Tag: ethiopian news in amharic
የኢትዮጵያ መንግሥት ገመና (ተመስገን ደሳለኝ – ከዝዋይ እስር ቤት)

መሐሙድ የሱፍ የተወለደው በ1980ዓ.ም ከሶማሌ ክልል ርእሰ-መዲና ጅጅጋ 500 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውዶሀን ከተማ ነው፡፡ ለቤተሰቡ ሰባተኛ ልጅ ሲሆን፤ አምስት እህቶችእና ሦስት ወንድሞች አሉት፡፡ በጅጅጋ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ መዝለቁቢሳካለትም፤ ከዚህ በላይ ግን ሊቀጥል አልተቻለውም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኢትዮጵያመንግስት የደህንነት ሠራተኞች የ1999ዓ.ም የግንቦት ሃያ በዓል በጅጅጋ ከተማ ስታዲዬም በተከበረበት ዕለት፣ የኦጋዴን ነፃአውጪ ግንባር (ኦብነግ) በሰነዘረው የቦንብ ጥቃት ተሳትፈሃል በሚል ለእስር በመዳረጉነው፡፡ ይህንን ተከትሎምከምድራችን አስከፊ ማሰቃያዎች መካከል ግንባር ቀደም በሆነውና የክልሉ
ነዋሪ “ጄል-አዳብ” (የገሃነም እስር ቤት) እያለ በሚጠራው ማጎሪያ ውስጥ እጅግ በጣም የከፋ ምድራዊ መከራ እንደተቀበለሀዘን በተጫነው ድምፅ ይናገራል፡፡ በሠውነቱ የተለያዩ ክፍሎች ላይ እንደ ፍም ቀልተው የሚታዩት ጠባሳዎቹም ያሳለፈውንሥቃይ አፍ አውጥተው ይመሰክራሉ፡፡ ለአራት ወራት ያህል አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻው ተቆልፎበት፤ ሃያ አራት ሠዓታትሙሉ እጆቹ በካቴና ተቀፍድደው፣በቀን ከአምስት ጊዜ በላይ ለምርመራ እየተጠራ ያለዕረፍት ከባድ ስቅየት (ቶርቸር)ሲፈፀምበት ቆይቷል:፡ በመጨረሻም ለአንዲትም ቀን የፍርድ ቤት ደጅ ሳይረግጥ፣ ለኦብነግ አባላት አንድ ፓኬት ሲጋራሲያቀብል እጀ-ከፈንጅ ተይዟል በሚል ክስ የጅጅጋ ዞን ፍርድ ቤት በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን እዛው እስር ቤት ሆኖከኢትዮጵያ ሬዲዮ የዜና እወጃ እና ከቪኦኤ ሶማሊኛ ፕሮግራም ሠምቷል፡፡
ከፍርዱ በኋላም በተመሳሳይ ወንጀል ከተከሰሰ አንድ እስረኛ ጋር በካቴና ተጠፍሮ በቀን አንድ እንጀራ ለሁለት ተካፍሎእንዲበላ እንደ ውሻ እየተወረወረለት 60 ቀናትን አሳልፏል፡፡ መሐሙድ በተለይም በእንቅልፍ ወቅት እርሱ ወይምየሰንሰለት ደባሉ የተገላበጠ እንደሆነ ካቴናው የሚያደርስበትን የመለብለብ ቃጠሎ ሲያስታውስ ዓይኖቹ በእንባ ይሞላሉ፡፡በአሁኑ ወቅት በዝዋይ ማጎሪያ ከባድ ጥበቃ ለሚደረግባቸው ብቻ በተመደበ ‹‹ዘጠነኛ ቤት›› ውስጥ አስራ አንድ ሶማሊኛተናጋሪዎችን ጨምሮ በድምሩ ሰላሳ አራት ሰዎች ጋር ከዛሬ ነገ የግፍ ፍርዱ ተፈጻሚ ሊሆንብኝ ይችላል በሚል ሰቀቀንእየባነነ በስጋት ተጠፍንጎ መኖር ከጀመረ እነሆ ሰባት ዓመት ሊደፍን ሦስት ወራት ብቻ ቀርተውታል፡፡
የተዋረደው የፍትሕ ሥርዓት!. . .
ርግጥ ነው ይህ በጨረፍታ ያቀረብኩት አሳዛኝ ታሪክ የመሐሙድ የሱፍ ብቻ አይደለም፡፡ ሌሎች ሰባት ‹‹አባሪዎቹ››ስቃዩንም ሆነ የሞት ፍርዱን ይጋሩታል (በነገራችን ላይ በአንድ መዝገብ የተወነጀሉት እነዚህ ስምንት የሞት ፍርደኞች፡-መሐድ ኢብራሂም፣ አረብ ሰዋኔ ዱልባንቲ፣ ሐሰን መሐመድ ዑስማን፣ ሐሰን መሐመድ ዓሊ፣ ሙክታር መሐመድ ዓብዱላሂ፣ከድር ሽኩር ሙሳ እና ካሚል ዓብዱልናስር እንኳን በጋራ መንግሥት ላይ ሊያሴሩ ቀርቶ እርስ በርስም የተዋወቁት እስር ቤትውስጥ ነው፡፡ ከጅጅጋ ወደ ዝዋይ ‹‹ዘጠነኛ ቤት›› ተዘዋውረው በርካታ ዓመታትን ያሳለፉትም በጭካኔው ወደርእንደማይገኝለት የሚነገረው የክልሉ ፕሬዚዳንት አብዲ
በአደራ እንዲቀመጡ በመተላለፋቸው መሆኑን ነግረውኛል፡፡) እንደ መሐሙድ ሁሉ እነርሱም ፍርድ ቤት ቀርበውአያውቁም፤ ምንም ዓይነት የሰውም ሆነ የሰነድ ማስረጃ አልተቆጠረባቸውም፡፡ እዚህ ጋ የማነሳው አሳዛኝ ገጠመኝከመካከላቸው አንዳቸውም ራዲዮ ስላልነበራቸው የተጣለባቸውን የሞት ፍርድ ውሳኔ የሠሙት፣ ዜናው ከተላለፈ ከበርካታቀናት በኋላ ሬዲዮ ካላቸው እስረኞች መሆኑ
ነው፡፡ ይህ እጅግ አሳፋሪና አስደንጋጭ መንግሥታዊ ውንብድና በደንብ ይብራራ ዘንድ ለተከሳሶቹ ከተሰጣቸው ባለ አንድገፅ የክስ ቻርጅ የሁለቱን ብቻ በአዲስ መስመር እጠቅሳለሁ፡-‹‹በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ አቃቤ ሕግና ፍትሕቢሮ በሶማሌ ክልላዊ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት
ጅጅጋ
የዐ/ሕግ/መ/ቁ 90/2000
ዝዋይ እስር ቤት ያለው
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከሳሽ፡- ዐ/ሕግ
ተከሳሽ፡- ሐሰን መሐመድ ዑስማን (ሐንን መድቤ)
ዕድሜ፡- 21
ሥራ፡- ተማሪ
አድራሻ፡- ጅጅጋ ከተማ፡- 06 ቀበሌ
ወንጀል
በ1996ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ.መ.ሥ.ሥ.ህ.ቁ. 240(3) እና 251(መ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣
የወንጀል ዝርዝር
ተከሳሽ ከመስከረም 1999 ዓ.ም. ጀምሮ እራሱን ኦ.ብ.ነ.ግ. እያለ ከሚጠራው ተቃዋሚና አሸባሪ ድርጅት ጋር በራሱፈቃድ
በዚሁ በጅጅጋ ከተማ ከላይ በተጠቀሰው ዓመተ-ምህረት አባል በመሆን በጫካ በዚሁ አካባቢ ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋርበከተማም
ሆነ በጫካ በመገናኘት በኢኮኖሚ ረገድ የሚያስፈልጋቸውን፡- ጫማ፣ ልብስ የመሳሰለውን እዚያው ድረስ ሄዶ በማቀበልአብሮ
ሲንቀሳቀስ በመቆየቱ ተከሶ ቀርቧል፡፡››
ሁለተኛው የክስ ቻርጅ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፡-
‹‹በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ አቃቤ ሕግና ፍትሕ ቢሮ
በሶ/ክ/መ/ ጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት
ጅጅጋ
የዐ/ሕ/መ/ቁ 90/2000
ከሳሽ፡- ዐ/ሕግ
ተከሳሽ፡- መሐድ ሼክ ኢብራሂም
ዕድሜ፡- 28
ሥራ፡- የለውም
አድራሻ፡- ጅጅጋ ከተማ፡- ቀበሌ 05
1ኛ ክስ
ወንጀሉ
በ1996 ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ/መ/ህ/ ቁ. 241 እና 251(መ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣
የወንጀሉ ዝርዝር
ተከሳሹ በ1998 ዓ.ም. ወራትና ቀኑ በውል ካልታወቀ ጊዜ ጀምሮ እራሱን ኦ.ብ.ነ.ግ. እያለ ከሚጠራው ተቃዋሚ የፖለቲካ
ድርጅትና አሸባሪ ጋር በራሱ ፈቃድ አባል በመሆን ከዚህ ሕገ-መንግሥቱን ከሚፃረር ድርጅት በቀጥታ ፌዴሬሽኑእንዲከፋፈል፣ ክልሉን
የመገንጠል ዓላማ ለማሳካት ይህንኑ ድርጅት ከዚሁ በጅጅጋ ከተማ ለጊዜው ካልተያዘ ግብረ-አበሩ ጋር በመሆን ይህንኑአሸባሪ ድርጅት
በሚያስፈልገው ማቴሪያል ሁሉ፡- ጫማ፣ የፖሊስ የደንብ ልብስ፣ መድሃኒት. . . የመሳሰለውን በማቀበሉ፡፡
2ኛ ክስ
ወንጀሉ
በ1996ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ/መ/ህ/ ቁ. 36 (ለ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣
የወንጀሉ ዝርዝር
ተከሳሹ ከ1996 ዓ.ም. ጀምሮ የተለያዩ መ/ቤቶች ማለትም፡- የክልሉ ት/ቢሮን፣ የቀብሪ-ደሐር ት/ቢሮን፣ እንዲሁም የMSF
እና የተለያዩ መሥሪያ ቤቶችን እና የትምህርት ተቋማትን ማህተም በማስመሰል አትሞ እና የኃላፊዎችን ፊርማ ዓይነትአስመስሎ
በማስፈር ሐሰተኛ ሰነድ አዘጋጅቶ በመገኘቱ ተከሶ ቀርቧል፡፡››
(ሁሉም የክስ ቻርጆች ማኅተም እና አንጋው አፈወርቅ ምንተስኖት የተባለ የክልሉ ዐቃቤ ሕግ ፊርማ አላቸው)
እነሆም ያለአንድ ምስክር፣ ያለምንም የሰነድ ማሰረጃ፣ አንድም ቀን ችሎት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃል ሳይጠየቁ እና
ሳይከራከሩ (ያውም የዞን ፍርድ ቤት) በነዚህ በስም በጠቀስኳቸው በስምንቱ ኢትዮጵያውን ላይ የሞት ቅጣትን የመሰለየመጨረሻ
ውሳኔ እንደቀልድ አስተላልፎባቸዋል፡፡ (በነገራችን ላይ ሌሎች 13 የኢትዮጵያ-ሶማሌ ተወላጆችም በተመሳሳይ የሐሰትውንጀላ የዕድሜ
ልክ እስር ተፈርዶባቸው ዝዋይ ይገኛሉ፡፡ የሚገርመው ጉዳይ ደግሞ ም ቢሆኑ መጀመሪያ ተጠርጥረው በተያዙበት ወንጀልአይደለምየተጠየቁት፡፡ ጉዳዩ ጭራሽኑ በምርመራም ወቅት አልተነሳም) መቼም በዚህ መልኩ በተቀናበረ የውሸት ክስ ከ20-27 ዓመት የሚገኙ
ወጣቶችን በሲኦላዊ እሳተ-ነበልባል ስቅየት ውስጥ እንዲያልፉ ከማድረግም በዘለለ፣ ብሩህ ቀናቸውን አጨልሞ ላይመለሱወደመቃብር
የሚሸኝ ቅጣት ሲጣል ከመመልከት የበለጠ የትኛውንም ዜጋ የሕሊና ስቃይ ውስጥ ከትቶ፣ አንገት አስደፍቶ፣ በቁጣ ቀስቅሶ
ወደአደባባይ የሚያወጣ ገፊ-ምክንያት አለ ብዬ አላምንም፡፡
ማነው ተጠያቂው?
በእነዚህ ንፁሃን ኢትዮጵያውያን ላይ ‹በጄል-አደብ› የደረሰባቸው በነውረኝነት የታጀለ ኢ-ፍትሐዊ ፍርድ እና ስቅየት፣
የሥርዓቱን እውነተኛ ማንነት ገሃድ የሚያወጣ ተጨባጭ ተግባር መሆኑ ባይካድም፡ ይህንን አረሜናዊ ድርጊት በፊት-አውራሪነት
የመሩት፡- ኮሎኔል ሞኒ መንገሻ በጊዜው የክልሉ የፀረ-ሽብር ግብረ-ኃይል ዋና ኃላፊ የነበረ አሁን ወደአዲስ አበባ ተቀይሮ‹ሕገ-ወጥ
የሠው ዝውውር ወንጀል መከላከል› ኃላፊ፣ ቢኒያም የተባለ የክልሉ የደህንነት ኃላፊ፣ ሻለቃ ዘገየ በክልሉ የፌዴራል ፖሊስኃላፊ፣
ወልደአራዌ የክልሉ ፖሊስ ም/ኮሚሽነር፤ እንዲሁም ሻለቃ ወንድሜ፣ ሻለቃ በለጠ እና ታሰረ የተባሉ ኃላፊነታቸውንለይተው
የማያስታውሷቸው ግለሰቦች መሆናቸውን ግፉአኖቹ በተሰበረ ልብ፣ ምሬት በሞላው ድምፅ፣ ተስፋ በቆረጠ ስሜትሲተርኩልኝ ዓይኖቼ
ላይ የተቋጠረው የእንባ ከረጢት ገንፍሎ እንዳይፈስ ብርቱ ትግል ማድረጌን አልሸሽግም፡፡
የሆነው ሆኖ እነዚህ የሥርዓቱ ሹማምንት የፍርድ ቤት ደጅ ሳይረግጡ፣ የሞት ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ባደረጓቸው
ምስኪኖች ላይ የማሰቃያ ጥበቦቻቸውን በሙሉ ከሞከሩባቸው በኋላ፡- ‹‹ሞት እንፈርድባችኋለን!!›› እያሉ ያስፈራሯቸውናይዝቱባቸው
ነበር፤ እነርሱም፡- ‹‹እናንተ ፍርድ ቤት ናችሁ እንዴ?›› ብለው በግርምትና ባለማመን ሲጠይቋቸው፣ ማናአህሎኝነትያሳበጣቸው የፀጥታ
ኃላፊዎች እንዲህ በማለት አስረግጠው መልስ መስጠታቸውን ሰምቻለሁ፡-
‹‹አዎን! ፍርድ ቤት ማለት እኛ ነን!!››
በርግጥ ከዚህ ሁሉ መከራ በኋላ የተላለፈባቸው ውሳኔ፣ ያውም በሞት እንዲቀጡ የሚል መሆኑን ስናስተውል የዛቻውን
መነሾ መረዳቱ አዳጋች አይሆንብንም፡፡ በአናቱም በምርመራ ወቅት ዕድል ፊቷን ያዞረችበትን ተጠርጣሪ እዛው እስረኛ ፊትበሽጉጥ
ግንባሩን በርቅሰው እንደ መናኛ ነገር ሜዳ ላይ ይዘረጉት እንደነበረ የዓይን እማኞች ይመሰክራሉ፡፡
በጥቅሉ ይህ ሁነት በሀገሪቱ አለቅጥ የተንሰራፋውን የፍትሕ እጦት፣ የሠብአዊ መብት ጥሰት፣ ዳኞች ከሕግ ይልቅ ከቤተ-
መንግሥት በሚላክላቸው የፍርድ ውሳኔ ንፁሃኑን ለምድራዊ ስቃይ ከመዳረግም አልፈው ተርፈው በጭካኔሕይወታቸውንም
እንደሚነጠቁ በቂ ማስረጃ ይመስለኛል፡፡
‹‹ጄል-አዳብ››
የክልሉ ኗሪዎች ‹‹ጄል-አዳብ›› (የገሃነም እስር ቤት) እያሉ የሚጠሩት የጅጅጋው ማሰቃያ ቤት ክፍሎች የተሠሩት አራትመቶ
ታሳሪዎችን እንዲይዙ ታስቦ ቢሆንም፣ አብዛኛውን ጊዜ ከአራት ሺህ በላይ ታሳሪዎች እንደሚታጎሩበት አረጋግጫለሁ፡፡ይህም አንድ
ሰው ከአንድ ሰዓት በላይ በእንቅልፍ ማሳለፍ እንዳይችል አድርጎታል፡፡ ምክንያቱም ቦታውን ለተረኛው የመልቀቅ ግዴታአለበትና፡፡
ምናልባት እንቅልፍ ቢጥለው እንኳ ተረኞቹ ቀስቅሰው (ጎትተው) ያስነሱታል፡፡
ከ‹‹ጄል-አዳብ›› በሕይወት ተርፎ የሚወጣ ሰው ዕድለኛ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ በዚህ ቦታ ከቤተሰብ ጋር መገናኘት ጭራሽ
አይሞከርም፡፡ ማሰቡ እንኳ እንደ ቅንጦት ነው የሚታየው፡፡ በእስር ቤቱ አጥር ሦስት መቶ ሜትር ክልል ርቀት ዙርያ ውስጥመገኘትም
ለከባድ ስቃይ (አንዳንዴም ለሞት ቅጣት) ይዳርጋል፡፡ በሃያ አራት ሰዓት አንዴ፣ አንድ እንጀራ ለሦስት እየተቃመሱለአምስት ዓመት
በዛ እስር ቤት ያሳለፈ ምስኪን አጋጥሞኛል፡፡ ይህ ወጣት በ2004ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ሦስት ዓይነት ተላላፊ በሽታ(ተቅማጥ፣
ሰውነትን የሚያሳክክና ጉሮሮን አሳብጦ ለአዕምሮ መቃወስ የሚዳርግ) ተከስቶ በቀን እስከ አስራ አራት ሰው ድረስ ይሞትእንደነበር
ያስታውሳል፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ሕክምና ብሎ ነገር አልነበረም፡፡ እንዲያውም በግልባጩ የክልሉ አስተዳዳሪዎችጭካኔያቸውን (ኢ-
ሠብአዊነታቸውን) ወለል አድርገው የሚያሳብቁ ድርጊቶች መፈፀማቸውን አላቋረጡም፡፡ ለማሳያ ያህልም እስረኛው ከሌሊቱስድስት
ሰዓት ላይ በአንድ ድምፅ እንዲህ የሚል መፈክር እንዲያሰማ መገደዱን እዚህ ጋ መጠቀስ ይቻላል፡-
‹‹መለስ ዜናዊ ሐኖላዶ!›› (መለስ ዜናዊ ለዘላለም ይኑር!)
‹‹አብዲ ሑመድ ዑመር ሐኖላዶ!››
‹‹ኢትዮጵያ ሐኖላዶ!››
ኦብነግ ሐዳኦዶ!›› (ኦብነግ ይውደም!)ሌላው አስገራሚ ጉዳይ ቤተሰብ ታሳሪ ልጁ በሕይወት ይኑር ይሙት የሚያውቀውከማጎሪያው በስንት ጊዜ አንዴ የሚፈታ
ሰው ሲገኝ ብቻ የመሆኑ እውነታ ነው፡፡ እናም ድንገት በአንዲት ‹ዕድለኛ› ቀን አንድ ታሳሪ ከ‹‹ጄል-አዳብ›› የተለቀቀእንደሆነ ወሬው
ከመቅጽበት ይዛመትና ለሳምንታት አሊያም ለወራት የእስረኛው ቤት በእንግዶች እስከ አፍ-ገደፉ ጢም ብሎ ይውላል፡፡የተለመደ
ነውና እሱም ያለመታከት የቀረበለትን ጥያቄ በሚከተለው መልኩ ሲመልስ ይከርማል፡-
‹‹ኦ!… እገሌ ከሞተ እኮ ሁለት ዓመት አለፈው›› ፤ “እገሌማ ሲያሳዝን! ካረፈ ገና አንድ ወሩ ነው”፤ “ኦ! እገሌ ለወደፊቱ
እግዜር ይጠብቀው እንጂ እስካሁን በሕይወት ይገኛል…” ወዘተ ወዘተ. . .
የረሃብ አድማ
ለሰላማዊ ሰልፍ ሲዘጋጁ ታፈሰዉ የታሰሩት የረሃብ አድማ ጀመሩ
አንዳርጋቸው ፅጌ እንዴት ተያዘ? – ተስፋዬ ገብረአብ
አንዳርጋቸው እንዴት ከወያኔ እጅ ሊገባ እንደቻለ ዛሬም ድረስ ግልፅ መረጃ የለም። የተለያዩ መላ ምቶችን እየሰማን፣ እያነበብን ቆይተናል። አንዳርጋቸውን በቅርብ ከሚያውቁት አንዱ እንደመሆኔ እኔም ካለኝ መረጃ በመነሳት የራሴን ግምት መውሰዴ አልቀረም። የኔን ግምት ይፋ ከማድረጌ በፊት ሌሎች የሚሉትን ለመስማት በሚል እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ ሳልፅፍ ቆይቼ ነበር። አሳማኝ መረጃ ሳይፃፍ ወይም ሳይገለፅ ጊዜው ስለረዘመ እነሆ! እኔም የግል አስተያየቴን ለማኖር ወሰንኩ… (ቅዳሜ ለንባብ ይበቃል)
በቦረና ዞን ገላን ወረዳ የአንድነት አባላት ታሰሩ – አንድነት
በቦረና ዞን ገላን ወረዳ የአንድነት አባላት መታሰራቸውን ከአከባቢው በደረሰን ሪፖርት አረጋግጠናል። የታሳሪዎቹ ስም ዝርዝር አቶ በድሉ መንግስቱ በቦረና ዞን ገላን ወረዳ ሰብሳቢ፣ አቶ ቆንጨሪ ሳፋይ አባል አቶ ንጉሴ ገልገሎ አባል አቶ ብርሃኑ ሳፋይ አባል ሲሆኑ፤ ሰብሳቢው አቶ በድሉ መንግስቱ የታሰሩት የመንግስትን ስም አላግባብ አጥፍተሀል ተብለው ነው። በተያያዘ ዜና በምስራቅ አሩሲ የኦሆዴድ አባል፣ የጢዮ ወረዳ የሲቪል […]
ዜጎቻችንን በስደት አውሬና ውሃ እየበላቸው የሚገኘው በሃገራቸው ሰርቶ የመኖር ዋስትና ስለተነፈጉ ነው!! – ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
ኢትዮጵያችን ከምትታወቅባቸው ዘርፈ ብዙ ገዥ- ወለድ ችግሮች መካከል ስደት አንዱ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ዜጎቻችን በሀገራቸው ላይ ሰርተው የመኖር ዋስትና በመነፈጋቸው፤ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው እናስተዳድራችኋለን በሚሉ ገዥዎች በመጨፍለቁ የተሸለ ነፃነትና ኑሮ ፍለጋ እግራቸው በመራቸው መሰደድ የተለመደ ሁኗል፡፡ ገዥው ፓርቲም ከራሱ የስልጣን ቆይታ በስተቀር ሀገራዊ አደጋ እየሆኑ የመጡና የዜጎችን ስነ-ልቡና የሚጎዱ ሁነቶችን እንደማንኛውም ዜጋ አድማጭ ከመሆን በዘለለ ችግሩን […]
አምንስቲ ኢንተርናሽናል የሰብአዊ መብት ተቋም ለሰልፍ በወጡ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የተወሰደውን አሰቃቂ እርምጃ አወገዘ::
የታሰሩ እንዲፈቱ በፖለቲካ ድርጅቶች ላይ የሚደረገው ወከባና ጫና እንዲቆም በመግለጫው ጠይቋል::
http://www.andargachewtsige.com/?p=343

የኮንጎ ዜጎች ከማያዉቁት ጠላት የተደቀነባቸው ስጋት
በሰሜን ምሥራቅ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ውስጥ እየደረሰ ያለዉ ጥቃት ማሕበረሰቡን ከፍተኛ ስጋት ላይ እደጣለዉና መፍትሄ አልባ እንዳደረገዉ ተገልፆአል። የሲቪሉ ማሕበረሰብ ድርጅቶች አማፅያን የሚያደረሱት ጥቃት ለመከላከል የዓለም አቀፉን ርዳታ ጠይቀዋል።
በሃገራችን ላለው ችግር የሴቶች ተደራጅቶ መታገል አስፈላጊ እና ወቅታዊ ምላሽ ነው፦ ኤደን መስፍን, ኖርዌይ
ዛሬ ዛሬ ከረጅም አመታት ጀምሮ በሃገራችን የተነሳው የሴቶች መብት ይከበር የሚለውን ይህዝብ ጥያቄ ለመቃረን እስኪመስል ድረስ ከባለፉትም ጊዜያቶች በባሰ ሁኔታ የሴቶች መብት እየተጣሰ ይገኛል። ከዛም አልፎ ተቆርቋሪ አካል የሌላቸው የሃገራችን ሴቶች ህይወታቸው አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል። ለዚህም በየጊዜው ወደ ተለያዩ አፍሪካና አረብ ሃገራት በተለይም በሱዳን በየመን የሚፈልሰው የኢትዮጵያውያን ሴቶ ች ቁጥር መጨመር ማረጋገጫ ነው። በተለያዩ […]
ጥቂት ቆይታ- ከአል-በላቢል ጋር
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 10, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ
ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክር ቤቱ ህዳር 30/ 2007 ዓም ባወጣው መግለጫ “በሀገራችን ህዝባዊ ሥርዓት ለማምጣትና በህግ የበላይነት የሚያምን መንግስት ለመመስረት በምናደርገው ትግል ሁሉ የሚጠበቅብንን መስዋእትነት ለመክፈልና ሀገራዊ ግዴታችንን ለመወጣት ዝግጁ” ነን ብሎአል። “ሰማያዊ ፓርቲን ጨምሮ ዘጠኝ ትብብር የፈጠሩ ፓርቲዎች በህዳር ወር ያወጡት መርሐ ግብር አንድ አካል የሆነውን የ24 ሰዓት የተቃውሞ የአደባባይ …
በደቡብ ክልል ፍተሻው ከወትሮው በተለየ መጨመሩን የአይን እማኖች ገለጹ
ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንዳንድ ተጓዞች ለኢሳት እንደገለጹት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚታየው ፍተሻ ጨምሯል። ከዲላ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ ተሳፋሪ ለኢሳት እንደገለጸው ፖሊሶቹ ተሳፋሪውን ወዴት ነው የምትሄዱት? ለምንድነው የምትሄዱት በማለት ከመጠየቅ ጀምሮ የሰዎች ኪሶች በመግባት ፍተሻ ያደርጋሉ። በሽተኞችንና ህጻናትን የታቀፉ እናቶች ሳይቀሩ ፍተሻ በሚል ፖሊስ ጣቢያ ታጉረው መዋላቸውን …
በቀይ ባህር ዳርቻ ላይ ከሰመጡት ከ70 በላይ ኢትዮጵያውያን መካከል የአብዛኞቹ አስከሬን አልተገኘም
ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ወደ የመን ሲጓዝ የነበረ ጀልባ ሰጥሞ ከ79 ያላነሱ ኢትዮጵያዊያን ያለቁ ሲሆን እስካሁን ከ14 ያልበለጡ ሰዎች ብቻ አስከሬን መገኘቱን ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት ገልጿል። የሟቾች ቁጥር አስቀድሞ በመገናኛ ብዙሃን እንደተገለጸው ሳይሆን 79 መሆኑን ግሩም አክሎ ተናግሯል። በሌላ በኩል ደግሞ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕጋዊ ጉዞን ከአንድ ዓመት በላይ አግዶ …
በጋምቤላ 2 የምክር ቤት አባላት አዲስ አበባ ላይ ታሰሩ
ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት በካውች ማሞና ኦብዱል ኦቻር የሚባሉትን ባለስልጣኖች አውርዷቸዋል። ግለሰቦቹ ያለመከሰስ መብታችን የተነሳው በህገወጥ መንገድ ነው በማለት ወደ አዲስ አበባ ተጉዘው የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትን ለማግኘት ሙከራ ቢያደርጉም፣ ደህንነቶች ይዘው አስረዋቸዋል። ባለስልጣኖቹ ከውጭ ሃይሎች ጋር ትገናኛላችሁ በሚል መከሰሳቸውን የአኝዋ ሰርቫይቫል ዋና ሃላፊ አቶ ኒካው …
በአዲስአበባ ባለፉት ሶስት ቀናት የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት በዛሬው ዕለት ተባብሶ በአብዛኛዎቹ ማደያዎች በተሸከርካሪዎች ወረፋ ተጨናንቀው ዋሉ፡፡
ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጋቢያችን በአራት ኪሎ፣ በቦሌ፣ በካዛንቺስ፣ በልደታ አካባቢዎች የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎችን ተዘዋውሮ እንደተመለከተው በብዙዎቹ ማደያዎች በዛሬው እለት ነዳጅ ቢኖርም ነዳጅ ለመቅዳት የተሰለፉ ተሸከርካሪዎች በመብዛታቸው ረጃጅም ሰልፎች መታጣቸውንና የትራፊክ መጨናነቅ መከሰቱን መታዘብ ችሎአል፡፡ በዓለም ገበያ ላይ የነዳጅ ዋጋ መቀነስን ተከትሎ ከትላንትና ህዳር 30 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ ንግድ ሚኒስቴር መጠነኛ …
የሰብአዊ መብት መታሰቢያ ዕለትና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ይዞታ
ዛሬ የኖቤል መሥራች አልፍረድ ኖቤል የሞተበት ዕለት መታሰቢያ ሲሆን የሚታሰበውም ለዓለም ሰላም ጉልሕ አስተዋጽዎ ለሚያደርግ ለሚያደርጉ የኖቤል የሰላም ሽልማት በመሰጠት ነው። የሚሰጠውም በኖርዌይ መዲና በኦስሎ ሲሆን ፤በተለያዩ የሳይንስ ዘርፎች ፤ ውጤታማ ለሆኑ ድግሞ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ነው ሽልማቱ የሚሰጠው።
ሃየሎም አርኣያን በጨረፍታ
![]() |
| Hayelom Ar’aya |
ለማያዉቁት ጠላት የኮንጎዋዊያን ስጋት
በሰሜን ምሥራቅ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ውስጥ እየደረሰ ያለዉ ጥቃት ማሕበረሰቡን ከፍተኛ ስጋት ላይ እደጣለዉና መፍትሄ አልባ እንዳደረገዉ ተገልፆአል። የሲቪሉ ማሕበረሰብ ድርጅቶች አማፅያን የሚያደረሱት ጥቃት ለመከላከል የዓለም አቀፉን ርዳታ ጠይቀዋል።
ሲአይኤን ያጋለጠው ሠነድ
የአሜሪካው የስለላ ተቋም «CIA» በሽብርተኝነት ተጠርጣሪ እስረኞችን በምርመራ ወቅት በከፍተኛ ሁናቴ ማሰቃየቱን የሚያጋልጠው ሠነድ በስተመጨረሻ ይፋ ሆኗል። የሰብአዊ መብት ተሟጋቿ ሎውራ ፒተር ሠነዱን፦ «ለበርካታ አሜሪካውያን እጅግ አስደንጋጭ ነው» በማለት ገልፀዋል።
የሰብዓዊ መብቶች ቀን በአዲስ አበባ
በተለይ አዲስ አበባ ከተማ በሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎችና የሴቶች ጥቃት ፖሊሶችና የሕግ ተርጓሚዎች ተገቢዉን ድጋፍ እንደማያደርጉ ይባስ ብለዉም ወንጀሉን የሚያባብሱ ተግባራት እንደሚፈጽሙ ተገለጸ።
የዩጋንዳ የኤሌክትሪክ አውቶሞቢልና የቴክኖሎጂ ይዞታ በአፍሪቃ
ከአፍሪቃው ክፍለ ዓለም ፣ ሞሮኮ፣ ለኃይል ምንጭ ፣ ከነዳጅት ዘይት ይልቅ ለፀሐይ ሙቀትና ብርሃን የላቀ ግምት የሰጠችበት እንቅሥቃሤ በአወንታዊነት ሲጠቀስ፣ ዩጋንዳ ለተፈጥሮ ተስማሚ ነው ያለችውን በኤሌክትሪክ የሚሽከረከር አውቶሞቢል መሥራት ብቻ
ሚስጢረኛ መፅሐፍ ተናግሮ አናጋሪ ከበላይ ገሰሰ
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ውሳኔዎችን አስተላለፈ!!
‹‹አገዛዙ የወሰደውና ወደፊት የሚወስደው ከእስካሁኑ የባሰ አረመኔነት እርምጃ ይበልጡን ያጠናክረናል›› የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ትናንት ህዳር 30/2007 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ትግሉን ያጠናክራሉ ያላቸውን ውሳኔዎችን አስተላለፈ፡፡ ብሄራዊ ምክር ቤቱ ያስተላለፋቸው ውሳኔዎች ‹‹ህወሓት/ኢህአዴግ በፈፀመው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እና እስር ምክንያት ክፍተት ሳይፈጠር የፓርቲው እንቅስቃሴ እንዲቀጥልና ትግሉም እንዲጠናከር የሚያስችሉ ናቸው›› ሲሉ የብሄራዊ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰይድ […]
ህዝብን በማይሽር ቁስል አየጎዱ በፕሮፓጋንዳ ማከም አይቻልም:: – ከምኒሊክ ሳልሳዊ
ህዝብን በማይሽር ቁስል አየጎዱ በፕሮፓጋንዳ ማከም አይቻልም:: የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጥያቄና የኮሚቴው መፈታት ጥያቄ በአስቸኳይ ሊመለስ ይገባል:: ሙስሊም ወገኖቻችን ለሃገራቸው እና ለነጻነታቸው ምን ያህል ቀናኢ መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል:: ወቅሰን ወቅሰን ወንጅለን ወንጅለን የሰለቸን ለመስማትም የታከተን ነገር ቢኖር ያለፉት ስርአቶች ላይ እና ሌላው ላይ ማሳበብን አንዱን ከአንዱ ለማፋጀት ማፈራረጅን መጠቋቆምን የመሳሰሉት ኢሕአዴጋዊ ባህርያት ናቸው::ወያኔ ኢሕኣዴግ የጭንቅ ነገር […]
በቅርቡ የታሰሩት የአንድነት አባላት ሺሻይ አዘናው እና አንጋው ተገኝ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጸመበት ተረጋገጠ!
በመቀሌ ዞን የአንድነት አመራር አባል የነበረው ወጣት ሺሻይ አዘናው ጥቅምት 22 በደህንነት ኃይሎች ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ በመቀሌ በሚገኝ አንድ እስር ቤት ኮማንደር ሰዓረ በሚባል የፖሊስ አዛዥና እርሱ በሚመራቸው ፖሊሶች ከፍተኛ የሆነ ድብደባ ተፈፅሞበታል። ከዚያ በኋላ የት እንዳለ ሳይታወቅ ተሰውሮ ቢቆይም፤ በአሁኑ ሰዓት ማዕከላዊ እየተባለ በሚጠራው የማሰቃያ እስር ቤት እንደሚገኝና በዚህም ቦታ በተከታታይ ለአራት ቀናት ሌሊት […]
የሳምንቱ የራዲዮ መፅሔት ወጎች፤
የሳምንቱ የእረፍት ጊዜ የእሁድ ምሽት የመዝናኛ ምርጫችሁ ከአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ።
ኮ/ል መንግሥቱ ኃይለማሪያም እና የሀይሌ ፊዳ ሞት
መድረክ የተቃውሞ ሰልፍ ጠራ
የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ስብስብ የሆነው መድረክ የኢህአዴግ አገዛዝ በህዝባችን ህገመንግስታዊ ነጻ የመምረጥ መብት ላይ የሚፈጽማቸውን የመብት ረገጣዎች እንዲያቆም፣ በሃገራችን ነፃ ፣ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ተአማኒነት ያለው ምርጫ እውን እንዲሆና የምርጫ ሜዳውም ለሁሉም እኩል የተመቻቸ እንዲሆን ለመጠየቅ ለታህሳስ 5 ቀን 2007 ዓም የተቃውሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ መጥራቱን አስታውቋል። መድረክ ለኢህአዴግ አገዛዝ የውይይትና የድርድር ጥያቄዎችን በተደጋጋሚ ቢያቀርብም፣ አገዛዙ …
በእስር ላይ በሚገኙት የ9 ፓርቲዎች ትብብር አባላት ላይ የተወሰደውን እርምጃ የተለያዩ የተቃዋሚ ድርጀቶች አወገዙ
ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ የሽግግር ካውንስል ለኢሳት በላከው መግለጫ የአፓርታይድ ስርአትን እአካሄደ ያለው የወያኔ አገዛዝ በሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላይ የወሰደው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ ሊወገዝ ይገባዋል ብሎአል። የኢኮኖሚ እድገት አምጥቻለሁ እያለ ፕሮፓጋንዳ የሚነዛ መንግስት ፣ በስልጣን ላይ ለመቆየት ብቸኛ መተማመኛው ሃይል መሆኑን አሳይቷል ያለው የሽግግር ካውንስል፣ ሁሉም የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎችና የአለማቀፉ ማህበረሰብ ድርጊቱን እንዲያወግዙ …
ኦሮምያ ክልል ከሶማሊ ክልል ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት እንዳልቻለ ገለጸ
ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ የጸጥታ ሃላፊ እንደገለጹት በደቡብ እና በቤንሻንጉል ክልሎች አጎራባች ወረዳዎች አሉ ችግሮችን ለመፍታት አንዳንድ ሙከራዎች ቢደረጉም፣ ከሶማሊ ክልል ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት አለመቻሉን ገልጸዋል። በደቡብ ክልል በአንዳንድ ወረዳዎች የድንበር ችግር መኖሩን የገለጹት ሃላፊው፣ ችግሩን ለመፍታት እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል። ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ጋር ያለውን የድንበር ውዝግብ ለመፍታት ተደጋጋሚ ሙከራ መደረጉን …
በጎንዶመስቀል ከተማ ከደም በቀል ጋር በተያያዘ በተደረገ የተኩስ ልውጥጥ ከ3 ያላነሱ ሰዎች ተገደሉ
ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በደራ ወረዳ ጉንዶመስቀል ከተማ ላይ አንድ ከተማ ውበቱ የተባለ ሰው ሃብታሙ ሺበሺ የተባለን ሰው መግደሉን ተከትሎ፣ ገዳይን ለመያዝ በተደረገ ጥረት ሰኞ ህዳር 29፣ 2007 ዓም በአካባቢው ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ተካሂዷል። ከተማ ውበቱ የተባለው ሰው በ1999 ዓም የሰዎች ለሰዎች የተባለውን ድርጅት ገንዘብ ከዘረፈ በሁዋላ …
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 09, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የስደተኞች ብዛትና የባህር ላይ እልቂት
ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ቅዳሜ በአል-ማካ የወደብ ከተማ አካባቢ ስደተኞችን የጫነች ጀልባ መስመጧን እና 70 ኢትዮጵያውያን መሞታቸውን የየመን አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ-ገፁ አስታውቆ ነበር። ይህ መረጃ እስካሁን አልተረጋገጠም
ህዝብን በማይሽር ቁስል አየጎዱ በፕሮፓጋንዳ ማከም አይቻልም::
ህዝብን በማይሽር ቁስል አየጎዱ በፕሮፓጋንዳ ማከም አይቻልም:: #Ethiopia #EthioMuslims #MinilikSalsawi በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ ሽብር ግድያ እስር ድብደባ እንግልት በጅምላ አፈሳ ዘረፋ ንጥቂያ እና ከፍተኛ የሆነ ኢሰብአዊነት እና ጭፍጨፋ በመንግስት ነኝ ባይ ሃይሎች በይፋ በአደባባይ ተፈጽሟል::ይህንን መንግስታዊ ሽብር የማይሽር ጠባሳ በመላው ኢትዮጵያውያን ላይ ጥቁር ነጥብ አስቀምጧል:: የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጥያቄና የኮሚቴው መፈታት ጥያቄ በአስቸኳይ ሊመለስ ይገባል::ሙስሊም ወገኖቻችን ለሃገራቸው እና ለነጻነታቸው ምን ያህል ቀናኢ መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል::
http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … ost_9.html

የሊማዉ የአየር ንብረት ለዉጥ ጉባኤ
የዛሬ አምስት ዓመት ኮፐንሃገን የተካሄደዉ የአየር ንብረት ለዉጥ ጉባኤ ብዙ ተብሎለትና ብዙ ተጠብቆበት ካለ ዉጤት መጠናቀቁ ብዙዎችን ግራ ያጋባ ብቻ ሳይሆን ተስፋም ያስቆረጠ መስሎ ነበር።
የሳዑዲ ግብረ-ሠናይ ድርጅት ሆስፒታል በኢትዮጵያ
ድርጅቱ ቀደም ሲል ሆስፒታሉን አዲስ አበባ ዉስጥ ለመገንባት ጥያቄ ቢያቀርብም የከተማይቱ መስተዳድር ለሆስፒታሉ ማስገንቢያ የሚሆን መሬት ባለመፍቀዱ ትግራይ ዉስጥ ለማስገንባት ወስኗል።
ፀረ አይሁዳውያን ርምጃ በፈረንሳይ
ፈረንሳይ በሚኖሩ አይሁዶች በሚታየው ዘረኝነት እና በሚፈፀምባቸው ጥቃት አንፃር በርካታ ሰዎች ባለፈው እሁድ በፓሪስ አቅራቢያ በምትገኘው ክሬቴይ ሰልፍ ወጥተዋል።አይሁዶች ሀብታሞች ናቸው የሚል የቆየ አነጋገር እንዳለ ይሰማል። ይኸው አነጋገርም ዛሬም ድረስ ብዙ ጠላት አፍርቶባቸዋል።
ዓለም አቀፉ ፍርድ ቤትና አፍሪቃ
ትናንት በተጀመረዉ ሥብሰባ ላይ የአፍሪቃ መንግሥታት ፍርድ ቤቱ ከዓለም አቀፍነቱ ይልቅ አፍሪቃዉያንን ለመክሰስና ለመቅጣት ያለመ ነዉ በማለት ወቅሰዉታል። ፍርድ ቤቱ ከተመሠረተ ጀምሮ የከሰሳቸዉ ወይም የቀጣቸዉ በሙሉ አፍሪቃዉያን ፖለቲከኞች ናቸዉ።



