የዓለም ጤና ድርጅት ባልደረባ ዶክተር ክርስቶፈር ዳይን እንደሚሉት ችግሩ ፈጥኖ ካልተገታ የምዕራብ አፍሪቃ ሐገራት በፖለቲካዊ ቀዉስ መናወጣቸዉ የማይቀር ነዉ።የዳይን ጥናት እንደሚማመለክተዉ የኤቦላ ስርጭት በዚሑ ከቀጠለ የተለካፊዉ ቁጥር ከአንድ ወር በኋላ ከሃያ ሺ ይበልጣል።

የኤኮኖሚክስ ፕሮፌሰር ጌታቸዉ በጋሻዉ ግን ሁለቱ ተቋማት የአሜሪካና የአዉሮጳን ጥቅም ከማስከበር አልፈዉ ለአፍሪቃ የሚረዳ ነገር መክረዉ፤አድርገዉም አያዉቁም።ኢትዮጵያም የዕዳዋን መጠን ለመቆጣጠር የራስዋን ጠቃሚ መርሕ መከተል ነዉ የሚገባት።

በ1768 እኤአ የተጻፈና ጥንታዊ አባባሎችን የያዘ አንድ ‹‹AN ETHIOPIAN SAGA›› የተሰኘ መጽሐፍ ሳነብ ‹‹ጨረቃዋን እያየህ፣ ጨለማውን ግን እየተጠነቀቅ ተጓዝ›› የሚል ጥንታዊ ብሂል አየሁ፡፡ ይህ ለጥንቱ መንገደኛ የተሰጠ የጠቢብ ምክር ነው፡፡

የጥንቱ ተጓዥ ጤፍ በምታስለቅመው ጨረቃ መጓዙ ሁለት ጥቅሞች ይሰጡት ነበር፡፡ በአንድ በኩል በቀን ከሚገጥመው ሙቀትና የፀሐይ ቃጠሎ ይድናል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ መንገዱን በሩቁ ስለማያየው ‹ለካ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል› እያለ መንፈሱ እንዳይደክም ያደርገዋል፡፡

በተለይም ደግሞ መንገደኞቹ በዛ ካሉ፣ ሰብሰብ ብለው በአንድ ቤት ታዛ ሥር ወይም በአንድ ዛፍ ጥላ ሥር ያርፉና በአራተኛው ክፍለ ሌሊት(ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት በኋላ) ተነሥተው የጨረቃዋን ብርሃን እየተከተሉ መጓዝ ነው፡፡ ያን ጊዜ  ነው እንግዲህ ‹ከጨለማው እየተጠነቀቁ፣ ነገር ግን ጨረቃዋን እያዩ›› የሚጓዙት፡፡

መንገደኞቹ ጨረቃዋን የሚያዩዋት ለሁለት ነገር ነው፡፡ በአንድ በኩል ጨረቃዋ መጀመሪያ እየደመቀች፣ በኋላ ደግሞ እየደበዘዘች መጓዟ የሌሊቱን ማለፍና የቀኑን መምጣት ይነግራቸዋል፡፡ በተለይ የበረሐ መንገደኞች ከሆኑ የጨረቃዋ እየደበዘዘች መሄድ ለእነርሱ መልካም ዜና አይደለም፡፡ የሙቀቱን መምጣት እያረዳቸው ነውና፡፡ የፀሐዩን ግለትም እነርሱም ሆኑ የጭነት ከብቶቻቸው አይቋቋሙትም፡፡ በሌላም በኩል የጨረቃዋን ብርሃን እየተከተሉ የሚጓዙት፣ በአካባቢው ሌላ ብርሃን የለምና፣ አንዳንድ ጊዜ ጨረቃዋን ደመና ሲጋርዳት ተግ እያሉ፣ በጠራ ሰማይ ላይ ፍንትው ብላ ስትወጣ ደግሞ መንገዱን ያዝ ያዝ እያደረጉ ስለሚገሠግሡ ነው፡፡

በዚህ ጉዟቸው የሚከተሉት የሚያተኩሩት በጨረቃዋን ላይ ብቻ አይደለም፡፡ ምንም እንኳን ጨረቃዋ መንገዱን ብታሳያቸውም ጫካው፣ ሸለቆውና ገደላ ገደሉ ደግሞ በተቃራኒው ድቅድቅ የሆነ ጨለማን ይፈጥራል፡፡ ጥጋጥጉ ሁሉ ከጨረቃዋ ደማቅ ብርሃን ተጋርዶ አንዳች መርግ የመሰለ ጽልመት ይጋርደዋል፡፡ ይኼ ደግሞ የጨረቃዋ ብርሃን ላጋለጣቸው አራዊት ዋና መደበቂያ፣ ለሽፍቶች ዋና መሸሸጊያ ነው፡፡ አንዳንዴም ጨረቃዋ ፍንትው ብላ ስትወጣ ከተገለጠው አካባቢ ግራና ቀኝ ያለው አስፈሪና ምን እንደያዘ የማይታወቅ ሥርቻ ይሆናል፡፡

የጨረቃ ብርሃን እንደ ፀሐይ አይደለም፡፡ የፀሐይ ብርሃን ከሙቀቱ ጋር ስለሚመጣ አካባቢውን ይቀይረዋል፡፡ የብርሃኑ ወገግታም መከለያዎችን እንኳን ተሻግሮ የብርሃን ፍንጣቂ ይለቅበታል፡፡ የፀሐይ ብርሃን ከጨረቃ የተሻለ ምለክዐት አለው፡፡ ጨረቃ ግን ድምቀት ነው ያላት፡፡ አካባቢውን ታስውበዋለች እንጂ አታሞቀውም፡፡ በዚህ የተነሣ ለጨረቃ መንገደኞች ግራ ቀኙ አስፈሪ ነው፡፡  ከሆነ ርቀት በላይም በጨረቃ ብርሃን መንገዱን ማየት አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ ለዚህም ነው ‹‹ጨለማውን ተጠንቀቅ›› የተባለው፡፡

አንዳንድ ጊዜ ሕይወት የጨረቃ መንገድ ትሆናለች፡፡ ብርሃንና ጨለማ፣ ድምቀትና ፍርሃት አብረው የሚገኙባት፡፡ መንገድህን ታውቀዋለህ፤ ነገር ግን ከመንገድህ ግራና ቀኝ የሚጠብቅህን ወጥመድ በሚገባ ላታውቀው ትችላለህ፡፡ ቀና ስትል እንደምታያት ጨረቃ እጅግ የደመቁ ተስፋዎችን፣ ድሎችንና አጋጣሚዎችን ታገኛለህ፡፡ ነገር ግን ጨረቃ ጨረቃዋን ብቻ ስታይና ነፍስህን በሐሴት ስታጥለቀልቅ ደግሞ ከግራና ቀኝህ ከሚገኙት ጉድባዎች፣ ሸለቆዎች፣ ጥሻዎችና ጥጋጥጎች  የደበተ ጨለማ፣ የሚያስፈራም አውሬ፣ የሸመቀም ጠላት ያጋጥምሃል፡፡

መንገደኛው ጨረቃዋን ለማድነቅ በቂ ዕድልን አያገኝም፡፡ መጓዝ ስላለበት፡፡ አንድ ቦታ ቆሞ፣ በደስታ ተደሞ፣ በፍቅሯ ተውጦ፣ በብርሃንዋ ተመስጦ ‹ጨረቃ ድንቡል ቦቃ፣ ዐጤ ቤት ገባች ዐውቃ›› እላለሁ ቢል፣ እርሱ በጨረቃዋ ውበት በተመሰጠበት ጊዜ ከማያውቀው ጥሻ ብቅ የሚል አውሬ ወይም ጠላት አይጠፋም፡፡ አለበለዚያም ደግሞ የሚጣላ ባይሆንም የሚያስደነግጥ ኮሽታ አያጣም፡፡ ስለዚህም በአንድ ልቡ ቀና ብሎ ውበቷን እያየ፣ በአንድ ልቡም መንገድ መንገዱን እያስተዋለ፡፡ አልፎ አልፎም ደግሞ ግራና ቀኙን እየገላመጠ ይጓዛል፡፡

ሕይወት እንደ ጨረቃዋም የምታምር፣ የምትስብ፣ ኑሩብኝ ኑሩብኝ የምትል፣ አንዴ እየጎደለች ሌላ ጊዜ ብትሞላም፣ የምትፈነጥቅና መንገድ የምታሳይ፣ በተስፋና በጉጉትም የተሞላች ናት፡፡ ሕይወት እንደ ጨረቃዋ ፍስስ የምትል፣ የሚዜምላትና የምትናፈቅም ናት፡፡

በሌላም በኩል ደግሞ ሕይወት ተስፋና ደስታ፣ ርካታና ሰላም ብቻ አይደለችም፡፡ መንገደኛው ጨረቃዋን ብቻ እያየና በእርሷም እየተደሰተ ብቻ መጓዝ እንደማይችለው፡፡ ሕይወት ጥሻዎችና ገደሎች፣ ጫካዎችና ጉድባዎችም አሏት፡፡ የጨረቃዋ ብርሃን እንደሚያስደስተው ሁሉ የጫካዎቹ ጥላ፣ የጥሻዎቹ ዝምታ፣ የገደሎቹ ድብታና የገደሎቹም ጨለማ ያስፈራል፡፡ አንድም እዚያ ምን እንዳለ አለመታወቁ፣ አንድም ደግሞ እዚያ አውሬና ጠላት ሊኖር መቻሉ፡፡ የጨረቃዋን ብርሃንና ድምቀት ምን ብንወድደው፣ ጊዜ ሰጥተን ልናጣጥመውም ብንፈልግ እንኳን በግራ በቀኝ ያለው ጨለማና ፍርሃት ግን በቂ ጊዜም በቂ ልብም አይሰጠንም፡፡ ደግሞ እርሱንም እናስባለን፤ ደግሞ እርሱንም ማየት እንፈልጋለን፤ ደግሞ የእርሱንም ዝምታና ጨለማም ማጥናት እናስባለን፤ ምን ሊኖር እንደሚችል፣ ከማናውቀው ምንም ውስጥ ምን ሊወጣ እንደሚችል እንገምታለን፡፡ ከግምታችን ተነሥተንም እንሠጋለን፡፡

ያለፈውን እናስታውሳለን፡፡ ያለፉትንም እናስባለን፡፡ በዚህ ዓይነት መንገድ ስለተጓዙ ሰዎች የተነገረውንም ታሪክና ትርክት እናስታውሳለን፡፡ ተረቶቹንና ንግሮቹን እናመጣለን፡፡ ለጨለማውና ለዝምታው ትርጉም እንሰጣለን፡፡ እንጠረጥራለን፡፡ ኮሽታዎችንና ንቅናቄዎችን ሁሉ እናዳምጣለን፡፡ ለእያንዳንዱ ድምጽ ትርጉም እንሰጣለን፡፡ እንዲህ እያልንም በጨረቃ ድምቀት ተደስተን፣ በግራ ቀኙ ጨለማ ደግሞ ሠግተን እንጓዛለን፡፡ እንዲህ ናት ሕይወት፡፤ ተስፋ ብቻ አይደለችም ሥጋት አላት፣ ደስታ ብቻም አይደለችም ኀዘን አላት፤ የምትታይ ብቻ አይደለችም የማይታይም ክፍል አላት፡፡ የሚታወቅ ብቻ አይደለችም የማይታወቅም አካል አላት፡፡ ለዚህም ነው ቀደምቶቻችን ‹ጨረቃዋን እያየህ፣ ጨለማውን ግን እየተጠነቀቅክ ተጓዝ› ያሉን፡፡

ጨረቃዋን ለማያዩ ሰዎች ሕይወት ጎምዛዛ ብቻ ናት፡፡ ድብርትና ሥጋት የሞላባት፡፡ ምንም ዓይነት የደስታ ፍንጣቂ የማይታይባት፡፡ ከንቱ ብቻ ናት፡፡ ችግርና ጉስቁልና ብቻ የሰፈነባት፡፡ ጨለማውን ለማያዩ ሰዎች ደግሞ ሕይወት ደስታና ፈንጠዝያ፣ ሰላምና እርካታ፣ ፌሽታና ዝላይ ብቻ ናት፡፡ ሁለቱም ግን ይጎዳሉ፡፡ ጨረቃን የማያዩ ሰዎች ሕይወትን ለማጣጣም ዕድል አያገኙም፡፡ ምንም ዓይነት በጎ ነገርንም ከሕይወት አይጠብቁም፡፡ ምንም ዓይነት ደግ ነገር አይታያቸውም፡፡ ምንም ዓይነት ውበት አይገለጥላቸውም፡፡ ሁሉም ጨለማ ብቻ ነው፡፡ ጨለማውን የማያዩ ሰዎች ደግሞ ምንም ዓይነት ዝግጁነት፣ ጥንቃቄና ችግርን የመፍታት ጥበብ የላቸውም፡፡ ሣር ሣሩን ብቻ ሲያዩ ገደል ውስጥ የመግባት ዕጣ ይገጥማቸዋል፡፡ ማሩን እንጂ የንቧን መናደፍ፣ ጽጌረዳውን እንጂ እሾሁን አያዩም፡፡ ሕይወት መዝለልና መዘነጥ፣ መብላትና መተጣት፣ መሳቅና መጫወት ብቻ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህም በተወጉና በተነደፉ ጊዜ ይደናገጣሉ፡፡ በቶሎም ተስፋ ይቆርጣሉ፡፡

በሕይወት በጤነኛ መንገድ ለመጓዝ የተሻለው ጥበብ ጨረቃዋን ማድነቅና በብርሃኗ መሄድ፣ ጨለማውንም መጠንቀቅ ነው፡፡ ሕይወት በጨረቃ ብርሃንና በጨለማው መካከል የተሠመረች ስላች መንገድ ናትና፡፡ እዚህ ላይ ጠቢብ ሰው ሚዛኑን ይጠብቃል፡፡ እዚህ ላይ ጠቢብ ሰው አንድ ዓይኑን በጨረቃዋ ሌላውንም ዓይኑን በጨለማው ላይ ተክሎ ይጓዛል፡፡ ጠቢብ ሰው ሁለቱን ዓኖቹን አንድ ነገር ላይ አይተክልም፡፡ ብዙ ጊዜ አንድን ነገር በሁለት ዓይኖቻችን ነው የምናየው፡፡ ማየት ያለብን ግን የዚያን ነገር ጨረቃና ጨለማ ነው፡፡ ጨረቃዋን በአንድ ዓይን ጨለማውን ደግሞ በሌላው ዓይን፡፡ ሕይወት በጨለማና በጨረቃ መካከል መጓዝ ነውና፡፡

ሜልበርን፣ አውስትራልያ

ዓለም በኤቦላ ስጋት መታመስ ሲጀምር በቀድሞዋ ዛየር በዛሬዋ ዴሞክራቲክ ሬፐብሊክ ኮንጎ ተኅዋሲውን ያገኙት የቤልጅየም ተወላጁ ፕሮፌሰር ፒተር ፒዮ መታወስ ጀመሩ።ፕሮፌሰሩ በአሁኑ ወቅት የለንደን የግል ንጽህናና የምድር ወገብ አካባቢ በሽታዎች ትምህርት ቤትን በሃላፊነት ይመራሉ።

ዋይ ! ዋይ ! (በሙሾ ዜማ ይውጡት) ንዋይ ዋይ! ዋይ! ንዋይ ንዋይ ሞተ አሉ በቁሙ ንዋይ ሞተ አሉ በቁሙ ጨለመችበት ዓለሙ (2) ንዋይ በንቁላል ተመታ ንዋይ በንቁላል ተመታ ሊዘፍን መጥቶ በማታ (2፟) ዋይ! ዋይ! ንዋይ ዋይ! ዋይ! ንዋይ ምን ይላት ይሆን ለሚስቱ ምን ይላት ይሆን ለሚስቱ በንቁላል ገምቶ ደረቱ (2) ጀግናው ፈረሰ ለሆዱ ጀግናው ፈረሰ […]

በቅድሚያ መጽሓፉን ጊዜ ሰጥተህ በማንበብ አስደማሚ ምልከታ በመስጠትህ ከልብ አመሰግናለሁ ። የተጻፈበትም አንዱ አላማ ይህ ስለሆነ። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በእይታህ ላይ እነዚህ ጉድለት ይታይባቸዋል ብለህ ያነሳኸው እና የወደፊት ግምቶችህ ላይ የተወሰነ አስተያየት ለመስጠት የሚጋብዙ ስለሆነ ትንሽ ማለት ፈለኩ። በዚህ አጋጣሚ ሌሎች በመጵሀፉ ይዘት ላይ ዝርዝር ግምገማ ላደረጉ ሰዎች ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ለእያንዳንዱ አስተያየት መስጠት ከጊዜ አኳያ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ የማልዘልቅበትን መንገድ ልጀምረው አልፈለኩም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተመስገን ደሳለኝ

በዚህ ተጠየቅ ጨርፈን የምንመለከተው በኮሙኑዮኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የነበረውና ዛሬ በስደት የሚገኘው የአቶ ኤርሚያስ ለገሰን “የመለስ ትሩፋቶች፣ ባለቤት አልባ ከተማ” የተሰኘው መጽሐፍን ነው፡፡ የመድብሉ ጻሐፊ ኤርሚያስን በግል አላውቀውም፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁት አቶ በረከት ስምዖን እርሱን እና ሽመልስ ከማልን ምክትሎቹ አድርጐ በሚኒስቴር ዲኤታ ማዕረግ መሾሙን በግዮን ሆቴል ለጋዜጠኞች ይፋ ባደረገበት ዝግጅት ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

“ዩናይትድ ስቴትስ የራሷን ጥቅሞች ለማስጠበቅ ወደ ኋላ እንደማትል ሁሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተመሰረተበትና ያለበትን ዓላማም ከማክበርም አታፈገፍግም፤” የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ።

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መስከረም ፲፬(አሥራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን የአብዮታዊ ዲሞክራሲ የትምህርት መመሪያን ለማጥመቅ ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ በአገሪቱ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ስልጠናውን በግዳጅ እንዲወስዱ እየተደረጉ ነው። በአንዳንድ አካባቢዎች ተማሪዎቹ የፖለቲካ ስልጠና እንዳለ አስቀድመው በመስማታቸው ፣ ከስልጠናውን የቀሩ ሲሆን፣ የገዢው ፓርቲ የወረዳ ሹሞች መምህራን ተማሪዎችን እንዲያመጡ የተለያዩ ዘዴዎችን እንዲጠቀሙ እያግባቡ ነው። አንድ …

መስከረም ፲፬(አሥራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብአዴን ንብረት በሆነው ጥረት ኮርፖሬት ውስጥ የሚገኙት ጣና ሞባይል ና ዘለቀ እርሻ ልማት ድርጅቶች በያዝነው አመት ከ225 ሚልዩን ብር በላይ ኪሳራ እንዳጋጠማቸው በ2007 ዓም መግቢያ ላይ በተደረገው የድርጅቱ ግምገማ ላይ ተገልጧል። አቶ አለምነው መኮንን የአማራውን ህዝብ መሳደባቸውን ተከትሎ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ አመራሮችን ለማሳመን የተደረጉ ስብሰባዎች ና የተሃድሶ …

መስከረም ፲፬(አሥራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመላ አገሪቱ ከ40 ሚሊዮን በላይ መጻፍና ማንበብ የማይችሉ ወጣት እና ጎልማሶች አሉ ያሉት አቶ ሺፈራው ፤  ይህንን የትምህርት እድል ያለገኙ ወጣቶች እና ጎልማሶች አማራጭ ትምህርት እንዲያገኙ የተደረገው ሙከራ አፈፃጸሙ ከዜሮ በታች ነው ብለዋል። በኢህአዴግ የእቅድ ትውውቅ መድረክ ላይ እንደቀረበው በጎልማሶች የትምህርት አቀራረብ  አማራ 0.9፣ ኦሮምያ ፣ 0.71 …

መስከረም ፲፬(አሥራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዋጋ ንረትን ያረጋጋሉ ተብሎ በመንግሥት ልዩ ድጋፍ በተለይ በአዲስአበባ ከተማ የተቋቋሙት የሸማቾች የህብረት ሥራ ማህበራት በሙስናና ብልሹ አሠራር ውስጥ በመዘፈቅ አንዳንዶቹ በተቃራኒው የዋጋ ንረትን የሚያባብሱ ሥራዎች ውስጥ መሰማራታቸው መረጋገጡን ከአስተዳደሩ የተገኘ ሰነድ ጠቆመ፡፡ 250ሺ ያህል አባላት ያሉዋቸው 153 መሰረታዊ ማህበራትና 10 ዩኒየኖች እንዲሁም 1 ሺ 815 አዲስ …

ዓለም በኤቦላ ስጋት መታመስ ሲጀምር በቀድሞዋ ዛየር በዛሬዋ ዴሞክራቲክ ሬፐብሊክ ኮንጎ ተኅዋሲውን ያገኙት የቤልጅየም ተወላጁ ፕሮፌሰር ፒተር ፒዮ መታወስ ጀመሩ።ፕሮፌሰሩ በአሁኑ ወቅት የለንደን የግል ንጽህናና የምድር ወገብ አካባቢ በሽታዎች ትምህርት ቤትን በሃላፊነት ይመራሉ።

Jennifer Hudson ሶስትኛዋ የሆንውን የእስቱዲዮ አልበሟን በገበያ ላይ አወላለቸ ፡፡ የአልበሙ መጠሪያ JHUD የተባለ ሲሆን በወስጡ 10 ዜማዎችን አካቷል በዛሬው የሙዚቃ ቃና ፕሮግራም ከዚሁ አዲስ አልበም የተመረጡ ዜማዎችን እና ሰለሞን ክፍሌ ስለ Frank Sinatra ያዘጋጀው ፕሮግራም ትካቷል፡፡

የስዊድን የሕግ ባለሞያዎች በስብዕና ላይ ወንጀል ፈፅመዋል ባሉዋቸው ከፍተኛ የኤርትራ ባለሥልጣናት ላይ ክስ እንዲመሠረት ያቀረቡበትን ጥያቄ የስዊድን ዓቃቤ ሕግ ውድቅ ካደረገባቸው በኋላ ይግባኝ ማመልከቻ አስገብተው መልሳቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

በሶርያ እና በኢራቅ የሚንቀሳቀሱትን የ«አይ ኤስ» ተዋጊዎች የሚቀላቀሉት አውሮጳውያን ቁጥር ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ በአንድ ሶስተኛ መጨመሩን የአውሮጳ ኅብረት የፀረ ሽብርተኝነት ክፍል አስታወቀ።

በተወለዱ 28 ቀናት ጨቅላዎች ለሞት የሚዳረጉበት ምክንያት ከነፍሰጡር እናት ጤንነትና አመጋገብ ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። የእርግዝና ክትትልና በወሊድ ወቅትና ከወሊድ በኋላ እንክብካቤ በማድረግ በተወለዱ እስከ 28 ቀናት ውስጥ የሚሞቱ ህጻናትን ቁጥር መቀነስ ይቻላል።

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጄኔቫ ሲካሄድ በሰነበተው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ግምገማ ላይ አቋሙን ያስታወቀው አለማቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ ኢትዮጵያ የሰአብአዊ መብት ድንጋጌዎችን እንደምታከብር ቃል መግባት ብቻ ሳይሆን፣ በተጨባጭ ገለልተኛ ወገኖች እስር ቤቶችን እንዲገበኙ፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት የሚካሄዱባቸውን ቦታዎች እንዲጎበኙና በደል የደረሰባቸውን ወገኖች ለማነጋገር እንዲፈቀድላቸው ጠይቋል። የሰብአዊ …

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው በአቶ ገዱ አንዳርጋቸው በተመራው ስብሰባ ላይ ዳኞች የስርአቲ ደጋፊ እንዲሆኑ እየተገደዱ ባለበት ሁኔታ እንዴት ነጻ ዳኝነት ሊሰጥ ይችላል በማለት ጠይቀዋል። የድርጅት አባላት ያልሆኑ ዳኞችም ስራቸውን ለመስራት እየተቸገሩ መምጣታቸውን መናገራቸውን ጋዜጣው ዘግቧል። ይሄው በመላው አገሪቱ በሚደረገው የፖለቲካ ስልጠና የገዢው ፓርቲ ደጋፊ አባላት ሳይቀሩ በስርአቱ ላይ …

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ስራ በሚገኘው ደጀና አቬሺን ውስጥ የሚሰራ ስሙ በውል ያልታወቀ አንድ ወታደር በግቢው ውስጥ ለሚሰሩ  ሰራተኞች  በተከፈተው ሻሂ ቤት ውስጥ በአስተናጋጅነት የምትሰራዋን በደብረዘይት ነዋሪ የሆነች ወጣት በስድስት ጥይቶች ተኩሶ መግደሉን የአይን እማኞች ገለጹ። ትናንት 11 ሰአት ላይ ሰራተኞች ሰርቪስ አውቶቡስ ለመያዝ በተሰለፉበት ወቅት፣ ወታደሩ በአስራዎች …

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከደቡብ ሱዳን ታፍነው የተወሰዱት የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ኦኬሎ አኳይ በእስር ቤት ውስጥ ከሌላ እስረኛ ጋር ተጋጭተዋል በሚል ሰበብ ከፍተኛ ድብደባ ከደረሰባቸው በሁዋላ ጸሃይ ላይ ለረጅም ሰአት እንዲቀመጡ ተደርገዋል። አቶ ኦኬሎ ድብደባው የተፈጸመባቸው ቂልንጦ እየተባለ በሚጠራው  እስር ቤት ውስጥ ሲሆን፣ በእስር ቤት ሃላፊዎች መረጃ እንዲያቀርብ ተብሎ …

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ 130 የሚሆኑ የቻይና ኩባንያዎች ለአፍሪካ መሪዎች በእስር ቤት ጥቅም ላይ የሚሆኑ የማሰቃያ መሳሪያዎችን ይሸጣሉ። የኤልክትሪክ ንዝረት ያላቸው   ከብረት የተሰሩ ሹል ዱላዎችና ሌሎችም  የማሰቃያ መሳሪያዎች ለአፍሪካ እና ለእስያ አገራት መሸጣቸው በአህጉራቱ ውስጥ የሚታየውን ሰብአዊ መብት እረገጣ አባብሶታል። በአለም ላይ ስለት ያላቸውን የንዝረት ብረቶችን የምታመርተው …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በተወለዱ 28 ቀናት ጨቅላዎች ለሞት የሚዳረጉበት ምክንያት ከነፍሰጡር እናት ጤንነትና አመጋገብ ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። የእርግዝና ክትትልና በወሊድ ወቅትና ከወሊድ በኋላ እንክብካቤ በማድረግ በተወለዱ እስከ 28 ቀናት ውስጥ የሚሞቱ ህጻናትን ቁጥር መቀነስ ይቻላል።

ሐይማኖት አለሙ በተዋኝነት፤በአዘጋጅነትና በፀፌ ተዉኔትነት በኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ዉጪ በተለይ ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ በበርካታ ድራማዎች ተሳትፏል። ሐይማኖት በተለያዩ ቲያትሮች በሥራ-አስኪያጅነትና በአዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲም በመምሕርነት ያገለገለ የጥበበብ ሰዉ ነበር። 68 ዓመቱ ነበር።

የጀርመን መከላከያ ሚኒስትር ኦዙላ ፎንዴር ላይን፤ የኤቦላ ተዋኅሲ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገዉ ጥረት ለመካፈል በፈቃደኝነት ወደ ምዕራብ አፍሪቃ ለሚሄዱ ወታደሮችን እና ሲቪል ሰራተኞች ትናንት ጥሪ አደረጉ።

ከፊል ሰነዓን ባመሰቃቀለዉ ዉጊያ 350 ሐምሳ ያክል ሰዎች ተገድለዋል።በሺሕ የሚቆጠሩትን ከቤት ንብረታቸዉ አፈነቃሏል።ሁለቱ አማፂያንና የሐገሪቱ መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሸምጋይነት ተኩስ ለማቆም ከተስማሙ ካለፈዉ ዕሁድ ወዲሕ ግን ከተማይቱ ተረጋግታለች።

ትክክለኛ የቋሚና አላቂ ንብረት ምዝገባና አስተዳደር፣ ተቀባይነት ያለውና እምነት የሚጣልበት የገንዘብ ገቢና ወጪ እንቅስቃሴ፣ ግልጽና ወጥነት ያለው የግዥ አፈጻጸም፣ ብቁ የቁጥጥር ሥርዐት ባለመዘርጋቱ የቤተ ክርስቲያናችን ጥቅል ሀብት አይታወቅም፡፡ በማንኛውም ሕጋዊና ዘመናዊ የሒሳብ ምርመራ አሠራር እጅግ ኋላ ቀር በኾነው በነጠላ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ እና በሞዴላሞዴሎች አሠራር የቤተ ክርስቲያንን ገንዘብ እና ንብረት ከብኩንነት፣ ከመዘረፍ እና ከመጭበርበር ለማዳን …

መስከረም ፲፪(አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምዕራብ አርማጮሆ ወረዳ የአብርሃጅራ ነዋሪዎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በተደረገው ህዝባዊ ስብሰባ በመሬት ስሪት ፣በልማት ና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ቅሬታወች ቀርበዋል፡፡በውይይቱ ላይ በመገኘት ቅሬታቸውን ያቀረቡት ነዋሪዎቹ “የወረዳው አመራሮች እርስ በርስ በመሻኮት ስልጣን ለመያዝ ሰዎችን ያስገድላሉ የበላይ አመራሮችን የኑሮ ሁኔታ በማጥናት ቤት ሰርተዋል፣ሃብት አከማችተዋል በማለት እነርሱም የበላይ አለቆቻቸውን …

መስከረም ፲፪(አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ባወጣው መግለጫ ፍትህ ሚኒስቴር ሃምሌ 28፣ ቀን 2006 ዓም በፋክት፣ ሎሚ፣ ጃኖ፣ አዲስ ጉዳይ፣ እንቁ መጽሄቶችና አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ ላይ ያቀረበው ክስ በህገመንግስቱ የሰፈረውን ሃሳብን የመግለጽ ነጻነት ፣  ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው የሰብአዊ መብቶች አለማቀፍ መግለጫ አንቀጽ 19 ፣ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች አለማቀፍ ቃልኪዳን አንቀጽ 19 …

መስከረም ፲፪(አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ገዢው ፓርቲ ለመጪው ምርጫ በሚያደርገው ዝግጀቱ የመንግስት ሰራተኞችን፣ መመህራንና ተማሪዎችን በማስገደድ የሚሰጠው የፖለቲካ ስልጠና እንደቀጠለ ሲሆን፣ ባሳለፍነው ሳምንትም በርካታ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጥያቄዎች ተነስተዋል። በአዲስ አበባ በኢትዮ-ቻይና ቲቪቲ በነበረው ስልጠና ላይ ” ከ23 አመታት በሁዋላ አሁንም እራሳችሁን ከደርግ ጋር እያነጻጸራችሁ ነው? ደርግ ከሻእቢያ፣ ከእናንተ ጋርና ከሶማሊያ ጋር ጦርነት …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የ85 ሰዎች ገቢ ከግማሽ ከሚበልጠዉ የዓለም ሕዝብ ይበልጣል።—የዓመዓቱ ግብ ያልተሳካዉ በፖለቲካዊ ዳተኝነት፤ በዕዉቀት እጦት ብቻ አይደለም።በጥቅም ሽኩቻ እና ዕቅዱ የሐብት ክፍፍል የሚያነሳ በመሆኑም ጭምር እንጂ