አወ – የተግባር እርምጃ አማራጭ የሌለው መፍትሔ ስለሆነ እኔ በበኩሌ ትግሌን በተግባር ጀምሬአለሁ፡፡ ከታች ለዘረዘርኳቸው እርምጃዎች እናንተም ጨምሩበትና ወደ ተግባር እንግባ!!! «ጠብታ ውሃ ነው ደንጋይ የሚበሳ፣ እንጩህ ዝም ብለን – ሕዝብ እስከሚነቃ፣ አገር እስኪነሳ፡፡» – ሜሮን ጌትነት እውነት ነው ሜሮን – እንጩህ !!! ዝምታው ይሰበር!!! ህወሃት በሰላም፣ በምርጫ ስልጣኑን ይለቃል ማለት ሰማይ ይታረሳል ብሎ ማሰብ […]

የወያኔ ባለስልጣኖች ብዙ ሰዓት የፈጀ የውስጥ ስብሰባ ማድረጋቸው እና በስብሰባው ሀይለኛ የሆነ የእርስ በእርስ የቃላት ሽኩቻ ማድረጋቸውንና የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታውን ማን ይያዘው በሚለው ጉዳይ በመካከላቸው አለመግባባት መፈጠሩ የደረሰን ዜና ያስረዳል:: በደረሰን ዜና መሰረት በስብሰባው አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ላይ ከባለስልጣናቱ ከኢህአዲግ የተለያዩ ወቀሳ እና ትችት የደረሰባቸው ሲሆን በደረሰን ዜና መሰረት ጠቅላይ ሚኒስር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ የጠቅላይ […]

ምንጮቻችን እንደገለጹልን ወያኔ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ብዙዎቹን የትግራይ ተወላጆችን 1 ለ 5 በሚል አደራጅቷል:: ይህም በአሻንጉሊቶቹ የተከበበት ኢህአዲግ ካለው መሰል አደረጃጀት ጎን ለጎን ነው:: እነኝሁ 1 ለ 5 የተደራጁት የወያኔ አባላትም ወደዱም ጠሉም ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜ ለሚመደብላቸው ሰው ስለሚኖሩበት፣ ስለሚሰሩበት በአጠቃላይ ስላዩት፣ ስለሰሙት፣ ስለሰለሉት ዘገባ (ሪፖርት) ያደርጋሉ:: ባለፈው እሁድ ከተካሄደውና ወያኔ እራሱ ተወዳዳሪ፣ እራሱ […]

ፓትርያርኩ ጠቅላላ ጉባኤው በላካቸው ብፁዓን አባቶች እና ተሳታፊዎች ላይ በራቸውን ዘጉ የፓትርያርኩን ዳተኝነት በማጋለጥ ፍትሕን የሚጠይቁ የዐደባባይ ሰላማዊ ሰልፎች ይካሔዳሉ በአማሳኞች እና በተሐድሶ መናፍቃን ላይ የሚደረገው ተጋድሎ በየአጥቢያዎቹ ይቀጣጠላል ማስረጃ የተገኘባቸውን አማሳኞች በአገሪቱ ሕግ ለመጠየቅ የባለሞያዎች ቡድን ተቋቁሟል *       *       * ፬ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ባለ18 ነጥቦች …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፤ የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎች ኅብረት ጋር በተደረጉ ተከታታይ የሁለትዮሽ ውይይቶችና ስምምነቶች፡ ህዝባችን ላለፉት 24 ዓመታት ያለነፃነት በህወሓት የግፍ አገዛዝ ሥር ፍዳውን የሚያይበት ዋና ምክንያት፤ ሕዝብን መሠረት ያደረገና ብሄራዊ ጥቅምን ያስቀደመ፤ በአንድ ማዕከል የሚንቀሳቀስ ሁሉን አቀፍ የአማራጭ አካል በማቋቋም ሥርዓቱን ለማስወገድ […]

የንቅናቄው መነሻ የጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔ እና የፓትርያርኩ አባታዊ መመሪያ ነው ከ25 በላይ አማሳኝ የአድባራት አለቆች እና ጸሐፊዎች ላይ በቂ ማስረጃዎች ተሰብስበዋል የተሐድሶ አራማጅ ሰባክያንን የሚጋብዙ አለቆችና የስብከተ ወንጌል ሓላፊዎች ተለይተዋል የደብረ ናዝሬት ቅ/ዮሴፍ፣ የመካነ ሰማዕት ቅ/ቂርቆስ እና ጃቲ ኪዳነ ምሕረት ተጠቅሰዋል የሀ/ስብከቱ ሥ/አስኪያጅ የሰንበት ት/ቤቶቹን አመራሮች ‹‹እኔ ራሴ አሳስራችኋለኹ›› አሏቸው ‹‹እንቅስቃሴው ይቀጥላል፤ የመላው የአ/አ ሰንበት …

የአሜሪካን መንግስትና የአውሮፓ ፓርላማ በኢትዮጵያ የተካሄደውን ምርጫን አጣጣሉ በነቀምቴ የወያኔ ታጣቂዎች በተማሪዎች ላይ ጉዳት አደረሱ ምርጫውን ተከትሎ አዲስ አበባ በክልል ፖሊስ፤ ፌዴራል ፖሊስ፤ና መከላከያ ሰራዊት ተከባለች፡ልዩ ሃይል በወልመራ በድብቅ ሰፍሯል የዓለም እግር ኳስ ማሕበራት ፌደሬሽን ባለሥልጣናት የታሠሩና የተከሰሱበት የሙስና ቅሌት የፖለቲካዊ ሽኩቻ መልክ  እየያዘ ነዉ። በሩሲያ ላይ የተጣለው የምዕራባዊያን ማዕቀብ የታሰበውን ያህል ተፅእኖ አልፈጠረም posted by Aseged TameneFiled […]

ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫውን ውጤትም ሆነ ሒደት እንደማይቀበል አስታወቀ

በዘንድሮ አምስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ለመጀመርያ ጊዜ ተካፋይ የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ፣ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. የተካሄደውን ምርጫ ውጤትም ሆነ ሒደት እንደማይቀበል አስታወቀ፡፡

የፓርቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቱ አቶ ስለሺ ፈይሳና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ግንቦት 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በፓርቲው ጽሕፈት ቤት ለአገር ውስጥና ለውጭ ጋዜጠኞች መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው፣ የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉት ያስታወቁት፡፡

‹‹ነፃነት በሌለባት ኢትዮጵያ ሕዝባዊ አስተዳደር መትከል ዘበት ነው›› በሚል ርዕስ በሰጠው መግለጫ ፓርቲው እንዳስታወቀው፣ የ2007ን ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ ሲወስን በዚህች አገር ገለልተኛና ብቃት ያላቸው ተቋማት እንደሌሉና ገዥው ቡድንም እውነተኛ ምርጫ እንደማይፈቅድ ግልጽ ማድረጉን፣ በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ የተካሄደው ምርጫ ውጤትም ተቀባይነት የለውም ሲል በመግለጫው አስታውቋል፡፡

‹‹በሕገወጥ የአፈና ሥርዓት የተካሄደው የ2007 ዓ.ም. ጠቅላላ ምርጫ የሚያመለክተው ኢትዮጵያ አሁንም ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ልታካሂድ ቀርቶ፣ በኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከተካሄዱት ምርጫዎች ጋር እንኳን ሊወዳደር የሚይችል እጅግ ኢ-ፍትሐዊ፣ ወገንተኛና ተዓማኒነት የሌለው በመሆኑ ሰማያዊ ፓርቲ ሒደቱንም ሆነ ውጤቱን አይቀበለውም፤›› በማለት ሰማያዊ ፓርቲ አስታውቋል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ከጋዜጠኞች የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን፣ አመራሮቹም ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ከተነሱ ጥያቄዎችም መካከል ቁጥራቸው ካልተገለጹ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበሮች የማሸነፍ ዕድል ይኖረናል የሚል ግምት አላችሁ ወይ የሚል የነበረ ሲሆን፣ የፓርቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ይልቃል፣ ‹‹ያልተገለጹ መቀመጫዎችን ለማሸነፍ ምንም ተስፋ የለንም፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ በመግለጫው፣ ‹‹ፓርቲያችን በዚህ አፈናና ጭቆና ውስጥ ከሕዝብ ለተሰጠው ክብር ያመሰግናል፡፡ በምርጫ ሒደቱ የተደበደባችሁና የተሰደዳችሁ የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች፣ ፓርቲያችን ዛሬ በኢትዮጵያ ሕዝብ ተዓማኒ፣ ተወዳጅና ተስፋ የተጣለበት እንዲሆን እናንተ ላይ የደረሰው መከራና በደል ትልቁን ድጋፍ ይወስዳልና ክብርና ምሥጋና ይገባችኋል፤›› ብሏል፡፡

‹‹የዜጎች ነፃነት ሳይከበር ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ሊደረግ ስለማይችል አሁንም ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብታችን እስከሚከበሩ ድረስ ሰማያዊ ፓርቲ በሚያካሂደው የነፃነት ትግል ኢትዮጵያዊያን ከጎኑ እንዲቆሙ ይጠይቃል፤›› በማለት የፓርቲው መግለጫው ያትታል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ በበርካታ የምርጫ ክልሎች ከኢሕአዴግ በመቀጠል የመራጮችን ድምፅ ማግኘቱን፣ ከተለጠፉት የውጤት ማሳወቂያ ዝርዝሮች ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

በ2007 ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ ለመሆን ወደ ፉክክር መድረኩ ገብቶ የነበረው የአዲስ ትውልድ ፓርቲ (አትፓ) የምርጫ በጀት የት እንደገባ አለመታወቁን የፓርቲው ዕጩዎች ተናገሩ፡፡ 

በኦሮሚያ ክልል በኢተያ ምርጫ ክልል የፓርቲው ዕጩ የነበሩትን አቶ ተሾመ ደረሰን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎችም የፓርቲው ተወካዮች የነበሩት ግለሰቦች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ አስፈላጊውን የምርጫ ፎርማሊቲ አሟልተው ወደ ምርጫ ፉክክሩ ከገቡ በኋላ በቅድመ ምርጫው ወቅት ምንም ዓይነት የምረጡኝ ቅስቀሳም ሆነ ማስታወቂያ ሳያከናውኑ የቀሩት፣ ፓርቲው የተመደበለት በጀት ሥራ ላይ ባለመዋሉ ምክንያት እንደነበር ተናግረዋል፡፡ 

የፓርቲው ሊቀመንበር የነበሩት አቶ አስፋው ጌታቸው ውጭ አገር ከሄዱ በኋላ፣ በተወካዩ ግለሰብ እጅ የነበረው ገንዘብ ለምርጫ ተግባራት መዋል ሲገባው የውኃ ሽታ ሆኖ መቅረቱን አባላቱ ጠቁመዋል፡፡ 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ባከፋፈለው በጀት መሠረት የአዲስ ትውልድ ፓርቲ (አትፓ) 487,999.03 ብር የደረሰው ሲሆን፣ ፓርቲው ግን በበርካታ ቦታዎች ዕጩ ተወዳዳሪዎችን በምርጫው ቀን ማቅረብ አለመቻሉ ታውቋል፡፡ 

በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ለሪፖርተር የሰጡት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕዝብ ግንኙነት ባልደረባ አቶ ደምሰው በንቲ፣ ቦርዱ ይህንን በተመለከተ ምንም ዓይነት ሪፖርት እስካሁን እንዳልቀረበለት ጠቁመው፣ ፓርቲው ግን አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ አሟልቶ ለምርጫው የተመዘገበ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የፓርቲው መሥራችና ሊቀመንበር እንደሆኑ የሚነገርላቸው አቶ አስፋው ጌታቸው በ1968 ዓ.ም. አዲስ አበባ ከተማ ተወልደው በግብርና ኢኮኖሚ ከሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ በቢኤ ዲግሪ የተመረቁ መሆናቸው በፌስቡክ አካውንታቸው ላይ የሠፈረውና ፓርቲውን አስመልክቶ የተቀመጠው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ቀደም ሲል የነበረውን የፖለቲካ ሁኔታና አሁን ያለውን ገዥ ሥርዓት በማጣጣም፣ አዲሱ ትውልድ የሚኖረውን ሚና ከግምት በማስገባት እንደተቋቋመ የሚነገርለት አዲስ ትውልድ ፓርቲ ከተመሠረተ ሦስት ዓመታት አስቆጥሯል፡፡

ለጊዜው በጉዳዩ ላይ ምንም ነገር ማለት እንደማይቻል ለሪፖርተር የገለጹት አቶ ደምሰው፣ ምርጫ ቦርድ የሚከታተለው ነገር ካለ ወደፊት የሚታወቅ እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡ ሪፖርተር በሊቀመንበሩ ተወክለዋል የተባሉትን ግለሰብ በተደጋጋሚ በስልክ ለማነጋገር ያደረገው ሙከራ ግለሰቡ የስልክ ጥሪ ባለመመለሳቸው ምክንያት አልተሳካም፡፡

አቶ አስፋው አሜሪካ ከሄዱ ሁለት ወራት እንዳለፏቸው የሚገልጹት የፓርቲው አባላት፣ የመመለሳቸው ጉዳይ አጠራጣሪ ነው ሲሉ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡  

 

የኮበለሉ መኮንንና አክራሪነትን ሰበኩ የተባሉ ሼክም ክስ ተመሥርቶባቸዋል

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ምክትል ፕሬዚዳንት መሆናቸው የተገለጸውና አድራሻቸው በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ማክሰኝት ከተማ መሆኑ የተጠቀሰው አቶ ዘመነ ምሕረቱ ታከለ፣ በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ግንቦት 18 ቀን 2007 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

 

ተከሳሹ በሰው ሕይወት፣ አካልና ንብረት ላይ ጉዳት ለማድረስ፣ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፈራረስ ዓላማ ካለውና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ከተፈረጀው ግንቦት ሰባት ድርጅት ጋር አብረው ለመሥራት መስማማታቸውን፣ ክስ የመሠረተባቸው የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በክሱ አስፍሯል፡፡

ምክትል ፕሬዚዳንቱ መስከረም 18 ቀን 2007 ዓ.ም. በጎንደር ከተማ በሚገኘው የመኢአድ ጽሕፈት ቤት ውስጥ አባላቱን በመሰብሰብ ‹‹የወያኔ መንግሥት መውደቂያው ደርሷል፡፡ አንድ የጦር አውሮፕላን፣ 12 የጦር ጄኔራሎች መንግሥትን ከድተው ወደ ኤርትራ ገብተዋል፡፡ ኢሕአዴግን በጦር ካልሆነ በሰላማዊ መንገድ ከሥልጣን አይለቅም፡፡ የሕዝብ እምቢተኝነትን በመፍጠር የወያኔን መንግሥት መጣል አለብን፡፡ በ2007 ዓ.ም. የሚካሄደው አገራዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ አይካሄድም፡፡ ወደ ምርጫው አንገባም፡፡ ሌላ አማራጭ መጠቀም አለብን…›› በማለት ሕጋዊ አማራጮችን ትተው የኃይል አማራጮች ለመጠቀም ሲቀሰቅሱ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ ጠቅሷል፡፡ 

ምክትል ፕሬዚዳንቱ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ቦምብ አወራወርና መሣሪያ መፍታት የሚችል በማነጋገርና በጥምቀት በዓል ላይ ተልዕኮ መፈጸም የሚችል ሰው ሲያፈላልጉ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ ጠቁሟል፡፡ በአጠቃላይ ምክትል ፕሬዚዳንቱ የሽብር ዓላማን ለማራመድ በማሰብና የሽብርተኝነትን ድርጊት ለመፈጸም ማቀድ፣ መዘጋጀት፣ ማሴርና ማነሳሳት ወንጀል መከሰሳቸውን የክስ ሰነዱ ያብራራል፡፡

ከመኢአድ ምክትል ፕሬዚዳንት ጋር በአንድ የክስ መዝገብ በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው፣ አድራሻቸው አዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ውስጥ መሆናቸው የተጠቆመው አቶ ጌትነት ደርሶ አዱኛ ናቸው፡፡ እሳቸውም የግንቦት ሰባት ድርጅት አባል በመሆን እንደ አቶ ዘመነ ምሕረቱ የሽብር ድርጊት ለመፈጸም መንቀሳቀሳቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ 

ተከሳሹ ከድርጅቱ ጋር አብሮ ለመሥራት በመፈለግ ወደ ኤርትራ በመሸጋገር የግንቦት ሰባት ከፍተኛ አመራር ከሆኑት ዶ/ር ክፈተው አሰፋ ጋር በመገናኘት፣ ስለድርጅቱ ዓላማ ፖለቲካዊ ሥልጠና መውሰዳቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ በወታደራዊ ሥልጠና የመሣሪያ ተኩስ፣ የዒላማ ተኩስ፣ መከላከልና ማጥቃት በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮችና በኤርትራ መንግሥት ወታደሮች መሠልጠናቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ይገልጻል፡፡ ተከሳሹ ለድርጅቱ አባላትን እንዲመለምሉና ወደ ኤርትራ ወታደራዊ ሥልጠና መስጫ ካምፕ እንዲልኩ የፌስቡክ አካውንት [email protected] የሚል አድራሻ እንደተሰጣቸውም ክሱ ያብራራል፡፡ በአጠቃላይ የሽብር ድርጅቱ አባል በመሆናቸው፣ በማንኛውም መልኩ በሽብርተኝነት ድርጅት ውስጥ መሳተፍ ወንጀል መከሰሳቸው የክስ ቻርጁ ያስረዳል፡፡ 

በተመሳሳይ የክስ መዝገብ ክስ የተመሠረተባቸው ሌላው  ተጠርጣሪ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ የካ ክፍለ ከተማ ውስጥ ነዋሪ መሆናቸው የተገለጸው አቶ መለሰ መንገሻ የተባሉ ግለሰብ ሲሆኑ፣ ራሱን የኢትዮጵያ አርበኞች ግንባር ብሎ በሚጠራው ቡድን ውስጥ አባል ሆነው የተገኙ መሆናቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ጠቁሟል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት በሰው ሕይወትና አካል ላይ ጉዳይ ለማድረስ መንቀሳቀሳቸውን፣ በትጥቅ ትግል ሥልጣን ለመያዝ ከሚንቀሳቀስ ቡድን ጋር ማበራቸውን፣ በኤርትራ አውሃጅራ አካባቢ ለሚንቀሳቀሰው የሽብር ቡድን ከፍተኛ አመራር ከሆኑት ግለሰብ ጋር በተለያዩ ጊዜያት በስልክ በመገናኘት አባላትን ይመለምሉ እንደነበር በክሱ ተካቷል፡፡ ተከሳሹ የኢትዮጵያ የመንግሥት ባለሥልጣናት በሚበዙበት አካባቢ እንዴት ጥቃት መፈጸም እንዳለበት ለሽብር ድርጅቱ አመራሮች ገለጻ በማድረጋቸው፣ በሽብር ተግባር ላይ በመሳተፍ ወንጀል መከሰሳቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ 

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ግንቦት 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ሌላው ክስ የመሠረተው የአየር ኃይል ባልደረባ በሆኑት ምክትል መቶ አለቃ አንተነህ ታደሰ ዘውዴ በተባሉት ተጠርጣሪ መኮንን ላይ ነው፡፡

ምክትል መቶ አለቃው ወደ ኤርትራ እንዲኮበልሉ ምክንያት የሆናቸው ቀደም ብሎ የአየር ኃይል ባልደረባ የነበረውና ባልታወቀ ምክንያት በጥቅምት ወር በ2007 ዓ.ም. ወደ ኤርትራ መሄዱ በተጠቀሰው ምክትል መቶ አለቃ ዳንኤል የሸዋስ ጋር በፌስቡክ በመገናኘት መሆኑን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ “Doni Yeshu Sweet” በሚል አድራሻና በተለያዩ ስልኮች ይገናኙ እንደነበርና ታኅሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም. ከደብረ ዘይት አየር ኃይል በመነሳት ወደ ኤርትራ ጉዞ እያደረጉ መንገድ ከሚያሳያቸው ሌላ ሰው ጋር ታኅሳስ 26 ቀን 2007 ዓ.ም. ወሮታ ከተማ ላይ መያዛቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ ወንጀልም መከሰሳቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በተለያዩ የክስ መዝገቦች ክስ ከመሠረተባቸው ውስጥ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ቶንጎ ወረዳ ሻንቦላ ከተማ ሻንቦላ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ውስጥ ነዋሪ መሆናቸው የተጠቀሰው ሼክ መሐመድ አብዱል ቃድር የሚባሉ ተጠርጣሪ ናቸው፡፡ 

ተከሳሹ በመንግሥት ላይ ተፅዕኖ ለማሳደርና ኅብረተሰቡን ለማስፈራራት የእስልምና ሃይማኖትን እንደ ሽፋን በመጠቀም፣ በኃይል እስላማዊ መንግሥት ለማቋቋም ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡

ሼክ ሐመድ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቶጎ ወረዳ ጎሬ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ውስጥ በሚገኙ መስጊዶች በመዘዋወርና ሙስሊሙን ማኅበረሰብ በማሰባሰብ፣ ‹‹እኛ የካዋርጃ እምነት ተከታይ መሆን አለብን፡፡ ለመንግሥት አትታዘዙ፡፡ ግብር አትክፈሉ፡፡ ጤና ጣቢያ ሄዳችሁ እንዳትወልዱ፡፡ ወላጆች ልጆቻችሁን ትምህርት ቤት አትላኩ፡፡ የእኛን አስተምህሮ የማይከተል ካፊር ነው፤›› ብለው በግልጽ በመናገር፣ ኅብረተሰቡ በመንግሥት ላይ እምነት እንዳይኖረው ማድረጋቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያብራራል፡፡

‹‹የሻንቦላና የአካባቢው ነዋሪዎች በአጠቃላይ መመራት ያለብን በሸሪዓ ሕግ ወይም እስላማዊ መንግሥት መሆን አለበት፤›› በማለት በመቀስቀስና የሽብርተኝነት ድርጊት ለመፈጸም በማቀድ በማሴር፣ በማዘጋጀትና በማነሳሳት ወንጀል ሼኩ መከሰሳቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ይገልጻል፡፡

 

ለአፍሪካ ልማት ባንክ የተወዳደሩት አቶ ሱፍያን አህመድ ሳይመረጡ ቀሩ

የአፍሪካን ልማት ባንክን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት ዕጩ ሆነው የቀረቡት የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሱፍያን አህመድ ሳይመረጡ ቀሩ፡፡

ናይጄሪያዊ የግብርናና የገጠር ልማት ሚኒስትር የ55 ዓመቱ ኦኪንውሚ ኦዴሲና የባንኩ ፕሬዚዳንት አድርጎ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ግንቦት 20 ቀን 2007 ዓ.ም. መርጧቸዋል፡፡

ባንኩን ላለፉት አሥር ዓመታት ሲያስተዳድሩት የቆዩትን ሩዋንዳዊውን ዶናልድ ካቤሩካን ለመተካት አቶ ሱፍያንን ጨምሮ ስምንት ዕጩዎች ቀርበው የነበረ ቢሆንም፣ በምርጫ ሥነ ሥርዓቱ አቶ ሱፍያን በሁለተኛ ዙር ከውድድር ውጪ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

አቶ ሱፍያን ቀደም ብሎ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ሆነው ባስመዘገቡት ስኬት የማሸነፍ ዕድላቸው ከፍተኛ እንደሚሆን ተጠብቆ ነበር፡፡ አቶ ሱፍያን ከ20 ዓመታት በላይ በመሩት ሚኒስቴር ካከናወኗቸው ዓበይት ተግባራት መካከል፣ በአገሪቱ ሲከሰት የነበረውን ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ወደ ነጠላ አኃዝ በማውረድ ረገድ የተጫወቱት ሚና ይነገርላቸዋል፡፡ በአገሪቱ አዲስና የቅርብ ክስተት ከሆኑት ውስጥ፣ አገሪቷ በዓለም ቦንድ ገበያ ውስጥ ተሳታፊ መሆኗም ከሚጠቀሱላቸው ተግባራት መካከል ይካተታል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ አቶ ሱፍያን የባንኩ ሁለተኛ የሥራ ቋንቋ የሆነውን ፈረንሳይኛ ቋንቋ መናገር የማይችሉ በመሆናቸው ከፍተኛ ፈተና ሊገጥማቸው እንደሚችል የገመቱም ነበሩ፡፡ በተለይ አንዳንድ የመስኩ ባለሙያዎች የፕሬዚዳንትነቱን ውድድር ለምዕራብ አፍሪካ አገሮች ተወካዮች የተሻለ ቅድመ ግምትን ሰጥተውም ነበር፡፡

በስምንተኛው የባንኩ ጉባዔ ላይ ይፋ በሆነው የምርጫ ሥነ ሥርዓት ላይ አሸናፊ በመሆን የተመረጡት ናይጄሪያዊው ኦዴሲና ‹‹ዛሬ ታላቅ ኃላፊነትን ተቀብያለሁ፤›› በማለት ደስታቸውን ከሚጠብቃቸው ኃላፊነት ጋር በማያያዝ ገልጸዋል፡፡

በቅድመ ምርጫ ወቅት ስምንቱ ዕጩዎች ለውድድሩ የየራሳቸውን ስኬትና አሸናፊ ከሆኑ ለባንኩ ይበጃል ያሉዋቸው ዕቅዶች አቅርበው ነበር፡፡ በተለይ አቶ ሱፍያን ኢትዮጵያ ላለፉት አሥር ዓመታት አስመዝግባዋለች ያሉትን የኢኮኖሚ ዕድገትና የገንዘብ ግሽበትን በመቆጣጠር ልማትን እንዴት ማፋጠን ያስችላል ያሉትን ዕቅድ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡

ተሰናባቹ ፕሬዚዳንት ካቤሩካ በበኩላቸው በጉባዔው ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ለተተኪያቸው የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክት በማስተላለፍ መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል፡፡ ‹‹ለተተኪዬ መልካሙን ሁሉ እመኝለታሁ፡፡ አሥር ዓመት በፍጥነት መሄዱን አይቻለሁ፡፡ እጅግ ውስብስብና ውጥረት የተሞላበት ሥራ ነበር፡፡ ቢሆንም ግን አስደሳች የሥራ ወቅት ነበር፡፡ በእርግጥ ይኼን ሥራ ብዬ ከምጠራው ተልዕኮ ብለው ይሻለኛል፤›› ሲሉ ባንኩን ለአሥር ዓመት ያስተዳደሩት ዶናልድ ካቤሩካ በባንኩ ስላሳለፉት የሥራ ዘመን ተናግረዋል፡፡

 

በፕሮቪደንት ፈንድ የታቀፉ የግል ድርጀት ሠራተኞች ወደ ግል ድርጅቶች ጡረታ እንዲዘዋወሩ የሚያስገድድ ማሻሻያ አዋጅ ተረቀቀ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመጪው ሳምንት ይወያይበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የግል ድርጅት ሠራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 715/2003 በሐምሌ ወር 2003 ዓ.ም. ተግባራዊ መሆን ከመጀመሩ በፊት፣ የፕሮቪደንት ፈንድ ሽፋን ያላቸው የግል ድርጅት ሠራተኞች በነበራቸው የፕሮቪደንት ፈንድ ተጠቃሚነት ለመቀጠል እንዲወስኑ፣ ወይም በግል ድርጅት ሠራተኞች ጡረታ ስለሚሸፈኑበት ሁኔታ ሊስማሙ እንደሚችሉ ይደነግጋል፡፡

ይሁን እንጂ በሠራተኞች የማኅበራዊ ዋስትና ሽፋን ላይ ልዩነት እንዳይኖር ለማድረግ ሲባል፣ ይኼንንና ሌሎች አንቀጾችን የሚያሻሽል ረቂቅ በግል ድርጅቶች ሠራተኞች የማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ተዘጋጅቶ ለፓርላማው ተልኳል፡፡

በፕሮቪደንት ፈንድ ይሸፈኑ የነበሩ ሠራተኞችን አንድ ወጥ ወደሆነው የግል ሠራተኞች የማኅበራዊ ዋስትና ማምጣት ያስፈለገው፣ ዜጎችን በአንድ የማኅበራዊ ዋስትና ሥርዓት ውስጥ ተጠቃሚ ማድረጉ በዜጎች መካከል የሚኖረውን የመብትና የጥቅም ልዩነት የሚያስወግድ በመሆኑ እንደሆነ የረቂቅ ማሻሻያ አዋጁ ማብራሪያ ያስረዳል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ሠራተኛው በነበረው የፕሮቪደንት ፈንድ ተጠቃሚነት እንዲቀጥል ማድረጉ የሠራተኛውን ተተኪዎች (ልጆችና ቤተሰቦች) የዘለቄታ የማኅበራዊ ዋስትና መብትና ጥቅም የሚያሳጣ በመሆኑ መሻሻሉ አስፈላጊ እንደሆነ ማብራሪያው ይጠቅሳል፡፡

በመሆኑም ከሰኔ 16 ቀን 2003 ዓ.ም. በፊት ተቀጥረው ይሠሩ በነበሩት የግል ድርጅቶች ውስጥ የጡረታ ወይም የፕሮቪደንት ፈንድ ሽፋን የነበራቸውና በዚሁ በነበራቸው የጡረታ ወይም የፕሮቪደንት ፈንድ ተጠቃሚነታቸውን የቀጠሉ ሠራተኞች በግል ድርጅቶች ሠራተኞች ጡረታ ሥርዓት እንዲሸፈኑ ማሻሻያ ረቂቁ መቅረቡን ያስረዳል፡፡ ከላይ የተጠቀሰው ማሻሻያ የሃይማኖት ድርጅቶች ሠራተኞች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች ሠራተኞችና መደበኛ ባልሆነ የሥራ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በፈቃደኝነት ላይ ተመሥርተው የግል ድርጅት የማኅበራዊ ዋስትና ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ይገልጻል፡፡

በፕሮቪደንት ፈንድ ወይም ቀድሞ በነበራቸው ጡረታ ለመቀጠል ተስማምተው ሲቆጥቡ የነበሩ ሠራተኞች ፈንድ፣ ወደ ግል ድርጅቶች ሠራተኞች ጡረታ ፈንድ እንደሚዘዋወር ረቂቅ ማሻሻያው ያስረዳል፡፡ ይህ ቢሆንም በፕሮቪደንት ፈንድ የቆጠቡት ወደ ግል ድርጅቶች ጡረታ ፈንድ በሚዘዋወርበት ጊዜ፣ በፕሮቪደንት ፈንዱ የተቀመጠው ከሚገባው መጠን በላይ የተከፈለ ከሆነ ልዩነቱ ለሠራተኞች ተመላሽ እንደሚደረግ ማሻሻያ ረቂቁ ይገልጻል፡፡

በዚህ ረቂቅ አዋጅ ላይ ፓርላማው በቀጣዩ ሳምንት ተወያይቶ ረቂቁን ለተጨማሪ ዕይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ይመራዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

 

ምርጫ ቦርድ ማጣራት አደርጋለሁ ብሏል

የተሻሻለው የምርጫ ሕግ በአንድ የምርጫ ጣቢያ መመዝገብና መምረጥ ያለበት መራጭ ከአንድ ሺሕ በላይ መሆን የለበትም ቢልም፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በርከት ያሉ የምርጫ ጣቢያዎች ከአንድ ሺሕ በላይ ነዋሪዎችን በማስመረጥ ሕጉን

መጣረሳቸው ታይቷል፡፡ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ፣ ‹‹እኛ የምናውቀው በሁሉም ምርጫ ጣቢያ አንድ ሺሕና ከዚያ በታች መራጭ መመዝገቡንና መምረጡን ነው፡፡ የተባለውን ስህተት አጣራለሁ፤›› ብሏል፡፡

ይኼንኑ ችግር የአፍሪካ ኅብረት ታዛቢ ቡድን ግንቦት 18 ቀን 2007 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ጊዜያዊ ሪፖርቱ ጠቁሞታል፡፡ የሪፖርተር ዝግጅት ክፍል ያሰማራቸው ጋዜጠኞችም በአንድ የምርጫ ጣቢያ ከአንድ ሺሕ በላይ መራጮች መሳተፋቸውን በማስረጃ ማረጋገጥ ችለዋል፡፡

የሪፖርተር ጋዜጠኞች ከጎበኟቸው የምርጫ ጣቢያዎች መካከል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ የተወዳደሩበት በኦሮሚያ አርሲ ዞን ምርጫ ጣቢያ ኢተያ 01-2ሀ-1 ማሳያ ነው፡፡

አቶ አባዱላ ከላይ በተገለጸው የምርጫ ጣቢያ 1,214 ድምፅ በማግኘት አንደኛ ደረጃ ሲይዙ፣ የኦብኮ ተፎካካሪያቸው ደግሞ 10 ድምፅ አግኝተዋል፡፡ በመሆኑም በዚህ ምርጫ ጣቢያ ብቻ 224 መራጮች ከሕጉ በተቃራኒ ተሳትፈዋል፡፡

በፓርላማው የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በተወዳደሩበት በስልጤ ዞን ዱና ምርጫ ጣቢያ በብቸኝነት ተወዳድረው 1,459 ድምፅ አግኝተዋል፡፡ በመሆኑም በዚህ ምርጫ ጣቢያ ከሕጉ በተቃራኒ 459 መራጮች ተስተናግደዋል ማለት ነው፡፡ ወ/ሮ ሙፈሪያት በተወዳደሩበት ሌላ ምርጫ ጣቢያ በቅበት ምርጫ ክልል ሸ/ገሬም ቁጥር 0-1 ምርጫ ጣቢያ ብቻቸውን ተወዳድረው 1,370 ድምፅ አግኝተዋል፡፡ ይኼ ማለት በምርጫ ጣቢያ ከሕጉ በተጣረሰ መልኩ 370 መራጮች ተሳትፈዋል፡፡

 በተጨማሪም በወላይታ ሁለገብ ምርጫ ክልል በቦዲቱ ቆርኬ ምርጫ ጣቢያ ከመድረክ ዕጩ ጋር የተወዳዳሩት የኢሕአዴግ ተወካይ አቶ አማኑኤል አብረሃም 1,182 ድምፅ ሲያገኙ፣ የመድረክ ተፎካካሪያቸው አንደ ድምፅ አግኝተዋል፡፡ በመሆኑም በዚህ የምርጫ ጣቢያ 183 መራጮች ያላግባብ ተስተናግደዋል፡፡

ሌላው በደቡብ ክልል ሃዲያ ዞን ስቄ 02 ምርጫ ክልል የኢሕአዴጉ አቶ ዮሴፍ ዳኤሞ 1,051 ድምፅ ያሸነፉ ሲሆን የመድረክ፣ የሰማያዊና የቅንጅት ተፎካካሪዎቻቸው ደግሞ አንደ ቅደም ተከተላቸው 171፣ 19፣13 ድምፆች አግኝተዋል፡፡ በመሆኑም በዚህ የምርጫ ጣቢያ 254 መራጮች ያላግባብ ተሳትፈዋል፡፡

በደሴ ከተማ ሮቢት ክፍለ ከተማ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ አብተው በሚወዳደሩበት ምርጫ ጣቢያ 22 ላይም 1,049 መራጮች ተመዝግበው የነበረ መሆኑን ሪፖርተሮቻችን አረጋግጠዋል፡፡

ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቱን ቦርዱ ይፋ ባደረገበት ወቅት ስለጉዳዩ የተጠየቁት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር፣ ‹‹አንድ ምርጫ ጣቢያ የሚያስተናግደው አንድ ሺሕ መራጮችን ብቻ ነው፡፡ እኛ የምናውቀው በአንድ ምርጫ ጣቢያ ከአንድ ሺሕ በላይ መራጭ አለመመዝገቡን ነው፤›› ብለዋል፡፡

የምርጫ ሕጉ በአንድ ምርጫ ጣቢያ ከአንድ ሺሕ በላይ መራጭ መመዝገብ የለበትም እንደሚል የገለጹት ዶ/ር አዲሱ፣ በአገር አቀፍ ደረጃ 45,795 ምርጫ ጣቢያዎች እንዲቋቋሙ የተደረገውም በዚሁ ሥሌት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

‹‹ከአንድ ሺሕ በላይ ያስተናገዱ ምርጫ ጣቢያዎችን ማጣራትና መመርመር ይኖርብናል፡፡ በመሆኑም ይኼንን ጥያቄ በተመለከተ ይኼ ነው ብለን የምንሰጠው መልስ የለም፤›› ብለዋል፡፡ 

የተሻሻለው የኢትዮጵያ ምርጫ ሕግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 ዓ.ም. በአንቀጽ 22(6) ላይ ‹‹እያንዳንዱ ምርጫ ጣቢያ የሚያስተናግደው የመራጮች ብዛት ከ1,000 መብለጥ የለበትም፤›› በማለት ይደነግጋል፡፡

 

ኢሕአዴግና አጋሮቹ በጊዜያዊ ውጤት ሙሉ በሙሉ ማሸነፋቸው በመድበለ ፓርቲ ሥርዓቱ ላይ ጥያቄ አስነሳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ካደረገው የ442 የፓርላማ መቀመጫ ውጤት ውስጥ ኢሕአዴግና አጋር ድርጅቶቹ ሙሉ ለሙሉ አሸነፉ፡፡ በቦርዱ ጊዜያዊ የውጤት መግለጫ መሠረት፣ በምርጫው የተወዳደሩ ተቃዋሚ

ፓርቲዎች አንድም የፓርላማ ወንበር አላገኙም፡፡ ይህም ውጤት በመድበለ ፓርቲ ሥርዓቱ ላይ ጥያቄ አስነስቷል፡፡

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይህንን ጊዜያዊ ውጤት ግንቦት 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ይፋ ካደረገ በኋላ፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎችና አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች የመድብለ ፓርቲ ሥርዓቱ ላይ ጥያቄ ማንሳት ጀምረዋል፡፡ የአገሪቱ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓትም ወደ ውድቀቱ እየተሽቆለቆለ ነው ብለዋል፡፡ የ2007 ጊዜያዊ የምርጫ ውጤትም ለዚህ ዓይነተኛ ማሳያ መሆኑን እየጠቀሱ ይገኛሉ፡፡

የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን ግን በዚህ አይስማሙም፡፡ ‹‹በአገሪቱ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እንዲኖር ዋናው ነገር አሠሪ ሕግ መኖሩ ነው፡፡ ይህ ካለ በማንኛውም ጊዜ ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ ሊመጣ ይችላል፤›› ብለዋል፡፡

በማንቸስተር ዩኒቨርሲቲ የልማት ፖሊሲና አስተዳደር የዶክትሬት ተመራማሪ የሆኑት አቶ ኢዮብ ባልቻ ግን፣ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ማለት በርካታ ፓርቲዎች መኖራቸው ብቻ አለመሆኑን ይገልጻሉ፡፡ በመሆኑም በአገሪቷ ውስጥ ያሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃዋሚና ጠንካራ ሆነው ሊንቀሳቀሱ የሚችሉበት ሥርዓት ሊኖር ይገባል ብለዋል፡፡ ከፖለቲካ ፓርቲዎቹ መብዛት ይልቅም ፓርቲዎቹ የሚንቀሳቀሱበት ተቀባይነት ያለው ሥርዓት መኖሩ ነው ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ማበብ ወሳኝ የሆነው ነገር ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ‹‹በኢትዮጵያ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ርዕዮተ ዓለምን የሚከተለው የኢሕአዴግ ፓርቲ የራሱን ኃይል ሲያደራጅ ቆይታል፡፡ ይህ ገዢ ፓርቲም የአገሪቱን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ለውጥ ከመቆጣጠሩም ባለፈ በልማታዊ ትርክት እየተደገፈ ይገኛል፤›› ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል ኢሕአዴግ ለዚህ ዓይነት ድል የበቃው ተቃዋሚዎች ለሕዝቡ አማራጭ ሐሳብ ማቅረብ ባለመቻላቸው መሆኑን አቶ ሬድዋን ይገልጻሉ፡፡ ‹‹ሕዝቡ ምንም እንኳን ቅሬታ ቢኖረውም፣ ከተቃዋሚዎች የቀረበለት አማራጭ ስለሌለ ከእኛ ጋር መቀጠሉን ያመላከተ ውጤት ነው፤›› ብለዋል፡፡ ተመራማሪው አቶ ኢዮብ ግን ኢሕአዴግ በየደረጃው የፈጠረው የሕዝብ አደረጃጀት ሕዝቡን ለመቆጣጠር፣ ለማታለል፣ ለመቅጣትና ለመሸለም ዓይነተኛ መንገድ ስለሆነለት ይህንን ዓይነት ውጤት በቀላሉ ሊያገኝ ችሏል ብለዋል፡፡ በፓርቲና በመንግሥት መካከል ያለው መዋቅር ልዩነት የለውም የሚሉት አቶ ኢዮብ፣ የገዢው ፓርቲ ፍላጐት ከሌሎች ማናቸውንም ዓይነት ፍላጐቶች ቀድመው ይታያሉ ብለዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የአንድ ለአምስት አደረጃጀት፣ የልማት ሠራዊት አደረጃጀት፣ የወጣት ሊግ፣ የሴቶች ሊግና ሌሎችም አደረጃጀቶች ኢሕአዴግ ምርጫውን እንዲያሸንፍ አስችለውታል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ አቶ ሬድዋን ግን ኢሕአዴግ በአርሶ አደሩ፣ በዝቅተኛውና በመካከለኛው ኅብረተሰብ ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራቱ ማሸነፉን ገልጸዋል፡፡

የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መርጋ በቃና በበኩላቸው፣ ‹‹ምርጫው ከፍተኛ ፉክክር የታየበት ነው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያደረጉት የምርጫ ቅስቀሳና ያቀረቡት የዕጩዎች ብዛት የዚህ ማሳያ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ አሳታፊ የሆነ የውድድር ሜዳ አዘጋጅቷል፡፡ ከዚህ ውጪ ሕዝቡ ይጠቅመኛል ብሎ ድምፁን የሰጠውን ውጤት ተቀብሎ ማወጅ ነው የምርጫ ቦርድ ሥራ፤›› ብለዋል፡፡ የቦርዱ ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር ደግሞ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ አማራጭ ሐሳቦቻቸውን ለሕዝብ ለመግለጽ ያደረጉት ፉክክር፣ ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓቱ መኖር አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ፓርቲዎቹ ተወዳድረው ያገኙት ውጤት ሌላው ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በምሳሌነት ባቀረቡት የምሥራቅ ሸዋ የምርጫ ውጤት መድረክ 12,834 ድምፅ ሲያገኝ፣ ኦሕዴድ/ኢሕአዴግ 40,357 ድምፅ አግኝቷል ብለዋል፡፡ ሆኖም ግን አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ይህን የዶክተሩን ሐሳብ አይቀበሉትም፡፡ ምክንያቱም ገዢው ፓርቲና ተቃዋሚዎች በበርካታ የምርጫ ጣቢያዎች ያገኙት የድምፅ ልዩነት እጅግ ሰፊ ነው በማለት ነው፡፡ ለምሳሌ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተወዳደሩበት የምርጫ ጣቢያ ተቃዋሚዎች ምንም ድምፅ አለማግኘታቸው ሌላው ማሳያ ነው ይላሉ፡፡

አቶ ሬድዋን በ2007 ምርጫ ድምፃቸውን ለኢሕአዴግ ያልሰጡትን ዜጐች አሁን ያለውን የመልካም አስተዳደር ችግርና የመንግሥት አገልግሎትን አሳታፊነትን በማስተካከል በቀጣይ የእነዚህን ዜጐች ድምፅ እንደሚያገኙ እምነት አላቸው፡፡ ተመራማሪው አቶ ኢዮብ ግን ኢሕአዴግ ይህን የማድረግ ብቃቱም ሆነ ፍላጐቱ ስለሌለው፣ ተቃዋሚዎች ጠንክረው በመሥራትና የተሻለ ስትራቴጂ በመከተል የመረጧቸው ዜጐችን የሚያገለግሉበትን መንገድ ሊፈልጉ ይገባል ብለዋል፡፡  

ቦርዱ ባወጣው ጊዜያዊ ውጤት መሠረት በትግራይ ክልል ሕወሓት/ኢሕአዴግ ካሉት 38 መቀመጫዎች 31 ሲያገኝ፣ በአማራ ክልል ካሉት 138 መቀመጫዎች ብአዴን/ኢሕአዴግ 107ቱን ማሸነፍ ችሏል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ኦሕዴድ/ኢሕአዴግ ከ178 የፓርላማ መቀመጫዎች 150 ሲያገኝ፣ በደቡብ ክልል ደኢሕዴን/ኢሕአዴግ ከ123 መቀመጫዎች 95ቱን ማግኘት ችሏል፡፡

በአፋር ክልል አብዴፓ ከስምንት መቀመጫዎች ስድስት አግኝቷል፡፡ በቤንሻንጉል ጉምዝ ቤጉሕዴፓ ከዘጠኝ መቀመጫዎች ሰባት አግኝቷል፡፡ በጋምቤላ ክልል ጋሕዴን ከሦስት መቀመጫዎች ሦስቱንም አግኝቷል፡፡ በሐረሪ ከሁለት መቀመጫዎች ሐብሊና ኦሕዴድ/ኢሕአዴግ አንድ አንድ ማግኘታቸውን የቦርዱ ጊዜያዊ መግለጫ አስታውቋል፡፡

በተመሳሳይ በሶማሌ ክልል ሶሕዴፓ ከ23 መቀመጫዎች 16 አግኝቷል፡፡ በአዲስ አበባ ካሉት 23 መቀመጫዎች ኢሕአዴግ 23ቱን ማሸነፉ ተገልጿል፡፡         

 

ጦማሪ አቤል ዋበላ ችሎት በመድፈር ጥፋተኛ ተባለ

በተጠረጠሩበት የሽብርተኝነት ወንጀል ከአንድ ዓመት በላይ በእስር በቆዩት ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ላይ ተጨማሪ ምስክሮችን ለማሰማት፣ ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ ግንቦት 18 ቀን 2007 ዓ.ም. ለፍርድ ቤት ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ተደረገ፡፡

ክሱን እየሰማ የሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የዓቃቤ ሕግን የተጨማሪ ጊዜ ጥያቄ ውድቅ ያደረገው፣ የተከሳሾቹ ጠበቆች ያቀረቡትን መቃወሚያና ራሱ ፍርድ ቤቱ ቀደም ባለው ችሎት የሰጠውን ትዕዛዝ መሠረት አድርጎ ነው፡፡ 

ከሳሽ ዓቃቤ ሕግ ቀደም ባሉት ችሎቶች 18 የሰው ምስክሮችን አሰምቶ ቀሪ ምስክሮችን ሊያገኛቸው እንዳልቻለ በመግለጽ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠውና ቀሪ ምስክሮችን ለማቅረብ ሲጠይቅ፣ ፍርድ ቤቱ “ለመጨረሻ ጊዜ” በማለት ተጨማሪ ምስክሮችን እንዲያቀርብ ማዘዙን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ዓቃቤ ሕግ ግንቦት 18 ቀን 2007 ዓ.ም. በነበረው ቀጠሮ ቀርቦ ምስክሮቹን ሊያገኛቸው እንዳልቻለ በመግለጽ፣ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቆ ነበር፡፡ 

የተከሳሾች ጠበቆች ቀደም ብሎ በነበረው ችሎት ዓቃቤ ሕግ ጥያቄውን ማንሳቱንና ፍርድ ቤቱም “የመጨረሻ” ብሎ ትዕዛዝ ሰጥቶት እንደነበር አስታውሰው፣ ድጋሚ ጥያቄው ውድቅ እንዲደረግ ጠየቁ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ጠበቆቹ ቀደም ባለው ችሎት ዓቃቤ ሕግ በኤግዚቢትነት እንዳስያዛቸው ለፍርድ ቤቱ ያሳወቀውን ሲዲዎች ኮፒ እንዲሰጣቸው አመለከቱ፡፡

ዓቃቤ ሕግ በበኩሉ ተከሳሾችም ሆኑ ጠበቆቻቸው የማያውቁት አዲስ ቪሲዲ እንዳለው ለፍርድ ቤቱ ሲያመለክት፣ የተከሳሾች ጠበቆችም እንዲሰጣቸው ጠየቁ፡፡

ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹ ጠበቆች ያቀረቡትን ተቃውሞና አዲስ የቀረበውን ቪሲዲ ይሰጠን ጥያቄ ላይ እንዲሁም ዓቃቤ ሕግ ባቀረበው ቪሲዲ ላይ ብይን ለመስጠት በይደር ቀጠሮ ሰጥቶ ችሎቱ ተጠናቀቀ፡፡ 

ፍርድ ቤቱ በማግሥቱ ግንቦት 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ተሰይሞ ዓቃቤ ሕግ ምስክሮቹን እንዲያሰማ የተሰጠው ጊዜ ለመጨረሻ መሆኑን በመንገር፣ ተጨማሪ የጊዜ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉንና ምስክሮቹን እንደማይሰማ አስታወቀ፡፡

በኤግዚቢት የተያዙ ሲዲዎች ተገልብጠው (ኮፒ) ተደርገው እንዲሰጣቸው የተከሳሾች ጠበቆች ያቀረቡትን ጥያቄ በሚመለከት ፍርድ ቤቱ በሰጠው ምላሽ፣ ሲዲዎቹ የተዘጋጁት ከተከሳሾቹ ላፕቶፖች ላይ ተገልብጠው በመሆኑና ዓቃቤ ሕግ በሰነድ አዘጋጅቶ ያቀረባቸው ወይም ለተከሳሾችም የተሰጡ ዶክመንቶች ተመሳሳይ ስለሆኑ በድጋሚ መስጠቱ አስፈላጊ አለመሆኑን አስረድቷል፡፡

ዓቃቤ ሕግ አዲስ ያቀረበውን ቪሲዲ በሚመለከት “ማስረጃ ይሆናል ወይስ አይሆንም?” የሚለውን ፍርድ ቤቱ በቅድሚያ አይቶ ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ብይን እንደሚሰጥበት ገልጿል፡፡  

ፍርድ ቤቱ በይደር ያቆየውን የዕለቱን ሥራ በማጠናቀቅ ላይ እያለ ከጦማሪያኑ መካከል፣ ጦማሪ አቤል ዋበላ እጁን በማውጣት ጥያቄ እንዳለው በማመልከት “ቪሲዲው ሶሊያና ሽመልስን ብቻ የሚመለከት ነው ወይስ እኛንም ይጨምራል?” የሚል ጥያቄ ሲያቀርብ ፍርድ ቤቱ ‹‹አልተፈቀደልህም ተቀመጥ›› አለው፡፡ አቤል ጥያቄውን በመቀጠሉ ፍርድ ቤቱ ‹‹ሥነ ሥርዓት ተቀመጥ›› ሲለው ‹‹ራሳችሁ ሥነ ሥርዓት›› የሚል ምላሽ ሰጠ፡፡ 

የተከሳሾቹ ጠበቃ ወደ አቤል በመጠጋት ካረጋጉትና እንዲቀመጥ ካደረጉት በኋላ ለችሎቱ አመለከቱ፡፡ ተከሳሹ መጠየቅ የፈለገው ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ቪሲዲ የሚመለከተው ሶሊያናን ብቻ ወይም እነሱንም ያጠቃልል እንደሆነ ለማወቅ እንደሆነና ለችሎቱም ምላሽ የሰጠው በስሜታዊነት ስለሆነ ፍርድ ቤቱ ይቅርታ እንዲያደርግለት ጠየቁ፡፡

ፍርድ ቤቱ የጠበቃውን ማመልከቻ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ‹‹ራሱ ሊናገር ያሰበውን ገልጾ ይቅርታ ይጠይቅ››  በማለት አዘዘ፡፡ 

ጦማሪ አቤል ዋበላ ምንም ያጠፋው ነገር እንደሌለና ይቅርታ የሚያስጠይቀው ነገር አለመኖሩን ሲናገር፣ ፍርድ ቤቱ በችሎት መድፈር ጥፋተኛ ብሎታል፡፡ 

በዚህ ጊዜ ሁሉም ተከሳሾቹ (9ኙም) ከተቀመጡበት ተነስተው አቤል የተናገረው የሁሉም እንደሆነ በመግለጽ እሱ ብቻ ተነጥሎ ጥፋተኛ መባል እንደሌለበት በመግለጽ፣ አንድነታቸውን ለማሳየት ቢሞክሩም ፍርድ ቤቱ በውሳኔው ፀንቷል፡፡ ጠበቃውም ችሎቱ በተግሳጽ እንዲያልፈው የቅጣት ማቅለያ አቅርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ፍርድ ለመስጠት ለግንቦት 25 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

 

መድረክ የምርጫው ውጤት በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ጠየቀ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. የተከናወነው አምስተኛው ጠቅላላ ምርጫ መሠረታዊ የሆኑ ሕገ መንግሥታዊና ሌሎች የምርጫ ሕጎችን በጣሰ ሁኔታ የተከናወነ በመሆኑ፣ ይኼንን የሕግ ጥሰት የሚያጣራ ገለልተኛ የሆነ አጣሪ አካል እንዲቋቋም ጠየቀ፡፡ 

ፓርቲው ይህን ጥያቄ ያቀረበው ግንቦት 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ስድስት ኪሎ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽሕፈት ቤቱ ለአገር ውስጥና ለውጭ ጋዜጠኞች በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነው፡፡ 

በዕለቱ መግለጫውን የሰጡት የወቅቱ የመድረክ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣ የፓርቲው የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ዶ/ር መረራ ጉዲናና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ናቸው፡፡ 

‹‹ምርጫው የአገሪቱን ሕገ መንግሥትና ያሉትንም ሕግጋት ሁሉ የጣሰ ነው፡፡ ስለሆነም ወገንተኛ ያልሆኑ ዜጎች ያሉበት ገለልተኛ አካል ተቋቁሞ፣ በምርጫው ሒደት የተከሰቱት የሕግ ጥሰቶች እንዲያጣራ መድረክ አበክሮ ይጠይቃል፤›› በማለት ፕሬዚዳንቱ ጠይቀዋል፡፡ 

ፕሮፌሰር በየነ ከምርጫው ዕለት ቀደም ብሎ በከፍተኛ ሁኔታ መሠረታዊ የሕገ መንግሥት፣ የምርጫ ሕግጋትና ሌሎች የሥነ ምግባር ጥሰቶች ተፈጽመዋል ብለዋል፡፡ 

ለአብነትም ያህል ሲጠቅሱ፣ ‹‹ለመድረክ 303 የፓርላማ ተወዳዳሪዎችን አዘጋጅተን ያቀረብን ቢሆንም፣ ምርጫ ቦርድ ግን ዕውቅና የሰጠልን ለ270 ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱንም የሚያስረዳን አካል አልነበረም፤›› በማለት መድረክ መጉላላት የጀመረው ከምርጫው ዕለት ቀደም ብሎ እንደነበር አውስተዋል፡፡ 

ሌላው ፕሬዚዳንቱና ሌሎች የመድረክ አመራሮች ያነሱት ነጥብ ደግሞ፣ ከምርጫው ቀደም ብለው የተከናወኑት የሕዝብ ታዛቢዎች ምርጫና የምርጫ ቅስቀሳ በችግር ውስጥ መከናወናቸውን ነው፡፡ 

‹‹የምርጫው ዕለት ሲቃረብ ደግሞ ዕጩ ተወዳዳሪዎቻችን ተደብድበዋል፣ ታስረዋል፤›› ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ የዘንድሮ ምርጫ የምርጫ ሕጎችን፣ የሥነ ምግባር ደንቦችንና ሕገ መንግሥቱንም ጭምር የጣሰ የምርጫ ሒደትና አፈጻጸም ያሳየ መሆኑን መድረክ ገምግሟል ብለዋል፡፡ ‹‹ስለዚህ ምርጫው ነፃ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ አይደለም የሚል ድምዳሜ ላይ ፓርቲው ደርሷል፤›› በማለት አክለው አብራርተዋል፡፡ 

ከዚህ በተጨማሪም የፓርቲው አመራሮች የታሰሩ አባሎቻቸውንና ደጋፊዎቻቸውን መንግሥት እንዳፈታ ጠይቀዋል፡፡ 

 

የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን በዕቅድ ዘመኑ ለማጠናቀቅ ታስቧል

ሙሉ ትኩረቱን በአምስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ አድርጎ የቆየው ኢሕአዴግ መራሹ መንግሥት፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተገለጸው ጊዜያዊ ውጤት መንግሥት መመሥረት መቻሉን ካረጋገጠ በኋላ፣ በጅምር የሚገኘውን ሁለተኛውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዝግጅት ላይ ትኩረት አደረገ፡፡

በብሔራዊ ፕላን ኮሚሽን ባለቤትነትና በ13 ዓብይ ኮሚቴዎች አማካይነት የመጀመርያው ረቂቅ ፕላን ቢዘጋጅም፣ ዝግጅቱ በምርጫውና በሌሎች የተለያዩ ምክንያቶች በተያዘለት የጊዜ ገደብ መካሄድ አልቻለም ተብሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ምርጫው ከሞላ ጎደል በመጠናቀቁ የመጀመርያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ከአንድ ወር በኋላ ተጠናቆ ሁለተኛው ዕቅድ መተግበር መጀመር ስለሚኖርበት፣ መንግሥት ሙሉ ትኩረቱን በዕቅድ ዝግጅቱ ላይ ማድረጉ ታውቋል፡፡

የብሔራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ፈቃዱ ለማ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ቀን ባይቆረጥለትም ሁለተኛው የአምስት ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ረቂቅ ዕቅድ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ይፀድቃል፡፡

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዕቅዱን ካፀደቀ በኋላ ኅብረተሰቡ እንዲወያይበት የሚደረግ መሆኑን፣ ከኅብረተሰቡ የሚቀርበው አስተያየት ታክሎበት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ አቶ ፈቃዱ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ምንጮች እንደገለጹት፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በአገሪቱ እየተካሄደ ያሉ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን በአጠቃላይ ለማጠናቀቅ ታቅዷል፡፡ በተለይ በመንገድ መሠረተ ልማት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ በቴሌኮም ማስፋፊያና በባቡር መስመር ግንባታ ከፍተኛ በጀት እንደሚመደብ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል፣ በቅርቡ የመሠረተ ልማት ተቋማት ኃላፊዎችን ሰብስበው በአምስት ዓመት ውስጥ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን ማገባደድ እንደሚያስፈልግ መናገራቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ከመሠረተ ልማት ግንባታዎች በተጨማሪ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በተመረጡ ከተሞች የኢንዱስትሪ ዞኖችን ለመገንባት ታቅዷል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር አርከበ እቁባይ የሚመራው የኢንዱስትሪ ዞን ልማት ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ፣ በሐዋሳ፣ በባህር ዳር፣ በመቐለ፣ በኮምቦልቻና በድሬዳዋ ከተሞች በአሥር ቢሊዮን ዶላር ወጪ የኢንዱስትሪ ዞኖችን በሰፊው የማልማት ዕቅድ እንዳለው ተገልጿል፡፡ ይህ ዕቅድ ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም. መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ እንድትሠለፍ የማድረግ አቅም እንዳለው በመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ታምኖበታል፡፡

ነገር ግን ምንጮች እንደለገጹት፣ እስካሁን በሁለተኛው የአምስት ዓመት ዕቅድ የሚካተቱና የማይካተቱ ዝርዝር ፕሮጀክቶች አልታወቁም፡፡ ለምሳሌ ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. በሚጠናቀቀው የአምስት ዓመት ዕቅድ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት የነበረው በመላ አገሪቱ የሚገኙ ቀበሌዎችን የሚያገናኝ መንገድ ግንባታ፣ በሁለተኛው ዕቅድ መካተቱ ወይም አለመካተቱ አልታወቀም፡፡

ሁሉን አቀፍ የገጠር መንገድ ግንባታ ፕሮግራም ሲካሄድ የቆየው በማዕከላዊ መንግሥት በሚመደብ የምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች ልዩ በጀት ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት የምዕተ ዓመቱ የልማት ግብ ፕሮግራም በመጠናቀቁ በ2008 ዓ.ም. የሚመደብ በጀት የለም፡፡  

 

ታሪካዊው የቅዱስ እንጦንስ ጽሌ በአርተፊሻል ተቀይረዋል ከተባሉት አንዱ ነው የስእለት እና የስጦታ ወርቆች እና የብር ጌጣጌጦች በየመሸታ ቤቱ እየተሸጡ ነው የውጭ ኦዲት እንዲካሔድ በፓትርያርኩ የተሰጠው መመሪያ ተግባራዊ አልተደረገም በየመሸታው አስነዋሪ ሥራ የሚያዘወትሩ ካህናት ለምእመናን መራቅ ምክንያት ኾነዋል የፓትርያርኩ ልዩ ጸሐፊ ንቡረ እድ ኤልያስ ለችግሩ መባባስ ተጠያቂ ተደርገዋል (ኢትዮ-ምኅዳር፤ ቅጽ 03 ቁጥር 107፤ ቅዳሜ ግንቦት 22 …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

* ጥቃቱ በአኑድ መስጊድ ለአርቡ እኩለ ቀን ጸሎት የተሰበሰቡትን ለማጥቃት የታለመ ነበር ተብሏል * ፍንዳታው ከመስጊዱ መኪና ማቆሚያ በመፈንዳቱ አደጋው ሊቀንስ ችሏል * በጥቃቱ አራት ሰዎች ሲሞቱ በርካታዎች ቆስለዋል ፣ ንብረት ወድሟል * አጥፍቶ አጥፊው የሴት አበያ ለብሶ ተደብቆ ማለፉ ተጠቁሟል ባሳለፍነው ሳምን ከደማም የቅርብ ርቀት በምትገኘው በቃጢፍ ውስጥ ባንድ መስጊድ ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት የ […]

‹‹በኃይል በተቀማ ድምፅ የሚመሰረት መንግስት በህዝብ ተቀባይነት የለውም›› • ‹‹በሂደቱ በመቆየታችን የኢህአዴግን አውሬነት አሳይተናል›› ኢ/ር ይልቃል • ‹‹የአፍሪካ ህብረት ራሱንም ሌላም ማዳን የማይችል የእንጨት ድስት ነው›› አቶ ስለሽ ሰማያዊ ፓርቲ የ2007 ዓ.ም ሀገራዊ ምርጫ ሂደቱንም ሆነ ውጤቱን እንደማይቀበለው አሳወቀ፡፡ ፓርቲው ዛሬ ግንቦት 21/2007 ዓ.ም በጽ/ቤቱ ‹‹ነጻነት በሌለባት ኢትዮጵያ ሕዝባዊ አስተዳደር መትከል ዘበት ነው!›› በሚል ለሀገር […]

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን በሃመር ወረዳ በዲመካ ከተማ እና አካባቢዋ የሚኖሩ አርብቶአደሮች ” እኛ ድምጽ ሳንሰጥ” እንዴት ኢህአዴግ አሸነፈ ይባላል በሚል ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ከጸጥታ ሃይሎች ጋር ሲታኮሱ መቆየታቸውን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ አንድ ሻለቃ ጦር እና የፌደራል አባላት ወደ አካባቢው በመንቀሳቀስ በወሰዱት እርምጃ ከፍተኛ ጉዳት …

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለማስከበር በሚያደርገው ቀጣይ ትግል ህብረተሰቡ ከጎኑ እንዲቆምም ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል። የፓርቲው አመራሮች “‹‹ነጻነት በሌለባት ኢትዮጵያ ሕዝባዊ አስተዳደር መትከል ዘበት ነው!›› በሚል ርእስ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በምርጫው ሂደት በመቆየታቸው የኢህአዴግን አውሬነት ማሳየታቸውን በመጥቀስ፤ ‹‹በኃይል በተቀማ ድምፅ የሚመሰረት መንግስት በህዝብ ተቀባይነት የለውም››ብለዋል። ‹‹ምርጫው ከዚህ …

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባና በክልሎች የኤሌክትሪክ ኃይል በየዕለቱ እየተቆራረጠ ምርታማነት ባሽቆለቆለበት በዚህ ወቅት ሚኒስቴሩ ለጎረቤት ሀገራት ባለፉት 10 ወራት ብቻ 606 ነጥብ 5 ሚሊየን ኪ.ዋ. የኤሌክትሪክ ኢነርጂ በመሸጥ ዳጎስ ያለ ገቢ ማግኘቱን ይፋ አድርጓል፡፡ በሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ችግር ከጊዜ ወደጊዜ ተባበሶ በቀን በአማካይ አንድ ጊዜ የሚጠፋበትና …

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቄራ ምድብ ችሎት የቀረበችው ወ/ሮ ንግስት፣ መንግስት በሊቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ በአይ.ኤስ.አይ.ኤስ የሽብር ቡድን የተፈጸመውን የሽብር ድርጊት ለማውገዝ ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አዲስ አበባ ላይ ጠርቶት በነበረው ሰልፍ ላይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳትና ሰላማዊ ሰልፍን በማወክ›› ተጠርጥራ እንደታሰረች ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ማስረዳቱን …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ዓመታዊ ጉባኤው የሚካሔድበት ወቅት ‹‹የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን›› በሚል ተሠይሟል በአ/አበባ ሰንበት ት/ቤቶች ፀረ ሙስና እና ፀረ ኑፋቄ ንቅናቄ ላይ አቋም እንደሚይዝ ይጠበቃል ዋና ሓላፊው፣ ‹‹የአ/አበባዎችን ጥያቄ እንዳትቀበሉ›› በሚል ያደረጉት እንቅስቃሴ ተነቅቶበታል የሀ/ስብከቱ ሥ/አስኪያጅ ለአንድነቱ ልኡካን የውክልና ደብዳቤ ባለመጻፍ በዓላማ ተባብረዋቸዋል በዓለ ጰራቅሊጦስን ተንተርሶ በየዓመቱ የሚካሔደው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ …

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ የግንቦት15ቱን ምርጫ መቶ በመቶ ማሸነፉ ከተገለጸ በሁዋላ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል። ምንጮች እንደገለጹት በርካታ ፊደል ቀመስ አባሎቹ ኢህአዴግ አሸነፍኩ ያለበትን የድምጽ ልዩነት አልተቀበሉትም። ውጤቱን የሚቃወሙ የግንባሩ አባላት ” ህዝቡ ከእንግዲህ በሰላም መንግስት እቀይራለሁ የሚለው እምነቱ ተሟጦ የሃይል አማራጭን ብቻ እንዲመለከት ከማድረጉም በላይ፣ የሃይል አማራጭን የሚከተሉ ሃይሎች …

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እንደ አዲስ ስታንዳርድ ዘገባ እየተካሄደ ባለው ዓመታዊው የባንኩ የቦርድ ስብሰባ ላይ ነው ለፕሬዚዳንትነቱ ሲወዳደሩ ከነበሩት ስምንት ዕጩዎች መካከል የገንዘብ ሚኒስትሩ ሶፊያን አህመድ የሴራውሊዮኗን ሳሞራ ሚሸል ካማራን ተከትለው ሁለተኛው ተሰናባች ሆነዋል። ቦርዱ እንደ አውሮፓያኑ አቆጣጠር ባለፈው ፌብሩዋሪ 11 ቀን አቢጃን በሚገኘው የባንኩ ዋና ጽህፈት ቤት ባደረገው ስብሰባ ባንኩን …

ኢሳት ዜና ግንቦት 18 2007 በየመን መዉጫ አጥተዉ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን መካከል በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸዉን ጨምሮ ከሁለት እሺ በላይ ሰደተኞችን ከየመን ወደ ኢትዮጵያ ማጓጓዙን አለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም ገለጠ። ድርጅቱ የሳዉዲ አረቢያ፥ ሱዳንና፥ ጂቡቲን የድንበር ግዛት በመጠቀም ስደተኞቹን ወደአገራቸዉ መመለስ መቻሉን አስታዉቋል። በየመን መዉጫን አጥተዉ የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች መንግስት ዜጎችን ለመታደግ በቂ ጥረት አላደረገም ሲሉ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ግንቦት 19/2007 የ5ኛውን አገራዊ ምርጫ ጊዜያዊ ዉጤት ገለፀ፡፡ የመጨረሻዉ ዉጤት ሰኔ 15/2007 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሚገለጽ መሆኑን እንደተጠበቀ ሆኖ ጊዜያዊ የምርጫው ዉጤት ‹‹እስካሁን በደረሰን ሪፖርት መሰረት ብቻ›› በማለት ቦርዱ ገልጿል፡፡ በቦርዱ ዛሬ የተገለፀው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤቶች ግዜያዊ ውጤት እንደሚከተለው ነው፡፡ 1. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካሉት 547 ወንበሮች የ442ቱ ጊዜያዊ የምርጫ ዉጤት ተ/ቁ ክልል የምርጫ ክልል/ወንበር ብዛት ያሸነፈው ወንበር ብዛት ያልተገለፁ (ቀሪ) ወንበር ብዛት አሸናፊ የፖለቲካ ፓርቲ 1 ትግራይ 38 31 7 ህወሓት/ኢህአዴግ 2 አፋር 8 6 2 አብዴፓ 3 አማራ 138 107 31 ብአዴን /ኢህአዴግ 4 ኦሮሚያ 178 150 28 ኦህዴድ/ኢህአዴግ 5 ኢትዮጵያ ሶማሌ 23 16 7 ኢሶዴፓ 6 ቤንሻንጉል ጉምዝ 9 7 2 ቤጉህዴፓ 7 ደቡብ ብ/ብ/ህዝቦች 123 95 28 ደኢህዴን/ኢህአዴግ 8 ጋምቤላ 3 3 – ጋሕአዴን 9 ሐረሪ 2 11 — ሐብሊኦህዴድ/ኢህአዴግ 10 ድሬዳዋ ከ/አስተዳደር 2 11 — ኢሶዴፓኢህአዴግ 11 አዲስ አበባ ከ/አስተዳደር 23 23 – ኢህአዴግ ድምር 547 442 105 2. ለክልል ምክር ቤቶች ካሏቸው  1900 ወንበሮች የ1508 ጊዜያዊ የምርጫ ዉጤት ተ/ቁ ክልል የወንበር ብዛት ያሸነፈው ወንበር ብዛት ያልተገለፁ (ቀሪ) ወንበር ብዛት አሸናፊ የፖለቲካ ፓርቲ 1 ትግራይ 152 123 29 ህወሓት/ኢህአዴግ 2 አፋር 96 77 19 አብዴፓ 3 አማራ 294 230 64 ብአዴን /ኢህአዴግ 4 […]

የወቅቱ ሰበካ ጉባኤ የኹለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለመገንባት ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቅቋል የቦታ፣ የሕንፃ እና የልዩ ልዩ ገቢ ማስገኛ ተቋማት ኪራይ ማጣራት በመገባደድ ላይ ነው የሊ/ን የማነ፣ የዋና ጸሐፊነትም የሥ/አስኪያጅነትም ሥልጣን የተጠያቂነት ዕንቅፋት ፈጥሯል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት እና አድባራት÷ የመሬት እና የሕንፃ ኪራይ፣ የመካነ መቃብር አጠቃቀም እና የመኪና ሽልማት ጉዳዮችን አጥንቶ የመፍትሔ ሐሳብ እንዲያቀርብ ከጠቅላይ …

አንድነት ፓርቲ በህዝብ ዘንድ እያገኘ በመጣው ከፍተኛ የህዝብ ተቃባይነት ስርአቱ ለስልጣኑ አንደ ሚያሰጋው በመገንዘብ ፓርቲውን ማፍረሱ የቅርብ ግዜ ትዝታ ነው:: ፓርቲውን አፍርሶ ጠንካራ የሚባሉ ለፓርቲው ብዙ ያገለገሉ ሰዎችን እያሳደደ በማሰር በመደብደብ ላይ ይገኛል …… አቶ አዲሱ ካሳሁን ለረዥም ግዜ በፓለቲከው ላይ የራሱን እስተወፆ ሲያበረክት በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የፓለቲካ ስራ ሲሰራ ቆይቶል በዚህም ምክነያት […]

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሶስቱ ጋዜጠኞች ዛሬ ግንቦት 19/2007 ዓ.ም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ መዝገቡ የተቀጠረው አቃቤ ህግ አሉኝ ባላቸው ሲ.ዲዎች እና ቀሪ ምስክሮቹን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ብይን ለመስጠት ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡ ቀሪ ምስክሮቹን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ […]

በባህር ዳርቻዎቹ ፓሪስና ኒስ ከተሞች ውስጥ የሚገኙ 140 የፈረንሳይ ሆቴሎች 4700 ክፍሎቻቸውን ለአንድ አዲስ ክስተት ማሰናዳት ነበረባቸው፡፡ ባለፈው ሳምንት በተካሔደ ሥነ ሥርዓት ከመላው ዓለም የተውጣጡ 6,400 ሰዎች በፓሪስና በኒስ ከተሞች ለአራት ቀናት ጎዳናዎችንና መዝናኛ ሥፍራዎችን አጣበው ሰንብተዋል፡፡ ቢሊየነሩ ቻይናዊ ሊ ጂንዩዋን ይባላሉ፡፡ የ57 ዓመቱ ባለፀጋ ቲየንስ ግሎባል የተባለው ተጨማሪ ምግቦችና ንጥረ ነገሮች አምራች ኩባንያ ከ20 […]