Tag: ethiopian news in amharic
The first female stage Actress, Artist Selamawit G. Selassie passed away በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ተዋናይት ወ/ሮ ሰላማዊት ገብረሥላሴ ማረፋቸው ተነገረ።

The first female stage Actress, Artist Selamawit G. selassie passed away .. በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ተዋናይት ወ/ሮ ሰላማዊት ገብረሥላሴ ማረፋቸው ተነገረ። ነፍስ ይማር ። ከአንድ ዓመት በፊት ድንቅ መጽሔት ከቤታቸው ቃለ መጠይቅ አድርጎላቸው ነበር፣ እነሆ ለማስታወሻ ….
ሠላማዊት ገ/ሥላሴ – የመጀመሪያዋ የሴት አርቲስት (በጽጌ አይናለም የድንቅ መጽሔት ሪፖርተር ከአዲስ አበባ)
አብዛኛውን ጊዜ አስቸጋሪው ነገር ለአንድ ነገር የመጀመሪያ ሆኖ መገኘት ነው፡፡ በተለይም ደግሞ ማህበረሰቡ…
አንጋፋው ሻዕቢያ
ራትን ቁርስ ላይ
የኢቦላ ስብሰባ በአዲስ አበባ
ባለፈው ሣምንት ውስጥ የምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮች የጋራ ልማት ትብብር ተቋሙ ኢጋድ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሮችና ባለሙያዎች አዲስ አበባ ላይ ተሰብስበው ኢቦላ ተከስቶ በነበረባቸው አካባቢዎችና ዓመታት የነበረውን ልምድ መነሻ በማድረግ ሊደረግ በሚገባው ጥንቃቄና ዝግጅት ላይ ተነጋግረዋል፡፡
በስብሰባው ላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን ካቀረቡት ባለሙያዎች መካከል የሕክምናና የኅብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ባለሙያው፣ በኢትዮጵያና በሌሎችም የአፍሪካ ሃገሮች የበሽታዎች ሥርጭትና ቁጥጥር ላይ የሠሩት ዶ/ር አያና የኔአባት ይገኙበታል፡፡
እስክንድር ፍሬው አነጋግሯቸዋል፤ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
“አሕመድ ያ ሐቢቢ”
በዘጠኙ ፓርቲዎች ሰልፍ ላይ የተወሰደውን ህገወጥ እርምጃ እናወግዛለን! – ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
በዘጠኙ ፓርቲዎች ትብብር ላይ የተወሰደውን እርምጃ ተከትሎ አንድነት ፓርቲ መግለጫ አወጣ፡፡ አንድነት በመግለጫው በትብብሩ አመራሮችና አባላት ላይ የተወሰደውን እርምጃ አውግዟል፡፡ ፓርቲው በዘጠኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮችና አባላት ላይ የተወሰደውን ህገ-ወጥ እርምጃ ተከትሎ አስፈላጊውን መረጃዎች ካሰባሰበ በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡ ሙሉውን መግለጫ ከታች ተመልከቱ፡፡ በዘጠኙ ፓርቲዎች ሰልፍ ላይ የተወሰደውን ህገወጥ እርምጃ እናወግዛለን! አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት ሰላማዊ […]
70 ኢትዮጵያውያን ቀይ ባህር ላይ አለቁ
ኀዳር ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ስደትን የህይወታቸው የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ በጅቡቲ በኩል አድርገው ወደ የመን ለመግባት የሞከሩ 70 ኢትዮጵያውያን ቀይ ባህር ላይ ሰጥመው መሞታቸውን የየመን ባለስልጣናት ገልጸዋል። ታይዝ በምትባለዋ ግዛት የሚገኙ ባለስልጣናት ለአሶሴትድ ፕሬስ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያውያኑን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረችው ጀልባ ባጋጠማት ከባድ አውሎ ንፋስና ማእበል አል ማክታ እየተባለ ከሚጠራው ወደብ ራቅ ብሎ …
መሪዎች ቢታሰሩም ትግሉ እንደማይቆም የ 9 ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች አስታወቁ
ኀዳር ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የምርጫ ስርዓት ለውጥ እንዲደረግ ለመጠየቅ ህዳር 27 ቀን የአዳር ተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ወደ አደባባይ በወጡት 9 የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮች ላይ የፌደራል ፖሊስ አባላት ድብደባ በመፈጸም ወደ እስር ቤት ቢወስዱዋቸውም፣ የትብብሩ አመራሮች ግን ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ኢትዮጵያውያን ለትግሉ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። ሶስተኛ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት …
ቦርድ የወጡ አንዳንድ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ሶማሊያ እንዲዘምቱ ጥሪ ቀረበላቸው
ኀዳር ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከዚህ ቀደም ሶማሊያ ውስጥ ዘምተው የነበሩና መከላከያን የአገልግሎት ዘመናቸውን በመጨረስ ወይም በጉዳት የለቀቁ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ መከላከያ ተመልሰው እንዲዘምቱ በደብዳቤ ጥሪ ቀርቦላቸዋል። የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ጥሪው የደረሳቸው ወታደሮች ጥሪውን ለመቀበል ፈቃደኞች አልሆኑም። ጥሪ የተደረገላቸው የሰራዊት አባላት “የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሰላም አስከባሪ ሃይል በሚል ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ …
በዘጠኙ ፓርቲዎች ሰልፍ ላይ የተወሰደውን ህገወጥ እርምጃ እናወግዛለን! ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት ሰላማዊ ታጋዮችና በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማሳደዱን አሁንም ቀጥሎበታል። የዘጠኙ ፓርቲዎች ትብብር ለህዳር 27 ጠርተውት በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመንግስት ኃይሎች የተወሰደውን እጅግ አረመኔያዊ የሆነ ህገ ወጥ እርምጃ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ በጥብቅ ያወግዛል።
እነዚህ ፓርቲዎች የሀገሪቱ ህገ መንግስት፣ የስብሰባና ሰልፍ አዋጁ በሚፈቅደውመሰረት ለአዲስ አበባ መስተዳድር ሰልፍ እንደሚያደርጉ ቀኑንና ቦታውን ጠቅሰውአሳውቀዋል፤ በአዋጁ መሰረት ደግሞ ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ እንጂ ፍቃድ መጠየቅ ግድ የሚል አይደለም። ነገር ግን ህገ ወጥ በሆነ ሁኔታ ህጉ በሚፈቅደው መሰረት ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ከሰማያዊ ፓርቲ ፅህፈት ቤት እየወጡ የነበሩትን ሰልፈኞች በመንግስት ኃይሎች ከፍተኛ የሆነ ድብደባ
እንዲፈፀምባቸው ተደርጓል።
ከዚህም ባሻገር የትብብሩ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት አፍሶ በመውሰድ በጨለማ ክፍል ውስጥ አስሯቸው ይገኛል። ወዳጅና ዘመድ እንዳይጠይቃቸው መደረጉም የአንድነት ከፍተኛ አመራሮች ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ በትናንትናው ዕለት በአካል ተገኝተው አረጋግጠዋል።
የአዲስ አበባ አስተዳደር ይሄ ጉዳይ በአግባቡና ህጉ በሚፈቅደው መንገድ መፍታት ሲችል፤
በሚዲያ እርምጃ እወስዳለሁ ብሎ ማወጁና በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ግፍ
እዲፈፀም በማድረጉ ሀላፊነቱን መውሰድ አለበት። በተለይ ኢህአዴግ የ2007
ምርጫ እየቀረበ ባለበት ሁኔታ እንዲህ ዓይነቱ አፈናና ህገወጥ እርምጃ መውሰዱ
ምርጫውን ችግር ውስጥ የሚከት ጉዳይ መሆኑ ሊገነዘብ ይገባል። አንድነት
ፓርቲ ይሄ ጉዳይ በዝምታ የሚያየው ነገር አይሆንም፤ በቅርቡም አስፈላጊውን
መረጃዎች ሁሉ አሰባስቦ ጋዜጣዊ ይሰጥበታል።
የዘጠኙ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት በህገ መንግስቱ ላይ የተቀመጠውን
ሰላማዊ ሰልፍ የማድርግ መብት ከመጠቀም ውጪ ያጠፉት ምንም ዓይነት ነገር
ስለሌለ በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል። ገዥው መንግስት ከህግና ከስርዓት ውጪ
በሰላማዊያን ዜጎች፣ በፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ላይ እየወሰደ ያለውን
አፈና፣ ድብደባና እስር እንዲያቆም፤ የህግ የበላይነትን፣ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ
መብቶችን እንዲያከብር አለም አቀፉ ማህበረሰብ ተገቢውን ጫና እንዲያሳድሩ
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ ጥሪውን ያቀርባል። በተለይ
ደግሞ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ይህ ህገወጥና አረመኔያዊ
ድርጊት በዝምታ ሊያልፈው አይገባም፤ ኢህአዴግ በቃህ ሊለው ይግባል።
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ
ህዳር 29 /03 /2007
አዲስ አበባ
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 08, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የዚምባብዌዉ ገዥ ፓርቲ ጉባኤ
የዘጠና አመቱ የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ የዛኑ ፒ.ኤፍ. መሪ ሆነው በድጋሚ ተመርጠዋል። የፕሬዝዳንቱ ባለቤት ግሬስ ሙጋቤም በፓርቲው የሴቶች ክንፍ መሪ በመሆን ወደ ፖለቲካው መቀላቀላቸው ይፋ ሆኗል።
ተቃዉሞ ሠልፍ፤ ድብደባና እስራት በኢትዮጵያ
አሳካሪ-እና ግልፅ ያልሆነ ፖለቲካ።ለአዲስ አበባ በርግጥ እንግዳ አይደለም።ጥንት እንደ ቅዳሜዉ ነበረች።የዛሬ አርባ አመት የጥንት ሥርዓቷ መለወጡ በታወጀ፤ ያለምንም ደም የኢትዮጵያ እንከን እንዲወድም በተዘመረባት ማግስትም በደም ኩሬ ተነከረች።በ1983 ያቺ ጉደኛ ከተማ የሠላም፤ ዲሞክራሲን ጉዞ መጀመሯ ተነግሮባት ሳያበቃ በሌላ ደም ጨቀየች።
በሳምንቱ መጨረሻ የተኪያሄዱ የስፖርት ክንውኖች
በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ ቸልሲ ቅዳሜ ዕለት የመጀመሪያውን ሽንፈት ቀምሷል። በጆሴ ሞሪንሆ የሚመራው ቸልሲን ጉድ ያደረገው በ7ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ኒውካስል ዩናይትድ ነው። በጀርመን ቡንደስ ሊጋ ባየር ሙይንሽን እየመራ ነው፤ ዶርትሙንድ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ተደጋጋሚ ሽንፈት ለምን?
9 ኛዉ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በኢትዮጵያ
ዘጠነኛዉ የኢትዮጵያ ብሄር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንና እና ሕገ መንግሥቱ የፀደቀበት 20ኛ ዓመት ዛሬ በቢኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ርዕሰ ከተማ አሶሳ ላይ መከበሩ ተገለፀ።
በተለያዩ የዩናይትድ ስቴትስ ከተሞች የቀጠለዉ ተቃዉሞ
የዩኤስ አሜሪካ ፖሊስ ያልታጠቀ ጥቁሮች ላይ ያደረሰዉን ግድያ ተከትሎ በዩኤስ አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች የጀመረዉ ተቃዉሞ በሳምንቱ መጨረሻ በበርካታ ከተሞች እጅግ ጎልቶ መታየቱ ተነግሮአል።
የሳምንቱ ትኩስ የስፖርት ወሬዎች
በሲንጋፖር ማራቶን የሴቶቹን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዋጋነሽ አማረ አሸነፈች።
ተስፋዬ ደበሳይ- አንጋፋው ኢህአፓ
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች ‹‹ህገ መንግስቱን በኃይል በመናድ›› ወንጀል ተከሰሱ
በሰላማዊ ሰልፉ ታፍሰው አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ (ሶስተኛ) ታስረው የሚገኙት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ‹‹ህገ መንግስቱን በኃይል በመናድ›› ወንጀል ተከሰው 14 ቀን ተቀጠረባቸው፡፡ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ አቶ አርጫፎ ኤርዳሎ፣ አለሳ መንገሻና ሌሎቹም የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች፣ አባላትና በሰልፉ ላይ የታፈሱ ዜጎች አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው ለታህሳስ 13/2007 ዓ.ም ተቀጥሮባቸዋል፡፡ ችሎቱ በዝግ የታየ […]
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች አባላትና በሰልፉ ላይ የታፈሱ ዜጎች ‹‹ህገ መንግስቱን በኃይል በመናድ›› ወንጀል ተከሰሱ
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች ‹‹ህገ መንግስቱን በኃይል በመናድ›› ወንጀል ተከሰሱ
#Ethiopia #AddisAbebaprotest #EPRDF #Blueparty #Miniliksalsawi
– ‹‹ህገ መንግስቱን ማየት አለብኝ›› ዳኛው
– በርካታ ህዝብ ተገኝቶ የነበር ቢሆንም እንዳይገባ ተከልክሎ ችሎቱ በዝግ ታይቷል፡፡
– የአብዛኛዎቹን ታሳሪዎች ቤት ሊፈትሽ እንደሚችልም ከፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
Minilik Salsawi
በሰላማዊ ሰልፉ ታፍሰው አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ (ሶስተኛ) ታስረው የሚገኙት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ‹‹ህገ መንግስቱን በኃይል በመናድ›› ወንጀል ተከሰው 14 ቀን ተቀጠረባቸው፡፡ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ አቶ አርጫፎ ኤርዳሎ፣ አለሳ መንገሻና ሌሎቹም የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች፣ አባላትና በሰልፉ ላይ የታፈሱ ዜጎች አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው ለታህሳስ 13/2007 ዓ.ም ተቀጥሮባቸዋል፡፡
ችሎቱ በዝግ የታየ ቢሆንም ሶስተኛ ከሚገኙት ሴት ታሳሪዎች ጠይቀን ማረጋገጥ እንደቻልነው ‹‹ሁከት በመፍጠር ህገ መንግስቱንና ህጋዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ እና መንግስት ያልፈቀደው ሰልፍ በመውጣት›› የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ ታሳሪዎቹ በበኩላቸው ‹‹እኛ ህጋዊና ሰላማዊ ታጋዮች ነን፡፡ በህጉ መሰረት ሰልፉን እንደምናደርግ አሳውቀናል፡፡ በመሆኑም የዋስ መብታችን ተከብሮ ልንለቀቅ ይገባል›› ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ አቃቤ ህግ ‹‹ምርመራዬን አልጨረስኩም፡፡ የምሰበስበው ተጨማሪ መረጃ አለ፡፡ መረጃዎችን ይደብቁብኛል፡፡ ሌሎች ተባባሪዎችም አሉ፡፡›› ሲል የጊዜ ቀጠሮ እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ በሌላ በኩል ዳኛው ‹‹ህገ መንግስቱና ሌሎቹም ህጎች ለሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ እንጅ ማስፈቀድ አይጠበቅም የሚሉ ከሆነ ህገ መንግስቱንና ሌሎቹንም ህጎች ማየት አለብኝ፡፡›› ብለው 14 ቀጥረውባቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ ‹‹የምሰበስበው ተጨማሪ መረጃ አለ፡፡›› ባለው መሰረት የአብዛኛዎቹን ታሳሪዎች ቤት ሊፈትሽ እንደሚችልም ከፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከታሳሪዎቹ መካከል 9ኝ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ለየብቻቸው ቅዝቃዜ የበዛበትና ጨለማ ቤት ውስጥ እንደታሰሩ የታወቀ ሲሆን በምርመራ ወቅት ከፍተኛ ድብደባ እየተፈጸመባቸው እንደሆነም አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ ሆኖም ዳኛው የቀረበውን አቤቱታ ትኩረት ሳይሰጡ እንዳለፉት ታሳሪዎቹ ገልጸውልናል፡፡ ታሳሪዎቹ አራዳ ምድብ ችሎት በቀረቡበት ወቅት ችሎቱ በበርካታ የፌደራል ፖሊስ ታጥሮ ታይቷል፡፡ የፍርድ ሂደቱን ለመከታተል በርካታ ህዝብ ተገኝቶ የነበር ቢሆንም እንዳይገባ ተከልክሎ ችሎቱ በዝግ ታይቷል፡፡
ኢህአዴግ የታገለለት የቡድን መብት በተግባር የታለ!? – ድምፃችን ይሰማ
ኢህአዴግ የታገለለት የቡድን መብት በተግባር የታለ!?
ያቀረብነው ‹‹የሃይማኖት ነጻነት ይከበርልን›› ጥያቄ የዜግነትም የቡድንም መብት ቢሆንም ይኸው ሶስት ዓመት ሙሉ ምላሽ ተነፍጎታል!
ሰኞ ህዳር 29/2007
ሃገራችን ኢትዮጵያ ብዙ ብሄር ብሄረሰቦች በጋራ የሚኖሩባት እንደመሆኗ መጠን ህብር የተላበሰ ማህበረሰብን አቅፋለች። በተመሳሳይም ብዝሃ ሃይማኖትን መርህ አርርጋ ሃይማቶችን ከጥንስሱ ጀምሮ ተቀብላ ያስተናገደችም ሃገር ነች። ይሁን እንጂ ብሄር ብሄረሰቦችም ይሁኑ ሃይማኖቶች በሃገሪቱ አስተዳዳሪዎች በእኩል የታዩበት እና እንደዜጋ በተመሳሳይ መልኩ የተዳደሩበት የታሪክ አጋጣሚ አናሳ ነው። ያም ሆኖ ማህበረሰባችን እንደ ህዝብ የሚደርሱበትን የበላይ ተጽዕኖዎች ተቋቁሞ ለዘመናት አብሮ ኖሯል።
የታሪካችን ዳራ የሚያሳየው አብይ መገለጫ ይህን ቢመስልም ቅሉ የነበሩትን የበደል እና ኢ-ፍትሃዊነት ፈተናዎች መቋቋም ሲሳናቸው ለአማራጭ መፍትሄ የተነሱበት አጋጣሚ በርካታ ነው። በሃገራችን በከፍተኛ ህዝብ ቁጥር የሚወከሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ከማህበረ-ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ህይወት በስልት እና በግዳጅ ሲገለሉ ማስተዋል የተለመደ የታሪካችን ገጽታ ነው። ስለዚህም ነው መንግስት ለብሄር ጥያቄም ይሁን የሃይማኖት ነጻነትን ለሚሹ የህብረተሰባችን ክፍሎች ተገቢ ምላሽ መስጠት የሚያሻው። ይህ ባልሆነበት ግን ሁለቱም ቢሆን መብታቸውን ለማስከበር መነሳታቸው አይቀሬ ነው። ይህም በሃገራችን የቅርብ ጊዜ ታሪክ የተስተዋለ እውነታ ነው። ከእነኚህ ተገፊ የህዝብ አካላት መካከል የተወሰኑ ብሄር ብሄረሰቦች እና ሃይማኖታዊ ቡድኖች ቀዳሚዎቹ ሲሆኑ በስርዓተ ጾታ ተጽዕኖ ስር የወደቁ የሃገራችን ሴቶችም ተመሳሳይ መድሎ እና መገለልን አስተናግደዋል።
ይህ ሲባል አንድ የሃገራችን ሴት በሴትነቷ ከሚደርስባት ጫና ባሻገር በምታምንበት ሃይማኖት፣ ብሎም በወከለችው ብሄረሰብ መገለል ምክንያት ድርብርብ ግፍን ልታስተናግድ የምትችልበት እድል ሰፊ ነው። በእርግጥም ከተለመደው የስርዓተ ጾታ ጫና ባለፈ መንግስት በወሰደው የሃይል እርምጃ እና የሒጃብ ማገድ ጸረ-ሴኩላሪዝም ዘመቻ ብዙ ሙስሊም ሴቶች ሰለባ መሆናቸው ቀጥሏል። በአንጻሩም የአንድ እምነት ተከታይ በሃይማኖቱ ሰበብ ከሚደርስበት መገፋት ባለፈ በብሄሩ ምክንያትም ለመገለል የሚዳረግበት አሰራር ለዘመናት ተስተውሏል። በመሆኑም ከብሄራቸው እና ቋንቋቸው ጋር የተዛመደ መድልዎን ሲቃወሙ ከብሄር ጉዳይ ጎን ለጎን የሃይማኖት ነጻነት ጥያቄን አብረው ያነገቡ ቡድኖችን ማግኘት የተለመደ ይሆናል። በብዙዎቹ የሃገራችን ክፍሎች እንደሚስተዋለው የአንድ ብሄር ተወላጆች በአንድም ይሁን በሌላ የታሪክ አጋጣሚ ሙሉ በሙሉ፣ አልያም በአብዛኛው የአንድ ሃይማኖት ተከታይ ሊሆኑ ይችላሉና። የሃገራችን ነባራዊ ገጽታ እንደሚያስረዳው ተገፊ የሆኑ የሃይማኖት እና የብሄር መገለጫዎች በአንድ የህብረተሰብ ክፍል ውስጥ ተነባብረው የመገኘት እድላቸው ሰፊ ነው። ስለሆነም መንግስት የብሄር መብትን ማስከበር የሚችልበት ሁኔታ ሊፈጠር ቢችል እንኳን የሃይማኖት እኩልነትን እስካላረጋገጠ ድረስ እነኚህ የሃገራችን ህዝቦች በበደል አዙሪት ውስጥ ይኖራሉ ማለት ነው። ከዚህ መሰል የበደል ድግግሞሽ ለመላቀቅ ሁለቱንም የቡድን መብቶች ያለምንም መሸራረፍ በህገ-መንግስቱ መርሆች መሰረት ማረጋገጥ ብቸኛ አማራጭ ሆኖ ይታያል።
ይሁን እንጂ የኢህአዴግ መንግስት ‹‹ሴኪውላር (ዓለማዊ) መንግስት በመመስረት አስከብሬዋለሁ›› የሚለውን የሃይማኖት እኩልነት አጀንዳ መልሶ በቀን ብርሃን ሲንደው ተስተውሏል። ‹‹መንግስታዊ ሃላፊነትን ከሃይማኖታዊ ሚና ነጥያለሁ›› ያለው መንግስት በሃይማኖታችን አዛዥ ናዛዥ ከነበሩት ቀደምት ሃይማኖታዊ መንግስታት መሪዎች በምንስ ተለየ? ሌሎች አካላትን ‹‹የአጼውን ስርዓት ናፋቂ›› ሲል የሚያወግዝበትስ አቅም ይኖረዋልን? ለቡድን መብት መከበር የታገለ እና በተግባርም እውን መሆኑን የሚሻ ቢሆን ኖሮ ሙስሊሙን ከሃገራችን ሁለገብ የህይወት ዘርፍ ማግለልን እና ሃይማኖታዊ የቡድን መብቱን በጠራራ ጸሃይ መግፈፍን ጀብዱ አድርጎ ሊቆጥር ባልቻለ ነበር። መንግስት ለቡድን መብት ዘብ በቆመ ኖሮ ባለፉት ሶስት የትግል ዓመታት ላነሳናቸው ህገ መንግስታዊ የእምነት ነጻነት ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ በህጋዊ መንገድ ሊሰጥ በቻለ ነበር። ቀደም ካሉት ዓመታት ጀምሮ የእምነት ተቋሞቻችንን በመቆጣጠር በሃይማኖታችን ላይ የተፈጸመው ደረቅ ጣልቃ ገብነት ከጅምሩ የሃይማኖት እኩልነት ጥያቄን ‹‹ጥያቄ ምልክት ውስጥ›› ባላስገባም ነበር።
ሙስሊሙን የማጥቃቱ ዘመቻ ሙስሊም ሴቶችን እና ወጣት ተማሪዎችን በስመ ሴኩላሪዝም ከትምህርት በማፈናቀል እየተተገበረ ይገኛል። በመሆኑም የኢህአዴግ መንግስት ረጅም ዘመን ትግል ለሃይማኖትም ሆነ ለጾታ እኩልነት ከወሬ ያለፈ ቁርጠኝነት እና ለመርህ ተገዥነት እንዳላሳየ ሙስሊሙ ላነሳቸው የመብት ጥያቄዎች ጆሮ ከመንፈጉ እና ከዚህ ሙስሊም ሴቶችን አነጣጥሮ ከሚያጠቃው መንግስታዊ መድሎ የበለጠ ሁነኛ ማሳያ የለም። በተለይ ደግሞ መንግስት በደነገገው መመሪያ ምክንያት በርካታ እህቶቻችን ጦሳቸውን እያዩበት ያለው ሒጃብ ኢህአዴግ ‹‹እኩልነትን አጎናጸፍኳቸው›› በሚላቸው ብሄሮችም ዘንድ እንደ ባህል መዘውተሩ አንድ እውነታ ነው። እነኚህ ብሄሮች ባህላቸው እና ቋንቋቸው እውቅና ከተቸረው አለባበሳቸውንም በነጻነት ሊተገብሩ የሚችሉበት አጋጣሚ በአመት አንዴ በጭፈራ በሚከበረው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ብቻ ሊሆን አይገባም። የቡድን መብት የሆነው የብሄር እኩልነት እና የሃይማኖት ነጻነት ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ከሚውልበት ከዚህች የአንድ ቀን የሚዲያ ሽፋን ሊያልፍ ይገባል። በዓመት አንዴ የሚደረግ ጭፈራ የእኩልነት ማሳያ እና መለኪያ ፈጽሞ ሊሆን አለመቻሉን መንግስት ራሱ የሚገነዘበው እውነታ ነው። በብሄር ብሄረሰቦች በዓል ላይ ሂጃብ መልበስ መብት እና ባህል ተደርጎ በትምህርት ተቋማት ግን መታገዱ ማን የት ላይ እንዲኖር እንደተሳበ የሚያረጋግጥ ነው፡፡
በዚህ ረገድ መንግስት በ‹‹ልዩ ድጋፍ›› ወደዩኒቨርስቲ አመጣሁ የሚላቸውን የ‹‹ታዳጊ›› ክልል ተወላጅ ሴቶች በአለባበሳቸው ምክንያት ብቻ መልሶ ከዩኒቨርስቲው በሃይል እያባረረ ነው። እውን ታዲያ የታዳጊ ክልሎችን እና በውስጣቸው የሚኖሩ ብሄሮችን የወደፊት እጣ ፈንታ ሊቀይሩ የሚችሉ የተማሩ የሰው ሃይሎችን እያፈናቀሉ ‹‹በልዩ ድጋፍ የክልሎችን ዓቅም ገነባን፣ ሴቶችን አበቃን›› ለማለት ያስደፍራልን? ይህ የመንግስት መድሏዊ አሰራር የሴቶችን፣ ሙስሊሞችን፣ ብሄር ብሄረሰቦችን (ባህሎችን) እና የታዳጊ ክልሎችን ተዋጽዖ የሚፈታተን ከመሆኑም በላይ በየትኛውም መልኩ የቡድን መብት ለብሄሮችም ይሁን ለጾታዎች፣ እንዲሁም ለሃይማኖቶች እንዳልተረጋገጠ የሚያመላክት አብይ ተጨባጭ ነው። በተለይ ይህ እውነታ በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ ጎልቶ የሚታይ መሆኑ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ‹‹የመንግስት የቡድን መብት ማስከበር ሂደት ሆን ተብሎም ይሁን በቸልታ ለምን እኛን አይመለከትም? ለምንስ መድልዎ ይፈጸምብናል?›› የሚል ጥያቄ እንዲያነሱ ይገፋል።
አዎን! የቡድን መብት አስከብራለሁ የሚለው መንግስት ከቃላት ጨዋታ ባለፈ በተግባር የታገዘ መሬት ላይ የሚወርድ መፍትሄ መሻት ግድ ይለዋል። በመርህም ይሁን በአፈጻጸም ረገድ የብሄር እና የእምነት ነጻነትን እና እኩልነትን ማረጋገጥ ያልቻለ መንግስት ህዝብን የማስተዳደር የሞራል ብቃት ሊኖረው አይችልም። በተለይም ለዘመናት ታገልኩለት ለሚለው እና ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ለሚደሰኩርለት የቡድን መብት ጥያቄ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ መፍትሄ ሰጥቶ ለጉዳዩ መቋጫ ያላደረገ መንግስት እንደምንስ ‹‹ለቡድን መብት ታጋይ እና ጠበቃ ነኝ›› ሊል ይቻለዋል!? ለሃገራችን ግማሽ ህዝብ መሰረታዊ የህልውና ጉዳይ የሆነውን የእምነት መብት ገርስሶ ‹‹ለሃይማኖት እኩልነት ሰራሁ›› ቢል ማንስ ይሰማዋል!? ‹‹ንግግርህን እንዳልሰማ ተግባርህ ይጮህብኛል›› እንዲል ብሂሉ ከንግግር በላይ ጮሆ የሚናገረው እና ሰሚ ጆሮ የሚያገኘው ተግባሩ አይደለምን!!? የቡድንም ይሁን የተናጠል መብቶች በቃላት ሽንገላ፣ በአሰልቺ ፕሮፖጋንዳ እና በሚዲያ ልፈፋ ሊመሰረቱ አይችሉም። ይህ ሁሉ መሬት ላይ ጠብ የሚያደርገው ምንም ፋይዳ የለውምና!! ህዝብ በዕለት ተዕለት ህይወቱ ሊያስተውል የሚችለውን እውነተኛ እኩልነት እና የመብት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ይሻል። ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ግን መብትን ከመጠየቅ ይልቅ ከጠባቂነት ተላቆ ወደማስከበር ምዕራፍ ይሸጋገራል። ባለፉት ሶስት ዓመታት የተስተዋለው ህዝባዊ የመብት ማስከበር እንቅስቃሴ የሚያመላክተውም ይህንኑ ነው።
ዛሬ መንግስት ህዝብን ጆሮ ሰጥቶ ሊያደምጥ ግድ የሚልበት ጊዜ ላይ ተደርሷል። ህዝብ በተራ ሽንገላ የሚታለልበት ዘመንም አልፏል። ከሌላው የዓለማችን ክፍሎች በተለየ የሰለጠነ አካሄድ ‹‹መብቴን አላስነጥቅም›› ማለትን መርሁ አድርጓል። ይህ ህዝብ ‹‹መሪዎቹ›› ለዘመናት ታገልንለት ቢሉም በተግባር ግን እውን ላላደረጉለት የቡድን መብትም ይሁን ግለሰባዊ ነጻነቶች መከበር በሰላማዊ መንገድ መትጋቱን ይቀጥላል። ከገባበት ‹‹የመብቴ ይከበር›› ትግልም ምንም አይመልሰውም – የመብቱ በእውን መረጋገጥ ሲቀር!!
ህዝብ መርህን ባማከለ መልኩ እንደሚፈልገው መኖርን እንጂ እንዲኖር በተደረገው መልኩ ማሰብን አይሻም። ላለፉት ሁለት ዓስርት ዓመታት የተሰበከውን ሁሉ ጠንቅቆ ተረድቶ አፍረጥርጦ መጠየቅን እና ‹‹ለምን?›› ማለትን ተለምዶው አድርጎታል። ይህ የህዝብን የብስለት ደረጃ አመላካች ነው። መብት እና ግዴታውን ለይቶ የተረዳ ህዝብን ፈጽሞ እያታለሉ መኖር የማይቻል ሆኗል። አልገዛም ባይነት እና ለጭቆና እምቢተኝነትን በስብዕናው የተላበሰ ዜጋ በግዳጅ አምባገነንነትን ሊጭኑበት አይፈቅድም። ያለው የህግ መርር እንዲተገበር በህጋዊ መንገድ መጠየቁም አይቀሬ ነው፤ ማስተካከል የማይችል የስልጣን ጥመኛ ሲገጥመው ግን መብት እና ፍላጎቱን የሚያሟላበትን እና የሚያሟላለትን አማራጭ ለመፈለግ ይገደዳልና።
በእውን የቡድን መብት መከበሩን ማረጋገጥ ካስፈለገ በማህበረ-ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ፣ እንዲሁም ሌሎች ተቋማዊ አሰራሮች የሁሉንም አቻ ተሳታፊነት በተግባር ማሳየት የግድ ነው። በማህበራዊ ግልጋሎት ተደራሽ ያልሆነን፣ በልማት ፖሊሲ ያልታቀፈን፣ በአግላይ ፖሊሲ የተገፋን፣ በህግ ስርዓቱ ተበዳይ የተደረገን አንኳር የህዝብ ክፍል ይዞ ‹‹የብሄሮችን እኩልነት አረጋገጥኩ›› ብሎ በየዓመቱ መዘመር የብሄሮች እና የሃይማኖቶች እኩልነትን ከወረቀት ባለፈ ሊያረጋግጥልን አይችልም። በማደግ ላይ ባለች ሃገር ውስጥ ‹‹ታዳጊ›› የሚባሉ በርካታ ክልሎች እና ብሄረሰቦች ባሉበት ሁነት የብሄሮች እኩልነትን መረጋገጥ የሚያሳይ ተጨባጭ አስረጂም አይገኝም። በተለይ ደግሞ እነኚህ ክልሎች እና ብሄሮች በብዛት የአንድ ሃይማኖት ተከታዮች መሆናቸው ግምት ውስጥ ሲገባ እና በሌሎች ክልሎች እንደሚገኙት የእምነት ወንድሞቻቸው ሁሉ እነሱም በእምነታቸው ምክንያት በደል እና የሃይማኖት መብት ጥሰት ማስተናገዳቸው የሃይማኖት እኩልነትም እንዳልተረጋገጠ በቂ ማሳያ ነው።በመሆኑም እውነተኛ ፍትህ እና እኩልነት የሰፈነበት ሁለንተናዊ ህይወት በሃገራችን ላሉት ሁሉም ብሄሮች እና ብሄረሰቦች፣ እንዲሁም እምነቶች (ሃይማኖቶች) እንዲረጋገጥ ማድረግ ለነገ የማይባል አጣዳፊ የመንግስት ግዴታ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።
መንግስት ወደራሱ ዞር ብሎ የሚናገረውን እና የሚፈጽመውን ተዛምዷዊነት ፈትሾ በግልጽ ተግባሩን እንደ ቃሉ ማድረግ መጀመር ይጠበቅበታል፡፡ ይህን ካልፈቀደ ደግሞ ህዝብን ተግባር አልባ በሆነ ጮሌ ምላስ ለመሸንገል መታገሉን ትቶ በአዋጅ የመንግስት ፖለቲካዊ ማዕዘናትና እኩልነት ጽንሰ ሐሳቦች መፍረሳቸውን ሊያውጅ ይገባል!! ያኔ ህዝብም የ‹‹ህግ ይከበርልን›› ጥያቄውን ፍትህ እስኪሰፍን እና መብቱ እስኪከበርለት በቁርጠኝነት ይገፋበታል፤ አልያም ‹‹ፈጽሞውኑ ህግ የለም!›› ሲል ስለ ህጋዊነት ይሰብካል!!
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

አርቲስት ይግረም ደጀኔ
በበርካታ አጫጭር እና ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች ላይ በትወና ተሳትፏል። በተለይ በቅርቡ በቴሌቪዥን በተላለፈው የ«ሰው ለሰው» ተከታታይ ድራማ እና አሁን በመታየት ባለው «ሞጋቾቹ» ድራማ ይታወቃል። መንፈሣዊ ዜማዎቹም በኢንተርኔት እና በሲዲ ተሰራጭተዋል።
ምንም ያህል ልዩነት ቢኖረው የአንድን አገር ህዝብ የማይለወጠው የጋራ ማንነቱ ዜግነቱ ነው፡፡ – ከምኒሊክ ሳልሳዊ
የአንድ ‹‹ህዝብ›› የእምነት፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ… መብቱ በግለሰብ ደረጃ ካልተጠበቀለት በስተቀር የ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ…›› መብት ሊጠበቅ አይችልም፡፡ ችግሩ የ‹‹ብሄርና›› ሌሎች ማንነቶችን የሚጠቀሙ የፖለቲካ ቡድኖች ከግለሰብ ማንነት ይልቅ ጥቅል ማንነትን የሚያስቀድሙት ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ መሆኑ ነው፡፡ ከፊሉን በእምነቱ፣ ከፊሉን በኢኮኖሚው፣ ከፊሉን እናከብርልሃለን በሚሉት ቋንቋው፣ ከፊሉን በነጻነቱ…. እያሉ ግን ሁሉንም ይጨቁኑታል፡፡ ሁሉንም ይጎዱታል፡፡ መስፈርቱ በብሄር ሳይሆን በግለሰብ ቢሆን […]
የግለሰብ መብት ካልተከበረ የብሄር ብሄረሰቦች መብት ሊከበር አይችልም::
ምንም ያህል ልዩነት ቢኖረው የአንድን አገር ህዝብ የማይለወጠው የጋራ ማንነቱ ዜግነቱ ነው፡፡
Minilik Salsawi
የአንድ ‹‹ህዝብ›› የእምነት፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ…መብቱ በግለሰብ ደረጃ ካልተጠበቀለት በስተቀር የ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ…›› መብት ሊጠበቅ አይችልም፡፡ ችግሩ የ‹‹ብሄርና›› ሌሎች ማንነቶችን የሚጠቀሙ የፖለቲካ ቡድኖች ከግለሰብ ማንነት ይልቅ ጥቅል ማንነትን የሚያስቀድሙት ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ መሆኑ ነው፡፡ ከፊሉን በእምነቱ፣ ከፊሉን በኢኮኖሚው፣ ከፊሉን እናከብርልሃለን በሚሉት ቋንቋው፣ ከፊሉን በነጻነቱ…. እያሉ ግን ሁሉንም ይጨቁኑታል፡፡ ሁሉንም ይጎዱታል፡፡ መስፈርቱ በብሄር ሳይሆን በግለሰብ ቢሆን ግን የሚድበሰበስ ነገር አይኖርም፡፡….. የአንድን አገር ህዝብ የማይለወጠው የጋራ ማንነቱ ዜግነቱ ነው፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የግለሰቦች ጥርቅም እስከሆኑ ድረስ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ ጽንፈኛ፣ አሸባሪ፣ ኪራይ ሰብሳቢ፣ ተላላኪ፣ ኒዮ ሌንራል፣…….የሚባሉት መለጠፊያዎች እየተሰጧቸው አሳራቸውን የሚበሉት ‹‹ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› ናቸው፡፡
ምንም ያህል ልዩነት ቢኖረው የአንድን አገር ህዝብ የማይለወጠው የጋራ ማንነቱ ዜግነቱ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ከሌሎች ህዝቦች ይልቅ የሚያመሳስሉን፣ የምንጋራቸው በርካታ እሴቶች አሉን፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያውይነታችን (ዜግነታች) የጋራችን ነው፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰብ፣ ህዝብ ተብሎ በጅምላ ዜግነት ሊሰጠው አይችልም፡፡ አንድ ሰው ኢትዮጵያዊ ለመሆን መደራጀት አይጠበቅበትም፡፡
በሚሊዮን የሚቆጠሩ ግለሰብ ኦሮምኛ ተናጋሪዎችን ‹‹ኦሮሞ››፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩትን ግለሰብ አማርኛ ተናጋሪዎች ‹‹አማራ››፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ግለሰብ ሶማልኛ ተናጋሪዎን ‹‹ሶማሊ››…….እያሉ ነው ኢትዮጵያውያንን ‹‹ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› በሚል አዲስ ማምነት የሚደረድሩን፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰብ፣ ህዝብ የሚባለው ከግለሰቦች እንጅ ከምንም የመጣ አይደለም፡፡ የብሄር ብሄረሰቦች መብት መከበር ካለበት መጀመሪያ መቅደም የሚገባው የስሪታቸው የግለሰቡ መብት ነው፡፡
ኦሮሞ፣ አማራ፣ትግሬ….› እየተባሉ የተቦደኑት ህዝቦች አንድ አይነት አይደሉም፡፡ እንዲያውም ኦሮምኛ ተናጋሪው ‹‹ኦሮሞ›› ከሚባለው ውጭ ከአማርኛ ተናጋሪው ጋር የሚጋራው በርካታ ማንነቶች ይኖሩታል፡፡ አማርኛ ተናጋሪው ‹‹አማራ›› ከተባለው ይልቅ ከኦሮምኛ ተናጋሪው ጋር የሚያመሳስሉት በርካታ ማንነቶች ይኖሩታል፡፡ ለአብነት ያህል ትግርኛ፣ አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ሶማሊኛ፣ ….ተናጋሪው ህዝብ ከቋንቋውም በላይ አንዱ የሌላውን ድንበር ተሸግሮ ከሌላኛው ቋንቋ ተናጋሪ ጋር በእምነት፣ በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ሌሎች ገመዶች ይገናኛል፡፡ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የአንድ ብሄር ሰዎች አይደሉም፡፡ የሙስሊሙ እንቅስቃሴ እንዲህ እስካሁን በጥንካሬ የዘለቀው በድንበር ተሸጋሪው ማንነቱ እንጅ በጠባብ ‹‹የብሄር›› ማንነት ታጥሮ አይደለም፡፡ ኦርቶዶክሶቹ፣ ፕሮቴስታንቶቹ፣ ካቶሊኮቹ በ‹‹ብሄር›› የታጠሩ አይደሉም፡፡
የአንድ ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ…›› የእምነት፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ…መብቱ በግለሰብ ደረጃ ካልተጠበቀለት በስተቀር የ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ…›› መብት ሊጠበቅ አይችልም፡፡ ችግሩ የ‹‹ብሄርና›› ሌሎች ማንነቶችን የሚጠቀሙ የፖለቲካ ቡድኖች ከግለሰብ ማንነት ይልቅ ጥቅል ማንነትን የሚያስቀድሙት ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ መሆኑ ነው፡፡ በ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ሶማሊ…….›› ስም በጅምላ ከመነገድ ያለፈ ስለ እያንዳንዱ ህዝብ አያስጨንቀቃቸውም፡፡ 30 ወይንም 40 ሚሊዮን የአንድ ‹‹ብሄር›› ህዝብ በአንድ ጉዳይ ሊከፋ አይችልም፡፡ ቢያንስ ከገዥዎች ጋር ሆኖ የሚጠቀም አይጠፋም፡፡
ከፊሉን በእምነቱ፣ ከፊሉን በኢኮኖሚው፣ ከፊሉን እናከብርልሃለን በሚሉት ቋንቋው፣ ከፊሉን በነጻነቱ…. እያሉ ግን ሁሉንም ይጨቁኑታል፡፡ ሁሉንም ይጎዱታል፡፡ መስፈርቱ በብሄር ሳይሆን በግለሰብ ቢሆን ግን የሚድበሰበስ ነገር አይኖርም፡፡ ሁሉም የግለሰብ መብቶች እስከተከበሩ ድረስ የአገሪቱ ህዝብ መብት ይከበራል፡፡ የግለሰብ መብት ካልተከበረ ግን የማንም መብት ሊከበር አይችልም፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የግለሰቦች ጥርቅም እስከሆኑ ድረስ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ ጽንፈኛ፣ አሸባሪ፣ ኪራይ ሰብሳቢ፣ ተላላኪ፣ ኒዮ ሌንራል፣…….የሚባሉት መለጠፊያዎች እየተሰጧቸው አሳራቸውን የሚበሉት ‹‹ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› ናቸው፡
ዘመነ መሳፍንትና የፖለቲካ መሪዎቻችን የወረሱት ቅርስ አንዱዓለም ተፈራ
በዘመነ መሳፍንት ወቅት፤ ለስሙ በዙፋኑ ላይ የዘር ግንድ ያለውን ሰው አስቀምጠው፤ ራሳቸውን እንደራሴ በመሾም፤ ጉልበተኞች ያደረጉት ሁሉ ግልጽ ነው። የውጭ ሀገር መንግሥታት ደግሞ በወኪሎቻቸው አማካኝነት ፀረ-ኢትዮጵያ ሚና ተጫወቱ። በደንብ በዝርዝር የሚያስረዳ መዝገብ ግን አላገኘሁም። ከዚህም ከዚያም ለቃቅሜ የተገነዘብኩትን ይዣለሁ። የእስክንድርያውን የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን በመጠቀም፤ ግብፅና ቱርክ በአንድ በኩል፣ በፖርቹጋሎች የተጀመረውን ግንኙነት በመጠቀም፤ የካቶሊክ ቤተክርስትያን በሌላ በኩል፣ […]
የአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የተወሰደውን የሀይል እርምጃ እንደሚያወግዙ ገለፁ!! ምርጫ 2007 የኢህአዴግ መጨረሻ ወይስ የመጨረሻው መጀ መሪያ››በሚል ርዕስ የክርክር መድረክ ተካሔደ!!
በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት እየተካሔደ በሚገኘው የክርክር መድረክ ላይ ተሳታፊ የሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በትላንትናው እለት የ9ኙ ፓርቲዎች ህብረት የጠራውን የ24 ሰዓት ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ የመንግስት ሀይሎች የወሰዱትን ኢ-ህገመንግስታዊ እርምጃ አጥብቀው እንደሚያወግዙ ገልፀዋል፡፡ በአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ‹‹ምርጫ 2007 የኢህአዴግ መጨረሻ ወይስ የመጨረሻው መጀሪያ››በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ክርክር በትዝጋጅው ፕሮግራም መሰረት ተካሂዱዋል፡፡ […]
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 07, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
ብርሀነ መስቀል ረዳን በጨረፍታ
![]() |
| Berhane Mesqel Redda |
የስልጣን ሽግሽግ ለሙጋቤ ተከታይ
የፕሬዚዳንት ሙጋቤ ባለቤት የዚምባቡዌ ቀጣይ የሀገር አስተዳዳሪ ለመሆን ራሳቸውን እጩ እስከመሆን አበቁ። ቀዳማዊት እመቤት ግሬስ ሙጋቤን የገዢው ዛኑ ፒ ኤፍ ፓርቲ ሀራሬ ውስጥ ባካሄደው ስብሰባ የ49 ዓመቷን ወ/ሮ ከሴቶች ክፍል ተጠሪ አድርጎ ሰይሟል። ወይዘሮ ግሬስ አንዱን ቀን የሀገሪቷ ፕሬዚዳንት መሆን እንደሚሹም አመላክተዋል።
የስልጣን ሽግግር ለሙጋቤ ተከታይ
የፕሬዚዳንት ሙጋቤ ባለቤት የዚምባቡዌ ቀጣይ የሀገር አስተዳዳሪ ለመሆን ራሳቸውን እጩ እስከመሆን አበቁ። ቀዳማዊት እመቤት ግሬስ ሙጋቤን የገዢው ዛኑ ፒ ኤፍ ፓርቲ ሀራሬ ውስጥ ባካሄደው ስብሰባ የ49 ዓመቷን ወ/ሮ ከሴቶች ክፍል ተጠሪ አድርጎ ሰይሟል። ወይዘሮ ግሬስ አንዱን ቀን የሀገሪቷ ፕሬዚዳንት መሆን እንደሚሹም አመላክተዋል።
በአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ትግላችን አይቆምም! የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ባለፈው አንድ ወር ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል መርሃ ግብር ቀርጸን ስንቀሳቀስ ዋናው አላማችን የስርዓቱን አረመኔያዊነት ለህዝብ በማጋለጥ የኢትዮጵያ ህዝብ በትግሉ እንዲሳተፍ ማድረግ ነው፡፡ እንደጠበቅነው ገና ከጅምሩ የህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ትግላችንን በጭካኔ ለማስቆም ጥሯል፡፡ ህዳር 7/2007 ዓ.ም የመጀመሪውን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በጠራንበት ወቅት ስብሰባውን በኃይል በትኗል፡፡
ትብብራችን ከመቸውም ጊዜ በላይ ያሰጋው ህወሓት/ኢህአዴግ በተለይ የህዳር 27/28 2007 ዓ.ም የአደባባይ አዳር ሰልፍን እንዳይካሄድ የትብብሩን አመራሮችና አባላቶቻችን በማዋከብ፣ በመደብደብና በማሰር ተጠምዶ ሰንብቷል፡፡ በተለይ በትናንትናው ዕለት ሰልፍ በወጣንበት ወቅት ስርዓቱ አመራሮችንን፣ አባላቶቻችንን፣ ተሳታፊዎችንን እንዲሁም አልፎ ተርፎ መንገደኛውን ህዝብ በጭካኔ ደብድቧል፡፡ አፍሶ አስሯል፡፡ ሙስሊም እህትና ወንድሞቻችን በየጎዳናው ታፍሰው የአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ሰለባዎች ሆነዋል፡፡ በርካቶችም በእ
በየ እስር ቤቶቹ ታጉረዋል፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ከ300 በላይ የትብብሩ አመራሮችና አባላት የታሰሩ ሲሆን የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ድርሶባቸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆነው አቤል ኤፍሬም ራሱን እስኪስት ተደብድቧል፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ የተገኙ ሴት አመራርና አባላት አንድ አገርን እየመራሁ ነው ከሚል አካል በማይጠበቅ መንገድ በጭካኔ ተደብድዋል፡፡ እነዚህ በጭካኔ የተደበደቡ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ህክምና እንዳያገኙ ተከልክለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በጥበቃ ሰራተኝነት የሚሰሩ የ72 አመቱ አቶ ቀኖ አባጆቢር ከስራ ሲወጡ በደህንነት ኃይሎች ታፍነው የተወሰዱና እስካሁን የት እንደደረሱ ያልታወቀ ሲሆን ይህም አገዛዙ የመጨረሻው የአረመኔነት ደረጃ ላይ እንደደረሰና ይህን የስርዓቱ ውንብድና ለማስቆም ጊዜ የማይሰጠው ተግባር መሆኑን በግልጽ የተገነዘብንበት ነው፡፡
አገዛዙ በትናንትናው ዕለት በፍጹም ሰላማዊ ሰዎች ላይ የወሰደው የውንብድና እና አረመኔያዊ እርምጃ በትግሉ ውስጥ የምንጠብቀውና ስርዓቱ ለኢትዮጵያ የማይበጅ መሆኑን ዳግመኛ ያያ
ረጋገጠበት ነው፡፡ የትናንትናው ትላችን አገዛዙ ለይስሙላ እከተለዋለሁ ከሚለው ‹‹ህጋዊ ሰርዓት›› ይልቅ ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ቆርጦ መነሳቱን እና በህገ መንግስት ስም ህዝብን የሚበድልበትን የአረመኔያዊነት ጭንብል ገልጠን ለዓለም ያሳየንበት የትግላችን ውጤት ነው፡፡
አገዛዙ ላላፉት 24 አመታት ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ሲጥር ቆይቷል፡፡ በትናንትናው ዕለት የፈጸመው ፍጹም አረመኔያዊ እርምጃም እንደተለመደው ሰላማዊ ታጋዮችን ያሸማቅቃል ብሎ አስቦ እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የአገዛዙ አረመኔያዊነት ከሰላማዊነታችን ፍጹም ወደኋላ ሊያንሸራትተን አይችልም፡፡ ወደ ትግል ስንገባ የስርዓቱን ጭካኔና ለኢትዮጵያ የ
ማይመጥን መሆኑን አውቀንና የሚያስከፍለውን መስዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተንም ነው፡፡ አሁንም አገዛዙ የህዝብን ድምጽ በማፈን ስልጣኑን ለማስጠበቅ ተመሳሳይ እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን፡፡ ነገር ግን መጀመሪያውንም ትግሉን ስንቀላቀል አስበን የገባነው እየቆሰልን፣ እየታሰርንም፣ እየሞትንም ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ ለመሆን ነውና ከትግላችን ቅንጣት ሊያደናቅፈን አይችልም፡፡ ስለሆነም ወደፊትም ይህን የአገዛዙን አረመኔያዊነት በማጋለጥና ህዝቡን በትግሉ በማሳተፍ ለኢትዮጵያ የሚገባት ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመመስረት በቀጣይነትም ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን፡፡
በዚህ አጋጣሚ ሰላማዊ ሰልፉን ለማሳካት እንዲሁም የህወሓት/ኢህአዴግ ቡድን የፈጸመውን ጭካኔ በማውገዝ ከጎናችን ለቆማችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡ ከህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ጋር የሚደረገው ትግል እልህ አስጨራሽ፣ ከፍተኛ መስዋዕትነት የሚያስከፍልና የእያንንዳንዳችን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ተገንዝበን ሁላችንም በጋራ እንድንቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን
ያለ መስዋዕትነት ድል የለም፡፡
የምርጫ ስትራቴጂ እንዴት ይሁን? ግርማ ሠይፉ ማሩ
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ዋለልኝ መኮንን-አፈና ያልገታው የአመጽ ድምጽ
![]() |
| Walelign Mekoneen |
Registration for condominium homes for Ethiopian diaspora will start next week በውጪ ሃገራት ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የማህበራት ቤቶች ምዝገባ በቀጣዩ ሳምንት ይጀመራል
9ኙ ፓርቲዎች በጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ በፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ ደረሰባቸው፤ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት የታፈሱት አመራሮች ማዕከላዊ አጠገብ ወደሚገኘው እስር ቤት ተዛወሩ!
9ኙ ፓርቲዎች በጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ በፓርቲ አመራሮች እና የሰልፉ ተሳታፊዎች በፌዴራል ፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው ሲሆን በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የታፈሱትና ጨርቆስ ፖፖላሬ እስር ቤት ታስረው የነበሩት የፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና የሰላማዊ ሰልፍ ተሳታፊዎች ማዕካለዊ ጥግ ወደሚገኘውና በተለምዶ ሶስተኛ ተብሎ ወደሚጠራው እስር ቤት መዛወራቸው ታወቀ፡፡ ታሳሪዎቹ ከጨርቆስ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ሶስተኛ የተዛወሩት ከምሽቱ አንድ ሰዓት በኋላ ሲሆን […]
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 06, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የባርነት ስርዓት በሞሪታንያ
በይፋ ለሦስት ጊዜያት እንደተገረሰሰ ቢነገርም፥ ዛሬም ቢሆን በሞሪታንያ የባርነት ስርዓት ጭቆና አልተወገደም። የዕድሜያቸውን እኩሌታ በባርነት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አንድ ሞሪታኒያዊ ትውስታቸውን ያካፍላሉ። በመካከለኛው አፍሪቃ ሪፐብሊክ የሰፈረው የፈረንሣይ ጦር ሠላም ማስፈን ተስኖታል እየተባለ ነው።
ያስጠበቡኝ ጠባብ የኦሮሞ ልሂቃንና ያስጠበበኝ አመለካከታቸው
(በአማን ነጸረ) ባለፈው ጽሑፍ እንዳመለከትኩት፡- ሁለት ጽንፍ የያዙ ኃይላት ያገሪቱን የፖለቲካ መድረክ ተቆጣጠረዋል–ያንድነት ኃይላት ነን ባዮችና ብሔረሰባውያን፡፡ የየራሳቸው በጎ ጎን እና መነሻ እንዳላቸው የምረዳ ቢሆንም በጎ በጎውን ላቆየውና የሚያሥከፋኝን ልናገር፡፡ (ባለፈው ጽሑፍ ስለአማራ ልሂቃንና አስተሳሰባቸው ያወሳሁ ሲሆን አሁን ደግሞ የኦሮሞ ልሂቃንን እቃኛለሁ፡፡ 1– ያለፈው ሥርዓት የሕዝብ ለሕዝብ ማኅበራዊ ገጽታ የሌለው ይመስል ስለጭቆና ዘላለም እያወሩ ፖለቲካውን ብቻ ማጮኽ ርካሽነት ነው!!በፖለቲካውም ቢሆን የኃይለሥላሴን ከፊል-ፊውዳል ሥርዓት በመታገል ረገድ እንደ ልሂቅም፤እንደ ማኅበረሰብም በግልና በነጠላ የሰሜኑ ክፍል ያደረገው ጥረት ከኦሮሚያው ያነሰ አይመስለኝም፡፡ትረካው ቢስተካከል!! 2— “ለእኛ እስከተመቸን ድረስ ሌላው ስለ እኛ ፖሊሲ አያገባውም” የሚል አስበርጋጊና በተለይ ሀቀኛ የኦሮሞ ትግልን ሳይቀር ሌላው ማኅበረሰብ በጥርጣሬ እንዲመለከት ማድረግ ለሌላው ስሜት አለመጨነቅ ነው–ራስ ወዳድነት!!ቢቻል ትግላችን ጭቆናውን ለሚያለባብሰው ልሂቅ የሚተርፍ እንዲሆን መስራት፣ካልሆነም መብታችን ላይ የቆመውን ልሂቅ ነጥሎ ብቻውን ማስቀረት ሲቻል በልሂቁ ሰበብ ሕዝብ ማስቀየም ማንንም አይጠቅምም!!መጀመል ይቅር!! 3– ምኒልክ በሰላም እጅ ያልሰጠውን የኦሮሞ ክፍል በኃይል ማስገበሩ ባይካድም በሂደቱ በተፈጠው አብሮነት አድዋ ላይ የውጭ ወራን በጋራ መመከታችንና በዚህም ዛሬ ማንኛውም የኦሮሞ ተወላጅ የትም አገር ቀና ብሎ እየሄደ፣በግንኙነቱ እንደ ነጭና ጥቁር የልዩነት አጥር ሰርተን ሳይሆን በማ/ሰብ ደረጃ እንደ ማንኛውም ኢ/ዊ ርስ በርስ ከመሳፍንቱ ሳይቀር ተጋብተን ተዋደን መኖራችን እየታወቀ፣“የኢ/ያ ታሪክ የ100 አመት ነው” የሚለውን ትረካ በበኩሌ በፍጹም ባልቀበለውም እሱም ቢሆን የጋራ ማንነት ለመገንባት ከበቂ በላይ መሆኑን ባለማስተዋል፣ምኒልክ ሲዘምቱ በአከባቢያዊ ገዥዎች ቅርምት የተያዘች እንጅ አንድ […]
የብሔር ብሔረሰቦች ቀን፣ ዋለልኝ መኮንንና የከሸፈው ፕሮጀክት
(በፍቃዱ ወ/ገብርኤል) የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ቀን ሲከበር ዘጠነኛ አመቱን የያዘ ሲሆን በአገረ አሜሪካም ለመጀመሪያ ጊዜ በኮሎምበስ ኦሃዮ ይከበራል። የብሄር ብሄረሰቦች ቀን የሚከበርበት ዋና ዓላማ ለዘመናት ተጨቁነውና ተመዝብረው፤ ተንቀውና ተገልለው በሁለተኛና ሶስተኛ የዜግነት ደረጃ ይታዩ የነበሩትን ብሄር ብሄረሰቦች መብትና ነጻነት ያረጋገጠውን የፌደራል ስርአት ለመዘከርና አጽናኦት ለመስጠት ሲሆን በዚህም በአል ብሄር ብሄረሰቦች በተወካዮቻቸው አማካይነት ራሳቸውን የሚያስተዋውቁበትና ከሌሎች የሚተዋወቁበት፤ ልምዳቸውንና አገራዊ ጉዳዮችን የሚወያዩበት፤ የጋራ እምነታቸውንና ተስፋቸውን የሚጋሩበት የአንድነታቸው የደስታ መግለጫ መድረክ ነው። የኢትዮጵያ ፌደራል ስርአት የህዝቦችን እኩልነት ያረጋገጠና ላለፉት ሁለት አስርተ አመታት ለአገሪቱ አንድነት ሰላም መረጋጋትና እድገት መሰረት የጣለ አዲስ ግኝት ነው። ይህ ህያውና አዳጊ ተመንዳጊ የሆነ የአንድነት መሰረት ዛሬ ኢትዮጵያ በጽናት እንድትቆም ያስቻላት ብቻ ሳይሆን በምታደርገው ፈጣንና ሁለገብ የዕድገት ጎዳና ጉዞ ከምትራመድበት ሁለት እግሮችዋ መካከል የመጀመሪያው ነው። እንደሚታወቀው ሁለተኛው ደግሞ የምትመራበት የልማታዊ መንግስት መርሃ ግብር ነው። የብሄር ብሄረሰብች ቀን ሲታሰብና ሲዘከር የዛሬዋ ኢትዮጵያ የመንፈስና የነፍስ አባት (Founding Father) ከሆነው ከታጋዩ ከመለስ ዜናዊ ጋር ስሙ ሳይጠቅስ የማይታለፈው ዋልልኝ መኮንን ነው። የብሄር ብሄረሰቦች የመብትና የእኩልነትን ጥያቄ በአደባባይ በማስተጋባት የአደባባይ ምስጢርንቱ ተገፎ በኢትዮጵያ የፖሊቲካ መድረክ የመሃል መስመር ስፍራ (main stream politics) እንድሆን ካበቁት ስመ-ጥር የመላው ኢትዮጵያ ህዝቦች ልጆች መሃል ዋለልኝ መኮንን አንዱ ነው። ዋለልኝ መኮንንን የተለየ ቦታ እንዲሰጠው የሚያደረገው የንጉሱን ስርአት ጸረ-ህዝብነትና በህዝቦች ላይ የተጫነውን ‘fake’ የ”ኢትዮጵያዊንትን” ጭንብል በዛ በጭለማ ዘመን በሰላ ብዕሩ በአደባባይ ማራቆቱ […]





