በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው አደጋ ላይ ነው
62 ሕፃናት ተገድለዋል
Ethiopia Zare (ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን 2007 ዓ.ም.፣ April 2, 20015)፡- የየመን ሑቲ ሚሊሽያ አማጽያንን ለማጥቃት በሳውዲ ዐረቢያ መሪነት በየመን ላይ እየተወሰደ ያለው የአየር ድብደባ በአገሪቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ስጋት ውስጥ እንደከተታቸው ታወቀ። ለሣምንት በዘለቀው የአየር ጥቃት 62 ሕፃናት መገደላቸውን ዩኒሲኤፍ ገለፀ።