ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በብዙዎች ዘንድ አስቂኝ ተብሎ የተተቸውን የ2007 ዓም ምርጫ ተከትሎ በኦሮምያ ብቻ ከ640 በላይ የመድረክ ደጋፊዎች ሲታሰሩ፣ 66 በድብደባ ጉዳት ደርሶባቸዋል፣7 አባለት በጥይት ቆሰልዋል፣ 2 አባላት ደግሞ መገደላቸውን መድረክ አስታውቋል። ከምርጫው ጋር በተያያዘ የሚታሰሩ ሰዎች ቁጥር በሺዎች እንደሚቆጠር መረጃዎች ያመለክታሉ። መድረክ እንዳለው በምርጫ 2007 ማግሥት በመድረክ …

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክረምቱ ወቅት 119 የሚሆኑ የብአዴን አባላት በድሬዳዋ ከተማ የደህንነት እና መረጃ መሰብሰብ ስልጠና ተሰጥቷቸው በክልሉ ከተሰማሩት መካካል አንዱ የሆነው ሰራተኛው እንደገለጸው፣ ማንኛውም ደህህነት ሰራተኛ የስለላ ሪፖርቱን ተክሌ ለተባለ የደህንነት ሰራተኛ ሲያቀርብ መቆየቱን ለኢሳት ተናግሯል። ስልጠናውን ከወሰዱት የደህንነት ስራተኞች መካከል አንዳንዶች በምስራቅ ጎጃም ደብረማርቆስ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ …

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የማህበራዊ ጥናት መድረክ በቅርቡ ባካሄደው ጥናት በአዲስአበባ የግሉ የጤና ዘርፍ ከፍተኛ የጥራት መጓደልን ይዞ የተጋነነ የአገልግሎት ክፍያ እየጠየቀ መሆኑን ገልጿል። ጥናቱ በአዲስአበባ ከሚገኙ ክሊኒኮችና ሆስፒታሎች መካከል በ34ቱ ላይ ያተኮረ ሲሆን አገልግሎት ክፍያ (ዋጋን) በተመለከተ በመንግስት ሆስፒታሎች የካርድ ክፍያ አማካይ ዋጋ 5 ብር ሲሆን፣ በግል ክሊኒኮች …

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ” የሰማዕታት ደም ይጮሃል፤ ይጣራል” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ ፣ ወንጀሉን የፈጸሙት የመንግስት አካላት ናቸው ብሎአል። ወንጀለኞች ለፍርድ ይቅረቡ ብሎ እንደማይጠይቅም አስታውቋል። “ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም በደብረ ማርቆስ ከተማ እጅግ በሚሰቀጥጥ ጭካኔ እንደ እባብ ተቀጥቅጦ የተገደላው የሰማያዊ ፓርቲ ቆራጥ ታጋይ ሳሙኤል አወቀ የስርዓቱ አገልጋዩች …

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምርጫው በአሳፋሪ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከትሎ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች የመድረክ ደጋፊዎችን ቤቶች መቃጠላቸውን፣ መደብደባቸውንና ማሳደዳቸውን የአርባምንጭ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በተለይ በላካ ቀበሌ ብዙ ሰዎች አካላ ጎደሎ ሆነዋል፣ ቤቶቻቸውም ተቃጥሎባቸዋል የሚሉት ነዋሪዎች፣ የቀበሌ አመራሮች ከሰኔ 15 በሁዋላ መግቢያችሁን ፈልጉ እየተባሉ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ዳዊት ጉበዜ እና አዛውንት እናቱ ወ/ሮ …

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምርጫ ቦርድ የታገደው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ ) ፕሬዝደንት የሆኑት አቶ ማሙሸት አማረ ከሳምንታት እስር በሁዋላ በ5 ሺ ብር ዋስ እንዲፈቱ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢያስተላልፍም፣ ውሳኔው ለሁለተኛ ጊዜ በፓሊስ ተጥሶ ወደ እስር ቤት ተወስደዋል። ግንቦት 26/2007 ቦሌ የሚገኘው ችሎት አቶ ማሙሸት የቀረበባቸው ክስ እንደማያስከስሳቸው …

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ ሰበብ አስባቦች የሚጣልብን ቅጣትና እገዳ ተገቢ አይደለም በሚል ሰኔ 8፣ 2007 ዓም ለአንድ ቀን የስራ ማቆም አድማ አድርገው የነበሩት የሰሜን ጎንደር ዞን ሾፌሮች፣ ፣ ከአድማው በሁዋላ ችግራቸውን የሚሰማ እና መፍትሄ የሚሰጥ አካል ይኖራል ብለው ሲጠብቁ፣ በተቃራኒው ከስራ መታገዳቸውን ተናግረዋል። ሾፌሮች እና ባለሃብቶች እንደሚናገሩት “የመንግስትን ትእዛዝ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

“ለማንኛውም የምከፍለው ዋጋ ለለሃገሬና ለነፃነት ነው፡፡ በአካል ብታሰርም ህሊናዬ አይታሰርም፡፡ ከገደሉኝም ትግሌን አደራ!!! አገራችን የወያኔ ዘረኞች ብቻ መፈንጫ መሆን የለባትም! ትግላችን የነፃነት፤ ጉዞአችን ጎርባጣ፤ መድረሻችን ነፃነት፤ ታሪካችን ዘላለማዊ ነው፡፡” ሳሙኤል አወቀ ፊስቡክ ገፅ ላይ የተገኘ ሰኔ 8/2ዐዐ7 ዓ.ም፡፡ ምስራቅ ጎጃም ግንደ ወይን 1978 ዓ/ም ተወልዶ – በህግ የዲፕሎማ እና ዲግሪውን ሰርቷል፡፡ ሣሙኤል አወቀ የሠማያዊ ፓርቲ […]

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል የሽብርተኝነት ክስ የቀረበባቸው ሰባት የአየር ኃይል አባላት ነገ ሰኔ 12/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ይቀርባሉ፡፡ አቃቤ ህግ በሰኔ 7/2007 ዓ.ም ባቀረበባቸው ክስ ላይ እንደተመለከተው፣ ተከሳሾቹ የወንጀል ህጉ አንቀጽ 32(1)(ሀ)ን እና የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጅ አንቀጽ 7(1) ስር የተመለከተውን በመተላለፍ በሽብተኝነት ተከስሰዋል፡፡ በክሱ የተመለከቱት ተከሳሾች የሚከተሉት […]

የሳሙኤል አወቀ ስርዓተ ቀብር ላይ ደርሰው ወደ ደብረማርቆስ ሲመለሱ የነበሩት ለቀስተኞች ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ወደ ደብረማርቆስ እንዳይመለሱ መታገታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ለቀስተኞቹ በመኪና እየተመለሱ በነበረበት ወቅት ከቢቸና ወደ ደብረማርቆስ 80 ኪሎሜትር አካባቢ የምትገኝ የትመን የተባለች ቦታ ላይ ፖሊሶች ያስቆሟቸው ሲሆን ‹‹በዚህ ሰዓት መንቀሳቀስ አትችሉም›› በሚል የሾፌሩን መንጃ ፈቃድ ከቀሙ በኋላ ለሚሊሻ አስረክበዋቸው ሄደዋል፡፡ ለቀስተኞቹ […]

Originally posted on ሐራ ዘተዋሕዶ:
በቅ/ሲኖዶስ ውሳኔና በፓትርያርኩ ቡራኬ ያጠኑትን በማያገባቸው የገቡ ደንቆሮዎች ብለዋቸዋል የሰ/ት/ቤቶችን፣ ከኮብልስቶን ሥራ ይልቅ ከአፋችን ሙዳይ ምጽዋት የሚነጥቁ በሚል ዘልፈዋል በሒሳብ አያያዝ፣ በመልካም አስተዳደርና በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ያተኮረ ሥልጠና ተጀምሯል አለቆችን፣ ጸሐፊዎችንና ሒሳብ ሹሞችን ጨምሮ የሀ/ስብከቱና የክፍላተ ከተማ ሓላፊዎች ይሳተፋሉ ያለበቂ ዝግጅት የተጀመረው ሥልጠና ከወሬ ያላለፈ በሚል በተሳታፊዎች ክፉኛ ተተችቷል ለሥልጠናው ድጋፍ ከንግድ…

በቅ/ሲኖዶስ ውሳኔና በፓትርያርኩ ቡራኬ ያጠኑትን በማያገባቸው የገቡ ደንቆሮዎች ብለዋቸዋል የሰ/ት/ቤቶችን፣ ከኮብልስቶን ሥራ ይልቅ ከአፋችን ሙዳይ ምጽዋት የሚነጥቁ በሚል ዘልፈዋል በሒሳብ አያያዝ፣ በመልካም አስተዳደርና በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ያተኮረ ሥልጠና ተጀምሯል አለቆችን፣ ጸሐፊዎችንና ሒሳብ ሹሞችን ጨምሮ የሀ/ስብከቱና የክፍላተ ከተማ ሓላፊዎች ይሳተፋሉ ያለበቂ ዝግጅት የተጀመረው ሥልጠና ከወሬ ያላለፈ በሚል በተሳታፊዎች ክፉኛ ተተችቷል ለሥልጠናው ድጋፍ ከንግድ ባንክ የተገኘው ብር …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሰኔ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ ለመብት የሚታገሉ የከተማዋ ወጣቶች በአንድ የፖሊስ ጣቢያ ላይ የፈጸሙትን ጥቃት ተከትሎ የፌደራል ፖሊስና የጸረ ሽብር ግበረሃይል አባላት በከተማዋ ተገኝተው እጃቸው አለበት ብለው የጠረጠሩዋቸውን የቴፒ ወረዳ አስተዳዳሪን ጨምሮ 7 ፖሊሶችን ይዘው አስረዋል። ባለስልጣኖቹ የከተማውን ህዝብ ያነጋገሩ ሲሆን፣ ህዝቡ በነጻነት እጦት እየተሰቃየ መሆኑንና ወጣቶች እርምጃ የሚወስዱት ከዚህ ተነስተው …

ሰኔ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከሳምንት በፊት አልሸባብ የተባለው የሶማሊያ ታጣቂ ሃይል በቡርካባ ግዛት ጃሚዮ በሚባል ቦታ ላይ በኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ ድንገተኛ ጥቃት ከፍቶ ከ30 በላይ ወታደሮችን ከገደለ በሁዋላ፣ በርካታ ቁስለኞች ሞቃዲሹ በሚገኘው የአፍሪካ ህብረት ቁጥር ሁለት ሆስፒታል ውስጥ ተኝተው በመታከም ላይ ናቸው። አሚሶም በመባል የሚታወቀው በሶማሊያ የሰፈረው የአፍሪካ ህብረት ጦር በአልሸባብ …

ሰኔ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጋምቤላ ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት በጋምቤላ እርሻ ስራ ተሰማርተው የሚፈለግባቸውን የመሬት ኪራይ እዳ ባልከፈሉ 150 ባለሀብቶች ላይ ያወጣው የማሳሰቢያ ደብዳቤ እንደሚያመለክተው፤ የጋምቤላን መሬት የተቀራመቱት ከ90 በመቶ የሚልቁት የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች የትግራይ ተወላጆች ናቸው። ባለሀብቶቹ ከ2006 እስከ 2007 ሰኔ ወር ድረስ ያለባቸውን ውዝፍ እዳ አጠቃለው እንዲከፍሉ በወጣው የማስጠንቀቂያ …

ሰኔ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰኔ አንድ ተጀምሮ ሰኔ 20 የሚጠናቀቀው ግምገማ ከፍተኛ አመራሮችን፤አዛዦችን እንዲሁም ተራ የፖሊስ አባሎችን አካቷል። ከጉለሌ ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው የግምገማው ይዘት በፖሊስ ስነምግባር ዙሪያ ነው። በግምገማው ወቅት አንድ ባለ ሳጅን ማዕረግ ያለውና አንድ ኮንስታብል ፖሊስ በስልካቸው ውስጥ የግንቦት ሰባት፤የሰማያዊ ፓርቲና የሌሎች ተዛማጅ ድርጅቶች መረጃዎች በስልካቸው ውስጥ …

ሰኔ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የምርጫ 2007 ቅስቀሳን ተንተርሶ በህዝቡ ዘንድ የሚቀርቡትን ጥያቄዎች ለመመለስ በሚል ሲንቀሳቀስ የነበረው ኢህአዴግ፤ በከተማዋ በልዩ ልዩ ክፍለ ከተሞች ለረዢም አመታት ለኖሩ የይዞታ ባለመብቶች ከምርጫው በፊት ሰጥቶት የነበረውን በባለ ቀለም የብአዴን አርማና የኢትዮጵያ ሰንደቃላማ ያሸበረቀ የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ መልሶ በመውሰድ ውሳኔውን ለመሻር እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ ኢህአዴግ “በየክፍለ …

ጴትሮስ አሸናፊ በቅዱስ መጽሐፍ በአለማችን ረጅሙን እድሜ ማቱሳላ( 969 ዓመት )መኖሩን አንብበናል። (ዘፍ 5፣27) ከዚያም ለጥፋት ውሃ ምክንያት በሆነው የሰው ኃጢአት ምክንያት 120 መድረሱን ብናነብም ይስሐቅ 180 ዓመት መኖር ችሏል። ከዚያም ወርዶ 70 ከበዛም 80 ዓመት ሲሆን ይህንን ካለፈ ትርፉ ድካምና መከራ እንደሆነ ነግሮናል። «የዘመኖቻችንም ዕድሜ ሰባ ዓመት፥ ቢበረታም ሰማንያ ዓመት ነው ቢበዛ ግን ድካምና […]

ሰኔ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአረና ፓርቲ የአመራር አባል የሆነው አምዶም ገብረስላሴ በፌስ ቡክ ገጹ እንደጻፈው ፣ የ48 አመቱ አቶ ታደሰ ኣብርሃ የተባሉ የዓረና-መድረክ ኣባልና የምዕራባዊ ዞን የዓረና ኣመራር ኣባል ትናንት ማታ 09 / 10 / 2007 ዓ/ም በሶስት ሰወች ታንቀው ተገድለዋል። አቶ ታደሰ ኣብራሃ በቓፍታ ሑመራ ወረዳ ማይካድራ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ …

(ሰንደቅ፤ ፲ኛ ዓመት ቁጥር ፭፻፲፤ ረቡዕ ሰኔ ፲ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም.) የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አብያተ ክርስቲያናት ሰንበት ት/ቤቶች ሙስና እና ብልሹ አሠራር እንዲወገድ፣ መልካም አስተዳደር እና ፍትሕ እንዲሰፍን፣ አስተምህሮ እና ሥርዐት እንዲጠበቅ ላቀረቧቸው ጥያቄዎች ውሳኔ እንደሚሰጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ አስታወቀ፡፡ የሰንበት ት/ቤቶቹ፣ በአማሳኝ የአስተዳደር ሓላፊዎች እና በቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ውስጥ …

አንድ በስልጣን ላይ የተቀመጠ አካል ተቀዳሚ ተግባር የዜጎችን ደህንነት መጠበቅ መሆኑን ጤነኛ አዕምሮ ያለው የሰው ልጅ የሚገነዘበው ጥሬ ሃቅ ነው፡፡ እንደ እርግማን ዛሬ በኢትዮጵያ የስልጣን እርካቡን የተቆጣጠረው ቡድን የሚገዛቸውን ዜጎች የሚያያቸው እንደጠላት እንጅ የመንግስትን ጥበቃ እንደሚፈልጉ፤ በጠላትነት የፈረጃቸው ዜጎች በከፈሉት ግብር ስልጣን ላይ መቆየት መቻሉን እንኳን ባለስልጣናቱ መረዳት ተስኗቸዋል፡፡ ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም በደብረ […]

ባሳለፍነው እሁድ ናይሮቢ ኢስሊ የተበለ ቦታ የከተሙ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰማራቸው ሲቪል የለበሱ ደህንነቶች ከተለያዩ የመገናኛ መሳሪያዎች ጋር በቁጥጥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ያገኘሁት መረጃ ያመለክታል፡፡ በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ግለሰቦቹን በተመለከተ ሲያቀርቡት የነበረው ጥቆማ በመጨረሻ ሰሚ ጆሮ በማግኘቱ የኬንያ የጸረ ሽብር ግበረ ሀይል ግለሰቦቹን ከያሉበት ለቃቅሞ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ስደተኞቹን አስደስቷል፡፡ታሳሪዎቹ በቀጣዩቹ ቀናቶች ፍርድ ቤት […]

በሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው የሚገኙትና ጉዳያቸው እየታየ የሚገኘው እነዘላለም ወርቅአገኘሁ ከረፋዱ 4፡30 ላይ ልደት በሚገኘው 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀረቡ፡፡ ችሎቱ ዛሬ ተሰይሞ የነበረው በተከሳሾቹ ላይ አቃቤ ህግ ባቀረበው የሰነድና የሰው ማስረጃ ላይ ብይን ለመስጠት እንደሆነ ያወሱት የመሃል ዳኛው ሸለመ በቀለ፣ አቃቤ ህግ ለአራተኛ ጊዜ ተጨማሪ ማስረጃዎችን እንዳቀረብ ጊዜ ይሰጠኝ በሚል ያቀረበው ጥያቄ ችሎቱ ያልተቀበለው በመሆኑ ውድቅ […]

አማካሪዎቹ ከቤተ መንግሥቱ ወጥተው ለአራት ወራት ያህል መከሩ፡፡ አነሡ ጣሉ፤ በመጨረሻም የደረሱበትን ሐሳብ በብራና ጽፈው ወደ ንጉሡ ዘንድ መጡ፡፡ የተጠቀለለውንም ብራና ሰጡት፡፡ ንጉሡም ገለጠና አነበበው፡፡ እንዲህ ይል ነበር ‹‹ይህም ያልፋል››፡፡ ለምን? አላቸው ንጉሡ፡፡ በየትኛውም የሥልጣንና የሀብት ከፍታ ላይ ብትሆን፣ በየትኛውም የዝናና የክብር ሠገነት ላይ ብትደላደል፣ ‹ይህም ያልፋል› ብለህ ካሰብክ ግፍ አትሠራም፣ ፍትሕ አታዛባም፣ ድኻ አትበድልም፣ […]

የትውልድ ቦታው አሶሳ አከባቢ የሆነ የፌዴራል ፖሊስ አባል ሌሎች ሶስት የፌዴራል ፖሊስ አባላትን እና አንድ ቻይናዊን በምዕራብ ሀረርጌ ሚኤሶ ወረዳ ልዩ ስሙ ቦርደዴ በተባለ ቦታ በጥይት ተኩሶ ከገደላቸዉ በሃላ መሰወሩን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል:: የፌደራል ፖሊሶችና የኦሮምያ ፖሊስ ገዳዩን ለመያዝ በጭሮ፣ ሚኤሶ፣ በዴሳ፣ ገለምሶና አዋሽ ከተሞች ቤት ለቤት እየገቡ ፍተሻ በማካሄድ ላይ ናቸው። ፖሊሶቹ ለሰበተ-ሚኤሶ ባቡር […]

ሁለቱን ዶክተሮች ያፋጠጠው የቦንጋ ምርጫ

ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም.መካሄድ ሲገባው፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ውሳኔ የተላለፈው ምርጫ ሰኔ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. በደቡብ ክልል በካፋ ዞን፣ በቦንጋ ጊምቦ ገዋታና በዴቻ ወረዳ ተከናውኗል፡፡

የግል ዕጩውን ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስና የደኢሕዴን/ኢሕአዴግ ዕጩ ዶ/ር መብራቱ ገብረ ማርያም ያፋጠጠው ይህ ምርጫ፣ ቀደም ብሎ ግጭት ስለተካሄደበት ነበር ለሌላ ጊዜ የተላለፈው፡፡ ለዚህ ምርጫ 67,707 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፣ 95 በመቶ የሚሆኑ መራጮች ድምፃቸውን መስጠታቸውን የምርጫ ክልሉ ኃላፊዎች አስታውቀዋል፡፡ በውጤቱም ዶ/ር መብራቱ ዶ/ር አሸብርን በሰፊ ውጤት ማሸነፋቸውን በማግሥቱ በምርጫ ጣቢያዎች ከተለጠፉ ውጤቶች ለመረዳት ተችሏል፡፡

በምርጫ 2002 በወቅቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ብርሃኑ አዴሎን በሰፊ ልዩነት ያሸነፉት ዶ/ር አሸብር፣ በዘንድሮ ምርጫ አልቀናቸውም፡፡ ዶ/ር አሸብር በቅርቡ ለፓን አፍሪካ ፓርላማ ሁለተኛ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ቢመረጡም፣ የዘንድሮ ምርጫ ከብዷቸዋል፡፡ ተፎካካሪያቸው ዶ/ር መብራቱ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ናቸው፡፡ በምርጫ 2002 ለደቡብ ክልል ምክር ቤት ተወዳድረው ሲያሸንፉ፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለምርጫ የቀረቡት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ ባለፈው እሑድ በተካሄደው ምርጫ በምርጫ ጣቢያዎቻቸው ተገኝተው ድምፃቸውን የሰጡት ዶ/ር መብራቱ (በስተቀኝ)፣ ዶ/ር አሸብር (በስተግራ) ድምፃቸውን ለመስጠት ተሠልፈው ይታያሉ፡፡ የቦንጋን የዘገየ ምርጫ በተመለከተ የተዘጋጀው የነዓምን አሸናፊ ዘገባ ለመመልከት እዚህ ይጫኑ፡፡ 

 

ሰማያዊ ፓርቲ በደብረ ማርቆስ ለምርጫ በዕጩነት ያቀረበው አባሉ ተገደለ

ፓርቲው ክፍፍል ተፈጥሯል መባሉን አስተባበለ 

ሰማያዊ ፓርቲን በመወከል በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ ለተወካዮች ምክር ቤት በደብረ ማርቆስ ከተማ ተወዳዳሪ የነበረው አባሉ ወጣት ሳሙኤል አወቀ፣ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ከምሽቱ 2፡00 አካባቢ

በስለት ተወግቶና ተደብድቦ ተገደለ፡፡ ፓርቲው አባሉ መገደሉን ለሪፖርተር በማረጋገጥ፣ ነገር ግን በማን እንደተገደለ ማጣራቱን አለማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

ወጣት ሳሙኤል ወደ መኖሪያ ቤቱ ሲያመራ በሁለት ሰዎች ተደብድቦ ጉዳት ስለደረሰበት ወደ ሆስፒታል እንደተወሰደ ሕይወቱ ሊያልፍ መቻሉን፣   የፓርቲው ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

ወጣት ሳሙኤል ከቀድሞው የአንድነት ፓርቲ ጀምሮ በተቃውሞ ጎራ ሲታገል የቆየ መሆኑንና ፓርቲው ለሁለት ሲከፈል ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በምሥራቅ ጎጃም ዞን የፓርቲው ጸሐፊ ሆኖ መሥራቱን አቶ ዮናታን ጠቁመዋል፡፡ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለተወካዮች ምክር ቤት ተወዳድሮ ነበር፡፡

ነገር ግን ከምርጫው በኋላ ሟች ወጣት ሳሙኤል ከመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ተደጋጋሚ ዛቻና ማስፈራሪያ ይደርሰው እንደነበር አቶ ዮናታን ገልጸዋል፡፡ የሟቹ የፌስቡክ ግድግዳ ላይ በተጻፈ ማስታወሻም ይህንን የሚጠቁሙ መረጃዎች መስፈራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ አቶ ዮናታን ግን በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ስለመገደሉ ለጊዜው ተጨባጭ ማስረጃ እንደሌላቸው፣ ፓርቲው ጉዳዩን በመከታተል ላይ እንደሆነ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

ወጣት ሳሙኤል በፌስቡክ ግድግዳ ላይ ግንቦት 26 ቀን 2007 አሰፈረው በተባለው ማስታወሻ ላይ፣ ‹‹በስልኬ እየተደወደ ያለ ፍላጎቴ ደኅንነት እያስገደደኝ ይገኛል፡፡ ተገደልሁም፣ ታሰርሁም፣ ታፈንኩም ነፃነት አይቀርምና ለማስረጃነት የደኅንነቶችን ስም፣ ፎቶግራፍና አድራሻ፣ እንዲሁም በሐሰት ምስክርነትና በከሳሽነት የተደራጁ አካላት ተወካዮች አስመዘግባለሁ፡፡ ማንኛውንም የምከፍለው ዋጋ ለአገሬና ለነፃነት ነው፡፡ ከታሰርኩም ህሊናዬ አይታሰርም፡፡ ከገደሉንም ትግሌን አደራ…›› የሚል ይነበባል፡፡ ይህንን ማስታወሻ በተመለከተ በመንግሥት በኩል ምንም ዓይነት አስተያየት አልተሰጠም፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ ሰማያዊ ፓርቲ ከሰኔ 4 እስከ 5 ቀን 2007 ዓ.ም. የምክር ቤት ስብሰባ ማድረጉን፣ በዋነኛነት በሚቀጥለው ወር ጠቅላላ ጉባዔ ከመካሄዱ በፊት የቅድመ ሪፖርት ውይይት እንዳደረገ አቶ ዮናታን ገልጸዋል፡፡ ለግንቦቱ ምርጫ ማስፈጸሚያ በተደረጉ ወጪዎችና የበጀት አጠቃቀም ጉዳይና ፓርቲው ከተመሠረተ ጀምሮ ሲጠቀምበት በነበረው ሕገ ደንብ ጉዳይ፣ በከፍተኛ ክርክር የታጀበ ውይይት መደረጉንም አቶ ዮናታን አስረድተዋል፡፡

በተለይ በበጀት ጉዳይ በአባላት መካከል የጋለ ክርክር ተካሂዶ የነበረ ቢሆንም፣ በመግባባት ተጠናቋል ብለዋል፡፡ ነገር ግን በፓርቲ ውስጥ ‹‹ከፍተኛ ፍትጊያ ያለው›› ክርክር የተለመደ ቢሆንም፣ በፓርቲው ውስጥ መከፋፈል እየተፈጠረ ነው ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ መሠረተ ቢስ ነው ሲሉ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ‹‹እኛ ዝም ብለን ተሰብስበን አንበተንም፡፡ ከፍተኛ የሐሳብ ፍጭት የምናደርግ ስብስብ በመሆናችን ክርክራችን መከፋፈል የሚባል ነገር አያመጣም፤›› በማለት አስታውቀዋል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ከምርጫው በፊት 92 ሚሊዮን ብር ለምርጫ ማስፈጸሚያ መድቤያለሁ ብሎ ከገለጸ በኋላ፣ መንግሥት በፓርቲው የገንዘብ ምንጭ ላይ ምርመራ አደርጋለሁ ማለቱ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን አቶ ዮናታን ፓርቲው እስካሁን ምንም ዓይነት ምርመራ እንዳልተደረገበት ጠቁመዋል፡፡

 

መንግሥት በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ የግል ኩባንያዎች በግዙፍ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እንዲሳተፉ ሊፈቅድ ነው፡፡ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የግል ኩባንያዎች

የፍጥነት መንገድ መገንባት፣ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨትና ለመስኖ አገልግሎት የሚውሉ ግድቦች መገንባት እንዲችሉ ፈቅዷል፡፡ 

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ሕግ ዲፓርትመንት ኃላፊ አቶ ዋሲሁን አባተ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የመንግሥትና የግሉ ዘርፍ ትብብር ትልቅ ቦታ ተሰጥቶታል፡፡

በዚህ መሠረት የግል ኩባንያዎች በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ ትልቅ ድርሻ እንዲኖራቸው ከማድረጉ ባሻገር፣ ከዚህ ቀደም ተሳታፊ ባልሆኑባቸው የመሠረተ ልማት ዘርፎች ውስጥ ተዋናይ እንዲሆኑ እየተመቻቸ መሆኑን አቶ ዋሲሁን ገልጸዋል፡፡

መንግሥት በቅርቡ ይፋ በሚያደርገው የአምስት ዓመት ዕቅድ ሰነድ በተዘረዘረው መሠረት፣ የግል ባለሀብቶች የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን አካሂደው አገልግሎት በመስጠት የንግድ ሥራ ማካሄድ ያስችላቸዋል፡፡

ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ ነው፡፡ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የሕግ ዲፓርትመንት ባዘጋጀው የሕግ ማዕቀፍ ላይ የተቀጠሩ አማካሪ ድርጅቶች አስተያየት እየሰጡ መሆኑ ታውቋል፡፡

ረቂቅ ሕጉ ከፀደቀ በኋላ የግል ኩባንያዎቹ በሚፈልጓቸው የመሠረተ ልማት ዘርፎች የሚሰማሩ ሲሆን፣ ከአዋጁ ባሻገር አሠራሩን የሚደግፍ ደንብ እንደሚዘጋጅም ታውቋል፡፡

በኢትዮጵያ የመንገድና የኃይል ማመንጫ ባለቤት የሆነ የግል ኩባንያ የለም፡፡ ለመስኖ አገልግሎት የሚውል ግድብም ቢሆን ከራስ ፍጆታ አልፎ ለኪራይ አገልግሎት ያዋለ የግል ኩባንያ እንደሌለ ይታወቃል፡፡ እየተዘጋጀ ባለው ዕቅድ ግን አንድ ኩባንያ በራሱ ወጪ የፍጥነት መንገድ ገንብቶ ለተጠቃሚዎች ክፍት በማድረግ መንገድ እንደሚችል ተቀምጧል ተብሏል፡፡ 

በኢትዮጵያ ብቸኛው የፍጥነት መንገድ ከአዲስ አበባ አዳማ ድረስ የተዘረጋው 80 ኪሎ ሜትር ባለ ስድስት ረድፍ መንገድ ብቻ ነው፡፡ በቻይናው ሲሲሲሲ ኩባንያ የተሠራው ይህ መንገድ የሚተዳደረው መንግሥት ባቋቋመው የልማት ድርጅት ሲሆን፣ መንገዱ የአገልግሎት ክፍያ እየተከፈለበት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ 

‹‹ከእነዚህ ግንባታዎች የግሉ ዘርፍ ልምድ በመውሰድ የራሱን ግንባታ ሊያካሂድ ይችላል፤›› በማለት አቶ ዋሲሁን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ በብቸኝነት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ሥልጣን ያለው መንግሥታዊው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነው፡፡ የገጠሩን የአገሪቱ ክፍል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ለማሻሻል ብሔራዊ ኃይል ማስተላለፊያ ከተዘረጋበት መስመር 15 ኪሎ ሜትር ርቀው የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች፣ ከተለያዩ አማራጭ የኃይል አቅርቦቶች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጩ ሲደረግ ቆይቷል፡፡ የመነጨውን ኃይል የሚያስተዳድሩትም ያመነጩት የኅብረተሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡ 

በአሁኑ ዕቅድ ግን የታሰበው የግሉ ዘርፍ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወሰን ታሪፍ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያቀርብ ይደረጋል ተብሏል፡፡

መንግሥት በሁለተኛው የዕቅድ ዘመን ራሱን የቻለ 12 ሺሕ ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት አቅዷል፡፡ ይህ ዕቅድ ይተገበራል ተብሎ የሚጠበቀው የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች ከተሳተፉ ብቻ ነው ተብሎ በመታመኑ፣ በተለይ በአሁኑ ወቅት በግድብ ግንባታ የተሰማሩ ኩባንያዎች ተስፋ እንደተጣለባቸው ተመልክቷል፡፡ 

በሌላ በኩል ለመስኖ ልማት አመቺ በሆኑ ወንዞች ላይ የግሉ ዘርፍ ግድብ እንዲገነባ ሁኔታዎች ይመቻቻሉ ተብሏል፡፡ በግድቡ ዙርያ በእርሻ ሥራ የተሰማሩ ኩባንያዎች ውኃውን እንዲጠቀሙ እየተደረገ የአገልግሎት ክፍያ ይፈጽማሉ ተብሏል፡፡

በአሁኑ ወቅት ይህንን ሥራ እየሠራ የሚገኘው የአዋሽ ተፋሰስ ባለሥልጣን ብቻ ነው፡፡ ባለሥልጣኑ በአዋሽ ወንዝ ላይ ሥልጣን የተሰጠው በመሆኑ ከአዋሽ ወንዝ ጠልፈው የሚጠቀሙ አልሚዎች ኪራይ እንዲከፍሉ ሲደረግ ቆይቷል፡፡ 

አሁን በተያዘው ዕቅድ፣ የግል ኩባንያዎች የግድብ ግንባታ በማካሄድ የውኃው አገልግሎት ኪራይ ማስከፈል እንዲችሉ ይደረጋል፡፡ 

መረጃዎች እንደሚጠቁሙት መንግሥት በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በዋናነት ለማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ትኩረት ሰጥቷል፡፡ ይህንን ዕቅድ ለማሳካት በዋናነት የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ፣ አገሪቱን ከአላስፈላጊ ብድር ለመታደግ ተስፋ እንደተደረገ ተመልክቷል፡፡ የልማታዊ መንግሥት ሞዴል በሚከተሉ አገሮች የግሉ ዘርፍ መንግሥት በሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሠረት በኢኮኖሚው ውስጥ ጉልህ ሚና እንዲጫወቱ ማድረግ የተለመደ ነው፡፡     

 

የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደቡብ ሱዳን (ጁባ) ቅርንጫፍን በመመሳጠር መዝብረዋል ብሎ በጠረጠራቸው ሠራተኞች ላይ ሰኔ 9 ቀን 2007 ዓ.ም. ክስ መሠረተ፡፡

የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ክሱን የመሠረተው፣ በስምንት የቅርንጫፉ ሠራተኞች ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡ 

ተጠርጣሪዎቹ በቅርንጫፍ ባንኩ በኃላፊነትና በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ ሲያገለግሉ የነበሩ ናቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ሰኔ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ግለሰቦቹን የጠረጠራቸው እርስ በእርስ በመመሳጠር ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ከጁባ ቅርንጫፍ ንግድ ባንክ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል ነው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የተለያዩ ቅርንጫፎች የመጋዘን ሠራተኞችን በሙስና ወንጀል በመጠርጠር ምርመራ ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡

የተጠረጠሩት ሠራተኞች በተለያዩ የምርት ገበያው ስድስት መጋዘኖች የ11 ሚሊዮን ብር ምርት ማጉደላቸውን ክሱ ያመለክታል፡፡

 

ኢትዮጵያና ኬንያ በኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነታቸው መሠረት፣ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ለማካሄድ ሐሙስ ሰኔ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ኮንትራክተሮች ጋር ውል ይፈርማሉ፡፡

በሁለቱ አገሮች በጋራ የሚካሄደው የኃይል መስመር ዝርጋታ 1,068 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፣ ኢትዮጵያ መገንባት ያለባትን 437 ኪሎ ሜትር የኃይል መስመር በሁለት ኮንትራቶች ተከፍሎ ለቻይና ስቴት ግሪድ ኩባንያ ይሰጣል፡፡ ስቴት ግሪድ በአሁኑ ወቅት ከህዳሴ ግድብ የሚወጣው ኤሌትሪክ የሚተላለፍበትን መስመር በመገንባት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቻይናው ስቴት ግሪድ ጋር ሐሙስ ይፈራረማል፡፡

በኬንያ በኩል የሚገነባው 631 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፣ የኬንያ መንግሥት በሦስት ኮንትራቶች የሚከፈለውን ይህን ፕሮጀክት በዚህ ሳምንት ለህንድ ኩባንያዎች ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ታውቋል፡፡

ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 1.2 ቢሊዮን ዶላር የሚፈልግ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ወገን ያለውን የአፍሪካ ልማት ባንክ ፋይናንስ ያደርገዋል፡፡ በኬንያ በኩል ያለውን አፍሪካ ልማት ባንክና የፈረንሣይ የልማት ኤጀንሲ ፋይናንስ ያደርጋሉ ተብሏል፡፡

በዚህ ፕሮጀክት ውስጥ ባይጠቃለልም በሁለቱም አገሮች ሁለት የማከፋፈሪያ ጣቢያዎች ይገነባሉ፡፡ ፕሮጀክቶቹን የዓለም ባንክ ፋይናንስ እንደሚያደርግ ታውቋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ኮንትራት በግምገማ ሒደት ላይ የሚገኝ በመሆኑ በጀቱ አልታወቀም፡፡

የሚገነባው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር 500 ኪሎ ቮልት ኃይል በአንድ ጊዜ ማስተላለፍ (ዳይሬክት ከረንት) አቅም ያለው ሲሆን፣ ይህም በአፍሪካ ትልቁ እንደሚያደርገው ታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ኮንስትራክሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ሆሮ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ይህ ፕሮጀክት ለሁለቱ አገሮች ኢኮኖሚያዊ ትስስር ትልቅ ጠቀሜታ አለው፡፡

ኢትዮጵያ ለኬንያ 400 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ ከዓመታት በፊት የመግባቢያ ስምምነት አድርጋለች፡፡ ይህ መስመር ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ የምትሸጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል ይተላለፋል ተብሏል፡፡

ፕሮጀክቱ ሰፊ እንደመሆኑ መጠን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ረዥም ጊዜ የፈጀ በመሆኑ፣ ኮንትራቱ ከተፈረመ በኋላ ወዲያውኑ ወደ ግንባታ ይገባል፡፡ 

በቀጣይ በኢትዮጵያ በኩል ወላይታ ሶዶ፣ በኬንያ በኩል ሱሳዋ ላይ 2,000 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል የመሸከም አቅም ያለው ማከፋፈያ ጣቢያ ይገነባል፡፡ 

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሙስና ወንጀል የተገኙ የመሬት ይዞታዎችን ያለምንም ዕውቀት የገዙ የከተማ ነዋሪዎች የመሬት ባለቤትነት ዕጣ ፈንታ ሊወስን ነው፡፡

ምንጮች እንደገለጹት፣ የከተማው አስተዳደር በመሬት ይዞታዎቹ ላይ አስተዳደራዊ ውሳኔ ለመወሰን ያስችለው ዘንድ በይዞዎቹ ላይ ጥናት የሚያደርግ ኮሚቴ አቋቁሟል፡፡

ኮሚቴው ከሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ባለሙያዎች ጋር በመሆን ምን ያህል ነዋሪዎች የመሬት ይዞታቸው በሙስና የተገኘ መሆኑን እየተገነዘቡ ግዥ ፈጽመዋል? ምን ያህሉስ ባለማወቅ ግዥ ፈጽመዋል? የሚለውን የመለየት ሥራ በማከናወን ለአስተዳደሩ ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ከሁለት ሳምንት በፊት የአሥር ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌማን፣ የሙስና ወንጀል ፍሬ የሆኑ የመሬት ይዞታዎች ላይ የሚኖሩ ዜጎች የመጨረሻ እልባት ለምን እንዳልተሰጠው ተጠይቀው ነበር፡፡

በመኖሪያ ማኅበራት ስም በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ይዞታዎችን በሙስና በሕገወጥ መንገድ የያዙትን ኮሚሽኑ እንዲቀጡ ማድረጉን ያስታወሱት ኮሚሽነሩ፣ በሕገወጥ መንገድ የተያዙትን የመሬት ይዞታዎችም የአዲስ አበባ አስተዳደር ሕጋዊ ሥርዓት እንዲያስይዘው ከፍርድ ቤት ጭምር ትዕዛዝ መሰጠቱን አስታውሰዋል፡፡

‹‹በዚህ ጉዳይ ውስጥ ሁለት ነገሮች አሉ፡፡ አንዱ በትክክል በሕገወጥ መንገድ የተያዘ መሬት መሆኑን እያወቁ ተሳትፎ ያደረጉ አሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ እነዚህ ወንጀለኞች በማኅበር ውስጥ የተያዙ ቦታዎችን በሙሉ አልያዙትም፣ ለንፁኃን ሸጠውታል፡፡ ምናልባትም ትክክለኛ ነው በማለት የየክፍላተ ከተማ ማኅበራት ማደራጃዎች አረጋግጠውላቸው ገዝተውታል፡፡ ስለዚህ ሁለቱን ለይቶ አስተያየት መስጠት ያስፈልጋል፤›› ብለዋል፡፡

ፀረ ሙስና ኮሚሽን ወንጀለኞችን የወንጀል ፍሬያቸው ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ማድረጉን የተናገሩት ኮሚሽነር ዓሊ፣ በቅን ልቦና የገዙና የመስተዳደር አካላት ሕጋዊ ነው ብለዋቸው ማረጋገጫ ሰጥተዋቸው የገዙ ሰዎች ደግሞ እንዴት ሊስተናገዱ እንደሚገባ አስተዳደሩ የሚወስነው ይሆናል ብለዋል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ አፀደ ዓባይ መረጃ እንዲሰጡ ቢጠየቁም፣ መረጃ እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡

በ1997 ዓ.ም. የተካሄደውን ምርጫ ተከትሎ በአዲስ አበባ ከተማ የተፈጠረውን የሥልጣን ክፍተት በመጠቀም፣ ከ500 በላይ የመኖሪያ ቤት ማኅበራት በሕገወጥ መንገድ ከሁለት ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መያዛቸውና ፀረ ሙስና ኮሚሽንም ተከታትሎ መሬቱን ማስመለሱ ይታወቃል፡፡

 

 

‹‹ተከሳሾች ማስረጃ የማየት ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው ተጥሷል››  የተከሳሾች ጠበቃ

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና በጋዜጠኞች ክስ ላይ ያቀረበው የሲዲ ማስረጃ በችሎት ውስጥ እንዳይታይ፣ ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. የከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በየነ፡፡

የዓቃቤ ሕግ የሲዲ ማስረጃ ጉዳይዋ በሌለችበት የሚታየው አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ ላይ የቀረበ ነው የተባለ ሲሆን፣ ሌሎች ዘጠኝ ተከሳሾች በግብረ አበርነት በፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ በዚሁ ክስ ተካተዋል፡፡

‹‹በአንደኛ ተከሳሽ ላይ የቀረበውን የሲዲ ማስረጃ በጽሕፈት ቤት ተመልክተነዋል፡፡ ከሌሎች ተከሳሾች ጋር የተገናኘ ባለመሆኑ በችሎት መታየቱ አስፈላጊ ሆኖ አላገኘነውም፤›› በማለት የችሎቱ ዳኛ ባለፈው ሰኞ በዋለው ችሎት ብይን ሰጥተዋል፡፡

የፍርድ ቤቱን ውሳኔ የተቃወሙት የተከሳሾች ጠበቃ አቶ አመሐ መኮንን፣ ‹‹እኛ የነበረን አረዳድ ቀጠሮው የተያዘው የሲዲ ማስረጃው በዝግ ችሎት ወይም በክፍት ችሎት፣ ማለትም ታዳሚዎች ባሉበት ወይም በሌሉበት ይታይ በሚለው ላይ እንጂ ዳኞች ብቻ በጽሕፈት ቤት ይዩት በሚል ጉዳይ አልነበረም፤›› ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል፡፡

‹‹አሁን የተደረገው ትክክለኛ የዳኝነት አሠራር ነው ብለን አናምንም፡፡ የእኛ ደንበኞች በግብረ አበርነት በተከሰሱበት መዝገብ የቀረበውን ማስረጃ ሊያዩ ይገባል፤›› ሲሉ አቶ አመሐ ተከራክረዋል፡፡

የተከሳሾቹ ሌላው ጠበቃ አቶ ሽብሩ በለጠ በበኩላቸው፣ የቀረበው የሲዲ ማስረጃ ከተከሳሾች ዕይታ ውጪ መሆን እንደሌለበትና ማስረጃውን ማየት ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው መሆኑን በፍርድ ቤት ተከራክረዋል፡፡

ፍርድ ቤቱም ጉዳዩ ብይን የተሰጠበት እንደሆነና የተከሳሽ ጠበቆች አስተያየት ተመዝግቦ ወደፊት ይግባኝ ሊሉበት እንደሚችሉ ገልጿል፡፡

የሰባቱ ጦማሪያንና የሦስቱ ጋዜጠኞች የክስ ሒደት ከ13 ወራት በላይ የፈጀ ሲሆን፣ ዘጠኙ ተከሳሾች ከሚያዝያ 2006 ዓ.ም ጀምሮ የዋስ መብት ተከልክለው በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ ባለፈው ሰኞ ማለዳ በዋለው ችሎት ደማቅ ቀይ ካኒቴራ ለብሶ ከነበረው አቤል ዋበላ በስተቀር ስምንቱ ተከሳሾች አንድ ዓይነት ጥቁር ካኒቴራ ለብሰው ችሎቱን ታድመዋል፡፡ አቤል ከሁለት ሳምንት በፊት በዚሁ የክስ ሒደት ፍርድ ቤት ተዳፍረሃል ተብሎ የስድስት ወራት እስራት በገደብ እንደተፈረደበት ይታወሳል፡፡     

የዓቃቤ ሕግ ማስረጃዎች መጠቃለላቸውን ተከትሎ ተከሳሾቹ የቀረበባቸውን ክስ መከላከል ይገባቸዋል ወይስ አይገባቸውም በሚለው ላይ ፍርድ ቤቱ ብይን ለመስጠት ለሐምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጠሮ ይዟል፡፡ 

በአገሪቱ የወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ መሠረት ፍርድ ቤቱ ይከላከሉ የሚል ብይን ከሰጠ ተከሳሾች የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ይጀምራሉ፡፡ የዓቃቤ ሕግ ማስረጃ በቂ ሆኖ ካላገኘው ግን በነፃ ሊያሰናብታቸው ይችላል፡፡

ተከሳሾቹ የግንቦት ሰባትና የኦነግን ዓላማ ተቀብለው ለሽብር ተግባር ተደራጅተዋል ተብለው በፀረ ሽብር ሕጉ አንቀጽ ሦስት ንዑስ አንቀጽ ሁለት ‘የኅብረተሰቡን ወይም የኅብረተሰቡን ክፍል ደኅንነት ለከፍተኛ አደጋ ማጋለጥ’ እንደተከሰሱ የዓቃቤ ሕግ የክስ ቻርጅ ያስረዳል፡፡ 

 

ኢትዮጵያና ሱዳን የሁለቱ አገር ሕዝቦች ያለቀረጥና ታክስ መገበያየት የሚችሉበትን ነፃ የንግድ ቀጣና ለማቋቋም ከስምምነት ላይ ደረሱ፡፡

ሰኔ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. የሁለቱ አገሮች የጋራ የቴክኒክ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ፣ በሁለቱም አገሮች ነፃ የንግድ ቀጣናው እንዲቋቋምና በእነዚህ የንግድ ቀጣናዎች የሁለቱም አገሮች ገንዘብ መገበያያ እንዲሆን መስማማታቸውን ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡ 

የሱዳን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልራህማን ዲራር ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት፣ የንግድ ቀጣናዎቹን ከማቋቋም በተጨማሪ የሁለቱ አገሮች የመገበያያ ገንዘቦች ዝውውር መኖሩም ለሁለቱ አገሮች የንግድ ልውውጥ እንደሚጠቅም ተናግረዋል፡፡ 

በሁለቱ አገሮች የሚቋቋሙትን ነፃ የንግድ ቀጣናዎችን ምቹ ቦታ የሚለይ አማካሪ ኩባንያ እንደሚቀጠር፣ ኩባንያውም በተቀጠረ በ45 ቀናት ውስጥ ውጤቱን ለጋራ የቴክኒክ ኮሚቴው እንደሚያቀርብ መረጃው ያመለክታል፡፡

የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴው ከነፃ የንግድ ቀጣናው በተጨማሪ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሱዳን ቅርንጫፉን እንዲከፍት፣ እንዲሁም የሱዳን ባንኮች በኢትዮጵያ ጽሕፈት ቤታቸውን እንዲከፍቱ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ 

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሌሎች አገሮች ቅርንጫፎቹን መመሥረት የሚችል ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም በደቡብ ሱዳን ቅርንጫፎች ያሉት መሆኑ ይታወቃል፡፡ 

በኢትዮጵያ ግን የውጭ አገር ባንኮች የባንክ አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ በሕግ ተከልክሏል፡፡ በመሆኑም ሊከፈት የሚችለው የሱዳን ባንክ ጽሕፈት ቤት የማማከር አገልግሎትና ሌሎች ባንክ ነክ ያልሆኑ አገልግሎቶችን ነው መስጠት የሚችለው፡፡ 

የሁለቱ አገሮች የቴክኒክ ኮሚቴ ከዚህ ቀደም በተስማማው መሠረት፣ ሁለቱን አገሮች በየብስ የሚያገናኝ ትራንስፖርት ለመጀመር ከወራት በፊት ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል፡፡