ወታደራዊ ኦፊሰሮች ወደ ሲናን መንደር ሄደው ለውትድርና የሚቀጠሩ ወጣቶችን ይመዘግቡ ነበር፡፡ የሲናን ወታደራዊ አቋም የሚያመረቃ ሆኖ ስለተገኘ እርሱንም መዘገቡትና ወደ ቁስጥንጥንያ (የአሁኗ ኢስታንቡል) ወሰዱት፡፡ እዚያም ልዩ ልዩ ትምህርቶችን እንዲያጠና አደረጉት፡፡
የሲናን የጥበብ ተሰጥኦ መታየት የጀመረው በ1530 ድልድዮችንና ልዩ ልዩ ወታደራዊ ግንባታዎችን መስራት ሲጀምር ነው፡፡ በ1539 ግን ከውትድርናው ዓለም ተሰናብቶ የሲቪል ግንባታዎችን ጀመረ፡፡ በቀጣዮቹ 40 ዓመታትም ቱርክን በዓለም ዙሪያ ያስጠሯትን የልዩ ልዩ ግንባታዎችን ንድፍ እየወጠነ በራሱ አመራር በማስገንባት ለአግልግሎት አበቃ፡፡
ሲናን በህይወት ዘመኑ 79 መስጊዶችን፣ 34 ቤተ መንግሥቶችን፣ 33 የህዝብ የመታጠቢያ ገንዳዎችን (በተለምዶ “Turkish bath የሚባሉት)፣ 19 የመቃብር ስፍራዎችን፣ 55 ትምህርት ቤቶችን፣ 16 የድኾች መኖሪያ ማዕከላትን፣ 7 የከፍተኛ ደረጃ መድረሳዎችን፣ 12 ታላላቅ ምግብ ቤቶችን ሰርቷል፡፡ የፍሳሽ መውረጃዎች፣ ፋውንቴኖች፣ ሆስፒታሎችና ሌሎችንም ገንብቷል፡፡ የሁሉንም ግንባታዎች ንድፍ (ዲዛይን) የሰራው ራሱ ሲሆን በመሃንዲስነት አስጀምሮ የሚጨርሰውም እርሱ ነበረ፡፡
ከሲናን ግንባታዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱት የሱሌይማኒያ መስጊድ (በፎቶው ላይ ያለው)፣ የሻሕ ዛድ መስጊድ እና የሰሊም መስጊድ ናቸው (የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ በኢስታንቡል ነው የሚገኙት፤ የሰሊም መስጊድ ግን በኢድሪን ከተማ ነው የተሰራው)፡፡ ሲናን የኔ ምርጥ ስራ ነው የሚለው “የሻህ ዛድ መስጊድ”ን ነው፡፡ የኪነ-ህንጻ ጠበብት በጣም የሚያደንቁት ግን የሱለይማኒያ መስጊድን ነው፡፡
—-
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 6/2007
—-
The writer, Afendi Muteki, is a researcher and author of the ethnography and history of the peoples of East Ethiopia.  You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click the following link to go to his page.

Image
– የድሬደዋ አየር ሃይል መምሪያ በግምገማ ታመሰ::
– መጭውን ውህደት የሚያሳፈጽሙ የአርበኞች ግንባር አባላት ከአውሮፓ እና አውስትራሊያ ተወከሉ::
http://ireport.cnn.com/docs/DOC-1200173
አርብ እለት ከድሬዳዋ ተነስተው በደቡባዊ ኤርትራ አሰብ ዘልቀው የገቡት የወያኔው አየር ሃይል አብራሪዎች እና ቴክኒሺያኖች በደህና ሁኔታ ውስጥ ሲገኙ በኤርትራ የአየር ክልል የተቀበላቸው እና በ1987 አመተምህረት በወያኔ እና የደርግ መኮንኖች የሰለጠነው የሻእቢያ ኮማንዶ ጦር አጅቧቸው ወደ አስመራ ቤተመንግስት ከገቡ በኋላ በቤተ መንግስቱ ውስጥ ለሁለት ቀን በእንግዳ ማረፊያ ክፍል ውስጥ ቆይተው ወደ ሆቴል መዘዋወራቸውን ከአስመራ የተገኙ ምንጮች ጠቁመዋል::

በቤተ መንግስት ቆይታቸው አስፈላጊ ጥያቄዎች እና ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን ከደምህት ጦር ጋር በመቀላቀል እየተገነባ ባለው ዘመናዊ አየር ሃይል ውስጥ አገልግሎት እንዲሰጡ የተጠየቁ መሆኑን ምንጮቹ ሲናገሩ አብራሪዎቹ ግን ወደ አውሮፓ ለመጓዝ ፍላጎቱ እንዳላቸው እና አውሮፓ ሆነው ትግሉን መርዳት እንደሚችሉ ሲናገሩ ተደምጠዋል::አብራሪዎቹ እጃቸውን የሰጡትም ሆነ የተቀላቀሉት ከኤርትራ መንግስት ጋር እንጂ ከሌላ አካል ጋር እንዳልሆነ ምንጮቹ አረጋግጠዋል::

ከደብረዘይት አየር ሃይል አከባቢ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በድሬዳዋ ያለው የአየር ሃይል ካምፕ ሃላፊዎች ላይ ከፍተኛ ግምገማ ተደርጓል::በዚህም መሰረት የሃገሪት የአየር ክልል ሳይቀር ከራዳር ውጪ ነው የሚል ጉዳይ ተነስቶ መነጋገሪያ እና መገማገሚያ ሆንዋል::እርስ በርስ መወነጃጀል እንኳን ባልተደፈረበት ግምገማ ላይ እያንዳንዱ መኮንን ሃላፊነቱን ወስዶ ዋጋ ሊከፊል ዪገባዋል ሲሉ ከፍተኛ አዛዦች በቁጣ ተናግረዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ በመጪዎቹ ሳምንት በሚካሄደው የግንቦት ሰባት እና የአርበኞች ግንባር ውህደት ላይ እስካሁን ወኪል ያላከው የአርበኞች ግንባር አንድ ሰው ከአውሮፓ አንድ ሰው ከአውስትራሊያ በመምረጥ ለእህደት ስብሰባው ማስትላለፉን ምንጮቹ ተናግረዋል::የተመረጡት አስመራ እንደደረሱ በውህደቱ ዙሪያ ንግግር እንደሚጀመር እና የፊርማው ውህደት እንደሚጸድቅ ኮሎኔል ፍጹምን ዋቢ ያደረጉ ምንጮች ጠቁመዋል::

ኒዮሊበራል ሀይሎች በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ምርጫ ከ 10 አመታት በፊት እንደሞከሩት ሁሉ የቀለም አብዮት ለመቀስቀስ እየተጠቀሙበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሰሱ።

ታኀሳስ ፲፬(አስራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአየር ሃይል ባልደረባ የሆኑት ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝ ከበረራ ቴክኒሻኑ ጸጋ ብርሃን ግደይ ጋር በጋራ በመሆን የሚያበሩትን ሄሊኮፕተር ይዘው ከጠፉ በሁዋላ የአየር ሃይል አዛዦች አስቸኳይ ግምገማ ከተጠሩ በሁዋላ እርስ በርስ እየተገማገሙና ከእነዚህ ሰዎች ጋር ግንኙነት አላቸው ብለው የሚያስቡትን የአየር ሃይል አባላት ለማሰር እንቅስቃሴ መጀመራቸውን …

ታኀሳስ ፲፬(አስራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መድረክ ባወጣው መግለጫ  በሀገራችን የምርጫ ሂደት የነበሩ ጉድለቶችንና በተለይም በ2002 የሀገራችን የምርጫ ሂደት የወረደበትን አዘቅት በሚገባ በጥልቀት ገምግሞ እነዚህን ቀደም ባሉት ምርጫዎች የነበሩ ጉድለቶችን ማረምና ማሰተካከል ለ2007 ምርጫ ነፃ፣ ፍትሓዊና ዴሞክራሲያዊ መሆን የምኖረውን ወሳኝ ሚና በግልጽ ቢያስቀምጥም፣ ይህንን እውነታ በአግባቡ መገንዘብ ያልቻሉና ከ1997 እና ከ2002 ምርጫዎች ደካማ …

ታኀሳስ ፲፬(አስራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ታህሳስ 10 /2007 ዓ.ም ለአምስት ሰዎች ሞትና ለበርካቶች አካል መጉደል ምክንያት በሆነው የተቃውሞ ሰልፍ ዙሪያ የገዢው መንግስት አስቸኳይ  መግለጫ እንዲሰጡ ያስገደዳቸው የኃይማኖት አባቶች በመስቀል አደባባይ ዙሪያ ላይ የቀረበውን ጥያቄ በደስታ እንደተቀበሉት በመግለጫቸው መስጠታቸው እና ምዕመኑን እንደ ጥፋተኛ በመቁጠር ማግለላችው እንዳበሳጫቸው በትላንትናው ዕለት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢ …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ከ100 000 ሺ በላይ ስደተኞች አውሮጳ በተለይ ኢጣሊያ መግባታቸው፣ የቀኝ አክራሪዎች-የውጭ ሃገር ዜጎች ጥላቻ መባባስ፣ ብሎም በአውሮጳ ምክር ቤት አሸናፊ ሆነው መውጣት እንዲሁም ሌሎች አበይት ነጥቦች በዛሬው አውሮጳ እና ጀርመን ጥንቅራችን ተካቷል።

የዓለም የምግብ እና የእርሻ ድርጅት በተገባደደዉ ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት የተሻለ የሰብል ምርት መገኘቱን በቅርቡ ይፋ አድርጓል። በተቃራኒዉ በመላዉ ዓለም ወደ805 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ በቂ ምግብ እንደማያገኝም ጠቁሟል። ከአየር ንብረት ለዉጥና ከለዉጡ መዘዞች በመታገል የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጥረቶች በተለያዩ ሃገራት እየተሞከሩ ነዉ።

«የምዕራብ ፀረ-እስልምና የአውሮፓ አርበኞች» በጀርመንኛ ምህፃሩ ፔጊዳ የተሰኘዉ ኅብረት ፤ የጀርመን ዋና የመነጋገሪያ ርዕስ ከሆነ ሰነበተ። ህብረቱ ተቃውሞ ቢገጥመውም ትናንት 10ኛውን የተቃውሞ ሰልፍ በድሬስድን ከተማ አካሂዷል።

የኢቦላ ተሐዋሲን ጨምሮ በአፍሪቃ የረሀብ አደጋም ስጋት እንደፈጠረ ተገለጠ። ከአፍሪቃ ጋር የሚደረግ የንግድ ግንኙነት ኅብረተሰቡን በማይጎዳ መልኩ መሆን እንደሚገባው የጀርመን መራሒተ-መንግሥት የአፍሪቃ ልዕክ ተገልጧል። የምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት ኢቦላን ለመዋጋት ለሚያደርጉት ጥረት ጀርመን የምትሰጠው ድጋፍ እንደሚቀጥል አስታውቃለች።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የደቡብ ሱዳንን ቀውስ ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ማዕቀብ የመጨረሻው አማራጭ ሊሆን እንደሚችል አመለከቱ። ከዚህም ሌላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አገራቸው ተጨማሪ ጦር ወደ ሶማሊያ ለማዝመት ዝግጁ እንደሆነች መግለፃቸዉንም የፈረንሳይ ዜና ወኪል ዘግቧል።

መኢአድ (የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት) አንጋፋ ድርጅት ነው። ከመስራቹ ከፕሮፌሰር አስራት ጀመሮ የዚህ ድርጅት አባላትና ደጋፊዎች እጅግ ብዙ ዋጋ ከፍለዋል። ብዙዎች ሞተዋል፤ ብዙዎች ታስረዋል። ከማንም ድርጅት ባልተናነሳ ገዢው ሙሸት አማረ በሚመራዉና በአቶ አበባው በሚመራው ቡድን መካከል ያሉ ልዩነቶች በአሁኑ ወቅት መኢአድ ትንች በተጠናከረ መልኩ ወደፊት እንዳይሄድ አድርጎታል። የነዚህ ሁለት ቡድኖች ዉዝግብ ገና አልተፈታም። ሕጋዊዉ የመኢአድ […]

“ለነፋስ ተርባይኖች” ግዢ በሚል ሰበብ በየአመቱ እንደዘበት የሚባክነው የቢሊዮን ብሮች ሃብት ሲታይ፣ በእርግጥም በኢትዮጵያ ታሪክ አቻ የማይገኝለት ቅሌት ነው ማለት ይቻላል። በየትኛውም አገር ቢሆን፣ በበለፀጉት አገራትም ጭምር፣ ከፍተኛ ሃብት በከንቱ እንዲባክን ማድረግ አሳፋሪ ተግባር ነው። አብዛኛው ህዝብ ችግረኛ በሆነባት፣ ሩብ ያህሉ ካለምፅዋት ሕይወቱን ማቆየት በማይችልባትና ገና አንገቷን ቀና ለማድረግ በምትውተረተር ደሃ አገር ውስጥ፣ በፈቃደኝነት ሃብት […]

Image

“ካልመለሱልኝ በውጊያ አስመልሰዋለሁ::” የደነገጠው ወያኔ
(ምንሊክ ሳልሳዊ)
ስርአቱን ከዱ የተባሉት አብራሪዎች ከድሬዳዋ ተነስተው በጅቡቲ ድንበር አስታከው በአሰብ ዘልቀው ኤርትራ ያሳረፉት ሄሊኮፕተር በሱዳን በኩል እንዲመለስለት ሻእቢያን መጠየቁን የሱዳን ዲፕሎማቶች ጠቆሙ::

ወያኔ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚያደርገውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እና በአየር ሃይሉ ውስጥ የሚፈጸመውን ደባ በመቃወም ከድተዋል የተባሉት 2 ፓይለቶች(ካፒቴን ሳሙኤል እና ቢሊሊኝ )እና አንድ ቴክኒሽያን(ጸጋ ብርሃን)ለኤርትራ መንግስት እጃቸውን የሰጡ ሲሆን ይህንንም የወያኔው ቴሌቭዥን ጣቢያ እማኝነቱን ሰቷል:: http://andargachewtsige.com/?p=383 ) አብራሪዎቹ ይዘውት የሄዱትን ሄሊኮፕተር እንዲመለስለት ወያኔ የሱዳን ዲፕሎማቶችን የላከ ሲሆን ሻእቢያ የማይመልስ ከሆነ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ከባድ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አንድ ለስርአቱ ቅርብ የሆነ ድህረገጽ ጽፏል::

በሃገር ውስጥ እና በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንደ ፖለቲካ ድል ሲቆጥሩት አንዳንዶቹ ወያኔ የሻእቢያን አየር ሃይል በሰው ሃይል እየገነባ ሊሆን ይችላል ከጀርባ ሌላ ደባዎች በወያኔ እና ሻእቢያ ሊሰራ ይችላል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አልጠፉም::የወያኔ መክላከያ ሰራዊት አጸፋዊ እርምጃ ይወስዳል የሚል ስጋት ቢያይልም;ሃገር ወዳዶች ግን ምንም እርምጃ አይወስድም የፍርሃት ዛቻ ነው ሲሉ ተደምጠዋል::

ቁም ነገር ቅጽ 13 ቁጥር 193 ታህሣስ 2007

ለሶደሬ

መነሻ

በሀገራችን የኪነ ጥበብ ሙያ ውስጥ በሙያው አንቱ የተባለ አንድ አርቲስት ከዓመታት በፊት በአንድ ፊልም ላይ እንዲተውን ጥያቄ ይቀርብለታል፡፡ ጥያቄውን ተቀብሎ…

ትግራይ ክልል ላይ የሚፈፀሙትን ጭቆናዎች ሳይታክት አጋልጧል። ዘረኝነትን ፣ አምባገነንነትን ፣ ሙሰኝነትን ፣ ኢ-ፍትሐዊነትን አውግዟል። ሰብአዊነትን በማስቀደም ሰውን በሰውነቱ የሚለካ ምርጥ ኢትዮጵያዊ ነው-አብርሃ ደስታ፡፡ አብርሃ ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ የብዙ ሰዎችን ቀልብ ለመሳብ ከመቻሉም በላይ ፤ “ፌስቡክን” ከፌዝ-ቡክነት በመታደግ የተለያዩ ጠቃሚ መረጃዎችን ሲያቀብለን ነበር፡፡ በመግቢያችን ላይ በአጭሩ እንደተገለጸው ይህ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ፣ የአሁኑ የፖለቲካ እስረኛ […]

ጓድ ቆምጬ አምባው በስማቸው የሚነገሩትን ጨዋታዎች በኔ ስም የተፈጠሩ ተረቶች ይሏቸዋል፡፡ ሰውዬውን በቅርበት የሚያውቁት ግን በርሳቸው ስም የተፈጠሩት ጨዋታዎች ከፊል እውነታ እንዳለባቸው ይናገራሉ፡፡ በርካታ ሰዎች ጨዋታዎቹን እያወሱ የሰውዬውን ጅልነት ሊያሳዩ እንደሚፈልጉ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ቆምጬ አምባው ነገር የገባቸው ብልጥ ነበሩ እንጂ በጭራሽ ጅል አይደሉም፡፡ ይህንን ለማሳየት እንዲቻለንም በርሳቸው ስም ከሚነገሩት ጨዋታዎች መካከል ጥቂቶቹን እንጽፍላችኋለን፡፡ ***** በደርግ […]


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
በህይወት እስካለን ድረስ ተረት መተረታችንን አናቆምም፡፡ እነሆ ለዛሬም በምሥራቁ የሀገራችን ክፍል እየተደጋገሙ የሚነገሩ ሁለት ትራጄዲ ተረቶችን አዘጋጅተንላችኋል፡፡
===የተንኮል ገበቴ===
እናት አንድ ልጅ ብቻ ነበራት፡፡ ይህንንም ልጅ በብዙ ልፋት ካሳደገችው በኋላ ለአቅመ አዳም ሲደርስ ዳረችው፡፡ ታዲያ የልጁ ሚስት እናትዬውን የምትወድ አልነበረችም፡፡ በብዙ አድራጎቷ ትበድላታለች፡፡ ይብስ ብሎ ደግሞ እናትየዋ ታወረች፡፡ ሚስትም በደሏን አጠናከረች፡፡ በተለይም ሴትዮዋን በጣም የምትበድለው ለእናትዮዋ በምታቀርበው ምግብ ነው፡፡
 ለምሳሌ ለእራት ገንፎ ስታቀርብላት ባሏም ሆነ ሌላ ሰው ዐይኑን እንዳይጥልበት በገንፎው ላይ ቅቤ ትጨምርበታለች፡፡ ነገር ግን ቅቤው ወደ መሬት እንዲፈስ ገንፎው የሚቀርብበትን ገበቴ በአንድ በኩል በስታዋለች፡፡ ልጁ እናቱ ገንፎ በቅቤ የበላች ስለሚመስለው ሚስቱን አይናገራትም፡፡ ሆኖም ገንፎው ቀስ እያለ ወደ መሬት ስለሚፈስ እናትዮዋ አታገኘውም (እናትዮዋ ዐይነስውር መሆኗን አስታውሱ)፡፡
ዘመን አለፈ፡፡ የልጁ እናትም አረፈች፡፡ ልጅየውም ካገባት ሚስቱ አንድ ልጅ ወልዶ ሞተ፡፡ የትናንትናዋ ሚስት የአዲሱ ልጅ እናት ሆነችና ከልጇ ጋር መኖር ጀመረች፡፡ ልጇ ለአቅመ አዳም ሲደርስ እርሷም በተራዋ ከአንዲት ወጣት ጋር በጋብቻ እንዲጣመር አደረገችው፡፡ ሶስቱ ሰዎች በአንድ ላይ መኖር ጀመሩ፡፡ እናት ስታረጅ እንደ ትልቋ እናት (የሞተችው የቧላ እናት) ታወረች፡፡ አንድ ቀን ምግብ ሲቀርብላት ገንፎው ቅቤ የሌለው ሆነባት፡፡ ወዲያውኑ የሆነ ነገር ትዝ አላትና ገበቴውን መዳበስ ጀመረች፡፡ በርግጥም እንደጠረጠረችው ገበቴው በአንድ በኩል የተበሳ ሆኖ አገኘችው፡፡ እናም ድሮ ስትፈጽመው የነበረውን በደል በማስታወስ ከልቧ አዘነች፡፡ እንዲህም አለች፡፡
“አይ ገበቴ! አይ ገበቴዋ! ከምኔው ዞረሽ ወደኔ መጣሽ?!! ግድ የለም፡፡ የእጄን ነው ያገኘሁት፡፡ ያኔ የባሌን እናት ባልበድል ኖሮ ዛሬ ምግቤ እኔ በቀደድኩት ገበቴ ባልተሰጠኝ ነበር”
የሴትዮዋ ንግግር ከልጁ ሚስት ጆሮ ጥልቅ አለ፡፡ እናም ሚስት በሰማችው ነገር ሽምቅቅ አለች፡፡ “ለካስ የኔም የወደፊት እጣ በዚህች ገበቴ መብላት ነው?” እያለች አሰላሰለች፡፡ ወዲያውኑ የባሏን እናት ይቅርታ ጠይቃ ያቺን የተንኮል ገበቴ እንክትክት አድርጋ ሰባበረቻት፡፡ እናትም ምግባቸው በጤነኛ ገበቴ ይቀርብላቸው ጀመር፡፡
===ሁለቱ አባቶችና ሁለቱ ልጆች===
ልጅና አባት አብረው ይኖሩ ነበር፡፡ አባት ልጁ ትዳር እንዲይዝ ካደረገው በኋላ ሁሉንም ነገር አስረከበው፡፡ ለራሱም ጡረተኛ ሆኖ ከልጁ ቤት ጀርባ ከነበረች አንዲት አነስተኛ ጎጆ መኖር ጀመረ፡፡ ይሁንና አባትዬው በጸባዩ ነጭናጫ ነው፡፡ በተለይ ልጅ ለስራ ወደሌላ ቦታ በሚሄድበት ጊዜ የልጁን ሚስት በሆነ ባልሆነው ይነዘንዛታል፡፡ ሚስትም በንጭንጩ ተማረረችና ባሏ ሲመጣ “ወይ አባትህን ከዚህ ቤት አርቅልኝ፤ ወይ ደግሞ ፍታኝ” አለችው፡፡
ልጁ ወደ አባቱ ሄደና “አባቴ! እዚህ ቤት ስትኖር አፍህን ዝጋልኝ!! ካልሆነ ግን ወደ ገደል እወረውርሃለው” በማለት አስጠነቀቀው፡፡ አባትም “አረ አትወርውረኝ! ከእንግዲህ አፌን እይዛለሁ” በማለት ተማፀነው፡፡ በመሆኑም አባት ከነርሱ ጋር መኖሩን ቀጠለ፡፡ ነገር ግን አባት ቃሉን ሊያከብር አልቻለም፡፡ ልጁ ከቤት እስኪወጣ ጠብቆ ሚስትዬውን ይጨቀጭቃት ገባ፡፡ በዚህ የተናደደችው ሚስት ወደ ባሏ ሄዳ “ነገ አባትህን ከዚህ ቤት ካላስወጣህልኝ እሄድልሃለሁ” አለችው፡፡ ባልም “ግድ የለም! ነገ ገደል ውስጥ እጥለዋለሁ” አላት፡፡
በንጋቱ ልጅየው ሽማግሌ አባቱን ወደ ገደል ሊወረውረው ተነሳ፡፡ ከገደሉ ጫፍ ላይ ካደረሰው በኋላም “አባቴ! ብትፈልግ ገደል ግባ! ብትፈልግ የፈለግከውን ሁን፡፡ አባቴ ስለሆንክ ግን በራሴ እጅ አልወረውርህም፡፡ ትዳሬንም እወዳለሁና ከቤቴ እንድትመለስ አልፈቅድልህም” አለው፡፡ አባትየውንም እዚያው ትቶት ሄደ፡፡
ዘመን አለፈ፡፡ የድሮው ልጅ በተራው አባት ሆነ፡፡ ልጁም አገባ፡፡ አባትም ከልጁ ጋር መኖር ጀመረ፡፡ ታዲያ እርጅና ሲመጣ ይህኛውም  አባት ልክ እንደ ድሮው አባት ጨቅጫቃ ሆነ፡፡ የልጁን ሚስት በረባ ባልረባው ይጨቀጭቃት ጀመር፡፡ ልጁም ጭቅጭቁ ሲሰለቸው አባትዬውን ወደ ገደል ሊወረውረው ተሸክሞት ተነሳ፡፡ ረጅም ርቀት ከተጓዙ በኋላ የታዘለው አባት ልጁን እንዲህ አለው፡፡
  “እዚሁ ጋ ብትተወኝ ይሻለኛል፤ እኔም ያኔ አባቴን ከዚህ አላሳለፍኩትም”፡፡
*****
  አያድርስ ነው ወገን! “ሁሉም የዘራውን ነው የሚያጭደው” የሚለው ምሳሌ አሁን ላይ የማይሰራ ቢመስልም ጊዜው ሲደርስ እውነት መሆኑ አይቀርም፡፡ አላህ ከእንዲህ ዓይነት ክፋት ይጠብቀን፡፡
በነገራችን ላይ የመጀመሪያውን ተረት የነገሩን ጎረቤቴ የነበሩት “ሀቦ ኑሪያ” ናቸው፡፡ ሁለተኛውን ተረት የአባቴ የቅርብ የስጋ ዘመድ ከሆኑት ሼኽ ሙሐመድ ሑሴን ቲርሞ የሰማሁት ነው (በኋላ ላይ ስብሐት ገብረእግዚአብሄር ጽፎት ባነበውም ተረቱን በቅድሚያ የሰማሁት ከሼኽ ሑሴን አንደበት ነው)፡፡
——
አፈንዲ ሙተቂ
ግንቦት 26/2006
አዳማ!!
—–
Afendi Muteki is a researcher and author of the ethnography and history with special focus on the peoples of East Ethiopia. You may follow him on his blog and his facebook page by clicking the following links

ከመከላከያ ሰራዊት እንዲባረሩ የታሰቡ ከፍተኛ ባለማእረግ መኮንኖች ለስርአቱ ደህንነት ሲባል በቦታቸው እንዲቆዩ መደረጉ ታወቀ::

ክምርጫ መረጋጋት በኋላ በርካታ መኮንኖች ሊባረሩ ይችላሉ::
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

በከፍተኛ የመከላከያ ሰራዊት አመራር ውስጥ በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰራ የነበረው ሌተናል ጄነራል አበባው ታደሰ ባለፈው አመት ከቦታው መባረሩ ተከትሎ መባረር አለባቸው ተብለው ውስጥ ለውስጥ የተጨረሰላቸው በርካታ ከፍተኛ ባለማእረግ መኮንኖች ቢኖሩም፤ ከኋላ ሊነሳ የሚችለውን ችግር ግምት ውስጥ በማስገባት በተደረገው ግምገማ ላይ በማስጠንቀቅያ ብቻ እንዲታለፉ መደረጉን ታውቋል::

መባረር አለባቸው ተብለው ከተቀመጡት ከፍተኛ መኮነኖች አብዛኛዎቹ የሌተናል ኮረኔል ማእረግ ያላቸው እንደሆኑ የገለፀው መረጃው የጄኔራል አበባው ተከታዮች ስለሆኑና እንቅፋት ስለሚፈጥሩብን ተብለው እንዲባረሩ የተወሰነባቸው ቢሆንም፤ በመጪው ምርጫ ታሳቢ በማድረግ በህዝቡ መሃል ገብተው ኢህአዴግን ለመጣል ሊያነሳሱ ስለሚችሉ ግምገማ በማድረግ በማሰጠንቀቂያ እንዲታለፉ መደረጋቸውን መረጃዎች አምልክተዋል::መረጃዉም አያይዞ እንደጠቀሰው ክምርጫ መረጋጋት በኋላ በርካታ መኮንኖች ሊባረሩ ይችላሉ::

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 13፣ 2007 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የስልጠና ልምምድ እያደረገ የነበረ አንድ የኢፌዴሪ አየር ኃይል ተዋጊ ሄሊኮፍተር ከሃዲው አብራሪ ቴክኒሻኑንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን የኢፌድሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ  ሄሊኮፍተሩ ባፈው አርብ ከጧቱ 2 ሰዓት ከ35 ጀምሮ በመደበኛ የስልጠና ልምምድ ላይ ነበር፡፡ …

ታኀሳስ ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአየር ሃይል ምንጮች እንደገለጹት ሰሞኑን ኤም አይ 35 የተባለ የውጊያ ሄሊኮፕተር ይዘው በመጥፋት ወደ አልታወቀ ስፍራ የተጓዙት ሁለቱን አብራሪዎችና አንድ ቴክኒሻንን ለመፈለግ አየር ሃይል በተለያዩ አካበባዎች  አሰሳ ሲያደርግ ቢቆይም በመጨረሻ ፍለጋው እንዲቋረጥ ተደርጓል። ፍለጋው እንዲቋረጥ የተደረገበት ዋና ምክንያት አብራሪዎቹ ሆን ብለው መጥፋታቸውና ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው …

ታኀሳስ ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጠኝ የፖለቲካ ድርጅቶችን ያቀፈው ትብብር ባወጣው መግለጫ የባህርዳር ከተማዋ ነዋሪዎች ባዶ እጃቸውን ሆነው በሰላማዊ መንገድ ባሰሙት የተቃውሞ ድምጽ መንግስት የህዝቡን ጥያቄ ለማፈን በወሰደው ዘግናኝና አሰቃቂ በጥይት የታገዘ የኃይል እርምጃ እስካሁን የአምስት ንፁኃን ዜጎች ህይወት መቅጠፉን አስታወሶ፣  ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑ አዛውንት እማሆይንና አካል ጉዳተኛ ጨምሮ በርካቶችን በማቁሰል የአካል …

ታኀሳስ ፲፫(አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ፓርላማ አሸባሪ ብሎ ከፈረጃቸው ድርጅቶች ጋር በቀጥታ እየተገናኙ የሀገራችንን ጥቅምና ሰላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች አሉ ሲሉ ጠ/ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ተናገሩ፡፡ ጠ/ሚኒስትሩ ዛሬ በጽ/ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የፓለቲካ ፓርቲ አባላት እየታሰሩ መሆናቸውን አስመልክቶ በቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አሸባሪ ከሚባሉ ቡድኖች በቀጥታ እየተገናኙና እያቀዱ ሀገር …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በባህር ዳር ከተማ ዓርብ ታኅሣሥ 10 ቀን 2007 ዓም ድንገት በተቀሰቀሰ ግጭት ከሦስት እስከ አምስት ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ተሰማ። በርካቶችም መቁሰላቸው ተጠቅሷል። ሆኖም የደረሰዉን የጉዳት መጠን በትክክል የሚያረጋግጥልን የመንግስት አካል አላገኘንም።

ለዋሽንግተን ሐቫና ግንኙነት አሮጌዉ ዓመት አዲስ ተስፋ ፈንጥቋል። ከአፍሪቃ በስተቀር የሌላዉን ዓለም አበይት ክንዉኖች በሁለት ክፍሎች ቃኝተን፤ የማላላን ገደኛ፤ የማሌዥያን ፈሪሰኛ ግን ጉደኛ ዓመት እንሸኘዉ፤

ገዢው ፓርቲ ሕወሃት/ኢሕአዴግ የእምነት ነጻነትን በመጋፋት ፣ ታቦት ቢወጣበትና የጥቅምት በዓል በሚከበርበት በባህር ዳር የመስቀል አደባባይ “ልማት” በሚል ስም ለባለሃብቶች ቦታዎች ሊሰጥ ማሰቡን ተከትሎ ሕዝቡ ለአስተዳደሩ ብሶቱን በደብዳቤ ለማስገባት፣ በቦታው ሄዱ ለማነጋገር ቢሞክር፣ ለሕዝብ ጥያቄ ደንታ የሌላቸው የሕወሃት/ኢሕአዴግ ባለስልጣናት፣ ቦታውን ለባላሃብቶች ለመስጠት በመወሰናቸው፣ ሕዝቡ የእምነት ነጻነቱን ለማስከበር ባለስልጣናት ዉሳኔያቸዉን እንዲቀለብሱ ለማድረግ፣ በራሱ አነሳሽነት ፣ በሺሆች […]

Image

በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የሚደርሰዉን በድልና ጭቆናን በመቃወምና የኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳዮችአስመልክቶ በዋሽግተን ዲሲ የሚገኘዉ ፈርስት ሒጅራህ ፋዉዴሽን የ አቋም መግለጫ አወጣ
ባለስድስት ነጥብ የሆነዉ የ አቋም መግለጫ የ ኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳዮች ያጠቃለለ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግስት በዜጎቹ ላይ የሚያደርሰዉን በደልና ጭቆና ለመታደግ ፈርስት ሒጅራህ ፋዉዴሽን አገራዊ ሐላፊነቱን ለመወጣት የሚጠበቅበትን ሁሉ እደሚያደርግ የ አመራር አካላቱ ለ ቢቢኤን ገልጸዋል። የአቋም መግለጫዉም እንደሚከተለዉ ይነበባል፦

• ሆን ተብሎ ሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ መንግስት ሲፈፅም የቆየዉን ኢሰብአዊ ድርጊት ባዲስና በከፋ መልኩ የጀመረዉን እርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን

• ሙስሊም እህቶቻችንን የእምነት ነፃነት በመንፈግ ባአዲስ አበባ ዩኒፈርሲቲና በሌሎች የትምህርት እንዲሁም በመንግስት መስሪያ ቤቶች ሂጃባቸዉን እንዲያወልቁ የማስገደዱ ጉዳይ ሙስሊም ሴቶችን ከእምነታቸዉና ከትምህር እንዲሁም ከእምነታቸዉና ሰርተዉ ከመኖር ምረጡ እየተባሉ የሚደረግባቸዉን ተፅእኖን አጥብቀን እናወግዛለን

• በግፍ ታስረዉ ባሉት የሙስሊም መሪዎች ቤተሰቦች ሂጃባችሁን ካላወለቃችሁ ገብታችሁ ወዳጆቻችሁንን መጠየቅም ሆነ ምግብ ማቅረብ አትችሉም ተብለዉ የሚደርስባቸዉን መጉላላት በጥብቅ የምናወግዝ መሆናችንንም እንገልፃለን

• እንዲሁም ጠቅላይ ሚኒስቴር ሃይለማርያም ደሳለኝ ካንድ ጠቅላይ ሚንስቴር በማይጠበቅ አፀያፊ አነጋገር ጨዋዉንና ታታሪ ሰራተኛዉን የስልጤን ብሄረ ሰብ መዝለፋቸዉን አጥብቀን እንቃወማለን

• በቪዎች የሚቆጠሩትን ካገርና ከወገን ተለይተዉ ቤተሰቦቻቸዉንና ዘመዶቻቸዉን ለመርዳት የሚደርስባቸዉን ያካልና የመንፈስ ተፅእኖን በመቇቇም ለሚያደርጉት መስዋእትነት መመስገንናና መደነቅ ሲገባቸዉ ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ባልተገራ አንደበታቸዉ እህቶቻችንን ገረዶች ብለዉ አንቇሸዉ መጥራታቸዉ እጅጉን አስከፍቶናል። የኢትዯዽያ ህዝብንም ይቅርታ ይጠይቁ ዘንድ እናሳስባለን።

• በተጨማሪም በቅርቡ ሰማያዊ ፓርቲ በጠራዉ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ሰልፈኞች ላይና እንዲሁም ባህር ዳር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ የወጣዉ ክርስቲያን ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመዉን ኢሰብአዊ መንግስታዊ እርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን

“ፈርስት ሂጅራ ፋዉንዴሽን የኢትዯዽያ መንግስት ከቀን ወደቀን የህዝቡን ሰብአዊ መብት እየጨፈለቀ መቀጠሉን አጥብቀን እንደሚያወግዝና ሌላዉም የሰዉ መብት ያገባኛል የሚል ስብእና ያለዉ ሰዉ ያወግዝ ዘንድ ጥሪዉን ያቀርባል” በሚል የጥሪ መልክት የ አቋም መግለጫዉ ተቋጭቷል። የፈርስት ሒጅራህ የአመራር አካላት መጠነ ሰፊ የሆነዉን ጭቆናና በደል ለመታደግ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ እንደሚሰሩ በመግለጽ በቀጣይነትም የሚያከናዉኗቸዉ የተቃዉሞ መርሃ ግብሮች እንደሚኖሩ ለቢቢኤን ገልጸዋል።

የአሸባሪ ሚስት ድሮም አሸባሪ ናት ሂጃብ አውልቂ ከተባለች ለምን አታወልቅም አይደለም ሂጃብ ይቅርና ካስፈለገን ቀሚሳቸውን አሶልቀን እናያቸዋለን (አቶ አምባዬ የማረሚያ ቤቱ ሃላፊ) አቡ ዳውድ ኡስማን በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙት ኮሚቴዎቻችን እና ኡስታዞቻችን የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በዚህ ሳምንት የጀመረውን ሙስሊም ሴቶችን ሂጃባችሁን አውልቃችሁ ሳንፈትሻቹ አትገቡም የሚለውን ክልከላ አስመልክቶ ለማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ሃላፊ ላቀረቡት አቤቱታ በማረሚያ […]

አምርረህ ልትታገልበት የሚገባ በቂ ምክንያት ካለ አላማው አንድና አንድ “ማሸነፍ” የሆነ ትግል እንጂ የትግል አይነት የሚባል ነገር የለም። አዎ ያለው ትግል ነው። ቢቸግር ነው እንጂ ችግሩ “አይነት” የሚለው ቃል ችግር ሆኖ አይደለም። ትግሉ ላይ ሲሆን አጠቃቀማችንና አረዳዳችን ግን በጣሙኑ ግራ ያጋባል። “ምግብ” ለሚለው ያጋራ መገለጫ ስር ጨጨብሳ፤ ሙዝ ፤ ወተት የመሳሰሉ ምግቦች እንዳሉ ለማሳያት ሳይሆን […]

በህይወት እያሉ ተረት ለመሆን የበቁትና በጎጃም ክፍለ ሀገር የደብረ ወርቅ ወረዳ አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ “ቆምጫ አምባው” በዚህ ፎቶግራፍ የምትመለከቷቸው ሰውዬ ናቸው፡፡ አቶ ቆምጬ በአሁኑ ወቅት በትውልድ ከተማቸው በጥብቅና ሙያ ላይ ተሰማርተዋል፡፡ (ፎቶ፡ ዘ-ኢትዮጵያ ጋዜጣ)

Image