በምርጫ ቦርድ ፖለቲካዊ ውሳኔ የአንድነት ፓርቲን ሰርተፊኬትና ማህተም ያገኙት አቶ ትዕግስቱ አወሉና ተከታዩቻቸው በመካከላቸው በተነሳ ልዩነት ምክንያት በምርጫው በዕጩነት ከቀረቡ ሰዎች መካከል 10ሩ ከምርጫው ራሳቸውን ለማግለል መወሰናቸውን በመጥቀስ ደብዳቤ ለምርጫ ቦርድ ቢያስገቡም ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ደብዳቤያቸውን እንዲስቡና በምርጫው እንዲሳተፉ እንደተነገራቸው ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የመረጃ ምንጭ ተናግሯል ፡፡ እንደ ምንጩ አቶ ትዕግስቱ ሐሰተኛ የስም ዝርዝር በማዘጋጀት […]

Ethiopiana election 2015 (VOA)(ቪኦኤ) በኬንተኪ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ደረሰ ጌታቸው፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና የመገናኛ ብዙኃን ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ እና የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር፣ አሁን በዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ውስጥ የሚሠራው መስፍን ነጋሽ አስተያየታቸውን ሰጥተውበታል። ጽዮን ግርማ አወያይታቸዋለች።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጠ/ሚኒስትሩ በፓርላማ ተገኝተው ከኢህአዴግ የም/ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸውን ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን በዚህ ምላሻቸውም በስም ያልጠቀሱዋቸውን ተቃዋሚዎች አስጠንቅቀዋል። የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ወደምርጫው የገቡት በግማሽ ልብ መሆኑን ፣ የብጥብጥና የሁከት አማራጭ ከተገኘ ያንን ለማካሄድ የሚያስቡ ናቸው ሲሉ ፈርጀዋቸዋል። ” የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎቹ በአንዳንድ አካባቢዎች ከወዲሁ እኛ አሸንፈናል፣ ከተሸነፍን ደግሞ ምርጫው ተጭበርብሮአል፣ ይህንን አውቃችሁ ምላሽ መስጠት አለባችሁ ብለው ሕዝብን […]

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትሩ በፓርላማ ተገኝተው ከኢህአዴግ የም/ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸውን ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን በዚህ ምላሻቸውም በስም ያልጠቀሱዋቸውን ተቃዋሚዎች አስጠንቅቀዋል። የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ወደምርጫው የገቡት በግማሽ ልብ መሆኑን ፣ የብጥብጥና የሁከት አማራጭ ከተገኘ ያንን ለማካሄድ የሚያስቡ ናቸው ሲሉ ፈርጀዋቸዋል። ” የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎቹ በአንዳንድ አካባቢዎች ከወዲሁ እኛ አሸንፈናል፣ ከተሸነፍን …

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ረዩተርስ ከካይሮ እንደዘገበው በሳውድ አረቢያ የሚመራው የጥምር ሃይል በየመን በአንድ አለማቀፍ የበጎ አድራጎት ጽህፈት ቤት ላይ በወሰደው ጥቃት 5 ኢትዮጵያውያን ሲገደሉ 10 የሚሆኑት ደግሞ ቆስለዋል። ጥቃቱ የሃውቲ ሚሊሺያዎች ዋና ደጋፊ ተደርጎ በሚቆጠረው ሃጅያ ግዛት ውስጥ በሚገኘው ማይዲ ከተማ ላይ በከባድ መሳሪያና በአየር መፈጸሙን የዜና ድርጅቱ ገልጿል። …

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ2005 ዓም ቁጥራቸው ከ20 ሺ ያላነሰ በአብዛኛው ከመስራቅና ምእራብ ጎጃም የመጡ ዜጎች፣ ክልሉን ለቀው እንዲወጡ በመታዘዛቸው ቁጥራቸው በውል ያልተወቁት መንገድ ላይ ሲሞቱ፣ ሌሎች ደግሞ ቤት ንብረታቸውን አጥተዋል። በጊዜው ኢሳትና ሌሎች የመገናኛ ብዙሃን ባደረሱት ተጽኖ መንግስት ተፈናቃዮች እንዲመለሱ ቢያደርግም፣ አጥፊዎችን ለፍርድ የማቅረቡ ጉዳይ ለረጅም ጊዜ ሲጓተት ቆይቶ …

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል፤ አባላትን መልምለዋል፤ ለሽብርተኛ ቡድኑ መረጃ አቀብለዋል፤ እንዲሁም ወደኤርትራ በመኮብለል የሽብር ድርጅቱን ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ተሰናድተው ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ በሚል የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በ7 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ መመሰርቱን …

ERTA

የመን ውስጥ አምስት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በአየር ድብደባ ህይወታቸውን ማጣታቸውን መንግስት አስታወቀ በአየር ድብደባው ሌሎች ሁለት ኢትዮጵያዊያንም ከባድና ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳች ጽህፈት ቤት ለኢብኮ በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡

በሰሜን የመን ሃራድ በሚባለው አካባቢ በሚገኘው…

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ቡድኑ እስከ ዛሬ ተዘዋውሮ በጎበኛቸው አካባቢዎች ያነጋገራቸው ተወዳዳሪዎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ምርጫው ነፃ እና አሳታፊ እንዲሆን ምርጫ ቦርድ ሁሉንም ወገን እንዲያወያይ መጠየቃቸውን የቡድኑ መሪ የቀድሞው ናሚብያ ፕሬዝዳንት ሂሲኬ ፑኜ ፑሃማባ አስታውቀዋል።

በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ 19ኛ ወንጀል ችሎት ጉዳያቸው እየታየ፣ እና በእነዘላላም ወርቅአፈራሁ የክስ መዝገብ ተከስሰው የሚገኙት እነሀብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ ባህሩ ታዬ …የአቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት ለሰኔ 1፣ 2 እና 3 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ዛሬ በችሎት ጸሀፊ በኩል እንደተሰጣቸው ጠበቃቸው አቶ ተማም አባቡልጉ ገልጸዋል፡፡ ተከሳሾቹ ወደፍርድ ቤት ቢመጡም […]

ሰበር ዜና፡- የቦንጋ ምርጫ በግጭት ምክንያት ለሌላ ጊዜ ተላለፈ

በደቡብ ክልል በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ጊምቦ የምርጫ ክልል በግል ዕጩነት ተመዝግበው የሚወዳደሩት የዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች፣ ደኢሕዴን/ኢሕአዴግን ከወከሉት ዶ/ር መብራቱ ገብረ ማርያም ደጋፊዎች ጋር

በመጋጨታቸው ምክንያት በሥፍራው በመጪው እሑድ ግንቦት 16 ቀን 2004 ዓ.ም. ይካሄድ የነበረው ጠቅላላ ምርጫ ለሌላ ጊዜ መተላለፉን፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ወንድሙ ጐላ ለሪፖርተር አስታወቁ፡፡

‹‹የሁለቱ ዕጩዎች ደጋፊዎች ግጭት በመፍጠራቸው ምክንያት ምርጫውን በሰከነ ሁኔታ ለማካሄድ ይቻል ዘንድ፣ በዚያ ምርጫ ክልል የሚካሄደው ምርጫ ሌላ ጊዜ እንዲከናወን ተላልፏል፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡

አቶ ወንድሙ የተቋረጠው ምርጫ መቼ እንደሚካሄድ ግን አልገለጹም፡፡ 

 

ተቃዋሚው አረና ትግራይ “በአባሎቼ ላይ ተፈፅሟል” ባለው ድብደባና ለምርጫ ቅስቀሣ ሥራ በተከራያት መለስተኛ አውቶቡስ ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በመላው የትግራይ ክልል የጀመረውን የምረጡኝ ቅስቀሣ ዛሬ ማቋረጡን ይፋ አድርጓል። ዘጋቢያችን ግርማይ ገብሩ የተሽከርካሪዋ የኋላ መስትዋትና መብራት መሰባበሩን በሥፍራው በአካል ተገኝቶ ተመልክቷል። ድብደባ ተፈፀመብን ከሚሉ ሰዎች መካከል ደግሞ ከአፅቢ ከተማ የመጡት አቶ ሄድሮም ኃይለሥላሴ እራሣቸው ላይ በመፈንከታቸው […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሚያዝያ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ገዢው ፓርቲ ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ ህዝቡን አስተባብረው ህዝባዊ አመጽ ያስነሱ ይሆናል በሚል የሚጠረጥራቸውን ወጣቶች ሁሉ እያፈሰ ከማሰር አልፎ ፣ አንዳንዶች እየተገደሉ ሌሎች ደግሞ አሰቃቂ ድብደባ እየተፈጸመባቸው ነው። በባህርዳር ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ የሚማር አንድ የመድረክ አባል እንደሆነ የሚታወቅ የ3ኛ አመት ተማሪ ግቢው ውስጥ ወድቆ ከተገኘ በሁዋላ …

ሚያዝያ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው ግንቦት 12/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት በሃያዎቹ የእድሜ ክልል የሚገኙት ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ እየሩሳሌም ተስፋው ፣ ፍቅረማርያም አስማማው እና ደሴ ካህሳይ ናቸው። ተከሳሾች “ኤርትራ ውስጥ መቀመጫውን ባደረገውና በሽብርተኝነት በተፈረጀው ግንቦት ሰባት ስር አባል ሆነው የሽብር ተልዕኮ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ወስነው …

ከአዲስ አበባ በደረሰን መረጃ በባለ ጎማ ታንክ በከትማይቱ  በማስፈራራት ጀምሮአል። በምርጫ ቅስቀሳ የፈራው የወያኔ መንግስት ፓርቲዎችን በክርክሩ መርታት ሲሳነው በተደረጉት ምርጫዎች ሁሉ አይተናል በክርክሩ የህዝብ አመኔታን ያጣው ገዢው ወያኔ የሚጨብጠው ቢያጣ ንቢቱን ተመስሎ በተሰራ ባለ ጎማ ታንክ በከትማይቱ ላይ ይደነፋ ጀምሮአል ድሮም ኮሮጆ በመስረቅ  ነው 25 ዓመት በሃይል የገዛው ። ገዥው የወያኔ መንግስት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ አምስተኛው የኢትዬጲያ ብሄራዊ […]

‹‹በይልቃል ጌትነት እና በዮናታን ተስፋዬ ላይ መስክር እያሉ ያሰቃዩኛል›› ብርሃኑ ተ/ያሬድ በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የፌደራል አቃቤ ህግ በቀን ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም በእነ ብርሃኑ ተክለያሬድ ላይ የመሰረተው ክስ ከሦስት ሳምንታት በኋላ ዛሬ ግንቦት 12/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በንባብ ተሰምቷል፡፡ በብርሃኑ ተ/ያሬድ ስም በተከፈተው የክስ መዝገብ ላይ አራት ሰዎች የተካተቱ ሲሆን፣ እነዚህም […]

የሰንበት ት/ቤቶቹን አንድነት ለማገድ እና አመራሩን ለመበተን መታቀዱን ተቃውመዋል በአጥቢያዎች የተቀናጀ ፀረ ሙስና እና ፀረ ኑፋቄ እንቅስቃሴ እንደሚካሔድ ተጠቁሟል ‹‹የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እንጂ የበዓላት ማድመቂያ ብቻ ቄጤማ አይደለንም››/ወጣቶቹ/ (ሰንደቅ፤ ፲ኛ ዓመት ቁጥር ፭፻፮፤ ግንቦት ፲፪ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም.) በምዝበራ ላይ የተሰማሩ አማሳኝ የገዳማት እና የአድባራት ሓላፊዎች የሀብት ምንጭ እንዲመረመር፣ ማስረጃ በቀረበባቸው የተሐድሶ መናፍቃን፣ በሕገ ወጥ […]

ሶደሬ ሚድያ 

ሀና መሀመድ አብዱል ከሪም በጆርዳን ልጇን በቀዶጥገና ስትገላገል የቀዶህክምና ያደረገላት ዶክተር ሞባይሉን ሆዷ ውስጥ እንደረሳው ተጠርጥሯል ነገር ግን ስልኩ እንቅስቃሴ እስኪያሰማ ድረስ አላወቀችም ነበር፡፡

የ36 ዓመቷ ሀና በግል ሆስፒታል ሲሆን ልጇን የተገላገለችው ሆዷ ሲንቀሳቀስ በተመለከቱ ጊዜም መልሰው እዚያው ሆስፒታል…

ሰማያዊ ፓርቲ ከምርጫ እንደወጣ ተደርጎ እየተቀሰቀሰ እንደሆን ታወቀ • ‹‹ሰማያዊ በሚያደርገው ቅስቀሳ ስለተደናገጡ ያደረጉት ነው›› አቶ ስለሽ ፈይሳ ሰማያዊ ፓርቲ ከ2007 ዓ.ም ምርጫ ራሱን አግልሏል በሚል አዲስ አበባ ውስጥ የተሳሳተ ቅስቀሳ እየተደረገበት እንደሆነ የሰማያዊ ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ስለሽ ፈይሳ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ማንነታቸውን ያልታወቁ አካላት ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በገዥው ፓርቲ በሚደርስበት ጫና ምክንያት […]

በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ጥቃቱ በተደራጀ መንገድ መቀጠሉ ተሰማ

በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ የነበረው ጥቃት ጋብ ብሎ የነበረው ቢሆንም፣ በተደራጀ መንገድ እንደገና መጀመሩን በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ 

ለበርካታ አፍሪካውያን ሕይወት መጥፋትና ንብረት መውደም ምክንያት የሆነውን ‘ዜኖፎብያ’ (የዘረኝነት ጥቃት) የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካወገዘ በኋላ፣ ለተወሰኑ ጊዜያት ተቀዛቅዞ የነበረው ጥቃት እንደገና አገርሽቶ 14 የኢትዮጵያውያን ሱቆች በቀናት ውስጥ እንደተቃጠሉ፣ በደርባንና በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በቃጠሎ የሰው ሕይወት ባይጠፋም አንድ ኢትዮጵያዊ አቅሉን ስቶ ሆስፒታል መግባቱን አቶ ኤፍሬም ጠቁመዋል፡፡ 

ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በደርባንና በአካባቢው ወይም ክዋዙሉ ናታል በሚባለው አውራጃ ከጥቂት ቀናት በፊት ለኢትዮጵያውያን የሱቅ ባለቤቶች የማስፈራሪያ ደብዳቤም እንደደረሳቸው ተናግረዋል፡፡ ለሪፖርተር በኢሜይል የደረሰው ደብዳቤ በአሥር ቀናት ውስጥ እስከ እሑድ ግንቦት 9 ቀን 2007 ዓ.ም. አካባቢውን ለቀው እንዲሄዱ፣ ያለበለዚያ ግን ሞት እንደሚጠብቃቸው የሚያትት ነው፡፡ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በቅጽል ስማቸው ‹‹የኡምላዚ ነጋዴ ገዳዮች›› ተብለው የሚታወቁት እነዚህ ጥቃት ፈጻሚዎች የሞት ደብዳቤ መሆኑን በመንገር፣ ለኢትዮጵያዊያኑ እንደሰጧቸው አቶ ኤፍሬም አስረድተዋል፡፡

እንደ አቶ ኤፍሬም ማብራሪያ፣ ጥቃቶቹ ድንገት ሳይሆን ለዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ ናቸው፡፡ ‹‹በብዙ ሚዲያዎች ያልተነገረው በመጋቢት ወር አካባቢ የደረሰው የአምስት ኢትዮጵያውያን ተቃጥሎ መሞትም የዚህ ማሳያ ነው፤›› ያሉት አቶ ኤፍሬም፣ የቅርብ ጊዜው ጥቃት በደቡብ አፍሪካ መንግሥትና በዓለም አቀፍ ጫና ለጥቂት ቀናትም ጋብ ብሎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ለዓመታት ለፍተው ያፈሩት ንብረታቸውን ያጡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ ከተሞች በመሸሽና ከዘመድ ተጠግተው በመኖር ላይ እንደሆኑም ጠቁመዋል፡፡ አንዳንዶች ያላቸውን ንብረት በመያዝ ሱቆቻቸው እንደገና ለመክፈት ጥረት በማድረግ ላይ ቢሆኑም፣ ብዙዎቹ ሱቆች (ኮንቴይነሮችን) ጨምሮ በደቡብ አፍሪካውያን መወረሳቸውንም ይገልጻሉ፡፡

በቀን ይደረግ የነበረው ተቀይሮ ጥቃት ፈጻሚዎች ሱቆችን በምሽት በእሳት እያቃጠሉ መሆናቸውን ያስረዳሉ፡፡ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. የአቶ ኤፍሬምን ጨምሮ አምስት ሱቆች መቃጠላቸውን፣ አቶ ኤፍሬም ግሮሠሪያቸው በመቃጠሉ ምክንያት 400 ሺሕ ብር ያህል እንዳጡ ተናግረዋል፡፡ ዘረፋዎችም እየጨመሩ እንደሆኑ ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያውያንን የሚኖሩበት ቦታ በመሄድ ማስፈራራቱም እንደቀጠለ ይናገራሉ፡፡ በሚያዝያ ወር አካባቢ በነበረው ጥቃት ምክንያት 15 ያህል ሰዎች በቁጥጥር ሥር ቢውሉም፣ በዋስትና መውጣታቸውን አቶ ኤፍሬም ይናገራሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያውያን ለፖሊስ የከሰሱ ሲሆን፣ ጉዳያቸውም እየታየ እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ በቅርብ የተቃጠሉ ሱቆች 40 ያህል መሆናቸውን አሁን ደግሞ ከ50 መብለጣቸውን ያስረዳሉ፡፡ በሱቆች መቃጠልና በዘረፋው ምክንያት ከ800 እስከ 1,000 የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን እንደተጐዱም ያክላሉ፡፡ 

በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን 6,000 ያህል ይገመታሉ የሚሉት አቶ ኤፍሬም፣ ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ለብዙ ኢትዮጵያውያን ደም መፋሰስ ምክንያት ሊሆን እንደሚችሉም ያስረዳሉ፡፡ ‹‹የነበረው ጥቃት ጋብ ያለ ቢመስልም ተዳፈነ እንጂ አልጠፋም፡፡ አሁንም እሳቱ እንደተቀጣጠለ ነው፡፡ በዚህ ከቀጠለም የኢትዮጵያውያን ደም እንደሚፈስ ምንም ጥርጥር የለውም፤›› ብለዋል፡፡ 

ኢትዮጵያዊያኑ ሥራ መጀመርና ከደቡብ አፍሪካውያን ጋር አብሮ በሰላም መሥራት እንደሚፈልጉ የሚናገሩት አቶ ኤፍሬም፣ ይህ ግን የማይቻል እንደሆነም ግምታቸውን ይናገራሉ፡፡ ቢሆንም ግን ሕይወታቸው አደጋ ውስጥ ሆኖም ብዙዎች ወደ ሥራ ለመመለስ በመጓጓት ላይ መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡ ‹‹ንብረቱን የተቀማና የተቃጠለበት ስደተኛ ብዙ ነገር ያጣ ቢሆንም፣ አሁንም ወደ ሱቁ መሄድን መርጧል፤›› በማለት ያለውን አስቸጋሪ ሁኔታ ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤምባሲ የዙሉን ንጉሥ ጉድዊል ዝዌልቲንና ቤተሰቦቻቸውን፣ እንዲሁም ሌሎች የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናትን በማናገር ጉዳዩን ለመፍታት እየጣረ ቢሆንም ሁኔታው ግን አስቸጋሪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ 

በሚያዝያው ጥቃት ምክንያት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 30 ያህል ኢትዮጵያውያንን ለመመለስ ችሏል፡፡ በአጠቃላይ ከ100 የሚበልጡ ኢትዮጵያውያን የተመዘገቡ ሲሆን፣ የመጀመሪያዎቹ ተመላሾች በቅርቡ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ እንደሚሉት፣ ደቡብ አፍሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደቡብ በአፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ችግር እንዲፈታ ጥረት እያደረገ ነው፡፡ አሁን ደረሰ የተባለውን ጥቃት በተመለከተ ግን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ እንደሌለው አቶ ተወልደ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የመመለሱን ሥራ የኢትዮጵያ መንግሥት የጀመረው ቢሆንም፣ በርካታ ኢትዮጵያውያን ግን ከሞት ጋር መጋፈጥን መምረጣቸው ታውቋል፡፡ መፍትሔው ምን ይሆን? ለሚለው አቶ ኤፍሬም ሲመልሱ፣ ‹‹የደቡብ አፍሪካ መንግሥትና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በዚህ ጉዳይ ጣልቃ ገብተው ጠንካራ ዕርምጃ እንዲወሰድ መደረግ አለበት፤›› ብለዋል፡፡ 

አሁን ደረሰ የተባለውን ጥቃት አስመልክቶ በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ሙሉጌታ ከልልን በስልክ ለማግኘት ጥረት ቢደረግም ሊሳካ አልተቻለም፡፡  

 

 

ዳሸን ባንክ የአዲሱ ፕሬዚዳንት ሹመት እንዲፀድቅለት ጥያቄ አቀረበ

ሁለት ምክትል ፕሬዚዳንቶችን ሰይሟል

የዳሸን ባንክ ሥራ አመራር ቦርድ በተሰናባቾቹ የዳሸን ባንክ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት ምትክ በተጠባባቂነት የተሰየሙትን አዲስ ተተኪዎች ሹመት እንዲያፀድቅለት፣ ለብሔራዊ ባንክ ጥያቄ አቅርቦ ምላሽ እየጠበቀ ነው፡፡

የዳሸን ባንክ ቦርድ በፈቃዳቸው ኃላፊነታቸውን ለቀዋል የተባሉትን የቀድሞውን ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ወልደ ሥላሴን ተክተው የባንኩ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ ያጫቸው አቶ አስፋው ዓለሙን ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክም ሹመቱን እንዲያፀድቅለት ቦርዱ ጥያቄውን አቅርቧል፡፡ ከአቶ ብርሃኑ ቀደም ብሎ የሥራ መልቀቂያ ባስገቡት በቀድሞው ምክትል ፕሬዚዳንት በአቶ አበበ ተክሉ ምትክ ደግሞ አቶ ጌትነት ደሴ ተጠባባቂ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው እንዲሠሩ ቦርዱ የሰየማቸው መሆኑ ታውቋል፡፡ አቶ ጌትነት ይህንን ኃላፊነት እንዲይዙ ከመደረጉ በፊት የባንኩ ፕሬዚዳንት ልዩ አማካሪ በመሆን ሲያገለግሉ ነበር፡፡

ባንኩ ለሁሉም የባንኩ ከፍተኛ የኃላፊነት መደቦች በተጠባባቂነት የመደባቸው አዲሶቹ ተሿሚዎች በባንኩ ውስጥ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች የቆዩ ናቸው ተብሏል፡፡ አዲሱ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት አቶ አስፋው የባንኩ የኦፕሬሽን ማኔጅመንት ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ናቸው፡፡ በአቶ አስፋው ተይዞ የነበረውን የኦፕሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንትነት ቦታ ደግሞ አቶ ኃይሉ ቡልቡላ  እንዲይዙት ተደርጓል፡፡ አቶ ኃይሉ ወደዚህ ኃላፊነት እንዲያድጉ እስከተደረበት ጊዜ ድረስ የባንኩ ቄራ ቅርንጫፍ ዋና ሥራ አስኪያጅ ነበሩ፡፡ አቶ ብርሃኑ መጋቢት 26 ቀን 2007 ዓ.ም. ባስገቡት መልቀቂያ ደብዳቤ ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል ቢባልም፣ ከኃላፊነት የለቀቁት በግዳጅ እንደሆነ ይነገራል፡፡ የምክትላቸውም ስንብት በተመሳሳይ የሚታይ ነው እየተባለ ነው፡፡

የዳሸን ባንክ ማኔጅመንት መዋቅር አንድ ፕሬዚዳንትና አራት ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንደሚኖሩት ያሳያል፡፡ ሆኖም ከአራቱ የምክትል ፕሬዚዳንቶች ቦታዎች የሦስቱ ኃላፊዎች ተሹመውላቸው ሲሠራባቸው ቆይቷል፡፡ አንድ የምክትል ፕሬዚዳንት (ስትራቴጂክ ፕላኒንግ) ቦታ ግን እስካሁን አልተሾመበትም፡፡ ይህ የስትራቴጂክ ፕላኒንግ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ቦታ አዲስ በመሆኑ ምደባ ሳይደረግ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ አስፈላጊነቱ ታምኖ የፀደቀ ስለሆነ አዲሱ የስትራቴጂክ ፕላኒንግ ምክትል ፕሬዚዳንት ይመደባል ተብሎ እንደሚጠበቅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡

ዳሸን ባንክ በአገሪቱ ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ የግል ባንኮች ውስጥ በሀብት ክምችቱ በመጀመርያ ደረጃ ላይ የሚቀመጥ ነው፡፡ የአገሪቱን የፋይናንስ ተቋማት ዓመታዊ ክንዋኔዎች የሚያሳዩ አኅዛዊ መረጃዎችም ከሌሎች የግል ባንኮች ብልጫ ያለው ትርፍ እንደሚያስመዘግብ ያሳያሉ፡፡ የ2007 ዓ.ም. የአሥር ወራት የሥራ አፈጻጸምን የሚያመለክተው የመጀመርያ ደረጃ ሪፖርት የባንኩ ሀብት 24 ቢሊዮን ብር መድረሱን ይጠቁማል፡፡ ይህም ከሌሎች የግል ባንኮች ብልጫ ያለው ሀብት እንዳለው የሚያሳይ ነው፡፡ ከዳሸን ባንክ ቀጥሎ የተቀመጠው አዋሽ ባንክ ሀብቱ 22.4 ቢሊዮን ብር ነው፡፡

ላለፉት አሥር ተከታታይ ዓመታት ከፍተኛውን ትርፍ እያስመዘገበ የዘለቀው ዳሸን ባንክ የ2007 ዓ.ም. የአሥር ወራት ክንውኑ የሚያሳየው፣ አሁንም ከሌሎች ባንኮች ብልጫ ያለው ትርፍ ማግኘቱን ነው፡፡ 

ባንኩ በአሥር ወራት ከግብር በፊት ያገኘው ጠቅላላ ትርፍ 760 ሚሊዮን ብር መሆኑን መረጃው ያመለክታል፡፡ በ2006 ዓ.ም. ባንኩ ከ980 ሚሊዮን ብር በላይ ማትረፉ ይታወሳል፡፡ ዳሸን ባንክ ከ720 በላይ ባለአክሲዮኖችን ያሉት ሲሆን፣ እስካለፈው ወር መጨረሻ ድረስ የተከፈለ ካፒታሉ 1.23 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡ ይኼም ከአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ቀጥሎ ሁለተኛው ከፍተኛ የተከፈለ ካፒታል ነው፡፡ የአዋሽ ባንክ የተከፈለ ካፒታል 1.48 ቢሊዮን ብር ነው፡፡

ዳሸን ባንክ ከምሥረታው ጀምሮ የነበሩት አቶ ተከተል ሀብተ ጊዮርጊስ የመጀመርያው ፕሬዚዳንት ነበሩ፡፡ ቀጥለውም አቶ ልዑል ሰገድ ተፈሪ የተሾሙ ሲሆን፣ እሳቸውን የተኩት ደግሞ አቶ ብርሃኑ ወልደ ሥላሴ ናቸው፡፡ አቶ ብርሃኑ በቅርቡ ከሥልጣናቸው ሲገለሉ፣ አሁን ለፕሬዚዳንትነት አቶ አስፋው ታጭተዋል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ሹመቱን ካፀደቀው አቶ አስፋው አራተኛው የባንኩ ፕሬዚዳንት ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

 

ከየመን 2,524 ዜጎች መመለሳቸውን መንግሥት አስታወቀ

የመን ውስጥ በተፈጠረው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት አደጋ ላይ የወደቁ ኢትዮጵያውያን ምን ያህል እንደሆኑ በውል ባይታወቅም፣ ከአራት ሺሕ በላይ ስደተኞች ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው በአስቸኳይ ለመመለስ ሰንዓ በሚገኘው ኤምባሲ መመዝገባቸው ተገለጸ፡፡

ሰኞ ግንቦት 10 ቀን 2007 ዓ.ም. የገቡትን ጨምሮ 2,524 ዜጎች ወደ አገራቸው መመለስ መቻሉን መንግሥት አስታወቀ፡፡ 

በዕለቱ ከረፋዱ አምስት ሰዓት ይገባሉ ተብሎ የተጠበቁት የየመን ተመላሾች ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማሪፊያ ሲደርሱ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ ደከምከም ያሉና ሕፃናት የያዙ ተመላሾች ይበዙ ነበር፡፡

በዕለቱ ወደ አገራቸው የተመለሱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር 260 መሆኑን፣ ቀደም ሲል የገቡትን ጨምሮ እስካሁን 2,524 ስደተኞች ኢትዮጵያ መግባታቸውን፣ ዶ/ር ቴድሮስ በሥፍራው ለተገኙት ጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡ 

የየመን መንግሥትን በምትደግፈው ሳዑዲ ዓረቢያና በኢራን በሚደገፉት የሁቲ አማፂያን መካከል በተነሳው የእርስ በርስ ጦርነት በተለይ የውጭ አገር ስደተኞች አደጋ ላይ ወድቀዋል፡፡ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ኤምባሲ ላይ ጥቃት በመፈጸሙ ምክንያት በኢትዮጵያውያኑ ዘንድ ፍርኃትንና ድንጋጤን ፈጥሮ እንደነበር ሪፖርተር ያነጋገራቸው ተመላሾች ተናግረዋል፡፡ ተመላሾቹ እንደሚሉት፣ ብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በአገሪቱ ገጠራማ አካባቢዎችና በጠረፍ አካባቢዎች የሚገኙ በመሆናቸው ለአደጋ የተጋለጡ ናቸው፡፡ 

መንግሥት በቀን ከ200 እስከ 400 ስደተኞች ወደ አገራቸው እየመለሰ መሆኑን፣ እስካሁን የተመዘገቡት ከ4,000 በላይ ዜጎች በሚቀጥሉት አራትና አምስት ቀናት ውስጥ ጠቅልለው ወደ አገራቸው እንደሚገቡ ዶ/ር ቴድሮስ አስረድተዋል፡፡ 

ሚኒስትሩ ከጋዜጠኞች ጋር የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው ወደ ተመላሾች ፊታቸውን ሲያዞሩ ከተመላሾቹ አንዱን ወጣት፣ ‹‹ተቸገራችሁ አይደል? ዘገየንባችሁ? ኤርፖርቱ እኮ ጥቃት ስለደረሰበት የእሱን ዕድሳት እየጠበቅን ነበር፡፡ ነገር ግን አልተሳካም፤›› ሲሉት፣ ወጣቱም መልሶ፣ ‹‹ዶ/ር በጣም ነው የምናመሰግነው፡፡ በተቻላችሁ መጠን ደርሳችሁልናል፡፡ ረድታችሁናል፤›› በማለት መልሶላቸዋል፡፡ ሌሎችም ተመሳሳይ አስተያየት ነበራቸው፡፡ 

በየመን እየተካሄደ ባለው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት በሊቢያ በኢትዮጵያን ላይ የተፈጸመው ዓይነት ጉዳት እንዳለ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹እስካሁን ይህ ነው የሚባል ጉዳት የደረሰበት ሰው የለም፡፡ ለደከሙትና ለታመሙት ቅድሚያ ሰጥተን ነው እያመጣን ያለነው፤›› የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ 

ከተመላሾች መካከል አንዱ የሆነው ወጣት መኮንን ገበየሁ ሁኔታውን በተመለከተ ለሪፖርተር እንደገለጸው፣ በሶማሊያ በኩል በባህር አድርጎ ነበር ወደ የመን የገባው፡፡ ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት እምብዛም አስቸጋሪ ነገር አልገጠመውም፡፡ ጦርነቱ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ ግን፣ ‹‹ወደ አገሬ የምገባበት ቀን ናፍቆኝ ነበር፡፡ በጣም ነው የሚያስፈራው፤›› ብሏል፡፡ መመለስ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ኤምባሲ ሄደው መመዝገብ እንዳለባቸው የሰማው መኮንን፣ ተቀጥሮ ይሠራው የነበረውን አስተናጋጅነት ጥሎ መምጣቱን ይናገራል፡፡ እሱ ይኖር የነበረው በዋና ከተማ ሰንዓ ነበር፡፡ በጣም የሚያስጨንቀው በጠረፍ አካባቢዎች ስላሉት ኢትዮጵያውያን መሆኑንም ተናግሯል፡፡ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ሠራተኞች የተደረገለትን ትብብርም አመስግኗል፡፡ 

ፈይሰል አህመድም ከተመላሾች መካከል አንዱ ነው፡፡ ከሦስት ዓመት በፊት በጂቡቲ በኩል ነበር ወደ የመን የተሻገረው፡፡ ያለፈበትን አሰቃቂ ጉዞ ማስታወስ አይፈልግም፡፡ ‹‹ስደት ሲባል አስቸጋሪ ነው፡፡ የእኛ ዓይነቱ ስደት ሕገወጥ ነው፡፡ ሕጋዊ የሚባል ስደት የለም፤›› በማለት በስደት ሆኖ የደረሰበት የከፋ እንደሆነ ገልጿል፡፡ ቀደም ሲል የመን እንደገባ ገጠር በመሄድ በአንድ እርሻ ውስጥ ተቀጥሮ ያርስ እንደነበር ይናገራል፡፡ ቀጥሎም እርሻውን ትቶ ወደ ከተማ በመግባት ተቀጥሮ የፅዳት ሥራ ይሠራ ነበር፡፡ ‹‹አሁን በጣም አስቸጋሪ ሆኗል፡፡ መብራት የለም፡፡ ውኃ የለም፡፡ ምግብ የምናበስለው በጋዝ ነበር፡፡ ጋዝ ደግሞ አይገኝም፡፡ ችግር ላይ ወድቀን ነበር፤›› ብሏል፡፡ 

ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ ጊዜ ጀምሮ ስደተኞች የከፋ ችግር እንደሚገጥማቸው የገለጸው ፈይሰል፣ በኢትዮጵያዊያን ላይ በተለይ የሚደርስ አደጋ እንዳለ ከሪፖርተር ጥያቄ ቀርቦለት ነበር፡፡ ፈይሰል፣ ‹‹ሁለቱም ወገኖች አንደኛው የሌላኛው ደጋፊዎች ናችሁ እያሉ ያስፈራሩናል፡፡ ነገር ግን በተለየ ጥቃት አልፈጸሙብንም፡፡ ነገር ግን ጦርነቱ የከፋ ነው፡፡ እላይህ ላይ ቤት ይፈርሳል፤›› ብሏል፡፡ 

የፈይሰል ሥጋት ብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን በጠረፍ አካባቢዎች ስለሚሠሩና ጦርነቱም የከፋው እዚያ ስለሆነ ጉዳት እየደረሰባቸው ሊሆን ይችላል የሚል ነው፡፡ ‹‹እንዳንድ ጊዜም አልቃይዳ ናችሁ ይሉናል፤›› ብሏል፡፡ ‹‹እባክህን የተቀሩት ኢትዮጵያውያንን እንዳይገድሏቸው መንግሥት እንዲረዳቸው ንገርልን፤›› በማለት አስተያየቱን አጠቃሏል፡፡ 

በተያያዘ ዜና ከሊቢያ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን የማስወጣት ሥራ ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑን፣ በቅርቡ በሁለቱም አካባቢዎች (በትሪፖሊና በቤንጋዚ) የሚገኙት   100 ስደተኞችን ለማስመለስ መንግሥት በዝግጅት ላይ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

 

አክጉን ግሩፕ የተባለው የቱርክ ኩባንያ በአሥር ቢሊዮን ዶላር በሰንዳፋ አካባቢ ለመገንባት ላቀደው ኢትዮ ተርኪሽ የኢንዱስትሪ ዞን ያስጠናውን የአካባቢና ማኅበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ፣ የአካባቢና የደን ሚኒስቴር ውድቅ አደረገው፡፡

ሚኒስቴሩ ይህንን የተፅዕኖ ጥናት ውድቅ ማድረጉንም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማክሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. አስታውቋል፡፡

ሚኒስትሩ አቶ በለጠ ታፈረ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለፓርላማ ባቀረቡበት ወቅት፣ ኩባንያው ያቀረበው ጥናት ግልጽነት የጐደለው ነው ብለዋል፡፡ 

አክጉን ግሩፕ ሰንዳፋ አካባቢ ለማስገንባት ከኦሮሚያ ክልል 100 ሔክታር መሬት ተረክቦ የተወሰኑ እንቅስቃሴዎችን ያደረገ ቢሆንም፣ ግንባታ እንዳይጀምር በመንግሥት ታግዶ ቆይቷል፡፡

ይህ የሆነበት ምክንያት የኢንዱስትሪ ዞኑ ይዞታ ከለገዳዲ የውኃ ማጣሪያ ያለው ርቀት አምስት ኪሎ ሜትር ርቀት ብቻ ያለው በመሆኑ፣ በአዲስ አበባ የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ላይ ውኃውን በመበከል ችግር ይፈጥራል የሚል ሥጋት ነው፡፡

ይሁን እንጂ ኩባንያው ችግሩን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሥራዎችን እንደሚያከናውን በመስከረም ወር 2007 ዓ.ም. ለሪፖርተር ገልጾ ነበር፡፡ የአክጉን ግሩፕ የቦርድ አባል የሆኑት ሚስተር ዩኑስ አክጉን በወቅቱ የአካባቢ ተፅዕኖ ማስተካከያ ዕቅድ መንደፋቸውን ጠቁመው ነበር፡፡ ይህንንም ለማድረግ የተፅዕኖ መቋቋሚያ የአካባቢና የማኅበራዊ ተፅዕኖ ጥናት እንደሚያካሂዱ ገልጸው ነበር፡፡ 

የአካባቢና የደን ሚኒስትሩ ለፓርላማ ባቀረቡት ሪፖርት ግን የቀረበው የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ መሠረታዊነት ግልጽነት የጐደለው፣ አገሪቱ የምትጠቀምበትን አሠራር ያላሟላና ባለድርሻ አካላትን ያላሳተፈ በመሆኑ ውድቅ ተደርጓል፣ በመሆኑም ኩባንያው እንዲያስተካክል ተነግሮታል ብለዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር አርከበ እቁባይ አክጉን ግሩፕ ወደ ሐዋሳ ወይም ድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ዞን እንዲሸጋገር ሐሳብ ማቅረባቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ኩባንያው ግን በአዲስ አበባ ዙሪያ እንዲሆንለት ጥያቄ እያቀረበ ይገኛል፡፡   

 

ዘ ኢስት አፍሪካን የተሰኘ ድረ ገጽ 50 የሚሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ የታጠቁ የኢትዮጵያ ወታደሮች የኬንያን ድንበር በማቋረጣቸው ምክንያት፣ የኬንያ የፀጥታ አካላት በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ መሆናቸውን ዘገበ፡፡ መንግሥት ግን አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጠየቁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ተወልደ ሙሉጌታ ‹‹ብዙም የተጠናከረ መረጃ የለኝም፤›› በማለት ለሪፖርተር ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በኬንያ ሰሜናዊ ሁር ግዛት የሚገኘውን ኢለሬት ፖሊስ ጣቢያን የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የተቆጣጠሩት የሁለቱ አገሮች ድንበር ለማካለል የቅየሳ ሥራ ከተጠናቀቀ ከአንድ ሳምንት በኋላ እንደሆነ፣ የኬንያ ፖሊስን ጠቅሶ ድረ ገጹ አስነብቧል፡፡

ክላሺንኮቭ መሣሪያዎችን የታጠቁ የኢትዮጵያ ወታደሮች በአሥር ተሽከርካሪዎች ተጭነው የኬንያን ድንበር 16 ኪሎ ሜትሮችን ያህል አቋርጠው በመግባት ገዥ ቦታዎችን በመያዝ፣ የፖሊስ ጣቢያውን የከበቡ መሆናቸውና በአካባቢው ቅኝት ማድረጋቸውን፣ እንዲሁም ፎቶግራፎችን ማንሳታቸውንም እንዲሁ ድረ ገጹ አስነብቧል፡፡

በድረ ገጹ ዘገባ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ሥፍራውን እንደሚለቁ ቃል መግባታቸውን ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ሠራዊት ድንበሩን ያቋረጠበትን ምክንያት ያልጠቀሰው ድረ ገጹ፣ የኢትዮጵያ ጦር ዘንድሮ ለሦስተኛ ጊዜ የኬንያን ድንበር ማቋረጡን አስታውሶ ዘግቧል፡፡

የኬንያ መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኮሎኔል ዴቪድ ኦቦነዬ ስለክስተቱ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው፣ ‹‹ኢትዮጵያና ኬንያ ዘለግ ያለ ዕድሜ ያስቆጠረ ግንኙነት ያላቸውና ወዳጆች ከመሆናቸው አንፃር ኢትዮጵያውያኑ የከፋ ነገር ያደርሳሉ የሚል እምነት የለኝም፤›› በማለት መግለጻቸውን ድረ ገጹ አስነብቧል፡፡

ጉዳዩን አስመልክቶ በማኅበራዊ ድረ ገጾች አስተያየታቸውን ያሰፈሩ ሰዎች፣ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የኬንያን ድንበር በማለፍ የገባው በመጪው እሑድ የሚካሄደው ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ሥጋት እንዲካሄድ አስተማማኝ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡ በተለይ አልሸባብን የመሳሰሉ ሰርጎ ገቦች የፀጥታ ሥጋት እንዳይሆኑ ለማድረግ የተከናወነ ድርጊት መሆኑንም አክለዋል፡፡ 

 

ብረታ ብረት ኮርፖሬሽን ተርባይን ማምረቻ ፋብሪካ ሊገነባ ነው

በ350 ሚሊዮን ብር ያስገነባውን ትራንስፎርመር ፋብሪካ አስመርቋል

በግዙፉ መንግሥታዊ የኢንዱስትሪ ተቋም የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ሥር የሚገኘው የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ፣ የተርባይን ፋብሪካ ሊገነባ መሆኑን አስታወቀ፡፡ 

በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መጀመሪያ ላይ ማለትም በ2008 ዓ.ም. የመጀመሪያ ወራት የተርባይንና የጄኔሬተሮች ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን፣ የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ የኢንዱስትሪ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ አሰፋ ዮሐንስ ገልጸዋል፡፡ 

በአሁኑ ወቅት ኢንዱስትሪው ለኃይድሮ ፓወር ማመንጫነት የሚያገለግሉ ተርባይኖችና ጄኔሬተሮች ዲዛይን የማድረግ አቅም መፍጠሩን የገለጹት ሻለቃ አሰፋ፣ በቀጣዩ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን መርሐ ግብር መጀመሪያ ላይ የተፈጠረውን አቅም ወደ ማምረት፣ መትከልና ሥራ ማስጀመር ይቀየራል ብለዋል፡፡ 

ፋብሪካውን ለማቋቋም ምን ያህል ወጪ ያስፈልጋል የሚለውና ሌሎች የአዋጭነት ጥናቶች በመካሄድ ላይ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን በ2002 ዓ.ም. በአሥር ቢሊዮን ብር ካፒታል ሲመሠረት፣ የ200 ሺሕ ብር መንቀሳቀሻ ካፒታል ተፈቅዶለት በኮርፖሬሽኑ ሥር የተደራጀው የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ በአሁኑ ወቅት ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል እንደሚያንቀሳቅስና በሥሩም ሰባት ፋብሪካዎች መቋቋማቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ 

በቅርቡ በ350 ሚሊዮን ብር ካፒታል ከአዲስ አበባ በ20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ታጠቅ የኢንዱስትሪ ዞን ያስገነባውን የትራንስፎርመር ፋብሪካ ግንቦት 9 ቀን 2007 ዓ.ም. አስመርቋል፡፡ 

የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ይህንን ፋብሪካ ከመገንባቱ ቀደም ብሎ የተለያዩ ትራንስፎርመሮችን ምርትና ዕድሳት በማድረግ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያቀርብ የነበረ መሆኑ ይታወሳል፡፡ 

ከዚህ በተጨማሪም የተለያዩ መጠን ያላቸው ትራንስፎርመሮችን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ማቅረቡን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ 

ነገር ግን ቀደም ሲል የሚያመርትበት ወርክሾፕና የአገሪቱ የትራንስፎርመር ፍላጎት መጨመር ራሱን የቻለ ፋብሪካ እንዲያቋቁም አስገድዶታል፡፡ በመሆኑም በቡራዩ ታጠቅ የኢንዱስትሪ መንደር በ28 ሔክታር ላይ ያረፈ ፋብሪካ በቻይናው ፖሊ ግሩፕ አማካሪነት ገንብቶ በይፋ አስመርቋል፡፡ 

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪና የኢንፎርሜሽንና ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የአገሪቱ የትራንስፎርመር ፍላጎት በዚህ ፋብሪካ እንደሚሸፈን ገልጸዋል፡፡ 

‹‹ኢትዮጵያውያን አይችሉትም›› የሚል አስተሳሰብ የነበራቸው ወዳጅ አገሮችን ያሳመኑ ፕሮጀክቶችን የኢትዮጵያ ብረታ ብረት ኮርፖሬሽን ማረጋገጡን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ከትራንስፎርመር ማምረቻ ፋብሪካው በተጨማሪ በ300 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያስገነባው የኬብልና ዋየር ማምረቻ፣ የፓወር ፋክተር ኮሬክተርና የኮምፓክት ሰብስቴሽን ማምረቻ፣ በ350 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተገነባ የኢንጂን ማምረቻ ፋብሪካ፣ በ300 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተገነባ የሶላር ፓናል ማምረቻ ፋብሪካ፣ በ200 ሺሕ ብር የተገነባ የሞተርና ጄኔሬተር ፋብሪካ በሥሩ ይገኛሉ፡፡ 

 

የፊታችን እሑድ በሚደረገው ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ የሆነው የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በዘንድሮ የምርጫ ተሳትፎው ላይ በርካታ ችግሮች እየገጠሙት ቢሆንም፣ በምርጫው እስከ መጨረሻው ድረስ ተሳትፎው እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡ 

‹‹ለመርሆዋችን ተገዥ በመሆን የምርጫ ተሳትፎአችን እስከ መጨረሻው ይቀጥላል፤›› በሚል ርዕስ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ፣ በምርጫ ተሳትፎው ላይ እየደረሱ ነው ያላቸውን ችግሮች ኢዴፓ ገልጿል፡፡

ፓርቲው ያገኛቸውን ነፃ የአየር ሰዓቶች በመጠቀም አማራጮቹን ለሕዝብ እንዳያደርስ በሚዲያ ተቋማት የደረሰበትን ሳንሱር፣ በየክልሉ በሚወዳደሩ ዕጩዎቹ ላይ የማዋከብ፣ የማስፈራራት፣ ስም የማጥፋትና የመደብደብ ዕርምጃዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው፣ ዕጩዎቹና ደጋፊዎቹ ቅስቀሳ እንዳያደርጉ መከልከላቸው፣ የፖስተር መቀደድ እንደ ገጠመው፣ ባነሮችን ከቦታቸው ላይ መሰወርና ዕጩዎቹን ከሥራ ማባረር፣ ደመወዝ መከልከል፣ ከአገልግሎት ማግለልና የመሳሰሉት እየደረሱበት ካሉ ችግሮች መካከል ተጠቃሽ እንደሆኑ አስታውቋል፡፡

ኢዴፓ በዚህ መጠኑ ያለፈ ተፅዕኖ ምክንያት በክልል የሚገኙ ጥቂት ዕጩዎቹ ራሳቸውን ከምርጫ እንቅስቃሴ ለማግለል የሚያስገድዳቸው ሁኔታ እንደተፈጠረ በመግለጫው የጠቆመ ቢሆንም፣ የፓርቲው የጥናትና ምርምር ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ ግን ችግሩ በድርድር ተፈቶ አሁን ዕጩዎቹ ሥራዎቻቸውን በአግባቡ እያናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

አቶ ዋሲሁን፣ ‹‹ቁጫና ወላይታ ላይ አባሎቻችን ከሌሎች ፓርቲ አባላት ጋር በመሆን ከምርጫው ራሳቸውን እንደሚያገሉ ገልጸው የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን ችግሩ በመፈታቱ ሥራቸውን ቀጥለዋል፡፡ የምርጫ ቅስቀሳውንም ሲያከናውኑ ነበር፤›› በማለትም አክለዋል፡፡

‹‹ፓርቲያችን እነዚህ ከመጠን ያለፉ ጫናዎች ቢኖሩም፣ አባሎቻችንና መዋቅሮቻችን ችግሩን ተቋቁመው በምርጫው ውስጥ የሚያደርጉትን ተሳትፎ እስከ መጨረሻው እንዲዘልቁበት ጥረት እየተደረገ ይገኛል፤›› በማለት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም በምርጫው ተሳታፊነቱን እንደሚያረጋግጥ ኢዴፓ በመግለጫው አስታውቋል፡፡

በዚህ አገር የምርጫ ሥርዓቱ ጠንካራ መሠረት ላይ ሊቆም የሚችለው በማኩረፍና ራስን ከምርጫ ሒደት በማግለል ሳይሆን፣ በሒደቱ ውስጥ በመቆየት ችግሮችንና ጫናዎችን በመቋቋም፣ በማጋለጥና ችግሮች እንዲፈቱ ጥረት በማድረግ ነው ብሎ እንደሚያምንም ኢዴፓ አትቷል፡፡

በዘንድሮ ምርጫ ከሚሳተፉ 58 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የሆነው ኢዴፓ፣ 165 ዕጩዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ 501 ዕጩዎችን ካቀረበው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) እና 270 ዕጩዎችን ካስመዘገበው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በመቀጠል፣ በርካታ ዕጩዎችን በማስመዝገብ ሦስተኛ ፓርቲ መሆኑን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል፡፡ በቦርዱ መረጃ መሠረት 139 ዕጩዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ በአራተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ ነው፡፡   

 

በርካታ የውጭ ኩባንያዎች ከንፋስ ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት አሳዩ

በሰኔ 2007 ዓ.ም. መጨረሻ በሚጠናቀቀው የአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን፣ ከንፋስ ከሚገኝ የኤሌክትሪክ ኃይል 894 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ቢታሰብም፣ ማሳካት የተቻለው 324 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ መሆኑ ተገለጸ፡፡ 

 

ይህ 324 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሊገኝ የቻለው ከአዳማ አንድ 51 ሜጋ ዋት፣ ከአሸጎዳ 120 ሜጋ ዋትና ግንቦት 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ከተመረቀው አዳማ ሁለት 153 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ድምር ነው፡፡ 

ሌሎች ፕሮጀክቶች በሚፈለገው ፍጥነት መሄድ ባለመቻላቸው ዕቅዱ ወደሚቀጥለው አምስት ዓመት መሸጋገር ግድ ሆኖበታል፡፡ በዕቅድ ዘመኑ ግንባታቸው ተጀምሮ ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቁ የነበሩት አይሻ 300 ሜጋ ዋት፣ መሶቦ-ሐረና 42 ሜጋ ዋት፣ አሰላ 100 ሜጋ ዋትና ደብረ ብርሃን 100 ሜጋ ዋት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡ 

እነዚህ ፕሮጀክቶች ግን እስካሁን ፋይናንስም ሆነ ኮንትራክተር አላገኙም፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፣ እነዚህን የንፋስ ኃይል ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለማግኘት በርካታ ኩባንያዎች ፍላጎት እያሳዩ ነው፡፡ 

ምንጮች እንደገለጹት የአይሻን ፕሮጀክት የቻይናው ዲዶንግ ፎንግና የጀርመኑ ላፍቶ ኩባንያዎች ለማልማት ፍላጎት አሳይተዋል፡፡ ከእነዚህ ኩባንያዎች በተጨማሪ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የፕሮጀክቱ ተሳታፊ እንዲሆን መንግሥት ፍላጎት አሳይቶ በድርድር ሒደት ላይ ይገኛል፡፡ 

አዳማ ሁለትን የገነቡት ኃይድሮ ቻይናና ሲጂሲ ኦቨርሲስ አሰላ ላይ ይገነባል ተብሎ የሚጠበቀውን የንፋስ ኃይል ፕሮጀክት በአዳማ ሦስት ስም ለመረከብ ድርድር እያካሄዱ ነው፡፡ 

ነገር ግን የአሜሪካው ዲሴንቴ ኩባንያን ጨምሮ የቱርክ፣ የቻይናና የአውሮፓ ኩባንያዎች የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ለማግኘት ፍላጎት እያሳዩ በመሆናቸው ውድድሩ መካረሩን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ 

እነዚህ የውጭ ኩባንያዎች ይዘው የመጡት በዓለም አቀፍ ደረጃ የወቅቱ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ከመሆኑም ባሻገር፣ አንድ ተርባይን ያለው የማመንጨት አቅም አሁን ካለው 1.5 ሜጋ ዋት የበለጠ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ድርጅት በሩን ለድርድር እንዲከፍት እንዳደረገው ታውቋል፡፡ 

ከአዲስ አበባ ከተማ 95 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተገነባው አዳማ ሁለት ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በተመረቀበት ወቅት የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ ዓለማየሁ ተገኑ እንደተናገሩት፣ የአዳማ ሁለት ፕሮጀክት ሥራ መጀመር በአገሪቱ ከንፋስ ኃይል ይመረት የነበረውን 171 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ወደ 324 ሜጋ ዋት አሸጋግሮታል፡፡ 

‹‹እነዚህ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ከውኃ ማመንጫ ጣቢያዎች ጋር የተጣጣመ የኃይል ስብጥር ለመፍጠር ጠቀሜታ አላቸው፤›› ያሉት አቶ ዓለማየሁ፣ ‹‹የዝናብ እጥረት በሚያጋጥምበት ወቅት የንፋስ ኃይል የሚጨምር በመሆኑ፣ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ከመዘርጋት አንፃር ጉልህ ሚና ይጫወታል፤›› በማለትም የፕሮጀክቱን ጠቀሜታ አብራርተዋል፡፡ 

በአሁኑ ወቅት ከውኃና ከንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 2,368 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃ ያመለክታል፡፡ 

ኢትዮጵያ ከውኃ 50 ሺሕ ሜጋ ዋት፣ ከንፋስ 1.3 ሚሊዮን ሜጋ ዋት፣ ከእንፋሎት ከአሥር ሺሕ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳላት መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ 

በሰኔ 2005 ዓ.ም. ተጀምሮ በግንቦት 2007 ዓ.ም. የተጠናቀቀው አዳማ ሁለት 102 ተርባይኖች አሉት፡፡ አንዱ ተርባይን 1.5 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ ይህ ፕሮጀክት 345 ሚሊዮን ዶላር ሲወጣበት፣ 85 በመቶ በቻይናው ኤግዚም ባንክ፣ ቀሪው 15 በመቶ ደግሞ በኢትዮጵያ መንግሥት የተሸፈነ መሆኑ ታውቋል፡፡ 

 

አወዛጋቢ በነበረው የባዮ ሴፍቲ ወይም የደኅንነት ሕይወት ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የፓርላማው የተፈጥሮ ሀብትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለመጀመርያ ጊዜ ጥልቅ የተባለ ውይይት ካደረገበት በኋላ፣ በረቂቁ ላይ ማሻሻያዎችን በማከል ማክሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ፓርላማው አፀደቀው፡፡

በ2001 ዓ.ም. በጄኔቲክ ምሕንድስና የተለወጠ ህያው ወደ ኢትዮጵያ በሚገባበት ወቅት፣ በኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ደህንነት ላይ ጉዳት እንዳያደርስ የሚያስችል እጅግ ጥብቅ የተባለ የኢትዮጵያ የደኅንነት ሕይወት አዋጅ ፀድቆ ነበር፡፡

የዚህ አዋጅ መፅደቅ በወቅቱ ተከስቶ ለነበረ ድርቅ በጄኔቲክ ምሕንድስና የተለወጠ የስንዴ ዕርዳታ ወደ አገር እንዳይገባ ተፅዕኖ ፈጥሮ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ 

ይህ አዋጅ በጄኔቲክ ምሕንድስና የተለወጡ ዘሮች ወይም ህያዋን ለጥቅም እንዳይውሉ ይከልክል እንጂ ለምርምር፣ ለትምህርትና ለሙከራ በዝግ ላብራቶሪ መከናወን የሚቻልበትን ሁኔታ አመቻችቷል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንን በዝግ ላብራቶሪ የተፈቀዱ ምርምሮችን ለማድረግ የተቀመጡት መሥፈርቶች አስቸጋሪነትና የአዋጁ ዓላማም ወደ መከልከል ያመዘነ በመሆኑ፣ ረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ ጥቅምት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ለፓርላማ ቀርቦ ነበር፡፡ 

ረቂቅ አዋጁ የተመራለት የተፈጥሮ ሀብት ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ከጥቅምት 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ አምስት መድረኮችን በማዘጋጀት ከተለያዩ የአገር ውስጥ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጐ፣ የውሳኔ ሐሳቡን ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ለምክር ቤቱ አቅርቧል፡፡

በማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ አንቀጽ ሁለት ንዑስ አንቀጽ 1(5) ላይ የሰፈረውን ድንጋጌ ሙሉ በሙሉ ሰርዞታል፡፡ 

የተሰረዘው አንቀጽ ‹‹የተጤነ ልቀት›› ማለት ከግንዛቤ በመነጨ ስምምነት ልውጥ ህያውን ለንግድ፣ ለምግብ፣ ለዕርዳታ ምግብ፣ አካባቢን ለማፅዳት፣ ለማስተማሪያነት፣ ለምርምር፣ ለመስተዋት ቤት፣ ለውኃ ውስጥ እርባታ፣ ለእንስሳት መኖ፣ ወይም ለሌላ የእንስሳት ግብዓት፣ ለሰው ወይም ለእንስሳት ሕክምና ወይም ለማስወገድ ወደ አካባቢ መልቀቅ እንደሆነ ያስቀምጥ ነበር፡፡ 

ይህ ማሻሻያ ረቂቅ አንቀጽ ላይ በኢትዮጵያ የሚገኙ የአካባቢ ጥበቃ አቀንቃኞች እንዲሰረዝ ከፍተኛ ግፊት ሲያደርጉ ነበር፡፡ ለዚህ የሚሰጡት ምክንያት ደግሞ የተለወጠ ህያው ወደ አካባቢ መለቀቁ በኅብረተሰብ ጤና ላይ ጠንቅ እንደሚኖረውና የኢትዮጵያን ብዝኃ ሕይወት ይበርዛል የሚል ነው፡፡

ይህንን ሥጋት ከግምት ውስጥ ያስገባው የፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ አንቀጹን ሙሉ በሙሉ ሰርዞታል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ብሔራዊ የደኅንነት ሕይወት አማካሪ ኮሚቴ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወጣ ደንብ በሕግ እንዲቋቋምና የኮሚቴው ተግባርም ደኅንነተ ሕይወትን በተመለከተ መንግሥትን ማማከር ነው፡፡ 

ቋሚ ኮሚቴው የአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች ያቀረቡት ሐሳብን ሙሉ በሙሉ ባይቀበልም፣ የተደረጉት ሁለት ማሻሻያዎችና ብሔራዊ አማካሪ ኮሚቴ በሕግ እንዲቋቋም መደረጉን ሪፖርተር  ያነጋገራቸው ባለሙያዎች ተቀብለዋል፡፡

ሁለተኛ የተባለው ማሻሻያ ‹‹በግንዛቤ የመነጨ ስምምነት እንዲሰጠው ለሚኒስቴሩ ማመልከቻ የሚያቀርብ ማንኛውም ሰው በላከው አገር ሕግ ዕውቅና ያለው መሆን አለበት፤›› ይላል፡፡ 

በረቂቁ ተቀምጦ የነበረው ግን ‹‹ከግንዛቤ የመነጨ ስምምነት እንዲሰጠው የሚጠይቅ የውጭ ላኪ፣ በላኪው አገር ሕግ ኃላፊነት እንዲወስድ የሚፈቀድለት መሆኑን የሚገልጽ በራሱ በላኪው የተፈረመ ሰነድ ማቅረብ አለበት፤›› የሚል ነው፡፡

የአካባቢ አቀንቃኞቹ ይህ አንቀጽ መሻሻል እንዳለበት፣ ምክንያቱም ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በአገራቸው ኃላፊነት እንዲወስዱ የሚገልጽ ደብዳቤ መጻፋቸው ተጠያቂ ስለሚያደርጋቸው፣ በአገራቸው ሕግ ራሳቸው ዕውቅና ያላቸው መሆን ይገባቸዋል ሲሉ አቤቱታቸውን ሲያሰሙ ነበር፡፡ 

ከግንዛቤ የመነጨ ስምምነት የሚል ስያሜ ያለው ፈቃድ ማግኘት ማለት፣ የተለወጠ ህያውን ወደ አካባቢ የመልቀቅ እንቅስቃሴን ለማካሄድ የሚያስችል ብቻ ነው፡፡ ፓርላማው በቋሚ ኮሚቴው የቀረበለትን የውሳኔ ሐሳብ በሙሉ ድምፅ በመቀበል ረቂቁን አፅድቆታል፡፡     

 

በትላንትናው እለት በገዢው ፓርቲ የደህንነት ሀይሎች ተይዞ ወደማዕከላዊ ተወስዶ የነበረው የሰማያዊ ፓርቲው አቤል ኤፍሬም ማዕከላዊ በሚገኙ የገዢው ፓርቲ ደህንነቶች ከትላንት ከቀኑ 5 ሠዓት ጀምሮ እስከ እኩለሌሊት በተፈፀመበት ከፍተኛ ድብደባ ኩላሊቱ በመጎዳቱ ዛሬ ጠዋት 11 ሠዓት ላይ ወደምንሊክ ሆስፒታል እንደተወሰደ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አቤል ከመያዙ ከአንድ ቀን ቀደም ብሎ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች […]

አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ማን ናቸው?

አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና አቡነ ተክለ ሃይማኖት(EMML 3051) 18ኛው መክዘ
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በ13ኛው መክዘ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ግብጻዊ ቅዱስ ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መረጃዎች መሠረት ወደ ኢትዮጵያ ገቡ የሚባለው በዐፄ ላሊበላ ዘመን ነው፡፡ የትውልድ ቦታቸው በላዕላይ ግብጽ ንሒሳ   (የአሁኑ ባሕቢት አል ሐጋራ) ነው፡፡ [በርግጥ አንዳንድ ሊቃውንት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ኢትዮጵያዊ መሆናቸው፤ ነገር ግን የወላጆቻቸው ስም በሚገባ ለመታወቅ ባለመቻሉ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እናታቸው አቅሌስያ (ቤተ ክርስቲያን)፣ አባታቸውም ስምዖን (ካህን) እንደተባሉና የዚህም ምክንያቱ ከቤተ ክርስቲያን የተገኙ ለማለት መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ አንድ መጽሐፈ ታሪክም ‹አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ብጹዐን ወቅዱሳን ተወልዱ በኢትዮጵያ› ይላል፡፡EMML 5538,f 55]
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከ500 ዓመታት በላይ በዚህ ምድር ላይ መኖራቸውንና ከትግራይ እስከ ሸዋ ባለው ክፍል ተዘዋውረው ማስተማራቸውን፡፡ በዚህም ምክንያት ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስንና ምድረ ከብድ ገዳማትን መትከላቸውን ታካቸው ያሳያል፡፡ ያረፉት በዐፄ ሕዝብ ናኝ ዘመን (1414-1418ዓም) ነው፡፡ ጻድቁ በትግራይ አቡዬ፣ በአማራው አቡነ፣ በኦሮሞዎች ዘንድ ደግሞ አቦ በመባል ይታወቃሉ፡፡ ዋናዎቹ ገዳሞቻቸው ሁለት ሲሆኑ ዝቋላ በኦሮምያ ክልል፣ ምድረ ከብድ ደግሞ በደቡብ ክልል ይገኛሉ፡፡ 

አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን
1.      ከውጭ መጥተው ኢትዮጵያ ውስጥ ከኖሩ ቅዱሳን አንዱ ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የሚታወቁት ቅዱሳን ከአመጣጣቸውና አኗኗራቸው አንጻር በሦስት ይመደባሉ፡፡ ኢትዮጵያ ተወልደውና ኖረው ኢትዮጵያ ያረፉ(አብዛኞቹ ቅዱሳን በዚህ ምድብ ናቸው)፣ ከውጭ መጥተውና ኖረው ኢትዮጵያ ያረፉ(ሰላማ ከሣቴ ብርሃን፣ማኅበረ ጻድቃን፣ ተሰዓቱ ቅዱሳን፣ አባ ሊባኖስ፣ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ እጨጌ ዕንባቆም) ኢትዮጵያ ተወልደው ውጭ ኖረው ያረፉ(አቡነ ኤዎስጣቴዎስ፣ ሙሴ ጸሊም፣ ሙሴ ሐበሻው(ሙሳ አል ሐበሽ)፣ገብረ ክርስቶስ(አብዱል መሲሕ))፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በውጭ ሀገር ተወልደው ኢትዮጵያ መጥተው ኖረው ካረፉት ቅዱሳን የሚመደቡ ናቸው፡፡
2 1በቁም ከሚሳሉ ጥንታውያን ሥዕሎች አንዱ ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የግድግዳና የብራና ላይ ሥዕሎች መካከል ለብቻቸው በቁም በአብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት ከሚሳሉት አራት ቅዱሳን (አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ፣ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና አቡነ አረጋዊ) አንዱ ናቸው፡፡ የቁም ሥዕላቸው ከወሎ ገነተ ማርያም እስከ አዲስ አበባ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ግድግዳ ላይ ይገኛል፡፡
3 2. ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀጥለው በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የሚከበሩ ጻድቅ ናቸው፡፡ በ1990 ዓም በነበረው የሰበካ ጉባኤ የአብያተ ክርስቲያናት ቅጽ መሠረት በመላ ሀገሪቱ ከ2620 በላይ በአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ስም የሚጠሩ አብያተ ክርስቲያናት ነበሩ፡፡
4 3. የንጉሥ ዐዋጅ ቅድስናቸውን ካወጀላቸው ቅዱሳን አንዱ ናቸው፡፡ በዓላቸው በመጋቢትና በጥቅምት 5፣ በጥቅምት 27 እና በታኅሣሥ 29 እንዲሆን ንጉሥ ሕዝብ ናኝ ዐውጇል፡፡
5 4. በ14/15ኛው መክዘ የጸሎት መጻሕፍት የሥርዓተ ጸሎት ቅደም ተከተል መሠረት ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀጥለው ለምልጃ የሚጠሩት ገብረ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡
6 5. በሰዓታትና ኪዳን ጸሎት ጊዜ ገድላቸው ከሚነበቡ ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን (አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ አቡነ አረጋዊ) አንዱ ናቸው፡፡
7 6. የአራዊት አባቶች ከሚባሉት(አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ አረጋዊ፣ አቡነ በርተሎሜዎስ) አንዱ ናቸው፡፡
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በሕዝቡ ባሕል ውስጥ፤ ለምን?
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን በተለየ በሕዝቡ ባሕል ውስጥ ቦታ አላቸው፡፡ በሕዝቡ ባሕል ውስጥ ቦታ በመያዝ ከቅድስት ድንግል ማርያም ቀጥሎ ያለውን ቦታ ሳይዙ አይቀሩም፡፡ የዚህን ምክንያት በርግጠኛነት መናገር ከባድ ይመስለኛል፡፡ የእኔ ግምት ግን ከሁለት ነገር የመነጨ ነው፡፡
1.      አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በሽምግልናቸው የሚታወቁ ጻድቅ በመሆናቸውና በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሽማግሌ ካለው የከበሬታ ሥፍራ የመነጨ ሊሆን ይችላል፡፡
2.     ሲመጡ ከቅዱስ ላሊበላ፣ ሲያርፉ ከንጉሥ ሕዝብ ናኝ ጋር ከነበራቸው ግንኙነት ባለፈ ከቤተ መንግሥቱ ርቀው የኖሩ ሕዝባዊ አባት በመሆናቸው የተነሣ የተፈጠረ ሕዝባዊ ቅቡልነት ሊሆን ይችላል፡፡
ማሳያዎች
፩. በይትበሃሎች
1.      አስታራቂነት፡- ነብርና አንበሳ አይስማሙም፤ በአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሥዕል ሥር ግን ነብርና አንበሳ ተስማምተው ይታያሉ፡፡ በዚህ የተነሣ ለመታረቅ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን ለማስታረቅ የሚሄዱ ሽማግሌዎች ‹አቦን ሆነን መጥተናል› ይላሉ፡፡
2.     የአቦ ጠበል፡- አንድ ሰው እየተመገበ ቢያንቀው ‹የአቦ ጠበል› እያልክ ውኃን ሦስት ጊዜ ጠጣው ይባላል፡፡
3.     የአቦ ብቅል፡- አንድ ሰው ከማያውቀው ቦታ ስሙ ቢጠራና በአካባቢው የሚያውቀውን ሰው ቢያጣ የጠራው ሰይጣን ሊሆን ስለሚችል ‹‹የአቦን ብቅል እፈጫለሁ› በል ይባላል፡፡
4.     የአቦ መገበሪያ፡- አንድ ሰው አንድን ነገር አጥፍቶ ተሠውሮ እንደማይቀመጥ ለመግለጥ ‹‹የአቦን መገበሪያ የበላ ሲለፈልፍ ይውላል›› ይባላል፡፡
5.     አቦ ሰጥ፡- አንድ ሰው የማያውቀውን ነገር በግምት ሲናገር ‹አቦ ሰጥ› ይባላል፡፡
6.     በአቦ ይዤሃለሁ፡- አራዊት የቤት እንስሳትን እንዳይበሉባቸው ገበሬዎች ‹በአቦ ይዤሃለሁ› ብለው ይገዝቷቸዋል፡፡
7.     የአቦ መንገድ፡- በሰሜን ሸዋ መራኛ አካባቢ ባሉ ሕዝቦች ዘንድ ‹የአቦ መንገድ› የሚባል ብሂል አለ፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሚዳ ከሚገኘው የአቡነ መልከ ጼዴቅ ገዳም ጥቂት ጊዜ ቆይተዋል ይባላል፡፡ በኋላ ከዚያ ገዳም ሲወጡ አቡነ መልከ ጼዴቅ ‹‹የት ሊሄዱ ነው›› ብለው ቢጠይቋቸው ‹እርሱ ወደ መራኝ›› ብለው መለሱላቸው፡፡ ከተማው ‹‹መራኛ›. የተባለው በዚህ ምክንያት ነው ይባላል፡፡ ታድያ በዚህ ምክንያት አንድ ሰው መድረሻውን በውል ሳያውቀው መንገድ ሲጀምር መንገዱ ‹የአቦ መንገድ› ይባላል፡፡
8.     የአቦ ቁራ፡- ሰይጣን በቁራ ተመስሎ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ዓይናቸውን ሊያወጣ ስለመጣ በጎ ነገር የያዘ መስሎ የሚመጣ ክፉ ሰው ‹የአቦ ቁራ› ይባላል፡፡
9.     በአቦ በሥላሴ፡- በሕዝቡ ብሂል ውስጥ ከሥላሴ ጋር ተያይዘው ብዙ ጊዜ የሚጠሩት ገብረ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ‹በአቦ በሥላሴ› ሲባል አጥብቆ መለመን ነው፡፡ በሕዝባዊ መዝሙሮችም ውስጥ ‹በአምስት አቦ ናቸው በሰባት ሥላሴ› የሚል ሐረግ በተደጋጋሚ ይሰማል፡፡
፪. በባሕላዊ ዘመን ቆጠራ
አቦ በገበሬው የወቅት አከፋፈል የዘመን መክፈያ ናቸው፡፡
1.      በገበሬው የዘመን ቆጠራ ክረምት የሚገባው ‹የሐምሌ አቦ› ዕለት ነው፡፡ የሚወጣው ደግሞ ‹የጥቅምት አቦ›፡፡
2.     በልግ ይገባል የሚባለው በየካቲት አቦ ስለሆነ ገበሬው ‹የካቲት አቦን አይተህ ተሰደድ› ይላል፡፡ በየካቲት አቦ ዝናብ ካልጣለ በልግ የለም ማለት ስለሆነ ሀገርህን ልቀቅ ነው፡፤
3.     በገበሬው ዘንድ የወሩ መግቢያ የአቦ ቀን ነው፡፡ ቀጠሮ ሲይዝ ‹አቦ በዋለ በዚህኛው ቀን› ብሎ ነው፡፡
      . አቦና ዐርበኛነት
የአቦ ቤተ ክርስቲያን ካህናት በአንኮበር፣ በጎንደርና በአዲስ አበባ ስማቸው ከዐርበኛነት ጋር ይነሣል፡፡ በሦስቱም ቦታ የሚገኙት የአቦ ቤተ ክርስቲያን ካህናት በአምስት ዓመቱ የጣልያን ወረራ በግልጽ አርበኞችን ደግፈዋል፣ ወደ በረሐ ወርደውም ታግለዋል፡፡ በዚህ ምክያትም ሦስቱም አብያተ ክርስቲያናት በጣልያን ዝርፊያና አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡ የሦስቱም ካህናት ወደ በረሐ ሲገቡ የገጠሙት ግጥምም በሥነ ቃላችን ተላልፎ እኛ ዘመን ደርሷል፡፡
አንኮበር፡-
አቡዬን ብዬ እንጂ ይህን ሁሉ ማይ
አገሬ አይደለም ወይ ዠማና አዳባይ
ጎንደር
ፊት አቦ ጎንደር፡-
እንኳን እኔ ጀግናው የፊት አቦ ልጅ
ጎንደሬ ለጣልያን አይሰጠውም እጅ
ቀበና አቦ፣ አዲስ አበባ፡-
ወግጅልኝ ድጓ ወግጅልኝ ቅኔ
ወንዶች ከዋሉበት እውላለሁ እኔ
፬. ስምና አቦ
እስከ አሁን ድረስ ባለው ባሕል ከእግዚአብሔርና ከቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች ውጭ ስማቸው ስም የሚሆነው አቦ ናቸው፡፡ ‹አቦ ነሽ፣ አቦ ነህ› የሚል ስም አለን፡፡ በሌሎቹ ቅዱሳን ግን የለም፡፡ ዘርፍ ይጨመርበታል፡፡ ወለተ፣ ገብረ እንደሚለው ያለ፡፡
፭. አቦና ጠበል
የገጠር ሰው ትዳር ሲይዝ መጀመሪያ የሚጠጣው አቦን ነው፡፡ አቦን ቀድሞ የጠጣ ትዳሩ ይሠምራል፣ ከሰውም ጋር በሰላም ይኖራል ተብሎ ይታመናል፡፡
፮. አቦ የቅኔ መማሪያ
‹አቦ ቅኔ› ለቅኔ ተማሪ የመማሪያ ሁለት ቤት ቅኔ ነው
‹አቦ ውርዝው እምነ ኩሉ በለጡ
አንድ እንጀራ በጨው እስመ በማለዳ ለምጠጡ
ማጠቃለያ
ከላይ ያየናቸውን ሥነ ቃላውያን መረጃዎች መሠረት ስናደርግ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከሌሎች የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን በላይ በሕዝቡ ውስጥ ባሕላዊ ቦታ እንዳላቸው ያሳየናል፡፡ የዚህ ምክንያቱ ምናልባት ‹ሽምግልናቸው› ሽምግልናን ከሚያከብረው ባሕላችን ጋር ተስማምቶ ወይም አብዛኛው ታሪካቸው ከቤተ መንግሥት የራቀ መሆኑ ሕዝባዊ ቅቡልነትን ስላስገኘላቸው ሊሆን ይችል እንደሆነ እንጃ፡፡ በዚህ ረገድ ከእርሳቸው የላቀ ባሕላዊ ቦታ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ያላት ቅድስት ድንግል ማርያም ናት(የማርያም መቀነት፣ የማርያም አራስ፣ የማርያም ፈረስ፣ የማርያም ግርዝ፣ ማርያም በሽልም ታውጣሽ፣ ማርያም ትቅረብሽ፣ ወዘተ)፡፡
ይህ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ባሕላዊ ቦታ ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን በእምነት ውስጥ ካላቸው ቦታ በተጨማሪ በሕዝቡ ውስጥ ያላቸውን ሀገራዊ ሥፍራ የሚያሳይ፣ እነርሱን በተመለከተ የምንሠራቸው ሥራዎች የት ድረስ የሕዝቡን ታሪካዊና ባሕላዊ መሠረት ጭምር ሊያንጹ ወይም ሊንዱ እንደሚችሉ ደግመን እንድናስብ የሚያመለክተን ማሳያ ነው፡፡ 
ላስ ቬጋስ፣ ኔቫዳ

  በኢትዮጵያ ካሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ በቀጣይ በሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ምን ይጠብቃል? በከተማ ያሉ ወጣቶች ድምፃቸውን ሊሰጡት እንደሚችሉ የሚገፀው ፓርቲው የሚያጋጥሙ እንቅፋቶች እንዳሉ ሆነው በከተማ አካባቢ በሚኖረው ምርጫ ከፍተኛ ድምፅ ሊያገኝ እንደሚችል ፓርቲው ይገልፃል ሮይተርስ በዚህ ጉዳይ ላይ ፓርቲው ያለውን አቋም ጨምሮ ትንታኔን ይዞ ቀርቧል ቀሪውን ይመልከቱ Ethiopia’s newest party takes […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለኢሳት የሚደርሱት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ በተለይ በሰሜን የአገሪቱ ክፍል አብዛኛው ህዝብ ረብሻ ይነሳል ብሎ ያምናል። በዚህም የተነሳ ቀድም ብለው ገንዘባቸውን ባንክ ያስቀመጡ ሰዎች ገንዘባቸውን እያወጡ ለምግብ የሚውሉ የእህል ዘሮችን፣ ጨውና ሌሎችንም እቃዎች እየገዙ ነው። ወፍጮ ቤቶች ሰሞኑን ተጨናንቀው ታይተዋል። አቅም ያለው ቤተሰብ ለሶስት …

ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ በተካሄደው የብአዴን ማእከላዊ የዞን ጽህፈት ቤት ሃላፊዎች ውይይት በቀጣይ ምን ማድረግ አለብን የሚለውን መመሪያ ለአባላቱ ባስተላለፈው የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክት፣ ድርጅቱ በርካታ ችግሮች እንዳሉበት የድርጅቱ ልዩ ልዩ አመራሮች ተናግረዋል፡፡ የብአዴን ማእከላዊ ዞን ጽህፈት ቤቱ ሃላፊ ሲናገሩ የብአዴን አመራሮች በ1990 ዓ.ም ከታየው የጥገኝነት ዝቅጠት አንስቶ …

ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ቤተእስራኤላውያን ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ በአገሪቱ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍንና ዘረና የሆነው ፖሊስ እንዲያዝ ጠይቀዋል። ከሳምንታት በፊት የተካሄደው ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ ደም አፋሳሽ ሆኖ ቢጠናቀቅም ፣ የአሁኑ ሰልፍ በሰላም ተጠናቋል። ከ185 ሺ በላይ ቤተእስራኤላውያን በእስራኤል ምድር የሚኖሩ ሲሆን ከዘረኝነት ጋር በተያያዘ የተለያዩ አድሎዎች ይፈጸሙባቸዋል። ከዚህ …