የዚምባብዌዉ ገዥ ፓርቲ ጉባኤ

የዘጠና አመቱ የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ የዛኑ ፒ.ኤፍ. መሪ ሆነው በድጋሚ ተመርጠዋል። የፕሬዝዳንቱ ባለቤት ግሬስ ሙጋቤም በፓርቲው የሴቶች ክንፍ መሪ በመሆን ወደ ፖለቲካው መቀላቀላቸው ይፋ ሆኗል።