ነጻነት ዋጋ ያስከፍላል። አገር ቤት ያሉ ወገኖቻችn እጅግ በጣም ከባድና ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ለሰላም፣ ለዴሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነት ፣ ለነጻነትና ለኢትዮጵያ አንድነት፣ እልህ አስጨራሽ ትግል እያደረጉ ነው። «ሽብርተኞች ናቸው» በሚል በቃሊት ፣ በቂሊንጦ፣ ዝዋይ በመሳሰሉ ዘግናኝ እሥር ቤቶች እየማቀቁ ያሉ ፣ የሰላምና የዴሞክራሲ አርበኞች የሆኑ፣ ብርቅዬ የኢትዮዮጵያ ልጆችን መመልከቱ ይበቃል። አንዱዋለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን፣ በቀለ ገርባ፣ […]

የሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን በአዲስ አበባ ሰልፍ እንደሚያደርግ አሳወቀ። ሰልፉ የሚደረግበት ቀን የዳግማይ ትንሳኤ ቀን ሲሆን፣ ለሰልፉ እውቅና ከአስተዳደሩ፣ ይገኝ አይገኝ ገና የታወቀ ነገር የለም። የአዲስ አበባ አስተዳደር ከአንድ አመት በፊት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ከአራት ኪሎ እስከ ጥቅር አንበሳ ጋር እስካለዉ ሃዉልት ድረስ፣ ሰልፍ እንዲያደርግ እውቅና መስጠቱ፣ ይታወቃል። ለሰማያዊ ተፈቅዶ በነበረበት ቦታ፣ መጋቢት 28 ቀን […]

በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ መንግስት ሀገሪቱን ተቆጣጥሮ ስልጣን ከያዘ 23ዓመት አስቆጠረ። ይህን ያህል አመት በስልጣን ቆይቶ ህዝቡን በሰላም መምራት አልቻለም። ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ህዝብ ነፃ አውጥቻለሁ፣ ሀገሪቱንም እያሳደኩ ነው..ቢልም ህዝቡ ግን፥ ኑሮ ተወደደ፣ ሀገራችን ተከፋፈለች፣ ዲሞክራሲ የለም፣ ሰብአዊ የመብት ረገጣ እየተፈጸመ ነው በማለት ማማረሩን ቀጥሎዋል። ከብዙ ኢትዮጵያውያኖች ጋር በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ ገብቶዋል። […]

በታዋቂዉ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ አቶ ኦባንግ ሜቶ የሚመራዉ የሶሊዳሪቲ ንቅናቄ፣ የሚሊዮኖች ድምድ ለመሬታ ባለቤትነት እና ለፍትህ እንቅስቅሴን እንደሚደገፍና የእንቅስቃሴዉም አካል እንደሚሆን ባወጣዉ መግለጫ ገለጸ። ሶሊዳሪቲ «እኛም ከሚሊዮኖች አንዱ ነን» በሚል ባወጣዉ መግለጫ፣ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንቅስቃሴዉን እንዲቀላቀሉና የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስቧል። በግለሰብ ደረጃ ተራ ሰዎች ብንሆንም፣ ከተባበረንና ሚሊዮኖች ከሆነን ፣ ሊቋቋመን የሚችል ምንም ኃይል እንደሌለ የገለጸው የሶሊዳሪቲ […]

‘ዜጎች ነንና ፍትሓዊ ልማት ያስፈልገናል’ ሲንል አሰሩን። ‘ደማችን ገብረናልና ሰለማዊ ሰልፍ የመውጣት መብታችን ይከበርልን’ ስንል ደበደቡን። ‘ብዙ መስዋእት ከፍለናልና ነፃነታችንን አትንፈጉን’ ስንል ትጥቃችንን አስፈቱን። መብታችንን ለማስከበር ስንሞክር ገደሉን። ግን ይህን ሁሉ ወላጆቻችን፣ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የከፈሉት መስዋእት ዓላማው ምን ነበር? ደርግን ደምስሶ ሌላ ደርግ መመስረት? ይሄማ ሊሆን አይችልም። ደርግ’ኮ ደርግ ያሰኘው ተግባሩ ነው። ደርግን የምንጠላው ደርግ […]

በሽብር ወንጀል ተከስሰው በክርክር ላይ የሚገኙት የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጥያቄዎች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትና ሌሎችም ተከሣሾች ለፍርድ ቤት ሲሰጡ የቆዩትን ቃል ዛሬ አጠቃልለዋል።

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የጀርመን የኤኮኖሚና የልማት ትብብር ሚኒስቴር ሀገሪቱ ለልማት የምታዉለዉን የርዳታ በጀት ማሳደጉን አስታወቀ። ምክር ቤት ከትናንት በስተያ በልማት በጀቱ ላይ ክርክር አካሂዷል። የተቃዉሞ ፖለቲከኞች ሀገሪቱ ከዓመታት በፊት ለአዳጊ ሃገራት የልማት ርዳታ የበለጸጉት በየዓመቱ እንዲያዋጡ ከተስማሙበት መጠን ለመድረስ ጀርመን ይቀራታል ሲሉ ተችተዋል።

ማንኛውንም መንገድ ተደቅመው ዳግም ወደ ሳውዲ አረቢያ የሚሰደዱ ወጣት ኢትዮጵያንኖች ባለፈው ህዳር ወር የሳውዲ ዓረቢያ መንግሥት በሀገሪቱ የሚገኙ ህገ ወጥ የሚለውን ስደተኞች እያሰረ ከሀገር ሲያባርር፤

ተክለሚካኤል አበበ (ቶሮንቶ)

የማርቆስ ብዙነህ ደብዳቤ፤

1-       “በርካታ ትምህርት ቤቶች፤ ዩኒቨርስቲና የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ፤ የተጠየቀው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን” ይላል፤ በአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቅ ክፍል ሀላፊ፤ በአቶ ማርቆስ ብዙነህ ማንደፍሮ፤ መጋቢት 23 ቀን 2006/2014 የተፈረመው ደብዳቤ፡፡ አንድነት፤ ሰልፉን ለማድረግ ያቀረባቸው መስመሮች 3 ሲሆኑ፤ ሶስቱም መስመሮች ከቀበናው የአንድነት ጽ/ቤት ይነሳሉ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከሁለት ሣምንታት በኋላ አዲስ አበባ ላይ የሚያካሂዱት የእግር ጉዞ ዓላማ በተመሣሣይ ፆታ ግንኙነትና በሌሎችም “መጤ” ባሏቸው ልማዶች ወይም የባሕል ዘርፎች ላይ ግንዛቤ መፍጠር መሆኑን አዘጋጆቹ ማኅበራት አስታውቀዋል፡፡

ሁለቱ ማኅበራት ዛሬ በሰጡት መግለጫ የተመሣሣይ ፆታ ግንኙነት “ሊወገዝ የሚገባ ነው” ብለዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መጋቢት 28 ቀን ይደረጋል ተብሎ የተጠበቀዉ የአንድነት የእሪታ ቀን ሰልፉ ፣ «ሰልፍ እንዲደረግ በታሰበበት ቀን፣ ሌሎች ዝግጅቶች ስላሉ በቂ ጥበቃ ልናሰማራ አንችልም» በሚል እውቅና ባለመስጠቱ ለሚያዚያ 5 ቀን መተላለፉ ይታወቃል። የሚያዚያ አምስቱን ሰልፍ በተመለከተ ምላሽ የሰጠው የአዲስ አበባ አስተዳደር፣ በሚያዚያ 5 ቀን ፣ ሩጫ ስለሚኖር ሰልፉ ለቅዳሜ ሚያዚይ 4 ቀን እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለአንድነት ፓርቲ […]

የአንደኛዉ የዓለም ጦርነት ከመጀመሩ በፊት አባታቸዉ የቀድሞዉ የጀርመን የቅኝ ግዛት አፍሪቃ ሃገር ከካሜሩን ወደ ጀርመን ሲገቡ፤ በደስታ ነበር አቀባበል የተደረገላቸዉ። ቆየት ብሎ ግን አፍሪቃዊዉ በቆዳ ቀለም ላይ የተመሰረተ ጥላቻን አዩ፤ እየቆዩም የቅኝ ግዛት ፊልሞችን በተመለከተ በሚሰሩ ፊልሞች ላይ አጫጭር ተዉኔቶችን እንዲተዉኑ ተደርገዋል።

ዩጋንዳ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት በእስር የሚፈለጉትን የዓማፂው ቡድን «ሎርድ ሬዚስተንስ አሚ፣ » በምሕፃሩ « ኤል አር ኤ» መሪ ጆሴፍ ኮኒን ለመያዝ በጀመረችው እንቅስቃሴ ላይ ዩኤስ አሜሪካ ተባብራ ትሰራለች። በዚሁ ትብብሯ ቀደም ሲል 100 ወታደሮች የላከችው የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ባለፈው

የጀርመን ሩዋንዳ ትብብር በመግባባትና በጋራ ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ እንደሆነ የሩዋንዳ ባለስልጣን አመለከቱ። የሩዋንዳ የትምህርት ሚኒስትር ዴታ ማቲያስ ሃርባሙንጉ ሀገራቸዉ በአሁኑ ወቅትም በትምህርት ዘርፍ ከጀርመን የዳበረ ልምድ እየተጠቀመች ነዉ ይላሉ።

በዓባይ ዳር በሚገኝ መንደር የምትኖር አንዲት ወፍ ነበረች፡፡ በዚያ ወንዝ ለሚዋኙም ሆነ ለሚሻገሩ ደምፅዋን አሠማምራ ትዘምር ነበረች፡፡ ደግሞ ላባዎቿ በኅብር ቀለማት የተሞሉ ነበሩ፡፡ እርሷ ላይ የሌሉ የአዕዋፍ ቀለማት አልነበሩም፡፡ ዝማሬና ዜማዋ ከቶ አይቀየሩም፡፡ በዚህም የተነሣ ዝማዋን ለምደውት አብረዋት የሚያዜሙ ብዙዎች ነበሩ፡፡ በዙሪያዋ ያሉ አዕዋፍ፣ ከወንዙ ለመጠጣት የሚመጡ አራዊት፣ በወንዙ ውስጥ የሚገኙ ዐሣት አብረዋት ያቀነቅናሉ፡፡ እንኳንና በነፍስ የሚኖሩ ሰዎችና በደመ ነፍስ የሚንቀሳቀሱ እንስሳት ቀርተው ዕጽዋት እንኳን እንደ ቅኔ ማኅሌት እንደ ገባ ደብተራ አብረዋት ያሸበሽባሉ፡፡ የእርሷ ዝማሬ ምንም የማይመስላቸው በወንዙ ዳር የተጎለቱት ድንጋዮች ብቻ ናቸው፡፡

እንዲህ እያለች ስትኖር ለዐቅመ ዕንቁላል ደረሰች፡፡ ጎጆ ልትቀልስም አሰበች፡፡ እንጨትና ሣር ሰብስባ ቤቷን የአንድ ጎጆ ባጥ ሥር መቀለስ ጀመረች፡፡ እንጨትና ሣር ደልድላ ጭድ በመካከሉ ልታስቀምጥ ስትል የሠፈሩ ልጆች መጡና በድንጋይና በእንጨት ፍርስርሱን አወጡባት፡፡ እርሷ ለመሥራት አንድ ወር የፈጀባትን እነርሱ ለማፍረስ አፍታም አልወሰደባቸው፡፡ ልጆቹ ጎጆዋን አፍርሰው የጀግንነት ስሜት ተሰምቷቸው እየሳቁና እየተደሰቱ ሄዱ፡፡ እርሷ ግን መከራዋን ታቅፋ ቀረች፡፡ መገንባት እንደ ማፍረስ መች ቀላል ነውና፡፡

መቼም ያለ ጎጆ አይኖር፤ ያለ ጎጆም ዕንቁላል አይጣል፡፡ ያለ ጎጆም ጫጩት አይፈለፈል፡፡ አማራጭ አልነበራትምና ዛፍ ላይ ሣርና እንጨቱን መሰብሰብ ቀጠለች፡፡ ልጆቹ ዐውቀው እንዳያፈርሱባትም በቅጠል ሸፈንፈን አደረገችው፡፡ ዕንቁላሉ መደላድል እንዲያገኝም ጭድ በመካከሉ ረበረበችበት፡፡ ነፋስ ወዝውዞ እንዳይጥለው በልጥ ከግንዱ ጋር ጠለፈችው፡፡ የፀሐይ ብርሃን እንዲያገኝም በስተ ምሥራቅ በኩል በር ሠራችለት፡፡ ከሥራዋ እፎይ ብላ ዕንቁላሏን ልትጥል ስትደላደል ግን እንደ አውሎ ነፋስ የሚያስገመግም ድምፅ ከወደ ዛፉ አካባቢ ሰማች፡፡ ድምፁም ወደ እርሷ ጎጆ እየቀረበ መጣ፡፡

ጎጆዋ ተነቃነቀ፡፡ የመሬት መንቀጥቀጥ የመጣ መሰለ፡፡ ቱር ብላ ወጣችና ዙሪያዋን እያንዣበበች ተመለካከተች፡፡ የሰማይ ስባሪ የሚያህል አሞራ እርሷ ጎጆ የሠራችበት ዛፍ፣ ያውም ጎጆው ከተንጠለጠለበት ግንድ ላይ ክንፉን እያማታ ቆሟል፡፡ አንዳች የሚበላ አጥንት በምንቃሩ ወሽቆ ከሥጋው ጋር ይታገላል፡፡ እርሱ ከሥጋው ጋር በታገለ ቁጥር የእርሷ ጎጆ ይነቃነቃል፡፡ ክንፉን ግራና ቀኝ ባማታው ቁጥር ኃይለኛ ነውጥ ይፈጥራል፡፡ ነውጡ በተፈጠረ ቁጥርም የእርሷ ጎጆ ይፈርሳል፡፡ አሞራው ጎጆዋን በግማሽ አፍርሶት ሄደ፡፡ እርሷም በዚያ አሳዛኝ ዝማሬዋ ታስተዛዝል ጀመር፡፡

እያስተዛዘለች እያለ አሞራው አሁንም እንደገና ከእርሱ ቁመት የማይተናነስ ሙዳ ሥጋ ይዞ መጣ፡፡ ለክፋቱ ደግሞ እዚያው ግንድ ላይ ቆሞ ቀሪውን የወፍ ጎጆ ይነቀንቀው ጀመር፡፡ አሞራው አራተኛ ጉርሻ ላይ ሲደርስ ጎጆው ሙሉ በሙሉ ፈረሰ፡፡ የወፏም ዝማሬ ወደ እንጉርጉሮ ተለወጠ፡፡የት ትሂድ? የትስ መሄጃ አላት? ወፍ ባትሆን ተመኘች፡፡ ግን ወፍ ናት፡፡ አሞራው ለመብላት ሲል ጎጆዋን ያፈርሳል፡፡ እርሷ ግን ጎጆዋን እሠራ ብላ የአንዲት ፍሬ ፍርካሽ እንኳን ለመቅመስ ዕድል አልነበራትም፡፡

አዝና አዝና ስትጨርስ የግድ ነውና ጎጆዋን ለመሥራት እንደገና ፈለገች፤ እንደገና አሰበች፡፡ እንደገናም ሣርና እንጨት፣ ቅጠልና ጭድ ፍለጋ መንከራተት ጀመረች፡፡ የነበረው እንዳልነበረ ሆኗልና እንደገና ሀ ብላ ወጠነች፡፡ አሁን ዜማዋ ከፊል እንጎርጉሮ፣ ከፊል ምሬት፣ ከፊል ደግሞ ተስፋ ሆኗል፡፡ ተስፋ ያልቆረጠችው ተስፋ ያለው ነገር አግኝታ አይደለም፡፡ ተስፋ ከመቁረጥ የሚሻል ሆኖ እንጂ፡፡

አሁን ከሰውም ከእንስሳትም ርቃ ዓባይ ዳር በሚገኝ የደንገል ዛፍ ላይ ጎጆዋን መሥራት ጀመረች፡፡ ምናልባት በዓለም ከመኖር ብሕትውናው ይሻል ይሆን ብላ፡፡ ‹‹ወይከውን ከመ ዕጽ እንተ ትክልት ኀበ ሙሐዘ ማይ – በወንዝ ዳር እንደተተከለች ተክል ይሆናል፤ እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ – ፍሬዋን በየጊዜው እንደምትሰጥ፤ ወቆጽላኒ ኢይነግፍ – ፍሬዋም እንደማይደርቅ›› የሚለውን አስባ፡፡

እንደ ገና ድካም እንደገና ልፋት፡፡ ጎጆዋን ልትቀልስ፣ ዕንቁላሏን ልትጥል፤ ጫጩት ልትፈለፍል፡፡ ከመጀመሪያው ቤት ሁለተኛው፣ ከሁለተኛውም ሦስተኛው ከበዳት፡፡ እንጨቱ እየተማገደ፣ ሣሩ እየተመደመደ፣ ጭዱም እየተወሰደ አልቋል፡፡ ለምለሙ ጊዜ አልፎ የበጋው ደረቅ ወቅት መጥቷል፡፡ በቅርብ ይገኝ የነበረው ነገር ሁሉ ርቋል፡፡ ግን ምን ይደረጋል፡፡  

ክንፏን እስከሚያማት ድረስ ባክና በሰበሰበችው እንጨት፣ ሣርና ጭድ ጎጆዋን ለሦስተኛ ጊዜ ቀለሰች፡፡ አንድ ሦስት ቀን የቀደመው መዓት ይመጣል ብላ ብትጠብቅ ምን የለም፡፡ እንዲህ ከሰውም ከእንስሳም መራቁ ይሻላል ብላ በምርጫዋ ተደሰተች፡፡ አንድ አንድ እያለችም ዕንቁላሏን መጣል ጀመረች፡፡ ችግሩ ግን ያን ጊዜ መጣ፡፡ እርሷ ዕንቁላሏን ጥላ ምግብ ፍለጋ ሄዳ ስትመለስ ዕንቁላሏን አታገኘውም፡፡ ሁለት ሦስት ቀን ወድቆ ይሆናል ብላ አሰበች፤ ጥፋቱም የእርሷ እንደሆነ አመነች፡፡ እንዳይወድቅ ለማድረግም ጎጆዋን እንደገና አጠባበቀች፡፡ በአራተኛው ቀን ግን አሁንም ዕንቁላሏን አላገኘችውም፡፡ ፈለገችው፡፡ እንዳች ስባሪ በአካባቢው አላገኘችም፡፡ በአምስተኛው ቀን ዕንቁላሏን ጥላ ከጎጆዋ ወጣችና እልፍ ብላ በሌላ ዛፍ ላይ ተቀምጣ የሚሆነውን ማየት ጀመረች፡፡

እነሆ ጉዱ፡፡

እርሷ ወጣ ከማለቷ አንድ ዕባብ በግንዱ ላይ እየተሳበ መጣ፡፡ ዕባቡ የመጣው ከወንዙ ዳር ነው፡፡ አስጠሊታ ራሱን ወደ ጎጆዋ አዝልቆ ዕንቁላሏን ሰለቀጠው፡፡ ነፍስ አልነበራትም እንጂ ድንጋጤው ነፍሷን ያወጣው ነበር፡፡ አሁን የከፋ አደጋ መጣ፡፡ ቤቷ አይደለም የፈረሰው፤ ዕንቁላሏ ነው የሚበላው፡፡ ምትኳ፣ ዘሯ፣ ተስፋዋ፣ ሀልወቷ፣ ኑባሬዋ ነው የሚበላው፡፡ ዕንቁላል እንዳትጥል አልተከለከለችም፤ የምትጥለው ግን ለሌላ ሆነ፡፡ እርሷ አንድ ቀን ዕንቁላል መጣል ታቆማለች፡፡ ያን ጊዜ ህ ዕንቁላል የለመደ ዕባብ እርሷን መብላት ይጀምራል፡፡ ከሁሉም ተገላገልኩ ብላ የመጣችበት ቦታ ከሁሉም የባሰ ሆነ፡፡

በረረረች፣ ከነፈች፣ ወጣች፣ ወረደች፣ ከነፋሱም ጋር ሄደች፣ ከነፋሱም በተቃራኒም ነጎደች፡፡ መሬት ወረደች፣ ወንዝ ውስጥ ገባች፡፡ በመጨረሻ ደከማት፡፡ ሲደክማት አንድ ዛፍ ላይ ቆማ እንዲህ እያለች ታንጎራጉር ጀመር፡፡

ኦ እለሎ፣ ኦ እለሎ

ኦ እለሎ፣ ኦ እለሎ

ወዴት ሄጄ ልኑር

ወዴት ሄጄ ልሥራ፤

ባጡ ሥር ስሠራ

ልጆቹ መከራ፣

ዛፉ ላይ ስሠራ

አሞራው መከራ፣

ወንዙ ዳር ስሠራ

ዕባቡ መከራ፡፡

ወዴት ሄጄ ልኑር፣

የት ሄጄ የት ልሥራ፤

የት ውዬ የት ልደር፤

 © ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሁለተኛውን የሕዝብ ንቅናቄ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ፓርቲው ከዚህ ቀደመ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል የሕዝባዊ ንቅናቄ መድረኮች አዘጋጅቷል። አሁን ደግሞ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪ ቃል ፕሮግራሙን ይፋ አድርጓል። ባለፈው እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም በደሴ ከተማ ፕሮግራሙን በሰላማዊ ሰልፍ አከናውኗል። በደሴ ስለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍና “የሚሊዮኖች ድምፅ […]

የማርቆስ ብዙነህ ደብዳቤ፤ 1- “በርካታ ትምህርት ቤቶች፤ ዩኒቨርስቲና የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ፤ የተጠየቀው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን” ይላል፤ በአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቅ ክፍል ሀላፊ፤ በአቶ ማርቆስ ብዙነህ ማንደፍሮ፤ መጋቢት 23 ቀን 2006/2014 የተፈረመው ደብዳቤ፡፡ አንድነት፤ ሰልፉን ለማድረግ ያቀረባቸው መስመሮች 3 ሲሆኑ፤ ሶስቱም መስመሮች […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለመጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ሊያደርገው ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የመስተዳድሩ የሰላማዊ ሰልፍና ማሳወቂያ ክፍል ዘግይቶ በጻፈው ደብዳቤ የሰልፉ ቀን በሌላ ፕሮግራም መያዙን በመጥቀስ የቀን ለውጥ እንዲደረግ መጠየቁ አይዘነጋም፡፡ ፓርቲው የቀረበውን አስተያየት በመቀበል ሰልፉ ለሚያዚያ 5 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ መወሰኑን በመግለጽ ለመስተዳድሩ አሳውቋል፡፡ሆኖም መስተዳድሩ ዕለቱ በታላቁ ሩጫ መያዙን በመጥቀስ ለፖሊስ ጥበቃ […]

የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ አራት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በደሴ ሰላማዊ በማድረግ የተጀመረ ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች በማድረግ ይቀጥላል። በደሴ ከተማ የተደረገዉን እንቅስቃሴ በደንቬር የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ስፖንሰር ያደረጉት ሲሆን፣ በአዲስ አበባ የሚደረገዉን የመጀመሪያው እንቅስቅሴን ላስ ቬጋሶች፣ ሃዋሳ አትላንታዎች፣ ድሬደዋን የደብተራ ፓልቶክ ክፍል፣ […]

«ከምዕራብ ሸዋ ተፈናቅለው በፌዴሬሽኑ አፈ ጉባዔ አግባቢነት የተመለሱት ዜጎች መሬታቸውን በሃይል ተነጠቁ» ሲል ፍኖት ዘገበ። “ከሰላሳ የማያንሱ የምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ ባጅላ ዳሌ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነዋሪዎች «ወደ ክልላችሁ ተመለሱ » ተብለው መሬታቸውን ለመነጠቅ መቃረባቸውን ለማመልከት አዲስ አበባ በመምጣት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተ/ብርሃንን ካናገሩ በኋላ አፈ ጉባኤው ‹‹ወደ ቀዬአችሁ […]

ኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢና በአካባቢዋ በሚገኙ ስደተኞች ላይ በመንግሥቱ እየተፈፀመ ነው የሚሉት አፈሣና እሥራት በእጅጉ እያሣሰባቸው መሆኑን ስደተኞቹ እየገለፁ ነው፡፡

የኬንያ መንግሥት በሃገሪቱ ውስጥ እየደረሱ ያሉት ፍንዳታዎች ለፀጥታዬ አደጋና ሥጋት ደቅነዋል በሚል ስደተኞች ወደዚያ ሲገቡ ወደየተመደቡባቸው ሠፈሮቻቸው እንዲመለሱ በቅርቡ ማስታወቂያ አውጥቶ እንደነበረ ይታወሣል፡፡

ከዚያ ማስታወቂያ ወዲህ ባለፉት ከአምስት እስከ ሰባት በሚሆኑ ቀናት ብዙ ስደተኞች እየታፈሱና እየተንገላቱ መሆኑ ይሰማል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የደቡብ ሱዳን ገዥ ፓርቲ – የሱዳን ሕዝብ አርነት ንቅናቄ – ኤስፒኤልኤም ውስጣዊ ችግር ከተፈታ የሃገሪቱ ችግርም ሊፈታ ይችላል ሲሉ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የኢህአዴግ ሊቀመንበር ኃይለማርያም ደሣለኝ ተናግረዋል፡፡

ፓርቲው ራሱን ለሚገመግምበትና ለሚያይበት ቀጣይ ስብሰባ መንገድ የሚጠርግ ውይይት አዲስ አበባ ላይ ተከፍቷል፡፡

ውይይቱን የሚያስተባብሩትና የሚመሩት የኢትየጵያው ገዥ ፓርቲ ኢህአዴግና የደቡብ አፍሪካው ገዥ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ምክር ቤት – ኤኤንሲ ሲሆኑ በኢትየጵያ በኩል የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዩ አማካሪ አቶ በረከት ስምዖን በዚሁ ኃላፊነት ተሰይመዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

 

ባለፉት አርባ ዓመታት አፍሪካ በካፒታል ሽሽት ምክንያት ከ103 ትሪሊዮን ዶላር በላይ ማጣቷ ተገለፀ፡፡

አፍሪካ ይህንን ገንዘብ ማስቀረት ችላ ቢሆን ኖሮ የሚሌኒየሙን የልማት ግቦች ከማሳካት የበለጠ ብልፅግና ይኖራት ነበር ተብሏል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምፅን ዘገባ ያዳምጡ

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም አንድነት በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የያዘውን ፕሮግራም እንዲያራዝም መጠየቁን ተከትሎ አንድነት ሰልፉን ለሚያዚያ 5 ቀን 2006 በማራዘም የእውቅና ደብዳቤ ጠይቆ ነበር፡፡ መስተዳድሩ በዕለቱ ሌላ ፕሮግራም መየዙን በማውሳት ሰልፉ ሚያዚያ 4 ቀን 2006 ሊደረግ እንደሚችል የእውቅና ደብዳቤ ለፓርቲው ጽፎ ነበር፡፡ ፓርቲው በበኩሉ ዕለቱ ለሰላማዊ ሰልፍ አመቺ አለመሆኑን አስረድቷል፣ መስተዳድሩ ፓርቲው […]

ሎንዶን ብሪታን ዉስጥ በዝቅተኝነት ከሚመደቡት ትምህርት ቤቶች በአንዱ ይማር የነበረ አዳጊ ኢትዮጵያዊ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቢድ ካምሮንን ጨምሮ የሀገሪቱ 19 ሚኒስትሮች ወደተማሩበት ኮሌጅ የመግባት እድል አገኘ።

‘አረና ትግራይ’ በትግራይ ክልል ምሥራቃዊ ዞን አፅቢ ወምበርታ ሕዝባዊ ስብሰባ ለማካሄድ በተንቀሳቀሰበት ባለፈዉ ቅዳሜና እሁድ ከፍተኛ የአመራር አባላቱን ጨምሮ አባላቱና ደጋፊዎቹ መታሰራቸዉንና በድንጋይ መደብደባቸውን አመለከተ።

በአሁኑ ወቅት የአፍሪቃና የአውሮፓ የኤኮኖሚ ግንኙነት አዲስ አቅጣጫ እንዲከተል ያስፈለገበት ምክንያትና ጥቅሙ ምንድነው ? የኤኮኖሚ ግንኙነቱ በሁለቱ ክፍለ ዓለማት የፖለቲካና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይስ ምን ዓይነት ተፅእኖ ያሳድራል ?ከኤኮኖሚው ዓለም የሚያነሳቸው ጉዳዮች ናቸው ።

በዛሬው የሙዚቃ ቃና ፕሮግራም በአሜሪካ የቢል ቦርድ ሰንጠረዥ ላይ ከመቶዎቹ ምርጥ ዜማዎች መካከል በዚህ ሳምንት ከአንድኛ እስከ አስረኛ ደረጃ የወጡትን ምርጥ ዜማዎች ያጠቃልላል::

በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ በአክራሪነት የተፈረጁት ‹አንዳንድ ግለሰቦች›÷ ‹‹አንዲት ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት›› የሚሉቱም ናቸው፡፡ ታዲያ ምን ይበሉ?! ‹‹በይፋ አክራሪ ናችኹ ያለን አካል የለም፡፡›› /ተስፋዬ ቢኾነኝ፤ የማኅበር ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ/ ‹‹በጉዳዩ ላይ የጠራ ነገር የለም፤ ነገር ግን ጢስ አለ፡፡ ከጢሱ በስተጀርባ ያለው እሳት ይኹን እሳተ ገሞራ ባይታወቅም ለጊዜው ግን ማኅበሩን በተመለከተ ግልጽ የኾነ ነገር የለም።›› /ዲ.ን ዳንኤል ክብረት/ …