ወለላዬ ከስዊድን

አቶ ዘለሌ ፀጋ ስላሴ ዝግጅቱን በንግግር ሲከፍቱቅዳሜ ጥቅምት 20 ቀን 2008 ዓ.ም. (ኦክቶበር 31 ቀን 2015 እ.ኤ.አ.) በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም ለአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ መርጃ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ተደረገ። በዝግጅቱ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ተገኝተዋል። በቦታው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት አቶ አበበ ቦጋለ የውጪ እንቢተኝነት ሊቀመንበር እና አቶ ቸኮል ጌታነህ የንቅናቄው ከፍተኛ አመራር ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አትሌት ከላሊ ንጉሴ አብርሃ

ከላሊ ንጉሴ ይባላል፡፡ የረዥም ርቀት እና ማራቶን ሯጭ ሲሆን አሁን የሚገኘው በስደት ቶሮንቶ፣ ካናዳ ውስጥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በነበረበት ወቅት ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር ያሳለፈውን የህይወት ተሞክሮ በማስመልከት ከኢትዮጵ ዛሬ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል፤ እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

እኔ እንዳዳመጥኩት Ené endadametkutጌቱ ኃይሉ

መቼም ሰው ይናገራል። እኔ ደግሞ ጆሮ ፈጥሮብኛልና እሰማለሁ። የምሰማውና የማዳምጠው ግን ይለያያል።

ባለፈው ሰሞን ቁጥር 00 ሰውዬ ሲናገሩ ሰማሁ፣ “የዛሬ አሥር ዓመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን” ብለው ሲናገሩ ሰማሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነፃነት ዘለቀ

Former TPDM fighters. የቀድሞ ዴምሕት አባላት

እንደምን ሰነበታችሁ። እንኳን ለአዲሱ ዓመት የ2008 ዓ.ም. ሁለተኛ ወር “ለጥቅምት አንድ አጥንት” በሠላም አደረሳቹ። ጥቅምት ብርዳምና ንፋሳም ነው። ዘንድሮም እንደዛው ነው። የአዲስ አበባ የሰሞኑ ብርድ ሚስት ያሳቅፋል። ግን ስንገናኝ ሠላምታ የማንለዋወጠው ለምንድነው? ብዙ መጣጥጥፍ ጸሐፊዎች ይህን ወግ ልማድ ረስተው በቀጥታ ሊያስተላልፉት ወደሚፈልገጉት ቁም ነገር ይገባሉ – ያበሳጩኛል። “እንዴት ሰነበታችሁ” ማለት ማንን ገደለ?

ሙሉውን አስነብበኝ …

እኔ እንዳዳመጥኩት Ené endadametkutጌቱ ኃይሉ

መቼም ሰው ይናገራል። እኔ ደግሞ ጆሮ ፈጥሮብኛልና እሰማለሁ። የምሰማውና የማዳምጠው ግን ይለያያል።

ባለፈው ሰሞን ቁጥር 00 ሰውዬ ሲናገሩ ሰማሁ፣ “የዛሬ አሥር ዓመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን” ብለው ሲናገሩ ሰማሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሙሉጌታ ሉሌ / Mulugeta Luleበልጅግ ዓሊ

“ደግ ደጉን ስናጣ፣ ኀዘኑ መረረ

ሞት አምላኩ ከድቶት፣ ገሎት በነበረ።”

– የሠፈራችን ሙሾ አውራጅ

እነሆ ጋሼ ሙሉጌታ ዐረፈ። ከዚህ ምስቅልቅሉና ቅጥ አምባሩ ከወጣ ዓለም በአካል ተለየ። ጋሼ ሙሉጌታ ከእንግዲህ የሀገሩን አፈር በሞቱ እንኳ ላይቀምስ ነው። ዛሬ የሰው ሀገር አፈር ለብሶ በዝምታ ማሸለቡን መርጧል። ሀገሩን እንደናፈቀ የተለያት ቢሆንም ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሸጋገር ትምህርት ሰጥቶን አልፏል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዩሱፍ ያሲን (ኦስሎ)

የዴሞክራሲያዊ ምንቕስቓስ ህዝቢ ትግራይ ዴምህት ሊቀመንበር የነበሩት አቶ ሞላ አስገዶም / Mola Asgedom

ከሰሞኑ ጫጫታ ባሻገር

የሞላ አስገዶም ኩብለላ፣ ፍርጠጣ ክሕደት ወይም በመንግሥት ደጋፊዎች እንደተባለው ወሽመጥ በጣሽ የጀግንነት ሥራ በአሥመራ ተጓዞችና ደርሶ – ተመላሾች መሓል እየተቋጠረ መጥቷል ብለን ያሰብነው ንትርኩን እንደገና አደበላለቀው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይቅርታ - የወያኔ ካርታ / yekerta ye tplf kartaይገረም አለሙ

1437ኛው የኢድ አል አድኻ (አረፋ) በዓል በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲከበር ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት፤ በሽብር ወንጀል ተከሰው ከተፈረደባቸው የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ችግሮች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት መካከል ስድስቱ በቅርቡ የተለቀቁት በእነርሱ ጥያቄና ጥረት እንደሆነ፤ ጥያቄአቸው ምላሽ በማግኘቱና ጥረታቸው በመሳካቱ መደሰታቸውን ገልጸው፤ ለመንግሥት ምሥጋና ማቅረባቸውን የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ ከስፍራው ባስተላላፈው ዘገባ አሰምቶናል። ወያኔ ግዜና ወቅት እየጠበቀ የሚጠቀምባት የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ የይቅርታ ካርድ በሌላ መንገድና መልክ ተመዘዘች ማለት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopian Transitions: At Home and Abroad (by Kebede Haile) / የኢትዮጵያውያን ሽግግር - በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር (ከበደ ኃይሌ)አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ

የመጽሐፉ ርዕስ፡- Ethiopian Transitions: At Home and Abroad (የኢትዮጵያውያን ሽግግር – በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር)

ፀሐፊ፡- ከበደ ኃይሌ

ቋንቋ፡- እንግሊዝኛ እና አማርኛ

ዋጋ፡- 32.99 የአሜሪካ ዶላር (ጠንካራ ሽፋን)

የገጽ ብዛት፡- 286

አሳታሚ፡- ኦልራይት ፐብሊሺንግ

ገበያ ላይ የዋለው፡- መስከረም 14 ቀን 2008 ዓ.ም. / ኦገስት 24 ቀን 2015 (እ.ኤ.አ.)

ደራሲና ፀሐፊ ከበደ ኃይሌ በቅርቡ እንግሊዝኛ እና በአማርኛ ቋንቋ የጻፉት “Ethiopian Transitions: At Home and Abroad” (የኢትዮጵያውያን ሽግግር – በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር) የተሰኘው መጽሐፍ በቅርቡ በገበያ ላይ መዋሉን ለኢትዮጵያ ዛሬ በላኩት ኢ-ሜይል ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከደርግ መፈክሮች / Revolutionary monument extols the virtues of communism. Courtesy Paul Henze. ጌቱ ኃይሉ

አቶ ዠ 57 ዓመታቸው ነው። መተዳደሪያ አላቸው። እንዴት ያለ ሙያ!! ባሥራ ሰባት ዓመታቸው የጀመሩት። አርባ ዓመት ሙሉ ያለማቋረጥ እየሠሩ ያሉት። ሰዉ ከሥራው በመንግሥት ለውጥ፣ በሰበብ ባስባቡ ሲባረር እሳቸው ሥራ አላጡም። ሥራቸው መፈክር አድምቆ መጻፍ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Prof. Mesfin Woldemariam. ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ይገረም አለሙ

ፈጣሪ ዕድሜ ከጥንካሬ ጋር ያደላቸው በሀገር ጉዳይ የማይታክቱት ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ሰሞኑን በምድረ አሜሪካ ነዋሪ ከሆኑ ኢትዮጵያውያን ጋር ያደረጉትን ውይይት፤ ዘመነ ቴክኖሎጂ ምስጋን ይግባውና በያለንበት ሆነነን ተከታትለናል። ከውይይቱ ታዳሚዎች ከቀረቡ በርካታ ጥያቄዎች አንዱ፣ “በያ ትውልድ ላይ ጨከኑበት” የሚል ነበር። ፕ/ር መስፍን ሲመልሱም፤ አልጨከንኩበትም እውነቱን ነው የተናገርኩት፣ አንዳንዶቹ እንደውም ተማሪዎቼ ነበሩና አነጋሬአቸዋለሁ፣ ፍላጎታቸው ለሀገርና ለሕዝብ ሳይሆን ሥልጣን ነበር ብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አንዱዓለም ተፈራ

መከወኛ ሃሳብ፤

ዛሬ ካለንበት የፖለቲካ ሀቅ ላይ ቆመን የነገዋን ኢትዮጵያ በሃሳብ ብንመለከት፤ ሶስት እውነታዎች ገጠው ይታያሉ። የመጀመሪያው፤ አሁን በሥልጣን ላይ ባለው የገዥ ቡድን አስተዳደር፤ ምንም ቢሆን ምንም፤ ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ሊኖራት አለመቻሉ ነው። ሁለተኛው ደግሞ፤ ኢሕአዴግ፤ ውስጡ እየነቀዘ፤ ወደ አንድ ፓርቲነት ከማደግ ይልቅ፤ በየድርጅቶቹ መጎነታተል እየተወጣጠረ፤ ከውስጥ መርቅዞ ወደ መበታተኑ በመሄድ ላይ ያለ መሆኑ ነው። ሶስተኛው ደግሞ፤ አሁን በያዝነው ሂደት፤ ሀገራችን እጅግ ወደ ከፋና ልትወጣበት ወደማትችለው መቀመቅ ውስጥ እየዘቀጠች መሆኗ ነው። እኒህ ፈጠው ያደገደጉ የፖለቲካ ሀቆች፤ በዚህ ጽሑፍ ተተንትነው ቀርበዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Magdalaወለላዬ ከስዊድን

አፄ ቴዎድሮስ ያሠሩትን መድፍ (ሴባስቶፖል) ወደ ተራራው አናት ለማውጣት እየተጣደፉ ነው። እሳቸው ጭምር በጉልበት እያገዙ ሲገፋ ውለው ረፋዱ ላይ ከሰፈር ደርሰው ሲመለሱ አንዱ መድፉን ከሚገፉት ተለይቶ ወደ ሰፈር ሲወርድ መንገድ ያገኙትና ቆም ብለው ወዴት ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ? ብለው ይጠይቁታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዮሃንስ ደሳለኝ (ጀርመን – ፍራንክፈርት)

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2007 ዓ.ም.  June 23, 2015)፡- በጀርመን ፍራንክፈርት ትላንት ሰኞ ሰኔ 15,2007 (June 22,2015) የእንግሊዝ ኮንስለር ፅ/ቤት የተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ። በዚሁ ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን በኩል ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው የተሰጡበትን 1ኛ ዓመት ለማስታወስና እንዲሁም ላለፉት አንድ ዓመት ሁኔታዎችን በለዘብተኝነት የምትመለከተው ታላቋ ብሪታንያ ለራሷ ዜጋ ምንም ዓይነት ድጋፍና ከለላ ባለመስጠቷ ለማውገዝና አስፈላጊውን እርምጃ እንድትወሰድ ለማሳሰብ የተጠራው የተቃውሞ ሠልፍ ከጅምሩ ደማቅና አላማውን ያሳካ ነበረ።IMG_1874.JPG

ሙሉውን አስነብበኝ …

EPRDF ኢህአዴግ

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. June 7, 2015)፡- የትግል ታሪኩ ጥንካሬ በገዛ አባላቱ ተጋኖ የሚነገርለት ኢህአዴግ ሥልጣን ይዞ በቆየበት 24 ዓመታት ለህልውናው አስጊ የሆኑ ፈታኝ ጊዚያቶች በተደጋጋሚ አሳልፏል። ከእነዚህ ውስጥ በ1993 ዓ.ም. አመራሩ ለሁለት ተሰንጥቆ በነበረበት ጊዜ የደረሰው ውጣውረድ፣ በቀድሞው ጠ/ሚንስትር ሞት የደረሰው ክፍተት እንዲሁም የ1997ቱ ምርጫ ባስከተለው ህዝባዊ ዓመጽ መሬት ነክቶ የመመለሱ አደጋ የሚጠቀሱ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከአንተነህ መርዕድ (ሚያዝያ 2007)
መሳይ መኮንንና ፋሲል የኔዓለም ወደ ኤርትራ ያደረጉት ጉዞ የብዙ ኢትዮጵያውያንን እንዲሁም የኤርትራውያን ወንድምና እህቶች ቀልብ መሳቡ እሙን ነው። በተለይም የፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ በብዙ መልኩ አስደምሞናል። እድላችን የተቆራኘነውና መነጋገሩና መብሰልሰሉ የሚገባ በመሆኑ ያለፍንበትን ሁሉ በትዝታ እንድፈትሽና አሁን የደረስንበትን እንዳይ ምክንያት ሆኖኛል። ነገሮችን ውስብስብና አጠቃላይ ከሆነ መልኩ ይልቅ ተጨባጭ ከሆኑ የግል ገጠመኞች ዙርያ ማውጋቱ የበለጠ ጉልህ ያደርገዋልና አንባቢዎቼም የራሳችሁ ገጠመኝ ዙርያ እየተሽከረከራችሁ የእኔን እንድትካፈሉ እጋብዛለሁ። በዚህ መልኩ ከምን ተነስተን የት እንዳለን ይታየናል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ራሳቸው በሚወዳደሩበት ምርጫ ያልመረጡ የመጀመሪያው የፓርቲ መሪ ሆኑ
Dr. Merera Gudina. ዶ/ር መረራ ጉዲና

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. May 24, 2015)፡-  በኢህአዴግ ተቃዋሚነት የብዙዎች ድጋፍ እንዳላቸው የሚታመነው የኦፌኮ (የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ) ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ዛሬ በተካሄደው ምርጫ ድምጻቸውን መስጠት (መምረጥ) አለመቻላቸው ታወቀ። ዶ/ር መረራ ፓርቲያቸውን ወክለው በተወለዱበት የጉደር ከተማ ተወዳዳሪ ቢሆኑም፤ ለራሳቸውም ይሁን ለሌላ ሰው ድምጻቸውን የሚሰጡበትን የምርጫ ካርድ በሰዓቱ ባለማውጣታቸው ዛሬ መምረጥ ሳይችሉ ቀርተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አዲስ አበባ ፀጥ እንዳለች ውላ አመሸች
Voters queue early in the morning to cast their votes in Ethiopia’s general election, Sunday May 24, 2015, in Addis Ababa, Ethiopia. Ethiopians voted Sunday in national and regional elections, the country’s first since the 2012 death of its longtime leader, but the ruling party is expected to maintain its iron-clad grip on power. (Mulugeata Ayene/Associated Press)

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. May 24, 2015)፡-  ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት የተካሄደውና የተጠናቀቀው ምርጫ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት አራት ምርጫዎች እጅግ የቀዘቀዘ መሆኑ ታወቀ። ተቃዋሚዎች ፓርቲዎች በታዛቢነት የመደቧቸው ሰዎች ምርጫውን እንዳይታዘቡ ጫና እንደተደረገባቸው ብሎም እንደታሰሩባቸው ገልጠዋል፤ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ በምርጫ ከተሳተፉት ፓርቲዎች ምንም አይነት ቅሬታ እንዳልደረሰው ገልጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopian election 2007 report by Aljazeera

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. May 24, 2015)፡- ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በተካሄደው ምርጫ ገዥው ፓርቲ ምርጫውን ያሸንፋል ተብሎ ይጠበቃል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል። አልጀዚራ በዚሁ ዘገባው ተቃዋሚዎች በገዥው ፓርቲ እንደሚዋከቡ፣ የምርጫ ቅስቀሳ እንዳያደርጉ መታገዳቸውንና የፓርቲ አባላቶቻቸው እንደታሰሩባቸው አትቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopian election 2015. እረጭ ያለው ምርጫበኢትዮጵያ የተካሄደውን የ2007ቱን ምርጫ አስመልክቶ የቪኦኤ ጋዜጠኛ ሰለሞን አባተ ባጠናከረው ዘገባ፣ “አዲስ አበባ ውስጥ ከባነሮቹና እጅግ ከተጋነነው የሙዚቃ ጩኸት በተረፈ አገሪቱ በ90 ሚሊዮን ሕዝብ የተመላች አትመስልም፤ ባልተለመደ ሁኔታ እረጭ ያለ ምርጫ” በማለት የምርጫውን ሁኔታ ገልጦታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopiana election 2015 (VOA)(ቪኦኤ) በኬንተኪ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ደረሰ ጌታቸው፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና የመገናኛ ብዙኃን ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ እና የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር፣ አሁን በዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ውስጥ የሚሠራው መስፍን ነጋሽ አስተያየታቸውን ሰጥተውበታል። ጽዮን ግርማ አወያይታቸዋለች።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ወለላዬ

PM Hailemariam Desalegn. ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ

ከስም ልጀምር፣ የዛሬ ወጣቶች በተለይ ዘፋኞች ስማቸው በመጠኑ ተቆርጦ ወይም አንሶ ሲጠሩ እየሰማን ነው፤ ቴዎድሮስ – ቴዲ ብዙ ባያስከፋም ተያይዘው የቀጠሉት ዘፋኞች ግን እስከ አባታቸው ስለሚያሳንሱት ኢትጵያዊ ስም መሆኑ ራሱ አጠራጣሪ የሆነብኝ ጊዜ አለ። እስቲ አሁን ጃህ ሉድ አጥሮ ነው ወይስ ተቆርጦ ቻቺ፣ ጃኪ፣ ጂጂ፣ አቢ፣ ኢሚ፣ ዮሲ፣ ጃኪ-ጎሲ፣ ሚሊ፣ ሚኪ፣ ዮኒ፣ … ልተዋቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አብርሃም ዘታዬ
ፌዴራል ፖሊስ በሊቢያ የተገደሉትን ኢትዮጵያውያኖች አስመልክቶ ለኀዘን የወጡትን ሲደበድብ

በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ ከደረሰብን ኀዘን ሳናገግም በሜዲትራንያን ባህር የሰጠሙ ወገኖቻችንን መርዶ ተረዳን። በአገር ቤት ከድሮም ጀምሮ በተናጥልም በጅምላም መጨፍጨፋችን አላቆመም። ባለቅኔው “ሞትና የላሊበላ ህንጻ ሁልጊዜ አዲስ ነው” ብሎ እንደተቀኘው ስለአዲሱ አሟሟታችን እንጉርጉሮ እናውጣለት ከተባለ በሰፈር ተደራጅተን እየሞትን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ክንፉ አሰፋ
ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ከሊብያ የተመለሱትን ኢትዮጵያውያኖች ሲቀበሉ

የፌስቡክ አርበኛው ቴድሮስ አድሃኖም ቦሌ ሄደው ከሊቢያ ነጻ የወጡ ዜጎችን ሲቀበሉ አየን። እፊታቸው ላይ የማፈር ሳይሆን የጀግንነት ስሜት ይነበባል። አቀባበላቸውም 90 ደቂቃ በኢንቴቤ የሚለውን ታሪክ ይመስላል። ኡጋንዳ ላይ የታገቱ ዜጎችዋን ለማስለቀቅ እስራኤል ያደረገችው ገድል። ቴድሮስ አድሃኖምም በኩራት እና በድል አድራጊነት ስሜት ነው ስደተኞቹን የተቀበሉት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ክንፉ አሰፋ

Obama Stop ISIS

ግብጽ የሃያ አንድ ክርስቲያን ዜጎችዋን በአይሲስ መታረድ ዜና እንደሰማች ዝም ብላ አልተቀመጠችም ነበር። ብሔራዊ የኀዘን ቀንም አላወጀችም። እንዲህ ነበር የሆነው። ከመቅጽበት ተዋጊ አውሮፕላኖችዋን አስነስታ ወደ ሊቢያ ላከቻቸው። የአይሲስ አራጆች የተከማቹበትን ደርና የተሰኘ ስፍራ እያከታተለች በቦምብ ቀጠቀጠችው። ብዙ አራጆች በድብደባው አለቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

“እያንዳንዳችን ወደልቦናችን መመለስ አለብን“ የክርስትና ተወካይ

“ቀዳዳውን አብረን እንድፈን“ የእስልምና ተወካይ

“በሰሃራ በረሃ አካላታቸው ለተበለተ ወገኖቻችን ዝም ማለት የለብንም“ የኤርትራ ተወካይ

Ethiopians and Eritrians protested in Sweden. በስዊድን ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን በጋራ ኀዘናቸውን ተወጡ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሚያዝያ 19 ቀን 2007 ዓ.ም. April 27, 2015)፡- ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከ10 ሰዓት (16፡00) ጀምሮ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከ2000 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን በሰርገልስ አደባባይ በመሰብሰብ በሊቢያ እና በደቡብ አፍሪካ አሰቃቂ ግድያ የተፈጸመባቸውን ወገኖቻቸውን በማሰብ ኀዘናቸውን እና ተቃውሟቸውን በጋራ ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አቢይ አፈወርቅ
Sydney candlelight vigil. በሊቢያ በደቡብ አፍሪካና የመን ለተገደሉ ወገኖቻችን በሲድኒ የሻማ ማብራት ሥነሥርዓት ተከናወነ

በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ያስቆጣቸው የሲድኒ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያን እሁድ ኤፕሪል 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ልዩ የሻማ ማብራት ስርአት አካሂደዋል። በዚህ በኒው ሳውዝ ዌልስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር አስተናባሪነት በተዘጋጀው ሥነሥርዓት ላይ ቁጥራቸው ከ350 በላይ የሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያን ተገኝተው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የታረዱትንና በጥይት የተደበደቡት ኢትዮጵያዊያን ሰማእታት ናቸው ‘ነፍስ ይማር’ ወይንም RIP ሊባልለት የሚገባው በቁሙ ለሞተው አይሲስ ነው።” ዲያቆን መምህር አድማሱ ዘባን
Ethiopia Zare (ሰኞ ሚያዚያ 19 ቀን 2007 ዓ.ም. April 25, 2015)፦ ራሱን የእስላም መንግስት በማለት የሚጠራው እና ዘግናኝ ግድያዎችን በንጹሃን ዜጎች ላይ በመፈጸም ላይ በሚገኘው ቡድን እጅ ህይወታቸውን ላጡ ኢትዮጵያዊያኖችና በሳውዝ አፍሪካ የሚገኙ ወገኖች ላይ የሚፍጸመውን ሰብአዊነት የጎደለው አስከፊ ድርጊት በመቃዎም በቫንኩቨር (ካናዳ) ታላቅ የሻማ ማብራት ስነ ስርዓት ተካሄደ።vancouver-vigil-01.JPG

ሙሉውን አስነብበኝ …

በደቡብ አፍሪካና በሊቢያ በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ኢሰብዓዊ ጥቃት ተቃወሙ
Ethiopians protested in Meelbourne. በሜልበርን የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በደቡብ አፍሪካና በሊቢያ በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ኢሰብዓዊ ጥቃት በመቃወም ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

ሚያዝያ 16 ቀን 2007 ዓ.ም. (April 24, 2015) የሜልበርን ኢትዮጵያዊያን ኮሚኒቲ እና ዲሞክራሲ ለኢትዮጵያ ድጋፍ ቡድን በሕብረት ባስተባበሩት የተቃውሞ ሰልፍ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር የነበረው ኢትዮጵያዊ ተሳትፎ ቁጣውን በመረረና እልህና ቁጭት በተንጸባረቀበት መልክ ሲገልጽ አርፍዷል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Abune Elias. ብፁዕ አቡነ ኤልያስ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. April 22, 2015)፡- ዛሬ ማምሻውን ከ12 ሰዓት (18፡00) ጀምሮ ለሁለት ሰዓታት በስቶክሆልም በደብረሰላም መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን በሊቢያ ለተገደሉት ወገኖቻችን በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የምስራቅ አፍሪካና የአውሮጳ ሊቀጳጳስ የተመራ ሥርዓተ ጸሎት ተደረገ። በርካቶች ሲያለቅሱ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ክንፉ አሰፋ

Eyassu Yukunualem and Balecha Belete, ISIS massacred them in Libya. የአይሲስ ሰለባዎቹ እያሱ ይኩኑዓምላክ እና ባልቻ በለጠ

ወጣት እየሩሳሌም አስፋው እንደወትሮው ቴሌቭዥን ከፍታ እየተመለከተች ነው። ብርቱካንማ ቱታ የለበሱና፣ እጆቻቸው የፍጢኝ የታሰሩ ወጣቶች በአሸባሪዎች ታጅበው ሲጓዙ ያሳያል ቴሌቭዥኑ። ለእርድ ከተሰለፉት ወገኖች ፊት ለፊት ላይ ያለው የእየሩሳሌም ወንድም ነበር። ሌላኛው ወንድሟም ከበስተኋላ ተሰልፏል። እያሱ ይኩኑዓምላክ እና ባልቻ በለጠ፤ ሁለቱም በዚያች ቅጽበት ክቡር ነብሳቸውን በግፈኞች ተነጠቁ። ከሁሉም የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ወዳጅ ዘመዶች የነዚህን ወገኖች አስከሬን አግኝተው ለመቅበር እድል እንኳን ባለማግኘታቸው ነው። የሁሉንም ልብ የሚሰብር ክስተት!

ሙሉውን አስነብበኝ …

Senakriem Mekonnen. ሰናክሬም መኮንንክንፉ አሰፋ

“አሜሪካ ይዞን ከሄደ በኋላ በዋሽንግተን ዲሲ አንድ የገበያ አዳራሽ (ሞል) ውስጥ ጥሎን ጠፋ … ፖሊስ ሁለት ግዜ ይዞን ነበር … በርሃብ ተቀጣን፣ ርሃብ ጸንቶበት ሆስፒታል የገባም ልጅ አለ። … በየሬስቶራንቱ እየዞርን ለምነናል።” ይላል አንድ የ11 ዓመት ሕጻን ሳይንቲስት። ሂውስተን ቴክሳስ ያሚገኘውን ናሳ የጠፈር ምርምር ተቋም ለመጎብኘት ከአዲስ አበባ ሄደው ነው አስሩ ሕጻናት ዲሲ ላይ የሚሰቃዩት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አንዱዓለም ተፈራ

Revolution. መማር እንችላለን ወይ?

ከ፲፱፻፷፮ ዓመተ ምህረቱ የየካቲት ሕዝባዊ መነሳሳት ጀምሮ፤ ለመብት፣ ለነፃነትና በሰላም ሠርቶ ለመኖር ያለው ትግል፤ ሳያርፍ በተከታታይ አሁንም እየተካሄደ ነው። በነዚህ ባለፉት ፵ ዓመታት፤ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፤ በትግሉ ከሕዝብ ጎን ተሰልፈው ሕይወታቸውን ሠጥተዋል። ቆራጥ የሕዝብ ጠበቃዎች ወጥተዋል፤ ሕይወታቸውን ላመኑበት ዓላማ በቆራጥነት በመሥጠት በጀግንነት ተቆጥረዋል። ትውልድ አልፎ ትውልድ ተተክቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Donald N. Levine. ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ነጻነት ለሀገሬ)

ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን፡ የልሂቃን ሁሉ ልሂቅ

ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን በዚህ ባሳለፍው ጥር ወር ኢትዮጵያን ለመጎብኘት የነበራቸው የረዥም ጊዜ ዕቅድ በህመማቸው ምክንያት የተጨናገፈ መሆኑን በኢሜይል መልዕክት ልከውልኝ ነበር። በዚያ አስበውት በነበረው ጉብኝት የሚከተሉትን ሶስት ዓላማዎች የማሳካት ዕቅድ ነበራቸው። እነርሱም፣

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፍቅር ለይኩን

ጎልጎታ Golgota by Geberekirstos Desta
በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ሳምንቱ ሰሙነ ሕማማት በሚል ሲጠራ የዛሬዋ ዕለት አርብ ደግሞ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መከራው፣ ሕማሙና ስቅለቱ በፍቅርና በትሕትና የሚታሰብበትና በተለያዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓቶች የሚዘከርበት ታላቅ ዕለት ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሊቃውንቶች ዘንድ “ደረቅ ሐዲስን ተናጋሪ” ተብሎ የሚጠራው ነቢዩ ኢሳይያስ አስቀድሞ በትንቢቱ፡-

ሙሉውን አስነብበኝ …

የማምነው ነገር፣ የሀገሪቷ ችግር ሲፈታ፤ እስክንድርም አብሮ እንደሚፈታ ነው”

የስደት ህይወት ሁሉንም ነገር ከዜሮ ያስጀምርሃል

የእስክንድር ፅናት እና ብርታት ከፈጣሪ የተሰጠው ፀጋ አድርጌ እመለከተዋለሁ

በሀገራችን ጉዳይ ላይ ለመሳተፍ የግድ ፖለቲከኛ መሆን አይጠበቅብንም” ሰርካለም ፋሲል (ጋዜጠኛ)

Eskinder Nega, Serkalem Fasil and Nafkot Eskinder
በአንባቢያን ዘንድ ታዋቂ የነበሩት “አስኳል”፣ “ሚኒሊክ”ና “ሳተናው” ጋዜጦች አንዷ አሳታሚ ነበረች። የ97 ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረ ግርግር ለእስር ከተዳረጉት ጋዜጠኞች እና አሳታሚዎች መካከልም አንዷ ነች – ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል። በሀገራችን የግል ፕሬስን በመጀመር ፈር ቀዳጅ የሆነው የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ሰርካለም ልጃቸው ናፍቆትን የወለደችው በቃሊቲ እስር ቤት መሆኑ ይታወቃል። 

ሙሉውን አስነብበኝ …

‹‹የማምነው ነገር፣ የሀገሪቷ ችግር ሲፈታ፤ እስክንድርም አብሮ እንደሚፈታ ነው›

‹‹የስደት ህይወት ሁሉንም ነገር ከዜሮ ያስጀምርሃል››

‹‹የእስክንድር ፅናት እና ብርታት ከፈጣሪ የተሰጠው ፀጋ አድርጌ እመለከተዋለሁ››

‹‹በሀገራችን ጉዳይ ላይ ለመሳተፍ የግድ ፖለቲከኛ መሆን አይጠበቅብንም››
ሰርካለም ፋሲል (ጋዜጠኛ)
—————–
በአንባቢያን ዘንድ ታዋቂ የነበሩት ‹‹አስኳል››፣ ‹‹ሚኒሊክ‹‹ና ‹‹ሳተናው›› ጋዜጦች አንዷ አሳታሚ ነበረች፡፡ የ97 ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረ ግርግር ለእስር ከተዳረጉት ጋዜጠኞች እና አሳታሚዎች መካከልም አንዷ ነች – ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል፡፡ በሀገራችን የግል ፕሬስን በመጀመር ፈር ቀዳጅ የሆነው የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ሰርካለም ልጃቸው ናፍቆትን የወለደችው በቃሊቲ እስር ቤት መሆኑ ይታወቃል፡፡ index.jpg
ከእስር ከተለቀቁም በኋላ እስክንድር የጋዜጣ ፍቃድ ቢከለከልም ሀገሬን ጥዬ አልመሄድም በሚል አቋሙ በመጽናቱ ጽሑፎቹን በተለያዩ በውጭ ሀገር ባሉ ድረ-ገጾች ላይ ማቅረብ ቀጠለ፡፡ በሀገር ውስጥ የግል ጋዜጦች ላይም ቃለ-ምልልስ በማድረግ የግል ሀሳቡን በድፍረት በማቅረብ ላይ ሳለ ነበር በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥሮ መስከረም 03 ቀን 2004 ዓ.ም ለእስር የተዳረገው፡፡ በፍርድ ሂደትም 18 ዓመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡ በዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ ውስጥ ባለቤቱ ሰርካለም ከጎኑ ነበረች፡፡
ሰርካለም በአሁኑ ወቅት በስደት አሜሪካ ሀገር ትገኛለች፡፡ የዚህ ሳምንት የ‹‹ፍቱን›› እንግዳ የሆነችው እ.አ.አ በ2007 ዓ.ም ከዓለምአቀፍ የሴቶች ሚዲያ ፋውንዴሽን “Courage in Journalism Award” የሚል ሽልማት ካገኘች በኋላ የሽልማት ገንዘቡን ለአምነስቲ ኢንተርሽናል ተቋም ድጋፍ እንዲውል ያደረገችው ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ነች፡፡ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የተወሰኑ ጥያቄዎችን (ስደትን፣ እስክንድርን፣ ልጃቸው ናፍቆትን በተመለከተ) በማንሳት እንዲህ አነጋግሯታል፡፡

በቅድሚያ ለቃለ-መልልሱ ፈቃደኛ በመሆንሽ በ‹‹ፍቱን›› መጽሔት ስም እናመሰግናለን፡፡
——

እኔም ለቃለ-ምልልሱ ዕድሉን ስለሰጣችሁኝ በአንባቢዎቻችሁ እና በራሴ ሥም አመሰግናለሁ።

ሰርካለም፣ ከሀገር ከወጣሽ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ? ለምን እንደወጣሽም በአጭሩ ንገሪን?
—————

ከሀገር ከወጣሁ አንድ ዓመት ከስድስት ወር አካባቢ ሆኖኛል። ከሀገር የወጣሁትም በግሌ ወስኜ ሳይሆን፣ ከእስክንድር ጋር ለረጅም ጊዜ ተነጋግረንበት፣ በጋራ በደረስነው ውሳኔ መሰረት ከሀገር ልወጣ ችያለሁ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ፣ ማንም እንደሚያውቀው ልጃችን ናፍቆት የተወለደው እኔ እስር ውስጥ ሆኜ ነው። በ1998 ዓ.ም የአንድ ወር ተኩል ነብሰ ጡር ሆኜ ነበር የታሰርኩት። የወለድኩትን ልጅ ማቀፍም ሆነ ማጥባት ሳልችል ነው ከልጄ ጋር የተለያየሁት። ከእስር ስንፈታ፣ ልጃችን አንድ ዓመት ሊሆነው የአንድ ወር ዕድሜ ሲቀረው ነበር ዳግም የተገናኘነው። በአጠቃላይ የልጃችን ታሪክ ከእስር እና ከመከራ ጋር የተያያዘ ነው። በአሁኑ ሰዓት ካለአንዳች ወንጀል፣ በሀሰት ክስ እስክንድር በግፍ 18 ዓመት ተፈርዶበት ቃሊቲ ይገኛል። ትላንት ቃሊቲ የተወለደው ናፍቆት ዛሬ ነብስ አውቆ፣ የልጅነት መቦረቂያ ጊዜውን አባቱ ጋር እየተመላለሰ ማሳለፍ ዕጣ ፈንታው ሆኖ ነበር። እስክንድርም ከእስሩ በላይ የልጁ መንከራተትና ስቃይ በየዕለቱ እረፍት እንደነሳው በተደጋጋሚ ይገልጽልኝ ነበር። ከዚህም ባሻገር ‹‹ይህ ህፃን ጥላቻ ይዞ ማደግ የለበትም፣ ቂም ይዞ ማደግ የለበትም›› በሚል መነሻ ናፍቆትን ይዤ ከሀገር ለመውጣት ተገድጃለሁ።

የስደት ሕይወትን እንዴት አገኘሽው?
————–

የስደትን ህይወት እንዲህ በቀላሉ መግለጽ እቸገራለሁ። የስደት ህይወት ሁሉንም ነገር ከዜሮ ያስጀምርሃል። የእውነት ሀገርህ የሚናፍቅህ፣ የእውነት መንደርህ የሚናፍቀው በስደት ዓለም ውስጥ ነው፤ በተለይ እንደእኔ በማኅበራዊ ህይወት ትስስር ቁርኝት ላደገ ሰው።
አሜሪካ በርህን ዘግተህ ጎረቤት አታውቅ፣ ጎረቤትህ አያውቅህ፣ መንገድ ላይ ረጅም መንገድ ብቻህን ብትሄድ አንድም ሰው ላታይ በምትችልበት ሀገር፣ ራስን ከዚያ ጋር ማላመዱ ትንሽ ያስቸግራል። ሀገርህ ላይ ያለው ማኅበራዊ ህይወት ቢናፍቅህም፣ በሌላ ጎኑ ያለው ነፃነት ደግሞ እጅግ ያሥገርማል። የሰውን መብት እስካልነካህ፣ ያሻህን ብትሆን ቀና ብሎ የሚመለከትህ እና የሚያስፈራራህ አንዳችም ሀይል የለም። ‹‹ስጋት ውስጥ ይጥለኛል›› ብለህ የምትጠነቀቀው ወይም የምታስበው አይኖርም። አሜሪካ የሁሉም ነች፡፡ ሁሉም እኩል ይስተናገድበታል። ሁሉም እኩል መብት አለው። …ይህ ግን የሥደትን ህይወት ጣፋጭ አያደርገውም። …ከነምናምኗ ሀገርን የመሰለ ምንም ነገር የለም።

ባለቤትሽ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በሽብርተኝነት ወንጀል 18 ዓመት ተፈርዶበት በቃሊቲ እስር ቤት ይገኛል፡፡ አንቺም ከማዕከላዊ እስከ ቃሊቲ በነበረው እስሩ በጥየቃ አብረሽው ነበርሽ፡፡ አሁን ከልጃችሁ ናፍቆት ጋር በአሜሪካ ቨርጂኒያ ትገኛላችሁ፡፡ ባለቤትን ከጎን አጥቶ ሕይወትን መኖር እና ልጅን ለብቻ ማሳደግ እጅግ ከባድ መሆኑ ይታወቃል፡፡ እስኪ በዚህ ጉዳይ ላይ ያለሽን ስሜት አጋሪን?
—————————-

እስክንድር “አሸባሪ” የሚል የሀሰት ታርጋ ተለጥፎበት ከታሰረ አራት ዓመት ሊሞላው ትንሽ ወራቶች ይቀሩታል። እስክንድር ሀገሩን እና ወገኑን የሚወድ ኢትዮጵያዊ እንጂ፣ ተሸባሪዎቹ እንደሚገልጹት “አሸባሪ” ወይም ህዝብና ሀገርን የሚጎዳ አንዳችም ነገር አድርጎ እንደማያውቅ የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሳይሆን፣ እነጆን ኬሪ በአደባባይ የመሰከሩለት ሀቅ ነው። የኢህአዴግ መንግሥት በግፍ፣ ማዕከላዊ ውስጥ (ለጊዜው ስማቸው ይቆየን) በሃላፊዎች ደረጃ ንፅህናው እየተነገረው ግን ‹‹ከአቅማችን በላይ ነው››፣ ‹‹ይታሰር ተብሏል፣ ትዕዛዝ ነው›› እየተባለ የታሰረ የግፍ እሥረኛ ነው። እስክንድር ላመነበት ነገር የሚያስከፍለውን ሁሉ ለመቀበል የተዘጋጀ ጠንካራ ሰው በመሆኑ፣ እኔም ለብቻዬ ልጃችንን ለማሳደግ በብዙ ማይልሶች ርቀት ላይ ብገኝም፣ ከሁለታችንም በኩል ጥንካሬ ብቻ እንደሚጠበቅብን አምናለሁ። በተለይ የእኛ ጥንካሬ፣ ለእስክንድር ሞራል እንደሚሆነው ስለማውቅ ልጅን ለብቻ ማሳደጉንም ሆነ ተለያይቶ በመኖሩ ጊዜያዊ አድርጌ ነው የምቆጥረው። ደግሞም እግዚያብሄር ይችላል!

በስደት ዓለም ሆናችሁ፣ ሰዎች ስለእስክንድር እና ስለእናንተ ያላቸው ያላቸው ቦታ …
————————-
….ከእኔ ልጀምር፣ ‹‹በእጅ የያዙት ወርቅ እንደመዳብ ነው›› ይላል የሀገሬ ሰው። እስክንድር በውጪ ዓለም በዚህ ደረጃ አድናቂ እና ተከታይ እንዳለው በጭራሽ አላውቅም። በተጓዝንበት ሥፍራ ሁሉ፣ ለእስክንድር ያላቸውን ክብር የሚገልጹ ሥደተኛ ወገኖቼ፣ ለእኔ እና ለናፍቆት የተለየ እንክብካቤና ፍቅር እያደረጉልን ይገኛሉ። ሁልጊዜ አዲስ ነው የምንሆንባቸው።

እስክንድር በእስር ላይም ሆኖ፣ መንፈሰ ጠንካራነቱ ወደር አይገኝለትም፡፡ ጠያቂ ሊያበረታታው ሄዶ ጠያቂውን አበረታቶ የሚመልስ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ነው፡፡ ስለእስክንድር የዓላማ ጽናት፣ ውስጣዊ ጥንካሬና ብርታት እሱን ለምታውቂው አንጻር ይህ ብትታቱ እነና ጽናቱ ከምን የመነጨ ነው?
———————-
የእስክንድር ፅናትና ብርታት ከምን የመነጨ እንደሆነ ለመግለፅ፣ ለመናገር ከቃላት በላይ ነው። በአጭሩ ማለት የምችለው፣ ከላይ (ከፈጣሪ) የተሰጠው ፀጋ አድርጌ ነው የምመለከተው። ምክንያቱም የሰው ልጅ የሆነ ቦታ ላይ ሲደክመው ወይም ተስፋ ሊቆርጥ ይችላል። እስክንድር ግን ብዙ መከራና ግፍ፣ እንግልት፣ በየጊዜው ቢደርስበትም፣ ለአንዲትም ቀን ‹‹አሁንስ ደከመኝ›› የሚል ነገር አስቦ አያውቅም። አካላዊ ስጋው ቢጎዳም መንፈሱ ግን ሁልጊዜ አዲስ፣ ሁልጊዜ ጠንካራ፣ ከራሱ አልፎ ሌላውን የሚያበረታታ ምርጥ የኢትዮጵያ ልጅ ነው። የእሱ መከራ መቀበል ከቆመለት ዓላማ ትንሽም እንደማያነቃንቀው በተግባር ያሳየ የዘመኑ ጀግና ነው። ሞራሉን ለመግደል በሀሰት ተወንጅሎ 18 ዓመት ቢፈረድበትም፣ ‹‹ለዴሞክራሲ መከፈል ያለበት ዋጋ ነው›› ብሎ ውስጡ ፀፀት እንደሌለበት አውቃለሁ። ውስጡ ትልቅ ሰላም እንዳለውም አውቃለሁ። ላመነበት ነገር የሚከፍለው ዋጋ ጥንካሬ እንጂ፣ ቁጭትን እንደማይፈጥርበት አውቃለሁ። ከምንም በላይ በሀሰት የተፈረደበት በመሆኑ፣ ለአሳሪዎቹን እንጂ የእሱ ጭንቅላት ነጻ በመሆኑ የጥንካሬው ምንጭም ሊሆን ይችላል – የሚፀፀትበትን ነገር ባለመፈፀሙ።

በባለሽበት ስቴት፣ በቅርብሽ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከልጇ ሃሌይ ጋር አሉ፡፡ በ1997 ዓ.ም ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረው ችግር፣ ከሁለቱም ጋር በቃሊቲ አብራችሁ ታስራችሁ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በስደት ዓለም አብራችሁ ትገኛላችሁ፡፡ አጋጣሚውን እንዴት ታይዋለሽ?
——————————-

እንዳጋጣሚ ሆኖ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ንግሥት ገብረህይወት (የቅንጅት ማዕከላዊ ኮሚቴ) …አሁን ደግሞ የቀድሞው የመንግሥት ጉዳዮች ኮሙኑኬሽን ሚኒስትር ደኤታ የነበሩት አቶ ኤርምያስ ለገሰ በአንድ አካባቢ እንገኛለን። ይህ ደግሞ፣ ቅርበታችንን ከጓደኝነት አልፎ ቤተሰብ እስከመሆን አድርሶናል። አንዳችን ሌላኛችን ቤት ለመድረስ ከአምስት ደቂቃ በላይ አይጠበቅብንም። በስደት ሀገር እንደዚህ ከምታውቀው እና ከምትግባባው ሰው ጋር አንድ አካባቢ መኖር፣ ውስጥህ ያለውን ብቸኝነት በትልቁ የሚቀርፍ ነው። በአጋጣሚ በአንድ አካባቢ መገኘታችን ለእኔ ትልቅ ደስታ ሰጥቶኛል።

በማኅበራዊ ድረ-ገጽ ላይ በንቁ በመሳተፍ እመለከትሻለሁ፡፡ ብዙ ጊዜ መረር ያሉ የቁጭት፣ የሀዘንና ልብን የሚነኩ ጽሑፎችን ትጽፊያለሽ፡፡ የጠቀስኳቸውን ስሜቶች ምን ፈጠራቸው?
————————-

በማኅበራዊ ድረ-ገፅ ላይ የሚጠበቅብኝን ወይም በምፈልገው መጠን እየተንቀሳቀስኩ እንዳልሆነ ይታወቀኛል። የዚህም ምክንያቱ፣ ልጄን በብቸኝነት ለማሳደግ የምሮጠው የህይወት ሩጫ በመጠኑም ቢሆን ገድቦኛል። ልጅ ትምህርት ቤት ማመላለስ፣ የልጄን ትምህርት በአግባቡ መከታተል እንዲሁም ለመኖር የሚያስችለንን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ መከወን በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው። ይህ ማለት ግን፣ ተሳትፎዬ ይቀንስ እንጂ፣ የሀገሬን ማንኛውንም ነገር ከመከታተል ወደ ኋላ ብዬ አላውቅም። ለተጠየኩት ጥያቄ መልሴ ግን፣ ባለችኝ ጊዜ የምፅፋት ነገር ምሬት እንደሚበዛባት አውቃለሁ። የዚህ ምሬት ምክንያት ደግሞ፣ ከሀገሬ መራቄ አንዱ ምክንያት ነው። ከሀገርህ ርቀህ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን ጭቆና ማድመጥ በጣም ያማል። ምናልባትም ከመላመድ ብዛት፣ ውስጡ ሆነህ (ሀገርህ ላይ) እምብዛም አይታወቅም፡፡ ራቅ ስትል ግን፣ ‹‹እንደዚህ ለምን ይሆናል?››፣ ‹‹..እስከመቼ?›› የሚለው ነገርን ነገር በተደጋጋሚ እንድታስበው ያደርግሃል። በትንሹም ቢሆን የእኔም መረር ያለ ፅሁፍ ከዚህ የመነጨ ነው ብዬ አስባለሁ።

በአሜሪካ ሆነሽ፣ እስክንድርን በተመለከተ ምን እያደረግሽ ነው?
————————–

ባለሁበት ሀገር፣ እስክንድርን በተመለከተ፣ ከተለያዩ አካላት ጋር እገናኛለሁ። ስቴት ዲፓርትመንት ከጎንግረስ ማኖች (Congress man)፣ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እንዲሁም የተለያዩ ተቋማት ስለእስክንድር የማያውቁት ነገር ባይኖርም፣ በተጨማሪ እኔም ስለሚገኝበት ሁኔታ እና በእስር ቤት ውስጥ ስለሚደርስበት የሰብዓዊ መብት ጥሰት አሳውቃቸዋለሁ። የሚገርመው ነገር በየሄድኩበት ትላልቅ ተቋማት በእስክንድር ጉዳይ ላይ ከበቂ በላይ መረጃ ያላቸው መሆኑን ነው። ‹‹እስክንድር አሸባሪ ነው›› የሚለውን የሀሰት ፍረጃ ጠንቅቀው እንደሚያውቁ በተደጋጋሚ በአንደበታቸው ሲገልፁ ይሰማል። ከኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በተጨማሪ፣ በትልቅ የኃላፊነት ቦታ ላይ የሚገኙ ባለሥልጣኖች ለእስክንድር ያላቸውን ክብር መስማት የተለመደ ነው። …ገፍተው ሌላ ነገር ማድረግ ባይችሉም እስክንድርን የሚመለከቱት በተለየ መነፅር ነው። ለጊዜው በዚህ እንቅስቃሴ ላይ እገኛለሁ። ወደፊት ግን እስክንድርን በተመለከተ ለመስራት የታሰበ ሰፊ ሥራ አለ። ጊዜው ሲደርስ የምገልጸው ይሆናል።

በግልሽ እስክንድር ከእስር ወጥቶ በቅርቡ እንገናኛለን የሚል እምነት አለሽ?
—————————
እስክንድር የጊዜ ጉዳይ እንጂ ከእስር እንደሚፈታ ጥርጣሬ የለኝም። መቼ? ለሚለው ግን እስክንድር ከዚህ በፊት እንደገለጸው ጊዜው ሊያጥርም ሊረዝምም ይችላል። ነገ ይፈታል፣ ከነገወዲያ ይፈታል ብዬ የቀን ስሌት አላስቀመጥኩም። አንድ የማምነው ነገር፣ የሀገሪቷ ችግር ሲፈታ፣ እስክንድርም አብሮ እንደሚፈታ ነው። እስከዚያው ከጨለማው ስር የሚወጣውን ብርሃን እጠብቃለሁ።

በሀገር ጉዳይ ላይ፣ ከሴት እህቶቻችን ምን ይጠበቃል?
———————-

በሀገሬ ጉዳይ ላይ ከሴት እህቶቻችን ብቻ ሳይሆን ሁሉም ሀገር ወዳድ ወገኖቻችን ንቁ ተሳትፎ በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ማድረግ አለባቸው እላለሁ። በሀገራችን ጉዳይ ላይ ለመሳተፍ የግድ ፖለቲከኛ መሆን አይጠበቅብንም። ከዚህ ባለፈ ሩቅ ሆኜ፣ እንዲህ ቢደረግ፣ እንዲያ ቢደረግ የሚል ነገር ለማስተላለፍ የሞራል ብቃቱ የለኝም። ‹‹እንዲህ አድርጉ›› ለማለት ከህዝብ ጋር ሆነህ በሀገር ላይ ተቀምጠህ እንጂ፣ በርቀት ሆኜ የምናገረው አንዳችም ነገር የለም።

በሀገር ውስጥ ለሚገኙ (ለሚያውቁሽና ለማያውቁሽ) ወገኖችሽ ያለሽ መልዕክት …
———————-
በመጨረሻ… ለሚያውቁኝ ወገኖቼ የማስተላልፈው መልዕክት፣ እስክንድር ከታሰረ ጀምሮ በሞራልም በገንዘብም ከጎናችን ላልተለያችሁን ወገኖቼ በያላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛ የሚል ነው፡፡

Semayawi Party in Stockholm, Sweden. በስዊድን የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር ራሱን አስተዋወቀEthiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. April 7, 2015)፡- ቅዳሜ አፕሪል 4 ቀን 2015 ዓ.ም. (ግንቦት 26 ቀን 2007 ዓ.ም.) የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር በስዊድን ተመስርቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በመግለጽ፤ የድጋፍ ማኅበሩ ራሱን አስተዋውቋል። በዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ዓላማና ተግባርን ጥሪ ለተደረገላቸው ተሰብሳቢዎች ያስረዱት አቶ ሰለሞን ጌታነህ የድጋፍ ማኅበሩ ሰብሳቢ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አንዱዓለም ተፈራ
Atse Tewodros. አፄ ቴዎድሮስ

እንደ እውነቱ ከሆነ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ገዥ ቡድን በእብሪት ተወጥሮ አገራችንን ሲጫወትባት፤ “እኛ የኔ ድርጅት! የለም የኔ ድርጅት!”፣ “እኔ ልምራ እናንተ ተከተሉኝ! የለም እኔ ልምራ እናንተ ተከተሉኝ!”፣ “እኔ እበልጣለሁ! የለም እኔ እበልጣለሁ!” እየተባባልን፤ በሌለ ሥልጣን ሽሚያ ልባችን ተወጥሮ፤ ዛሬ ትናንት፤ ነገ ደግሞ ዛሬ እየሆነ ዓመታትን አስቆጠርን።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዲ/ን ክንፈ ገብርኤል
Hosaena

ሆሣዕና ቃሉ የዕብራይስጥ ሲሆን ትርጓሜውም “አሁን አድን” ማለት ነው። እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት ከፋሲካ/ከትንሳኤ በፊት ያለው እሑድ “የሆሣዕና እሑድ” በመባል ይታወቃል። በዚህ ዕለትም በቤተ ክርስቲያናችን የሚዘመረው መዝሙር፣ ማኅሌቱ፣ ቅዳሴው፣ ምንባቡና ማንኛውም አገልግሎት ሁሉ ዕለቱን በታላቅና እጅግ ደማቅ በሆነ መንፈሳዊ ሥነ – ሥርዓት የሚዘከርበት፣ የሚታሰብበት ነው። ይህ በዓል እጅግ በደማቅና ልብን በሚመስጥ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓትና ድምቀት ከሚከበርባቸው ቅዱሳን ገዳማትና መካናት መካከል የአክሱሟ ርዕሰ አድባራት ጽዮን ማርያም እና በዚህ በአዲስ አበባችን የእንጦጦ ማርያም በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ነጻነት ለሀገሬ)
Sudanese President Omar al-Bashir, center, Egyptian President Abdel-Fattah el-Sissi, left, and Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn, right, shake hands after signing an agreement on sharing water from the Nile River, in Khartoum, Sudan, Monday, March 23, 2015. Egypt, Ethiopia and Sudan on Monday signed an initial agreement on sharing water from the Nile River that runs through the three countries, as Ethiopia constructs a massive new dam it hopes will help alleviate its electricity shortages. El-Sissi, al-Bashir and Desalegn welcomed the agreement in speeches in Khartoum’s Republican Palace on Monday. (AP Photo/Abd Raouf) (The Associated Press)

ከላይ ለዚህ ትችት የተሰጠው ርዕስ እንደሚያመለክተው በአንድ በኩል በገንዘብ እጦት ችግር ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ለማድረግ ባለመቻሉ ምክንያት የተገደበ ወይም ደግሞ እንደ ጅብራ ተገትሮ የቀረ ግድብ የሚል ትርጉምን የሚይዝ ሲሆን፤ ሌላው ትርጉሙ ደግሞ ከፍተኛ በሆነ የገንዘብ እጦት ችግር ምክንያት የተመደበለትን ገንዘብ በማብቃቃት ለመስራት በማሰብ ደረጃቸውን ባልጠበቁ ግብዓቶች በመጠቀም ለርካሽ የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ሲባል እንደምንም ተውገርግሮ የተሰራ ግድብ ብዙም ዘለቄታ ሳይኖረው በአንድ ወቅት አውዳሚ በሆነ መልኩ ተንዶና ተደርምሶ የህዝብ ሀብት እና ጉልበት መና ሆኖ ይቀራል የሚል ፍሬ ሀሳብን የያዘ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም (አዲስ አበባ)

ዓለም ሁሉ ጠላን፤ በየትም አገር እየሄድን ‹‹የሙጢኝ!›› ከራሳችን መሬት በጉልበት እየተነቀልን፣ ከራሳችን ቤት እየተባረርን፤ ከተወለድንበትና ከአደግንበት አካባቢ እየተፈናቀልን፣ ጭራውን ቆልምሞ እንደሚሮጥ ባለቤቱ እንዳባረረው ውሻ በአገኘነው አቅጣጫ እየሮጥን፣ እጃችንን እያርገበገብን ‹‹የሙጢኝ!›› እንላለን፤ የፈራነውን ሞት በየመንገዱ እናገኘዋለን፤ ሞትን ሸሽተን ሞት ያጋጥመናል፤ የሞቱ ልዩነት አይታየንም፤ በየመንገዱ የሚያጋጥመው ሞት የውርደት ሞት ነው፤ የብቸኛነት ሞት ነው፤ ዘመድ-ወዳጅ ለቀብር የማይገኝበት ሞት ነው፤ ሠለስት፣ አርባ፣ ሙታመት የማይወጣበት ሞት ነው፤ ባዕድ ምስጥ ያላሳደገውን አካል የሚበላበት ነው፤ የሞት ሞት ነው፡፡prof-mesfin-speaks-out-on-ethio.jpg

ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ከአገር አስወጥቶ ባዶ መሬት ብቻ ይፈልግ ይመስል የወያኔ ሎሌዎች በማስፈራራት ሁሉም አገሩን እየተወላቸው እንዲሄድ ያቀዱ ይመስላል፤ ጥንት ኢሰመጉ በምሠራበት ጊዜ በየጊዜው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሰዎችን በማስፈራራት ሰላማቸውን ለመረበሽ ወደስደት ወይም ወደወንጀል ተግባር የሚመሩ የወያኔ አባለች ነበሩ፤ አሁን እንደገና ብቅ ማለት ጀምረዋል፤ ሕጋዊ ሥርዓት እየላላ ጉልበተኞች በግላቸው ለዘረፋና ለቅሚያ እየተሰማሩ ይመስላል፡፡

ስለራሴ ላውራ፤ ከእኔ የሚፈልጉት ምን እንደሆነ እርግጠኛ አይደለሁም፤ የሚፈልጉት የምኖርበትን አፓርትመንት እንደሆነም አላውቅም፤ በእኔ ቤት ያለ ሀብት የሚባል ለወያኔ አገልጋዮች የሚጠቅም ሁለት የገብረ ክርስቶስ ስዕሎች ብቻ ናቸው፤ (በዚህ አጋጣሚ እነዚህን ስዕሎች ለመግዛት የሚፈልግ ያነጋግረኝ)፤ ከዚህ ሌላ ለወያኔ ዋጋ የሌላቸው መጻሕፍት ናቸው፤ ስለዚህም አሁን በእኔ ላይ የተሰነዘረው ጥቃት እኔን ወደስደት ለመግፋት የሚደረግ ሙከራ ይሆናል፤ በ1992 ግድም ተሞክሮ ነበር፤ አልሠራም፤ ዛሬ ይበልጥ አይሠራም፤ ለማናቸውም ምክንያቱን በትክክል ለማወቅ ባልችልም በእኔ ላይ ዘመቻ መጀመሩን አንድ በቅርብ ከማውቀው ወያኔ በትክክል ተረድቻለሁ፤ ይህንን ዘመቻ በመምራት ላይ ያለውንም ሰው ማንነት ተነግሮኛል፡፡

ይህ አገር የአንድ ጉልበተኛ ቡድን ነው ብዬ አልቀበልም፤ የአባቶቼና የእናቶቼ፣ የኤቶቼና የቅድማያቶቼ አጥንትና ደም የገነባው አገር ነው፤ ማንም ለስደት አይዳርገኝም፤ ማንም አስፈራርቶ ኢትዮጵያዊነት መብቴን መግፈፍ አይችልም፤ አልፈቅድለትም፤ በግልጽ በማያጠራጥር ቋንቋ ኑሮዬም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም እዚሁ ነው፤ ከኢትዮጵያ አፈር የሚለየኝ የለም፡፡

እኔን ለማጥቃት ላሰፈሰፉት ወያኔዎችና ሎሌዎቻቸው አንድ እውነት ልንገራቸው፤– በፈለጉትና በተመቻቸው መንገድ በእኔ ላይ በጉልበታቸው ግፍ ቢፈጽሙ ነገ በነሱ ላይ የባሰ ግፍ እንደሚደርስባቸው ይወቁት፤ ሁልጊዜም ከሕግ የወጣ ጉልበተኛነት ጉልበተኛነትን ያነግሣል፤ በመግደል ድል ይገኛል ብለው የሚያምኑ ወያኔዎች ትንሽ ቆም ብለው ያስቡ፤ በመሞትም ድል ይገኛል፤ በመሞትም ማሸነፍ ይቻላል፡፡

በእኔ ላይ የዘመተው ወያኔ ወይም ሎሌ ማናቸውም ሥራ ውጤት እንዳለው ማወቅ አለበት፤ አንድ ነገር አድርጎ ምንም ዓይነት ውጤት አያስከትልም ብሎ ማሰብ ድንቁርና ነው፤ ይህ የሳይንስ ሕግ ነው፤ For every action there is a reaction ይላል!

62 ሕፃናት ተገድለዋል
People gather at the site of an air strike at a residential area near Sanaa (Reuters)

Ethiopia Zare (ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን 2007 ዓ.ም.፣ April 2, 20015)፡- የየመን ሑቲ ሚሊሽያ አማጽያንን ለማጥቃት በሳውዲ ዐረቢያ መሪነት በየመን ላይ እየተወሰደ ያለው የአየር ድብደባ በአገሪቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ስጋት ውስጥ እንደከተታቸው ታወቀ። ለሣምንት በዘለቀው የአየር ጥቃት 62 ሕፃናት መገደላቸውን ዩኒሲኤፍ ገለፀ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ali Birra. ዓሊ ቢራ

ቋንቋዎቻችን የልዩነት፣ የጥላቻና የዘረኝነት ጽኑ ግምብ ሲሆኑብን!

ኒቆዲሞስ

የኃይማኖት ሊቃውንት በጥንት ዘመን ፍጥረት ሁሉ በአንድ ቋንቋ ይነጋገር እንደነበርና ቆይቶ ግን ይህ በአንድ ቋንቋ የመግባባት ጉዳይ ብዙም ሳይዘልቅ እንደተቋረጠ ያትታሉ። ምክንያቱን ሲያብራሩም ጥንታውያኑ ባቢሎናውያን ገናና ሥልጣኔያቸው ጫፍ በነካ ማግሥት ሰማይን የሚታከክና የፈጣሪን መኖሪያ፣ ክብሩንና ልዕልናውን የሚዳፈር ረጅምና ግዙፍ የሆነ ታላቅ ግምብ ለመገንባት ተነሱ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Sharpeville Massacreፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ነጻነት ለሀገሬ)

ደቡብ አፍሪካ እ.ኤ.አ. በ1960፣

እ.ኤ.አ መጋቢት 21/1960 ልክ ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት ወደ 5 ሺ የሚገመቱ ሰልፈኞች (እንደ አፓርታይድ ፖሊስ የተጋነነ መረጃ ከሆነ ደግሞ 20 ሺ ሰዎች) በደቡብ አፍሪካ በሻርፕቪሌ ከተማ በትራንስቫል ግዛት (በአሁኑ ጊዜ ከደቡብ አፍሪካ 9 ግዛቶች መካከል አንዷ በሆነችው እና ጋውቴንግ እየተባለች በምትጠራው ግዛት) ፖሊስ ጣብያ ፊት ለፊት ተሰባሰቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

W/o Abeba Gebrehiwot. ወ/ሮ አበባ ገ/ህይወት Ethiopia Zare (ሐሙስ መጋቢት 17 ቀን 2007 ዓ.ም. March 26, 2015)፡- የአዲስ አበባ የኢህአዴግ ጽ/ቤት የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ የነበሩት ወ/ሮ አበባ ገ/ህይወት፣ ኢህአዴግን መክዳታቸው ተሰማ። ወ/ሮ አበባ ኢህአዴግን የከዱት በቅርቡ ለስብሰባ በሄዱባት ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ መሆኑ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …