ዩጋንዳ ያለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በሕይወት አለ?
ይህን ጥያቄ ለመመለስ ካምፓላን ማዳረስ ኣያስፈልግም።የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የሚሊኒየሙ አከባበር ግዜ ነበረ። ከዛ ተሽመደመደ።ጁላይ ኢለቨን ካምፖላ በአልሻባብ አጥፍቶ ጠፊዎች አሰቃቂ ፍንዳታ በደረሠ ግዜ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አለሁ ብሎ ሲሯሯጥ ታየ።ከዛ በኋላ ነበር ኖቬምበር አስራአራት ቀን ሁለት ሺ አስር የኢትዮጵያ ኮሚኒቲን
ኖቬምበር አስራአራት ከሚሊኒየሙ በፊትና በኋላ ኮሚኒቲው ያከናወናቸውን ተግባራት የሚያትት ዝርዝር የስራና የሂሣብ ሪፖርት ቀርቦ የነበረው።ለአንድ ዓመት ያህልም በወገኖች ድጋፍ ቢሮ እስከመክፈትና የአባልነት መታወቅያም ለማህበረሠቡ አዳርሶ ነበር።ኮሚኒቲው በወቅቱ ያሣየው ፍጥነት የወያኔን ወኪሎች አስግቶአቸው ይሁን ወይም በሌላ ምክንት ቢሮውም ተዘጋ ፣አመራሩም ላይገናኙ የተማማሉ መሠለ።ከወያኔ ቆንስላ ሃላፊዎች ጋርም ምስጢራዊ ስብሰባ የተወሰኑ የኮሚኒቲው አመራሮች አደረጉ የሚል ወሬ ተሠማ።ያኔ ኮሚኒቲው ተሸረሸረ።
ዩጋንዳ ያለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ መተዳደርያ ደንቡ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ አባል መሆን እንደሚችል ስለሚገልፅ የወያኔ ቆንስላ ሠራተኞች ካሣደዱዋቸው የፖለቲካ ስደተኞች ጋር የአንድ ኮሚኒቲ አባል ለመሆን ሲመዘገቡ ታይተዋል።በየትኛውም ስፍራ የፅዋ ማህበርም ቢሆን ወያኔዋቹ በይፉም ሆነ በህቡህ ያን ማህበር ካልተቀላቀሉ፣
አልያም ካላፈረሱና ወይም በነሡ ሣንባ የሚተነፍስ ተለጣፊ ካልመሠረቱ ሞታቸው ነው።
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በዩጋንዳ ዛሬ ስሙ ከመኖሩ ባሻገር ተሽመድምዶ ያለው ፖሊዮ ይዞት አይደለም።የኮሚኒቲው አመራሮች የያዙትን ቦታ ለመልቀቅ ፈቃደኝነት ያላቸውም አይመስልም።የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ከሚሊኒየሙ በፊትም ሆነ በኋላ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የሚያደርጋቸውን ተግባራት በቅርበት ያውቃል።እንደዜጋም አቅሙ የፈቀደውን በማድረግ በወያኔ ቆንስላ ጥቁር መዝገብ በጠላትነት ተፈርጆ እንደሚገኝ የካምፓላ ሰማይ የሚያውቀው ዕውነታ ነው።
ወያኔ የሚሊኒየሙን በዓል በሱ ፊታውራሪነት ካምፓላ ላይ ለማክበር ሲሯሯጥ በወቅቱ ወያኔ ንፁሀንን እስር ቤት አጉሮ በዓሉን በጋራ እንድናከብር ሊያግባባና ሊያስፈራራ ሲሞክር የታሠሩት ይፈቱ፣ብሔራዊ ዕርቅ ይደረግ ብለን የተወሰንን ወገኖች በመናገራችንና ሚሊኒየሙን ያለወያኔ ተሣትፎ በደመቀ ሁኔታ በማሣለፋችን ነበረ የወያኔ ጥርስ ውስጥ የገባነው።
ባለፉት ሦሥት አመታት የወያኔ ቆንስላ ዩጋንዳ ካምፖላ ላይ እውነተኛ የፖለቲካ ስደተኞችንን በማሳደድ፣በማሠለልና መፈናፈኛ በማሳጣት ሕብረተሠቡን በዘር እስከማደራጀት ሠርቷል።
ኮሚኒቲውን አሽመድምዷል።ከአመራሩ የተወሠኑትን ፖስፖርት በመስጠት ከስደተኛነት አላቋል።የወያኔ ቆንስላ ቤተኛ የሆኑም እንዳሉ የአደባባይ ሚስጥር ነው።
በርካታ ወገኖች ኮሚኒቲው ባይቀበርም እንደሞተ ያምናሉ።እንደገና ለማጠናከርም ቢሞከር አሁን ካሉት የአመራር አባላት መካከል ከወያኔ ጋር በግልፅም ይሁን ውስጥ ለውስጥ የሚሞዳሞዱትን ለይቶ ለማውጣት አስቸጋሪ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ።
ከሁለት ዓመት በፊት በሕጋዊው ሲኖዶስ የሚመራውን የካምፖላ መካነ ሠላም መድሐንያለም ቤተክርስትያን የወያኔ ቆንስላ ካህናትና፣ ዲያቆናት እንዲሁም መዘምራንን በስውር አደራጅቶ ያካሄደው ትርምስ በእውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ከከሸፈና የአመፁ መሪ የነበሩት የቀድሞ አስተዳዳሪ የስደተኛ እስታተሳቸውን ወርውረው በወያኔ ፖስፖርት የአምስት ኪሎውን ቤተክህነት ከተቀላቀሉ ወዲህ ነገሮች እየጠሩ መጥተዎል።
ካምፖላ ላይ የፖለቲካ ስደተኛ መታወቅያ በደረታቸው ፣የወያኔ አክቲቭ ፓስፖርት ትራሳቸው ስር ሸጉጠው ትክክለኛ ስደተኞችን የሚሠልሉና ለአደጋ የሚያጋልጡትን ሆድ አደሮች ለማጋለጥ በዩጋንዳ የሚኖሩ ስደተኞች ለህልውናቸው ሲሉ በህብረት ሊቆሙ ይገባል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጥቂት የፖለቲካ ስደተኞች ስደተኛውን ብቻ ያቀፈ የስደተኞች ማህበር ለመመስረት እንቅስቃሴ እየተከናወነ ሲሆን ለስደተኛው መብት መከበር የሚሠራ ከማናቸውም የፖለቲካ ሃይሎች ተፅዕኖ ነፃ የሆነ ማህበር ለመመስረት የበኩሌን እገዛ ሳደርግ ብቆይም ለደህንነቴ ስጋት የሚፈጥሩ ሁኔታዎች በመፈጠራቸው ከማናቸውም ማህበረሠቡን ከሚመለከቱ ጉዳዮችራሴን አግልዬ እንደምገኝ ለመጠቆም እወዳለሁ።በተቻለ አቅም ስደተኛው የራሱን ማህበር ከወያኔ ሠርጎ ገቦች እንዲጠብቅ አሳስባለሁ።
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ እስከዛሬ የታመሙትን ወገን በማስተባበር ለማሣከም ያደረገው መልካም ተግባር ፣
የሟች ወገኖችን አስከሬን ከቤተሠብ ጋር መክሮ ለሐገራቸው አፈር እንዲበቁ በመስራቱ፣ምስኪን ስደተኞች ሲሞቱ በመቅበር የሠራውን ስራ በመዘከር ወደ ወያኔ ጉያ የተሸጎጠውና ፖራላይዝዱ ኮሚኒቲ እኔም ልክ የዛሬ ሦሥት አመት በተከናወነው የማሟያ ምርጫ የቦርድ አባል ሆኜ እስከዛሬ መቆየቴን እየጠቆምኩ በመላ ዓለም የምትገኙ ኮሚኒቲዎች ልምዳችሁን እንድታካፍሉኝ እንደ አንድ ዩጋንዳ ላይ በሚኖር ሐገር አልባ ስደተኛ በአክብሮት እጠይቃለሁ።
ተጨማሪ መረጃ ለሚፈልጉ ሁሉ ፀሀፊው በንፁህ ህሊና እውነቱን ብቻ ለመግለፅ ህሊናው ዝግጁ መሆኑን ይጠቁማል።
ጋዜጠኛ ደረጀ በጋሻው
ከኮሚኒቲው ቦርድ አባላት አንዱ

ድምጻችንን ከማሰማት አንቆጠብ..የኢትዮጵያ መንግስት ማላገጡን በሳዑዲም ዜጋችን መሞቱ ቀጥሏል..
በግሩም ተ/ሀይማኖት
ሪያድ ውስጥ ወገኖቻችን ላይ ዛሬም ጥቃት ተፈጸመ፡፡ ብጥብጥ ተፈጥሯል እባክህ በዚህ ስልክ ቁጥር ደውልልኝ ብሎ ቁጥር አስቀምጦልኝ አገኘሁ፡፡ 9665533…አደረኩና ደወልኩ፡፡ ከወዲያ ማዶ ምላሽ ስጠብቅ ኮለል ያለ የመደፈር ጥቃት የአትንኩኝ ባይነት ግርማ ሞገስ ባለው ድምጽ ‹‹ሀሎ!›› ተባልኩ፡፡ ሰላምታዬን አደረስኩና ብጥብጡ ምንድን ነው አልኩት፡፡ ‹‹..ይሄውልህ ግሩሜ በሪያድ መንፉሃ አውራ መንገዶች ሃገራችን ውሰዱን ብለን እቃችንን ሸጠን ወጥተናል፡፡ አምባሳደሩ መጣና ምንም ችግር የለም ወደ ሀገር ትገባላችሁ ብሎ ሄደ፡፡ ዛሬ ከቀትር በኋላ ወደ ብጥብት ተነሳ….(ዛሬ የሚለው ትላንት ማታ ስላውራሁት ነው)
Image
(እኔ እሱን ላቋርጥና የምለው ስላለኝ ቅንፌን ከፍቻለሁ፡፡ አምባሳደሩ በሉ ተብለው የታዘዙትን ነው ያሉት፡፡ ያ-ሳይሆን የሚያሳዝነው ቤታቸውን ጥለው ወጥተው አደባባይ መሆናቸውን እያዩ አላግጤ ንግግራቸውን ተናገው እና በአፍ ደልለው መሄዳቸውን ሌላ ምንጮቼ ገልጸውልኛል፡፡ ዜጋዬን..ያለው መንግስትም 25 ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገር መመለሱን በዜና እወጃው አሰውቋል፡፡ የተመለሱት ሰዎችን ምንነት በዜናው ላይ ከተደረገላቸው ቃለ-ምልልስ ማወቅ ይቻላል፡፡ የኢህአዴግ ካድሬዎች ዘውትር የሚያንቆረቁሩት ስልቹ ቃላትን ሲደግሙት ለሰማ ‹‹..አሀ! የእንትን ልማት ማህበር አባል…›› ብሎ መጥራቱ አይቀሬ ነው፡፡ ይህን ጥርጣሬዬን ይዤ ለአንዱ እንዴት ነው ለመግባት ያለው ሂደት አልኩት፡፡ ‹‹.1000 ሪያል ካለህ በአፋጣኝ ትጨርሳለህ….›› በስመአብ የደነገጥኩትን አትጠይቁኝ፡፡…እኔ በአረቡ አለም ያሉት ኤምባሲዎች ኮሙኒቲ ካልተመዘገብክ የአማራ ልማት ማህበር፣ የትግራይ፣ የኦሮሞ፣የጉራጌ..ምናምን አባል ካሆናችሁ እያሉ አገልግሎት ስለማጓተታቸው ስጠይቀው ይባስ ለፈጣን አገልግሎት 1000 ሪያል ጉቦ መባሉ እንዴት አያስደነግጠኝ? አሁን ለደወልኩለት እና እያናገርኩት ላለው ልጅም ይሄን ጥያቄ አቀረብኩለት…ወደ ዘገባዬ ተመለስኩ፡፡)

ወደ ሀገራችን መልሱን የሚለው ጥያቄያችንን ለማደናቀፍ ፖሊስ ሸባቦቹን ይዞ መጣ፡፡ (ሸባብ ማለት ወጣት ነው፡፡ ፖሊስ እነዚህን የመንደር ጎረምሶች ይዞ በመዞር ነው ዜጋዎቻችን ላይ ጥቃት የሚፈጽመው) ‹‹ለምንድነው እንደዚህ የምትሆኑት ሂዱ ብላችኋል መሄድ እንፈልጋለን ብለን ነው ቤት ንብረታችንን ጥለን የመጣነው ብለን ለማረጋጋት ሞከርን፡፡ በፊት ሲመጡ አሰር (የዘጠን ሰዓት ስግደት) እየሰገድን ነበር፡፡ በተፈጠረው ግርግር ሲያሰግደን የነበረውን ልጅ በጩቤ ወጉት፡፡ ከዛ ከፍተኛ ግርግር ነበር፡፡ ወደ ታፋው አካባቢ ነው የወጉት፡፡ እንግዲህ ኤምባሲው ምንድን ነው ስራው…(ወዳጄ የኤንባሲው ስራ እናንተን ማስደብደብ እና ከሳዑዲ የሚፈልጉትን ማግኘት) እንዴት ነው በዚህ ጭንቅ ሰዓት ኤምባሲው የሚያስከፍላችሁ ነገር አለ እንዴ? አልኩና ጥያቄ በስልክ ወረወርኩ፡፡ ቀበል አለና አይ! ጉዳዩን ቶሎ እንዲጨርሱልህ ላለመጉላላት ከፈለክ 1000 ሪያል የይጠይቁሀል….(ጉቦ መሆኑ ነው ወገኖቼ በዚህ የጭንቅ ሰዓት እነዚህ የኤምባሲ ሰራተኞች ጉቦ ይበላሉ…..የወገናቸውን ደም ይጠጣሉ፡፡ ኧረ!!!!…እባካችሁ እንተዛዘን….) ሌላው አሁንም የገዚው ፓርቲ አሸርጋጆች በድርጅታዊ አወቃቀር ሳይሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊን እንደ ዜጋ በማየት ማስተናገድ እንጂ በዚህ ሰዓት አባል የሆና ያልሆነ እያላችሁ እና ከዜጋ ህይወት ገንዘብ አስበልጣችሁ ኪሳችሁን ማደለብ ስታስቡ አሁንም ወገኖቻቻንን ለእልቂት አትዳርጉ፡፡

በዙሪያው የምንገኝ የመንፉሃን ግጭት ተከትሎ በተሰጠው ወደ ሃገር የመግባት እድል ለመጠቀም በቡዙ ሺህ የሚቆጥሩ ኢትዮጵያዊ መጠለያዎችን እያጨናነቀ ነው። በመካ ያለው ከባድ ሁኔታ ቢሆንም ያለው የባሰ ያስገረመው በሁለት ኢትዮጵዊያን መካከል በተፈጠረ ግጭት አንደኛው አንዱን ደጋግሞ በጩቤ በመውጋቱ አንደኛው ኢትዮጵያው ለህልፈተ ህይወት በቅቷል፡፡ ይህ ወገን ወገኑን የሚጎዳበት ሂደት በእንደዚህ አይነት አጣብቂኝ የስቃይ ህይወት ውስጥ ሆኖም መቀጠሉ ያሳዝናል፡፡

አሁንም በሽዎች የሚቆጠሩ ወደ መጠለያ ለመግባት እየጎረፉ ነው ። በመጠለያው ትናነት አንዲት የ9 ወር እርጉዝ ሞታ ተቀብራለች ። በመጠለያው የምግብና የመጥ እጠረቱ ደግሞ ኢትዮጰያውያኑነ አጥር ሰብረው እንዲወጡ እያስገደደ ነው ተብሏል። በሳዑዲ ያለው ሁኔታ መንግስት ቀዝቅዟል በማለት በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ በኩል ቢናገርም ቢገልጽም፡፡ሁኔታው የከፋ እና ፖሊስ አሁንም ወጣቶችን ይዞ በየቦታው እየዞረ ማስደብደቡን እንደቀጠለ መሆኑን ሳዑዲያ ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ይናገራሉ፡፡ በጣም አሳፋሪ መረጃ እየሰጡ ያሉት የመንግስት ተቋማት ዛሬም ይህንኑ እየደገሙት መሆኑ አሳዛኝ ኢ-ሰብአዊነት እየፈጽሙ መሆኑን ልብ ሊባል ይገባዋል፡፡

ከከተማው አርቀው ያስቀመጧቸው ካምፐ ውስጥ የምግብ እና ውሀ እጥረት መኖሩን አንድ መረጃ ሲያቀብለኝ የከረመ ወዳጄ አድርሶኛል፡፡ ሴቶች፣ ህጸናት፣.የስኳር በሽተኞች፣ አሉ፡፡ ካምፕ ውስጥ አስገብተው ከቀን አንዴ ብቻ ነበር እህል የሚሰጠን፡፡ አሁን ድንገት ሁለት ነው ማለት ከተቻለ ሁልቴ አንዴ የምትበላውን የሚያህል ያበሉሀል፡፡ የመጠለያው ሁኔታ እጅግ አስከፊ መሆኑን ነግሮኛል፡፡ በተጨማሪም በእስር እና ከእስር ወደ እስር ቤት መቀየር ላይ አስካሁን ብቻ 5 ሰዎች መሞታቸውን ይሄው የአይን እማኝ የሆነው የመረጃ ምንጬ ገልጾልኛል፡፡ በግሩም ተ/ሀይማኖት

ሰኞ ኖቨምበር 18 በ ዋሽንግተን ዲሲ በሚደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ለመሳተፍ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ በጋራ ለመሄድ እንዲቻል የሚክተሉት ግለሰቦች የማስተባበር ህላፊነት የተሰተጣቸው ስለሆነ የሚከተሉትን ስልኮች በመደወል ክቅዳሜ ክሰአት በፊት ቦታ እንድትይዙ አዘጋጅ ግብረሃይሉ ይጠይቃል። 1.እዮብ 617 513 7514 2.ካሳይ 857 928 8677 3.አበራ 617 304 2584 4.አብይ 617 953 7126 5.ዮናስ 617 447 8007

ህዳር ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሴቶች ካምፕ ያለው ሁኔታ እጅግ አስከፊ መሆኑን ኢትዮጵያውያን ሴቶች ይነጋራሉ። ቀን በጸሀይ ማታ ደግሞ በብርድ እንድናሳልፍ እየተገደድን ነው የምትለው ሌላዋ እስረኛ ሳሚራ፣ ህጻናት እና እናቶች በምግብ እጦት እየተጎዱ ለበሽታም እየተዳረጉ ነው ትላለች። ባለፉት አራት ቀናት የወለዱ እናቶች መኖራቸውን የምትገልጸው ሳሚራ፣ የሳውዲ ፖሊሶች ወላዶችን የት እንደወሰዱዋቸው እንደማታውቅ ገልጻለች። ሀብታም የተባለቸውም …

ህዳር ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሆነው ወጣት ብርሀኑ ተክለያሬድ ለኢሳት እንደገለጸው ምንም እንኳ የአዲስ አበባ መስተዳድር ፈቃድ ክፍል ፣ የሰላማዊ ሰልፍ መጠየቂያ ደብዳቤውን እንደማይቀበል ቢገልጽም፣ ፓርቲው ተቃውሞውን በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ለማድረግ ወስኖ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግስት ተባብሮ ተቃውሞ ማዘጋጀት ሲገባው፣ ፓርቲው እንዳያዘጋጅ መከልከሉ እንዳስገረመው ወጣት አሬድ …

ህዳር ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጄኔራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ፣ የኢትዮጵያ ሽግግር መንግስት ካንውነስል፣ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ማህበር በደቡብ አፍሪካ፣ ሂውማን ራይተስ ሊግ በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም መድረክ ድርጊቱን የሚያወግዙ መግለጫዎችን ለኢሳት ልከዋል።  

የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ኣስመልክቶ ላለፉት 9 እና 10 ዓመታት በተለይ ከመንግስት በኩል የሚሰማው እጥፍ ድርብ እድገት ወይንም በእንግሊዝኛው Double digit grorth ያውም ከ 11 በመቶ ያላነሰ ወይንም ከዚያ በላይ መሆኑ ይታወቃል። ተቃዋሚዎች በዚያች ኣገር ያንን ያህል እድገት ያውም በኢህኣዲግ የእጅ ኣዙር እዝ ኢኮኖሚ የማይታሰብ ነው እያሉ

የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ኣስመልክቶ ላለፉት 9 እና 10 ዓመታት በተለይ ከመንግስት በኩል የሚሰማው እጥፍ ድርብ እድገት ወይንም በእንግሊዝኛው «ዳብል ዲጂት ግሮውዝ» ያውም ከ 11 በመቶ ያላነሰ ወይንም ከዚያ በላይ መሆኑ ይታወቃል። ተቃዋሚዎች በዚያች ኣገር ያንን ያህል እድገት ያውም በኢህኣዲግ የእጅ ኣዙር እዝ ኢኮኖሚ የማይታሰብ ነው እያሉ

ሳዉድ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ዛሬም የድረሱልን ድምጻቸዉን እያሰሙ ነዉ። የሀገሪቱ መንግስት ላለፉት ወራት ሰጥቶ የቆየዉ የምህረት ቀነገደብ ካለፈ ወዲህ በዜጎችና የጸጥታ ኃይሎች ይፈጸምብናል የሚሉት በደልም ገደብ ማለፉን ይናገራሉ።

የሶማሊያዋ ራስ ገዝ ግዛት ፑንትላንድን በሳምንቱ መጨረሻ በመታዉ ኃይለኛ ማዕበል የሞቱት ሰዎች ቁጥር 300 መቶ ሊደርስ ይችላል ሲል መንግስት ስጋቱን እየገለጸ ነዉ። መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የደነገገ ሲሆን በማዕበሉ ለተጎዱ አካባቢዎችም ዓለም ዓቀፍ ርዳታ ጠይቋል።

ከዲያቆን ዓባይነህ ካሤ


ኢትዮጵያውያን ደማቸው የዐረብን አስፋልት አቀለመው፡፡ ባንዲራውን በራሱ ላይ ሸብ ያደረገው የእማማዬ ልጅ የእኔ ጀግና ማንነቱን እየተናገረ በአናቱ ላይ የወረደውን የድንጋዩን ናዳ በሀገሩ ፍቅር ተቋቁሞ በክብር አሸለበ፡፡ ለእርሱ ከዚህ በላይ ሌላ ድል አልነበረምና፡፡ ድንጋዩስ እርሱን አሳርፎታል፡፡ ነፍሱን ይማርልን እንጂ! ባንዲራችን ግን እንደተመታች እንደታመመች ናት፡፡ እውን ይኽ የሆነው በእኛ ላይ ነው? 


ይህቺ ባንዲራ እኮ ጨርቅ አይደለችም፡፡ ያ በሳኡዲ መሬት ተወግሮ የሞተው ወንድሜ የኮራባት በሞቱ ጊዜ የለበሳት የክብሩ፣ የማንነቱ መገለጫ እንጂ፡፡ ማንም ባይደርስለት ባንዲራው ነበረችለት፡፡ በእርሷ ተጽናና፡፡ ሞተ አልለውም መሰከረ እንጂ፡፡ ባንዲራ ለብሶ መከራን መጋፈጥ የሰማእታት ወግ ነው፡፡ 

ዳግማዊ ሆሎኮስት በኢትዮጵያውያን ላይ? እንዴት እንዴት? ደግሞ በ ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን፡፡ የሰውን ሕይወት የሚያስገብር ምን ጥፋት ተገኝቶ ነው ወይስ የሟርት መስዋእታቸው እኛ ነን፡፡ “ከሕግ አስከባሪው ፖሊስ” እስከ ዱርየው የእኅቶቻችን ክቡር ሰውነት እንደ ውሻ ሲጎተት ከማየት የሚዘገንን አረመኔነት ምን አለ? ይህ እኮ ንቀት ነው፡፡ ይህ እኮ ድፍረት ነው፡፡ ይህ እኮ የሀገርን ሉዐላዊነት መድፈር ነው፡፡ 


ምንም ዓይነት ወንጀል የሠራ ሰው የሚዳኝበት ሥርዓት አለው፡፡ ስንቶች አእምሯቸውን ስተው ተመለሱ…ዝም አልን፡፡ ስንቶች እንደ ከብት ከግመሎቻቸው እጅግ በተዋረደ ሁኔታ እንደ ሸቀጥ ተጠፍረው ተላኩልን…ያኔም ዝም አልን፡፡ ስንቶች ከፎቅ ራሳቸውን እየወረወሩ ተፈጠፈጡ… አሁንም ዝም አልን፡፡ ዛሬ ደግሞ በዚህ መጡ…ዝም እንዳልን እንቀጥል ይሆን? ስጋቴ ይህ ነው፡፡ አስኪ በማነህ ማነህ የተረፉትን እንድረስላቸው፡፡

ለመጽሓፋቸው (ኢትዮጵያን አትንኩ ለሚለው) ያልተገዙ በቀላሉ ይተውናል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው፡፡ ኢትዮጵያ እኮ ወንዝ እና ተራራዋን ማለት አይደለም፡፡ ከምንም በላይ ሕዝቧ እንጂ…ቀጥሎ ወንዝ እና ተራራዋ ሜዳ እና ሸለቆዋ…ወዘተ ይከተላሉ፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን ለማድረግ ብንተጋ፤

፩. በየቤቱ የተዘጋባቸውን እና በእንግልት ብዛት የሚቃስቱትን ፈልጎ ማግኘት እና አሰቸኳይ እርዳታ ማድረግ፣ መመለሻቸውን ማበጃጀት፣

፪. በየፖሊስ ጣቢያው ወይንም ወኅኒው የታሰሩትን ፈልጎ ማግኘት እና ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ከሚመለከታቸው ጋር መነጋገር፣

፫. የተቃውሞ ድምጻችንን በሕጋዊ መንገድ በያለንበት ማሰማት፣

፬. ችግር የደረሰባቸው፣ ሰብአዊ መብቶቻቸው የተጣሱባቸው ወገኖቻችን ከሳኡዲ ሁሉ ካሣ የሚያገኙበትን ማፈላለግ፣

፭. ከተመለሱም በኋላ የሚያገግሙበትን እና መደበኛ ኑሮ የሚገፉበትን ሁኔታዎች ማመቻቸት፡፡

፮. እነዚህን እና ሌሎችንም ጉዳዮች የሚፈጽም ብሔራዊ ኮሚቴ ማቋቋም፡፡

ለዚህ አልተፈጠርንምና፡፡

እንደ ኢህአዴግ ፈሪ ፓርቲ ከወደየት አለ? ጌታቸው ሺፈራው

beዚህ ጽሁፍ መግለጽ የምፈለግው የኢህአዴግን መጠነሰፊ ፍርሃት ያሳያሉ ያልኳቸውንጥቂት ምሳሌዎች ነው፡፡ እስካሁን እንደ ኢህአዴግ ፈሪ ፓርቲ አጋጥሞኝ ስለማያውቅም እንደ ኢህአዴግ ፈሪ ድርጅት ከወደየት አለ? ብሎ መጠየቁ አግባብ መስሎ ታይቶኛል፡፡ ፈሪው ድርጅት ‹‹የለም ከእኛ በላይ ፈሪ ድርጅቶች እዚህ እዚህ…አገር ይገኛሉ›› የማለት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ እንዲያውም እስካሁን የነበረበትን ከፍርሃት የመነጨ ድብቅነት በጥቂቱም ቢሆን እንደቀነሰ እንረዳለታለን፡፡ በድፍኑ ‹‹አይ እኛ ፈርተን አናውቅም!›› ቢል ግን ያው የተለመደ ስለሆነ የሚያምነው አያገኝም፡፡ ደግሞስ እየፈሩ ‹‹አልፈራንም›› ማለት ምን ማለት ነው? ‹‹አልፈራንምንስ ምን አመጣው? ኢህአዴግ የሚፈራውን ከመዘርዘር ይልቅ ራሱ የማይፈራቸው ነገሮች ካሉ ቢነግረን የተሻለ ነበር፡፡ እኔ ግን ከሚፈሯቸው ነገሮች መካከል በጣም ጥቂቶቹን ብቻ በመጥቀስ የፍርሃቱን መጠን ለማሰየት እሞክራለሁ፡፡ ህገ መንግስቱን ለብሄር ብሄረሰቦች መብት መከታ ነው የሚባለው የወቅቱ ህገ መንግስት የአቶ መለስና ለንጮ ለታ የፖለቲካ ማህተም ያረፈበት እንደሆነ ይነገርለታል፡፡ ይህ ህገ መንግስት እንደ አንቀጽ 39ን ያሉትን ጨምሮ ስለ የመሬት ፖሊሲ፣ አንድነትና ሌሎች ጉዳዮች ያለው ህጸጽ እንዳለ ሆኖ ከነ ድክመቱም ቢሆን ቢተገበር አሁን ካለንበት ብልሹ ፖለቲካ የተሻለ ስርዓት ሊመሰርት እንደሚችል ይታመንበታል፡፡ በተለይ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የአመለካከትና ሌሎች ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶችን ከዳር ዳር ከማጨቅ ውጭ ተግባራዊ ሲሆኑ አይታዩም፡፡

Image

ከተግባራዊነቱ ይልቅ ለይስሙላህነቱ እንዲውል ተደርጓል፡፡ ይህም የሆነው ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈሩት አብዛኛዎቹ መርሆች ተግባራዊ ቢሆኑ የገዥውን ፓርቲ ስልጣን የሚያሳጡ መስለው ስለሚሰሙት ነው፡፡ እናም ኢህአዴግ ‹‹ባለ ራዕዩ›› መሪ በበላይነት መርጠው ያጸደቁትን ህገ መንግስቱንም ቢሆን ለመተግበር ይፈራዋል፡፡ ስለሆነም በተቻለ መጠን ህገ መንግስቱ ላይ ያሉት መርሆች ተግባራዊ የማይሆኑበትን አጋጣሚ ሁሉ ይጠቀማል፡፡ ለዚህ አተገባበሩ የዳኝነት ሰርዓቱን ጨምሮ በጉዳዩ ተያያዥነት ያላቸውን አካላት የገዥውን ፖሊሲ የሚያቀነቅኑ እንዲሆኑ ጥሯል፡፡ ይህ ግን በቂ አልነበረም፡፡ በተለይ በ1997 በኋላ ኢህአዴግ እንደ አንዳች ነገር የሚፈራቸው ወሳኝ የህገ መንግስቱ መርሆች በጸረ ህገ መንግስት አዋጆች ታጥረው ተቀምጠዋል፡፡ የጸረ ሽብር፣ የሶቪክ ማህበራት፣ የፓርቲዎች የስነ ምግባር፣ የሚዲያ…..አዋጆች ህዝብን ብቻ ሳይሆን ህገ መንግስቱን አሽገው ለህዝብ እንዳይቆም ያደረጉ አዋጆች ናቸው፡፡ ተወዳዳሪ ፓርቲን ኢህአዴግ መድብለ ፓርቲን መርህን እቀበላለሁ እያለ የጠንካራ ፓርቲዎችን መኖር ግን በእጅጉ ይፈራል፡፡ ለዚህም ሲባል ከፓርቲዎች ጋር አብሮ ከመስራት ይልቅ ተገንጣዮችን በመፈልፈል የኢትዮጵያን ፓርቲዎች ከ80 በላይ አድርሷቸዋል፡፡ በእርግጥ ይህ የጠንካራ ፓርቲ ‹‹ፎብያ›› የጀመረው ህገ መንግስቱ ላይ ‹‹የበድብለ ፓርቲ›› በስምም ቢሆን ከተፈቀደ በኋላ አይደለም፡፡ ህወሓት በዱር እያለም ፓርቲዎችን ከዚህም በላይ ይፈራቸው እንደነበር ታሪኩ ያስረዳል፡፡ መጀመሪያ አካባቢ ኢህአፓ ከህወሓት ጎን ለጎን አብሮ ይንቀሳቀስ ነበር፡፡ ይሁንና የኢህአፓ ህብረ ብሄርነት ህወሓት የቆመለትን የመገንጠል ፖሊሲ አደጋ ላይ በመጣሉ ህወሓት ‹‹ከትግራይ መሬት ውጡልን ይህ የትግራይ ህዝብ መሬት ነው›› ብሎ አባረረው፡፡ የትግራይ አርነት ግንባርን (TLF)ንም የትግራይ ህዝብ ከአንድ በላይ ፖለቲካ ፓርቲ መሸከም አይችልም ብሎ አጥፍቶታል፡፡ እንዲያውም የትግራይ አርነት ግንባር አባላት ከህወሓት ጋር ለመደራደር ከተስማሙ በኋላ በተኙበት በህወሓት መጨፍጨፋቸውንና ይህን ዘግናኝ የጭፍጨፋ ሂደት አንዳንድ የህወሓት አባላት ለህዝብ ይፋ አድርገዋል፡፡ እንደራደር ብሎ የመጡትን ፖለቲከኞች መጨፍጨፍ መቼም ጀግንነት፣ ድፍረት ሊሆን አይችል፡፡ ኢህአዴግም እየተጠቀመበት የሚገኘው ይህን የህወሓትን የፍርሃት ልምድ ነው፡፡ ገና ስልጣን እንደያዘ ጠንካራ ከሚባሉት ኦነግ፣ ኦብነግና ሌሎች የብሄር ድርጅቶችን ጋር ከጥርጣሬም አልፎ አለመግባባት ውስጥ ገባ፡፡ በምትካቸው ደግሞ እንደ ኦህዴድ፣ ሶዴፓ ያሉ ደካማ ፓርቲዎችን ተገን ማድረግ ጀመረ፡፡ ለጠንካራ ፓርቲዎች በርካታ ደካማ ተገን ፓርቲዎችን የሚፈጥረው ኢህአዴግ ከመቼውም በላይ ስለፈራ 80 ያህል ደካማ ፓርቲዎች አገሪቱን ተፍልፍለዋል፡፡ ኢህአዴግ ተቃዋሚዎቹን ብቻ ሳይሆን አብረውት እየሰሩ የሚገኙትንም ቢሆን ‹‹በአጋር ፓርቲነት›› ስም ብቻ ፖለቲካውን ከእርቀት እንዲመለከቱ እያደረገ ነው፡፡ በአገሪቱ የረባ የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን እነዚህ ፓርቲዎች ያፈነግጡብኛልበማለትም የህወሓት/ኢህአዴግን አማካሪዎች በተቆጣጠሪነት ከማስቀመጥ ጀምሮ መረዎቻቸውን በተለያየ መንገድ ማግለል የተለመደ የፖለቲካው እቃ እቃ ጨዋታ ሆኗል፡፡ የሶማሊ፣ ጋንቤላና ቤንሻንጉልን ህዝቦች ስም ‹‹አጋር›› የሆኑት እነዚህ ፓርቲዎች መሪዎቻቸው ከአዲስ አበባ በተላከ ትዕዛዝ በተደጋጋሚ ገለል የሚደረጉት ያፈነግጡብኛል ብሎ ስለሚፈራቸው ነው፡፡ የአገር አንድነትን ኢህአዴግ የአንድነት ፍርሃት የሚጀምረው እስካሁንም ድረስ የትግራይን ህዝብ ነጻ ለማውጣት የቆምኩ ነኝ የሚለውን ስሙን ለመቀየር ከሚፈራው ህወሓት ነው፡፡ የህወሓት የተገንጣይ ስምም ቢሆን እስካሁን የማይቀየረው አንድነት ይቅርና ፌደራሊዝሙም ላይ ፍራቻ ሳላለው ይመስላል፡፡ ከዚህ ውጭ የትኛውም አንድነትን የሚወክል ወይንም የሚያንጸባርቅ ነገር ለህወሓት/ኢሀአዴግ ያስበረግገዋል፡፡ ልክ እንደ ህወሓት/ ኢህአዴግ ሁሉ የኢትዮጵያ አንድነትን የሚጠላው ሻዕቢያ መጀመሪያ የተረባረበው የአንድነት ዋነኛው መገለጫ የሆነው ሰንደቅ አላማው ላይ ነበር፡፡ ሻዕቢያ ባልታጣ መቋጠሪያ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ዋነኛው የዱቄት መቋጠሪያው አድርጎ ተጠቅሞበታል፡፡ በለስ (ቁልቋል) ሳይቀር የሚሸመጥጡት በኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ እንደነበር ይነገራል፡፡ ህወሓት በተለይ መጀመሪያ አካባቢ ትጥቅም ሆነ ስንቅ (ዱቄት) ይቀበል የነበረው ከሻዕቢያ ነውና ከሻዕቢያ የተለየ ተግባር ሊፈጽም እንደማይችል መገመት ቀላል ነው፡፡ አቶ መለስ ስልጣን ከያዙ በኋላ ስንደቅ አላማውን ጨርቅ ያሉት ከሻዕቢያ በወረሱት የአንድነት ፍርሃት መሆኑን እንረዳለን፡፡ ሁለቱም ድርጅቶች ይህ በደል የፈጸሙት ከሰንደቅ አላማው በስተጀርባ ያለውን አንድነት በእጅጉ ስለሚፈሩት ነው፡፡ ኢህአዴግ ለዚህ የረዥም ጊዜ ፍርሃት መሃል ላይ ያስቀመጠው ኮከብም ፍርሃቱን ሊያስወግድለት አይቻለም፡፡ አቶ መለስ ከመሞታቸው ከወራት ቀደም ብለው ሰንደቅ አላማውን የዘቀዘቁት አሁን ባለው ቅርጹም ቢሆን ስለሚፈሩት ይመስለኛል፡፡ ዛሬም ቢሆን ኢህአዴግ ራሱ መጥኖ በጠራው ጉዳይ ካልሆነ በስተቀርሰ ህዝብ በስፋት ባለኮከቡን ሰንደቅ አላማ በክብር ሲያነሳም ብርክ ይይዘዋል፡፡ አማራጭ ሚዲያን ኢትዮጵያ በሚዲያ ወደኋላ ከቀሩት አገራት መካከል የመጀመሪያዋ ናት፡፡ ለ90 ሚሊዮን ህዝብ ያለን አንድ ፕሮፖጋንዳ የሚሰራጭበት ቴሊቪዝን ጣቢያ ብቻ ነው፡፡ በአንጻሩ 6 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ላኦስ፣ ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ያላት ጃማይካ፣ አንድ ሚሊዮን ህዝብ ያላት ትሪንዳድና ቴቪጎ እያንዳንዳቸው የግልን ጨምሮ ባለ ሰባት ጣቢያዎች ናቸው፡፡ 400 ሺህ ህዝብ ያላት ማልታ 8፣ 36 ሺህ ህዝብ ያላት ሞናኮ 5 ጣቢያዎች ለህዝባቸው አማራጭ መረጃ ያስተላልፋሉ፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር የሚነጻጸር ህዝብ ያላቸው አገራት ደግሞ በርካታ ጣቢያዎች ባለቤቶች ሆነዋል፡፡ ለአብነት ያህል ከኢትዮጵያ ጋር በአባይ በኩል የምትተሳሰረው ግብጽ 98 ያህል ጣቢያዎች ባለቤት ነች፡፡ ከኢትዮጵያ ህዝብ ከግማሽ ያነሰ ህዝብ ያላት ጎረቤት ኬንያ እንዲሁም 34 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ዩጋንዳ እያንዳንዳቸው 8 ጣቢያ ያላቸው ሲሆን አብዛኛዎቹ የግል ሚዲያዎች ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ሚዲያ ይህን ያህል ከአገሪቱ ታሪክም ይሁን ህዝብ ጋር የሚቃረን የሆነው ኢህአዴግ በእጅጉ ስለሚፈራው ነው፡፡ ሚዲያ ህዝብን ያነቃል፣ ሙስናንና ሚስጥርን ያጋልጣል፣ አንድነትን ያጠናክራል፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማህበራት አማራጭ ሀሰብ ህዝብ ዘንድ እንዲደርስ ያደርጋል፡፡ ይህ የነቃ ማህበረሰብ የሚፈጥረው ሚዲያ ደግሞ ለአንድ ፓርቲና ግለሰብ የበላይነት ጸር ነው፡፡ ለህዝብ ልዓላዊነት እንጅ ለ‹‹አውራ ፓርቲ›› አያመችም፡፡ ስለሆነም ኢህአዴግን ከምንም በላይ ያስፈራዋል፡፡ ለዚህም ነው 90 ሚሊዮን ህዝብ አሰልች ፕሮፖጋንዳ በሚነዙ የመንግስት (ፓርቲ ሚዲያዎች) ብቻ የተወሰነው፡፡ በፍርሃቱ ምክንያትም የህትመት ሚዲያው አሳሩን ሊበላ የግድ ሆኖበታል፡፡ ህገ መንግስቱም ሆነ አዋጁ አማራጭ (የግል) ሚዲያን አይከለክልም፡፡ እንዲያውም በአዋጁ የብሮድካስት ሚዲያም በግል እንደሚፈቀድ ሁሉ አስቀምጧል፡፡ ይህ በሆነበት ግን አንድም የግል ቴሊቪዥን ጣቢያ የለንም፡፡ ሚዲያ ህዝብን እንደሚያነቃ የሚያውቀውና ይህንን የሚፈራው ኢህአዴግ ኢሳትን ጨምሮ በርካታ ሚዲያዎችን ለመዝጋት አገሪቱን ከፍተኛ ገንዘብ በማባከን ላይ ነው፡፡ በአንድ ወቅት አልጀዚራም ጭምር የታገደበት አጋጣሚ ተፈጥሯል፡፡ አማራጭ ሀሳብ የሚተላለፍበትን ሚዲያ እንዲህ የሚጠላው ‹‹አብዮታዊ›› ፓርቲ ፌስ ቡክን እንኳ ንቆ አልተወውም፡፡ በርካታ ፌስ ቡክ ላይ የሚጽፉ አካላት ጽሁፋቸው አገር ውስጥ እንዳነበብ ይደረጋል፡፡ እስክንድር ከታሰረባቸው ምክንያቶች ቀዳሚው ፌስ ቡክ ላይ በሚጽፋቸው ትንታኔዎቹ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ልክ የቻይና እና የኢራን አምባገነን ፓርቲዎች በአንድ ወቅት እንዳደረጉት ፌስ ቡክን ሊዘጋ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፍና የአደባባይ ሰልፍ በኢህአዴግ ዘንድ የሚፈራ ብቻ ሳይሆን የሚጠላም ተግባር ለመሆን ደርሷል፡፡ ታይቶ ከጠፋው የ1997 ምርጫ በኋላ ለአለፉት 8 አመታት ከድጋፍ ሰልፍ ውጭ የህዝብ ሮሮ የሚሰማባቸው ሰላማዊ ሰልፎች በግልጽም ሆነ በተዘዋዋሪ ታግደው ቆይተዋል፡፡ ባለፉት ስድስትና ሰባት ወራት የሰላማዊ ሰልፍ መብት እንደገና ተመልሶ የነበር ቢሆንም አሁን ግን እንደገና ታግዷል፡፡ ኢህአዴግ ሰላማዊ ሰልፍን ብቻ ሳይሆን አደባባዮችንና ጎዳናዎችን ኢትዮጵያዊ ታህሪር እንዳይሆኑ አብዛቶ ፈርቷል፡፡ ለአብነት ያህል 97ት ላይ ክፉኛ የደነገጠበት መስቀል አደባባይ ለድጋፍ ሰልፍ እንጅ ለሰላማዊ ሰልፍ ክልክል ሆኗል፡፡ ከዚህ አለፍ ሲልም ኢትዮጵያውያን ኳስ እንዳያዩበት ሁሉ እየተደረገ ነው፡፡ የናይጀሪያንና የኢትዮጵያን ጨዋታ መስቀል አደባባይ ላይ ለመመልከት ሰንደቅ አላማ ለብሰው የጎረፉ ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች ተደብድበው ተመልሰዋል፡፡ ሀይማኖት፣ ግለሰባዊነት፣ ነጻ ተቋም… ብቻ ኢህአዴግ የማያስፈራውን ነገር ቢናገር ይሻል ነበር፡፡ በእርግጥ አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ‹‹አንፈራም!ፓርቲው እንደማይፈራ ታሪኩ ይናገራል፡፡›› ብለውናል፡፡ እዚህ ላይ አቶ ሃይለማሪያም እንደተለመደው ተሳስተው ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም እሳቸው አይፈራም ብለው ለመከራከር የፈለጉት አርሳቸው ያልነበሩበትን የኢህአዴግን የጠብመንጃ ታሪክ ነው፡፡ መሳሪያ ያነሳ ሁሉ ግን ደፋርም ጀግናም አይደለም፡፡ እንዲያውም ፈሪ ዱላው፣ ጠብ መንጃው፣ መሳሪያው፣ መሰሪነቱም ከልክ በላይ በርካታዎች ናቸው፡፡ ከእነ ተረቱም ቢሆን የፈሪ ዱላ ይባላል እኮ፡፡ ፈሪ ይህን ያህል ጉዳት ሊያደርስበት የማይችለውን አካል ሁሉ ያለ አቅሙ ይደበድባል፡፡ በራሱ አይተማመንምና እንደገና እንዳያስፈራራው ያወድመዋል፡፡ አይደለም አንዳች የሚንቀሳቀስን አካል ይቅርና ጥላውን እንኳ አያምንም፡፡ የመዋጋት፤ የማሰር፣ የመፈረጅ ታሪክ ከዚሁ ከፈሪነት ባህሪው የመነጩ ናቸው፡፡ በአንጻሩ ደፋር ለመርህ ይታገላል፡፡ ለአቆመው ህግና ስርዓት ራሱንም የሚሰዋ ታማኝ ነው፡፡ ያቆመውን ስርዓት፣ አብሮት የሚኖረውን አካልና ራሱን ያምናል፡፡ በህዝብና በአገሩ ስለሚያምን፣ በራሱ ስለሚተማመን ህዝብን በፍቅር ያቀርባል፣ ተቀናቃኙን በፍቅር ይስባል እንጅ በግድ ወደኔ ካልመጣህ ብሎ ለማጥፋት ከሆነ አንዳች ነገር ፈርቷል ማለት ነው፡፡ ያኔ ፈርቷል፣ ተፍረክርኳል፣……ይባላል፡፡ ልክ እንደ ኢህአዴግ!

ወገናችንን በጥይት ሲደፉት በራሱ ላይ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንድራችንን ጠምጥመውበታል[1]። ጭካኔ በተሞለበት መንገድ የተገደለው ይህ ኢትዮጵያዊ አስከሬኑም በሰላም አላረፈም። በአካሉ ላይ ያረፈውን ጨርቅ በሴንጢ እየቆራረጡ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ሊደረግ የማይገባውን ሁሉ አደረጉበት። ድርጊቱ ናዚዎች በኦሽዌትስ ይፈጽሙት የነበረውን አሰቃቂ ግፍ ያስታውሰናል። በ21ኛው ዘመን እንዲህ አይነቱ ክስተት ይደገማል ብሎ የሚያስብ የለም። እነሆ ሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየፈጸመችው […]

ህዳር ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፉት 5 ቀናት ጀምሮ በሳውዲ አረብያ በተለያዩ የማጎሪያ ጣቢያዎች ታስረው በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ እንደቀጠለ ሲሆን፣ በዛሬው እለት 2 ሰዎች መሞታቸው ታውቋል። ኢትዮጵያውያኑ እንደሚናገሩት ሰዎቹ የተገደሉት ባልና ሚስቶችን ለመለያየት በተደረገ ሙከራ ላይ በተፈጠረ ግርግር ነው። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከሳዑዲው  አቻቸው ልዑል ሳውድ አል …

ህዳር ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አልሸባብ የተባለው አሸባሪ ቡድን እና በኤርትራ መንግስት እገዛ የሚንቀሳቀሱ የሽብር ቡድኖች በኢትዮጽያ ውስጥ የተለያዩ ስፍራዎች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም እየተዘጋጁ መሆናቸውን የሚያሳይ አስተማማኝ መረጃ ያለው መሆኑን የብሄራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎትና የፌደራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ሃይል ጥቅምት 27 ቀን 2006 ዓ.ም ካስታወቁ በኃላ በአዲስአበባ በመንግስት በግል ተቋማት ከወትሮው የተለየ ፍተሻ …

(ተመስገንደሳለኝ)
…ኢሠፓ መራሹ መንግስት በኢህአዴግ ከተተካ ጥቂት ወራት ቢያልፈውም፣ የተራዘመው የእርስ በእርስ ጦርነት ያልደረሰባቸው በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ አንዳንድ ከተሞችን ገና በቅጡ አልተቆጣጠራቸውም፤ በአናቱም በኢሠፓ መንግስት ሽንፈት ሳቢያ እንዲበተን ከተገደደው የ ገሪቱ መደበኛ ወታደር፣ አብዛኛው ከእነ ትጥቁ የትውልድ መንደሩንና ቤተሰቡን መቀላቀሉ በ ገሪቱ ላይ ከባድ ፍርሃት አንብሯል፤ በሰላም ወጥቶ ለመመለስ እርግጠኛ መሆን የማይቻልበት ከበባዊ አየርም አስፍኗል፡፡ በበርካታ ቦታዎች ተጠንተውና ታቅደው የሚፈፀሙ ወን ሎችም፣ ከአምስት እስከ አስራ አምስት በሚደርሱ ወታደሮች የተደራጁ ልዩ ልዩ ህገ-ወጥ ቡድኖች በየማዕዘኑ እያቆጠቆጡ መሆኑን አመላክቷል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነብዩ ሲራክ

የማለዳ ወግ

በሪያድ መንፉሃ በተከሰተው ሁከት ግራም ነፈሰ ቀኝ ተጎጅዎች እኛ ነን! እንኳንስ ሰው ተደብድቦ ፣ ሞቶባቸው፣ እንኳንስ መኪና ተሰብሮባቸው እንዲያውም እንዲው ናቸው። ከማለዳ እስከ ሌሊት የዘለቀውን ሁከት መቆጣጠር ይቻል ዘንድ ገና ሲ መር አቅጣጫውን አይተው የመንግስት ተወካዮችን የመከሩ በርካታ ነበሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

SHARE:

ታላቅ ሀገራዊ የተቃውሞ ጥሪ!

ከወገኖቻችን ጐን በመቆም ብሄራዊ ክብራችንን እናስመልሳለን

ሰሞኑን የሳውዲ አረቢያ መንግሥት በኢትዮጵያዊያን ላይ እየፈፀመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመቃወም ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ የተቃውሞ ጥሪ አስተላልፏል፡፡

በመሆኑም በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ኢሰብዓዊ ድርጊት ለማስቆምና የዜጐችን ህይወት ለመታደግ እንዲሁም ዜጐቻችን በአፋጣኝ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ መንግሥት እንዲያመቻች እና በተጨማሪም በዜጐቻችን ላይ ለደረሰው የአካል መጉደል፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈርና የህይወት መጥፋት ኃላፊነቱን የሚወስዱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ፤ ለተጐዱ ወገኖቻችንና ቤተሰቦቻቸውም አስፈላጊው ካሳ እንዲደረግላቸው ፓርቲያችን አበክሮ እያሳሰበ፤ የብሄራዊ ክብርና የወገኖች ስቃይ የሚያሳስባቸው አካላት በሙሉ በዚህ ታላቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
የተቃውሞ እንቅስቃሴ አፈፃፀም፡-
1. በዜጐቻችን ላይ የአካል መጉደል፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈርና የህይወት መጥፋት ያደረሰው የሳውዲ አረቢያ መንግሥት ኢምባሲ በሚገኝበት ቦታ አርብ ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት ጀምሮ የሚደረግ የተቃውሞ ሰልፍ፣
2. ከአርብ ጠዋት ጀምሮ እስከ እሁድ ማታ ድረስ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሀዘን ልብስ (ጥቁር ልብስ) በመልበስ በግፍ ለሞቱና ለተንገላቱ ወገኖቻችን ሀዘናችንን መግለፅ፣
3. የእምነት ተቋማት አርብ በመስጊድ በጁምአ ሥነ ሥርዓት ላይ እና ቅዳሜና እሁድ በአብያተ ክርስቲያናት የፀሎት ሥነ ሥርዓቶች ላይ ወገኖቻችንን በፀሎት እንዲታሰቡ፣
4. ቅዳሜ በሚደረገው የኢትዮጵያና የናይጄሪያ የእግር ኳስ ጨዋታ ላይ ተጫዋቾቻችን ጥቁር ሪቫን በክንዶቻቸው ላይ አጥልቀው እንዲጫወቱ፣ እንዲሁም መላው ደጋፊ ጥቁር ጨርቆችን በመያዝ ወይም ልብስ በመልበስ ሀዘኑንና ቁጭቱን እንዲገልፅ፣

በፓርቲው የተወሰነ በመሆኑ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ሲቪክ ተቋማት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዓለም አቅፍ ማኅበረሰቡ በአጠቃላይ መላው ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ወዳጆች በጠራነው የተቃውሞ ሰልፍና እንቅስቃሴዎች ላይ በመገኘት ከግፉአን ወገኖቻችን ጐን መቆሙን እንዲያረጋግጥ በአፅንኦት እንጠይቃለን፡፡
የወገኖቻችን ሰቆቃ እስኪያበቃ በፅናት እንታገላለን!!!

ከዛሬ 75 ዓመት በፊት ጀርመን ውስጥ በአይሁዶች ላይ የተፈፀመው ግፍ ሰሞኑን እዚህ ጀርመን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየታሰበ ነው ።
በጎርጎሮሳውያኑ ህዳር 9 ለህዳር 10 አጥቢያ 1938 ዓም በመላ ጀርመን የሚገኙ የይሁዲዎች ሙክራቦች ፣ ሱቆችና መኖሪያ ቤቶች በናዚዎች ትዕዛዝ እንዲወድሙ ተደርጓል ። ይሁዲዎችም ግፍ ተፈጽሞባቸዋል ።

አሁንም እዚያዉ ሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በተለያየ ችግር እየተሰቃዩ መሆናቸዉን እያስታወቁም ነዉ።በስልክ ያነጋገርናቸዉ ኢትዮጵያዉያን እንደሚሉት ወደ ሐገራቸዉ ለመግባት ቢፈልጉም ከሳዑዲ አረቢያ ፀጥታ አስከባሪዎች የሚደርስባቸዉን ድብደባና በደል ፍራቻ በየቤታቸዉ ለመሸሸግ ተገድደዋል።

ከሁለት ዓመታት በፊት በተሠራ ጥናት መሠረት ኢትዮጵያ ዉስጥ በመዉለድ የእድሜ ክልል ከሚገኙ ሴቶች 27 በመቶዉ የወሊድ መቆጣጠሪያ ስልቶችን ይጠቀማሉ። የሀገሪቱ የስነህዝብ ፖሊሲ አንዲት እናት በአማካኝ አራት ልጆች ብትወልድ የሚል ግብ ነዉ ያለዉ።

ኢትዮጵያና ኤርትራ የሚዋሰኑበት ከ 1000 ኬሎ ሜትር የድንበር ክልል ያላቸዉ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት በርካታ ኤርትራዉያን ሀገራቸዉን እየጣሉ ይሰደዳሉ። በሰሜን ምዕራብ ትግራይ አቅጣጫ ብቻ በቀን ከ 50 በላይ ኤርትራዉያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ እንደሆነም ተነግሮአል።

ክንፉ አሰፋ

ወገናችንን በጥይት ሲደፉት በራሱ ላይ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንድራችንን ጠምጥመውበታል። ጭካኔ በተሞለበት መንገድ የተገደለው ይህ ኢትዮጵያዊ አስከሬኑም በሰላም አላረፈም። በአካሉ ላይ ያረፈውን ጨርቅ በሴንጢ እየቆራረጡ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ሊደረግ የማይገባውን ሁሉ አደረጉበት። ድርጊቱ ናዚዎች በኦሽዌትስ ይፈጽሙት የነበረውን አሰቃቂ ግፍ ያስታውሰናል። በ21ኛው ዘመን እንዲህ አይነቱ ክስተት ይደገማል ብሎ የሚያስብ የለም። እነሆ ሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየፈጸመችው ነው። በስውር ሳይሆን በግልጽ። እንደ ኦሽዊትስ በታጠረ የማጎርያ ካምፕ ሳይሆን በአደባባይ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጠበቃ ስቴላ ያርዴእንቅስቃሴውን የጀመሩት ስዊድናዊ ጠበቃ ከኢትዮጵያውና ጋር ውይይት አደረጉ
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ኅዳር 3 ቀን 2006 ዓ.ም. Nov. 12, 2013)፦ ባለፈው ቅዳሜ ጥቅምት 23 ቀን 2006 ዓ.ም. (ኖቬምበር 2 ቀን 2013) የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ መድረክ በስዊድን የወያኔን መንግሥት በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ለማቅረብ የተጀመረውን ክስ መነሻ በማድረግ የክሱን ሂደት ከሚመሩት ከስዊድናዊው ጠበቃ ከስቴላ ያርዴ እና ከሌሎች እንግዶች ጋር በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ወይይት አደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በኢትዮጵያ ታሪክ ጥናት ታላቅ ቦታ ያላቸውን ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራትንና ፕሮፌሰር ዶናልድ ክራሚን ለማሰብ ሰኞ ጥቅምት 18 ቀን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ መርሐ ግብር ተዘጋጅቶ ነበር፡፡ በወቅቱ የሁለቱም ደቀ መዝሙር የነበረው ዶ/ር ውዱ ጣፈጠ ያቀረበውን ማስታወሻ እንብቡት፡፡


ዝክረ ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራትና ፕሮፌሰር ዶናልድ ክራሚ

ዉዱ ጣፈጠ( ዶ/ር)

ከተማሪዎቻቸው አንዱ

ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራትና ፕሮፌሰር ዶናልድ ክራሚ ሁለቱ በዩነቨርስቲ የትምህርት ቆይታዬና ብሎም በህይወቴ ላይ ቀና ተፅእኖ ያሳደሩ ታላቅ መምህሮቼ ነበሩ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ውስጥ የቅድመ-ምረቃ የታሪክ የአራተኛ ዓመት ተማሪ በነበርኩበት ጊዜ ከፕሮፌሰር ታደሰ ጋር የመጀመሪያን ትውውቅ አደረግን፡፡ ለቅድመ ምረቃ (ለቢ.ኤ.) ዲግሪ ማóóያ የምረቃ Òሁፍ ምርምር ለማድረግና ውጤቱንም ለመፃፍ እንድችል እርሳቸው አማካሪዬ ሁነው ተመድበው ነበር፡፡ በወቅቱ እርሳቸው የማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ስለነበሩ እርሳቸውን አግኝቶ ለማነጋገር ትንሸ ችግር ፈጥሮብኝ ነበር፡፡ ከትንሸ መመላለስ በኋላ አግኝቸ ራሴን ሳስተዋውቅ ትኩር ብለው እየተመለከቱ በርጋታ አዳመጡኝ፡፡ ከዚያም እስኪ ወደ ሌላ ነገር ከመግባታችን በፊት የራስህን ታሪክ፤ የቤተሰብህን፤የአስተዳደግህንና የትምህርትህን ነገር ግለፅኝ ብለው ጠየቁኝ፡፡ በጊዜው ይህ ሁሉ ምን ያደርጋል ብየ በየዋህነት ራሴን ጠይቄ ነበር፡፡ የርሳቸው አካሄድ የገባኝ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ነበር፡፡

  ለቅድመ ምረቃ የምርምር ስራ የሰራሁበት ርእስ ስለ ራጉኤል አብያተ ክርስቲያናት ታሪክ ነበር – እንጦጦና አዲስ አበባ መርካቶ ስለሚገኙት መንትያ አብያተ ክርስቲያናት፡፡ ፕሮፌሰር ታደሰ  በጣም ረጋ ያሉ፤ በተመስጦ የሚያዳምጡ፤ ቀስ ብለው የሚናገሩና እንዲህ አይነቶቹን ዋና ዋና ፍሬ ነገሮች አስተውለሀዋል ብለው በማስታወሰ መንገድ የሚያሳዩ ነበሩ፡፡ በዜያ ጊዜ እኔን ለመሰለው ገና ጀማሪ በማበረታታትና በሚቀጥለው ጊዜ ስንገናኝ አዲስ መረጃ እንደምታመጣ ተስፋ አለኝ ብለው የሚሸኙ ነበሩ፡፡ የሚያውቁትን መረጃ ጠቅሰው ፈልግ የሚሉ፤ መረጃ ሊሰጡ የሚችሉና ያውቃሉ ብለው የሚገምቷቸውን ሰዎችን ስም የሚነግሩና ሲቻልም የሚያስተዋውቁ ነበሩ፡፡

   በዚያ ጊዜ እጅግ ያስቸገረኝ ነገር ቢኖር ጽሕፈታቸውን ማንበቡ ነበር፡፡ ይህም ቢሆን ዲኑ ቢሮ ትሰራ የነበረች ወ/ሮ እልፍነሽ እንዳለ ተረር አድርጋ እያነበበች ችግሬን ታቃልልኝ ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ አብራቸው ስለሰራች ጽህፈታቸውን ያለችግር ማንበብ ችላ ነበርና፡፡

    አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመቀጠር እድል ባጋጠመኝ ወቅት ሁል ጊዜ ያለማቋረጥ ድጋፋቸውንና አበረታች ቃላቸውን ያለ ምንም ስስት ይነግሩኝ ነበር፡፡ ይህም የታሪክ ትምህርት ክፍል በርሳቸው ስር ሆኘ ምክራቸውን እጠየቅሁ እንዳነብና ልምድ እንዳገኝ መድቦኝ ነበርና፡፡ የመካከለኛውን ዘመን የኢትዮጵያ ታሪክ ለማጥናት የሚረዳኝን የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ሁለት ኮርስ እንድወስድ አበረታቱኝ፡፡ በጊዜው ኮርሱን ይሰጡ ለነበሩት ለዶ/ር አምሳሉ አክሊሉ አስተዋወቁኝ፡፡ ብዙ አልገፋሁበትም እንጅ የፈረንሳይኛና የጣሊያንኛ  ቋንቋ ትምህርት እንድማር አበረታተውኝ ነበር፡፡

   ቀጥሎም ታሪክ የማስትሬት ትምህርት በምማርበት ጊዜ ትልቅ ድጋፍ በማድረግ የተለመደ የማማከር ሀላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡ ለዚህ ዲግሪ ማóóያ   የምርምር ጥናቴ ርእስ የነበረው የዋግና የላስታ ታሪክ የሚል ነበር፡፡ እርሳቸው እንደነገሩኝም የላስታ መሪዎች የዛጉዌን ታሪክ ለመፃፍ እቅዳቸው እንደነበርና ይህንን ታሪክ ለመፃፍ በማሰቤ፤ የትምህርት ክፍሉም ሆነ እርሳቸው ሰለገፋፉኝ፤ በመቀበሌ ደስ እንዳላቸው ገልፀውልኛል፡፡

የምሰራበት የታሪክ ዘመን ራቅ ያለ በመሆኑና ታሪኩን ለማያያዝና መስመር የያዘ የታሪክ ዳራ እንዲኖረው ለማድረግ ያለ መሰልቸት ይመክሩኝ ነበር፡፡ ከሁሉም በላይ ስራየ ደከም ያለ ሲመስላቸው በራሳቸው ፅፈው ይህንን ጨምረው እያሉ ታሪኩ ወጥነት ኖሮት እንዲተረክ እጅግ ለፍተዋል፡፡ በምሳ ሰአት ጭምር ቁጭ ብለው እያረሙና እያስተካከሉ ይህ ነው ተብሎ የማይገለጽ ድካም አሳልፈዋል፡፡ በዚያ ጊዜ የማስተርስ ድግሪ ትምህርት አራት አመት ይወስድ ስለነበር የማስረከብያ ጊዜው እንዳያልፍብኝ ብለው አሜሪካን አገር ትኖር የነበረች የልጃቸውን ቀለበት ቀን በኔ ምክንያት ሳይሳተፉ ቀርተዋል፡፡ ችግር የለም አንተም ልጄ ነህ እንዳሉኝ” አስታውሳለሁ፡፡ በ|ላም በአሉ እዚህም ተከበረ፡፡

   በተለይም ደግሞ የታሪክ የዶክተሬት ትምህርት እንድማር በማሰብ፤ ለሌሎች እንዳደረጉት ሁሉ፤ እኔንም ከÝሮፌሰር ክራሚ ጋር አስተዋወቁኝ፡፡ በ1991 .ም. ወደ ኢሊኖይ ዩኒßርስቲ – ኧúርባና aምፔይን – በሄድኩ ጊዜ Ýሮፌሰር ክራሚ እንደ Ýሮፌሰር ታደሰ ሁሉ አገሩን በማስተዋወቅ፤ በማበረታታት፤ የሚቸግረኝን ነገር ሁሉ በማደረግ ትልቅ ድጋፍ አድርጎልኛል፡፡ እኔ በሄድኩበት አመት ከኬንያ የመጣውን ሌላ ተማሪ አይሮፕላን ጣቢያ ድረስ በመሄድ ተቀበለው፡፡ እኔንም እንደዚሁ፡፡ ሁለታችንም እቤቱ ወስዶ አሳረፈን፤ አስተናገደን፡፡ ቤት ተከራይተን ራሳችንን እስክንችል ድረስ ለሳምንት ያክል እቤቱ ተቀመጥን፡፡ እንግድነት በጣም ሳይሰማንና ተሳቀንም በችኮላ ቤት እድንከራይ ሳንሆን፡፡ አሜሪካ በደረስኩበት ጊዜ ምንም ገንዘብ አልነበረኝምና ገንዘብ እስካገኝ ድረስ ቤቱ እንድቀመጥ ጋብዞኝ ነበር፡፡ በተለይም ባለቤቱ ሚስ ሎሬይን ክራሚን እንደ እናት ነበር የምንመለከታት፡፡

  አገርን ለቅቆ፤ ባህርን ተaግሮ በሌላ አገር መኖር የሀገርና የወገን ናፍቆት አስቸጋሪ ቢሆንም በአመት በአል ቀናት ማለትም የአሜሪካን የምስጋና ቀን፤ ገናና፤ ፋሲካ በደረሰ ቁጥር Ýሮፌሰር ክራሚ ቤት እየተጋበዝን በአላቸውን በአል አድርገን ውለናል፡፡ ምናልባት በአጋጣሚ በከተማው ካልኖሩ በስተቀር፡፡ በእነዚህ በአላት ሌላ ከተማ የሚኖሩ ልጆቹና ¹ደኞቹ ስለሚሰባሰቡ በአላቸውን ደመቅ አድርገን ተደስተን አብረን አሳልፈናል፡፡ የኢትዮÉያ ቡና ተፈልቶ፤ የኢትዮÉያ ቱሪስት አስጎብኚ ድርጅት በሰራቸው የንግስተ ሳባ ስእል ባላቸውና በሚያማምሩት የቡና ስኒዎች አገራችን ያለን እስኪመስለን ድረስ ተጋብዘናል፡፡ ቢራና ወይንም ተጎንጭተናል፡፡

  በዩኒቨርስቲው የትምህርት መርሀ ግብርና ሌሎች ችግሮች በተከሰቱ ቁጥር እንደ አባታችንና እናታችን ቤት ሳንሳቀቅና ሳንፈራ ቢሮው ሄደን የገጠመንን ችግር አማክረን መፍትሄ አግኝተናል፡፡ በተቻለው ጊዜ ሁሉ እኛን ለማረጋጋትና ችግራችንን ለማቃለል ከልቡ ጥ[ል፡፡ አንዳንዴም ንዴታችንን ለማስረሳት ቢራ እየጋበዘ፡፡ ያውም ከሚያውቃቸው አንዳንድ ቀልዶች ጋር እያዋዛ፡፡ “ባርባ አራቱ የጎንደር ታቦታት’ እና ‘ነው እንዴ” ከሚሉ ሀገርኛ ቀልዶች ጋር፡፡

  በዚሁ የአሜሪካ ቆይታየም Ýሮፌሰር ታደሰም እዚያው ስለነበሩ የሁለቱ አማካሪዎቼና መምህሮቼ በአንድ ከተማ መገኘት ለአኔ ጥሩ አጋጣሚ ነበር፡፡ የዶክተሬት ዲግሪ ማóóያ የጥናት ሰራየ በኢትዮÉያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ላይ ስለነበር በቂ የሆነ ድጋፍና ምክር ለማግኘት ችያለሁ፡፡ ቀደም ብሎ ሁለቱ መምህሮቼና Ýሮፌሰር ሁሴን በኢትዮÉያ የሀይማኖት ጉዳዮች ላይ ምርምር ለማደረግ እቅድ ስለነበራቸው፤ እኔም በዚሁ እቅድ ውስጥ ተካትቸ ስለነበርና፤ የጥናት ርእሴም የዚሁ አካል ስለነበር የሁለቱ መምህሮቼ ድጋፍ አልተለየኝም ነበር፡፡

 ከሁለቱ መምህሮቼ ጋር የነበረኝ ቅርርብ በምርምር ስራ ላይ ብቻ የተወሰነ አልነበረም፡፡ ቤተሰባዊ ጭምር እንጅ፡፡ የÝሮፌሰር ታደሰ ሁለት ሴት ልጆች – ህይወቴና ህሊና ታደሰ – የቀለበት ስነ-ስርአታቸውን በተለያየ ወቅት ባደረጉ ጊዜ መጋበዝ ብuሳይሆን እኔም ሆንኩ የታሪክ ትምህርት ክፍል አባሎች እንደ ቤተሰብ አባል ንቁ ተሳታፊ ነበርን፡፡ ምንም ጊዜ የማይረሳኝና ምን ያህል Ýሮፌሰር ታደሰ እንደሚያቀርቡኝ የተረዳሁት በጊዜው ¹ደኛየ ነበረችውን ያሁኗን ባለቤቴን ይŸት እንድገኝ በጋበዙኝ ጊዜ ነበር፡፡ እርን በአካል አያውkትም ነበር፡፡ ነገር ግን መጠየቅ ይወዳሉና በማስተርስ ዲግሪ ማóóÎሁፌ ውስጥ ስማóን አይተው ጠይቀውኝ ነበርና አስረዳሁዋቸው፡፡ ታዲያ የግብŸ ጥሪ ወረቀት ሲሰጡኝ “¹ደኛህን ትተሀት እዳትመጣ፡፡ ልብ በል እርካልመጣች እዳትመጣ” ያሉኝ ነበር፡፡ የቀለበቱን ስነ-ስርአት አንስተን ባወራንቁጥር እኔና ዶ/ር አበበ ፍስሀ የተጫወታችሁት አይረሳኝም ይሉ ነበር፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ጊዜያት ከውጭ ለመጡ ቀደምት ¹ደኞቻቸው ግብŸ ባደረጉ ጊዜ እኔና የአሁኗ ባለቤቴ ተጋብዘን የባለቤታቸውን የወ/ሮ አልማዝን የተዋጣ የባልትና ሞያ ተkድሰናል፡፡

  Ýሮፌሰር ክራሚ የ60ኛ አመት የልደት በአሉን ባከበረበት ጊዜ በወዳጅነት ተጠርተን ተጋብዘን ነበር፡፡ ከባለቤቴ ጋር ምን እንስጠው ተባብለን ተመካከርንና ወይን እንግዛለት ተባባልን፡፡ መቸም የተማሪ አቅም ነው ብለን አነስ ያለች የጣሊያን ወይን ወሰድንለት፡፡ ከጥቂት ቀናት በ|ላ በÑፈልኝ ማስታወሻ ሌሎች ለልደቴ ከላኩልኝ ነገር ሁሉ እንደናንተ የሚጥም ወይን ያመጣልኝ የለም የሚል ቃል ነበረው፡፡


  Ýሮፌሰር ክራሚ ጋር ለመስክ ስራ አብረን አልተ¹ዝንም፡፡ ነግር ግን በአንድ አጋጣሚ ወሎ ላይ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የምርምር ስራ ሲያካሂድ ባቲ ከተማ አጠገብ አንድ ቀን አብሬው ውየ ነበር፡፡ ሰዎችን ሲያነጋግር የጥያቄውን አሰነዛዘርና በጥሞና ማዳመጡን መገንዘብ ችያለሁ፡፡  የማስተርስ ተማሪ በነበርኩ ጊዜ ከÝሮፌሰር ታደሰ ጋር በ1994 .ም. ከሌሎች ዘጠኝ ተማሪዎች ጋር ወደ ሰሜን ሸዋ ለሦስት ሳምንታት የመስክ ስራ አብረን ሄደን ነበር፡፡ ቡልጋን፤ በከፊል መርሀቤቴን፤መንዝን፤ ሸንኮራንና፤ ምንጃርን ጎበኘን፡፡ የማይረሳኝ ጉብኝት ነበር፡፡ በምግብ ሰአት ሁላችንም፤ እርሳቸውን ጨምሮ፤ በአንድ ተካፍለን እንበላለን፡፡ ሰዎችን እንዴት እንደምናነጋግር፤ መረጃ እንዴት መሰብሰብ እንዳለብን፤ እንዴት እንደምናቀነባብር በደንብ የተማርንበት ነበር፡፡ ማታ ማታ የቀኑን ስራችንን እንገመግማለን፤ የሚቀጥለውን ቀን ስራ እናቅዳለን፡፤ እንዲሁም በጠዋት ተነስተን ጉዞአችንን እነቀጥላለን፡፡
 በጉዞ ላይ ምንጊዜም መምህራችን ከማለዳ ጅምረው እያጫወቱን እን¹ዘለን፡፡ በማንኛውም ጉዳይ ላይ በርከት ያሉ ቀልዶችና ወጣቶች የሚያወሩትን ወሬ ሁሉ እያወጉ ያስቁናል፡፡ ከአራት ሰአት በ|ላ “እንግዲህ የኔን ጨረስኩ፤ በሉ አሁን ደግሞ የናንተን አምጡ” ይሉንና ከዚያ በ|ላ ተራቸውን አድማጭ ይሆናሉ፡፡ እኛም ምንም ሳንፈራ ማንኛውንም ነገር እናወራለን፡፡ ሀብታይ ዘራይ የተባለ ወፈር ያለ ተማሪ ከ|ላቸው ይቀመጥ ነበርና አጫጭሮቹን አላሳይ ብሎ ሲከልላቸው ጊዜ “መገዘዝ ዘወር በል አጫጭሮቹን ልይበት” እያሉ ያስቁን ነበር፡፡ መገዘዝ ቡልጋ ውስጥ የሚገኝ ግዙፍ ተራራ ነው፡፡ ከወራት በ|ላ የማጠቃለያ ስራየን ጽፌ ስሰጣቸው በአጋጣሚ ቡልጋን መÍፍ ረሳሁት፡፡ ቡልጋ ደግሞ የርሳቸው አገር ነው፡፡ ቁም ነገር መርሳቴን ለመግለጽ ‘poor Bulga ምስኪኗ ቡልጋ’ ብለው ስህተቴን በቀልድ አዋዝተው አስገረሙኝ፡፡ 
  ከቀን ጉዞአችን በ|ላ ማታ ወደ ማደሪያችን ስንመለስ ሁልጊዜም ቅድሚያ የሚሰጡት ስልክ ደውለው ባለቤታቸውን ማነጋግር ነበር፡፡ ይህ ምንም ቢሆን የማይቀር፤ስልክ አይሰራም ካልተባለ፤ በቀር የምይዘነጋ የእለቱ ስራ ነበር፡፡ እውነትም Ýሮፌሰር ሽፈራውእንዳለው “ምሳሌ ሊሆኑ የሚገባቸው አፍቃሪ ባል” ነበሩ፡፡ በ1990 .ም. ለ13ኛው የኢትዮጵያ ጥናት ጉበኤ ወደ ቶክዮ፤ ጃፓን፤ በሄድንበት ጊዜ Ýሮፌሰር ባህሩ የጋበዘንን ውስኪ አንድ ምሽት እየጠጣን እንዴት የትዳር ¹ደኛችሁን እንደተዋወቃችሁ አውሩ ተባለ፡፡ መጀመሪያ በእድሜ የምናንሰው አወራንና ቀጥሎ ደግሞ ትላልቆቹ አጫወቱን፡፡ በመጨረሻም Ýሮፌሰር ታደሰ ከባለቤታቸው ጋር እንዴት እንደተዋወቁ ሲያወሩን ፍቅር እስከ መቃብርን የሚወዳደር የፍቅር ጥምረት፤ እውነተኛና አስገራሚ ታሪክ ነበር፡፡ Ýሮፌሰር ታደሰና ወ/ሮ አልማዝ ፍቅራቸው እንደÐናና እንደ ደመቀ አብረው በፍቅር ኖረው አንድ አመት ባልሞላ የጊዜ ርቀት በሞት ተከታትለው አረፉ፡፡
  ዶ/ር ተካልኝ እንደሚያጫውተን Ýሮፌሰር ታደሰ ተማሪዎቻቸውን ይዘው ወደ መስክ የምርምር ስራ በየአመቱ ሲወጡ በጣም የሚያቀርቡአቸው ተማሪዎች አሉአቸው፡፡ ቦርሳቸውን የሚይዝላቸው፡፡ እነዚህን ተማሪዎች ‘ዳዊት’ የሚል ስም ተማሪዎቹ ያወጡላቸዋል፡፡ የመንፈሳዊ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የመምህራቸውን ዳዊት ተሸክመው እንደሚከተሉ ሁሉ፡፡ ታዲያ ዶ/ር ተካልኝ አንድ ጊዜ ይህንን ለÝሮፌሰር ታደሰ ሲያጫውታቸው “ለዚህ ነበር እንዴ ጉሉማን ዳዊት ትሉት የነበር፤ እኔ እኮ እስካሁን አላወቅሁም ነበር” ብለው ሳቁና አሳቁን፡፡ ዶ/ር ጉልማ አሁን የሚኖረው አሜሪካን አገር ነው፡፡ እኔም በወቅቱ ዳዊት መባሌን አልሰማሁም እንጅ የአመቱ ዳዊት ነበርኩ ማለት ነው፡፡
 Ýሮፌሰር ታደሰና Ýሮፌሰር ክራሚ ብዛት ያላቸውን የቅድመ ምረቃ፤ ማስተሬትና ዶክተሬት ተማሪዎች አማክረው አስመርቀዋል፡፡ ከድሮ ተማሪዎቻቸውም ጋር እንደ ስራ ባልደረባና እንደ ¹ደኛ ሁነው ብዙ ዘመናትን አሳልፈዋል፡፡ ተማሪዎቻቸውም እነዚህን የእወቀት አባቶቻቸውን አክብረው ኖረዋል፡፡ ሁለቱም ለንደን የዶክተሬት ድግሪ ተማሪ ከነበሩበት ጊዜ ጀምሮ በፍቅርና በመግባባት አብረው ሰርተዋል፤ ኖረዋልም፡፡ በሞትም ቢሆን ሁለት ወር ባልበለጠ ጊዜ በሞት ተከታትለው አልፈዋል፡፡ Ýሮፌሰር ታደሰ በግንቦት እንዲሁም Ýሮፌሰር ክራሜ በነሀሴ 2005 .ም.፡፡ ሞት አይቀሬ ነውና ሞት አለያይቶአቸዋል፡፡ እግዚአብሄር ነፍሳቸውን በአብርሀምና በያ˜ቆብ ቦታ እንዲያሳርፍ እንመኛለን፡፡ ለቤተሰባቸውም መÒናናትን ይስጣቸው፡፡  

ሰኞ፤ ጥቅምት 18/2006 .ም.

Image

ጥቁር ሽብር ወያኔ ቁምጣ የለበሰ ደርግ ነው ! እመኑኝ በየትኛውም የታሪክ ገጠመኝ የሳወዲ መንግስት የዚህ አይነት ድፍረት ያውም በአደባባይ በዜጎቻችን ላይ አሳይቶ አያውቅም ፡፡ ነገሮችን ተመልሰን ከተመለከትን ይህ ግፍና በደል የእኛው ባለስልጣናት ሳውዲወችን አደፋፍረው ያስፈፀሙት ጉዳይ ነው፡፡
ይህም ሁለት ፖለቲካዊ ምክንያቶች አሉት ፡፡ የመጀመሪያው ፡- የወያኔ ባለስልጣናት በሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጲያዊያንን ቦንድ እንዲገዙ በሰበሰቡበት ወቅት ተደጋጋሚ ተቃውሞ ደርሶባቸው እንደነበር የሚታወቅ ነው ፡፡ ይህም ድምፃችን ይሰማ ባሉ ሙስሊሞች ላይ በሃገር ውስጥ የሚደርሰው በደል ይቁም ለጥያቂያቸውም አጥጋቢ መልስ ይሰጥ በሚል ምክንያት ነበር ፡፡ ቂመኛው መንግስታችን ይህን እንደበደል በመቁጠር በእጅ አዙር ዜጎቻችንን እያስጋዘ ይገኛል ፡፡ ለዚህ በደሉ ሽፋን እንዲሆነው በቅርቡ በተለያዩ ሚዲያወቹ አረብ አገራት ላይ ያተኮሩ ወሬወችን ሲነዛ ቆይቷል ፡፡ የሳዲ መንግስት በሰጠው የጊዤ ገደብ የሚያስፈልጋቸውን መረጃ ሊጠይቁ ወደ ‹‹ኢትዮጲያ ኤምባሲ ›› የሄዱ ሚስኪን ለፍቶ አደሮች ቦንድ ግዙ እየተባሉ ሲመላለሱ የጊዜ ገደቡ አልቆላቸዋል ፡፡ ሁለተኛው ምክንያቱ ፡- አገር ውስጥ ያለው ‹‹የድምፃችን ይሰማ ›› እንቅስቃሴ አረብ አገራት ባሉ ኢትዮጲያዊያን የገንዘብ ድጋፍ ያገኛል በሚል ፍርሃት ነው ፡፡ፍርሃት ብቻ ሳይሆን በግልፅም በወቲቪ (የ ወያኔ ቴሌቪዥን ) በተደጋጋሚ ተናግሮታል ፡፡ በመሆኑም ይህን የራሱን ስጋት ለማስታገስና መመለስ ያልቻለውን የማይችለውንም የመብት ጥያቄ ለማፈን የገቢ ምንጭ ናቸው ያላቸውን በአረብ አገር የሚኖሩ ኢትዮጲያዊያንን ሰላም ደህንነትና ሂወት ጭምር በእጅ አዙር እየነጠቀ ነው ፡፡ (እዚህ ላይ ሳውዲወች የቴውድሮስ አድሃኖም ስምምነት አለበት ማለታቸውን እንዳንዘነጋ) አሁን ከወደኪዌት እንደምንሰማው ደግሞ ከስራቸው በገፍ የተፈናቀሉ ኢትዮጲያዊያን ሰልፍ እንወጣለን አልያም ስራ ይሰጠን እያሉ ነው ፡፡ እኒህ ኢትዮጲያዊያን ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከስራቸው የተፈናቀሉ ናቸው ፡፡
ወያኔ እና የወያኔ ጭፍን ደጋፊወች ማወቅ ያለባችሁ ጉዳይ ድህነት ትግልን ያባብሳል እንጅ አያዳፍንም ‹‹አፈር እየቃምን ድንጋይ እየቆረጠምን ደርግን ጣልነው ›› እንደምትሉት ይህም ህዝብ ሆነ ብላችሁ የምትጭኑበትን ድህነትና እንግልት ተቋቁሞ ድል ማድረጉ የማይቀር ነው ፡፡ ታውቁታላችሁ እናውቀዋለን ! ወያኔ ማለት ቁምጣ ለብሶ የመጣ ደርግ ነው ፡፡ ደርግ ቀይ ሽብር ብሎ ህዝብ ፈጀ ፤ ወያኔ በተዳፈነና የህዝብን መብት ፣ ነፃነትና ሂወት ጭምር በጋረደ ጨለማ አገዛዙ ጥቁር ሽብሩን አወጀ፡፡ እነሆ አገራችን በጥቁር ሽብር ውስጥ ወድቃለች ንጋትን ናፍቆ የተሰደደ ህዝብ በገፍ እየተሰቃየ ነው ፡፡ https://www.facebook.com/photo.php?v=286230021510610
Information for Ethiopia blog

የቀጣፊዎቹ ልሣን የሆነው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ትናንት ማታ በመስኮቱ ሦስት ሆዳም የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማህበር አመራሮች አቅርቦ ነበር።ሦስቱ ሆድ አደሮች በበረከትና በሺቀጥል ከማል ተጠፍጥፈው የተሠሩ የጋዜጠኞች ማህበር መሆናቸው ነው።
ኢነጋማ አባላቱና አመራሩ ተጠራርገው ከሐገር ከተባረሩበት የጥቅምቱ መሬት አንቀጥቅጥ ሕዝባዊ ማዕበል በአግአዚ ጭፍጨፋ ከከሸፈ ወዲህ የነበረከት ስሪቶቹ በቀቀኖች አይናቸውን በጨው አጥበው ዕአንድም ጋዜጠኛ በሙያው ምክንያት አልታሠረም።የምዕራቡ ሚዲያ የኢትዮጵያን ሚዲያ ገፅታ አለአግባብ እየኮነነ ነው።የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ ነው ዕዕሲሉ ለፈጣሪዎቻቸው ታማኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
ጋዜጠኛ ባንዳ ሆኖ ህሊናውን ሲያመክን ማየት እንዴት ያሣዝናል፧
በእስክንድር፣በርዕዬትና በውብሸት ኮራሁ።በአብርሐም፣በወንደሠንና በመሠረት አታላይ አፈርኩ።ሦሥቱም አታላዮች መሆናቸው ነው።ያታለሉት ግን ራሣቸውን ነው።ህሊናቸውን ነው።
የሐገራችን ሚዲያ መቃብር ከወረደ ስምንተኛ ዓመቱን በምንዘክርበት በአሁኑ ወቅት ጋዜጠኞችን አሸባሪ እያለች ዘብጥያ የምትወረውር ሐገር ውስጥ የአፍሪካ ሚዲያ መሪዎች መድረክ በመባል የሚታወቀው አኅጉር አቀፍ የሚዲያ ባለድርሻዎች የውይይት መድረክ ስድስተኛ ጉባዔውን ሲያከናውን በመለስ ዜናዊ ሚስጥራዊ መመርያና የተፈቀደ በጀት አማረ አረጋዊ ባለ ቀይ ጃኖው የሪፖርተር ጋዜጣ አሣታሚና የ ኤም ሲ ሲ ባለቤት እንዳለውዕየአፍሪካ ሚዲያ መሠረታዊ ችግሮች ሁለት ነጥቦችን አንስቷል፡፡ በዋናነት የጠቀሱት የሚዲያ ተቋማቱ አቅም ማነስና የሚዲያ ነፃነት ችግሮች መሆናቸውን፣ ሌላኛው ደግሞ የውጭ አገሮች አድልኦና ፍላጐት ነው ፡፡ በኢትዮጵያ የሚዲያ ነፃነት ችግር ቢኖርም ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር ሲነፃፀር የተሻለ ቢሆንም፣ ነገር ግን በሰፊው እየተዘገበ ያለው ስለኢትዮጵያ ብቻ ነው ዕአማረ አረጋዊ ዕበኢትዮጵያ የሚዲያ ነፃነት ችግር ቢኖርምዕሲሉ መናገራቸው የግሉ ፕሬስ የነፃነት ችግር እንዳለበት ከመሸም ቢሆን ያመኑ ይመስላል።
በቀጣይ ልጅ ደመቀ መኮንን አሉት እንደተባለው ጋዜጠኞቹ በሙያቸው ምክንያት አለመታሰራቸውን ገልጸዋል፡፡

ዕጋዜጠኞቹ በተግባር በሽብር እንቅስቃሴ ውስጥ ተገኝተዋል ለዚህም ተገቢውን ሕጋዊ ሥርዓት የተከተለ ዕርምጃ ተወስዶባቸዋል፤ዕዕ

ዕኢትዮጵያ ካለችበት ቀጣና አንፃር የሽብር እንቅስቃሴ ዋነኛ ሥጋቷ ነው፡፡ በመሆኑም መንግሥት የህልውና ጉዳይ አድርጐ ይመለከተዋል፤ዕ ብለዋል፡፡ ከዚህ ውጪ በጋዜጣዊ የሙያ ተግባሩ የተከሰሰ አንድ ግለሰብ ብቻ ነው በማለት አስረድተዋል፡፡
ዕበጋዜጣዊ የሙያ ተግባሩ የተከሰሰ አንድ ግለሰብ ብቻ ነው።ዕያሉት ጋዜጠኛ ስሙ ማን ይሆን፧በረከት ለምን ይህን ተናገሩ ብሎ እንደማይቆጣዎ ተስፋ እናድርግ፧ተላላኪው ቢሆኑም ቅሉ።
የኬንያው ምክትል ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣በወርቃማ ቃላት ይህን ብለዋል። ዕሙያዊ ተግባራቸውን በመወጣታቸው ጋዜጠኞችን ማሰርና መቅጣት ኋላ ቀር የሆነ አስተሳሰብ ነው፤ዕ ሲሉ ገልጸውታል፡፡

የሚዲያ ነፃነት በኬንያ መሠረቱ እንዲስፋፋ መንግሥታቸው የሚያምን መሆኑን የሚናገሩት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ይህንን የሚያደርጉት ለሚዲያ ተቋማቱ ሲባል ብቻ ሳይሆን ኬንያውያን ሥልጣን ላይ ያስቀመጧቸው መሪዎች እንዴት እያስተዳደሯቸው እንደሆነ የማወቅ መብት ስላላቸውና ስለሚገባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አንዳንድ የጉባዔው ተሳታፊዎች የአኅጉሪቱ የፖለቲካ አመራሮች ወይም መንግሥታት የሥልጣን ቆይታቸውን ለማራዘም የአኅጉሪቱ የሚዲያ ነፃነትን በሚያወጧቸው የተለያዩ አፋኝ ሕጐች ገድበዋል፡፡ የሚዲያ ባለሙያዎችም በእነዚህ ሕጐች ሰለባ ሆነዋል በማለት ጋዜጠኞች ተከራክረዋል፡፡ በርካቶችም ሙያዊ ተግባራቸውን በመወጣታቸው ሕይወታቸውን እስከማጣት ደርሰዋል በማለት በውይይቱ የተሳተፉ ጋዜጠኞችና የመስኩ ባለሙያዎች የአኅጉሪቱን የፖለቲካ አመራሮች ወቅሰዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ የሚዲያ ባለሙያዎች ባገኟቸው አጋጣሚዎች ሁሉ በሙያቸው ምክንያት በርካታ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እስር ቤት እንደሚገኙ በማሳያነት ይጠቅሳሉ፡፡
ይህን የመሠለ መድረክ መዝጊያ ላይ ነው የነበረከት በቀቀኖች ዕበኢትዮጵያ አንድም ጋዜጠኛ በሙያው ምክንያት አልታሠረም።የምዕራቡ ሚዲያ የሐገራችንን ሚዲያ ገፅታ አለአግባብ እየኮነነ ነው።የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ ነው።ዕየሚሉን።

ህሊና ከሌላቸው ሆዳምና አድርባይ ጋዜጠኞች ይሠውረን።

ፔን ዘ ኢትዮጵያ

በተለያዩ ዐረብ ሀገራት በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው በደልግሩም ተ/ኃይማኖት
ይድረስ ያልኩት በቀጥታ ባይደርሶትም መስማትዎ እንደማይቀር እገምታለሁ። ሰላም የምሎት ሰላምታ የእግዚአብሔር በመሆኑ ነው። እንጂ ጫንቃችን ላይ ተጎብራችሁ የዜግነት ክብንርን አውርዳችሁ የዜግነት ክብር የምታዘምሩ በሆናችሁ፣ በብሔር፣ በጎሳ ከፋፍላችሁ … ሰብዓዊ መብታችንን ገፋችሁ … ኑሮን መቋቋም እንዳንችል አድርጋችሁ ለስደት ስለዳረጋችሁን ሰላምስ ማለት አይገባም ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሃኢያን የተሰኘው ከባድ አዉሎነፋስ የፊሊፒንስን ምሥራቃዊ የባህር ዳርቻን ከመታ ዛሬ አራተኛ ቀን ተቆጠረ። የፈራረሱ ቤቶች መተላለፊያ መንገዶችን ዘግተዋል። የስልክ እና የመብራት መስመሮች ተቋርጠዋል።

በዛሬው የስፖርት ዝግጅት ለብራዚል 20ኛው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ግጥሚያ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን የፊታችን እሁድ ከናይጀሪያ ጋ የሚጠብቀው የመጨረሻ ጨዋታ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፣ እንዲሁም፣ የአዉሮጳ እግር ኳስ ክበቦች ባለፈው የሳምንት መጨረሻ ያደረጉዋቸው ግጥሚያዎች እና የሜዳ ቴኒስ ተካተዋል።

ሳዉዲ አረብያ የመኖርያ ፈቃድ የሌላቸዉን እና በሕገ-ወጥ መንገድ የሚኖሩ የዉጭ ሀገር ዜጎችን እያሳደደች ማሰር ከጀመረች ሳምንትን አስቆጥራለች። የኢትዮጵያ መንግስት በሳዉዲ የሚገኙ ዜጎቹን ወደ ሀገሩ ለመመለስ ማቀዱ ከተሰማ በኋላ ዛሬ፤

የአፍሪቃ ሚዲያ መሪዎች ጉባኤ ካለፈው ረቡዕ እስከ ዓርብ ድረስ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በዚህ ጉባኤ ላይ ከተካፈሉ ድርጅቶች መካከል ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተዉ ዓለም ዓቀፉ ድርጅት «ሲ ፒ ጄይ» ይገኝበታል።

ባለፈዉ ሐምሌ-ሐሰን ሩሐኒ ለፕሬዝዳትነት ሲመረጡ ፕሬዝዳንት ኦባማ ከአራት ዓመት በፊት ለዓለም ሠላም ከገቡት ብዙ ቃል-ኢምንቱን እንኳ ገቢር አላደረጉም።ከሰጡት አያሌ ተስፋ-አብዛኛዉ ከተስፋ አላለፈም።ያም ሆኖ ኦባማ ሲሆን እራሳቸዉን ካልሆነም ቢል ክሊንተንን እንጂ ጆርጆ ቡሽን እንዳልሆኑ አስመስክረዋል።

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ በአባቶቻችን ደም ታፍራና ተከብራ የኖረችው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በገዢው ፓርቲ ቸልታ፣ የፖሊሲ ችግርና የሀገር ፍቅር ማጣት የተነሳ ዜጎቿ በውርደት እንዲኖሩ ተፈርዶባቸዋል፡፡ ዛሬም መገለጫችን ስደት፣ ጦርነት፣ በዜግነታችን ክብር ማጣትና ሞት ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ሀገራዊ ውርደትና ሞት ከተበላሸ ሥርዓት የሚወለድ፣ ካልተስተካከለ የኢኮኖሚ ፖሊሲ የሚፈጠር ነው፡፡ ፓርቲያችን የተሻለ ኢኮኖሚ ፍለጋ፣ የተሻለ ማህበራዊ ፍትህ […]

እንደ ሰው አንድ የሚያደርገን ባሕርይ፣ እንደ ኢትዮጵያዊነትም ሁላችንንም የሚመለከተንና የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ልዩነት የማይነጣጥለው በደል በሳዑዲ አረብያ ግዛት እየተፈጸመ ነው። የጥቃት ዒላማዎቹ ኢትዮጵያውያን ናቸው። የጥቃቱ ልክ የለሽነትና አሰቃቂነት ደግሞ ይበልጥ የጎላው በሴት እህቶቻችን ላይ ነው። ይህ ዛሬ በሳዑዲ አረብያ የሚደረገው ጥቃትን ማስቆምና ቁጣችን መቆምያ እንደማይኖረው ማሳየት ለነርሱ ብቻ ሳይሆን ለራሳችን ደህንነትም ጭምር የምናደርገው ነው። ምክንያቱም ነገ ተመሳሳይ ጥቃትና በደል በመላው አለም ይስፋፋል። በአፍሪካ ሀገሮች የተበተኑ ኢትዮጵያን ከሶማሌና ኤርትራ ከሚሰደዱት በተለየ ይዘረፋሉ፣ ይደፈራሉ ይዋረዳሉ። እንደ አገር ልጅ አብረው እንዳይቆሙ በዘር በሀይማኖትና በፖለቲካ አቋም ምክንየት የተበተኑ ናቸው። ለሰላሳና አርባ አመት አምባገነኖች ያደረጉት ጭፈጨፋና በደል ፍርሃትን ሰማይ ጥግ አውጥቶታል። እናም ኢትዮጵያዊ በየተበተነበት ሁሉ ተኛ ሲሉት የሚተኛ አውልቅ ሲሉት እርቃኑን የሚቆም ፈሪ እንዲሆን ተደርጓል። ሲቸግረው የሚጮኸውን ያህል ሲመቸው ለወገን የሚደርሰው ጥቂቱ ነው። ይህ ሊቀጥል አይገባም!

ቀደም ባለው ጊዜ አንድ ኢትዮጵያዊ ጥቃት ቢደርስበት ባገኘው መሳርያ ዘነጣጥሎም ቢሆን ይገድል ስለነበር ማንም አይደፍረውም ነበር። በዘመነ ኮሎኒያሊዝም ኢትዮጵያውያን በሄዱበት ሁሉ አንገት የማይደፉና ክብራቸውን የማያስነኩ ነበሩ። ዛሬ ጠቁመው የሚያስይዙ፣ ወገናቸውን የሚያሻሽጡና የሚሰልሉት ሁሉ ኢትዮጵያውያን ናቸው። የዚህ ጽሁፍ መነሻም ሆነ መድረሻው የድሮውን አሁን እየሆነ ካለው ጋር ማወዳደር አይደለም። ለዚህ የሚሆን የቅንጦት ጊዜም የለንም። ዓላማው አሁን እየደረሰብን ያለውን በደል በቁርጠኛነት አንታገለው ነው። ይህ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ከዳር እስከዳር ማስነሳት ካልቻለና ቁጣቸውንም ለመላው አለም ማሳየት ካልቻለ እውነትም አገራችን እያበቃላት ነው ማለት ይቻላል።

የዱር አውሬ እንኳን ከዚህ የተሻለ ክብር አለው። እነዚህ አጅግ ሁዋላ ቀር የሆኑ አረመኔዎች ከእንስሳ እንኳን አንሰው አንዲት በፍርሃት ነብሷን የሳተችን ሴት አስር ሆነው የሚደፍሩትን እያየን የተደፈሩት ህጋዊ ናቸው ህገወጥ የሚል የሕግ አንቀጽ መረጣ ውስጥ ልንገባስ እንዴት ይቻለናል? በመላው አለም ያለ የሳዑዲ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ ሊደረግና የሳዑዲ ወሮበሎች በወጣት ሴቶች ላይ እያደረሱ ያለው ግፍ በመረጃም ተደገፎ በበራሪ ወረቀትም ተዘጋጅቶ ለአለም ሕዝብ ሊበተን ይገባዋል። ተፈጥሮ ዘይትን ስትቸራቸው አእምሮ ግን እንደነፈገቻቸው ከዚህ በላይ መረጃስ ከየት ይመጣል?
እንደ ትውስታ ከወሰድነው በኬንያ ያሉ ስደተኞች ላይ በደል ይደርስ በነበረበት ወቅት ያ በጨካኝነቱ የሚታወቀው መንግሥሰቱ ሀይለማርያም አንኳን “ኢትዮጵያውያኑ የተሰደዱት የምናራምደውን ፖለቲካ እንጂ ሀገራቸውን ጠልተው አይደለም…” በሚል ኬንያን ማስጠንቀቁን መስማቴ ትዝ ይለኛል። በየወሩ 40 ሺህ ሴቶችን እንልካለን እያለ እንደ እንቁላል በየአረብ ቤቱ ሲያከፋፍል የነበረው መንግስት ዛሬ ዜጎቹ እንዳይሆን መጫወቻ ሲሆኑ ዝም ብሎ መመልከቱ እጅግ የሚያሳዝን ነው። ኢትዮጵያውያኑ ምናልባትም ኤምባሲውን ራሱን መቆጣጠር የሚገባቸው እስኪመስል ያስቆጣል።
Image
በኢትዮጵያዊነት ላይ የተነጣጠረን ክፋት እንደ ሀገርና እንደ ሕዝብ ካላስቆምነው በሳዑዲ የተጀመረው መረን የጥላቻ ሰደድ ሊቀጣጥል የሚችልና የየሀገሩ የፖለቲካ ኪሳራ ማስተንፈሻ የሚሆነው አገር አጥቶ የተሰደደው ኢትዮጵያዊው ላይ ሁሉ ይሆናል። ይህንን በአስቸኳይ ለመቃወም ያሉ የትግል መንገዶች ሁሉ ክፍት ሊሆኑ ይገባል። እኔ አዘጋጀሁ እኔ ጠራሁ የሚል ደካማ የፖለቲካ ትርፍ ፍለጋ መንቀሳቀስ ሳይሆን ለሰብዓዊ ክብርና የመከራ ማጥ ውስጥ ሆነው የወገን ያለህ ለሚሉት እህት ወንድሞቻችን የድረሱልን ጥሪ ምላሽ እንስጥ። በጣም የሚያሳዝነው አብዛኞቹ ለስራ የሚሄዱት ወጣቶች የትምህርት ደረጃቸው አነስተኛ የሆነና በድህነት ውስጥ ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት የሆነው ይሁን ብለው ከቤታቸው የወጡ ናቸው። አንዳንዶቹም ግሩም እድል አንደሚገጥማቸው በደላላዎች እየተነገራቸው ከቤት ወጥተው የቀሩ ናቸው። ለኒህ አጋር መሆን ለሀገር እንኳን ደንታ ባይኖረን ለነብስ የሚበጅ ስራ ነው። የኢትዮጵያ ኮሙኒቲዎች፣ በኢትዮጵያ ስም የተቋቋሙ የሀይማኖት ማዕከላት፣ ሲቪክ የፖለቲካ ድርጅቶች በሙሉ ለዚህ ዓላማ ቢቻል አደራጆች ካልተቻለም ዋንኛ ተሳታፊዎች ሊሆኑ ይገባል። ይህ በደል እጅ ለእጅ ሊያስተሳስረንና አንድ ላይ እንድንቆም ሊያደርገን የሚችል የጋራ ጉዳይ ነው። ዛሬ ነገ ሳንል በተደራጀና አለም አቀፍ ትኩረት ሊኖረው በሚያስችል አቅሙ እንነሳ ለወገንም አንድረስ።የመከራ ቀናችንን ለማሳጠር እንደ ሕዝብም ከአንገታችን ቀና እንድንል በያለንበት እንትጋ!

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ እየታካሄደ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዞን ምክር ቤት 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በመገኘት በሀገራችን ኢትዮጵያ ባለው የፖለቲካ፤ የዲሞክራሲ እና የፍትህ እጦት እንዲሁም ሁሉንም ኢትዮጵውያንን የሚያሣትፍ የኢኮኖሚ እድገት ባለመኖሩ ምክንያት ብዙ ዜጎች ወደ ደቡብ አፍሪካ ሃገራትና ወደ አረብ ሀገራት በእግር ሳይቀር ለመሰደድ ከመገደዳቸው በተጨማሪ በጉዞ ወቅት በአውሬ መበላት በበሽታ […]

ሰሞኑን የኢሕአዴግ መንግሥት ይፈራል አይፈራም የሚል ጉዳይ ከፓርላማ ተነስቶ ወደ መገናኛ ብዙኃንም ደርሷል። ጉዳዩ የተነሳው የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ አዲሱ ፕሬዚዳንታችን በፓርላማ ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ ባቀረቧቸው የማማሻሻያ ሐሳቦችና ጠቅላይ ሚኒስትራችን በሰጡት ምላሽ ዙሪያ ነው። ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዝ ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት 13 ቀን 2006 ዓም በአወጣው ዕትሙ ‹‹’ፈሪ’ መንግሥት?›› በሚል ርዕስ ጋዜጠኛ የማነ ናግሽ ጥሩ […]

ኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር ሲዘመር ከሚያነሣቸው ነጥቦች መካከል ‹የዜግነት ክብር› የሚለው የተለየ ስሜት ይሰጠኛል፡፡ ለአንዲት ሀገር ሰው ትልቁ ዋጋው ‹የዜግነት ክብር› ነው፡፡ ሀገር አለኝ ብሎ ማሰብ፤ የሚያስብልኝ፣ የሚጮህልኝ መንግሥት አለኝ ብሎ ማመን፤ የእኔ ጉዳይ ጉዳዩ የሆነ አካል አለ ብሎ መመካት፡፡

እንዲህ እንደ ሰሞኑ ያለ፣ በሳዑዲ እየተፈጸመ እንዳለው ነገር ያለ ስናይና ስንሰማ ደግሞ ‹የዜግነት ክብር› መዝሙር ብቻ ይሆንብናል፡፡ ‹ኢትዮጵያዊ ማለት› ብለን ልንተረጉም ይቸግረናል፡፡ ማንም  የአራዊት ጠባይ ያለው ሁሉ ተነሥቶ መንገድ ላይ ደሙን የሚያፈሰው፣ እግሩን የሚቆርጠው፣ የሚደበድበውና በፈለገበት ቦታ የሚያሥረው ከሆነ፣ ይህማ እንኳን የዜግነት ክብር የስደተኛነት ክብርም አላገኘም ማለት ነው፡፡ ሀገር አልባ ጂፕሲዎች ከሚደርስባቸው ግፍ በላይ ባለሀገሩ ኢትዮጵያዊ ከደረሰበትማ ‹የዜግነት ክብር› የቱ ላይ ነው፡፡ ደግሞስ በአንድ ኢትዮጵያዊ ላይ ሰው መሆኑን የሚያጠራጥር ከዚህ በላይ ምን ሊደርስበት ይችላል፡፡

ይህ ነገር ሁለት ነገሮችን እንድናስብ ማድረግ አለበት፡፡

1.   የመንግሥት አካላት በየሀገሩ ያሉትን ዜጎቻችንን ለማወቅ፣ ለመከታተልና መብታቸውን ለማስከበር ያላቸውን ብቃት

2.እንዲህ ዓይነት ነገር በሌላ ጊዜና በሌላ ሀገር እንዳይደገም ልናደርገው የሚገባንን ዘላቂ መፍትሔ

የዜግነት ክብር የሚኖረው አንድ ዜጋ የትም ቦታ ቢኖር የዜግነት መብቱ እንዲከበርለት፣ በዜግነቱ እንዲኮራና የዜግነቱንም ግዴታ እንዲወጣ ሲደረግ ነው፡፡

ይህ የዜግነት ክብር እንዲጠበቅ መንግሥት፣ የዲፕሎማቲክ ሚሽኖች፣ የዲያስጶራ ማኅበረሰቦችና ጠቅላላው ሕዝብ ከዚህ ጊዜ የተሻለ የመንቂያ ጊዜ አያገኙም፡፡ ይህንን ለማሰብ እስከዛሬ የፈሰሰው ደም በቂ ካልሆን፤ የሚያስፈልገን የስንት ሰው ደም ይሆን?