የአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የተወሰደውን የሀይል እርምጃ እንደሚያወግዙ ገለፁ!! ምርጫ 2007 የኢህአዴግ መጨረሻ ወይስ የመጨረሻው መጀ መሪያ››በሚል ርዕስ የክርክር መድረክ ተካሔደ!!
በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት እየተካሔደ በሚገኘው የክርክር መድረክ ላይ ተሳታፊ የሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በትላንትናው እለት የ9ኙ ፓርቲዎች ህብረት የጠራውን የ24 ሰዓት ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ የመንግስት ሀይሎች የወሰዱትን ኢ-ህገመንግስታዊ እርምጃ አጥብቀው እንደሚያወግዙ ገልፀዋል፡፡
በአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ‹‹ምርጫ 2007 የኢህአዴግ መጨረሻ ወይስ የመጨረሻው መጀሪያ››በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ክርክር በትዝጋጅው ፕሮግራም መሰረት ተካሂዱዋል፡፡ በክርክሩ ወጣት ጋዜጠኛ ስለሺ ሀጎስ ‹‹ምርጫ 2007 የኢህአዴግ መጨረሻ ››መሆን አለበት በሚል መከራከሪያ ሀሳቡን ያቀረበ ሲሆን የአንድነት ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ሀላፊ ወጣት እንግዳ ወ/ጻዲቅ በበኩሉ ‹‹2007 ለኢህአዴግ የመጨረሻው መጀመሪያ ››መሆን አለበት በሚል ሀሳቡን አቅርቧል ፡፡ሁለቱም ተከራካሪዎች የክርክር ሀሳባቸውን ካቀረቡ በኋላ ከተሳታፊዎች የቀረቡላቸውን ጥያቄዎች አብራርተዋል፡፡ስለ ክርክሩ ዓላማና አስፈላጊነት የአንድነት ፓርቲን የህዝብ ግንኙነት ተጠባባቂ ሀላፊን ጠይቀን በሰጡን ምላሽ መሰረት፤ በፓርቲውና በህዝቡ መካከል የበለጠ መቀራረብ ለመፍጠርና በ2007 ግንቦት ለሚካሄደው ምርጫ ለምዳርገው ዘመቻ ህዝቡ በባለቤትነት የበኩሉን እንዲወጣ ለማድረግ እንደ ድልድይነት እንደሚጠቅምና በቀጣይ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ታላቅ ከተሞች በሀገሪቱ የሚገኙ ምሁራንን ያሳተፈና ህዝብ የሚሳተፍባቸው የክርክር መድረኮች እንደሚደረጉና ምርጫውን ህዝቡ በባለቤትነት እንዲቆጣጠረው ለማድረግ እንሰራለን››ብለዋል ፡፡
የክርክር ፕሮግራሙ በካናዳና በሰሜን አሜሪካ ለሚገኙ ፓልቶኮች በቀጥታ ስርጭት እንደተላለፈ እና በቀጣይ የሚደረጉ ክርክሮች በሀገር ውስጥ የሚገኙ ዜጎች የሚከታተሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡


