ትክክለኛውን የቀጠሮ ቀን ለማወቅ አልተቻለም (ኮማንደር ተክላይ ጥቅምት 22 ነው ሲሉ፤ ፖሊስ ጥቅምት 20 ነው ብሏል) ዘሬ መስከረም 22/2007 ዓ.ም በአራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ኃብታሙ አያሌው፣ የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ም/ሰብሳቢ አቶ የሸዋስ አሰፋ፣ የአረና ም/ የህዝብ ግንኙነት አቶ አብርሃ ደስታ እንዲሁም የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሽ […]

በፋሽሽቱ ወያኔ ከጋምቤላ ክልል በግፍ የተፈናቀሉ እና ከዘር ማጥፋት ወንጀል የተረፉት አማሮች ወደ መኢአድ ጽ/ቤት መጥተዋል፡፡ በጋምቤላ ክልል ሜጢ ከተማ ጎሽኔ ቀበሌ አቶ በለጠ ጌታቸው ጎጃም ቢቸና አካባቢ የመጡ የግራ እጃቸውን በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ በዚሁ ቀበሌ ከወሎ መካነሰላም ቦረና አካባቢ የመጡ አቶ ገበየሁ ኮስትር በጀርባቸው በኩል በከፍተኛ ሁኔታ በጥይት ከተመቱ በኋላ ጥይቱ በሰውነታቸው ውስጥ […]

መስከረም 25 ቀን በአዲስ አበባ ከተማ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የአንድነት ፓርቲ አዲስ አበባ ምክር ቤት ወጣቶች፣ ለአዲስ አበባ አስተዳደር የእውቅና ደብዳቤ ማስገባታቸው ይታወቃል። አስተዳደሩ ደብዳቤው በደረሰው በ48 ሰዓት መልስ ሳይሰጥ ዛሬ መስከረም 22 ቀን፣ በቂ ቅስቀሳ ሳይደረግ፣ «ነገ መጥታችሁ፣ የእውቅና ደብዳቤ አስገቡና ሰልፍ ማድረግ ትችላላችሁ» የሚል መልስ እንደሰጠ ለማረጋገጥ ችለናል። የአዲስ አበባ አንድነት ምክር ቤት […]

«ኦይሮፋይተር» የተባለው ዘመናዊ የጦር አይሮፕላን ሰውም ሆነ ዕቃ የሚጫንበት ዋናው አካል እንከን አለበት በማለት ጀርመን ለጊዜው ተጨማሪ ዩውሮፋይተር ከእንግዲህ ላለመግዛት ትናንት ካሳወቀች ወዲህ፤ አይሮፕላኑን በጋራ የሚሠሩት ኩባንያዎች፣ ላጋጠመው

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የቱርክ ፓርላማ ፤ የአገሪቱ ጦር ሠራዊት ከድንበር ማዶ ወደ ኢራቅና ሶሪያ በመግባት የ IS ታጣቂዎችን እንዲወጋ በተካሄደ የድምፅ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት መደገፉ ተነገረ። ከ3/4ኛ በላይ የሕዝብ እንደራሴዎች ያጸደቁት ውሳኔ በተጨማሪ የውጭ ሃገራት

በጀርመን እና በኢትዮጵያ መካከል፤ ያለዉ የትምርት የምርምር እና የባህል ልዉዉጥ ግንኙነት እጅግ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። በተለይ ከጎርጎረሳዉያኑ 1624 እስከ 1704 ከኖረዉ ጀርመናዊ ምሁር ሂዮብ ሩዶልፍ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያሉ ምሁራን በኢትዮጵያ ልዩ ልዩ ጥንታዊ ቅርሶች፤

ይህ በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ የተጀመረው 8028 አዲስ ነጻ የስልክ መስመር ነው። ለኢትዮጵያ አርሶ አደሮች እገዛና ምክር የሚያገኙበት ነጻ የስልክ መስመር ግልጋሎት ከተጀመረ ጥቂት ወራት ተቆጠሩ።

በኢትዮጵያ ዘላቂ የመሬት አያያዝን ለማጠናከር በሚል የዓለም ባንክ እና ተባባሪ ደጋፊ ድርጅቶች ለቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ከ100 ሚልዮን ዶላር በላይ ብድር ለመስጠት ፈቀዱ። ገንዘቡ የአፈር መመናመንን እና የደኖች መራቆትን

የቀድሞ የኖርዌይ ጠቅላይ ሚንስትር የንስ ስቶልትንበርግ አዲሱ የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ኪዳን ፣ ኔቶ ዋና ጸሐፊ በመሆን ትናንት በብራስልስ ስልጣናቸውን በይፋ ጀምረዋል። የ55 ዓመቱ ስቶልትንበርግ እአአ ከ2009 ዓም

ነገ መስከረም 22 ቀን በ”ሽብርተኛ” ክስ የተከሰሱት አራቱ ወጣት ፖለቲከኞች፣ ሃብታሙ አያለዉና ዳንኤል ሺበሺ ከአንድነት፣ የሺዋስ አሰፋ ከሰማያዊ እና አብርሃ ደስታ ከአረና ፣ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ። ወጣቶቹ ምንም አይነት ክስ እሰከአሁን ያልተመሰረተባቸው ሲሆን፣ ከሐምሌ አንድ ቀን ጀመሮ በማእከላዊ እሥር ቤት ነው የሚገኙት። እስረኞቹ ለምን እንደታሰሩ አያውቁም። ክስ ሳይመሰረትባቸው ነው ለ86 ቀናት የታሰሩት። ፖሊስ መረጃ ገና […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ወደ ጀርመን እና አውሮጳ ለሚመጡ ስደተኞች መብት የሚሟገተው «ፕሮ አዙል» የተባለው መንግስታዊ ያልሆነው የጀርመናውያን ድርጅት በሜዲትሬንያን ባህር በኩል አድርገው ወደ ኢጣሊያ ለመግባት ሲሞክሩ ባህር ውስጥ ሰምጠው የሚሞቱትን ስደተኞች አስመልክቶ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ አወጣ።

ኣንድ ዘመን ሁለቱም የአንድ ፓርቲ አባላትና ጓዶች ነበሩ፣ ፕሬዚዳንት ዲልማ ሩሴፍና ማሪና ሲልቫ! ከ 4 ቀናት በኋላ በሚካሄደው አቀፍ- አቀፍ ምርጫ ፣ የሆነው ሆኖ የመሪነቱን እርፍ ለመጨበጥ ሁለቱ ወይዛዝርት ብርቱ ፉክክር በማድረግ ላይ ናቸው።

የባሕርዳሩ ድርድር ጥሩ ተስፋ እየታየበት ነዉ።እዚያዉ ደቡብ ሱዳን ዉስጥም ግጭቱ እየቀዘቀዘ ነዉ።ይሁንና የድርድሩ ሒደትም ሆነ የግጭቱ መቀዛቀዝ፤ አምባሳደሩ እንደሚሉት ለዘላቂ ሠላም ዋስተና ከሚሆኑበት ደርጃ አልደረሱም።

በሜልበርን እምብርት እየተሽረከርን በያራ ወንዝ ዳርቻ ስንዋብ ወደ ሌላ አቅጣጫ የመሻገሪያ የእግረኞች ድልድይ ላይ ደረስን፡፡ የያራ ወንዝ ዓባይን በሰኔ መስሏል፡፡ እዚህ ወንዝ ዳር ነው የዛሬ 179 ዓም እኤአ 1835 የሜልበርን ከተማ የተቆረቆረችው፡፡ ከ242 ኪሎ ሜትር በላይ ይጓዛል ያራ ወንዝ፡፡ የመሻገሪያው ድልድይ ወንዙ መካከል በአንዲት አነስተኛ ጀልባ በምትመስል ኮንክሪት መሬት ላይ ቆሟል፡፡ ሀገሬዎቹ ደሴት ብርቃቸው ነው መሰለኝ ‹ፖኒ ፊሽ ደሴት› ይሏታል፡፡ መቼም ፈረንጅ ትንሽን ነገር ታላቅ በማድረግ የሚተካከለው የለም፡፡

ይህንን ድልድይ እያቋረጥን ስንሄድ በግራና ቀኝ በድልድዩ መደገፊያ ላይ የታሠሩና የተቆለፉ ቁልፎችን አየሁ፡፡ ሙሉ የድልድዩን ብረት ከጫፍ እስከ ጫፍ ይዘውታል፡፡ አንዳንዶቹ በሀገራችን ለስታድዮም በር ብቻ ሊውሉ የሚችሉ ቁልፎች ናቸው፡፡ እነዚህ በፍቅራቸው ላይ ሥጋት ሳይኖርባቸው አይቀርም፡፡ አንዳንዶቹ ቁልፎችም ከቻይኖች ዓይን እንኳን ያነሱ ናቸው፡፡ ይህንን ዓይነት ነገር የገጠመኝ ፓሪስ ነበረ፡፡ በፓሪስ የሚገኙ ድልድዮች በዚያ ስማቸውን ጽፈውና ቁልፋቸውን ቆልፈው በሚያንጠለጥሉ ፍቅረኞች ምክንያት ለአደጋ መጋለጣቸውን የከተማው ማዘጋጃ ቤት ቢጮህ እንኳን ሰሚ አላገኘም፡፡ በተለይ ፖንቴ ደስ አርትስ በዚህ የተቸገረ ድልድ ነው፡፡እዚህ ሜልበርንም ተመሳሳይ ሥጋት ከመዘጋጃ ቤቱ እየተሰማ ፍቅረኞች ግን ከድልድዩ ይልቅ ፍቅራቸው ያሳስባቸዋል፡፡ ድልድዩ ቢሰበር እኛ ደኅና እንሁን እንጂ መልሰን እንሠራዋለን፡፡ የኛ ፍቅር ከተሰበረ ማን ይጠግነዋል? ይላሉ፡፡

ይኼ ደግሞ ባልተጠገነ ፍቅር ምክንያት በልብ ሕመም የሞተችውን ሰርቢያዊቷን ናዳን ያስታውሳቸዋል፡፡ ናዳ በአንድ ትምህርት ቤት የምታስተምር ሴት ነበረች፡፡ ከሕይወት በአንዱ ቀን ሬልጃ ከተባለ የሰርቢያ የጦር መኮንን ጋር በፍቅር ወደቀች፡፡ ዘመኑ የአንደኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ ነበርና ሬልጃ ለጦርነት ወደ ግሪክ ሄደ፡፡ በሄደበት ግሪክ ‹‹እኔስ በአገሬ እንኳን ሰው ወፍ አለምዳለሁ›› የምትል ቆንጆ አገኘና ከእርሷም ጋር በፍቅር ወደቀ፡፡ በዚህም ምክንያት ናዳና ሬልጃ ተለያዩ፡፡ ናዳ በዚህ የተነሣ ኀዘንተኛና በሽተኛ ሆነች፡፡ ኀዘኑ ባስከተለባት የልብ ችግርም ምክንያት ገና በወጣትነቷ ሞተች፡፡

ይህ የናዳ ታሪክ የሰርቢያን ወጣቶች አስደነገጣቸው፡፡ የመጀመሪያውና የሁለተኛው የዓለም ጦርነት አያሌ ወዳጆቻቸውን ያሳጣቸው የአውሮፓ ወጣት ፍቅረኞችንም ልብ ነካ፡፡ በዚህም የተነሣ የሚፋቀሩ ወጣቶች ላለመለያየት ብለው፣ የናዳም ዕጣ ፈንታ እንዳይደርስባቸው ፈርተው ቁልፍ እየቆለፉ ናዳና ራጃ አዘውትረው ይገናኙበት ነበር በተባለው ድልድይ ላይ ማንጠልጠል ጀመሩ፡፡ ከሺ ዘመናት በፊት በአውሮፓ የነበረው ይህ ባሕል በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ምክንያት እንደገና አገረሸና አያሌ ድልድዮችን አጥለቀለቀ፡፡

የፓሪሱ የፍቅር ድልድይ

ከቀድሞ ጀምሮ የሰውን ልጅ ሲያስጨንቁት ከኖሩት ሰብአዊ ጸጋዎች አንዱ ፍቅር ነው፡፡ ሰው የተፈጠረው አፍቃሪ ፍጡር ሆኖ ነው፡፡ እንስሳት ይኼ የላቸውም፡፡ እንስሳት ለአንድ ነገር የሚኖር አዝማሚያ (affection) ነው ያላቸው፡፡ ፍቅር የአምላክ ጸጋ ነውና ይህ ሊኖራቸው የሚችለው ሰውና መላእክት ናቸው፡፡ ሰው ሥጋዊ ፍጡር ስለሆነ ነው ስሜትም የሚኖረው፡፡ ስሜት በመላእክት ዘንድ የለም፡፡ ፍቅር ግን አለ፡፡ ማሰብ ከሌለ ስሜት እንጂ ፍቅር አይኖርም፡፡ ፍቅር አንድን ነገር መፈለግ፣ ወደ አንድ ነገር መሳብና ከአንድ ነገር ጋር መቆራኘት ብቻ ሳይሆን አብሮ የሞራልና የእምነት ሕግጋትም አሉት፡፡ ለዚህ ደግሞ ማሰብን ይፈልጋል፡፡ ፍቅር በውስጡ ጽጌረዳ ብቻ ሳይሆን እሾህ፣ የዓሣ ሥጋ ብቻ ሳይሆን የዓሣ እሾህ፣ ማር ብቻ ሳይሆን የንብ ንድፊያ፣ አለው፡፡ አንዳንዴ ለመዳን መርፌን እንደምንወጋው፤ መርፌውም እንደሚያም፣ ነገር ግን መድኃኒቱ እንደሚያድነን፤ ለመድኃኒቱም ብለን የሚያመውን መርፌ እንደምንታገሠው፤ ፍቅርም እንዲህ ይሆናል፡፡ መድኃኒት የያዘ መርፌ ይሆናል፡፡ ይህንን ሁሉ ለማመዛዘንና ለመቀበል ደግሞ አሳቢ ፍጡር መሆን ግድ ነው፡፡ ስሜት የሚያውረውን ፍቅር ነው የሚያበራለት፡፡ ፍቅር ዓይናማ ነውና፡፡ ያውም የልቡና ዓይን፡፡
ሳውዝ ባንክ የእግረኞች ማቋረጫ
ሰው ፍቅርንና ስሜትን መለየት እያቃተው፣ አንዳንድ ጊዜም ከፍቅር ይልቅ ስሜቱን እያስበለጠ ነው ራሱን መከራ ውስጥ የሚጥለው፡፡ ስሜት ለፍቅር አንዱ ግብዐት እንጂ ብቸኛው ነገር አይደለም፡፡ በፍቅር ውስጥ ከስሜት ሌላ ማሰብ፣ መታገሥ፣ ራስን መግዛት፣ መሸከም፣ ቆራጥ፣ ኃላፊነትን መውሰድ፣ ይቅር ማለትና ሌሎችም አሉበት፡፡ ስሜት ግን የፍቅር ማስጀመሪያ እና ፍቅር ማለስለሻ ነው፡፡ ለአንድ መኪና ባትሪው የሞተሩ ማስነሻ እንደሆነው ሁሉ፤ በባትሪ ብቻ ግን መሄድ እንደማይቻል፤ ያለ ባትሪም መሄድ እንደማይቻል ማለት ነው፡፡ ስሜት እንደ መኪና ቅባቶችና ዘይቶች ያለ ነው፡፡ ቅባትና ዘይት ያነሰው መኪና ችሎ ችሎ አንድ ቀን ወይ ይነጫነጫል፣ ወይ ይቆማል፣ ወይ እሳት ያስነሣል፣ ወይ ሞተር ይነክሳል፡፡ ስሜት ጠፍቶባቸው ሞተር የነከሱ ብዙዎች ናቸው፡፡
ቅባትና ዘይት ግን ለሞተሩና ለሌሎች ዕቃዎች ሕልውና ሲባል የሚደረግ እንጂ በራሱ ሕልውናውን ለብቻ የሚያስቀጥል አይደለም፡፡ ለዘይቱ አይደለም ሞተሩ፤ ለሞተሩ ነው እንጂ ዘይቱ፡፡ እንደዚሁም ነው፡፡ በፍቅር ውስጥ ለሚገኙት ወሳኝ ነገሮች ነው ስሜት የሚያስፈልጋቸው፡፡ እንጂ ለስሜቱ አይደለም እነርሱ የሚያስፈልጉት፡፡ ስሜት ብቻ የያዙ ‹‹ፍቅረኞች›› ናቸው እንደ ሬልጃ እዚህም እዚያም መሄድ፣ ያዩዋትንም ሁሉ መመኘትና እንደ ተረት ገጸ ባሕርይ ‹‹ሲሄዱ፣ ሲሄዱ፣ ሲሄዱ›› የሚኖሩት፡፡

ይኼ እንግዲህ የሰው ዘር ሁሉ ጭንቀት ነውና እስኪ በቁልፍ አሥረን እንሞክረው ብለው ነው ስማቸውን ጽፈው፣ ቁልፍ ላይ ለጥፈው፣ ቁልፉንም ቆልፈው ድልድይ ላይ የሚያስቀምጡት፡፡እንዲህ ዘወትር ሳንለያይ ያኑረን ብለው፡፡ በተለይ በዚህ እና ባለንበት ዘመን ሰው የሰውን ጸባይ ቀርቶ የራሱን ጠባይ መቻል እያቃተው፣ ሰው አንዳች መሥዋዕትነትን ለመክፈል እየሰሰተ ባለበት ጊዜ መሸከምንና መሥዋዕትነትን የሚፈልገው ፍቅር በስሜትና በጊዜያዊ ፍላጎት (ፈቲው) እየተተካ በመሄድ ላይ ነው፡፡ ለዚህ ነው የሰው ልብ መሸከም ያቃተውን ነገር ድልድዮችን ለማሸከም መከራ የሚያየው፡፡ ድልድዮች ደግሞ ‹እናንተ ሸክማችሁ የከበደ ወደ እኔ ኑ›› አላሉም፡፡ በምን ዐቅማቸው ይሸከሙታል፡፡
ፍቅር ፍቅር አሉት ስሙን አሳንሰው

ከድንጋይ ይከብዳል ለተሸከመው ሰው

አለ የሀገሬ ገጣሚ፡፡

ሜልበርን፣ አውስትራልያ፡፡

ኢትዮጵያዉያኖች በኢትዮጵያ ኤምባሲ ባደረጉት የተቃዉሞ ሰልፍ፣ ኮከብ ያለበትን የአገዛዙ ባንዲራ አንስተው፣ የጠራዉን የኢትዮጵያ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ አላማ መትከላቸው ይታወቃል። መሳሪያ ያልታጠቁ፣ ወረቀትና ባንዲራ ብቻ በእጃችቸው የያዙ ሰላማዊ ዜጎች “ግርማ ብሩን ለማነጋገር እንፈልጋለን፣ ወንጀለኞች አይደለንም” በሚሉበት ጊዜ፣ አንዱ የኤምባሲ ጠባቂ፣ ጥይት መደቀኑና ሶስት ጊዜ መተኮሱ፣ በኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በአለም አቀፍ ሜዲያዎች ሁሉ በስፋት እየተዘገበ ነው። […]

መስከረም ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ትናንት ሰኞ በኦጋዴንና በጋምቤላ በተጨፈጨፉ ኢትዮጵያውያን ዙሪያ በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተወካዮችን ለማነጋገር በኢምባሲው አካባቢ በተገኙት  ኢትዮጵያውያን ላይ አንድ የስልጣን ደረጃው ያልታወቀ ሰለሞን ወይም በበረሃ ስሙ ወዲ ወይኒ የተባለ ግለሰብ ጥይቶችን በመተኮሱ የኢትዮጵያውያንንና አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስቧል። አለማቀፍ እውቅና ያላቸው ሮይተርስ እና  ዋሽንግተን ፖስት የመሳሰሉ የዜና አውታሮች ዜናውን …

መስከረም ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ወሎ ወግዲ ወረዳ የመሰናዶ እና የመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ መመህራን የስራ ማቆም አድማውን ያደረጉት መንግስት ቃል በገባው መሰረት የሃምሌ እና ነሃሴ ወር ደሞዝ ጭማሪ አልከፈለንም በሚል ነው። መመህራኑ የደሞዝ ጭማሪው ከተገለጸበት ጊዜ አንስቶ በታየው የዋጋ ንረት እየተሰቃየን ነው በማለት የወረዳውን አስተዳዳሪ ለማነጋገር ሙከራ ቢያደርጉም አስተዳዳሪው ለስብሰባ በሜዳቸው ሳይሳካለቸው …

መስከረም ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል ቡርጂ ወረዳ የመንግስት ስልጣን በተቆናጠጡ የወረዳ ሹሞች በተደጋጋሚ የደረሰባቸው አስተዳደራዊ በደልና የሰብኣዊ መብት ጥሰት ወንጀል እንዲጣራና በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ  አቤቱታ ያቀረቡ ነዋሪዎች ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውን ገልጸዋል። ከ1993 ዓ.ም ጀምሮ በወረዳው ዋና አስተዳዳሪ በአቶ አማሬ ቦሬና በ አቶ ጅሎ ቦነያ አማካይነት ያለአንዳች ምክንያት መታሰራቸውን፣ በእስር ወቅትም በተደጋጋሚ …

መስከረም ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ደልጊ ፣ሻውራ፣ ጎርጎራና ቋራን ለ70 ዓመታት በማገናኘት ያገለገለው ድልድይ በመንገድ ስራ በተፈጠረ የጥናት ችግር ቢፈርስም ተመልሶ ሊሰራ ባለመቻሉ ከፍተኛ ችግር ደርሶብናል በማለት የጯሂት ከተማ ነዋሪዎች አማረዋል፡፡ ከጎንደር ወደ ጯሂት በሚወስደው መንገድ ላይ በጣልያን መንግስት እንደተሰራ የሚነገረው የሱዳን ገደል ድልድይ ከአራት ወራት በፊት በመፍረሱ  ወላዶች፣አረጋውያንና የንግዱ ማህበረሰብ ከፍተኛ ችግር …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኤርትራ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ልዩ ዘጋቢ የሆኑት ሼኢላ ኬቴሩት ሰኞ ዕለት ጅርጅታቸው ይፋ ባደረገው ዘገባ እንደገለፁት በኤርትራ ባለው የሰብዓዊ መብት ረገጣ የተነሳ በርካታ የሀገሪቱ ሰዎች ከነዚህም ውስጥ በተለይ ወጣቶች ሀገሪቷን ለቀው ለስደት ተዳርገዋል።

በምዕራብ አፍሪቃ እየተስፋፋ የመጣውን አደገኛዉን የኤቦላ ወረርሽኝ ስርጭት ለመቆጣጠር በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥረቱ እንደቀጠለ ነው። ጀርመን በኤቦላ ተዋኅሲ ለተጠቁ የምዕራብ አፍሪቃ ሀገራት አስር ሚሊዮን ዩሮ ርዳታ እንደምትሰጥ አስታውቃለች።

መምህር ብርሃነመስቀል ንጉሤ ዘውዴ በአክሱም ዩኒቨርስቲ መምህር ሲሆን በአዳማ የአንድነት ፓርቲ አባል ነው የመጀመሪያ ዲግሪውን በ2001 ዓ.ም ከአዳማ ዩኒቨርስቲ በፔዳጎጂካል ሳይንስ ሁለተኛ ዲግሪውን በ2004 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሂዩማን ሪሶርስ ኤንድ ኦርጋናይዜሽናል ዴቨሎፐመንት ኢን ኢዱኬሽን አግኝቷል፡፡ አስከፊውን የኢህአዴግ ሥርዓት በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተቀላቀልኩት የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሳለሁ ነው:: በ1997 ዓ.ም በምስራቅ ሸዋ ናዝሬት የመኢአድ አባል […]

ወደ ጀርመን እና አውሮጳ ለሚመጡ ስደተኞች መብት የሚሟገተው «ፕሮ አዙል» የተባለው መንግስታዊ ያልሆነው የጀርመናውያን ድርጅት በሜዲትሬንያን ባህር በኩል አድርገው ወደ ኢጣሊያ ለመግባት ሲሞክሩ ባህር ውስጥ ሰምጠው የሚሞቱትን ስደተኞች አስመልክቶ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ አወጣ።

“ በሽብር” ተጠርጥረው በማዕከላዊ እስር ቤት የሚገኙት የፓርቲ አመራሮች ነሐሴ 27 እና ነሐሴ 29 ቀን አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው ለ3ኛ ጊዜ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀባቸው ሐብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ም/ኃላፊ የሺዋስ አሰፋ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት ም/ሰብሳቢ እና አብርሃ ደስታ የአረና ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ ሐሙስ […]

በትግራይ ክልል በተለያዩ ከተማዎችና ወረዳዎች የተደረገው ስልጠና በተሳታፊዎች ተቃዎሞ የገጠመውና ሰልጣኞችን ያስተባበረና ለአሰልጣኞቹ ፈተና የሆነ እንደነበር ከስፍራው ዜናውን ያደረሱን የዜና ምንጫችን ገልጸዋል፡፡ ገበሬዎችን እያታለላችሁ እኛን ለማታለል መጣችሁ አንድ ፓፓያ ቀርጻችሁ ልማት አለ ባገሩ በማለት 50 ጊዜ በቴሌቪዥን እያሳያችሁ፣ ዲሞክራሲ በሌለበት መልካም አስተዳደር በሌለበት ምን ልትነግሩን ምን ልትሰብኩን ነው የመጣችሁት በማለት የመድረክ መሪዎችን በጥያቄ ያስጨነቀ እንደነበር […]

በትግራይ ኣፅቢ 5 ጣልያናውያንና 2 ኢትዮዽያውያን በሕወሓት ፖሊሶች ለሰዓታት ታገቱ። የህወሓት ፖሊሶች ጋዘጠኞቹን ኣግቶ፣ ፈትሾ፣ ኣንገላትቶ ለቋቸዋል። ትናንት ሰኞ 19/ 01 / 2007 ዓ/ ም ለስራ ጉዳይ ወደ ኢትዮዽያ የመጡት በኣንድ ጣልያን የሚገኝ ቴሌቭዥን ጣብያ የሚሰሩ 4 ጣልያናውያን ጋዜጠኞችና ኣንድ ሌላ ኣገር ጎብኚ ጣልያናዊ ከሁለት ኣብሯቸው የሚሰሩ ኢትዮዽያውያን ጋራ ወደ ተለያዩ የገጠር ቀበሌዎች የጎበኙ ሲሆኑ […]

በጀርመን የኖርድራይን ቬስትፋልያ ፌዴራዊ ግዛት የሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ጠባቂዎች በስደተኞች ላይ ፈፀሙት የተባለው በደል በሀገሪቱ ብርቱ ወቀሳ እና ቁጣ አፈራርቋል። ድርጊቱን ያወገዘው የጀርመን መንግሥት ባስቸኳይ እንዲጣራ

በዋሽግተን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ትናንት በተቃዋሚ ሰልፈኞች እና በኤምባሲው የፀጥታ ሰራተኞች መካከል በተፈጠረ ግጭት ወቅት አንድ የኤምባሲዉ ሰራተኛ ተኩስ መክፈቱን ዜና ምንጭ ሮይተርስ ዘገበ።

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኤርትራ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ልዩ ዘጋቢ የሆኑት ሼኢላ ኬቴሩት ሰኞ ዕለት ጅርጅታቸው ይፋ ባደረገው ዘገባ እንደገለፁት በኤርትራ ባለው የሰብዓዊ መብት ረገጣ የተነሳ በርካታ የሀገሪቱ ሰዎች ከነዚህም ውስጥ በተለይ ወጣቶች ሀገሪቷን ለቀው ለስደት ተዳርገዋል።

በልጅግ ዓሊ

ባለፈው ዓመት ሃገራችንንም በሚመለከት አስደሳችም፣ አስከፊም፣ አስደናቂም፣ አናዳጅም ተግባሮች ተፈፅመዋል። አሮጌው ዓመት ለአዲሱ ዓመት ቦታውን ሲለቅ ፈጣሪ አምላክ አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የፍቅር፣ የመግባቢያና ችግሮቻችንን ሁሉ የምንፈታበት ዓመት ይሁን ማለታችን አልቀረም። ግን የዚህ ምኞታችን ፍፃሜ ከቅርብነቱ ሩቅነቱ በክፍፍላችን ምክንያት የጎላ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

”መሣርያውን ወደሚከራከሩት ሰዎች ደገነ እና ተኮሰ” ”He points the weapon at others who argue with him and fires” ሮይተርስ ከዋሽግተን ዲሲ ዛሬ የዘገበው። ዛሬ መስከረም 19፣2007 ዓም ዋሽግተን ዲሲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በተቃዋሚ ኢትዮጵያውያን ቁጥጥር ስር ውሎ ባለ ኮከቡ ሰንደቅ ዓላማ በነፃው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ተቀይሯል። ተቃውሞውን አስመልክቶ ኢሳት ዘግይቶ በለቀቀው ተጨማሪ ዘገባ ተቃዋሚዎቹ በኢምባሲው […]

ባለፈው ዓመት ሃገራችንንም በሚመለከት አስደሳችም፣ አስከፊም፣ አስደናቂም፣ አናዳጅም ተግባሮች ተፈፅመዋል። አሮጌው ዓመት ለአዲሱ ዓመት ቦታውን ሲለቅ ፈጣሪ አምላክ አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የፍቅር፣ የመግባቢያና ችግሮቻችንን ሁሉ የምንፈታበት ዓመት ይሁን ማለታችን አልቀረም። ግን የዚህ ምኞታችን ፍፃሜ ከቅርብነቱ ሩቅነቱ በክፍፍላችን ምክንያት የጎላ ነው። አንዳንዶቹ ቅራኔዎቻችንን መፍትሔ ለማግኘት ስናጠናቸው የችግሩን መንስዔ ለማግኘት እንኳን የተጠላለፉ በመሆናቸው በጣም የሚያስቸግሩ መሆናቸውን እንረዳለን። […]

አገር ቤት የሚታተመው ሪፖርተር ጋዜጣ ፣ በረእቡ መስከረም 7 እትሙ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከቱርክ የዜና አገልግሎት ኤጀንሲ አናዶሉ ጋር በቅርቡ ያደረጉት ቃለ ምልልስ ለአንባቢያኑ አቅርቧልል። ከቃለ መጠይቁ፣ በተለይም በምርጫውና በፖለቲካ እስረኞች ረገድ ጠቅላይ ሚኒስተሩ የመለሱትን ቀንጭቤ ለማቅረብ እወዳለሁ። “ ኢትዮጵያዊያን በዚህ ዓመት በአገር አቀፍ ምርጫ ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡ ምርጫውን የሥርዓቱ አካላት በሕግና በደንብ እንዲሠሩ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የቻይና ልዩ አስተዳደር ግዛት፥ ሆንግ ኮንግ ተማሪዎች መብታቸው እንዲከበር እና ነፃ ምርጫ እንዲካሄድ በመጠየቅ የጀመሩት የተቃውሞ ሰልፍ እጅግ በመጠናከሩ ድርጊቱ የሆንግ ኮንግን አስተዳደርን ብቻ ሳይሆን የፔኪንግ መንግሥትንም አስደንግጧል።

በአዲስ አበባ የአፍሪቃ አዳራሽ ዛሬ በአረንጓዴ ኤኮኖሚ እና በአካባቢ አየር ለውጥ ላይ ያተኮረ ጉባኤ ሲካሄድ ውሏል። የጉባዔው ተሳታፊዎች እንዳመለከቱት፣ ተፈጥሮን በሚጠብቅ እና የአካባቢ አየርን በማይበክል ሁኔታ ምርታማነትን በዘላቂነት

ባለፈው ዓመት ከዚህ አለም በሞት በተለዩት ካርል ሄንዝ በም የተቋቋመው የሰዎች ለሰዎች ድርጅት ባለፈው ዓመት በኢትዮጵያ ለ1862 በትራኮማ ለተጠቁ ሰዎች የቀዶ ህክምና አገልግሎት ማቅረቡን አስታወቀ። ድርጅቱ ትራኮማን ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ ለማጥፋት እየሰራ መሆኑንም አስታውቋል።