ኢሳት ዜና (ሰኔ 17 2007) በቀጣዩ ወር በኢትዮጵያ ጉብኝት የሚያደርጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ከተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት ተቃውሞ እንደገጠማቸው የእንግሊዙ ዘጋርዲያ ጋዜጣ የተለያዩ አካላትን ዋቢ በማድረግ ዛሬ ረቡእ ዘገበ። አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ፕሬዚዳንቱ በሰብአዊ መብት ረገጣና አፈና የምትታወቅ ሃገርን ለመጎብኘት መወሰናቸው ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ ላይ መሆናቸውንም ጋዜጣው አስነብቧል። የፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ …

አለም ዝም ያለው, ታላላቅ ሀያላን ሀገራት ሁሉ ፀጥ ብለው ተመልካች የሁኑበት አረመኔያዊው እውነተኛው ትርኢት በጭራሽ አላባራም. እንዲያውም ብሶበታል. ሶሪያ ደበነች, ኢራቅን ፈጁት, ሊቢያ ን አናወዟት, ግብፆችን አረዱ, ኢትዮጵያዊንኑ ወንድሞቻችን ደገሙ. ኮሪያ, አሜሪካ, ኤርትራ ብቻ ያልነካኩት የለም ግን ዝም ተብለዋል. ሀይ ባይ አልተገኘም. አንድ ቡድን አለምን ሲያስጨነቅ አለም መሪዎች ያጣች ይመስላል. ነገሩ ግራ የገባ ነው. ልምምዳቸው […]

ሰኔ ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ያሬድ ንጉሴ የተባለ ባለፈው ወር አውሮፓ የገባ አንድ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ለኢሳት እንደገለጸው በቅርቡ 25 ኢትዮጵያውያንና 2 ኤርትራውያን ሆነው ከሱዳን ወደ ሊቢያ ሲጓዙ፣ ደንጎላ በምትባል ቦታ ላይ በሱዳን የመከላከያ ሰራዊት አጃቢነት የመጣ ኢትዮጵያዊ የደህንነት ሰራተኛ የ48 አመት ጎልማሳ የሆነውን ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ከመኪና አስወርዶ በሽጉጥ እንደገደለው ገልጿል። …

ሰኔ ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ባለፉት ጥቂት ወራት በተቃዋሚ መሪዎች ላይ የተፈጸመው ግድያና በመላ አገሪቱ በተቃዋሚ ድርጅት አባላት ላይ የሚፈጸመው የሰብአዊ መብት ረገጣ በቅርቡ በተካሄደው ምርጫ ላይ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ነው ብሏል። የአፍሪካ ህብረትና የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን መርምረው ሪፖርት አለማድረጋቸውንም ድርጅቱ ወቅሷል። ምርጫው እስከሚካሄድበት ጊዜ …

ሰኔ ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእንግሊዝ አገር የሚገኘው ሪፕሪቭ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲፈቱ የእንግሊዙ ጠ/ሚኒስቲር ዴቪድ ካሜሩን አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቋል። አቶ አንዳርጋቸው ለአንድ ሳምንት መታሰራቸው ረጅም መሆኑ ሳያንስ ለአንድ አመት ታስረው መቆየታቸው ለማሰብም የሚከብድ ነው ሲል የህግ ድጋፍ በመስጠት የሚታወቀው የሰብአዊ መብት ድርጅቱ ገልጿል። በእንግሊዝ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሪፐሪቭ ዌብሳይት …

ሰኔ ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአሁኑ ወቅት የአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ አማካሪ የሆኑት ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ ሰሞኑን ከመንግስት መገናኛ ብዙሃን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ዕቅዱ የተለጠጠ መሆኑን አምነው ሙሉ በሙሉ ላለመሳካቱ ምክንያት ያሉዋቸውን ምክንያቶች ዘርዝረዋል፡፡ የመጀመሪያው የእድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በባህርይው መዋቅራዊ ለውጥን ታሳቢ ያደርጋል፡፡ ይህ ዕቅድ በራሱ ተለጥጦአል ብለዋል፡፡ የፋይናንስ ምንጭ ማፈላለጉ …

ሰኔ ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስት ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አይሲስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን ዘግናኝ ድርጊት ለመቃወም በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ድርጊቱን ለማውገዝ በስፍራው ተገኝታ የነበረችው ወ/ሮ ንግስት ወንዲፍራው ምክንያቱ ባልታወቀ ሰበብ ከ3 አመት ልጇ ጋር ግንቦት 19/2007 ዓ.ም ያለ ማዘዣ በፖሊስና በደኅንነት ኃይሎች ተወስዳ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ከታሰረች በሁዋላ ሰኔ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ዮሃንስ ደሳለኝ (ጀርመን – ፍራንክፈርት)

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2007 ዓ.ም.  June 23, 2015)፡- በጀርመን ፍራንክፈርት ትላንት ሰኞ ሰኔ 15,2007 (June 22,2015) የእንግሊዝ ኮንስለር ፅ/ቤት የተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ። በዚሁ ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን በኩል ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው የተሰጡበትን 1ኛ ዓመት ለማስታወስና እንዲሁም ላለፉት አንድ ዓመት ሁኔታዎችን በለዘብተኝነት የምትመለከተው ታላቋ ብሪታንያ ለራሷ ዜጋ ምንም ዓይነት ድጋፍና ከለላ ባለመስጠቷ ለማውገዝና አስፈላጊውን እርምጃ እንድትወሰድ ለማሳሰብ የተጠራው የተቃውሞ ሠልፍ ከጅምሩ ደማቅና አላማውን ያሳካ ነበረ።IMG_1874.JPG

ሙሉውን አስነብበኝ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ አሁንም ስቃይ ላይ መሆናቸው በኬንያ ወያነ የላካቸው ደህንነቶች ከተለያዩ የመገናኛ መሳሪያዎች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸው የአቢሲኒያ ባንክ ሰራተኞች የተቃዋሚ ድርጅት ደጋፊ ናቸው ተብሎ በኢሕ አዴግ ባለስልጣናት መፈረጃቸው በሁመራ አሸባሪዎች ገቡ በሚል ሽፋን ህወሃት ህዝቡን እያሸበረ መሆኑን ተነገረ የሰማያዊ ፓርቲ የምስራቅ ጎጃም ዞን ፀኃፊ ሳሙኤል አወቀ በወያኔ ጭፍሮች ባሳለፍነው ሳምንት መገደሉ ተሰምታልFiled under: NEWS […]

መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ ታስረው ሰኔ 15/2007 ዓ.ም በቄራ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት እንዲፈቱ የተወሰነላቸው ወንይሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ቤትሄልየም አካለ ወርቅ ዛሬ ሰኔ 16/2007 ከእስር ተፈትተው ሲወጡ በፖሊስና ደህንነቶች ታፍነው ታስረዋል፡፡ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ታስረው የነበሩት ኤርሚያስ ፀጋዬና ዳንኤል ተስፋዬ ከእስር ከተፈቱ በኋላ የ6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ፖሊሶች […]

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ምርጫ ቦርድ ጊዚያዊ ውጤቱን ይፋ ባደረገበት ወቅት የ105 ወንበሮችን ጉዳይ ግልጽ ባለማድረጉ አንዳንዶች “ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎች ለመካፋፈል አስቦ ያደረገው ሊሆን ይችላል” በማለት አስተያየት ሲሰጡ ቢቆዩም፣ ቦርዱ ግን ኢህአዴግ መቶ በመቶ ምርጫውን አሸንፋል በማለት የመጨረሻ ውሳኔውን ሰጥቷል። ዋናዎቹ የተቃዋሚ ድርጅቶች ሰማያዊ ፓርቲና መድረክ ምርጫውን ” አሳፋሪ” ነው …

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ችሎቱን የተከታተሉት በአቶ ማሙሸት የሚመራው መኢአድ ምክትል ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ለኢሳት እንደገለጹት አቶ ማሙሸት፣ ሰኔ 10፣ 2007 ዓም በ5 ሺ ብር ዋስ እንዲወጣ ፍርድ ቤት የወሰነ ቢሆንም፣ ፖሊስ ለመልቀቅ ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቶ ዛሬ ፍርድ ቤት አቅርቦታል። ፖሊስ፣ አቶ ማሙሸት ቢፈታ በምስክሮቼ ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ ሊያደርስባቸው …

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሰሞኑ በአዲስ አበባ የሚገኙ የታክሲ አገልግሎት ሰጪ የግል ባለንብረቶች ወደ አዲስ አበባ መንገድ ትራንስፖርት ጽ/ቤቶች ታፔላ ለመቀየር በሄዱበት ወቅት ከተለመደው የታፔላ ማስቀየሪያ አገልግሎት ክፍያ ውጪ ባልተጠበቀ ሁኔታ የ1ሺ ብር ቦንድ ካልገዛችሁ የሚል ግዳጅ ተጥሎባቸዋል ። “አሁንስ ወዴት እንሂድ? ለማን አቤት እንበል?” በማለት የታክሲ ባለንብረቶች ሲያማርሩ …

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ አንዳርጋቸውን ጨምሮ ሌሎች በእስር ላይ ያሉ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላትና የሲቪክ ማህበረሰብ አባላት እንዲፈቱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ይካሄዳል። በጀርመን በፍራንክፈርት፣ሙኒክ፣ዱስልዶርፍ እና በርሊን የሚካሄድ ሲሆን፣ በፍራንክፈርት የሚደረገው ተቃውሞ ለ24 ሰአታት ይቆያል። በጣሊያን ሮማ፣ በቤልጂየም ብራሰልስ፣ በእንግሊዝ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ዛሬ ቤተ እስራኤላዊያን ሰላማዊ ስልፍ  በቴል አቪብ ያደርጋሉ ምክንያቱም ባለፍው ቤተ እስራኤላዊ በፖሊስ ተመቶ ነበር ፖሊሱ እስር ቤት መግባት አለበት ብለው ሲጠይቁ የተሰጠው መልስ መጀመሪያ የተማታው ቤተ እስራኤላዊ ነው ፖሊሱ አይድለም የሚል ነበር ይህን ያስቆጣቸው ቤተ እስራኤላዊያን ዝም ብለው አልተመለከቱም በዛሬው እለት በአደባባይ ይወጣሉ አንድ ፍክራ አላቸው ይህም አንድ ሰው ለሁሉም ነው ሁሉም ለአንድ ሰው […]

የኢትዮጵያ መንግስት ያሰማራቸው ሰላዮች በህዝብ ጥቆማ ቢያዙም መለቀቃቸው ህዝቡን አስቆጥቷል ትናንት ረፋድ አካባቢ በናይሮቢ ነዋሪ የሆኑ ሶስት የፖለቲካ ስደተኛ ኢትዮጵያዊያን በኬንያ ፖሊስ ለጥያቄ እንደሚፈለጉ ተነግሯቸው ሲወሰዱ በዛ ያሉ ሰዎች ተፈላጊዎቹን በመከተል ፖሊስ ጣብያ ድረስ በማምራት የተያዙት እንዲለቀቁ አልያም ተላልፈው ለኢትዮጰያ መንግስት እንዳይሰጡ በመጠየቅ ምላሽ ካላገኙ ፖሊስ ጣብያውን እንደማይለቁ በማስረዳታቸው የፖሊስ ጣብያው ኃላፊዎች ሰዎቹን አሳልፈው እንደማይሰጡ […]

በኦሮሚያ ክልል፤ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች ድምፃችን ተሰረቀ በማለት ወደ ዩኒቨርሲቲ አስተዳዳሪዎች አቤቱታቸው ስላቀረቡ ብቻ በስርዓቱ ታጣቂዎች ጥይት እንደተተኮሰባቸው ተገለፀ። በምንጮቻችን መረጃ መሰረት በመቱ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደውን ምርጫ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ለተቃዋሚ ድርጅቶች መምረጣቸውን የተረዱት የስርዓቱ ካድሬዎች የምርጫው ኮረጆ ሰርቀው በመቀየር ኢህአዴግ 1568 አብላጫ በማግኘት አሸንፈዋል በማለት ግንቦት 17/ 2007 ዓ/ም ይፋ ያደረጉትን ውጤት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ስላልተቀበሉት ዓመፅ […]

«ትናንት፣ ዛሬም ሆነ ነገ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ዐማራው ስለሆነ፣» እያንዳንዱ ትግሬ ዐማራን በማጥፋት እንቅስቃሴ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን፣ የወያኔ የአገር-ውስጥ እና የውጭ የስለላ ቡድኖች ከፍተኛ አመራሮች በጥናቶቻቸው እንዳሣዩ የታመኑ የሞረሽ-ወገኔ ምንጮቻችን አረጋገጡ። የመረጃ ምንጮቻችን እንደሚያስረዱት፣ አጥኚዎቹ ከሕወሓት ፖሊት ቢሮ በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት የትግሬ-ወያኔን ዘረኛ አገዛዝ ያለፉትን የ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት ጉዞ መዝነው፣ ለሥልጣኑ አስጊው ማን እንደሆነ በመተንተን፣ […]

The post የትግሬ-ወያኔ አመራር በቅርቡ ባደረገው ስብሰባ ዐማራን ፈጽሞ ሳያጠፋ እንቅልፍ እንደማይወስደው ዳግም አረጋገጠ! appeared first on ሳተናው .

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

በጭካኔ ጥበብ ተንኮል የተካኑ፤ ስብዕናን ያጡ ለውነት የመከኑ፤ በሐሰት ተጠምቀው በውሸት የፀደቁ፤ በሌላው መከራ ሳቁ ተሳለቁ:: ሊጥሉት ሞክረው አልወድቅም ቢላቸው፤ ቀጥቅጠው ገደሉት በፈሪ ዱላቸው። በድቅድቅ ጨለማ ተስፋ በታጣበት፤ የነፃነት ትግል በደበዘዘበት፤ ሣሙኤል አወቀ እንደሻማ በርቷል፤ ለወገኑ ክብር በሕይወቱ ከፍሏል። ፈለጉን ተከተል አደራ ብሎሃል፤ ደሙ ከአጥናፍ አጥናፍ ይጣራል ይጮሃል፤ እምቢ በል ወገኔ ተነሣ ይልሃል፤ ፀጥ ያለው […]

ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሠራተኞች መልቀቅ ችግር ሆኖብኛል አለ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በክፍያና በሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ማነስ ምክንያት፣ በጣም በርካታ ሙያተኞች መልቀቃቸውንና በምትካቸውም ብቁ ሙያተኛ ለመቅጠር ክፍያው ሳቢ አለመሆኑን ገለጸ፡፡ 

የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ያለፉትን አሥራ አንድ ወራት የኮሚሽኑን የዕቅድ አፈጻጸም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሰኔ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ባቀረቡበት ወቅት ነው ይኼንን ችግር ያነሱት፡፡

እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፣ 12 ወንዶችና ሰባት ሴቶች በድምሩ 19 ሠራተኞች ሥራቸውን ለቀዋል፡፡ መሥሪያ ቤቱ ሠራተኞች መልቀቅና በምትካቸው መቅጠር ባለመቻሉ ባለፉት 11 ወራት ያጋጠመው ችግር በማለት ለፓርላማው አባላት አስረድተዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ለኮሚሽኑ ዕቅድ ማስፈጸሚያ ከመንግሥት የተፈቀደው የመደበኛ በጀት አነስተኛ ከመሆኑም በላይ፣ በየወሩ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የሚለቀቀው ወይም አንድ-አሥራ-ሁለተኛ የሚባለው አሠራር፣ በተለይም በኮሚሽኑ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች አሠራር ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩ ሌላው ኮሚሽኑን ያጋጠመው ተፅዕኖ እንደሆነ ኮሚሽነሩ  አስረድተዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙት እነዚህ ችግሮች ቢኖሩም፣ ኮሚሽኑ ያከናወናቸው ተግባራት መኖራቸውን ኮሚሽነሩ አስረድተዋል፡፡ በዚህም ረገድ በአጠቃላይ የ2007 ዓ.ም. አምስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ሕገ መንግሥቱን፣ የምርጫ ሕጎችንና ዓለም አቀፍ መሥፈርቶችን መሠረት ባደረገ ሁኔታ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብቶችን ጨምሮ የዜጎች ሰብዓዊ መብቶችን ባከበረ መንገድ እንዲፈጸም ክትትል ማድረጉን ገልጸዋል፡፡

የሴቶችና የሕፃናት መብትን ለማስጠበቅ እንዲቻል፣ በተለይም የመብት ጥሰት መንስዔ የሆኑትን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችና የግል ጥቃቶች ለመከላከል ብሎም ለማስወገድ የተጀመሩ ሕዝባዊ ንቅናቄዎችና መድረኮች እንዲጠናከሩ ኮሚሽኑ ያደረገው ድጋፍ እንዲሁ በበጀት ዓመቱ ከተከናወኑ ጠንካራ ክንውኖች መሀል የሚጠቀሱ መሆናቸውን ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል፡፡

ላለፉት አምስት ዓመታት ኮሚሽኑን በኮሚሽነርነት ሲያገለግሉ የነበሩት አባላት በአዲስ ለመተካት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኅብረተሰቡ የዕጩዎች ጥቆማ እንዲያደርግ ያስነገረ ሲሆን፣ በዚህም መሠረት በአዲሱ የፓርላማው የመጀመሪያ ዓመት  አዲስ ኮሚሽነር የሚመረጥ በመሆኑ፣ ይህ ሪፖርት በአምባሳደር ጥሩነህ አማካይነት የቀረበ የመጨረሻው ነው፡፡

 

የእነ አቶ መላኩ ፈንታ ክስ ለሁለተኛ ጊዜ የሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ አስነሳ

በቀድሞው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር በእነ አቶ መላኩ ፈንታ መዝገብ በከባድ ሙስና የተከሰሱ ነጋዴዎችና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የጉምሩክ አዋጅ ተጠቃሚ ሊሆኑ ይገባል ወይስ አይገባም በሚለው

ጉዳይ ላይ ለመወሰን፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉም እንዲሰጥ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 15ኛ ወንጀል ችሎት ሰኔ 12 ቀን 2007 ዓ.ም. ጉዳዩን መራለት፡፡

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክሱን መሠረት ያደረገው በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 411 (የመንግሥት ሥራን ለማያመች አኳኋን መምራት) እና በተሻሻለው የጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 622/2001 ላይ ነው፡፡ ይሁንና አዲሱ የጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 በቀድሞው ሕግ በወንጀልነት የተፈረጁ ድርጊቶችን የሚሽር ነው፡፡ ተከሳሾቹም ለፍርድ ቤቱ ያቀረቡት ጥያቄ በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 22(2) ላይ የወንጀል ክስ የቀረበበት ድርጊት ከተፈጸመ በኋላ የወጣ ሕግ ለተከሳሹ ጠቃሚ ሆኖ ከተገኘ፣ ከድርጊቱ በኋላ የወጣው ሕግ ተፈጻሚ እንደሚሆን ስለሚደነግግና የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 5(3)ም በተመሳሳይ ይኼንኑ የሚደነግግ በመሆኑ፣ በአዲሱ ሕግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከተሻሩት አንቀጾች ነፃ እንዲወጡ ነው፡፡

ይኼን ጥያቄ ካቀረቡት ተከሳሾቹ መካከል አቶ መላኩ ፈንታ፣ አቶ ገብረ ዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ (የቀድሞ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር)፣ አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር (የነፃ ትሬዲንግ ባለቤት)፣ አቶ ስማቸው ከበደ (የኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ባለቤት) እና ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ (የአዲስ ካርዲያክ ሆስፒታል መሥራችና ባለድርሻ) ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ አንዱ የሆኑት ዶ/ር ፍቅር ማሩ የተከሰሱት ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመመሳጠር የሕክምና ዕቃዎችን በሕገወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ አስገብተዋል ተብለው ነው፡፡ በአዲሱ የጉምሩክ አዋጅ ይኼ ድርጊት በገንዘብ የሚያስቀጣ እንጂ፣ የወንጀል ድርጊት ባለመሆኑ ነፃ መውጣት እንዳለባቸው ተከራክረዋል፡፡ ዓቃቤ ሕግ ግን ድርጊቱ ኮንትሮባንድ በመሆኑ ይኼ ድርጊት ግለሰቡን በወንጀል ከመጠየቅ አያድናቸውም ሲል ተከራክሯል፡፡ በተጨማሪም የወንጀል  ሕግ አንቀጽ 411 አሁንም እንዳልተሻረ አስታውሷል፡፡

ፍርድ ቤቱ የተከራካሪ ወገኖችን ክርክር ከሰማ በኋላ አዲሱ አዋጅ ተከሳሾቹን ይጠቅማል ወይስ አይጠቅምም የሚለውን ጭብጥ መርምሯል፡፡ ፍርድ ቤቱ በአዲሱ የጉምሩክ አዋጅ በቀድሞው አዋጅ ወንጀል የነበሩ ድርጊቶች መሻራቸውን ማረጋጡን ገልጿል፡፡ ይሁንና በአዲሱ አዋጅ አንቀጽ 182 ላይ ‹‹በሌሎች ሕጎች የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ይኼ አዋጅ ከፀናበት ቀን በፊት የተጀመሩ ጉዳዮች በነበረው ሕግ መሠረት ፍፃሜ ያኛሉ፤›› ተብሎ መደንገጉ ልዩ ሁኔታን እንደሚፈጥር አስገንዝቧል፡፡ የወንጀል ሕጉ ጠቅላላ ሕግ በመሆኑና የጉምሩክ አዋጅ ደግሞ ልዩ ሕግ በመሆኑ፣ በመርህ ደረጃ ልዩ ሕግ ከጠቅላላ ሕግ ቅድሚያ ተሰጥቶት ተግባራዊ እንደሚሆን አመልክቷል፡፡ ነገር ግን ሕገ መንግሥቱን የሚፃረር ሕግ በሕግነት ፀንቶ የማይቆም በመሆኑ፣ አዲሱ ሕግ ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚጣጣም ስለመሆኑ መመርመር እንደሚያስፈልግ ፍርድ ቤቱ አስታውቋል፡፡

በፍርድ ቤቱ ዕይታ የአዲሱ የጉምሩክ አዋጅ አንቀጽ 182 በሕገ መንግሥቱ ከተቀመጡት አንቀጽ 9፣ 13 (ሕገ መንግሥቱ የበላይ ሕግ ስለመሆኑና ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚፃረር ማንኛውም ሕግና ውሳኔ እንደማይፀና ይደነግጋሉ) እና 22 ጋር የሚጣጣም ባይሆንም፣ ሕገ መንግሥቱን የመተርጎም ሥልጣን የሌለው በመሆኑ የዚሁ ሥልጣን ባለቤት የሆነው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጉዳዩን መርምሮ ሕገ መንግሥቱን በመተርጎም፣ ውሳኔውን ለሐምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. እንዲያቀርብ መርቶታል፡፡ 

ይኼው ክስ ከዚህ ቀደም ባስነሳው ሌላ ሕገ መንግሥታዊ ጥያቄ የከፍተኛ የፌዴራል መንግሥት ባለሥልጣናት ጉዳይ በጠቅላይ ፍርድ ቤት የመጀመርያ ደረጃ ሥልጣን እንዲታይ የሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 25/88 አንቀጽ 8(1)፣ በሕገ መንግሥቱ የተቀመጠውን ይግባኝ የመጠየቅ መብት የሚጥስ ነው ተብሎ እንዲሻር ማድረጉ ይታወሳል፡፡

 

የቻይና መንግሥት ከፍተኛ ቴክኖሎጂ የሚጠቀሙ የኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ ትኩረት እንዲደረግ፣ ዝቅተኛና መካከለኛ ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ያደረጉ ፋብሪካዎች ደግሞ ተነቅለው ወደ አፍሪካ እንዲሄዱ ማዘዙ ተሰማ፡፡

ከአፍሪካ አገሮች በተለይ ግብፅና ኢትዮጵያ ተመርጠዋል፡፡ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ ዕድገት ይበጃሉ ያላቸውን ፋብሪካዎች ለመቀበል፣ ከቻይና ናሽናል ዴቨሎፕመንትና ሪፎርም ኮሚሽን ጋር ለመደራደር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

የቻይና መንግሥት ዝቅተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ከአገር ወጥተው እንዲሠሩ ውሳኔ ያሳለፈው፣ አገሪቱ በዓለም አቀፍ ገበያ ውስጥ ያላትን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፍተኛ ቴክኖሎጂ የሚጠቀሙ ፋብሪካዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል በማለቱ ነው ተብሏል፡፡ 

ከዚህ በተጨማሪም በቻይና የአገልግሎት ዘርፍን ለማሳደግና ከዚህ ቀደም ርካሽ የነበረው የሰው ኃይል በአሁኑ ጊዜ እየተወደደ በመምጣቱ፣ ፋብሪካዎቹ ከአገር ወጥተው በማደግ ላይ ባሉት ኢትዮጵያና ግብፅ እንዲተከሉ መመርያ ማስተላለፉ ተነግሯል፡፡

ይህንን እንደ መልካም አጋጣሚ የተመለከተው የኢትዮጵያ መንግሥት፣ ለአገሪቱ ዕድገት ወሳኝ የሚባሉ ፋብሪካዎችን በመምረጥና የቻይና መንግሥት ሊያቀርብ ስለሚችለው የፋይናንስ ሁኔታ ድርድር እንዲያደርግ፣ ኃላፊነቱን ለገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር መስጠቱ ታውቋል፡፡

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሱፍያን አህመድ የሚመሩት የልዑካን ቡድን በቅርቡ ወደ ቻይና ተጉዞ፣ ከቻይና ብሔራዊ ዴቨሎፕመንትና ሪፎርም ኮሚሽን ኃላፊዎች ጋር የመጀርያውን ድርድር ማካሄድ እንደሚጀምር ምንጮች ገልጸዋል፡፡ 

የአገሪቱን ኢኮኖሚ ከግብርና በማላቀቅ በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ መሠረት ላይ ለማሳረፍ ያቀደው የኢትዮጵያ መንግሥት በተለይ ለጨርቃ ጨርቅ፣ ለቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ለብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ ለስኳር ልማትና ለኬሚካል ኢንዱስትሪ ልማት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቷል፡፡

ይህንን ዕቅድ ለማሳካትም በዶ/ር አርከበ እቁባይ የሚመራው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን፣ በአሥር ቢሊዮን ዶላር ወጪ በተለያዩ ከተሞች የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በማቋቋም ላይ ይገኛል፡፡

ወደ ኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲቀላቀሉ የሚመረጡት የቻይና ፋብሪካዎች በእነዚህ የኢንዱስትሪ ዞኖች ውስጥ ወይም ራሳቸው በሚያቋቁሟቸው የኢንዱስትሪ ዞኖች ውስጥ ፋብሪካዎቻቸውን እንዲተክሉ እንደሚደረግ፣ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ለማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን ለማምረት አመቺ መሆኑን ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ መንግሥት ኢንቨስትመንት በተለይም የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ተዋናዮችን ለማረበታታት ያወጣቸው በርካታ ሕጎችና ማበረታቻዎች፣ እንዲሁም በአገሪቱ ያለው የሰው ኃይል አገሪቱን ተመራጭ ማድረጉን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

  

 

በቴክኒክና በንግድ ሥራ የሠለጠኑ 63 ሴቶች ሰኔ 12 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመረቁ፡፡ በሥልጠናው በወተትና የሥጋ ምርት አቅርቦት፣ እንዲሁም የቁም ከብት ንግድ ላይ ክህሎት የሚያሳድግ ግንዛቤ ማግኘታቸውን በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

ሥልጠናውን ያዘጋጀው የአሜሪካ መንግሥት በዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲው (USAID) ሲሆን፣ በ2004 ዓ.ም. በሴቶች ላይ በተደረገ ጥናት በወተት ምርት፣ በእንስሳት ዕርባታ፣ በአመራር ዕውቀት፣ በንግድ ሥራ አገልግሎቶች ተደራሽነት፣ ውሳኔ በመስጠት፣ በስኬታማ የንግድ ሥራ ዕቅድ አዘገጃጀት ረገድ የታዩትን ክፍተቶች ለመሙላት ነው ተብሏል፡፡ 

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ ‹‹ወደፊትን መመገብ›› በተሰኘ ፕሮግራሙ በግብርና ዕድገት ፕሮግራም የእንስሳት ገበያ ልማትና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ በሚያስችል አቅም መመረቅ በተሰኙ መርሐ ግብሮች፣ በመጋቢት ወር 2007 ዓ.ም. ሥልጠና ሰጥቷቸዋል፡፡ በሥልጠናው የተካተቱት ሴቶች የሥራ ፈጠራ አቅም እንዳላቸው የታመነባቸው መሆናቸው በመግለጫው ተመልክቷል፡፡ ሴቶቹ በአስተዳደርና በሥራ አመራር ክህሎት ሥልጠና የተሰጣቸው ሲሆን፣ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዝ የንግድ ሥራ ዕቅድ በመንደፍ ረገድም የቴክኒክ ዕውቀት ማግኘታቸው ተገልጿል፡፡

ሠልጣኞቹ ከአማራ፣ ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል እንዲሁም ከትግራይ ክልል የተውጣጡ ናቸው፡፡ በቆይታቸው ያገኙትን ክህሎት በአካባቢያቸው ለሚገኙ ሴቶችም እንደሚያካፍሉ ይጠበቃል፡፡

ሴቶች በእንስሳት ዕርባታና በእንስሳት ምርት አያያዝ የሚጫወቱትን ሚና ማሳደግ ለቤተሰብም ሆነ በአገር ደረጃ ከፍ ያለ ጠቀሜታ አለው ያሉት የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ ተወካይ ካለን ሒዩስ ናቸው፡፡ እሳቸው እንደሚሉት በንግድ ሥራ አስተዳደርና በአመራር ላይ ያተኮረው ሥልጠና፣ በእንስሳት ዕርባታ ዕምቅ አቅም ያላቸው አርዓያ ሴቶች ላይ ማተኮሩ፣ በዘርፉ የመሪነቱን ሚና እንዲጫወቱ ያግዛቸዋል፡፡ በሥልጠናው ያልተካተቱ ሴቶችም በሠልጣኞቹ አማካይነት ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ 

 

መንግሥት የፓርቲዎቹን መግለጫ ውድቅ አድርጓል

በአንድ ቀን ልዩነት የአረና/መድረክ እና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በተለያዩ ሥፍራዎች ተገድለው በመገኘታቸው ምክንያት ሰማያዊ ፓርቲና አረና/መድረክ በመንግሥት ላይ ወቀሳ አቀረቡ፡፡

ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. በአማራ ክልል በምሥራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ማርቆስ ከተማ አቶ ሳሙኤል አወቀ የተባሉ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ ሲገደሉ፣ በማግሥቱ አቶ ታደስ አብረሃ የተባሉ የአረና/መድረክ አባል በትግራይ ክልል ምዕራብ ዞን ማይካድራ ከተማ  መገደላቸውን ሁለቱም ፓርቲዎች አስታውቀዋል፡፡

አረና/መድረክ ባወጣው መግለጫ አባሉ በምዕራብ ትግራይ ዞን የድርጅቱ ጉዳይ ኃላፊ ሆነው በ2007 ምርጫ ወቅት፣ የፓርቲውን ሥራ በማደራጀትና በማንቀሳቀስ ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ የቆዩ መሆናቸውን፣ ሰኔ 9 ቀን 2007 ዓ.ም. ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ለጊዜው ባልታወቁና ቤታቸው በመጡ ሦስት ሰዎች ግድያ እንደተፈጸመባቸው አስታውቋል፡፡

ፓርቲው የገዳዮቹን ማንነት አለመታወቁን በጠቆመበት መግለጫ፣ ሟች አባሉ ከግድያው ቀደም ብሎ በመንግሥት የፀጥታ ሠራተኞች ወከባና ማስፈራርያ ይደርስባቸው እንደነበር ጠቁሟል፡፡

‹‹ለጉዳተኛው የሕክምና ዕርዳታ እንዲደረግላቸው ለማስተባበርና ወንጀለኞችም ለመከታተልና ለማስያዝ የተደረገው ሙከራ በፖሊሶች አለመተባበር›› ሳይሳካ መቅረቱን በመግለጫው አረና/መድረክ አስታውቋል፡፡

በተመሳሳይም ሰማያዊ ፓርቲ አቶ ሳሙኤል የተባሉ አባሉ ከመገደላቸው በፊት፣ በደኅንነት ሠራተኞችና በአካባቢው ሹሞች የግድያ ማስፈራርያ ይደርሳቸው እንደበር ገልጿል፡፡

የምሥራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምርያ በበኩሉ አቶ ሳሙኤል በሁለት ግለሰቦች መገደላቸውን ገልጾ፣ አንደኛው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር ውሎ ሲመረመር ግድያውን መፈጸሙን ማመኑን አስታውቋል፡፡

ነገር ግን የፖሊስን መግለጫ ሙሉ በመሉ ውድቅ ያደረገው ሰማያዊ ፓርቲ፣ ‹‹የሰማዕታት ደም ይጮሃል፣ ይጣራል›› በሚል ርዕስ ሰኔ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ‹‹ይህ ሥርዓት በሕግም፣ በሞራልም ኢትዮጵያን የማስተዳዳር ብቃት የለውም፡፡ ወንጀለኞችን ለፍርድ ይቅረቡ እያልን አናላዝንም፣ ወንጀለኞቹ የመንግሥት አካላት ናቸውና፤›› ሲል መንግሥትን ምንም ዓይነት ፍትሕ እንደማይጠብቅም ገልጿል፡፡

እንዲሁም አረና/መድረክ በበኩሉ በትግራይ ክልል ከ17 በላይ አባላት ጨምሮ በኦሮሚያ፣ በአማራና በደቡብ ክልሎች በአባላት ላይ እስራት፣ ግርፋትና ግድያ እየተፈጸመባቸው መሆኑን በመግለጫው አስፍሯል፡፡

መንግሥት በበኩሉ ክሶቹን ውድቅ በማድረግ ተገደሉ በተባሉት ሰዎች እጁ እንደሌለበት ገልጾ፣ ትችቶቹ ሁሉ እውነትነት የሌላቸው መሆኑን አስታውቋል፡፡

በጉዳዩ ላይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል፣ ‹‹ሁለቱም የተቃዋሚዎች አባላት በግለሰቦች መገደላቸውንና ጉዳዮችን ይዞ ለፍርድ ለማቅረብ ፖሊስ ምርመራውን ቀጥሏል፡፡ መንግሥት እንደሚያምነው የሁለቱ ዜጎች መገደል ምንም ዓይነት ፖለቲካዊ ይዘት የለውም፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በተለይ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ግድያ አሳዛኝ እንደሆነ፣ ሟች ከቀድሞ ደንበኞቹ ጋር በተፈጠረው አለመግባባት መገደሉን ፖሊስ አረጋግጧል  ካሉ በኋላ፣ አቶ ታደሰ በማይታወቁ ሰዎች ከመገደላቸውና ፖሊስ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ከማወቃቸው ውጪ፣ ገና መረጃው እንዳልደረሳቸው አቶ ሽመልስ ገልጸዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ የአረና/መድረክ አባልን ግድያ በተመለከተ የትግራይ ክልል የፀጥታና የደኅንነት ቢሮን ምላሽ ለማግኘት ሪፖርተር ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም፣ ኃላፊዎችን በስብሰባ ምክንያት ለማግኘት ባለመቻሉ አስተያየታቸውን ማካተት አልተቻለም፡፡ 

 

የ120 ሚሊዮን ዶላር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ስምምነት ተፈረመ

ኢትዮጵያና ኬንያን በኤሌክትሪክ ኃይል ለማገናኘት፣ በኢትዮጵያ በኩል የ433 ኪሎ ሜትር ኃይል ማስተላለፊያ መስመር መገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ፡፡ ስምምነቱ ሰኔ 12 ቀን 2007 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀና ግንባታውን ለማካሄድ የተመረጠው የቻይናው ስቴት ግሪድ እህት ኩባንያ ሲኢቲ ኩባንያ ምክትል ፕሬዚዳንት ሚስተር ቸንግ ዊ በሸራተን አዲስ ተፈራርመዋል፡፡ የኃይል መስመሩ አንደኛው ኮንትራት በ120 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የሚገነባ ሲሆን፣ ወጪው በአፍሪካ ልማት ባንክ ይሸፈናል ተብሏል፡፡ ግንባታው ከወላይታ ሶዶ ተነስቶ ኬንያ ድንበር ሞያሌ ላይ የሚቆም ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ያለውን 612 ኪሎ ሜትር የኃይል መስመር ኬንያ ትገነባለች፡፡ ኢትዮጵያ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ ለመሸጥ ስምምነት ያረገች በመሆኗ፣ አንዱን ኪሎ ዋት በሰባት የአሜሪካ ሳንቲም ለመሸጥ ስምምነት ተደርጓል፡፡

የቻይናው ኩባንያ የፈረመው በኢትዮጵያ በኩል ከሚገነቡት ሁለት ኮንትራክተሮች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በቅርቡ አንደኛው ኮንትራት ይፈረማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በኬንያ በኩል የሚገነባው የኃይል መስመር በሦስት ኮንትራቶች የተከፈለ ነው፡፡ ግንባታውን ለማካሄድ አሸናፊ ከሆኑ የህንድ ኩባንያዎች ጋር በቅርቡ ስምምነት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህ ግንባታ በ26 ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል፡፡ የቻይናው ኩባንያ ምክትል ፕሬዚዳንትም ግንባታው በተያዘለት ጊዜ ገደብ እንደሚጠናቀቅ ቃል ገብተዋል፡፡ በምሥሉ ላይ ኢንጂነር አዜብ አስናቀና የቻይናው ኩባንያ ምክትል ፕሬዚዳንት ቸንግ ዊ ስምምነቱን ከተፈራረሙ በኋላ፡፡

 

የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ባለፉት 11 ወራት አርባ ያህል ከፍተኛ ኪሳራ ሊያስከትሉ የሚችሉ የሳይበር (ኮምፒዩተርን መሠረት ያደረጉ) ጥቃቶችን ማምከኑን፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ፡፡

ኤጀንሲው ከተቋቋመ በርካታ ዓመታት ቢያልፉም፣ እንደ አዲስ በተነደፈው አሠራር መሠረት ለመጀመርያ ጊዜ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ሰኔ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ለምክር ቤቱ አቅርቧል፡፡

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ሜጄር ጄኔራል ተክለ ብርሃን ወልደ አረጋይ እንደገለጹት፣ የአገሪቱን ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ለማጥቃት የተሰነዘሩ የሳይበር ጥቃቶች ነበሩ፡፡

‹‹ወደ አገራችን የሚሰነዘሩ የሳይበር ጥቃቶች በርካታና ብዙ መልክ  ያላቸው ናቸው፤›› ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ‹‹አንዳንድ የጥቃት ዓይነቶች አገራችንን በተለየ ሁኔታ ዒላማ ያላደረጉ ነገር ግን ማንኛውም ተጋላጭ መሠረተ ልማትን የሚያጠቁ ሲሆን፣ እንደዚህ ዓይነት ጥቃቶች በየቀኑ ከዚህ አልፎም በየሰዓቱ የሚሠራጩ ናቸው፤›› ብለዋል፡፡

ሌሎች ሆን ተብሎ የኢትዮጵያን የሳይበር መሠረተ ልማት ለማጥቃት የሚለቀቁ ቫይረሶች መኖራቸውን የገለጹት ሜጀር ጄኔራል ተክለ ብርሃን፣ ወደ አርባ የሚጠጉ በአጠቃላይ መሠረተ ልማቱንና የተወሰኑ ቁልፍ ተቋማትን ዒላማ ያደረጉ ከፍተኛ ኪሳራ ሊያደርሱ የነበሩ የሳይበር ጥቃቶችን ለማምከን መቻሉን አስረድተዋል፡፡ ‹‹ጥቃቱ ቢደርስ ኖሮ ሊያስከትል የነበረው ኪሳራ በጣም ትልቅ ነበር፤›› ብለዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ ከዚህ ውጪ የሳይበር ጥቃቶቹ በየትኞቹ ቁልፍ ተቋማት ላይ እንደተሠነዘሩ፣ እንዲሁም ከየት አካባቢ እንደሆነ አልገለጹም፡፡ 

ከዚህ በተጨማሪ በቴሌኮም ማጭበርበር ተግባር ላይ የተሰማሩ 55 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን፣ ለዚህ የወንጀል ተግባር ሲጠቀሙባቸው የነበሩ ወደ 170 የተራቀቁና ዘመናዊ ሕገወጥ የቴሌኮም መሣሪያዎች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡ ግለሰቦቹ በቴሌኮም ወንጀል ተሰማርተው በነበረበት ወቅት 700 ሚሊዮን ብር ኪሣራ በኢትዮ ቴሌኮም ላይ ማድረሳቸውንም ተናግረዋል፡፡

ኤጀንሲው የተሰጠውን ተልዕኮ በተቀናጀና በተጠናከረ መንገድ ለመወጣት እንዲችል ቀደም ሲል የተጀመረውን በዘርፉ ያሉትን የሕግ፣ የፖሊሲና የስታንዳርድ ክፍተቶች በመለየት ክፍተቶችን ለመዝጋት እየሠራ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡

ከእነዚህም መካከል የሳይበር ወንጀል ሕግ ረቂቅ ማዘጋጀት አንዱ ሲሆን፣ በ2005 ዓ.ም. ለካቢኔ ቀርቦ የነበረ ነው፡፡ ረቂቅ ሕጉ ከፍትሕ ሚኒስቴር ጋር በመሆን እንደገና እንዲታይ በመወሰኑ በድጋሚ በመታየት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

  

እስራኤላዊው ምሁር ከስደት ተመላሽ ወገኖች አክራሪነት እንዳላጠላባቸው እርግጠኛ መሆን ያስፈልጋል አሉ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥርጣሬውን አጣጥሏል

በዓለም አቀፍ የፀረ ሽብር ተቋም ከፍተኛ ተመራማሪና በእስራኤል መንግሥት የዲፕሎማሲና የስትራቴጂ ተዛምዶ ማዕከል አማካሪ የሆኑት ዶ/ር ዮናታን ፋይን፣ ኢትዮጵያ ከስደት የምትመልሳቸው ዜጐቿ ከአክራሪነት ጥላ የራቁ መሆናቸውን

ማረጋገጥ እንደሚገባት አሳሰቡ፡፡ የደኅንነትና ዓለም አቀፍ ጥናት ምሁሩ ከሪፖርተር ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት ከየመን፣ ከሊቢያና ከሌሎችም የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች ወደ አገር ቤት በሚመለሱ ዜጐች ላይ መንግሥት አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት፡፡

ዓለም አቀፍ የሽብር ቡድኖችና ጽንፈኛ እምነትን የሚያራምዱ ግለሰቦችና ድርጅቶች በሞሉባቸው የመካከለኛው ምሥራቅና የሰሜን አፍሪካ አገሮች በብዛት የሚገኙት ኢትዮጵያውያን፣ በአንድም ሆነ በሌላ አጋጣሚ በእነዚህ አካላት ተፅዕኖ ሥር ወድቀው ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡ ይህም እነዚህ ወገኖች ወደ አገራቸው ገብተው ከሚገጥሙዋቸው የመልሶ መዋሀድ ተግዳሮቶች ጋር ተዳምሮ ላልተፈለገ የባህርይ ለውጥ ሊዳርጋቸው እንደሚችል ምሁሩ ገልጸዋል፡፡

ይህ ጥርጣሬ ለምን እንደገባቸው ተጠይቀው የመለሱት ምሁሩ፣ በተለያዩ የዓለም አገሮች የተደረጉ ጥናቶች የሚያሳዩት መረን ላወጣ አፈንጋጭነትና አክራሪነት እርሾ የሚሆኑት ባህርያት በሆነ ወቅት ወደ አገር ቤት ተመልሰው መኖር በሚጀምሩ ዜጎች ምክንያት የሚፈጠሩ ናቸው፡፡ በተለይ በርካታ ዜጐቿን በስደት የምታጣው አፍሪካ ዜጎቿ በልዩ ልዩ የዓለም ክፍሎች ከሚገጥማቸው የኑሮ ውጣ ውረድ ጋር ተዳምሮ፣ ለአዳዲስና የኑሮ ሁኔታን ሊቀይሩ ይችላሉ ለተባሉ አስተሳሰቦች በቀላሉ የመንበርከክ ዕድል እንዳላቸውም ገልጸዋል፡፡ በግብፅ፣ በሊቢያ፣ በምዕራብና በመካከለኛው አፍሪካ የሚገኙ በርካታ ዜጐች በእነዚህ አዳዲስ አስተሳሰቦች በመማረካቸው ምክንያት ወደ አገራቸው ሲመለሱም ይህንኑ አቋማቸውን እንደሚገፉበት ምሁሩ ያስረዳሉ፡፡

እስራኤላዊው ምሁር እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ የሚታየው ሁኔታ በዚህ ደረጃ የሚጠቀስ አለመሆኑን፣ የሕዝቡ የረጅም ዘመናት ተቻችሎ የመኖር ልማድ ለዚህ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን እንደሚያምኑ ገልጸው፣ ነገር ግን ይህ ሁኔታ በተለያዩ የውጭ ተፅዕኖዎችና አካባቢያዊ ሁኔታዎች ሊሸረሸር እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ ለዚህም ኢትዮጵያ የምትገኝበት የአፍሪካ ቀንድ አለመረጋጋትና ለአደገኛ ቡድኖች አመቺ ሥፍራ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ 

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ፣ የምሁሩ አስተያየት ምንም መሠረት የለውም ባይባልም ዓለም አቀፋዊ ገጽታን የተላበሰ መሆኑን በመጠቆም፣ ለጊዜው ግን ሥጋትን የሚያጭር አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡ ‹‹ይህንን ጉዳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀጥታ ባይመለከተውም፣ ጉዳዩ የሚመለከተው አካል ተገቢውን ሥራ እንደሚያከናውን እገምታለሁ፡፡ በእኛ በኩል ከየትም አገር የሚመጣ ዜጋ በኤምባሲዎችና በቆንስላዎች አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ ሲያሟላ እናስተናግዳለን፤›› ሲሉ አቶ ተወልደ ገልጸዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀዳሚ ዓላማም የዜጐችን ማንነትና ምንነት ማጥናት ሳይሆን፣ የነፍስ አድን ተግባሩን በማቀላጠፉ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ 

እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት አይኦኤም መረጃ፣ በየመን ብቻ ከ50 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን መኖራቸው ሲታወቅ እስካሁን ድረስ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸው ታውቋል፡፡ በሊቢያ የሚገኙ ዜጐችም በግብፅ በኩል ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ መሆናቸውንም የድርጅቱና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጀመረውን የነፍስ አድን ዘመቻ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት፣ በየትኛውም አገር የሚገኝ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ሊጠቀምበት የሚችል ዕድል መሆኑንም አቶ ተወልደ ገልጸዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በእስራኤል የሚገኙ ቤተ እስራኤላውያንን ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ምንም የቀረበ ጥያቄ አለመኖሩን፣ ጥያቄው ከቀረበ ግን እነሱንም ለመርዳት መንግሥት ዝግጁ መሆኑን አቶ ተወልደ አስታውቀዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለሪፖርተር ያጋሩት እስራኤላዊው ምሁር ዶ/ር ዮናታን፣ ኢትዮጵያውያኑ ቤተ እስራኤላውያን በእስራኤል እየገጠማቸው ያለው ፈተና አሳሳቢ መሆኑን፣ በአንዳንድ ምግባረ ብልሹ የፀጥታ ኃይሎች የሚፈጸመውን ጥቃትም አጥብቀው የሚቃወሙ በርካታ እስራኤላውያን መኖራቸውን በመጠቆም፣ የቤተ እስራኤላውያኑ የመብት ጥያቄዎች ሁሉ ምላሽ ሊያገኙ እንደሚገባቸው አቋማቸውን ገልጸዋል፡፡ ‹‹ይህ የዘር መድልኦ ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በሌሎችም ያደጉ አገሮች የሚስተዋል በመሆኑ፣ የእስራኤልን ሁኔታ አዲስ አያደርገውም፡፡ ከዚህ በፊት ሩሲያውያንን ጨምሮ ሌሎችም ትውልደ እስራኤላውያን በተመሳሳይ ችግር ውስጥ አልፈው እዚህ በመድረሳቸው፣ ቤተ እስራኤላውያኑም በቅርብ ጊዜ ችግራቸው እንደሚፈታ እገምታለሁ፤›› በማለት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተደጋጋሚ የሚከሰተውን የቤተ እስራኤላውያን ቁጣና የእስራኤል ባለሥልጣናትን ዘገምተኛ የመፍትሔ ዕርምጃ ገልጸውታል፡፡     

 

ባራክ ኦባማ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ሁሴን ኦባማ በሐምሌ ወር አጋማሽ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናትና ከአፍሪካ ኅብረት አመራሮች ጋር እንደሚመክሩ፣ ዋይት ሀውስ አስታወቀ፡፡

በሥራ ላይ ያለ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን ጎብኝቶ አያውቅም፡፡

የበርካታ አገሮች መሪዎች ይታደሙታል ተብሎ የሚጠበቀው ከሐምሌ 5 እስከ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. በሚካሄደው ሦስተኛው ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ጉባዔ ባራክ ኦባማ ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ይሁንና የዋይት ሀውስ መግለጫ ፕሬዚዳንቱ ለዚሁ ጉባዔ ስለመምጣታቸው የሚያወሳው ነገር የለም፡፡ 

ጉባዔው በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም. ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀውን የምዕተ ዓመቱ የልማት ግብን ይተካል የተባለለት ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመተግበር የሚያስችሉ የፋይናንስ ምንጮች ላይ ይመክራል፡፡ ይህንኑ ጉባዔ ለመከታተል ከ5,000 በላይ የአገር መሪዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የግል ተቋማት፣ የሲቪል ማኅበራትና የሚዲያ ተወካዮች አዲስ አበባ እንደሚመጡ ይጠበቃል፡፡

የዋይት ሀውስ የፕሬስ ጉዳዮች ኃላፊ ጆሽ ኧርነስት የኦባማ የኢትዮጵያ ጉብኝት አሜሪካ ከአፍሪካ አገሮች ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከርና በአፍሪካ ኢንቨስት የማድረግ ቁርጠኝነት ያላት መሆኑን ለማሳየት ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ አገሮችና ዜጎች ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲያመጡ፣ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት እንዲገቡና የደኅንነት ይዞታቸውን እንዲያጠናክሩ አሜሪካ የምታደርገው ጥረት አካል እንደሚሆንም ገልጸዋል፡፡ 

ፕሬዚዳንት ኦባማ በኬንያ የሚካሄደውን ዓለም አቀፍ የሥራ ፈጠራ ጉባዔ ከተከታተሉ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ታውቋል፡፡ የባራክ ኦባማ አባት ኬንያዊ ቢሆኑም ይህ ጉዟቸው እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚደረግ ነው፡፡   

 

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ምስማር ለማምረት ከሚያገለግለው ስታፋ ብረት (ዋየር ሮድ) ለዓመታት የቆየውን ታሪፍ ከለላ እንዲነሳ ማድረጉ ውዝግብ አስነሳ፡፡

የታሪፍ ከለላው መነሳት በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የምስማር ንግድ፣ አንድ ኩባንያ ብቻ በሞኖፖል እንዲቆጣጠር በር ከፍቷል የሚሉ ምስማር አምራች ኩባንያዎች ጉዳዩን ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ወስደውታል፡፡

ስታፋ ብረት ላይ የታሪፍ ከለላ በመነሳቱ ቅሬታቸውን ካቀረቡት 76 ፋብሪካዎች መካከል 46 የሚሆኑት ትላልቅ የምስማር ፋብሪካዎች፣ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ በሚገኘው ኦሮሚያ ልዩ ዞን ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ከምስማር አምራቾች በተጨማሪ በታሪፍ ከለላ መነሳቱ በትግራይ፣ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ለውኃና ለአፈር ጥበቃ የሚያገለግለው ጋብዮን (በሽቦ የተሠራ መረብ) የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ይገኙበታል፡፡ 

ሚኒስቴሩ ሚያዚያ 3 ቀን 2007 ዓ.ም. ባስተላለፈው መመርያ የስታፋ ብረት ከውጭ ሲገባ፣ 20 በመቶ የጉምሩክ ታክስና አምስት በመቶ ዊዝ ሆልዲንግ ታክስ እንዲከፈል አድርጓል፡፡ ሚኒስቴሩ እዚህ ውሳኔ አይ የደረሰው በአገር ውስጥ ስታፋ ብረት በብቸኝነት የሚያመርተው ስቲሊ አርኤምአይ ኩባንያ ለመጥቀም ሲሆን፣ የአገር ውስጥ ምስማር አምራቾች ስታፋ ብረት ከስቲሊ አርኤምአይ በመግዛት ሥራቸውን እንዲያካሂዱ ለማድረግ የታሪፍ ከለላውን አንስቷል፡፡

ቅሬታ አቅራቢ ምስማር አምራቾች የተላለፈው መመርያ አንዱን ወገን ማለትም ጥሬ ዕቃውን ማምረት ለጀመረው ስቲሊ አርኤምአይ ኩባንያ ለመደገፍ የወጣ እንጂ ፍትሐዊነት የሌለው አሠራር ነው በሚል ይተቻሉ፡፡

“በስታፋ ብረት ላይ የሁለተኛ ደረጃ ታሪፍ ከለላ መነሳቱን ይበልጥ አስቸጋሪ ያደረገው የስታፋ ብረት አገር ውስጥ ማምረት የጀመረው እስቲሊ አርኤምአይ እህት ኩባንያ የሆነው አስመን ላለፉት 15 ዓመታት የምስማር ገበያን 65 በመቶ ድርሻ የያዘ በመሆኑ ነው፤” በማለት ቅሬት አቅራቢ ኩባንያዎች ለሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት ባስገቡት ደብዳቤ ተገልጿል፡፡

ስቲሊ አርኤምአይ እና እህት ኩባንያው አስመን የስታፋ ብረትና የምስማር ዋጋ በሞኖፖል ለመወሰን እንዲችሉ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል በማለት፣ የሚኒስቴሩን መመርያ አግባብነት የሌለው እንደሆነ የቅሬታ አቅራቢዎቹ ደብዳቤ ጨምሮ ያስረዳል፡፡ የስቲሊ ኤምአርአይ የኦፕሬሽንና ፖሊሲ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ለማ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ስታፋ የሚሸጥበት ዋጋ ለሁሉም አምራች ኩባንያዎችም ሆነ ለእህት ኩባንያ አንድ ነው በማለት ምሳሌ ጠቅሰው አስረድተዋል፡፡ ደብዳቤው ሚኒስቴሩ መመርያውን ካስተላለፈ ከጥቂት ወራት በኋላ ጉዳዩን የሚያጠና ኮሚቴ ተቋቁሞ እንደነበርም ያስታውሳል፡፡ ኮሚቴውን የንግድ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ አህመድ ኑሩ የመሩ ሲሆን፣ ኮሚቴው ባካሄደው ጥናትም ስቲሊ አርኤምአይ የስታፋ ብረት በበቂ መጠንና በሚፈለገው ጥናት እያመረተ መሆኑን፣ የቀረበው የሞኖፖሊ ሥጋትም “በአሠራር ማስወገድ እንደሚቻል” በመጥቀስ የታሪፍ ማሻሻያው ተገቢ መሆኑን አስተያየት ሰጥቷል፡፡

የብረት አምራቾች ግን ይህንን ሐሳብ በፍፁም አልተቀበሉትም፡፡ የታሪፍ ከለላው የተነሳው ስቲሊ አርኤምአይን ሆን ብሎ ለመጥቀም ነው በማለት መከራከርያቸውን ያቀርባሉ፡፡ ይህ ውሳኔ የኢንቨስትመንት ፈቃድና የኢንቨስትመንት ማበረታቻ በተሰጣቸው በርካታ አምራቾች ላይ ሊያስከትል የሚችለው ተፅዕኖ አልታየም፡፡ ስቲሊ አርኤምአይ ከሚያመርታቸው ልዩ ልዩ ምርቶች አንዱን በመነጠልና በአንዱ ምርት ላይ ያነጣጠረና በርካታ አምራቾችን ከገበያ የሚያስወጣ ነው በማለት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ይናገራሉ፡፡ 

የበለጠ እሴት ጭማሪ ያለውና ከፍተኛ የሰው ኃይል የሚቀጥረው የምስማር ፋብሪካ ከውጭ በሚያስገባው የስታፋ ብረት ላይ የተነሳው የታሪፍ ከለላ በጥልቀት ያልታየና በጥናት ላይ ያልተመሠረተ ነው በማለት፣ ቅሬታቸውን በጽሑፍ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አቅርበዋል፡፡ 

የምስማር ፋብሪካዎቹ እንደሚሉት የታሪፍ ከለላ በመነሳቱ ስታፋ ብረት ከውጭ በማስገባት ምስማር ማምረት አዋጭ አይደለም፡፡ ከስቲሊ አርኤምአይ ስታፋ ብረት ገዝቶ ምስማር ማምረትም አዋጭ አይደለም ይላሉ፡፡

አዋጭ ያልሆነበት ምክንያት ሲያብራሩ፣ በተወሰደው ዕርምጃ የጥሬ ዕቃ መግዣና የምርቱ የመሸጫ ዋጋ በዋናነት የሚወሰኑት ስቲሊ አርኤምአይ እና እህት ኩባንያው አስመን ናቸው፡፡ በዚህ ምክንያት ለብዙ ዓመታት በሥራ ላይ የቆዩ የምስማር አምራች ኩባንያዎች፣ ‹‹ከሥራ እንድንወጣ እያደረገን ነው›› በማለት ቅሬታቸውን አስተጋብተዋል፡፡ “በተቀመጠው አቅጣጫ ጥሬ ዕቃ ከስቲሊ በመግዛት ሥራችንን እናስቀጥል ብለው የጀመሩ አንዳንድ የምስማር ፋብሪካዎችም ቢሆኑ፣ በዋናነት በስቲሊና በአስመን እየተፈጠረ ባለው የዋጋ መዛባት ሥራውን በተገቢው መንገድ ለመቀጠል ተቸግረዋል፤” በማለት ቅሬታ አቅራቢዎቹ በደብዳቤ ይገልጻል፡፡ 

በአቶ አህመድ የሚመራው ኮሚቴ በምስማር አምራቾቹ የቀረበው የሞኖፖሊ ሥጋት በአሠራር ማስወገድ እንደሚቻል የገለጸ ቢሆንም፣ የሞኖፖሊ ሥጋት እንዴት እንደሚወገድ የሚገልጽ የአሠራር ዘዴ ግን አያይዞ አላቀረበም በማለትም ይወቅሳሉ፡፡ 

“በስታፋ አምራቹ ስቲሊ አርኤምአይ እና በምስማር ምርት ትልቁን ድርሻ በሚያመርተው እህት ኩባንያው አስመን የሞኖፖል አሠራሮች ለማስወገድ የሚያስችል አሠራር ተቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ ሲገባ፣ አንድ ወገን ብቻ በማየት የተወሰነው ውሳኔ በዋጋ ላይ እንደተጠበቀው ከፍተኛ ችግር ያስከተለ መሆኑንና እንዲያውም አንዳንድ ፋብሪካዎች ከነጭራሱ እስከ መዘጋት ደርሰዋል፤” በማለት ቅሬታ አቅራቢ የምስማር ፋብሪካዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባቀረቡት ቅሬታ ይገልጻሉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ቅሬታ አቅራቢዎቹ እንደሚሉት ስቲሊ አርኤምአይ በስታፋ ብረት የነበረው ከለላ ሲነሳ፣ የምስማር ፋብሪካዎች የስታፋ ብረት ከውጭ ሲያስገቡና የምስማር ነጋዴዎች ያለቀለት ምስማር ከውጭ ሲያስገቡ የሚከፍሉት የጉምሩክ ቀረጥና ዊዝ ሆልዲንግ ታክስ ተመሳሳይ ስለሚሆን፣ ስታፋ ብረት ከውጭ አስገብቶ ምስማር ከማምረት ይልቅ ያለቀለት ምስማር በተመሳሳይ ቀረጥ ከውጭ አስመጥቶ መሸጥ የቀለለ እንደሆነ፣ የምስማር አምራቾች ከአስመጭዎች የተሻለ ከለላ እንደሚያስፈልጋቸው በመግለጽ አቤቱታቸውን አቅርበዋል፡፡

ነገር ግን የጥናት ቡድኑ “ይህ ጉዳይ ወደፊት ሊጠና ይገባል” በማለት ጉዳዩን በቀላሉ እንዳለፈውም ይጠቁማሉ፡፡ በምስማር ፋብሪካዎች የተነሱት ሥጋቶችና ችግሮች ከከለላው መነሳት ጋር ተያይዘው ካልተመለሱ የታሪፍ ከለላ ብቻ ማንሳቱ ለአንዱ ወገን ያደላ መሆኑን፣ ይህም የመልካም አስተዳደር እንዲሁም ፍትሐዊነት ጥያቄ የሚያስነሳ ነው በሚል ኩባንያዎቹ የቅሬታቸውን ስፋት በጽሑፍ አቅርበዋል፡፡ የተወሰደው ዕርምጃ ያስገኛል ተብሎ ከሚጠበቀው ፋይዳ አንፃር ሲታይ ያስከተላቸው ችግሮች ሚዛን የደፉ በመሆናቸው፣ ወደ ተግባር ሲለወጥም የተገመቱ ሥጋቶችን ለመከላከል አስቸጋሪ ስለሆነና እንዲሁም በውሳኔው ችግሮች ሲከሰቱ ለመፍታት የሚያስችል ሥርዓት አብሮ ያልታየ በመሆኑ፣ በብዙ መመዘኛዎች ሲታይ በስታፋ ብረት ላይ የተነሳው ከለላ እንደገና ሊጠና ይገባል በማለት ምስማር አምራች ኩባንያዎች ቅሬታቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አቅርበዋል፡፡

ስቲሊ አርኤምአይ በመስከረም 1997 ዓ.ም. በ486 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት የብረት ማቅለጥና የሮሊንግ ፋብሪካ በማቋቋም ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ ከዚህ በመቀጠል ኩባንያው አቅሙን በማሳደግ በአገር ውስጥ የሚመረት ስታፋ ብረት ባለመኖሩ በ726 ሚሊዮን ብር ወጪ ታኅሳስ 2006 ዓ.ም. አዲስ ፋብሪካ አቋቁሟል፡፡ ድርጅቱ በአጠቃላይ ሦስት ፋብሪካዎች አሉት፡፡ እነዚህ ፋብሪካዎች በዓመት 30 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በመጠቀም የአርማታ ብረትና ስታፋ ብረት ያመርታሉ፡፡ ስቲሊ አርኤምአይ ያቋቋመው አስመን ኩባንያ በበኩሉ ስታፋ ብረት በመጠቀም የተለያዩ ምስማሮችን ያመርታል፡፡ ስቲሊ አርኤምአይ ለሪፖርተር በሰጠው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ የግል ባለሀብቶች ወደ ኢንዱስትሪ ልማት ቀድመው ለሚገቡ ባለሀብቶች መንግሥት ሰፊና ጠንካራ ድጋፍ እንዳደረገለት አስረድቷል፡፡ “ይህ ከለላ የተሰጠው ለስቲሊ ሳይሆን ለብረት አምራች ኢንዱስትሪ ስለሆነ የኋልዮሽ የእሴት ጭማሪ አድርገው መዋለ ንዋያቸውን ላፈሰሱ ባለሀብቶች የተሰጠ ነው፤” በማለት አቶ ተፈራ ገልጸዋል፡፡ “በዚህ መሠረት ወደ ኢንዱስትሪው ቀድመው ለሚገቡም ሆነ የምርት ሰንሰለቱን ጠብቀው ለሚሠሩ፣ የታክስ ከለላና ሌሎችንም ማበረታቻዎች ይሰጣል፤” በማለትም መንግሥት ያደረገለትን ድጋፍ አስረድቷል፡፡ ኩባንያው በመቀጠል መንግሥት እነዚህን ማበረታቻዎች የሚሰጠው ባለሀብቶች በእነዚህ ማበረታቻዎች ተበረታተው በሰፊው ወደ ልማቱ እንዲገቡና በአገሪቱ የተያዘው የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ ግቡን እንዲመታ ለማድረግ እንጂ፣ የተወሰኑ ሰዎችን ጠቅሞ ሌላውን ለመጉዳት አይደለም ብሏል፡፡ 

ኩባንያው የቀረበበትን ክስ በሚመለከት እንደገለጸው፣ ከአሁን በፊት ስታፋ ብረት ከሚጠይቀው የተራቀቀ ቴክኖሎጂ፣ ዕውቀትና ከፍተኛ የካፒታል መጠን ምክንያት በአገሪቱ የማይመረት ነበረ፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ስቲሊ አርኤምአይ ለአርማታ ብረት እንደተደረገው ሁሉ የስታፋ ብረት በአገር ውስጥ በመመረቱና ምንም እንኳ ስታፍ ብረት ከአርማታ ብረት ጋር ሲነፃፀር የሚጠይቀው የማምረቻ ሒደትና የሚፈጀው ወጪ ከፍተኛ ቢሆንም፣ ለአርማታ ብረት ከተሰጠው የታክስ ከለላ እኩል ከለላ እንዲሰጠው መንግሥት ወስኗል፡፡ ይህም ምስማር ፋብሪካዎች ያቀረቡት በዘርፉ ውስጥ ለአንድ ዓይነት ምርት ብቻ ከለላ ተሰጥቷል የሚለው ትክክል አለመሆኑን ያስረዳል ሲሉ አቶ ተፈራ ተናግረዋል፡፡ 

“ይህ ማለት ከአሁን በፊት ለምስማር ጥሬ ዕቃነት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ከውጭ ሲገባ የነበረው የስታፋ ብረት ላለፉት አሥራ አምስት ዓመታት ሲደረግለት የነበረው የታክስ ከለላ ተነስቶ ቀረጥ እንዲቀረጥበት አደረገ እንጂ፣ ከውጭ ማስመጣት አልተከለከለም፤”  በማለት የስቲሊ አርኤምአይ መረጃ ይተነትናል፡፡

“ይህ የመንግሥት ውሳኔ የስታፋ ምርት በከፍተኛና በብዛት አገር ውስጥ የሚመረት በመሆኑ ካለው የኢንዱስትሪ ፖሊሲና የአገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ቁጠባ ከማጎልበት አንፃር ተመልክቶ የወሰነው ጉዳይ ነው፡፡ ውሳኔውም የተሰጠው ለእኛ ድርጅት ሳይሆን ለምርቱ የተሰጠ ዕውቅና ነው፤” በማለትም አክሏል፡፡

በአሁኑ ወቅት በአንድ ወገን ስቲሊ አርኤምአይ በሌላ ወገን ደግሞ በርካታ ምስማር አምራቾች በከፍተኛ ደረጃ በመወዛገብ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህንን ውዝግብ ለመፍታት የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴርና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያዳረጓቸው ጥረቶች ያልተሳኩ በመሆናቸው፣ ቅሬታ አቅራቢዎቹ መንግሥት በመስከረም 2005 ዓ.ም. ባሳተመው የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ሰነድ ላይ በተዘረዘረው መሠረት ልንስተናገድ ይገባል በማለት ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጉዳያቸውን መውሰዳቸውን አስታውቀዋል፡፡

 

ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም ለሌላ ለቅሶ በመሄድ ላይ የነበሩ ዜጎች ተደብድበው ተመልሰዋል በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ሰኔ 8/2007 ዓ.ም ደብረማርቆስ ከተማ የተገደለው የሳሙኤል አወቀ ለቅሶ እንዳይደርሱ ታገዱ፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ዛሬ ሰኔ 13/2007 ዓ.ም በጠዋት ከአዲስ አበባ ተነስተው የሳሙኤል አቀወ ቤተሰቦች ወደሚገኙበት ምስራቅ ጎጃም ዞን ግንደወይን እያቀኑ በነበረበት ወቅት አባይ ድልድይ ላይ […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ማኅበረ ቅዱሳንን በመወንጀል ‹‹ወጣቶቹን ሰብስባችሁ እሰሩልን›› ያሉ አስተዳዳሪዎች የፖሊስ እና የደኅንነት አካላትን በተባባሪነት ወቀሱ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳንን እንደተቋም መወንጀል አትችሉም፤ ፖሊስ የእናንተ ብቻ አይደለም፤ መጀመሪያ ራሳችኹን ፈትሹ›› /ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም/ የቅድመ ውይይት ምክክሩና ውይይቱ፣ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር የወሳኝነት ድርሻ ያላቸውን ማኅበረ ካህናትን፣ ማኅበረ ምእመናንና የሰንበት ት/ቤቶች ተወካዮችን ሊያካትት ይገባል፡፡ (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፭ ቁጥር ፰፻፭፤ …

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ በደቡብ ክልል አንድ የምርጫ አስተባባሪው አርብለት ተገድለው መገኘታቸውን አስታወቀ። የተቃዋሚ ፓርቲም በምርጫ 2007 ዙሪያ የዛሬውን ጨምሮ 4 አባላቱና ደጋፊዎቹ መገደላቸውን አስታውቋል። በዚህ ሳምንት እንደተገደሉ ተቃዋሚዎች ከገለጿቸው ሶስት ሰዎች በተጨማሪ በኦሮሚያና ደቡብ ክልል ህይወታቸው ማለፉ የተገለጸው አጠቃላይ ቁጥር ስድስት ደርሷል። በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ የተገደሉት አቶ ብርሃኑ ኤረቦ በትናንትናውለት በሁለት […]

ወደ ሚኒስቴሩ ካመሩት 25 አለቆች 20 ያኽሎቹ በዋና ሥራ አስኪያጁ በተደረገባቸው ጫና ያለፍላጎታቸው እንዲሔዱ መገደዳቸውን እየተናገሩ ነው በየሰንበት ት/ቤቶቹ የዕቅበተ እምነት፣ የመልካም አስተዳደር እና የፍትሕ መነሣሣት ማኅበረ ቅዱሳንን ወንጅለዋል፤ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን ልብሱን ለውጦ የመጣበት ነው›› /ኃይሌ ኣብርሃ/ ‹‹እንዴት አድርገን መከላከል እንዳለብን አሠልጥኑን እንጂ ስለ ሰላም መወያየት ምን ያደርግልናል?›› /የደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል አስተዳዳሪ/ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን …

አንጋፋው ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ በ67 ዓመታቸው አረፉ ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ – ግንቦት 13 ቀን፣ 1983 ዓ.ም. የወቅቱ የአገሪቱ ፕሬዘዳንት፤ ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርያም አገር ለቀው ሲወጡ ዜናውን ያነበበው ጋዜጠኛ ነበር። • ስርዓተ ቀብራቸው ነገ ሰኔ 14 ቀን 2007ዓ.ም በፈረንሳይ ለጋሲዮን ጉራራ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ 6፡00 ስዓት ይፈፀማል፡ መልክት ሼር በማድረግ ሀዘኑን አድርሱ፡፡ Filed under: NEWS

በባህርዳር ከተማ ትምህርታቸው ጨርሰው መንገድ ላይ ሲንቀሳቀሱ የተገኙት ወጣቶች ቦዞኔ እየተባሉ በጸጥታ አካላት ተገፈው ቤሻንጉል ወደሚገኘው የመንግስት እርሻ እንዲሰሩ መወሰዳቸው የተገኘው መረጃ አስታወቀ። ምንጮቻችን ከቦታው እንደገለፁት በባህርዳር ከተማ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ተመርቀው ስራ ያላገኙት ወጣቶች እለታዊ ንሮአቸውን ለመምራት ሲንቀሳቀሱ ስለተገኙ ብቻ በስርዓቱ ካድሬዎችና የፀጥታ ሃይሎች ቦዞኔ ተብለው እንዲያዙ ከተደረገ በኋላ ምንም ዓይነት የምግብና የህክምና አቅርቦት […]

በመከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ አባላት የሆኑት ወታደሮች በአገልግሎት ማብቂያ በሚል ምክንያት ያልተፈለጉትን ለማሰናበት ተብሎ በተካሄደ ስብሰባ ላይ ብዛት ያላቸው ወታደሮች አገልግሎታችን ግዜ ያበቃ በመሆኑ መሰናበት አለብን በማለታቸው የተነሳ ስብሰባው እንደተቋረጠ ታወቀ። ምንጮቻችን በላኩልን መረጃ መሰረት- በሰሜን እዝ በክፈለ ጦሩ አዛዦች ሜጀር ጀነራል ገብራት አየለና ብርጋዴር ጀነራል ማዓሾ በየነ የተመራው ስብሰባ ግንቦት 21 2007 ዓ/ም የተካሄደ […]