ተቃዉሞ ሠልፍ፤ ድብደባና እስራት በኢትዮጵያ

አሳካሪ-እና ግልፅ ያልሆነ ፖለቲካ።ለአዲስ አበባ በርግጥ እንግዳ አይደለም።ጥንት እንደ ቅዳሜዉ ነበረች።የዛሬ አርባ አመት የጥንት ሥርዓቷ መለወጡ በታወጀ፤ ያለምንም ደም የኢትዮጵያ እንከን እንዲወድም በተዘመረባት ማግስትም በደም ኩሬ ተነከረች።በ1983 ያቺ ጉደኛ ከተማ የሠላም፤ ዲሞክራሲን ጉዞ መጀመሯ ተነግሮባት ሳያበቃ በሌላ ደም ጨቀየች።