የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ፕሬዘዳንት ዶክተር ጫኔ ከበደ በትናንትናው ምርጫ ፓርቲያቸው ከሞላ ጎደል በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ባሉ አባላቱና ታዛቢዎቹ ላይ ጫና ሲደረግባቸው እንደነበር ገለጹ፡፡ አጠቃላይ የምርጫው ሂደት አሳፋሪ ነው ያሉት ፕሬዘዳንቱ በርካታ ምርጫ ታዛቢዎቻችን የታዛቢነት ካርዳቸው ተነጥቆ ከምርጫ ጣቢያዎች ተባረዋል ሲሉ ከሰዋል፡፡ “በዚህ ሁኔታ የሚካሄድ የድምጽ ቆጠራ በትክክል ይካሄዳል ብለን አናምንም፡፡ የዚህን ምርጫ ውጤት ለመቀበልም […]

ወኪላችን እንደዘገበው በሰቆጣ አካባቢ የተከሰተውን ከፍተኛ ድርቅ ተከትሎ አርሶደአሮቹ ወደ ምእራብ ጎጃምና ሌሎች የአማራ ክልል አካባቢዎች በመሰደድ ላይ ናቸው። ተፈናቃዮቹ ከክልሉ ባለስልጣናትም ይሁን ከፌደራል መንግስቱ ምንም አይነት እርዳታ አለማግኘታቸውን ገልጸዋል። ብዙዎቹ ተፋናቃዮች ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሲሆኑ፣ በሰፈሩባቸው አካባቢዎች ስራ ሰርተው ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ እየጠየቁ ነው። ተፈናቃዮቹ በዝናብ እጥረት ምክንያት ሰብላቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን ገልጸዋል። መንግስት በአካባቢው […]

ራሳቸው በሚወዳደሩበት ምርጫ ያልመረጡ የመጀመሪያው የፓርቲ መሪ ሆኑ
Dr. Merera Gudina. ዶ/ር መረራ ጉዲና

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. May 24, 2015)፡-  በኢህአዴግ ተቃዋሚነት የብዙዎች ድጋፍ እንዳላቸው የሚታመነው የኦፌኮ (የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ) ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ዛሬ በተካሄደው ምርጫ ድምጻቸውን መስጠት (መምረጥ) አለመቻላቸው ታወቀ። ዶ/ር መረራ ፓርቲያቸውን ወክለው በተወለዱበት የጉደር ከተማ ተወዳዳሪ ቢሆኑም፤ ለራሳቸውም ይሁን ለሌላ ሰው ድምጻቸውን የሚሰጡበትን የምርጫ ካርድ በሰዓቱ ባለማውጣታቸው ዛሬ መምረጥ ሳይችሉ ቀርተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አዲስ አበባ ፀጥ እንዳለች ውላ አመሸች
Voters queue early in the morning to cast their votes in Ethiopia’s general election, Sunday May 24, 2015, in Addis Ababa, Ethiopia. Ethiopians voted Sunday in national and regional elections, the country’s first since the 2012 death of its longtime leader, but the ruling party is expected to maintain its iron-clad grip on power. (Mulugeata Ayene/Associated Press)

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. May 24, 2015)፡-  ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት የተካሄደውና የተጠናቀቀው ምርጫ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት አራት ምርጫዎች እጅግ የቀዘቀዘ መሆኑ ታወቀ። ተቃዋሚዎች ፓርቲዎች በታዛቢነት የመደቧቸው ሰዎች ምርጫውን እንዳይታዘቡ ጫና እንደተደረገባቸው ብሎም እንደታሰሩባቸው ገልጠዋል፤ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ በምርጫ ከተሳተፉት ፓርቲዎች ምንም አይነት ቅሬታ እንዳልደረሰው ገልጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopian election 2007 report by Aljazeera

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. May 24, 2015)፡- ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በተካሄደው ምርጫ ገዥው ፓርቲ ምርጫውን ያሸንፋል ተብሎ ይጠበቃል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል። አልጀዚራ በዚሁ ዘገባው ተቃዋሚዎች በገዥው ፓርቲ እንደሚዋከቡ፣ የምርጫ ቅስቀሳ እንዳያደርጉ መታገዳቸውንና የፓርቲ አባላቶቻቸው እንደታሰሩባቸው አትቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopian election 2015. እረጭ ያለው ምርጫበኢትዮጵያ የተካሄደውን የ2007ቱን ምርጫ አስመልክቶ የቪኦኤ ጋዜጠኛ ሰለሞን አባተ ባጠናከረው ዘገባ፣ “አዲስ አበባ ውስጥ ከባነሮቹና እጅግ ከተጋነነው የሙዚቃ ጩኸት በተረፈ አገሪቱ በ90 ሚሊዮን ሕዝብ የተመላች አትመስልም፤ ባልተለመደ ሁኔታ እረጭ ያለ ምርጫ” በማለት የምርጫውን ሁኔታ ገልጦታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዛሬ የተካሄደዉን የኢትዮጵያ አምስተኛ ዙር ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ በርካታ የዶይቼ ቬለ ተከታታዮች አስተያየታቸዉን ልከዉልናል። ምርጫዉን አስመልክተንከዚህ ከቦን ስቱዲዮአችን ወደ ኢትዮጵያ በመደወል የተለያዩ አስተያየቶችንም አሰባስበናል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ የመደባቸው 4 የምርጫ ታዛቢዎች በገዢው ፓርቲ ተላላኪዎች መደብደባቸው ተዘገበ:: ምስራቅ ስቴ የተበደቡ የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢዎች 1. ታደለ ግዛው (ዳጉት ቀበሌ) 2. እሱ ያውቃል በላይ (ለዋዬ ቀበሌ) 3. ገብሬ ተፈራ (ደንጎልት ቀበሌ) 4. መልካሙ ነጋ (አበርጉት ቀበሌ) በተጨማሪም ይስማው ወንድሙ የተባለ የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢ በጥይት መሳቱን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ***** ‹‹ጋሞ […]

በአቦ በባድዮ ጉደር አምቦ ምርጫ ጣቢያዎች ምርጫውን ከቁጥጥር ውጪ ያደረጉ ችግሮች የተፈጠሩ ሲሆን በየምርጫ ጣቢያዎቹ የኢሓዴቅ የቅስቀሳ ፖስተሮች ተለጥፈዋል::ይህን ተከትሎ በጉደር ከፍተኛ የሆነ የጸጥታ መደፍረስ ተፈጥሯል::በታዛቢዎች እና በምርጫ ባለስልጣናት መካከል ከፍተኛ አለመግባባቶች ተፈጥረው እስከ ድብድብ ተደርስል::‹‹ከንብ ውጭ ምልክት የለም፡፡ ከዛም ካርድ ይቀዳሉ፡፡ ሶስት ቀበሌዎች ተዘዋውሬ አይቻለሁ፡፡ መምህራን ስለሚጠይቁ ችግር እየደረሰባቸው ነው፡፡ ይህ ምርጫ ይበላል?›› ኦሮሚያ […]

አቶ ዮናታን ተስፋዬ          -               አቶ ደምሰው በንቲ

–  ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቅሬታ አልደረሰኝም ብሏል

በአምስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ የሆኑ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫውን እንዲታዘቡ ያሰማሯቸው ግለሰቦች በተለያዩ ጫናዎች ምክንያት መገለላቸውን ገለጹ፡፡ የክልል የምርጫ ኃላፊዎች ክልከላው የተከናወነው ሕጉን መሠረት አድርጎ ነው ያሉ ሲሆን፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግን ከየትኛውም ፓርቲ ቅሬታ አልደረሰኝም ብሏል፡፡ 

ሰማያዊ ፓርቲ በተመሳሳይ በባሌ፣ በየም፣ በሲዳማና በደብረ ማርቆስ ያሰማራኋቸው ታዛቢዎች ተባረዋል ብሏል፡፡ በሐዋሳ ከተማ ከተሰማሩ ታዛቢዎች ሦስት አራተኛው እንዲሁ ለእስር ተዳርገዋል ያለው ሰማያዊ፣ አንዳንዳቹ በሚሊሻ ተከበው በቤታቸው በቁም እስር ላይ እንደሚገኙ የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡

መድረክ በበኩሉ በሐዋሳ ከተሰማሩ የፓርቲው ታዛቢዎች መካከል 60 በመቶ የሚሆኑት መታሰራቸውን በአካባቢው መድረክን ወክለው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩት ዶ/ር አየለ አሊቶ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ መድረክ በተመሳሳይ በመቐለ ያሰማራቸው ታዛቢዎች በተለያዩ ጫናዎች ራሳቸውን ከታዛቢነት ማግለላቸውን ገልጿል፡፡ 

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲም እንዲሁ በሐዋሳ ያሰማራቸው ታዛቢዎች መባረራቸውን ገልጿል፡፡ የአካባቢው የምርጫ ማስተባበሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ዱካሞ የሌላ ፓርቲ የታዛቢነት መታወቂያ ይዘው በመገኘታቸው ጉዳዩ እየተጣራ እንደሆነ ገልጸው፣ ግለሰቦቹ እንደሚፈቱ አስታውቀዋል፡፡

በባህር ዳር ከተማ ኢዴፓ ያሰማራቸው ከ60 በላይ ታዛቢዎች ቢኖሩትም፣ ድምፅ በመስጪያው ቀን ከ155 የምርጫ ጣቢያዎች በጣት የሚቆጠሩ ነው የተገኙት፡፡ ይህን በተመለከተ ሻምበል ያየህራድ ዘለቀ የባህር ዳር ከተማ ኢዴፓ አመራርና የተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ ለሪፖርተር፣ ‹‹አብዛኛዎቹ የፓርቲው ታዛቢዎች በምርጫ ጣቢያው ያልተገኙበት ምክንያት አላውቅም ፈርተው ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም በሁለት ምርጫ ጣቢያዎች ግን መታወቂያ ላይ ፎቶ አለጠፋችሁም ተብለው ከመግባት ተከልክለዋል፤›› ብለዋል፡፡ በባህር ዳር ምርጫ ክልል 115 የምርጫ ጣቢያዎች እንዳሉ ምርጫ ቦርድ ቢያሳውቅም፣ ኢዴፓ በደብዳቤ የተገለጹለት 111 ብቻ መሆናቸውን ሻምበል ያየህራድ ገልጸዋል፡፡

መኢአድም በሰሜን ሸዋ ዞን በደረሰባቸው ወከባ ታዛቢዎች ማሰማራት እንዳልቻለ የዞኑ የመኢአድ ምርጫ አስተባባሪ ሻምበል ባሻ አበራ በቀለ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደምሰው በንቲ፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአንድም ፓርቲ በጉዳዩ ላይ ቅሬታ እንዳልደረሰው ጠቁመዋል፡፡ ‹‹ተቃዋሚ ፓርቲዎች የምርጫ ታዛቢዎቻቸውን እንዲያሳውቁ በሰጠናቸው ጊዜ ብዙ ፓርቲዎች አልተጠቀሙም፡፡ በመሆኑም ጊዜውን አራዝመን ነበር፡፡ ከተራዘመም በኋላ ያላሳወቁ አሉ፡፡ በሕጉ እንዲያሳውቁ የሚያስገድድ ነገር ስለሌለ ዝም ብለናል፤›› ያሉት አቶ ደምሰው፣ ምናልባትም ይህን መታወቂያ ያልያዙ ሰዎች በታዛቢነት ቀርበው ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ቅሬታዎች የሚመጡት ከታችኛው እርከን ወደ ላይ በመሆኑ፣ ከክልል የምርጫ ኃላፊዎች ሲያልፍ ብቻ ወደ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንደሚመጣ አስገንዝበዋል፡፡ 

 

እሑድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በመላ አገሪቱ ድምፅ የመስጠት ሥነ ሥርዓት ተጀምሯል፡፡ ሪፖርተር ከአዲስ አበባ ከተማና ከተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች ዘገባዎችን ያስተላልፋል፡፡ በዚህም መሠረት አንባቢያን ድረ ገጹን እንዲጎበኙ እናሳስባለን፡፡

ደቡብ ክልል

በደቡብ ክልል በወላይታ ዞን በቦሎሶ ሶሬ ምርጫ ክልል 01 ጠቅላላ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ድምፃቸውን ይሰጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ሲሆን፣ መራጮች ቤተ ክርስቲያን በመሄዳቸው ምክንያት የመራጮች ቁጥር ዝቅተኛ እንደነበር ሪፖርተራችን ዘግቧል፡፡ በዚህ ምርጫ ከመድረክ በስተቀር ሌሎች የተቃዋሚ ፓርቲ ዕጩዎች ይወዳደራሉ፡፡ በወላይታ ዞን ሐረካት 3 የምርጫ ጣቢያ የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ተክለ ወልድ አጥናፉ ደኢሕዴግ/ኢሕአዴግን ወክለው ይወዳደራሉ፡፡ በእዚህ ምርጫ ክልል መራጮች በብዛት ታይተዋል፡፡ የመድረኩ ፕሮፌሰር በየነና የደኢሕዴግ/ኢሕአዴግ አቶ ዮሴፍ ዳኢሞ የሚወዳደሩበት የሐዲያ ዞን ማካማ 02 ምርጫ ክልል መራጮች በብዛት ወጥተው እየመረጡ ነው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ታዛቢዎችም አሉ፡፡

አዲስ አበባ

ምርጫ ክልል 17

የአዲስ አበባ ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በቀለ ከኢሕአዴግ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ፣ የኢዴፓ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ወንድወሰን ተሾመ እንዲሁም የኢራፓ ፕሬዚዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮን ያገናኘው የምርጫ ክልል 17 ምርጫ በከፍተኛ ተሳትፎ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ሪፖርተር ተዘዋውሮ ባያቸው የምርጫ ጣቢያዎች ቺቺንያ አካባቢ ከሚገኝ አንድ ጣቢያ በስተቀር ረጃጅም ሠልፎች ታይተዋል፡፡ 

ይህ ነው የሚባሉ ግድፈቶች ባይስተዋሉም በአብዛኛዎቹ የምርጫ ጣቢያዎች የተቃዋሚ ፓርቲዎች ታዛቢዎችን አላስቀመጡም፡፡ በተጨማሪም የምርጫ ሒደቱ ላይ ማብራሪያ እየተሰጠም ጭምር ምን ማድረግ እንዳለባቸው ምንም ዓይነት ግንዛቤ የሌላቸው መራጮችም ታይተዋል፡፡
       

. በኖርዌይ የሚኖሩ 29  የወያኔ ስላዮች ላይ ህጋዊ እርምጃ ሊወስድ መሆኑ ተነገረ . አባይ ፀሃየ፤ ስዩም መስፍንና  ፀጋይ በርሄ ድርጅታችሁን አድኑ ብለው ቢማጸኑም የቀድሞ ታጋዮች አለመቀበላቸው ተነገረ . የኢትዮጵያ ጦር የኬንን ድንበርን ለሶስተኛ ጊዜ ማለፉ ተዘገበ . የወያኔ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር በደብረማርቆስ ተቃውሞ ገጠማቸው . በትጥቅ ትግል ለዉጥ ለማምጣት የሚታገሉ ድርጅቶች የጥምረት ስምምነት ተፈራረሙ . […]

ምርጫ 2007

እሑድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ሒደት በጊዜ ሰሌዳው መሠረት፣ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፎ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡

በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስፈጻሚነት በሚካሄደው አምስተኛ ጠቅላላ ምርጫ፣ ከ36.8 ሚሊዮን በላይ መራጮች ተመዝግበው ድምፅ እንደሚሰጡ ሲጠበቅ፣ በመላ አገሪቱ 46 ሺሕ ምርጫ ጣቢያዎች መራጮችን ለማስተናገድ ተዘጋጅተዋል፡፡ በምርጫ ቦርድ መረጃ መሠረት እስካሁን ድረስ 319 ሚሊዮን ብር የወጣበት የዘንድሮ ጠቅላላ ምርጫ በርካታ ክስተቶች የታዩበት ሲሆን፣ በምርጫው ለመወዳደር ተመዝግበው የምርጫ ምልክቶች ከወሰዱ 58 ፓርቲዎች መካከል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) እና ሰማያዊ ፓርቲዎች ከምርጫ ቦርድ ጋር ሲነታረኩ ከርመዋል፡፡ ሰሞኑን ደግሞ በመጨረሻው ምዕራፍ በደቡብ ክልል በካፋ ዞን፣ በጊምቦ የምርጫ ክልል በግል ተወዳዳሪው ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስና በደኢሕዴግ/ኢሕአዴግ ዕጩ ዶ/ር መብራቱ ገብረ ማርያም ደጋፊዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ምርጫው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ አስገድዷል፡፡ በገጽ 6 ላይ የተስተናገደው የነዓምን አሸናፊ ዘገባ ከምርጫ 2007 ጋር የተገናኙ በርካታ ክስተቶችን ያስቃኛል፡፡  

 

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ

አምስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከመከናወኑ ከቀናት በፊት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጥያቄ ጊዜ ላይ እንዲገኙ የተደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ እሑድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚካሄደው ምርጫ ውጤት ይፋ የማድረግ ሥልጣን ያለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ብቻ ነው አሉ፡፡   

በፓርላማው የአሠራር ሥነ ሥርዓት ደንብ መሠረት ፓርላማው በወር አንድ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የመጥራትና የመጠየቅ ሥልጣን አለው፡፡ በዚሁ መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ተገኝተው በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቅድመ ምርጫው ሒደት ከሞላ ጎደል ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንደነበር መገምገሙን ተናግረዋል፡፡ 

‹‹እጅግ አብዛኞቹ የአገራችን ፓርቲዎች ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ያላቸውን ፍላጎት አሳይተዋል፡፡ ይኼ እጅግ አበረታች ነው፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹የምርጫው ዕለትና ከዚያም በኋላ ያለው በዚህ መልኩ ሊቀጥል እንደሚችል አመላካች ነው፤›› ብለዋል፡፡ 

ይሁን እንጂ አንዳንድ ለሰላማዊ ምርጫ በሙሉ ልባቸው ያልገቡ ፓርቲዎች መኖራቸውን፣ በተግባር የታየውን ሰላማዊ እንቅስቃሴ የማደፍረስ እንቅስቃሴ ውስጥ ናቸው በማለት ወቅሰዋል፡፡ 

‹‹አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ገና ከወዲሁ አሸንፈናል እያሉ እየቀሰቀሱ ነው፡፡ ይህንን የሚያደርጉት በግዳጅም ቢሆን ድምፃችንን ማስመለስ አለብን ብለው ለማነሳሳት ነው፤›› ብለዋል፡፡

ይህንን የሚያስቡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች የመጨረሻ ውጤቱ ጥሩ እንደማይሆንና ተመልሶ የሚበላው ራሳቸውን መሆኑን አውቀው በጥንቃቄ እንዲይዙት አስጠንቅቀዋል፡፡

‹‹ገዥው ፓርቲም ሆነ ተቃዋሚዎች ሥርዓቱን ጠብቀን ነው መሄድ ያለብን፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ ‹‹የምርጫውን ውጤት ገላጭ የምርጫ ቦርድና የምርጫ ቦርድ ብቻ ነው፤››  ብለዋል፡፡

ምርጫውን ለመታዘብ ፈቃድ ያገኙት የአፍሪካ ኅብረትና የኢትዮጵያ ሲቪክ ማኅበራት ጥምረትም ቢሆኑም፣ ትዝብታቸውን ከመናገር ውጪ ውጤት የመግለጽ ኃላፊነት የላቸውም ብለዋል፡፡ 

ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ ይቀጥላል የሚል ግምገማ ቢኖርም፣ አልፎ አልፎ የሚታዩ የግጭት ምልክቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ ነገር ግን የአንድ ሉዓላዊ መንግሥት ኃላፊነት ሕግና ሥርዓትን ማስከበር በመሆኑ መንግሥታቸው ለአንድ አፍታ እንኳን ‹‹ሸብረክ›› እንደማይል አስታውቀዋል፡፡

 

 

ሟች ሃና ላላንጎ ይህቺ ነበረች

– ከ17 ዓመታት እስከ ዕድሜ ልክ እስራት ተፈረደባቸው

ሃና ላላንጎ የተባለችውንና 16 ዓመቷ እንደሆነ የተነገረውን ታዳጊ፣ አስገድደውና ተፈራርቀው በመድፈር ለሞት መዳረጋቸው ተረጋግጦ ጥፋተኛ የተባሉት የታክሲ ሾፌሮችና ረዳቶቻቸው፣ ግንቦት 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ከ17 ዓመታት እስከ ዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተፈረደባቸው፡፡

የክስ ሒደቱን በዝግ ችሎት ሲሰማና ሲመረምር የከረመው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሦስተኛ ወንጀል ችሎት በአብላጫ ድምፅ በዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የፈረደባቸው፣ አንደኛ ተከሳሽ ሳምሶን ስለሺና ሁለተኛ ተከሳሽ በዛብህ ገብረ ማርያም ናቸው፡፡

እንዳልተማረና ነገሮችን ማገናዘብ እንደማይችል የቅጣት ማቅለያ ቢያቀርብም፣ በማስረጃ የተደገፈ ባለመሆኑ ፍርድ ቤቱ ያልተቀበለው ሦስተኛ ተከሳሽ በቃሉ ገብረ መድኅን በ17 ዓመታት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተፈርዶበታል፡፡ አራተኛው ተከሳሽ ኤፍሬም አየለ በ20 ዓመታት ጽኑ እስራት፣ አምስተኛው ተከሳሽ ተመስገን ፀጋዬ በ18 ዓመታት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ በልዩነት ፍርድ ሰጥቷል፡፡ 

ፍርደኞቹ ከዚህ በፊትም የተለያዩ ወንጀሎችን ፈጽመው የተቀጡ መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ ገልጿል፡፡ ዓቃቤ ሕግ ለቅጣት ማክበጃ ባቀረበው ሰነድ ላይ እንደተረጋገጠው አንደኛ ተከሳሽ በቅሚያ፣ ሁለተኛ ተከሳሽ አስገድዶ በመድፈር፣ ሦስተኛ ተከሳሽ ደግሞ በስርቆት ተፈርዶባቸው የነበረ ሲሆን፣ ሁሉም ፍርደኞች ቀደም ብሎ የተፈረደባቸውን ቅጣት ፈጽመው ከወጡ አምስት ዓመታት እንኳን ሳይቆዩ፣ በሃና ላይ ሌላ የወንጀል ድርጊት በመፈጸማቸው ቅጣቱን ከፍ እንዳደረገባቸውም ፍርድ ቤቱ አስታውቋል፡፡

18 ዓመት ያልሞላትንና ልዩ ጥበቃ የምትፈልግን ታዳጊ፣ ጭካኔ በተሞላበትና ለሕሊና (ሞራል) ተቃራኒ በሆነ መንገድ ተፈራርቀው በመድፈርና ከፍተኛ ደም እየፈሰሳት መንገድ ላይ አውጥተው በመጣል ከባድ ወንጀል መፈጸማቸውን፣ ዓቃቤ ሕግ ባቀረበባቸው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች መረጋገጡን ፍርድ ቤቱ በአብላጫ ድምፅ አስረድቷል፡፡

ፍርድ ቤቱ ክስ ከመስማት እስከ ውሳኔ (ጥፋተኛ እስከተባሉበት) ድረስ ችሎቱን ዝግ አድርጎ የነበረ ቢሆንም፣ ፍርዱን ግን በግልጽ ችሎት ወስኗል፡፡ 

ሃና ላላንጎ በመስከረም ወር 2007 ዓ.ም. ትምህርት ቤት ውላ ስትመለስ፣ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አየር ጤና አካባቢ ስትደርስ፣ አንድ ሚኒባስ የያዘ ወጣት “እንሸኝሽ” ብሎ ካስገባት በኋላ፣ ከረዳቱ ጋር በመሆን ወደ ጦር ኃይሎች አካባቢ ይዘዋት ይሄዳሉ፡፡ አንድ ቤት ውስጥ ይዘዋት ካመሻሹ በኋላ፣ በዚያው ክፍለ ከተማ ከቀራኒዮ መድኃኒዓለም ከፍ ብሎ ታጠቅ መንገድ ላይ ይዘዋት በመሄድ፣ ጓደኛቸው በተከራየበት አንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ባለ አንድ ክፍል ቤት ይዘዋት እንደገቡ፣ ፖሊስ በጊዜ ቀጠሮው ወቅት በግቢው የነበሩ እማኞች በመጥቀስ አስረድቷል፡፡ 

እንደ ፖሊስ የምርመራ ውጤት፣ ሃናን ከወሰዷት ሾፌርና ረዳቱ በተጨማሪ ሌሎች ሦስት ሰዎች እዚያው ስለነበሩ ሌሊቱን ለአምስት እየተፈራረቁ እንደደፈሯት፣ ሃና በመጨረሻዎቹ ቀናት እንደተናገረችም አመልክቷል፡፡ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ባደረሱባት የመድፈር ጥቃት ደም ሲፈሳት፣ ጦር ኃይሎች አካባቢ ሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን አጥር ሥር ተጥላ መገኘቷም በወቅቱ ተነግሯል፡፡ 

እህትና ወንድሟ ጦር ኃይሎች አካባቢ እንዳገኟት ወደ አለርት ሆስፒታል የወሰዷት ቢሆንም፣ በቂ ሕክምና ሳታገኝ ቆይታ ወደ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ሪፈር ብትደረግም፣ በተመሳሳይ ሁኔታ ያለምንም ሕክምና ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሪፈር መደረጓን መዘገቡ ይታወሳል፡፡ ጋንዲ ሆስፒታልም ወደ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ሪፈር አድርጓት፣ ዘውዲቱ ሆስፒታል የቻለውን ዕርዳታ እንዳደረገላት ተገልጿል፡፡ ሐና በደረሰባት ጉዳት አፋጣኝ የሕክምና ዕርዳታ ባለማግኘቷ፣ ብዙ ደም ፈሷት ስለነበርና ጉዳቱም ወደ ኢንፌክሽን ተቀይሮ ስለነበር ሕይወቷ ሊተርፍ አልቻለም፡፡ መስከረም 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡

 

 

 

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በአዲስ አበባ ከተማ ያለውን የመኪና ማቆሚያ (ፓርኪንግ) ችግር ለመፍታት፣ ለአልሚዎች መሬት እንዲቀርብ ከሁለት ሳምንት በፊት መመርያ መስጠቱን ምንጮች ገለጹ፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርበት እየተከታተለ 48 ቦታዎች ላይ ለመኪና ማቆሚያ (ፓርኪንግ) የሚያገለግሉ ሕንፃዎች እንዲገነቡ እንዲያደርግ መመርያ መስጠቱንም ጠቁመዋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰሎሞን ኃይሌ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ትዕዛዙ መስጠቱን ባያረጋግጡም፣ ለፓርኪንግ አገልግሎት የሚውሉት ቦታዎች ተለይተው መዘጋጀታቸውን ግን ገልጸዋል፡፡ 

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ይህን መመርያ ሊሰጥ የቻለው የሊዝ አዋጁና መመርያው ለመኪና ማቆሚያ ቦታ በመስጠት በኩል ክፍተት ያለበት በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡ የአገር ውስጥና የውጭ አገር አልሚዎች በተለያዩ ጊዜያት ለማኅበራዊ አገልግሎቶች ማለትም ለሆቴል፣ ለሆስፒታል፣ ለሞል፣ ለሪል ስቴትና ለመኪና ማቆሚያ የሚውል ቦታ እንዲሰጣቸው ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡ 

ነገር ግን አስተዳደሩ እነዚህን የቦታ ጥያቄዎች ላስተናግድ ቢል እንኳ በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ 21 እና በአገራዊ ፋይዳ መመርያ ቁጥር 15/2005 ላይ በግልጽ እንደሰፈረው፣ ‹‹ልዩ አገራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች›› የሚባሉት በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጡ የልማት ፕሮጀክቶች ወይም የትብብር መስኮች ለማስፋት ለሚደረጉ እንቅስቃሴዎች መሠረት እንዲጥሉ በመንግሥት የታቀዱ ፕሮጀክቶች ናቸው የሚል በመሆኑ፣ ለመኪና ማቆሚያ የሚያገለግሉ ሕንፃዎች ለመገንባት ቦታ መፍቀድ ከሊዝ አዋጁ ጋር ይጋጫል ተብሏል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ባለሙያዎች ከአልሚዎች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ለማስተናገድ መቸገራቸውን መግለጻቸውን፣ የከተማ አስተዳደሩም የሊዝ አዋጁ እንዲሻሻል ጥያቄ ማቅረቡን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 

አዳዲስ የቦታ ጥያቄዎች እስካሁን ምላሽ ባያገኙም የአዲስ አበባ የመኪና ማቆሚያ ችግር ሥር እየሰደደና ለከተማው ትራንስፖርት ፍሰት ማነቆ ሆኗል በሚል፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጣልቃ መግባቱን ምንጮች አመልክተዋል፡፡ 

ምንጮች ጨምረው እንደገለጹት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ሞዴል ፓርኪንግ ሕንፃዎችን እንዲሠራና የግል ባለሀብቶች ደግሞ ፕሮጀክታቸው እየታየ በልዩ ሁኔታ እንዲስተናገዱ ነው መመርያው የተሰጠው፡፡ 

ሌሎቹ ማኅበራዊ ፋይዳ ፕሮጀክቶች በምን መንገድ እንደሚስተናገዱ የተሰጠ አቅጣጫም ሆነ የአዋጅ ማሻሻያ እንዳልተደረገ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የመኪና ማቆሚያ ችግር መኖሩ ይታወቃል፡፡ 

 

ባንክ ለማቋቋም በምሥረታ ላይ እንዳሉ ያስፈልጋቸው የነበረውን ካፒታል ማሟላት ሳይችሉ የቀሩና በተለያዩ ምክንያቶች ሳይቋቋሙ ከቀሩ የግል ባንኮች ላይ አክሲዮን ገዝተው የነበሩ ባለአክሲዮኖች፣ ገንዘባቸውን እንዲወስዱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ  አሳሰበ፡፡

ብሔራዊ ባንክ ሳይቋቋሙ በጅምር ከቀሩት ከዘምዘም፣ ከኖኅ፣ ከፀሐይ፣ ከሐዋሳ፣ ከኮከብ፣ ከመርካቶ ሲቲና ከአፍሪ አግሮ ኢንዱስትሪ ባንኮች አክሲዮን ገዝተው የነበሩ ባለአክሲዮኖች፣ ገንዘባቸውን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. መውሰድ እንደሚኖርባቸው አሳስቧል፡፡

ከተጠቀሱት ባንኮች አክሲዮን ገዝተው እስካሁን ያልወሰዱ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች ከአደራጅ ኮሚቴዎቹ ክፍያ የሚገባቸው ለመሆኑ መረጃ በመያዝ ገንዘባቸውን ሊወስዱ እንደሚችሉ፣ የብሔራዊ ባንክ ማሳሰቢያ ያስረዳል፡፡ ገንዘብ አለን የሚሉት ወገኖች ለአክሲዮን ግዥ አውለውት የነበረውን ገንዘብ መውሰድ የሚችሉት፣ ባንኮቹን ለማቋቋም አክሲዮን ግዥ ካከናወኑበት የባንክ ቅርንጫፎች እንደሆነም ገልጿል፡፡

ከብሔራዊ ባንክ የተገኘው ተጨማሪ መረጃ እንደሚጠቁመው፣ ብሔራዊ ባንክ ገንዘባቸውን ላልወሰዱ አክሲዮን ገዥዎች ይህንን መልዕክት ያስተላለፈው አብዛኛዎቹ ባለክሲዮኖች ገንዘባቸውን የወሰዱ ቢሆንም፣ አሁንም በተለያዩ ምክንያቶች ገንዘቡን መውሰድ ያልቻሉ መኖራቸውን በማረጋገጡ ነው፡፡ ባለአክሲዮኖቹ ገንዘባቸውን ማግኘት ስላለባቸው የተላለፈ መልዕክት መሆኑን የሚገልጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የባለአክሲዮኖች ገንዘብ በዝግ አካውንት የተቀመጠ በመሆኑ አስፈላጊውን መረጃ በማቅረብ ሊወስዱ ይገባል፡፡ 

ሳይቋቋሙ ከቀሩት ባንኮች መካከል ዘምዘም ባንክ በወቅቱ ባንክ ለማቋቋም ይፈቀድ የነበረውን የተከፈለ ካፒታል ማሟላት የቻለ ቢሆንም፣ ወለድ አልባ የባንክ አገልግሎትን ብቻ ነጥሎ ለመሥራት ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ወደ ሥራ ሳይገባ መቅረቱ ይታወሳል፡፡

መደበኛውና የወለድ አልባ የባንክ አገልግሎቶችን አጣምሮ እንዲሠራ የቀረበውን ጥያቄ ባለመቀበሉ ዘምዘም ባንክ ወደ ሥራ መግባት ባይችልም፣ የሰበሰበውን ካፒታል ለሌላ ኢንቨስትመንት ለማዋል ዕቅድ ነበረው፡፡ ሆኖም የተሰበሰበው ገንዘብ ይመለስ በመባሉ ለባንክ ማቋቋሚያ ከተፈረመውና ከተከፈለው ከ370 ሚሊዮን ብር በላይ ውስጥ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነውን ባለአክሲዮኖች ወስደዋል ተብሏል፡፡ 

ሌሎቹ ባንኮች ሳይቋቋሙ የቀሩት ግን አክሲዮን በማሰባሰብ ላይ እያሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የባንክ ማቋቋሚያ የተከፈለ ካፒታል መጠን ከ100 ሚሊዮን ብር ወደ 500 ሚሊዮን ብር እንዲያድግ መመርያ በመውጣቱ ነው፡፡ በአዲሱ መመርያ መሠረት የተጠየቀውን ካፒታል ለማሟላት የማይቻል በመሆኑ፣ በመቋቋም ላይ የነበሩት ባንኮች የአክሲዮን ሽያጫቸውን እንዳቋረጡ ይታመናል፡፡ ፀሐይ ባንክ ደግሞ ለባንክ የሰበሰውን አክሲዮን ወደ ሌላ ኢንቨስትመንት እንዳዛወረው መግለጹ ይታወሳል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ከሁለት ዓመታት ተኩል በፊት የባንክ ማቋቋሚያ ካፒታል መጠንን 500 ሚሊዮን ብር እንዲሆን ከመወሰኑ በፊት፣ በ100 ሚሊዮን ብር ካፒታል መቋቋም የቻሉት የመጨረሻ ባንኮች ደቡብ ግሎባልና እናት ባንክ ናቸው፡፡ የባንክ ማቋቋሚያ የተከፈለ ካፒታል 500 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ከተወሰነ ወዲህ፣ እስካሁን አዲስ ባንክ አልተመሠረተም፡፡

 

 

 

–  ታግዶ የነበረው ብይን እንዲቀጥል ትዕዛዝ ተሰጠ

የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ከቤቶች ልማት ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት፣ የግብዓት አቅርቦትና አስተዳደር መምርያ ጋር በተገናኝ የመሠረተውን የሙስና ወንጀል ክስ እየሰሙ የሚገኙት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 18ኛ ወንጀል ችሎት ዳኞች እንዲነሱለት፣ ሚያዝያ 19 ቀን 2007 ዓ.ም. አቅርቦት የነበረው የአቤቱታ ደብዳቤ ውድቅ ተደረገ፡፡

የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ አቤቱታውን አቅርቦ የነበረው፣ በሙስና ወንጀል መጠርጠራቸውን ገልጾ ክስ በመሠረተባቸው የቤቶች ልማት ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ግብዓት አቅርቦትና አስተዳደር መምርያ ምክትል ሥራ አስኪያጅና  የኤቢፕላስት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ኩባንያ ባለቤት ጉዳይ ሲሆን፣ የችሎቱ ዳኞች ገለልተኛ ሆነው ይሠራሉ የሚል ዕምነት እንደሌለው በመግለጽ ነው፡፡

የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ባቀረበው የቅሬታ አቤቱታ እንደገለጸው፣ በአዋጅ ቁጥር 343/1997 አንቀጽ 38(2) መሠረት የምስክሮቹ ስም በሚስጥር እንዲያዝለት ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም፡፡

በዚህም ምክንያት ምስክሮቹ በተከሳሾች ማስፈራሪያ ስለደረሰባቸው ለመመስከር ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውን፣ ያቀረባቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በአንድነት ሳይመረምሩና መጣራት ያለበት ፍሬ ነገር መኖር አለመኖሩን ከማስረጃው አንፃር ሳይጣራ ፍርድ ቤቱ ምስክሮችን ሰምቶ ባጠናቀቀበት ዕለት የማጣርያ ምስክሮችን ጠርቶ መስማቱንም አስረድቷል፡፡ በመሆኑም በመዝገቡ አያያዝም ሆነ አጠቃላይ የክርክር ሒደት በችሎቱ ዳኞች ገለልተኛነት ላይ ጥርጣሬ ስላደረበትና በቀጣይ ለሚሰጠው ብይንም ሆነ ፍርድ ፍትሐዊነት ላይ እንደሚጠራጠር ዓቃቤ ሕግ በአቤቱታው ገልጿል፡፡ በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጽ 28(1) መሠረት በሌላ ችሎት እንዲታይለት ወይም ለዳኞች አስተዳዳር ጉባዔም አቤቱታ በማቅረቡ፣ ጉባዔው ምላሽ እስከሚሰጠው ድረስ  ሚያዝያ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ሊሰጥ የነበረው ብይን ታግዶ እንዲቆይ አድርጎ ነበር፡፡

ጉዳዩን እየሰማ የነበረውና እንዲነሳ የተጠየቀው ችሎትም በኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ አቤቱታ ላይ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡ ችሎቱ በትዕዛዙ ላይ እንደገለጸው፣ ዓቃቤ ሕግ የምስክሮቹ ስም በሚስጥር እንዲያዝለት ጠይቆ ተቀባይነት ካላገኘ ይግባኝ በማለት ‹‹ጉድለት አለ›› የሚልበትን አግባብ ማስረዳት ነበረበት፡፡ ምስክሮቹም ማስፈራርያ እንደ ደረሰባቸው ለችሎት ማመልከት ሲገባው አላመለከተም፡፡ ሌላው ፍርድ ቤቱ በማንኛውም ጊዜ ማንኛውንም ምስክር ጠርቶ መስማት እንደሚችል በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 143 (1) ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ የቀጠሮ አያያዝ ደግሞ የችሎት ሥልጣን በመሆኑና የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ለችሎቱ ያቀረበውም የክስ ሒደት ከሌሎች ክሶች በተለየ አግባብ የታየበት ሁኔታ ስለሌለ፣ በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጽ 27 መሠረት ዳኞችን ከችሎት ከሚያስነሱ ምክንያቶች ውስጥ አለመሆኑን ጠቅሶ አቤቱታውን ውድቅ አድርጎት ነበር፡፡

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 18ኛ ወንጀል ችሎት የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ‹‹ዳኞች ይነሱልኝ›› ጥያቄና ለመነሳታቸው ባቀረበው ምክንያቶች ላይ ችሎቱ ዝርዝር ማስረጃዎችን ከሕጉ ድንጋጌ ጋር ካስረዳ በኋላ፣ በአዋጁ አንድ ቅሬታ የቀረበበት ዳኛ እንዴት ከችሎት እንደሚነሳ ከማሳወቁ ውጪ ሦስት ዳኞች በአንድ ጊዜ እንዴት እንደሚነሱ ያለው ነገር እንደሌለም ጠቅሷል፡፡ ነገር ግን ምንም እንኳን ስለሦስት ዳኞች መነሳት ሕጉ የሚለው ነገር ባይኖርም፣ አንድ ዳኛ ከችሎት እንዲነሳ አቤቱታ ሲቀርብበት፣ የማይነሳበትን ምክንያት በያዘው መዝገብ ላይ አስፍሮ በሬጅስትራር በኩል ወደ ሌላ ችሎት ተመርቶ እንዲመረመር በሚያዘው መሠረት፣ ሦስቱም ዳኞች ዝርዝር ሐሳባቸውን በመዝገቡ አስፍረው በሬጅስትራር በኩል ለሌላ ችሎት እንዲመራ ትዕዛዝ ሰጥተው ነበር፡፡

በሬጅስትራር በኩል መዝገቡ የደረሰው ሌላው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ችሎት፣ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 25/1998 አንቀጽ 28/3/ መሠረት የዓቃቤ ሕግን አቤቱታ ፍሬ ነገር ከተገቢው የሕግ ድንጋጌ ጋር በማገናዘብ መርምሮ ብይን ሰጥቷል፡፡

ችሎቱ እንደመረምረው ዓቃቤ ሕግ ምስክሮቹ በሚስጥር እንዲያዙለትና ማንነታቸው እንዳይገለጽ ያቀረበውን አቤቱታ ችሎቱ (ስምንተኛ ወንጀል ችሎት) ውድቅ ያደረገው ‹‹ዳኞቹን ከችሎት ሊያስነሳቸው ይችላል ወይስ አይችልም?›› የሚለውን አይቶ ነው፡፡ በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጽ 27(1) ከ‹‹ሀ›› እስከ ‹‹መ›› ዳኞች እንዴት ከችሎት መነሳት እንዳለባቸው ከተዘረዘሩት ውስጥ የማይካተት ቢሆንም፣ በዚሁ አዋጅ ቁጥር ንዑስ አንቀጽ 1‹‹ሠ›› ሥር ዳኞች የሚነሱበት በቂ ምክንያት ካለ እንዴት እንደሚነሱ መደንገጉን ችሎቱ ጠቁሟል፡፡ 

በመሆኑም ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ፍሬ ነገር ‹‹ሊካተት ይችላል? ወይስ አይችልም?›› የሚለውን ጭብጥ ይዞ ችሎቱ ሲመረምረው፣ ዓቃቤ ሕግ የምስክሮቹን ማንነት መግለጽ ያቀረበውን ክስ እውነታ እንዳያውጣጣ የሚያደርገው ከሆነ ይግባኝ መጠየቅ ከሚገባው በስተቀር ለዳኞች መነሳት ምክንያት ሆኖ ሊወሰድ የሚያበቃ፣ ወይም አዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጽ 27(1-ሠ)ን የሚያሟላ አለመሆኑን ገልጿል፡፡

ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ በአንድነት ሳይመረምር ችሎቱ ምስክሮችን ሰምቶ በጨረሰበት ዕለት ማጣሪያ ምስክሮችን ጠርቶ መስማቱ አግባብ መሆን አለመሆኑን መመርመሩንም ችሎቱ ገልጿል፡፡ የክስና ማስረጃ አሰማምን በሚመለከት በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕግ ክፍል ሁለት አንቀጽ 136ና ተከታዮቹ ላይ መደንገጉንም ጠቁሟል፡፡ አንድ ችሎት መዝገብ ሳይመረምር በወ/ሥ/ሥ/ሕግ አንቀጽ 143(1) መሠረት ማስረጃ መስማት ይችላል፡፡ ችሎቱ ከመጀመርያ ጀምሮ እየሰማው የመጣ ጉዳይ ከሆነ የምስክር ቃልና ማስረጃን መርምሮ ለመለየት ቀጠሮ መስጠት ላያስፈልገው እንደሚችልም ችሎቱ አክሏል፡፡ በችሎቱ ተጨማሪ ማስረጃ አለመስማት፣ በችሎቱ ተጨማሪ ማስረጃ በማዘዝ መስማት፣ ዳኞቹ የሥነ ሥርዓት ሕጉን ሳይከተሉ ሠርተዋል አስብሎ ገለልተኛነታቸውን የሚያስጠረጥር አለመሆኑን ገልጾ ከችሎት የሚነሱበት በቂ ምክንያት አለመሆኑን አስታውቋል፡፡

የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ሌላው ያቀረበው አቤቱታ ችሎቱ (18ኛ ወንጀል ችሎት) ቀጠሮዎችን ሲሰጥ የቀኑን መቀራረብ (በአጭር በአጭር ቀናት) የዳኞችን ገለልተኝነት ላይ ጥርጣሬ እንዳሳደረበት ሲሆን፣ መዝገቡን የመረመረውም ችሎት ማብራርያ ሰጥቷል፡፡ መዝገቡ የሚያመለከትው ችሎቱ የተለያዩ ሥራዎችን ለማከናወን ቀጠሮዎችን በቀናት፣ በሳምንታትና በ15 ቀናት ልዩነት ሲሰጥ እንደነበር ከመዝገቡ ለመረዳት መቻሉን ገልጿል፡፡ የወ/መ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 94 (1) እና 94 (2 – መ) ላይ ተደንግጎ እንደሚታየው ፍርድ ቤት ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ ይረዳል ብሎ ካመነበት፣ የቀጠሮውን ሥርዓት የመምራት ሥልጣን የችሎቱ መሆኑንም ጠቁሟል፡፡ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 20 (1) ላይም የተከሰሱ ሰዎች ክሳቸውን በአጭር ጊዜ መስማትና እልባት ማግኘትም እንዳለባቸው መደንገጉንም አክሏል፡፡

በኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ አቤቱታ የቀረበበት 18ኛ ወንጀል ችሎትም የሰጠው ቀጠሮ፣ ሕጋዊ መሠረት ያለውና ሕገ መንግሥቱን በማክበርና የማስከበር ግዴታውን ከመወጣት የመነጨ እንጂ፣ ትክክለኛው ፍትሕ እንዳይሰጥ የሚያደርግ በቂ ምክንያት ሊሆን እንደማይችል ችሎቱ አስታውቋል፡፡

በአጠቃላይ በኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ የቀረቡት ‹‹ዳኞች ከችሎት ይነሱልኝ›› ምክንያቶች፣ ከምክንያቶቹ በስተጀርባ የዳኝነት ሥርዓቱ የማይፈቅደውና ከሥነ ምግባር ውጪ የተከናወነ ተግባር መኖሩን ካላመለከተና ዳኞቹ እውነተኛውን ፍርድ እንዳይሰጡ የሚያደርጓቸውን ምክንያቶች ያላስደገፈ መሆኑን ችሎቱ በብይኑ ገልጿል፡፡ ዳኞች በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 70 (3) በሙሉ ነፃነት ሕግን መሠረት አድርገው መሥራት እንዳለባቸው ከሚደነግገው አንቀጽ ጋር የሚጣረስና የአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጽ 27ን ዓላማና መንፈስን ያልተከተለ መሆኑን አብራርቶ፣ የቀረበውን አቤቱታ እንዳልተቀበለው በመግለጽ ውድቅ አድርጎታል፡፡ መዝገቡም ወደሚታይበት 18ኛ ወንጀል ችሎት ተመልሶ ቀጠሮውን ተከትሎ ብይኑ እንዲሰጥ አዟል፡፡

 

 

ኢንጂነር ታደሰ ተሰማ  ---------------    ዶ/ር ፍሬሕይወት ወልደሃና

– የኩባንያው ንብረት መዘረፉ ይነገራል

የከሰረው የሆላንድ ካር ኩባንያ ባለቤት ኢንጂነር ታደሰ ተሰማ ከሦስት ዓመት የውጭ አገር ቆይታ በኋላ ባለፈው ሳምንት ወደ አገር ቤት በመመለስ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፣ ኩባንያቸውን ለመታደግ ያስችላል ብለው ያቀረቡት ዕቅድ ከድርጅቱ ደንበኞች ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው፡፡ 

ኢንጂነር ታደሰ ለአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ሐሙስ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል በሰጡት መግለጫ፣ የከሰረው ኩባንያቸው በሐራጅ ቢሸጥ ማንም ተጠቃሚ እንደማይሆን ገልጸው፣ ይልቁንም ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ የሚያደርግ ዕቅድ ይዘው መምጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ ኢንጂነር ታደሰ ሞጆ በሚገኘው የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ውስጥ የሚገኙትን ያልተገጣጠሙ መኪኖች ገጣጥሞ የቅድሚያ ክፍያ ለከፈሉ ደንበኞች በማስረከብ፣ በቀጣይም ኩባንያው ያለበትን የባንክና የመንግሥት ዕዳ ለመክፈል ማቀዳቸውን አስታውቀዋል፡፡ ዕቅዳቸውን ለመንግሥት አቅርበው ተቀባይነት በማግኘቱ የሕግ ከለላ ተሰጥቷቸው ወደ አገር ቤት መመለሳቸውን፣ ለሥራ ማስኬጃ የሚሆን ስድስት ሚሊዮን ብር ይዘው መምጣታቸውን ለጋዜጠኞች አስረድተዋል፡፡ 

ኢንጂነር ታደሰ የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በኩባንያው ደንበኞች አካባቢ ከፍተኛ ተቃውሞ ቀስቅሷል፡፡ ከሦስት ዓመት በፊት ከኩባንያው መኪና ለመግዛት ቅድሚያ ክፍያ ከፍለው መኪኖቻቸውን ሳይረከቡ የቀሩ ግለሰቦች ቅሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ 

የከሰረው የሆላንድ ካር ገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ፍሬሕይወት ወልደሃና ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኢንጂነር ታደሰ ከመኪና ገዢዎች ጋር ሳይመክሩ ያቀረቡት ዕቅድ ተቀባይነት የለውም፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የባዮሜዲካል ማዕከል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ፍሬሕይወት፣ ባለሀብቱ ያቀረቡት ዕቅድ አዲስ አለመሆኑን፣ ለኪሳራ አጣሪ ዳኛና ለገንዘብ ጠያቂዎች ኮሚቴ ቀርቦ ተጨባጭ ማስተማመኛ የሌለው በመሆኑ ውድቅ የተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ 

‹‹በዕቅዱ መሠረት ኢንጂነር ታደሰ ስድስት ሚሊዮን ብር ይዤ መጥቻለሁ ነው የሚሉት፡፡ ኩባንያው ያለበት ዕዳ በትክክል መናገር ባይቻልም፣ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚሆን ይገመታል፡፡ ስድስት ሚሊዮንና 80 ሚሊዮን ብር በጣም የተራራቁ ናቸው፤›› ያሉት ዶ/ር ፍሬሕይወት፣ ‹‹ይህንን ዕቅድ መኪና ገዢዎችን (የኩባንያው ደንበኞችን) ሰብስበው ቢያወያዩ መልካም ነበር፡፡ ነገር ግን እስካሁን ካለው ሁኔታ ግለሰቡ በተጨባጭ ያደረጉት ነገር የለም፡፡ ደንበኞች የደረሰባቸውን ችግር ለመፍታት ያደረጉት ጥረት የለም፡፡ ከዘመን ባንክ ኃላፊዎች ጋር ተነጋግረው ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚያ ውጪ ከደንበኞች ጋር ያደረጉት ውይይት የለም፤›› ብለዋል፡፡ 

ደንበኞች ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደው ሲከታተሉ ብዙ ውጣ ውረድ እንደደረሰባቸው የሚናገሩት ዶ/ር ፍሬሕይወት፣ የኩባንያው ባለቤት አገር ጥለው በመኮብለላቸውና ኩባንያው በመዘጋቱ መረጃ ማግኘት አስቸጋሪ እንደነበር፣ ባለፉት ሦስት ዓመታት ሒደት ውስጥ ኪሳራ መታወጁን፣ የኪሳራ አጣሪ ዳኛና ንብረት ጠባቂ መሾሙን አስረድተዋል፡፡ ገንዘባቸውን ከፍለው ንብረታቸውን ያልተረከቡ ግለሰቦች እንደገና ገንዘብ በማዋጣት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ ቆይቶ ወደመቋጫው ላይ ሲደረስ፣ ባለሀብቱ ከስደት ተመልሰው የሰጡት መግለጫ ውዥንብር እንደፈጠረም አመልክተዋል፡፡ 

‹‹መንግሥት ከለላ አድርጎልኝ መጣሁ ቢሉም በትክክል ግዴታቸውን ለመወጣት የሚያስችላቸውን የፋይናንስ አቅም ይዘው እንዳልመጡ ድርጅቱ ያለበት ዕዳና ያለው ንብረት በግልጽ ያሳያል፡፡ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ መኪኖችን አስረክባለሁ ሲሉ ለዚህ የሰጡት ምንም መተማመኛ የለም፡፡ ከዚህም አልፎ ደንበኞች ለዳኝነት፣ ለጠበቃ፣ ለንብረት ጥበቃና ለመሳሰሉት ተያያዥ ወጪዎች ያወጡትን ተጨማሪ ገንዘብም ሆነ የዋጋ ግሽበትን በተመለከተ ኢንጂነር ታደሰ የጠቀሱት ምንም ነገር የለም፤›› ብለዋል፡፡ 

‹‹የኩባንያው ደንበኞች ጉዳያቸውን በፍርድ ቤት ሲከታተሉ ቆይተው የተፈረደላቸው አሉ፡፡ በሒደት ላይ ያሉ አሉ፡፡ ይግባኝ የጠየቁ አሉ፡፡ ተወስኖላቸው የፍርድ አፈጻጸም የሚጠብቁ አሉ፡፡ በተለያየ ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡ የደንበኞች ፍላጎት ግልጽ ነው፡፡ ገንዘባቸውን ማግኘት ነው፡፡ የተወሰኑት መኪናቸውን ማግኘት ይፈልጋሉ፡፡ አብዛኛው ግን የከፈለውን ገንዘብ ከነኪሳራው ማግኘት ይፈልጋል፤›› ያሉት ዶ/ር ፍሬሕይወት፣ ኢንጂነር ታደሰ ያቀረቡት ዕቅድ በኮሚቴያቸው ተቀባይነት እንዳላገኘ አስረድተዋል፡፡ 

‹‹ይዘውት የመጡት ሐሳብ ንብረታችንን እንደምናገኝ ማስተማመኛ ስለሌለው አልተቀበልነውም፡፡ በፍርድ ቤት ሒደት እንጨርሳለን፡፡ ዳር የደረሰ ጉዳይ ነው፤›› ብለዋል፡፡ አያይዘውም ኢንጂነር ታደሰ ኮሚቴውን ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ ደንበኞችን ማነጋገር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ ‹‹ደንበኞች ምን ይላሉ ብለው ማዳመጥ አለባቸው፡፡ አጠቃላይ ስብሰባ ተጠርቶ ከደንበኞች ጋር መወያየት አለባቸው፤›› ብለዋል፡፡ 

የሆላንድ ካር ንብረት የአገር ሀብት እንደሆነና ንብረት ለመሸጥ ብዙም ፍላጎት እንደሌለ የሚናገሩት ዶ/ር ፍሬሕይወት፣ አዋጭ የሆነና ለሁሉም ወገን የሚጠቅም ዕቅድ ይዞ መቅረብ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ 

ከሆላንድ ካር መኪና ገዝተው ያልተረከቡ ሰዎች ከ200 በላይ ናቸው፡፡ ለኩባንያው ብድር የሰጠው ዘመን ባንክ 34 ሚሊዮን ብር በላይ ይፈልጋል፡፡ የጉምሩክ ቀረጥና ግብር ዕዳ እንዲሁም የኩባንያ ሠራተኞች የአገልግሎት ክፍያ ጥያቄዎች አሉ፡፡ ኢንጂነር ታደሰ የኩባንያቸው ንብረት 180 ሚሊዮን ብር እንደሚገመትና ኩባንያው ያለበት ዕዳ 63 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የኪሳራ አጣሪ ቡድኑ ይህን አልተቀበለም፡፡ የኪሳራ መርማሪ ዳኛ አቶ አሰፋ ዓሊ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የተመሰከረለት የዋጋ ገማች የተመነው የሆላንድ ካር ንብረት 83,058,533 ብር ነው፡፡ ኩባንያው ላይ የቀረበው የዕዳ ጥያቄ 160 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነ፣ ከዚያ ውስጥ አጣሪ ቡድኑ መርምሮ በመረጃ ያረጋገጠው 74 ሚሊዮን ብር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አቶ አሰፋ ኢንጂነር ታደሰ ያቀረቡትን ዕቅድ በጥብቅ ተቃውመዋል፡፡ ባለሀብቱ በአካል መጥተው እንዳላናገሯቸው አረጋግጠዋል፡፡ በእርግጥ ከአንድ ወር በፊት የአገሪቱ የንግድ ሕግ በሚፈቅደው መሠረት የስምምነት ሐሳብ (Composition Proposal) በጠበቆቻቸው አማካይነት ማቅረባቸውን አልሸሸጉም፡፡ 

‹‹የኪሳራ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ፣ ዕዳ ከተጣራ በኋላ ባለቤቱ ድርጅቱን እንደገና ላንቀሳቅሰው እችላለሁ፣ በሐራጅ ቢሸጥ እንጎዳለን፣ ባለቤቶቹ ገንዘብ ጠያቂዎቹ ይጎዳሉ፣ ኩባንያውን አንቀሳቅሼ የእነርሱንም ዕዳ እከፍላለሁ የሚል ዕቅድ አቅርበው ነበር፡፡ ገንዘብ ጠያቂዎች ከተስማሙ (የማይስማሙ ከሆነ እንኳ ፍርድ ቤት ካፀደቀው) መልሰው ሊሠሩ ይችላሉ የሚል የሕግ መብት ስላለ፣ ያንን መብታቸውን ለመጠቀም የስምምነት ሐሳብ ከአንድ ወር በፊት ልከው ነበር፤›› ያሉት አቶ አሰፋ፣ በስምምነት ሐሳቡ ላይ የተጠቀሱ ችግሮችን ነቅሰው አውጥተዋል፡፡ 

‹‹ስድስት ሚሊዮን ብር አገኘሁ ይላል፡፡ ይህ ገንዘብ ያሠራል አያሠራም የሚለውን ለመወሰን አንችልም፣ ሙያችንም አይደለም፡፡ በሕግ የሚጠየቅ ለገንዘብ ጠያቂዎች ዋስትና ተቀማጭ መደረግ አለበት ይላል፡፡ በተጨባጭ ይህን አላደረጉም፡፡ ለማድረግ ስለመቻላቸውና ፈቃደኛ ስለመሆናቸው የገለጹት ነገር የለም፡፡ በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች ዕቅዱን እንደማንቀበል በጽሑፍ በጠበቆቻቸው በኩል ምላሽ ሰጥተናል፤›› ብለዋል፡፡ 

በፍርድ ሒደት ብዙ ርቀት ሄደው፣ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ንብረት ተቆጥሮ እንዲጠበቅ አድርገው፣ ከብዙ ትግል በኋላ ወደ ጨረታ ሒደት በገቡበት ወቅት ኢንጂነር ታደሰ በድንገት ከተሰወሩበት ብቅ ብለው መንግሥት ከለላ ሰጥቶኝ መጥቻለሁ በማለት የሰጡት መግለጫ፣ ሁሉንም ወገኖች ግራ ያጋባና የጨረታ ሒደቱንም እንዳጨናገፈ አቶ አሰፋ ተናግረዋል፡፡ 

ገንዘባቸውን ከፍለው መኪናቸውን ሳይረከቡ የቀሩ ግለሰቦች ባዋጡት ሁለት በመቶ ገንዘብ ቢሮ ተከራይተው ባቋቋሙት ተቋም ሥራቸውን እንደሚያካሂዱ የገለጹት አቶ አሰፋ፣ ግለሰቦቹ በፊት የተቀሙት ገንዘብ ሳያንስ ለተጨማሪ ወጪ መዳረጋቸውን፣ ይህን ገንዘብ በጥንቃቄ ሥራ ላይ በማዋል ተቋሙ የኩባንያው ደንበኞች ያጡትን ንብረታቸውን ለማስመለስ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስረድተዋል፡፡ ዘመን ባንክ አለኝ የሚለውን ገንዘብ ለማስመለስ በመያዣነት የያዘውን የኩባንያውን ንብረት (ፋብሪካ፣ መጋዘንና ሕንፃ) ለመሸጥ ሲነሳ እስከ ሰበር በደረሰ የፍርድ ቤት ክርክር ማስቆማቸውን ገልጸዋል፡፡ ባንኩ አለኝ የሚለውን መብቱን በፍርድ ቤት ያሉ ክርክሮች ሲያልቁ ከተወሰነለት ገንዘቡን እንዲወስድ ተስማምተው ወደ ሥራ መግባታቸውን አስረድተዋል፡፡ የድርጅቱ ሠራተኞችም በፍርድ ቤት አስወስነው የድርጅቱን መኪኖች ለማሸጥ ሲሞክሩ ማሳገዳቸውን ተናግረዋል፡፡ በአጠቃላይ እስካሁን 330 ንብረትና ገንዘብ ጠያቂዎች ያሉ መሆናቸውን፣ ከእነዚህ መካከል 242 ያህሉ መኪና ገዢዎች 74 ደግሞ የኩባንያው ሠራተኞች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ 

የኪሳራ መርማሪውና ንብረት ጠባቂው ከዘመን ባንክ ጋር ተባብሮ የመሥራትን አስፈላጊነት ተረድተው የኩባንያውን ንብረት በጨረታ ለመሸጥ በመገናኛ ብዙኃን ማስታወቂያውን አስነግረዋል፡፡ ለማስታወቂያ ብቻ ከ109 ሺሕ ብር በላይ ማውጣታቸውን የሚናገሩት አቶ አሰፋ፣ ስምንት ድርጅቶች የጨረታ ሰነድ መግዛታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ የኩባንያው ንብረቶች በአጠቃላይ በ83,058,533 ብር የመነሻ ዋጋ ለሽያጭ ቀርበዋል፡፡ 

የጨረታ ሰነዱን የገዙት ኩባንያዎች ሞጆ የሚገኘውን የድርጅቱን ፋብሪካና ሌሎች ንብረቶች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡ ጨረታው ሊዘጋ ጥቂት ቀናት ሲቀሩት ኢንጂነር ታደሰ በድንገት የሰጡት መግለጫ ገዢዎችን እንዳራቀ አቶ አሰፋ ይናገራሉ፡፡ በተጨማሪም በጨረታው መዝጊያ ዕለት ቅዳሜ ግንቦት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. የኢንጂነር ታደሰ ጠበቃ የኩባንያው ንብረት እንዳይሸጥ የሚከላከል የፍርድ ቤት ማገጃ ለእነ አቶ አሰፋ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም ምክንያት የጨረታው ሒደት ተቋርጧል፡፡ 

‹‹በሕግ ተቀባይነት ያለው አሠራር የሚመስለን ዋስትና የመስጠት አቅም ካላቸው፣ ገንዘብ ጠያቂዎችን በኮሚቴያቸው አማካይነት አነጋግረውና ተስማምተው ያንን ስምምነት በፍርድ ቤት አፅድቀው ወደ ሕጋዊ አሠራር መግባት ነው፡፡ አሁን የሰጡት መግለጫ ግራ መጋባት ፈጥሮ ሥራውም ቆሟል፡፡ ይህ የበለጠ ችግር፣ የበለጠ ጥፋት እንዲደርስ ያደርጋል እንጂ ጥቅም ያለው አይመስለኝም፤›› ያሉት አቶ አሰፋ፣ በቀጣይ ምን እንደሚሆን መናገር እንደሚቸግራቸው ተናግረዋል፡፡ 

የኮሚቴው አባላት በሰጡት አስተያየት ዙሪያ ሪፖርተር ያነጋገራቸው ኢንጅነር ታደሰ፣ ያቀረቡት ዕቅድ በመንግሥት ተቀባይነት አግኝቶ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተደራድረው እንዲሠሩ ተፈቅዶላቸው ወደ አገር ቤት እንደተመለሱ አስታውሰዋል፡፡

‹‹የቀረበው ዕቅድ ዋስትና አይሰጥም ለተባለው ንብረቱ የሚገኘው በእጃቸው ነው፡፡ በእጃቸው ላለ ንብረት እኔ እንዴት ዋስትና ልሰጥ እችላለሁ? እኔኮ መኪኖቹን ስጡኝና ገጣጥሜ ሸጬ ልስጣችሁ አላልኩም፡፡ እኔ ያልኩት የመንግሥትም ተወካዮች ያሉበት ኮሚቴ ተቋቁሞ እኔ ባመጣሁት ገንዘብ የቴክኒክ ጉዳዮችን ላመቻችና መኪኖቹን ገጣጥመን፣ እሴት ጨምረን ይሸጡና ደንበኞች መኪኖቻቸውን ይረከቡ፡፡ በቀጣይም ሌሎች ባለዕዳዎች ገንዘባቸው ይከፈላቸው ነው፤›› ብለዋል፡፡

ኢንጅነር ታደሰ በአካል መጥቶ አላናገረንም ለሚለው አቤቱታ በሰጡት ምላሽ፣ ከመጡበት ቀን ጀምሮ የኩባንያው ንብረቶች እንዳይሸጡ ለማሳገድ ሩጫ ላይ ስለነበሩ የሚመለከታቸውን ደንበኞች በጊዜ እጥረት ምክንያት እንዳላወያዩ አምነዋል፡፡ ነገር ግን የመንግሥት ተወካዮች ባሉበት በቅርብ ቀን ከደንበኞች ኮሚቴ፣ ከመርማሪ ዳኛና ከንብረት ጠባቂ ጋር ውይይት እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሞጆ ከሚገኘው የሆላንድ ካር መኪና መገጣጠሚያ 610 የመኪና ጎማዎች ከነቸርኬያቸው በቅርቡ መዘረፉን ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ፍሬሕይወት እንደማንኛውም ሰው መረጃውን እንደሰሙ ለሪፖርተር የገለጹ ሲሆን፣ የሕግ ባለሙያ የሆኑት አቶ አሰፋ በበኩላቸው ጉዳዩ በምርመራ ላይ ያለና ለፍርድ ቤት የቀረበ በመሆኑ አስተያየት እንደማይሰጡ ተናግረዋል፡፡ 

ኢንጅነር ታደሰ በበኩላቸው በሁኔታው ማዘናቸውን ለሪፖርተር ገልጸው፣ ‹‹610 የመኪና ጐማ ከነቸርኬው ሲዘረፍ ንብረት ጠባቂዎች የት ናቸው?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ኢንጅነር ታደሰ፣ ‹‹610 ጐማ ለማጓጓዝ በርካታ የጭነት ተሽከርካሪዎች ያስፈልጋሉ፡፡ ይህ ታቅዶና በቂ ዝግጅት ተደርጐ የተፈጸመ ወንጀል ነው፡፡ ንብረት ጠባቂዎች ኃላፊነታቸውን እየተወጡ አይደለም፡፡ ንብረቱን ፈርመው የተረከቡ ሰዎች ያስጠይቃቸዋል፡፡ 610 ጐማ ማለት የ110 መኪኖች ጐማዎች ተሰርቀዋል ማለት ነው፡፡ ምን ንብረት እንዳለና ምን ንብረት እንደተሰረቀ አይታወቅም፡፡ የንብረቱ ሁኔታ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ነው፤›› ብለዋል፡፡

አክለውም እርስ በርስ መወነጃጀሉ ቀርቶ በውይይት ችግሮችን ፈቶ ለሁሉም ወገን የሚጠቅም የመፍትሔ ሐሳብ ላይ መድረስ እንደሚበጅ፣ መንግሥትም ያስቀመጠው አቅጣጫ ይህንኑ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

 

ሟች ቀኝ አዝማች ግርማ አበበ

ከንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት እስከ ደርግ ሥርዓት ሶማሊያን አብጠርጥረው በማወቅና ከኢትዮጵያ ወገን የሶማሌ ክልልን በማስተዳደር፣ ብዙ እንደሠሩ የሚነገርላቸው ቀኝ አዝማች ግርማ አበበ በተወለዱ በ86 ዓመታቸው አረፉ፡፡ 

ቀኝ አዝማች ግርማ መንግሥታዊ ኃላፊነት ባለባቸው የሥራ ዘርፎች ላይ በመሰማራት ከ1943 ዓ.ም. ጀምሮ በጡረታ እስከተገለሉበት እስከ 1967 ዓ.ም. ድረስ በተለያዩ ጠቅላይ ግዛቶች እየተሾሙ አገልግለዋል፡፡ በ1943 ዓ.ም. የጋራ ሙለታ አውራጃ ዋና ፀሐፊ በመሆን የተመደቡ ሲሆን፣ በዚህ ጊዜም በአውራጃው ዘመናዊ ትህምርት እንዲስፋፋ ማድረጋቸውን ሐሙስ ግንቦት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. በቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ቀብራቸው በተፈጸመበት ወቅት የተነበበው የሕይወት ታሪካቸው ይዘክራል፡፡ 

በ1965 ዓ.ም. የኤልከሬ አውራጃ ገዥ፣ በ1966 ዓ.ም. የገናሌ አውረጃ ገዥ፣ በዚያው ዓመት የጅጅጋ አውራጃ ገዥ፣ እንዲሁም በደርግ መንግሥት በ1967 ዓ.ም. የጨርጨር አውራጃ ገዥ በመሆን ያገለገሉት ቀኝ አዝማች ግርማ በኢትዮጵያና በሶማሊያ ግንኙነት መንግሥታቱን በመምከርና መተግበር አለባቸው ስለሚሏቸው የአስተዳደር ሥርዓቶች ሲናገሩም ይታወቃሉ፡፡ ቀኝ አዝማች ግርማ የሶማሊያን ታሪክ በአራቱም አቅጣጫ አብጠርጥረው ያውቃሉ ከሚባሉ ጥቂት አንጋፋ ሰዎች አንዱ እንደነበሩ ይነገርላቸዋል፡፡ 

ከሦስት ዓመት በፊት ከሪፖርተር ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ‹‹ኢትዮጵያ ለሶማሌ ላንድ ዕውቅና የመስጠት የህልውና ግዴታ አለባት፤›› በማለት የተናገሩት የሚታወስ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ላይ ሊቃጡ የሚችሉ የአልሸባብ ጥቃቶችን ለመመከት ጥሩ አማራጭ አድርገው ከሚያቀርቧቸው የመፍትሔ ሐሳቦች አንዱ የሆነው ለሶማሌ ላንድ እንደ አገር ዕውቅና መስጠትን ሲሆን፣ ምንም እንኳ የሞቃዲሾ ሶማሊያም ኢትዮጵያን በድንበር የሚያዋስን አገር ቢሆንም፣ የሶማሌ ላንድ ሕዝብ ለኢትዮጵያ ካለው ወዳጅነት፣ ካለው የባህር በርና ሌሎች የኢኮኖሚ ጥቅሞች አኳያ መንግሥት ለሶማሌ ላንድ ዕውቅና መስጠት አለበት ብለው ያምኑ ነበር፡፡ 

ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ እንግሊዞች የኢትዮጵያን ጦር ለመርዳት መጥተው እንደነበር ለሪፖርተር ሲያስረዱ እንዳስታወሱት፣ በኦጋዴን ማረፊያቸውን አድርገው በቆዩ ጊዜ ሐርጌሳንም ይዘው ስለነበር፣ የኬንያ ሶማሌን ጨምሮ አምስቱን ሶማሌዎች በማዋሀድ አንድ አድርገው ለመግዛት አቅደው ነበር፡፡ ይህም ቢሆን ግን በ1941 ዓ.ም. ኦጋዴንን ለኢትዮጵያ ቢያስረክቡም፣ እንግሊዞች የኦጋዴንን ባላባቶች በመደለል ከኢትዮጵያ እንዲገነጠሉ ለማድረግ ሲሞክሩ እንደነበር ቀኝ አዝማች ግርማ አስታውሰዋል፡፡ 

ምንም እንኳ ኢትዮጵያ ከኦጋዴን ባሻገር ደገ ሃቡርንና ጅግጅጋን ከእንግሊዞች እጅ ቢረከብም፣ እግሊዞች ግን ጂቡቲን ጨምሮ የኬንያ ሶማሌን፣ ሶማሌ ላንድን፣ በወቅቱ በጣሊያን እጅ የነበረችውን ሞቃዲሾ ሶማሌን አንድ ላይ አዋህደው የመግዛት ሐሳባቸው አልተገታም ነበር፡፡ እንግሊዞች እንዳሰቡት አምስቱን ሶማሌዎች በማዋሀድ አንዲት የሶማሊያ አገር ለመመሥረት የነበራቸው ዕቅድ በኢትዮጵያ መንግሥት የወቅቱ ፖለቲካ እየጠነከረ መምጣት፣ በኦጋዴን በተነሳ ተቃውሞ ምክንያት ህልማቸው ሳይሳካ ቀርቷል የሚሉት ቀኝ አዝማች ግርማ፣ እንግሊዞች በእጃቸው ለነበሩት ሶማሌ ላንዶች ነፃነት ለመስጠት መገደዳቸውን ገልጸዋል፡፡ ይህንን ተከትሎ ግን የሞቃዲሾ አዲሱ አስተዳደር የአምስቱን ሶማሌዎች ውህደት ዕውን ለማድረግ ሶማሌ ላንድን ወዲያውኑ ወደ ራሳቸው በመቀላቀል ወደ ኢትዮጵያም መምጣት ጀምረው ነበር፡፡ በዚህ አካሄዳቸውም የኢትዮጵያን ሶማሌ ለመገንጠል የመጀመሪያውን ወረራ በ1956 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ላይ እንደፈጸሙ ቀኝ አዝማች ግርማ ለሪፖርተር በሰጡት ቃለ ምልልስ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ የሞቃዲሾ ሶማሊያ ከሶማሌ ላንድ መለየት የአምስቱን ሶማሌዎች ውህደትና የታላቋን ሶማሊያ መመሥረት ህልም ቢያከሽፍም፣ ሞቃዲሾ አሁንም ድረስ በሕገ መንግሥቷ ውስጥ ያስቀመጠችው በመሆኑ ይህ አቋም አሁንም ድረስ ለኢትዮጵያና ለሌሎች አገሮች ሥጋት እንደሆነ ቀኝ አዝማች ግርማ ዕምነታቸውን ገልጸው ነበር፡፡ 

‹‹ለጦርነት ስትራቴጂም ሆነ ለፖለቲካ ከሶማሌ ላንድ ጋር መተቃቀፉ ለኢትዮጵያ ትልቅ ጥቅም ይሰጣታል፤›› ያሉት ቀኝ አዝማች ግርማ፣ ለኢትዮጵያ ደኅንነትና ለወሰኗ መከበር ሶማሌ ላንድ ወሳኝ ሚና እንዳላት ገልጸው ነበር፡፡ ለሶማሌ ላንድ ዕውቅና መስጠት አፍሪካውያን ከቅኝ ገዦቻቸው በተረከቡት ወሰን ይፅኑ በሚለው ስምምነት መሠረትም ሶማሌ ላንድ ዕውቅና ማግኘት እንደሚገባት፣ ሞቃዲሾም በዚህ ስምምነት መሠረት ሶማሌ ላንድን ለግዛቷ አካልነት የምትጠይቅበት ምንም ዓይነት የታሪክ አብነት የላትም ብለዋል፡፡ 

ቀኝ አዝማች ግርማ ከወረዳ አስተዳዳሪነት እስከ ምክትል ገዥነት ከዚያም በዋና አገረ ገዥነት በተለያዩ ደረጃዎች የሶማሌ ግዛትንና የሐረር አውራጃዎችን ማስተዳደራቸው ይገራል፡፡ በአንድ ዓመት ውስጥ አራት ጊዜ የተለያየ ሹመት ተሰጥቷቸው አስቸጋሪውን የሶማሌ ክልል፣ ከአጎራባቾቹ ሶማሌ ላንድና ከሞቃዲሾ ሶማሊያ ጋር ተፋጠው እንዳስተዳደሩም የሕወይት ታሪካቸው ይዘክራል፡፡ 

የሁለት ወንዶችና የአንድ ሴት ልጅ አባት የነበሩት ቀኝ አዝማች ግርማ፣ በቀድሞው ሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሐብሮ አውራጃ፣ ገለምሶ ከተማ ተወልደው አድገዋል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት 60ኛ ዓመት የጋብቻ በዓላቸው በትዳር አብረዋቸው ከኖሩት ከወ/ሮ ጥሩ ወርቅ ሽፈራው ካፈሯቸው ልጆች በተጨማሪ የአሥር ልጆች አያትና የሁለት ልጆች ቅደመ አያት ለመሆን በቅተዋል፡፡ በሚያዝያ ወር ባለቤታቸው ከዚህ ዓለም ሲለዩ፣ ቀኝ አዝማች ግርማ ከወር በኋላ ተከትለዋቸዋል፡፡

ከመንግሥት አገልግሎት በጡረታ ከተገለሉ በኋላ በ1984 ዓ.ም. የሐረርጌ ተወላጆችና ነዋሪዎች መረዳጃ ማኅበርን በመመሥረትና በምክትል ሰብበሳቢነት በመምራት ተሳትፈዋል፡፡ 

 

 

የኢትዮጵያና የአሜሪካ ሹማምንት ስብሰባው ከተጠናቀቀ በኋላ

አምስተኛው የኢትዮ አሜሪካ የሁለትዮሽ የመከላከያ ምክር ቤት በአሜሪካ ባደረገው ስብሰባ፣ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የደኅንነት ድጋፍና ትብብር መገምገሙ ተሰማ፡፡

ስብሰባው ባለፈው ሳምንት ውስጥ በዋሽንግተን ለሦስት ተከታታይ ቀናት የተካሄዱ መሆኑን ከአሜሪካ ኤምባሲ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡ የኢትዮጵያን ልዑክ የመሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ ዩኑስ ናቸው፡፡ በአባልነት ከተሳተፉት መካከል ደግሞ የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተሩ ብርጋዴር ጄኔራል ተክለ ብርሃን ወልደ አረጋይና ሌሎች የደኅንነት ኃላፊዎች ይገኙበታል፡፡

የአሜሪካን ልዑክ የወከሉት ደግሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል ዴቪድ ሮድሪጌዝና በፔንታጎን የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ጸሐፊ ሚስ አማንዳ ዶሪ ናቸው፡፡ 

የስብሰባው አጀንዳ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያሉ የፀጥታ ጉዳዮችን መገምገምና የተናጠል መረጃዎችን መለዋወጥ እንደሆነ የኤምባሲው መረጃ ያመለክታል፡፡ በውይይቱ ወቅትም ትኩረት አግኘተው የነበሩት የየመን የደኅንነት ቀውስ፣ የሶማሊያና የደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ጉዳዮች መሆናቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምታደርገው የመከላከያና የደኅንነት ትብብር ግምገማ እንደተካሄደም ከመረጃው ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚሁ ወቅትም የአሜሪካ ጂኦ ስፓሻል የደኅንነት ኤጀንሲና የኢትዮጵያ የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ መሠረታዊ መረጃዎችን ለመለዋወጥና ትብብር ለማድረግ ስምምነት ፈርመዋል፡፡

የጅኦ ስፓሻል መረጃዎች ማለት ከአየር ላይ ወይም ከሳተላይት በመሬት ላይ የሚገኙ መረጃዎችን መሰብሰብና መተንተን ነው፡፡ 

ጂኦ ስፓሻል መረጃዎች የማዕድን ሀብቶችን ለማወቅና ለግብርናና ለመሳሰሉት ጥቅም የሚሰጥ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ በኩል ይህንን እንዲሠራ ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ ካርታ ሥራዎች ኤጀንሲ ነው፡፡ ይሁን እንጂ የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲም የጂኦ ስፓሻል ኢንተለጀንስ ሥራ የማከናወን ኃላፊነት በአዋጅ ተሰጥቶታል፡፡ 

ይህም ማለት ከሳተላይት ወይም ከአየር ላይ በመሬት የሚከናወኑ እንቅስቃሴዎችን ለደኅንነት ሲባል የመከታተልና የመተንተን ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ በሁለቱ ተቋማት መካከል የሚታየውን የኃላፊነት መጣረስ ለማስተካከልም የማሻሻያ ሥራ በመሥራት ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል፡፡

 

የኮንትራት ስምምነቱ በተፈረመበት ወቅት

በአዲስ አበባ ከተማ በዋና ዋና ጐዳናዎች ላይ ከ132.6 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ መንገድ ጠቋሚ ምልክቶችን ለማኖር፣ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን ከአንድ አገር በቀል ኩባንያ ጋር ተፈራረመ፡፡

ከ388 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቁ አምስት የመንገድ ግንባታዎች ለኮንትራክተሮች ተሰጡ፡፡ዓርብ ግንቦት 14 ቀን 2007 ዓ.ም. በባለሥልጣኑ ዋና መሥሪያ ቤት በተደረገው የኮንትራት ስምምነት ላይ እንደተገለጸው፣ በአዲስ አበባ በ52 መንገዶች ላይ የታቀዱትን መንገድ ጠቋሚ ምልክቶች ለመትከል ጨረታውን አሸንፎ ሥራውን የተረከበው፣ ዩኢ ኢንደስትሪያል የተባለው ኩባንያ ነው፡፡ በዚህ ጨረታ ላይ ሦስት ኩባንያዎች ተወዳዳሪ ቢሆኑም፣ ዩኢ ኢንደስትሪያል ያቀረበው ዋጋ ዝቅተኛ በመሆኑ አሸናፊ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ከዩኢ ኢንደስትሪያል ጋር ተፎካካሪ በመሆን ቀርበው የነበሩት ጐልድስቶን ኢንተርናሽናል ትሬዲንግ 145.2 ሚሊዮን ብር፣ ሲልክ ትሬዲንግ ኢንተርናሽናል ደግሞ 160.1 ሚሊዮን ብር አቅርበው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

የመንገድ ጠቋሚ ምልክቶቹን ለመትከል አሸናፊ የሆነው ኩባንያ ከ700 በላይ የሚሆኑ ምልክቶችን ተክሎ የሚያጠናቅቀው የኮንትራት ውሉ ከተፈረመበት ቀን አንስቶ በ270 ቀናት ውስጥ እንደሆነ በኮንትራት ስምምነቱ ላይ ተገልጿል፡፡ ምልክቶቹ አንፀባራቂ በሆነ አልሙኒየም የሚዘጋጁ ናቸው ተብሏል፡፡ ምልክቶቹ የመንገድ ስያሜዎችን፣ ርዝመትና ሌሎች መረጃዎችን የሚይዙ መሆኑን፣ የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ፍቃዱ ኃይሌ ገልጸዋል፡፡ እንዲህ ዓይነት ምልክቶች የሚታዩት በቀለበት መንገዱ ላይ ብቻ ነው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ 5.73 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸውን አምስት የመንገድ ሥራ ፕሮጀክቶችን ለማስገንባት ባለሥልጣኑ ከአራት ኮንትራክተሮች ጋር ስምምነት ፈጽሟል፡፡ በጥቅሉ ከ388.3 ሚሊዮን ብር በላይ ከሚወጣባቸው ከአምስቱ የመንገድ ፕሮጀክቶች ውስጥ እንይ ኮንስትራክሽን የሁለቱን ፕሮጀክቶች ጨረታ አሸንፏል፡፡

እንይ ኮንስትራክሽን ያሸነፈው አንዱ መንገድ ከሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ እስከ ቅድስት ማርያም – ምኒልክ ሆስፒታል – ጃንሜዳ ድረስ የሚዘልቀው 1.7 ኪሎ ሜትር መንገድ ግንባታ ነው፡፡ ይኼንን መንገድ በ74.9 ሚሊዮን ብር እንደሚገነባው ታውቋል፡፡ እንይ ኮንስትራክሽን ከዚህ ፕሮጀክት በተጨማሪ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ግቢ ውስጥ የአስፋልትና የኮብልስቶን መንገድ ለመገንባት የወጣውን ጨረታም አሸንፎ ሁለት የኮንትራት ስምምነቶችን ፈጽሟል፡፡ 

ሁለተኛውን የኢሲኤ ፕሮጀክት ያሸነፈበት ዋጋ 27.7 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ይህ የኢሲኤ የአስፋልትና የኮብልስቶን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ግማሽ ኪሎ ሜትር በአስፋልትና በኮብልስቶን ሲሆን፣  የመኪና ማቆሚያና የአስፋልት መንገድ ነው ተብሏል፡፡ የኢሲኤው ሥራ በ35 ቀናት መጠናቀቅ እንዳለበት ተገልጿል፡፡ 

ይህ ፕሮጀክት በፍጥነት ተሠርቶ እንዲያልቅ የተፈለገው ከሐምሌ 3 ቀን እስከ ሐምሌ 9 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የሚካሄደውን የፋይናንሲንግ ፎር ዴቨሎፕመንት ዓለም አቀፍ ጉባዔ ከመካሄዱ በፊት ለማድረስ እንደሆነ ባለሥልጣኑ አስታውቋል፡፡  

ከአቦ አደባባይ – ብሥራተ ገብርኤል ድረስ ያለውን 1.4 ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ ለማከናወን ጨረታውን በማሸነፍ ሥራውን የተረከበው አይኤፍኤች ኢንጂነሪንግ ነው፡፡ 30 ሜትር ስፋት ያለውን መንገድ ለመገንባት አይኤፍኤች አሸናፊ የሆነበት ዋጋ 99.4 ሚሊዮን ብር ሲሆን፣ ሥራውም በ365 ቀናት ይጠናቀቃል ተብሏል፡፡

የኮንትራት ስምምነቱ እንደሚያመለክተው ከሽሮሜዳ – ሐመረ ኖህ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ድረስ ያለውን 2.1 ኪሎ ሜትር መንገድ እንዲገነባ ጨረታውን ያሸነፈው የማነ ግርማይ ኮንስትራክሽን ኩባንያ ነው፡፡ ኩባንያው ይህንን መንገድ ለመገንባት አሸናፊ የሆነበት ዋጋ 187.02 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ መንገዱ ጠባብ በመሆኑ አሁን በ20 ሜትር ስፋት በአስፋልት ኮንክሪት ይገነባል፡፡ በስምምነቱ መሠረት መንገዱ 540 ቀናት ይጠናቀቃል ተብሏል፡፡

      

 

በአዲስ አበባ አቃቂ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የአረቄ ፋብሪካ የኢህአዴግ ባለስልጣኖች መሆኑን ያወቁ ሰዎች እንዳቃጠሉት ታወቀ።በአዲስ አበባ አቃቂ ክፍለ ከተማ የሚገኘው አረቄ ፋብሪካ ንብረትነቱ የከፍተኞች የኢህአዴግ አመራሮች የኩማ ደመቅሳና አዲሱ ለገሰ መሆኑን የተገነዘቡ ወገኖች ይህ ፋብሪካ በሃገርና በህዝብ ገንዘብ ተሰርቶ ለባለስልጣኖች ጥቅም ብቻ መዋል የለበትም በማለት ግንቦት 11/2007 ዓ.ም እንዳቃጠሉት የሚስጥሩ አዋቂ ምንጮቻችን ከከተማዋ ገለፁ። ፋብሪካው […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ምርጫው ሁለት ቀናት ብቻ ቀሩት። በመላ ሀገሪቱ አፈሳው፡ እስሩና እንግልቱ ተባብሶ ቀጥሏል። በአዲስ አበባ ብረት ለበስ ወታደራዊ ካሚዮኖች በብዛት እየታዩ ነው። ከወትሮው የተለየ የሰራዊት ቁጥር በየመንገዱ ላይ እንደሚታይ ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በተለይ ወጣቱ ከፍተኛ እንግልት እየደረሰበት ነው። በአሁኗ ኢትዮጵያ ወጣትነት ወንጀል የሆነ ይመስላል። _በአምቦ 18 ፖሊሶች ታስረዋል። ዶክተር መረራ ጉዲና ሰሞኑን በመንግስቱ ቴሌቪዥን […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ሚያዚያ 1/2007 ዓ.ም በብአዴን ኢህአዴግ ስርዓት የተለጠፈውን የምረጡኝ መቀስቀሻ ፖስተር በማየት ለውጥ ለማያመጣ ስርዓት አንመርጥም እያሉ እየቀደዱት መሆናቸውን ምንጮቻችን ገለፁ፣ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 04 በኢህአዴግ የተለጠፈውን የምርጡኝ መቀስቀሻ ፖስተር በማየት ለውጥ ለማያመጣ ስርዓት አንመርጥም በማለት እየቀደዱት መሆናቸውን የገለፀው ይህ መረጃ በህብረተሰቡ ተግባር የተናደዱት የስርዓቱ ካድሬዎች ምንም አይነት ወንጀል ላልፈፀመ ዜጋ አንተነህ የለጠፍነውን […]

የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን ተነፍጎ ባገር በቀሉ የወያኔ አፓርታይድ አገዛዝ ስረ ወድቆ ፍዳውን እያየ ነው። ስርአቱ ላለፉት 24 አመታት በሃገራችን ውሰጥ በፈጠራቸው ፖለቲካዊ፤ ማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ስነልቦናዊ ቀውሶች ምክንያት ተተኪው ወጣት ትውልድ ባስደንጋጭ ሁኔታ በየጊዜው አገሩን ጥሎ ሲወጣ በባህር ውስጥ በመስመጥና፤ ከዛም የተረፈው በአፍሪካና በአረብ አገሮች እጅግ አሰቃቂ ለሆኑ ውርደት ስቃይና ግድያ ተጋልጧል። ከምርጫ ሂደት ጋር በተያያዘ፤ […]

የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ከመቶ ዓመታት በላይ ነው። ይኼ ግንኙነት በሁለቱ ሃገሮች መካከል ሊኖር የሚገባውን የእኩልነትና የጋራ ጥቅም መሰረት ያደረገ እንደ ነበረ ታሪክ ያስታውሳል። መንግሥታት ቢለዋወጡም በሁለቱ ሃገሮች መካከል የተመሰረተው የቆየ ግንኙነት አይፈርስም የሚል እምነት አለኝ። የኢትዮጵያ ስደተኞች አሜሪካን የመጀመሪያ መድረሻ አድርገን አሜሪካዊ የሆንንበትና ወደፊትም የምንሆንበት ዋና ምክንያት የአሜሪካ አስኳል እሴቶች–ነጻነት፤ የግለሰብ ክብር፤ ፍትህ-ርትእ፤ የሰብአዊ መብቶች […]

እንደወትሮው ከኢትዮጵያ የሚመጡ ዜናዎች አያስደስቱም፤ ሀገራችን ከጥፋት ማማ ላይ መድረሷን ያሳያሉ። ለአራት ጊዜ በሸፍጥ ተመርጫለሁ ብሎ ሥልጣን ላይ ቂጥ ያለው ወያኔ ለአምስት ጊዜ ሊያወናብድ እየተዘጋጀ ነው። በየጊዜው ጥቂቶች ብቻ በገሃድ የምርጫውን ሸፍጥነት ሲያጋልጡ ምዕላተ ሕዝቡ ግን ከሹሹክታ ያለፈ እንደ ቡርዲና ቡርኪነፋሶ ዳር እስከዳር በአደባባይ ወጥቶ ሲቃወም አይታይም፤ ዘንድሮ ግን ሌላ ድርጅቶች ወይም ግለሰቦች ሣይጠብቅ እርሰ […]