ግርማ ካሳ

በወልቃይት ጠገዴና ቃብቲያ ሁመራ ህዝብ ላይ የታቀደው ድቡቁ የህወሓት ሴራ ሲጋለጥ | ምስጢራዊ መረጃ

በቅርቡ አንድ በትግሪኛ የተዘጋጀ ሚስጥራዊ ሰነድ በአማርኛ ተተርጉሞ ዘሃበሻ ላይ አነበብኩ። ህወሓት በወልቃይት ዙሪያ ያጋጠመውን ፈተና ለመመከት እንዲያስችለው ያዘጋጀው ሰነድ እንደሆነ ነው የተገለጸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ናኦሚን በጋሻው

Lencho Leta. ኦቦ ሌንጮ ለታ

በኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባር፣ ኦዴግ ውስጥ ያሉ አመራሮች በጣም የተከበሩ በሳል አመራሮች ናቸው። ለዓመታት በትግሉ ውስጥ ያለፉ፣ በርግጥም ለኦሮሞው ማኅበረሰብ የሚበጀውን እና የሚጠቅመውን የተረዱ። በኦሮሞውና በሌላው ማኅበረሰብ መካከል አለመተማመን እና መጠራጠር እንዳለ፣ ይሄንንም ለመግዛት እና ለመበዝበዝ እንዲያመቸው ሆን ብሎ ያደረገው ሕወሃት እንደሆነ በሚገባ የሚያውቁ። የኦሮሞው ማኅበረሰብ ከሌላው ጋር ያለውን ግንኙነትና ትስስር አጠናክሮ ለሁሉም እኩል የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ይቻል ዘንድ ፍላጎት አላቸው። በፖለቲካ አመለካከታቸው ጥሩ መስመር ላይ ያሉ ነው የሚመስሉት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጓድ ካፍትሌ

ጥያቄ ለአንባገነኖች፤ ዓለምን የሚገዛው ኃይል የቱ ነው?

“Whoever wishes to foresee the future must consult the past; for human events ever resemble those of preceding times. This arises from the fact that they are produced by men who ever have been, and ever shall be, animated by the same passions, and thus they necessarily have the same results.” Machiavelli

የዴሞክራሲ ጽንሰ ሀሳብ በዓለም ላይ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት የተለያዩ የአስተዳደር ስልቶች ተግባራዊ ለማድረግ ተሞክሯል። አብዛኞቹ የአስተዳደር ስልቶች ግን ኃይልን መሠረት ያደረጉ ስለነበሩ በመሪና በተመሪዎች መካከል ከፍተኛ ቅራኔን ሲያሳድር ኖሯል።መሪዎቹ ለሚገዙት ሕዝባቸው ወፍራም ዱላ ካሳዩ ሕዝቡ ቀጥ ለጥ ብሎ ይገዛልኛል ብለው ስለገሚገምቱ የሥልጣን ዕድሜያቸውን ለማራዘም የሚሊዮኖችን ደም በከንቱ አፍስሰዋል። የአንድ ቀን የሥልጣን ዕድሜያቸውን በአንድ ሺህ ሰዎች ደም ያቆዪታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አሊ ጓንጉል

አያሁለት ማዞሪያ (ሃያ ሁለት ማዞሪያ)፣ ምሿለኪያ (መሿለኪያ)

የተሰደዱ እና ባገር ውስጥ በየእስር ቤቱ የታጎሩትን ጋዜጠኞች እና ጸሃፍትን ብዛት ላሰበ ሰው አማርኛ አሁንም የሚጻፍበት ቋንቋ ሆኖ መዝለቁ እሰየው ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተስፋዬ ገብረአብ

PM Halemariam Dessalegn daughter wedding. ጠ/ሚ ኃይለማርያም በቅርቡ ሴት ልጃቸውን የሞቀ ሠርግ ደግሰው ሲድሩ

ኃይለማርያም ደሳለኝ ባለፈው ሣምንት ያደረጉት ቃለመጠይቅ አነጋጋሪ ነበር። ከኦሮሞ ህዝብ አመጽ ጋር በተያያዘ የሰነበተውን ችግር ሌላ አካል ላይ ማላከክ እንደማይገባ መናገራቸው ከኢህአዴግ ጠባይ አንፃር ያልተለመደ ነበር። በውስጥ ባለ ችግር ምክንያት የህዝብ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ባለማግኘታቸው ህዝብና መንግሥት ተቃቅረው ጉዳዩ ወደ ግጭት ደረጃ መድረሱን ማመናቸው አንድ እርምጃ ወደፊት ነው። ችግሩ የመልካም አስተዳደር እጦት መሆኑን መግለፅ መቻላቸው ይደነቃል። ኃይለማርያም በዚህ ደረጃ ችግሩን አምነውና ተቀብለው ሲያበቁ፤ በመጨረሻ ለተፈጠረው ችግር በጥቅሉ ህዝብን ይቅርታ ጠይቀዋል። ይቅርታ ጥየቃው ካንገት በላይ ነው ወይስ ካንገት በታች ለጊዜው ባናውቅም፤ ይቅርታ መጠየቅ በራሱ ሥልጣኔ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ PM Hailemariam Desalegnግርማ ሠይፉ ማሩ

“የመልካም አስተዳደር ችግር እንፈታለን፤ ሥልጣን ግን አንለቅም” መሆኑ ነው?
የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሪፖርትን በወፍ በረር ስንቃኛው የሚከተለው ይዘት እንዳለው መረዳት እንችላለን። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዓመቱ ከመጠናቀቁ ቀደም ብለው የዕድገት ቅናሽ እንደሚኖር በሰበብ ደግፈው አምነዋል። ይህም ደግሞ ገዢው ፓርቲ ከአስራ አንድ በመቶ የእድገት ልክፍት በግድም ቢሆን መላቀቁን የሚያሳይ ነው። ከዚህ ቀደም የፈለገውን ያህል ተግዳሮት ቢፈጠር ያልተተገበሩ ግዙፍ ዕቅዶች ዝርዝር ቢቀርብም “ቢሆንም 11 ከመቶ አድገናል” እንደ ነበር አንዘነጋውም። ጠቅላይ ሚኒሰትሩ የእድገት ቅናሽ መኖሩን ቢያምኑም “ትንሽ ቅናሽ ያሳያል” በሚል ማለፋቸው ዝናብ ከዘነበ መልሶ ለማቅራራት ዝግጅት እንዳለ አመላካች ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ገለታው ዘለቀ

የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ፔትሮ ፕሮሸንኮ በረሃብ የሞቱትን ሰዎች በመታሰቢያ ሐውልቱ ስር ሲያስቡ። President of Ukraine Petro Poroshenko attending a memorial on November 22, 2014 in Kyiv for the victims of the Holodomor, or the Famine-Genocide conducted by the Soviets in Ukraine in 1932-1933, which killed millions of Ukrainians. (Image: ImagineChina)

ታላላቅ ረሃቦች ተብለው በዓለም ታሪክ ከሚዘከሩት ውስጥ የቻይናውያን ረሃብ አይዘነጋም። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ1958-1961 ድረስ ቻይና ውስጥ ከፍተኛ ረሃብ ተከስቶ ወደ ሰላሳ ሚሊዮን ህዝብ ረግፏል። ብዙ ምሁራን እንደሚሉት ለዚህ አስከፊና ቻይናውያን ሊረሱት ለማይችሉት ረሃብ አንደኛ ተጠያቂ ማዖ ዚዳንግን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከደቡብ ኦሞ እስከ መተማ፤ ከጅጅጋ እስከ ጋምቤላ፤ ከመቀሌ እስከ ባሌ፤ ከወልቃይት እስከ ኮንሶ

ያሬድ ኃይለማርያም

የፌዴራል ፖሊስ ሠላማዊ ሰልፈኞችን ሲበትን

በአንድ ማሕበረሰብ ውስጥ ቅድመ-አያቶች፣ አያቶች፣ ወላጆችና ልጆች፤ ሦስትና ከዛም በላይ የሆነ ትውልድ ተመሳሳይ በሆኑ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መሃል ተተብትቦ የሚማቅቅ ከሆነ የዛ ማሕበረሰብ ጉዞ ጤናማነትና አቅጣጫ ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል። በእንዲህ አይነት ማሕበረሰብ ውስጥ መሰረታዊ የሆኑና የጎሉ ለውጦች ብዙም አይስተዋሉም። አንዳንዶቹም ለውጦች የቁልቁለት ጉዞ ውጤቶች ይሆኑና በራሱ ብቻ ሳይሆን በአያቶቹም ቁስል የሚማቅቅ፣ መቃብር ቆፋሪና ሸክሙ የከበደው ትውልድ ይፈጠራል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም፣ ነጻነት ለሀገሬ)

March 21, 1960 Sharpeville Massacre in South Africa

በየዓመቱ በአፍሪካ ውስጥ የተፈጸሙ ሁለት የህዝብ እልቂቶችን አስታውሳለሁ።

በወርሃ መጋቢት በደቡብ

አፍሪካ የጥቂት ነጮች የበላይነት ዘረኛ አገዛዝ/apartheid በሻርፕቪሌ ከተማ እ.ኤ.አ መጋቢት 21/1960 የፈጸመውን ዘግናኝ እልቂት አስታውሳለሁ። እንደዚሁም ሁሉ በተመሳሳይ መልኩ በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን በህይወት በሌለው በአምባገነኑ መለስ ዜናዊ ልዩ ትዕዛዝ እ.ኤ.አ ሰኔ 8/2005 እና ከህዳር 1-10/2005 እንዲሁም ከ14-16 በህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ (ዘ-ህወሓት) የጥቂት ጥቁሮች የበላይነት የጎሳ አገዛዝ/apartheid የተፈጸመውን አሰቃቂ እልቂት አስታውሳለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

People has been taken by federal police in south Ethiopia, Sumra.  በደቡብ ኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የሱምራ ብሔረሰብ አባላትን በገመድ አስሮ እየደበደበ አሰቃየ

ሰሞኑን በደቡብ ኢትዮጵያ በሚኖሩ ዜጎች ላይ የተፈጸመን የባሪያ ፍንገላን ዘመን የሚያስታውስ ኢሰብዓዊ ድርጊት የሚያሳይ ፎቶ በማኅበራዊ ድረ-ገጽ ተሰራጭቶ አጀኢብ ጉድ ብለናል። ነገሩ ትናንትን እየረሳን ዛሬ ለሚያጋጥመን ነገር አዲስ እየሆንን ጉድ ጉድ ለምንለው ለእኛ ነው እንጂ አዲስነቱ ለወያኔ ከበረሃ ጀምሮ አብሮት የኖረ ተግባሩ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተስፋዬ ገብረአብ

Prof. Ephraim Isaac ፕሮፌሠር ኤፍሬም ይስኃቅ

ዝነኛው አሸማጋይ ፕሮፌሠር ኤፍሬም ይስኃቅ መሰንበቻቸውን ሥራ እንደበዛባቸው ተሰምቷል። የኦሮሞን ህዝብ አመጽና ጥያቄ በሰላም ለመጨረስ እዚህም እዚያም እየደዋወሉ ልብ የሚነኩ እግዚአብሔራዊ ቃላት ተናግረዋል። የፕሮፌሠሩ ጥረት በደፈናው የሚነቀፍ ባይሆንም አይሳካላቸውም። የሽማግሌው የእርቅ መንገድ ጥሎ ማለፍ ይዘት እንዳለው ካለፈ ድርጊታቸው ትምህርት ተገኝቷል። በተጨማሪ ድርድር ወይም እርቅ ሲታሰብ መላ የኢትዮጵያን ህዝብ የመብት ጥያቄዎች ታሳቢ በማድረግ እንጂ፤ ጉልበት ካገኘው ኃይል ጋር ብቻ የመደራደር ዝንባሌ ያለፈውን ስህተት መድገም ይሆናል። በመሰረቱ ወያኔ በስውር ሽማግሌ መላክ መጀመሩ ጊዜ ለመግዛት ካልሆነ ከልብ እርቅና መደራደር ፈልጎ እንደማይሆን ይገመታል። ከፋፍሎ የማዳከም የህወሓት አካሄድ ገና ድሮ ተባኖበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

TPLF / ህወሓት

ወያኔዎች ለትግል በረሃ ገባን የሚሉበት ግዜ የንጉሡ ሥርዓት ፈርሶ ኢትዮጵያ ወዴት እንደምትሄድ አይደለም የት ላይ እንደቆመች እንኳን በቅጡ ያልየበት ወቅት ስለነበር፤ ለብሶት ዳርጎ ወደ ጫካ የሚያስኬድ ቀርቶ ከተማ ተቀምጦ ለማኩረፍ የሚያበቃ በደል ነበር ለማለት አይቻልም። ስለሆነም ወያኔዎች በዛን ወቅት ለትግል የተነሱት የአጼ ዮሐንስን ቤተ መንግሥት ይዘው የትግራይን መንግሥት የመመስረት ህልማቸውን ለማሳካት መንግሥት አልባው ወቅት ምቹ ሆኖ ስለታያቸው ነበር። ቢዘገይም ካሰቡት በላይ ተሳክቶላቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም፡- ነጻነት ለሀገሬ)

Ethiopian taxi drivers strike

በአሜሪካ “ባለሦስት-ጥፋት ሕግ“ እያሉ ይጠሩታል። ወንጀለኞች ሦስት ከባድ ወይም ደግሞ አስከፊ ወንጀሎችን የሰሩ ከሆነ ከ25 ዓመት እስከ እድሜ ልክ እስራት የሚያደርስ ቅጣት ይበየንባቸዋል።

ዘ-ህወሓት በኢትዮጵያ የታክሲ አሽከርካሪ ሾፌሮች ላይ ጦርነት አውጇል!

ሙሉውን አስነብበኝ …

ክንፉ አሰፋ

Jawar Mohamed ጃዋር መሐመድ

መገናኛ ብዙኀንን መቼ እና እንዴት መጠቀም እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ከፈጸመ በኋላ ግን እንደ በረሃ ተኩላ እያደፈጠ ይናከሳል። ሲናከስ ደግሞ ማንንም አይምርም። ውለታ የሚባል ነገር አያውቅም። ይሉኝታ አይነካካውም። እፍረትም በእርሱ ዘንድ የለችም። ከቶውን መቀበል እንጂ መስጠትን አያውቅም። አስር ተቀብሎ በዜሮ የሚሸኝ ጀግና ነው። በዚህ ተግባሩ አድናቂው ነኝ። “እኔ-ነኝ” ያለ የዲሲ ፖለቲከኛን ሳይቀር ከአንዴም ሁለቴ እንደማስቲካ እያኘከ መትፋቱን እንመሰክራለን። የጡት አባቱ የሆነው ኦነግንም ቢሆን ‘A Critical Assessment of the Oromo Liberation Front” በሚለው መጣጥፉ እንዳይሆን እንዳይሆን አድርጎ የጠረበ ፍጡር ነው። ይህ ሰው እንደገና ተመልሶ የ”ነፍጠኛውን ሜድያ” ለመጠቀም የማይሞክርበት ምክንያትም የለም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዳዊት ዳባ

ዛሬ እየሰፋ እየገዘፈና ጉልበት እያገኘ የመጣው ህዝባዊ እንቢታ ከዐረቡ ሀገሩ ህዝባዊ አልገዛም ባይነት የጀመረ ይመስለኛል። ያኔ ከዚህ ሥርዓት በዚህም መንገድ መገላገልም ይቻላል ለካ? የሚለው እሰቦት በአዕምሮው ያልዞረ ኢትዮጵያዊ ነበር ለማለት አይቻልም። የሥርዓቱም ደጋፊዎችም ቢሆኑ በግልባጩ እንቅልፍ ያጡበት ጉዳይ ነበር። አልገዛም ባይነቱ በኛ ሀገር ይሄ-ያ ይጎድለዋል። ይህ አደጋ አለው። በዚህ አንመሳሰልም ይሉ የነበሩትም ቢሆን ግምት ውስጥ አስገብተው አስበውበት ስለነበር ነው። ኃላፊነት ወስደው ይሠሩበት የጀመሩ ስብስቦች እርግፍ አድርገው ቢተዉትም። ድርጅቶች የስትራተጂ ለውጥ ቢያደርጉና ትኩረታቸው ወደሌላ ቢያዘነብልም ሂደቱ የሚገታ አልሆነም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

SMNE announced the formation of the Ethiopian Council for Reconciliation and the Restorative of Justice (ECRRJ) at a public meeting held at the Sheraton Hotel in Silver Springs, Maryland (February 14, 2016)

በአቶ ኦባንግ ሜቶ በሚመራው ድርጅት አዘጋጅነት በተጠራ ጉባኤ ላይ የተገኙ ኢትዮጵያውያን ስብሰባቸውን ያጠናቀቁት በሀገራችን ዕርቅ አስፈላጊ መሆኑ ላይ በመተማመንና ለዚህም ተግባራዊነት ዕርቅን ከራስ መጀመር እንደሚገባ አጽንኦት በመሰጠት መሆኑን ሰምተናል። የእስከዛሬው ተሞክሮአችን ተግባራዊነቱን እንድንጠራጠር ቢያደርገንም የአሰባሳቢዎቹ ተግባርም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የደረሱበት ድምዳሜ የሚደነቅ ብቻ ሳይሆን ለተግባራዊነቱ ድጋፍ ሊቸረው የሚገባ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተስፋዬ ገብረአብ

በዓለማችን ላይ ወጣቶች በአንድ ልብ የተሳተፉበት ያልተሳካ የአብዮት ታሪክ አናውቅም። የጊዜ ጉዳይ ብቻ ነው። ይህችን እየፃፍኩ ሳለ የማያቋርጥ፣ የተቀናጀ የአመፅ ዜና ከኢትዮ-ኦሮሚያ እየሰማሁ ነበር። ዝምታው ማብቃቱ ግልፅ ነበር። የኦሮሚያ ወጣቶች የሥርዓቱን ታጣቂ ኃይል በጦርና በጠመንጃ ይፋለሙት ይዘዋል። ከሻሸመኔ ወደ አዲስ አበባ መንገድ ተዘግቶአል። ልማደኛዋ ኮፈሌ ጦር ሜዳ ሆናለች። ብረት ለበስ ጦር ኮፈሌና ሻሸመኔ ገብቷል። በጥቅሉ ወለጋና ሐረርጌ ፀጥታ የለም። ሱሉልታ ብሶበታል። ጭራሽ ገበሬዎቹ ያስለቀቁትን መሬት መከፋፈል ጀምረዋል። ደራ ነፃ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ካሳ

የምታዩት ፎቶ ምን ያህል በኦሮሚያ ያለው እንቅስቃሴ በአክራሪዎች፣ በኦነጋውያን እንደተጠለፈ የሚያሳይ ነው

ከ25 ዓመታት በፊት ህወሓት/ኢህአዴግ ከፋፍሎ ለመግዛት በሚል የዘረጋው የዘር ፖለቲካ ወይንም የነርሱን አባባል ልጠቀምና “የብሔር ብሔረሰቦች” ፖለቲካ፣ ብዙዎች ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ሊያጠፋ የሚችል ትልቅ አደጋ “time bomb” እንደሚሆን ሲያስጠነቅቁ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

ወያኔ ብአዴንና ኦህዴድ የሚባሉ አገልጋዮቸን ፈጥሮ፣ ኢትዮጵያውያንን በጎሣ አከፋፍሎና ለአገዛዙ እንዲመቸው አድርጎ አደላድሎ ለ17 ዓመታት የተዋጋለትን ዓላማውን ተግባራዊ ከማድረግ አልፎ ሃያ አራት ዓመታት በሥልጣን መቆየት በመቻሉ ሊደነቅ ይገባል። ለዴሞክራሲ እንታገላለን የሚሉ እንደ ወፍ ዘራሽ በየቦታው በቅለው ሳይለያዩ ተለያይተው፣ ሳይነጋገሩ ተጣልተው፣ የቃላት እንጂ የተግባር ሰውነት ርቆአቸው ሃያ አምስት ዓመታት ስንዝር መራመድ ባልቻሉበት ወያኔ እኩይ ዓላማውን ለማሳካት አንድነቱን አጥብቆ፣ ገመናውን ደብቆ በሌሎችም ተጠቅሞ መዝለቅ መቻሉን ማድነቅ አለመቻል የራስን ድክመት ለመቀበል አለመፍቀድ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ ሰዎችን የሚያሸጋግሩ አሉ ብሎ ይጠረጥራል

Ethiopian Airlines 787 dreamliner የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን

Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም. Mar. 01, 2016)፡- ከአዲስ አበባ ሌሊት ተነስቶ ዛሬ ጠዋት በስዊድን መናገሻ ስቶክሆልም በሚገኘው የአርላንዳ አየር ማረፊያ ባረፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን የዕቃ ኮንቴይነር ውስጥ የተደበቀ የ27 ዓመት ዕድሜ ያለው አንድ ሰው መገኘቱን ፖሊስ ገለጸ። ይኸው ግለሰብ በስዊድን ጥገኝነት መጠየቁ ታውቋል። ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ ሰዎች የሚያሸጋግሩ ወገኖች እንዳሉ ጥርጣሬ አለኝ፣ ጉዳዩን እያጣራኹ ነው አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ወያኔ የኦሮሞ ጠላት ነው

አንተነህ መርዕድ

Abayi Tsehaye አባይ ፀሐዬ

መለስ ሲያጉረመርምበት ብርክ የሚይዘውና የሚሙለጨለጨው፣ ጓደኞቹን ደጋግሞ በፍርሃቱ የሸጠው አባይ ፀሃዬ ዞር ዞር ብሎ ሲመለከት ከሱ የተሻሉና የሚያስፈሩት ህወሃቶች የሌሉ መሆናቸውን በማረጋገጡ በየመድረኩ ብቅ እያለ መፎከርና መዘባረቅ የእለት ተእለት ሥራው ሆኗል። በተለይም በዋና ባለቤትነት የአዲስ አበባን መሬት ሸጦ ከጨረሰ በኋላ የአካባቢውን ገበሬዎች ከነመሬታቸው ሊቀራመት ያደባበት ተንኮል አልሠራ ሲል “ልክ እናስገባቸዋለን” ሲል ፎከረ። አሁን ደግሞ ፉከራው የለኮሰውን እሳት ማዳፈን ተስኖት “ወያኔ የኦሮሞ ጠላት አይደለም” የሚል የሽሽት ሽምጥ ሩጫ ይዟል። እሳቱ ግን እሱን ሳይለበልበው የሚመለስ አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ካሳ

በግምት ከሃያ አራት ዓመታት በፊት ይሆናል ቀኑ። በኢትዮጵያ እርቅና ሰላም እንዲኖር ብዙ ጊዜ የሚደክሙና የሚጸልዩ፣ ቄስ ቶሎሳ ጉዲና የሚባሉ አንድ መንፈሳዊ አባት፣ ምዕመናንን ሲያስተምሩ የተናገሩት፣ ሁልጊዜ የማስታወሰውና የማልረሳው አባባል ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጌታቸው ኃይሌ

Identity crisis ማነኝ?

ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ማንነት ዋና የመወያያ ርዕስ ሆኖ ቈይቷል። የሥነ ልቡና ምሁራን identity crisis የሚሉት ነው እንዳልል ያተኰረው “እኔ ማነኝ” ከሚለው ላይ አይደለም። ያተኮረው “ማንነት ከመሬት ጋር ይያያዛል ወይስ አይያያዝም?” ከሚለው ጥያቄ ላይ ነው። ውይይቱን እንዳዳመጥኩትና እንደሰማሁት፣ እኔም አስተያየቴን እንድሰጥ ተጠይቄ እንደተቸሁት፣ ማንነትን ከመሬት ጋር የሚያያይዙ እምነታቸውን ከኃይማኖት እምነት ደረጃ አድርሰውታል። ስለዚህ እነሱን በማስረጃ ማሳመን ሃይማኖታችሁን ለውጡ እንደማለት ሆኗል። “እምነቱ ሀገር አጥፊ ነው፤ ተውት” ቢባሉም፣ ማንነታቸው ከያዙት መሬት ጋር ከተቆራኘ፣ ይህ አደገኛ አቋማቸው ለሚያስከትለው ሀገራዊ ችግር አንዳች ሥጋት አይታይባቸውም። ክልል ይዞ ኢትዮጵያዊ መሆን ይቻላል የሚሉም አይጠፉም። መሳሳታቸውን መስማት አይፈልጉም፤ ግን ማንነት የሚዘራበት መሬት የሚያስፈልገው ዳጉሳ አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

የአበው ተረት ለልጅ የሳቁለት ለውሻ የሮጡለት ነው የሚለው። ለፖለቲከኛ ያጨበጨቡለት የሚል ቢጨመርበት ተስማሚ ይመስለኛል። ልጅ ከሳቁለት ሁሉ ቦታ እየገባ ነገር ያበላሻል፤ ውሻ ከሮጡለት ጥሎ ካላንደባለለ ወይ ካልቦጨቀ አይመለስም ፖለቲከኛም ካጨበጨቡለት አበው ልቤ አደገና ያለ ቁመቴ አላስገባ አለኝ የገዛ ቤቴ እንደሚሉት ይሆንና ከእኔ በላይ ለአሳር በሚል መታበይ ብዙ ጥፋት ያደርሳል ኋላም ራሱን ያዋርዳል። እኛም ጥሎብን ይሁን ባህል ሆኖብን ባይታወቅም እየኮተኮቱ ማሰደግ እየገሩ ለወግ ማዕረግ ከማብቃት ይልቅ እያሞካሹ ማበላሹትን እያጨበጨቡ ወደ ገድል መግፋቱን ተክነንበታል። በዚህ መንገድ ስንት ለሀገርና ለወገን ሊጠቅሙ ይችሉ የነበሩ ሰዎችን አጥተናል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ካሳ

አቶ ብርሃነመስቀል አበበ፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ መብት ዙሪያ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ጽሁፎችን ይጽፋሉ። ቢቢሲ በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ስርጭት እንዲኖረው ፔቲሽኖችን በማስፍረም አንድ ዘመቻ እንደነበረ የምናስታወሰው ነው። ይሄንን ዘመቻ ይመሩ ከነበሩት መካከል አቶ ብርሃነመስቀል አንዱ ነበሩ። እኔም ሆንኩም በርካታ ኢትዮጵያዊያን ፔቲሽኑ ላይ ፊርማችንን በማስፈር፣ ፔቲሽኑ ያልፈረሙ እንዲፈረሙ በማበረታታት እንደነ አቶ ብርሃነመስቀል ባይሆንም፣ የድርሻችንን አበርክተናል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Anon+

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥር 30 ቀን 2008 ዓ.ም. Feb. 08, 2016)፡- በኢህአዴግ መንግሥት ሙሉ ቁጥጥር ስር ያለውና ጋዜጦችንና መጽሔቶችን የሚያሳመው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ድረገጽ “አኖን ፕላስ” (AnonPlus) በተሰኙ ያልታወቁ ወገኖች ከቅዳሜ ጥር 28 ቀን ጀምሮ ተጠለፈ (ሐክ ተደረገ)። ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ ድረገጹ እንደማይሠራ ለመገንዘብ ችለናል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የላላው ጭቃአንዱዓለም ተፈራ

አሁንም ቀኑን እንቆጥራለን። ሌሊቱንም እንዲሁ። አሁንም የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባርን ተግባር እንዘረዝራለን። አሁንም ሰዎች በገዛ ሀገራቸው እንዳውሬ እየታደኑ፣ እየተያዙ፣ ይታሰራሉ፣ ከሀገር ይሰደዳሉ፣ ይገደላሉ፣ … እንላለን። አሁንም በየቤተክርስትያኑና በየመስጂዱ እግዚዖ እንላለን። አሁንም የሀገራችን ለም መሬት ከባለቤቱ ኢትዮጵያዊ እየተነጠቀ፤ ለሹማምንትና ለውጪ ሀገር ባለሀብቶች ተሠጠ እያልን እናላዝናለን። አሁንም ሹማምንት ጀኔራሎችና ዘመዶቻቸው፤ ከተማዎችን ፎቅ በፎቅ አድርገው፤ ድሃን ማደሪያ አሣጡት እንላለን። ምን የማንለው አለ! ብቻ በገባንበት አረንቋ አሁንም እንረግጣለን።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ካሳ

Dr Berhanu Nega. ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

አንዳንንድ ወገኖች በግንቦት ሰባቶች ላይ የግል ችግር ያለብኝ ይመስላቸዋል። አይደለም። ከነርሱ ጋር የዓላማ ልዩነት የለኝም። ልዩነቴ የስትራቴጂ ነው። ግንቦት ሰባት ውስጥ ያሉ ወገኖች ዳይናሚክ የሆኑ ትልቅ ፖቴንሻል ያላቸው እንደሆነ አውቃለሁ። ሊቀመንበሩ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ በቅንጅት ጊዜ ቁልፍ ሚና የተጫወቱ መሪ ናቸው። ብዙዎቻችንን ኢንስፓየር ያደረጉ። ሆኖም በግንቦት ሰባት አመራርነት የወሰዱት ስትራቴጂ ግን ያላቸውን ፖቴንሻል እንዲጠቀሙበት የረዳቸው አይመስለኝም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተስፋዬ ገብረአብ

Andargachew Tsege. አንዳርጋቸው ፅጌ

እነሆ! ቅዳሜ ዞሮ መጣ። በዚህች የቅዳሜ ምሽት ስለ አንዳርጋቸው ጥቂት አወጋ ዘንድ መንፈሴ መራኝ። አዲስ ነገር አትጠብቁ። ከቀንዱም ከሸኾናውም ዝም ብዬ አወጋለሁ። የምትሠሩት ሌላ አስቸኳይ ጉዳይ ካላችሁ ይህን ጽሑፍ ለማንበብ ጊዜአችሁን አታቃጥሉ። እንደው ዘና ብላችሁ ከሆነ ግን ብታነቡት ምንም አይላችሁም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

Goonder before and after 1991

ወቅቱ 1994 ክረምት ነው። በየዓመቱ ትምህርት ቤቶች ሲዘጉ መምህራንን አንድም በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ለማጥመቅ ሁለትም ሥራ ፈተው ከዋሉ የሚሠሩት ስለማይታወቅ ጠርንፎ ለማቆየት የሚዘጋጀው ስብሰባ ጎጃም ደብረ ማርቆስ በሦስት አዳራሾች እየተካሄደ ነው። ቤተ መንግሥት አዳራሽ፣ ሲኒማ ቤትና መንገድ ትራንስፖርት አዳራሽ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ካሳ

Tesfaye Gebreab, ተስፋዬ ገብረአብ

አቶ ተስፋዬ ገብረአብ በአንድ ወቅት የኢሕአዴግ ባለሥልጣን የነበሩ ሰው ናቸው። ጥሩ ፀሐፊ ናቸው። ከኦሮሞ ብሔረተኞች ጋር የቅርብ ግንኙነት አላቸው። አንድ ወቅት እንደውም የኦሮሞ ተማሪዎች ማኅህበር ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ቀርበው ነበር። በዚያን ወቅት “በሞጋሳ እኔም ኦሮሞ ነኝ” ብለው ነበር። ሞጋሳ አንድ ሰው “ኦሮሞ” ባይሆንም የኦሮሞን ባህልንና ቋንቋን ከተቀበለ፣ በኦሮሞ “ሽማግሌዎች” ፍቃድ “ኦሮሞ” የሚሆንብት ሥርዓት ነው (naturalized ኦሮሞነት)።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተስፋዬ ገብረአብ (Gadaa)

Abay Tsehaye. አባይ ፀሐዬ

ከኦሮሚያ አመጽ ጋር በተያያዘ አባይ ፀሐዬ ስሙ በተደጋጋሚ ይነሳል። አንዳንድ ደንፊ ንግግሮች መናገሩንም ስናነብ ሰነባብተናል። ምን እንደነካው እንጃ እንጂ ጠባዩ እንኳ እንዲያ አልነበረም። አባይ በጠባዩ ድመት መሆኑ ነበር የሚታወቀው። ሊያጠቃ ሲፈልግ እንደ ፈረስ ጋማህን እያሻሸ እንጂ እንደ ቋረኛው ካሳ ጎራዴ አያወዛውዝም። ከታላቁ የኦሮሚያ አመጽ ጋር በተያያዘ “በሚናገራቸው ንግግሮች” ግን ስሜቱን መቆጣጠር የተቸገረ ይመስላል። ዞረም ቀረ አባይ ፀሐዬ እና ጓደኞቹ የገጠማቸውን ጦርነት በአሸናፊነት ለመወጣት መጣራቸውን ቀጥለዋል። ይሳካላቸው ይሆን?

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይገረም አለሙ

Dr. Merera Gudan and Girma Seifu. ዶ/ር መረራ ጉዲና (በግራ) እና አቶ ግርማ ሰይፉ (በቀኝ)

ለዚህች ጽሑፍ መነሻ ምክንያት የሆነኝ አቶ ግርማ ሰይፉ “የዶ/ር መረራ የቡዳ ፖለቲካ እና መቀበል ያቃተው መራራ እውነት”በሚል ርዕስ ያስነበቡን ጽሑፍ ሲሆን፤ ርሳቸው ለጽሑፋቸው ምክንያት የሆናቸው ደግሞ “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” የሚለው የዶ/ር መረራ መጽሐፍ እንደሆነ ገልጸዋል። የቡዳ ፖለቲካ የሚለው ቃልም ከዚሁ መጽሐፍ የተገኘ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopia Oromo students protest addis ababa plan. የኦሮሞ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ላይ ያሰሙት ተቃውሞይገረም አለሙ

በሀገር ውስጥም በውጪም ቁጥራው እጅግ የበዛ ተግባራቸው ግን ብዙም የማይታይ ፓርቲዎች አሉ። እነዚህ የሚችሉት ተዋህደው አንድ በመሆን፤ የማይችሉት ተባብረው ትብብርም ይሁን ግንባር በመፍጠር የነጻነት ቀናችንን ለማፋጠን የሚያስችል ትግል ያደርጉ ዘንድ ስንመኝ፣ ስንጠይቅ፣ ስንማጸን፣ ይህን ባለማድረጋቸውም ስንኮንን ወዘተ ዓመታት ተቆጥረዋል። እነርሱ ግን መተባበሩ ቀርቶ መከባበሩ አልሆን ብሎአቸው፣ ተደጋግፎ መቆሙ ቢቀር አንዱ ለአንዱ እንቅፋት ከመሆን መቆጠብ ተስኖአቸው ወያኔ ያሻውን እንዳሻውና ባሰኘው መንገድና ግዜ እየፈጸመ ከዚህ እንዲደርስ አድርገውታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

Bewketu Seyoum and Yared Tibebu በእውቀቱ ሥዩም እና ያሬድ ጥበቡ

ከሁለት ቀኖች በፊት ስለበእውቀቱ ሥዩም አድናቆታቸውን በፌስቡክ ላይ የገለጹ ሁለት ሰዎች ነበሩ፤ ለበእውቀቱ ያላቸውን አድናቆት እኔም እጋራቸዋለሁ፤ ነገር ግን የእነዚህ ሰዎች አድናቆት በእውቀቱ ራሱንና ማንነቱን እንዲከዳ ይቃጣቸዋል። አንዱን አውቀዋለሁ፤ ከፖሊቲካና ከትጥቅ ትግል ወደስደት ”ነጻነት” የተሸጋገረ ያሬድ ጥበቡ የሚል የሚያኮራ ስም ይዞ የስደት መምህር የሆነ ነው፤ ሁለተኛው ሚስተር ቴዲ ገብርኤል ይባላል። እነዚህ ሁለት ስደተኞች በእውቀቱ ሥዩምን በጣም ስለሚወድዱትና ስለሚያከብሩት በአሜሪካ ስደተኛ ሆኖ እንዲቀርላቸው ይፈልጋሉ፤ በዚህ ብቻ ለኢትዮጵያ ያላቸውን ስሜት መገመት በጣም የሚያሳዝን ነው፤ ወደዝርዝር አልገባም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ሠይፉ ማሩ

“የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” ዶ/ር መረራ ጉዲና Dr. Merera Gudinas new bookዶ/ር መረራ ጉዲና “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች” በሚል አዲስ መጽሐፍ አስነብቦናል። በአንድ ጋዜጣ ላይ የዶክተር መረራ ከዩኒቨርሲቲ መሰናበት ያመጣው አንድ በጎ ጎን መሆኑን አንብቤያሁ። እኔም በዚህ እስማማለሁ። ብዙ የሀገራችን ፖለቲካኞች ጋዜጠኛ መቅረፀ ድምፅ ይዞ በሚጠይቃቸው ጥያቄ መልስ ከመስጠት የዘለለ ብዕርና ወረቀት አገናኝተው የሚያምኑበትን የፖለቲካ መስመር እና በግላቸው ያላቸውን ምልከታ ማካፈል ይቸግራቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተስፋዬ ገብረአብ

የህወሓትን የጓዳ ወግ ማወቅ አስቸጋሪ የነበረበት ዘመን እንደዋዛ አልፎአል። ዛሬ ቀዳዳቸው በዝቶ፤ ቴክኖሎጂውም አግዞ የፈፀሙት ብቻ ሳይሆን ያሰቡትም በቀላሉ ይገኛል። ዘመኑ የመረጃ ዘመን ነው። መረጃ ከሌለ ምንም ነገር የለም። ለችግሮች መፍትሄም አይገኝም። ወያኔ ዛሬ በአስር ሺዎች ኦሮሞዎችን በገፍ የሚያስረው ስለ ቄሮ በቂ መረጃ ስለሌለው መሆኑ ይታወቃል። ተቃዋሚ የፖለቲካ ተንታኞች ወይም የማህበራዊ ድረገፅ ፀሐፊዎች አንዳንድ ጊዜ አስቂኝ ስህተት ይሰራሉ። ማለትም ሳያውቁ ለወያኔ የሚጠቅም መረጃና ምክር ይፅፋሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ፊደል በላፕቶፕና በዲስክቶፕ ተቀርጾ አገልግሎት መስጠት ቻለ

The first Amharic, Geez laptop

Ethiopia Zare (ዓርብ ጥር 6 ቀን 2008 ዓ.ም. January 15, 2016)፡- ጋዜጠኛና ፀሐፊ ገነት አየለ የኢትዮጵያ ፊደላት እንደሌሎቹ የቋንቋ ፊደላት በላፕቶፕና በዴስክቶፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀርጸው ለተጠቃሚዎች አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ መቻላቸውን ከደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል። ይኸው የመጀመሪያው በኢትዮጵያ ፊደል የሚጽፍ ኮምፒዩተር በገበያ ላይ መዋሉ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በዮሐንስ ደሳለኝ (ጀርመን – ፍራንክፈርት)
በየዓመቱ ዲሰምበር 10 የሚከበረው የሰብዓዊ መብት ቀን ሐሙስ December 10,2015 በፍራንክፈርት የዋናው ባቡር ጣቢያ አካባቢ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ አመሸ። ከተለያዩ አገሮች የመጡ ተገን ጠያቂዎች የተገኙበት ይህ አከባበር ለየት ያለና የወቅቱ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚገባው ብርድ ያልበገረው ነበር።

 

frankfort 

ሙሉውን አስነብበኝ …

Students killed by federal police. የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተገደሉ፣ ተደበደቡአንተነህ መርዕድ

የመጀመሪያው የኬንያ ፕሬዝደንትና የነፃነት ታጋይ ጆሞ ኬንያታ ብዙ ጊዜ የሚጠቀስላቸው፣ ስለቅኝ ገዥዎች የተናገሩት እውነት ይህን ይመስል ነበር። “ሚሲዮኖች ወደ አፍሪካ ሲመጡ እነሱ መጽሐፍ ቅዱስ፤ እኛ ደግሞ መሬት ነበረን። ዐይናችንን ጨፍነን እንዴት እንደምንጸልይ አስተማሩን። ዐይናችንን ስንገልጠው ግን እነሱ መሬታችንን እኛ መጽሐፍ ቅዱሱን ታቅፈናል” አሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሩት አማኑኤል

ተደጋግሞ የሚነገር አንድ ጉዳይ አለ። ዴሞክራሲ ሒደት ነው፤ መልካም አስተዳደር በሒደት የሚመጣ ነገር ነው፤ የዴሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ሒደት ነው ወዘተ. ይባላል። ለጽሑፌ መነሻ የሆነኝ የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

• ችጋር ምንድን ነው? ሰፊ ቦታንና ብዙ ሕዝብን የሚሸፍን፣ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ፣ ምንም የሚላስ የሚቀመስ ጠፍቶ እንስሳት (ሰውንም ጨምሮ) ዕለት በዕለት የራሳቸውን አካል እስኪያልቅ ድረስ “እየበሉ” በመጨረሻም የሚሞቱበት ሁኔታ ነው፤ ረሀብ አካል ሲዳከም አካልን ለመገንባት የሚደረግ ጥሪ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Vacance ማስታወቂያጌቱ ኃይሉ

አቶ ዠ ደብዳቤ ጻፉ። 40 ዓመት ሙሉ መፈክር ሲጽፉ ኖረው፣ ኖረው፣ ኖረው አሁን አርቲስት ለመሆን የሚያበቃውን ዝግጅት የጨረሱ መስሎ ተሰማቸው። ሰሞኑን ለወጣው ማስታወቂያ “ብቁ ነኝ” ብለው አሰቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

PM Hailemariam Desalegn. ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝሩት አማኑኤል

ሕዝብ አዋቂ ነው። የፖለቲካ ሶሲዮሎጂስቷ ቴዳ ስኮፖል በሚያሳምን ሁኔታ እንደገለጸችውና በአገራችን በተግባር እንደሚታየው ሕዝብ ዝም ቢልም አፈናን ተቀብሏል ማለት አይደለም። በአፈና ውስጥ ያለ ሕዝብ ዝም ሲል እንድም ብናገርም ለውጥ አላመጣም ማለቱ ነው፤ አንድም ማኩረፉንና መከፋቱን መግለጹ ነው፤ አንድም የተመቻቸ ጊዜ እስኪያገኝ ድረስ አድብቶ መጠበቁ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Prof. Mesfin Woldemariam ፕ/ር መስፍን ወልደማርያምፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

በፌስቡክ የምንሰባሰበው ለመወያየት፣ አንዱ ከሌላው እንዲማር፣ መረጃዎችን በነጻነት እንድንለዋወጥ፣ ይህንን ሁሉ በማድረግ ራሳችንን ለማሻሻል፣ የእኛ መሻሻል እየተራባና እየተባዛ የአገርና የሕዝብ መሻሻል እንዲሆን፣ ከተቻለንም ከአገራችንና ከሕዝባችን አልፈን የምንታይ የዓለም አካል እንድንሆን መስሎኝ ነበር፤ ሳየው በዚያ መንገድ ላይ ያለንና ፌስቡክን ለበጎ ዓላማ እየተጠቀምንበት ያለን አይመስለኝም፤ ስለዚህ ወይ መታረም፣ አለዚያም በፌስቢክ ጊዜ ማጥፋቱን መተው ምርጫ ሊሆንብን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopia and the World Bank of Lies, Damned Lies and Statislies, by Prof. Almariamፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)

ጆን ሚልተን ገነትን ማጣት/Paradise Lost በሚለው መጽሀፋቸው “የቱም ዓይነት ቅጥፈት ቢሆን ዘለቄታዊነት የለውም የሰማይ ቁጣንም ይስባል።” በማለት ጽፈዋል። በእርግጥ ሚልተን ሊጨበጥ ሊዳሰስ ስለማይችለው ባዶ ምናብ ስለሚፈጥረው ስለሰይጣን እና ስለዕኩይ ምግባሩ ነበር የጻፉት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Prof. Getatchew Haile ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

መግቢያ፤

መጀመሪያ ለመግቢያ ያህል፥ “ዘመድ” የሚለውን ቃል እንዴትና ለምን እንደተጠቀምኩበት ላስረዳ። “ዘመድ” ማለት “ወገን” ማለት ነው። በእንግሊዝኛ “kin, family, tribe” ማለት ነው። በየሊቃቸው የሚመሩ የተለያዩ የመላእክት ሠራዊት “ዘመድ” ወይም “ነገድ” ነው የሚባሉት”–ዘመደ መላእክት፣ ነገደ መላእክት። ሌሎች ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው መጠሪያዎች “ቤት” (ቤተ አምሐራ)፣ “ጎሳ” (የጉጂ ጎሳ)፣ “ዘር” ናቸው። ዛሬ ደግሞ “ብሔረ ሰብ” የሚለው መጠሪያ ነግሧል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

በፈረንጆች ባህል እውቀት ሥልጣን ነው፤ እንዲያውም እውቀት ኃይል ነው ይላሉ፡፡

በኢትዮጵያ ባህል እውቀት ሥልጣን የለውም፤ እንዲያውም ሥልጣን እውቀት ይመስለናል፡፡

በ1951 ዓ.ም. በትግራይ ችጋርን በዓይኔ አይቻለሁ፤ በጆሮዬ ሰምቻለሁ፤ በአካሌ ቀምሼዋለሁ፤ ጠኔ ይዞኝ ተደግፌ ወደቤቴ ገብቻለሁ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነፃነት ዘለቀ

ውድ አንባቢያን ዛሬ ትንሽ ለየት ባለ ሁኔታ የልብ የልባችንን ነው የምንጫወተው። መደባበቅ ብሎ ነገር አይኖርም። ለምኑ ብለን? ለየትኛው ጊዜስ ብለን እንወሻሽ? “በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ” – መተዛዘብን ለዛሬ እንርሳት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopian Electric Power Corporation. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንጓድ ካፍትሌ ከአርባምንጭ

የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የደርግ ሥርዓት መገርሰሱን በማስመልከት ያስተላለፉትን መልዕክት ሰምቼ ነበር። መልዕክቱ ባጭሩ እንዲህ የሚል ነበር። “የድህነት ዘበኛ የነበረው ሥርዓት ስለተወገደ ከዚህ በኋላ ጦርነታችሁ ከዘበኛው ጋር ሳይሆን ቀጥታ ከጠላቱ (ድህነት) ጋር ነው።” በእርግጥ ደርግ ሥልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ ”ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር!” እያለ ሕዝቡ በድህነት እንዲማቅቅ አድርጓል። ከዚህ የተነሳ የሥርዓቱ መውደቅ ብዙዎችን በደስታ አስፈንጥዟል።

ሙሉውን አስነብበኝ …