የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም የበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ አደረጉ፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ አስተባባሪነት የተዘጋጀው ይህ ፕሮግራም እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ከቀኑ 7 ሰዓት እስከ 9፡ 45 ‹‹በጎ ፍቃደኝነት ለነጻነት›› በሚል መርህ በፓርቲው ጽህፈት ቤት ተከናውኗል፡፡

ዋና ዓላማውን በወሊድ ጊዜ በሚፈጠር የደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰት የእናቶች ሞትን ለመቀነስ መሆኑን የፓርቲው የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ወ/ሮ ሀና ዋለልኝ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የለጋሾቹ ምስል በከፊል

የሚቀጥለውን ትረካ ለመጻፍ ብዙ ሀሳብ ውስጥ ገብቼ ነበር፡፡ ብጽፈውስ ምን ዋጋ አለው የሚል ስሜትም ተጭኖኝ ነበር፡፡ ሆኖም ‹ጅብ በማያውቁት ሀገር ቁርበት አንጥፋልኝ› እንዲሉ ከላይ የተጠቀሰው ብርሃኑ ደቡር አባ መላ በአዲሶቹ አለቆቹ የተረቀቁለትን ቃለ መጠይቆች ሲያነበንብ መስማቱ ስለሰለቸኝ ‹ማን ያውጋ የነበረ ማን ያርዳ የቀበረ› በማለት የልጅነት ጓደኛዬን ሳልወድ ለማጋለጥ ወሰንኩ፡፡ እኔና ብርሃኑ ዳምጤ በአንድ ማዕድ እየበላን […]

ወ/ሮ አስቴር  ማሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር ሆነው ተሾመዋል፡፡

በኢትዮጵያ አንዲት ሴት እንዲህ ባለው ከፍተኛ ሥልጣን ላይ ስትቀመጥ ወ/ሮ አስቴር የመጀመሪያዋ ናቸው፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ

በደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖች መካከል ሲካሄድ የቆየው ድርድር ይህን ያህል ጊዜ በመውሰዱ ደስተኞች አይደለንም ሲሉ የምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮች የጋራ ልማት ባለሥልጣን – ኢጋድ ዋና አደራዳሪ የቀድሞ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ስዩም መስፍን ተናግረዋል።

የመንግሥትና የተቃዋሚ ተደራዳሪዎች ደረስንበት ያሉት ስምምነትም የተፈቱትን ባለሥልጣናት ያላካተተ ነው ሲሉ እንደማይቀበሉት ገልፀዋል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ

ለአፍሪካ የጤና ባለሙያዎች የጋራ መድረክ ይፈጥራል የተባለ የመላ አፍሪካ የሕክምና ዶክተሮችና የጤና ጉባዔ ከሁለት ሣምንታት በኋላ አዲስ አበባ ላይ ይካሄዳል፡፡

በዓይነቱ በአፍሪካ የመጀመሪያ እንደሆነ የተገለፀው ጉባዔ የሚዘጋጀው በአሜሪካ፣ በአውሮፓና በአፍሪካ ከሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ማኅበራትና ድርጅቶች ጋር በመተባበር ነው፡፡

እስክንድር ፍሬው ከሚያዘጋጁት ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ተነጋግሯል፤ ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይዘሮ አስቴር ማሞን የሲቭል ሰርቪስ ሚንስትር እና በምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር እና ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪ እንዲሆኑ በዛሬው ዕለት ሾመ። ምክር ቤቱ ይህን ሹመት ያፀደቀው በጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አቅራቢነት ነው።

«በቅርቡ ከአንድነት ለደሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጋር ለመዋሃድ ጥረት እያደረጋችሁ ነው ያላችሁት። ሂደቱ ምን ላይ ይገኛል ? » በሚል ከአዉስትራሊያ ከሚገኝ ኤስ፣ብ.ሲ ራዲዮ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የመኢአድ ሊቀመነበር አቶ አበባዉ መሃሪ በአንድነት እና በመኢአድ መካከል ያሉ ልዩነቶች ከባድ እንዳልሆኑ በመግልጽ ፓርቲዎቹ ዉህደት እንደሚፈጽሙ ያላቸውን ሙሉ ተስፋ ገልጸዋል። «ተበታትነን ገዢዉን ፓርቲ ለማሽነፍ ከአብድ ነው» ያሉት አቶ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የዩክሬንና የሩስያ ውዝግብ ተባብሷል ። በሩስያ ስር መሆን እንፈልጋለን የሚሉ ኃይሎች ካለፈው እሁድ አንስቶ በአንዳንድ የምሥራቅ ዩክሬን ከተሞች ነፃነታችንን አውጀናል እያሉ ነው ። በነዚህ ኃይሎች ላይ ዩክሬን እርምጃ እንዳትወስድ ሩስያ እያስጠነቀቀች ነው ።

ኃይለኛ ትኩሳት፤ ራስ ምታትና የጡንቻ ህመም ከሚያስከትላቸዉ የህመም ስሜቶች ይጠቀሳሉ። በትንፋሽ ሳይሆን ከአካል በሚወጣ ፈሳሽና በመነካካት ይተላለፋል። እስካሁንም መድሃኒት አልተገኘለትም ኢቦላ ቫይረስ። ከሳምንታት በፊት ጊኒ ዉስጥ በሽታዉ ተከስቷል

በስዊድን በካሮሊንስካ ኢንስቲቱት እና በ«ሳይንስ ፎር ላይፍ» በተባለ ድርጅት መሪነት አምስት የስዊድን ዩኒቨርሲቲዎችን ያጠቃለለው የካንሰር ተመራማሪ የጥናት ቡድን በዓይነቱ ልዩ የካንሰር መከላከያ ዘዴ እንዳገኘ

የጥቁር ዓባይ ምንጭ የሆነው የጣና ሐይቅ እና አካባቢው በሚገባ ካልተጠበቀ እና እንክብካቤ ካልተደረገለት በመጪው ጊዜ አሳሳቢ መዘዝ ሊከተል እንደሚችል የጀርመን የተፈጥሮ ጥበቃ ድርጅቶች ጠበብት ጠቁመዋል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

ባለፉት አራት አስርታት ሀገሪቱ አያሌ ተግዳሮቶችን መጋፈጧ ባይዘነጋም፤ በተለያየ ጊዜ ሚሊዮኖችን ካረገፈው አሰቃቂው ረሃብ በማይተናነስ መልኩ ሕዝቦቿን ዋጋ ያስከፈለ ጉዳይ ቢኖር የፍትሕ አለመከበር ያስከተለው ሁለንተናዊ ምስቅልቅሎሽ ነው ብሎ ለመናገር የሚያስደፍሩ በርካታ ማሳያዎች አሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዛሬ እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ/ም ዓረና ትገራይ ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ በምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወንበርታ ወረዳ ጠርቶ ያካሄደ ሲሆን ከትናትና ጀምሮ ህዝቡን ወደ ስብሰባው እንዲመጣ የሚቀሰቅሱ አባሎችና አመራሮች ከድንጋይ ውርወራና የቡድን ረብሻ ባለፈ ከተከራዩት አልጋ አስወጥቶ ሌሌት የትም ተጥለው እንዲወድቁ ለማድረግ እጅግ ኢ-ሰብአዊ ተግባር መፈፀሙን ተገልፆ ነበር ፡፡ የአፅቢ ፖሊስ አባላቶቻችን ከተከራየትና ገንዘቡን ከፍለው […]

የአንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ንቅናቄ በሚል የጀመረው እንቅስቃሴ፣ በዉጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ድጋፍ እያገኘ መጥቷል። ኢትዮጵያዉያን በአካባቢያቸው ካሉ የአንድነት ድጋፍ ማህበራት ጋር በመሆን ከሚደግፉት በተጨማሪ፣ የተለያዩ ሲቪክ ማህበራት፣ በዉጭ አገር ያሉ የፖለቲካ ደርጅቶች እንዲሁም ግለሰቦች ሳይቀር፣ ጉዳዩ የአንድ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን የሕዝብ ጉዳይ ነው፣ በሚል ከሚሊዮኖች አንዱ ነን እያሉ ነው። ከነዚህ፣ አገር ቤት እየተደረገ ያለዉን እንቅስቃሴ ከሚደግፉ […]

 

ሰኞ፤ መጋቢት 29 የዓለም የጤና ቀን ነው፤ ዕለቱን ምክንያት በማድረግም መንግሥታዊ ያልሆነው ዓለምአቀፍ ድርጅት ኸልፕኤጅ – ኢንተርናሽናል ዛሬ ባወጣው መግለጫ በዓለም ዙሪያ 76 ሚሊየን አዛውንት እጅግ አስፈላጊ የሆኑ የጤና አገልግሎቶችን ተነፍገው እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡

ኸልፕኤጅ “ዕድሜ ተግባር ይጠይቃል” ሲል በሰየመው ዘመቻው ከዕድሜ ጋር የተያያዙ ችግሮችንና የአገልግሎቶች አቅርቦቶች የሚገኙበትን ደረጃ ለማስተዋወቅ እየጣረ ነው፡፡

የኸልፕኤጅ-ኢንተርናሽናል የታንዛኒያ ዳይሬክተር የሆኑት አምለሰት ቴዎድሮስ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል “ዕድሜ ተግባር ይጠይቃል” የሚለው ዘመቻ ግብ በዕድሜ የገፉ ሰዎች ከመሪዎቻቸው ጋር በቀጥታ መነጋገር እንዲችሉ የተጠናከረ አቅም እንዲኖራቸው ማድረግ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን…

 

የጋዜጠኛና መምህርት ወ/ሮ ዓለምሰገድ ኅሩይ አስከሬን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ፤ ሰኞ፣ መጋቢት 29/2006 ዓ.ም በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መካነ-መቃብር ተፈፅሟል፡፡

ወ/ሮ ዓለምሰገድ ያረፉት ባለፈው ሣምንት መጋቢት 23/2006 ዓ.ም ነበር፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

አሜሪካ የሚገኘዉ የዓለም ዓቀፍ ወንዞች ተቋም፣ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጥናት ያካሄደዉ ቡድን ያወጣዉ ዘገባ፤ ግድቡ በተቀናጀ እና መጠነ ሰፊ ጥናት ላይ ያልተመሠረተ መሆኑን የሚጠቁም እንደሆነ ገለጸ።

ፓሪስ ውስጥ በተካሄደው የማራቶን ሩጫ ውድድር አሸናፊ የሆነው ቀነኒሣ በቀለ ጡንቻው ላይ ህመም ባይሰማው ኖሮ የበለጠ ፈጣን ሠዓት ሊያስመዘግብ ይችል እንደነበር ለዶቸቬለ ገለፀ። በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ ሊቨርፑል የዋንጫ ግስጋሴውን እያሳመረ ነው። ቸልሲ እና ማንቸስተር ሲቲ ዋነኞቹ የሊቨርፑል ተፎካካሪዎች ሆነዋል።

የምርጫዉ ሒደት፤ነፃነቱ፤ አፎካካሪ፤ አሳታፊነቱም፤ ያዩ እንደመሰከሩት ፤ለእልቂት ፍጅት ማዕከሊቱ ታሪካዊት ሐገር አዲስ ታሪክ ነዉ።አፊቃኒስታን።ዘንድሮ አስራ-ሰወስት ዘመን የተዋጋባትን-የዉጪ ጦር ሸኝታ የአስራ-ዘመን ታሪኳን ለሚቀይር ሌላ ታሪክም ተሞሽራለች።

የአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባ ክፍል ኦፊሰር የሆኑትን አቶ ማርቆስ ብዙነህን ለማነጋገር ዛሬ ጠዋት ወደ ቢሯቸው ያቀኑት ሶስት የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ አመራሮች በኦፊሰሩ ጥያቄያቸው ተቀባይነት ማግኘቱ እንደተነገራቸው ገልጸዋል፡፡ አንድነት ፓርቲ የ‹‹እሪታ ቀን›› በማለት የሰየመውን ሰላማዊ ሰልፍ ለመጋቢት 28 ቀን 2006 ለማድረግ ለመስተዳድሩ የእውቅና ጥያቄ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም መስተዳድሩ በከተማው የህዳሴ ግድቡን የተመለከቱ […]

አንድነት ፓርቲ ለመጋቢት 28/2006 ጠርቶት በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ለህዝብ የተዘጋጀ በራሪ ወረቀት ሲበትኑ በህገ ወጥ መንገድ በቁጥጥር ስር ከዋሉት የአንድነት ፓርቲ አባላት መካከል በስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ የሚገኙት አክሊሉ ሰይፉና ወርቁ እንድሮ መታሰራቸውን በመቃወም የርሃብ አድማ መምታታቸው ታውቋል፡፡ ሁለቱ ወጣቶች እስከ ነገ የማይለቀቁ ከሆነ ሚክሲኮ በሚገኘው ፍርድ ቤት ከፖሊስ ጣብያ እንደሚቀርቡ ይጠበቃል፡፡ አንድነት የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ […]

መግቢያ በዚህ ጽሁፍ ሥር ለውይይት ይሆን ዘንድ የምናነሳው ኣሳብ constitutional patriotism ወይም ህገ መንግስታዊ ቀናዒነት ወይም ኣርበኝነት የሚባለው ጽንሰ ሃሳብ ባለፈው በተከታታይ ካቀረብኳት የ Conventional Cultural Unity ወይም በስምምነት ላይ የተመሰረት ባህላዊ ውህደት ካልኩት ኣሳብ ጋር እንዴት እንደሚለያይና በኢትዮጵያ ሁኔታ ከሁለቱ ኣሳቦች የትኛው ተገቢና ችግር ፈቺ ሊሆን እንደሚችል ኣሳብ ለማፍራት ነው። በቅድሚያ ኣንድን ፖለቲካዊ የሆነ […]

እኛ የምናውቃት ኢትዮጲያ ከግማሽ በላይ ህዝቧ በመብራትና በውሃ እጦት የሚሰቃይባት ፣ በስልክና በኔትወርክ ችግር የሚማረርባት ፣ በመልካም አስተዳደር እጦት አሳሩን የሚበላባት ፣ አብዛኛው ህዝቧ የዛሬን እንጂ የነገን ማቀድ የማይችልባት ፣ የተለያዩ ተንታኞችና አለማቀፍድርጅቶች “ችግር አለ” ብለው የሚያስጠነቅቋት ፣ ለዲሞክራሲ ፈር ቀዳጅ መሆን የሚገባው የፖለቲካ ስርዓት የሚያስፈራና ደም ደም የሚሸትባት፣ ብዙ ዜናና ትንታኔ ስለ አንዲት የመንግስት […]

ከሓላፊነታቸው ውጭ የሚንቀሳቀሱ ፕሮቴስታንትና ጉዳዩን ፖሊቲካዊ ያደረጉ የደኅንነት አባላት ነን ባዮች የኮሌጁን ሓላፊዎች በመጫን ተጠርጣሪዎቹን ከተጠያቂነት ለማዳን እየሠሩ ነው፤ ተጠርጣሪዎቹ በኮሌጁ አስተዳደር የተከለከለ ስብሰባ በግቢው እንዲያካሒዱ ረድተዋቸዋል፡፡ በ‹ደኅንነት አባላቱ› የሚደገፉትና ‹‹የኢሕአዴግ ተወካዮች ነን›› የሚሉት ተጠርጣሪዎቹ፣ ለሃይማኖታቸው የቆሙትን ብዙኃኑን የኮሌጁን ደቀ መዛሙርት በስለትና በፌሮ ብረት የታገዘ ዛቻና ማስፈራራት እያደረሱባቸው ነው፤ ደቀ መዛሙርቱና የኮሌጁ አስተዳደር ጉዳዩን ለጸጥታ …


Source: Courtesy of www.adebabay.com/  PDF

 ይህ ጽሑፍ የእኔን የግል ምልከታና አስተያየት ብቻ የሚመለከት እንጂ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ስሙ የተጠቀሰውን ማኅበርም ሆነ ከእርሱ ጋር የአገልግሎት ግንኙነት ያላቸውን ተቋማት የማይመለከት መሆኑን አበክሬ በመግለጽ ልጀምር።  

  አንድ ብሒል አለ። ውሸትን ደጋግመው ቢናገሩት እንደ እውነት የሚቀበለው ሰው መፍጠር ይቻላል። ስለዚህም ሐሰተኞች ሐሰታቸውን ሳያሰልሱ በተናገሩት መጠን፦ አንደኛ ራሳቸውንም በሐሰታቸው እውነትነት ያሳምናሉ፤ ብሎም ሌሎችን ማሳመን ይችላሉ። ደጋግሞ የመናገር ጥቅሙ ይኼው ነው።

አንዳንድ እውነት የያዙ ሰዎች ደግሞ “እውነት እስከያዝን ድረስ ደጋግሞ መናገር ለምን ይገባል?” ብለው ያቀርባሉ። እውነት አላቸው። ፀሐይ ሲወጣ ጨለማ መሸሹ፣ ሻማ ሲለኮስ ብርሃን መፈንጠቁ ላይቀር “ጨለማን ማውገዝ ምን ጥቅም አለው?” ይላሉ። ይህም እውነት ነው። “ጨለማን ደጋግሞ ከማውገዝ አንድ ሻማ ማብራት” እንደተባለው። ነገር ግን ሐሰት ተደጋግማ በመነገሯ ተከታይ መፍጠር እስከቻለች ድረስ እውነትን ደጋግሞ በመናገር የሚመጣ ምን ችግር አለ? ሻማውንም እየለኮሱ እውነቱንም ደጋግሞ መናገሩስ? ስለዚህ በእውነት ተደጋግሞ መነገር፣ በሻማ መለኮስም አምናለኹ። ደጊመ ቃል እንዲሉ የኢትዮጵያ ሊቃውንት።

 እንኳን አገር ቤት ያለው አንባቢ ይቅርና እኛ ከአገራችን በብዙ ሺህ ማይሎች ርቀን የምንገኘው ሳንቀር በየዕለቱ የምንኮመኩመው አዲሱ ትኩስ ዜና የማኅበረ ቅዱሳን እና “የተጠመደለት ወጥመድ” ጉዳይ ነው። በማኅበራዊ ድረ ገጾች እና በጡመራ መድረኮች፣ እንዲህ በሕትመት ውጤቶች በሰፊው ሽፋን ያገኘ ጉዳይ ሆኗል። ብዙ ኢትዮጵያውያን (እምነት ሳይለይ) ይህንን ጣልቃ ገብነት በጽኑዕ እየተቃወሙት እያወገዙት ነው። “ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ የሚባል ከሆነ እኔም አክራሪነትን እወደዋለኹ” የሚሉ ሐሳቦች በብዛት ተጽፈው ተመልክቻለኹ።

“የአክራሪነቱ ነገር”፣ ነፍሳቸውን ይማረውና አቶ መለስ በፓርላማ ተናግረውት በነበረ ጊዜ፣ እኔን ጨምሮ ብዙ ፀሐፍት አስተያየታቸውን የሰጡበት ከመሆኑ አንጻር ወደዚያ መመለስ አይገባ ይሆናል። ማኅበሩ ከፓርቲ ፖለቲካ ጋር ግንኙነት እንዳለው በመንግሥት ሰዎች እና በደጋፊዎቻቸው የሚነሣውን ሐሳብ በተመለከተ ግን የግል አስተያየቴን ላሰፍር እወዳለኹ።

ማኅበሩ ፖለቲካ ውስጥ አለበት? ለመሆኑ ፖለቲካ ውስጥ መግባት/ አለመግባት ምንድነው? ማንኛውም ሰው የተባለ ፍጡር ፖለቲካዊ አመለካከት አለው። ፖለቲካ አልወድም የሚሉ ሰዎች ራሳቸው እንኳን ፖለቲካዊ አቋም አላቸው። ልዩነቱ እያወቁ ማወቅ እና ሳያውቁ መኖር ናቸው። የተለያዩ ሐሳቦች እስካሉ ድረስ፣ አስተዳደሮች፣ ገዢዎችና ተገዢዎች እስካለን ድረስ ፖለቲካዊ አመለካከቶች መኖራቸው ግድ ይመስለኛል። “ፖለቲካ እና ኮረንቲ በሩቅ” የሚለው ሰው ራሱ በኮረንቲ ከመጠቀም፣ ሕይወቱ በፖለቲካ ተጽዕኖ ሥር መውደቁ እስካለ ድረስ ፖለቲካ የማይነካው ኢትዮጵያዊ አይኖርም።

ይኼ በፖለቲካ ምሁራን ሳይሆን እኔን በመሳሰሉ ለፖለቲካው ዕውቀት ተርታ በሆንን ሰዎች ቋንቋ “ፖለቲካ ውስጥ መግባት ወይም አለመግባት” የምንለው የፓርቲ ፖለቲካ ውስጥ መግባት ማለታችን እንደሆነ ይሰማኛል። ፖለቲከኞች የምንላቸው እንደዚያ ያሉ ሰዎችን ነውና። ማኅበረ ቅዱሳን “ፖለቲካ ውስጥ ገባ/ አልገባም” የሚለውንም የምፈታው በዚሁ አንድምታውና አገባቡ ብቻ ነው።

ማኅበሩ በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ አባላት አሉት። አባላቱ ሰዎች እንደመሆናቸው ፖለቲካዊ አመለካከት አላቸው። ማኅበሩን በአባልነት ለመቀላቀል የሚያበቃቸው ግን ይህ ፖለቲካዊ አመለካከታቸው አይደለም። የአባላቱ የዓላማ አንድነትና መሠረቱ ማኅበሩ የሚያራምደው ቤተ ክርስቲያናዊ አቋም ብቻ ነው። በሃይማኖትና በአገልግሎት ዓላማ አንድ ናቸው እንጂ በፖለቲካ ርዕዮት የተሰባሰቡ አይደሉም። ሲጀመርስ ስለ ፖለቲካ አመለካከታቸው የት ተጠያይቀው? የት ተገማግመው? የት ተለካክተው? በየትኛው ጊዜ?

ስለዚህም ማኅበሩ አንድ ሃይማኖታዊ አቋም ያራምዳል እንጂ “አንድ ፖለቲካዊ አቋም” የሚባል የለውም። ሊኖረውም አይችልም። ለምን? ምክንያቱም “ፖለቲካዊ አቋምን ለማራመድ” መጀመሪያ ፖለቲካዊ አቋም መያዝ ያስፈልገዋል። ያንን ለማድረግ ደግሞ አባላቱን በሙሉ በዚህ ፖለቲካዊ አቋም ማሳመን ያስፈልጋል፤ ያንን ማድረግ ደግሞ አስቸጋሪ ብቻ ሳይሆን ማኅበሩ የያዘውን ሃይማኖታዊ አቋም የሚጻረርና ማንም ሳይነካው እንዲፈርስ የሚያደርገው ድማሚት ነው።

እዚህ ላይ መነሣት ያለበት ቁምነገር፤ የማኅበሩ አባላት በሃይማኖታዊም ሆነ በፖለቲካዊ አስተሳሰባቸው ራሳቸውን የቻሉ (ማለትም ማመዛዘን የሚችሉ) ክርስቲያኖች እንጂ የአንድ ቡድን ጀሌዎች አለመሆናቸውን ነው። ራሱን የቻለ አስተሳሰብ ያለው ማንኛውም ሰው፣ አባል የሚሆንበትን ድርጅት ያያል፤ ይመዝናል፣ ያስባል። እንደማይጠቅመውና እንደማይስማማበት ከተረዳ ይተወዋል። ጀሌ ግን የተነገረውን ተቀብሎ እንደ በቀቀን ያስተጋባል፤ ሳያውቅ አባል ይሆናል፤ በጥቂት ጥቅም ይደለላል፣ የሚኖርለትም-የሚሞትለትም ቋሚ መርሕ አይኖረውም።

ማኅበረ ቅዱሳንን እና አባላቱን በአገራችን ላለፉት 40 ዓመታት በጠነነው የፖለቲካ ድርጅት ጀሌነት መገምገም ትክክል የማይሆነው ለዚህ ነው። አባላቱ አገልጋዮች እንጂ ካድሬዎች አይደሉም። አመራር ላይ የሚቀመጡት ሰዎች በተራቸው ለማገልገል እንጂ ከሌላው አባል የተለየ መርሕ ለማራመድ አይችሉም። እናራምድ ቢሉም አባላቱ ጀሌዎች ስላልሆኑ ሊከተሏቸው የሚችሉበት ምንም መንገድ አይኖርም። የአባላቱ አንድነት በሃይማኖት እና በሃይማኖት ብቻ ነው። በበሰለ ሚዛን የሚለካቸው ቢኖር ኖሮ በዘር፣ በቋንቋ፣ በፖለቲካ አቋም፣ በትምህርት ደረጃ፣ በዕውቀት፣ በዕድሜ ወዘተ ወዘተ የተለያዩ እንጂ እንደ ሜዳ አህያ አንድ ወጥ እና ልሙጥ አለመሆናቸውን ይገነዘባል።

ስለዚህ አንድ አባል በግልጽ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ገብቶ የዜግነት ድርሻውን መወጣት ቢፈልግ ምን ማድረግ እንዳለበት ያውቃል። በማኅበሩ ውስጥ ያለውን የአመራር ኃላፊነት ማስረከብ ይኖርበታል። በዚህ ደረጃ በይፋ ከአመራርነታቸው በሰላም ተሰናብተው ወደፈቀዱት ይፋዊ የፖለቲካ መስመር መጓዝ የቻሉ ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ። ማኅበሩንም የፖለቲካ ድርጅታቸውንም መምራት የሚችሉበት መንገድ አይኖርም። እነርሱ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለማቸውን በማኅበሩ ላይ ለመጫን ቢፈልጉም እንኳን “የፍላጎት መላተም” (“conflict of interests”) ስለሚኖር ሊሳካላቸው አይችልም። የማኅበሩ አባላት በፖለቲካ መሳተፍ የዜግነት መብታቸው ሲሆን በማኅበሩ አገልግሎት መሳተፍ ደግሞ ሃይማኖታዊ የትሩፋት ሥራ እንደመሆኑ ማቻቻል የአባሉ ፈንታ ነው።

ማኅበሩ በፖለቲካ ውስጥ ገብቷል የሚለው (በተለይ በቤተ ክህነቱ ዙሪያ ያሉ ሰዎች) ከ1980ዎቹ ጀምሮ ሲያዜሙት የነበረ የሰለቸ ዜማ ነው። የሚነቅፉት ግን ማኅበሩ “ኢሕአዴግን አይደግፍም” ብለው ስላሰቡ እንጂ “ተቃዋሚ ነው ብለው ስላመኑ” ብቻ አይደለም። ለነገሩ እነዚህ መንግሥትን በዱላነት ለመጠቀም የሚፈልጉ፣ በመንፈሳዊም በዓለማዊም ሚዛን ቢመዘኑ ውኃ የማያነሱ ደመናዎች “ፖለቲካ” የሚሉት አጎብዳጅነትን ነው። መንግሥት እነሱን ይጠቀማል። እነሱም በአቅማቸው በመንግሥት ይጠቀማሉ።

ታዲያ ማኅበሩ የትኛውንም የፖለቲካ ድርጅት እንደማይደግፍ ነገሩን ሥራዬ ብሎ ለሚከታተል ለማንኛውም ሰው ግልጽ ሆኖ ሳለ በዚህ ጉዳይ መወንጀሉ ለምን አስፈለገ? ክርስቶስ አምላካችን ራሱ “ግብር አትክፈሉ ይላል? ለቄሳር አትገዙ ብሏል፤ ንጉሣችን ሳይሆን ንጉሥ ነኝ ብሏል” የሚል ፖለቲካዊ ክስ እንደቀረበበት ሃይማኖትን ብለው የሃይማኖት አገልግሎት ላይ የተሠማሩ ሰዎች በየዘመኑ የሚከሰሱበት ጉዳይ መሆኑን ማስተዋል ያስፈልገናል።

ቅዱስ ሉቃስ “ይህ ሕዝባችንን ሲያጣምም ለቄሣርም ግብር እንዳይሰጥ ሲከለክል ደግሞም፦ እኔ ክርስቶስ ንጉሥ ነኝ ሲል አገኘነው ብለው ይከሱት ጀመር” ሲል እንደጻፈው (ሉቃስ 23፥2)። በሌላው ዓለም ያለውን እንኳን ትተን በአገራችን ያለውን ብናስታውስ፣ ነገር ሰሪዎች በየዘመኑ የነበሩ ቅዱሳን አባቶቻችንን ከነገሥታቱ ጋር በማጋጨት በአደባባይ እስከመገረፍ ያደረሱበት ጊዜ፣ በግዞት በእስር እንዲማቅቁ ያደረጉበት ወቅት እንዳለ ታሪክ ያስተምረናል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን እና የደብረ ሊባኖስ እጬጌ ጻድቁ አባ ፊሊጶስን ለአብነት ብናንሣ አባ ጊዮርጊስ እንደተጋዘ፣ አባ ፊሊጶስ በአደባባይ ራቁቱን እንደተገረፈ እናነባለን።

ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት ላይ ያለ ማኅበር ትናንት እንደፈላ እንደ ክረምት አግቢ ሊታይ አይችልም። መንግሥት ይኼ ሁሉ ሐቲት አይጠፋውም። ማኅበሩ ተቃዋሚም ደጋፊም እንዳይደለ መግለጹ እስካሁን ጉንጭ አልፋ ከመሆን አልዘለለም። መደገፍ የማይችል አካል፣ ባይቃወምም እንኳን ገለልተኛ መሆኑ ለአደጋ ያጋልጠናል በሚል “ባልበላውም ጭሬ ላፍሰው” የዶሮ ፍልስፍና የተቃኘ ነው።

ከዚህም ባሻገር አባላቱ ከአንድ ዘርና ቋንቋ፣ ባህልና ፖለቲካዊ አቋም የመጡ አለመሆናቸው፤ ይልቁንም ሕብረ ብሔረሰባዊና ኢትዮጵያዊ መሆናቸው እንቅልፍ የሚነሣቸው አካላት መኖራቸው ግልጽ ነው። “አዳሜ በየቅርጫትህ ግባ” ሲባል አንድ ቅርጫት ውስጥ የማይጨመሩ፣ ከሌላውም ቅርጫት ካለው ጋር ዝምድናና ፍቅር ያላቸው፤ ከቅርጫታቸው ውጪ የሚያስቡ ሰዎች ያሉበት ማኅበር መሆኑ የሚያስፈራቸው አሉ።

በውጪ አገር ባሉ የተለያዩ የመንግሥት ተቃዋሚ ቡድኖች ዘንድ ማኅበረ ቅዱሳን ሲጠረጠር እንደኖረ እነርሱም በፈንታቸው “ማኅበረ ቅዱሳን የኢሕአዴግ ደጋፊ መሆን አለበት” ሲሉ ኖረዋል። ለምን እንዲህ አላችሁ ሲባሉ ምክንያቱም “ይህንን የሚያህል ትልቅ ተቋም እንዴት ነጻና ፍፁም ሃይማኖታዊ ብቻ ሊሆን ይችላል? ጠርጥር ጠርጥር” የሚል ጥርጣሬ ያቀርባሉ።

ማኅበሩ አብሯቸው ጀብ ጀብ ላለማለቱ ምክንያቱ ዓላማውና ተፈጥሮው መሆኑን ለመቀበል የአገር ውስጡም የዳያስጶራውም ቡድን፣ እነዚያም እነዚያም ይኸው እንደተቸገሩ አሉ። እነዚያ “የዚያ ደጋፊ ነው” እንዳሉት፣ እነዚያም “የዚያ ደጋፊ ነው” እንዳሉት። ማኅበሩ ደግሞ “አነ ዘክርስቶስ፣ አነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ እኔ የክርስቶስ ነኝ፣ እኔ የቤተ ክርስቲያን ነኝ” እንዳለ አለ። መጨረሻውን ደግሞ ዕድሜ ይስጠን እንጂ፣ እናየዋለን።

     ይቆየን – ያቆየን  
(ኤፍሬም እሸቴ)

Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በትናንቱ የአፍጋኒስታን ምርጫ ምንም እንኳን እስልምና አክራሪው የታሊባን ታጣቂ ቡድን ጥቃት እንደሚዘነዝር ዝቶ የነበረ ቢሆንም፤ ለምርጫው በርካታ ሕዝብ መውጣቱን እንደሚያደንቅ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ገለፀ። ግድያ የታከለበት በርካታ ግጭት ቢከሰትም፤ የትናንቱን ምርጫ የተመድ ስኬታማ ሲል አድንቋል።

የዕለቱ ርዕሶች፤
ካሜሮን፤ ሶስት ታጋጆች የደረሱበት አልታወቀም
ናይጄሪያ፤ 30 የሚሆኑ ሞቱ በርካቶች ቆሰሉ
ማሌዢያ፤ የተሰወረው አይሮፕላን ፍለጋ እና ፍንጭ
አፍጋህኒስታን፤ ኦባማ ምርጫውን አወደሱ
ጀርመን፤ ወደ ሀገሪቱ ሕገ ወጥ የሚገቡት ስደተኞች ቁጥር ክፉኛ ጨመረ
ኢትዮጵያ፤ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የፓሪሱን ማራቶን አሸነፈ

የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪቃል በደሴ የተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ በስፍራው የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ከፍተና አመራሮችና የዞን አመራሮች በሰልፉ ለተሳተፈው የደሴ ህዝብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ‪የደሴ ነዋሪዎችም “እድሜ ለአንድነት አስተነፈሰን” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል። የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት በሚል መሪ ቃል አንድነት ፓርቲ የጀመረውን ዘመቻ በማስመልከት የመጀመሪያውን ሰላማዊ ሰልፍ በደሴ ከተማ በተሳካ ሁኔታ ማድረጉ […]

የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች ለማሰራጨት እንረባረብ!

ኡስታዝ አቡበክር አህመድና ዳዒ ያሲን ኑሩ ያቀረቡት የክስ መከላከያ በጽሁፍና በድምጽ ተዘጋጅቶ ከታች በሚገኙት ሊንኮች ቀርቧል

1.የኡስታዝ አቡበክር አህመድ ክስ መከላከያው የፒዲኤፍ ጽሁፍ ሊንክ፡-

http://goo.gl/NRSNki

የኡስታዝ አቡበክር አህመድ ክስ መከላከያው የድምጽ ትረካ ሊንክ፡-

http://goo.gl/RSPs2Q

2.የዳዒ ያሲን ኑሩክስ መከላከያው የፒዲኤፍ ጽሁፍ ሊንክ፡-

http://goo.gl/abVvpS

የዳዒ ያሲን ኑሩ ክስ መከላከያው የድምጽ ትረካ ሊንክ፡-

http://goo.gl/FucbrB

መጋቢት 24 አህመዲን ጀበልና ኡስታዝ ያሲን ኑሩ የቀረቡበት ልዩ ዘገባ
በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ሊንክ

http://goo.gl/7p9z81

መጋቢት 25 ኡስታዝ በድሩ ሁሴንና
ካሚል ሸምሱ የቀረቡበት ቢቢኤን ልዩ
ዘገባ በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ሊንክ

http://goo.gl/TpX7ii

የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች
ለማሰራጨት እንረባረብ!
የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች ለማሰራጨት እንረባረብ!
to be continued ………..

Image