መስከረም ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በጌዲዮ ዞን ከድርቅ ጋር በተያያዘ የተፈጠረውን ረሃብ ተከትሎ በርካታ ዜጎች ወደ ከተማ እየፈለሱ ሲሆን፣ እርዳታ ማግኘት ባለመቻላቸው ጎዳና ላይ ማደር መጀመራቸውን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል። መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ያሰማሩዋቸው ባለሙያዎች በዞኑ 80 ሺ ህዝብ መራቡን ሪፖርት ሲያደርጉ፣ የዞኑ የመንግስት ባለስልጣናት በተቀራኒው በዞናቸው ምንም የተራበ ሰው …

መስከረም ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ መስተዳድር የኢህዴግ ድርጅት ጽ/ቤት ፣ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ረቂቅ ዕቅድ ዙሪያ በከተማው 10 ክ/ከተሞች በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች የተውጣጡ የተለያዩ የህ/ብ ክፍሎችን በሚያወያይበት መድረክ ፣ ነዋሪዎች አወያይ ካድሬዎችን ያስደነገጡ ጥያቄዎችን አንስተዋል። በጉለሌ ክ/ከተማ ስር የሚገኙ የ10 ወረዳዎችን የህብረተሰብ ክፍል በያዘው የወረዳ 9 አዳራሽ በርካታ ጥያቄዎች …

መስከረም ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመኪና አደጋ በከፍተኛ ሁኔታ የሰዎችን ሕይወት ቀጣፊ ከሆነባቸው አገራት ተርታ ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ አገር መሆኗን የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት በሪፖርቱ ገልጿል።ድርጅቱ ከመቶ ሺህ ተሽከርካሪዎች ውስጥ 3 ሺ 874 ሰዎች ለሞት እንደሚጋለጡና 80 % የሚሆነው የአደጋው ምንጭ የአሽከርካሪዎች ጥፋት ሲሆን፣ የተቀረው 20 በመቶ ደግሞ በመንገድ ችግሮች መሆኑን …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

በኢትዮጵያ እድሚያቸው ሳይደርስ የሚያገቡ በሺሕ የሚቆጠሩ ሴት ልጆች በርካታ ናቸው።
ከጎንደር የአሜሪካ ድምጿ ማርተ-ፋንደር ቮልፍ እንደዘገበችው የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት የአካባቢው ባለስልጣናት ለማኅበረሰቡ ግንዛቤ ለማስጨበጥ መጠነ ሰፊ ስራ ጀምረዋል።

በትናንቱ ምርጫ 35.5 በመቶ ድምጽ በማግኘት ያሸነፈው ፓርቲያቸው ሲሪዛ «ነፃይቱ ግሪክ» በአህፅሮቱ Anel ከተባለው ፓርቲ ጋር ተጣምሮ መንግሥት እንደሚመሰርት ተገልጿል ።

መስከረም ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለከተማ ቤቶች መስሪያ፣ ለልማት ወይም ህገወጥ ግንባታ በሚል አርሶ አደሮች ያለምንም ክፍያ ከይዞታ መሬታቸው እየተፈናቀሉ ማህበራዊ ቀውስ እየተፈጠረ መሆኑን ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። በኦሮምያ ክልል በ አዳማ ከተማ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርሶ አደሮችና ነዋሪዎች ቦታቸውን እንዲለቁ ማስጠንቀቂያ የደረሳቸው ሲሆን፣ በርካታ ቤቶችም …

መስከረም ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቃቢ ህግ ለፍርድ ቤት ባቀረበው ክስ ቀድም ብሎ 60 ሰዎች መገደላቸውን ከጠቀሰ በሁዋላ፣ አሻሽሎ ባቀረበው ክስ 126 ሰዎች በወረዳ አመራሮች ትእዛዝ መገደላቸውን ጠቅሷል። በማዣንግ፣ ጎደሬና ሚጤ በሃላፊነት ላይ የነበሩ የወረዳ አመራሮች ” ደገኞች ቦታችንን ለቀው ይውጡ፣ ደገኞች በማዣንግ ዞን ውስጥ የያዙትን የእርሻና የቡና ተክል መሬት ለማዣንግ …

መስከረም ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ ዓርብ መስከረም 7/2008 ዓ.ም በድንገት በጠራው የተቋራጮች ስብሰባ፣ በክልሉ የሚገነቡ የጤና ተቋማትን በመስራት ላይ ያሉ ተቋራጮች በሙሉ ሰብስቦ ፤የግንባታ ስራዎች በመጓተታቸው ምክንያት ከልዩ ልዩ ግብረ ሰናይ መንግስታት የተገኘ የዕርዳታ ገንዘብ በየጊዜው ተመላሽ መሆኑ ቢሮውን አሳስቦታ ብሏል። ተቋራጮች በተቻላቸው ፍጥነት ግንባታቸውን በማጠናቀቅ በዕርዳታ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና


click here for pdf

አሁን ባለንበት ዘመን ያለን የኢትዮጵያ ትውልድ የሀገራችንን ታሪክ፣ የሕዝቦች የእርስ በርስ ግንኙነትና የመሪዎቻችንን ሁኔታ ስንነጋገርና ስንጽፍ በአብዛኛው አሉታዊውን ነገር ይበልጥ ጎልቶ እንዲወጣ፣ ጥላቻ እንዲበቅል፣ ቂም እድሜ እንዲያገኝ፣ ልዩነት እንዲሰፋ፣ ጠብም ሥር እንዲሰድ በማድረግ ላይ የተመሠረተ ሆኖ ይታያል፡፡ ርግጥ ነው በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ የተፈጠሩ የመስተጋብር ችግሮች ሁሉ በኛም ሀገር ተፈጥረዋል፡፡ በኛ ሀገር የተፈጠሩትም በሌሎች ይገኛሉ፡፡ በዓለም ሕዝቦች ታሪክ ውስጥ የኩራትም የውርደትም፣ የፍቅርም የጠብም፣ የሰላምም የጦርነትም፣ የእኩልነትም የጭቆናም፣ የመረዳዳትም የመጠፋፋትም፣ የሥልጣኔም የስይጣኔም ታሪኮች አሉ፡፡ እንኳን በአንድ ሀገር የሚኖሩ የተለያየ ዘውግ፣ ቋንቋ፣ እምነትና የኑሮ ደረጃ ያላቸው ቀርተው በተመሳሳይ ቋንቋ፣ ባሕልና የኑሮ ደረጃ የሚገኝ የአንዲት ሀገር አንድ ወጥ ሕዝብ እንኳን በውስጡ ጽጌረዳም እሾህም አለው፡፡ 

የሚገርመው ነገር ኢትዮጵያን ከዓለም የተለየች የሚያደርጋት ምን እንደሆነ አለመታወቁ ነው፡፡ ኢትዮጵያኮ ሲኦልም አልነበረችም መንግሥተ ሰማያትም አልነበረችም፡፡ ሀገር ነበረች፣ አሁንም ሀገር ነች፡፡ ሀገር የሚገጥማት ፈተና ሁሉ ገጥሟታል፤ ሀገር የሚኖራት ጸጋ ሁሉ ታድሏታል፡፡ በአንዳንድ የታሪክ ምእራፏ ለመንግሥተ ሰማያት ጠጋ፣ በሌላው ምእራፏ ደግሞ ለሲኦል ጠጋ ብላ ይሆናል እንጂ፣ ፈጽማ ሲኦልና መንግሥተ ሰማያት ሆና አታውቅም፡፡ እኛ ልጆቿ ግን ወደ መንግሥተ ሰማያት ጠጋ ማለት ብቻ ሳይሆን ምድራዊት መንግሥተ ሰማያት ብትሆንልን እንወዳለን፤ ለዚያም እንሠራለን፡፡ ወደዚያ በተጠጋችበት ታሪክም እንኮራለን፤ ወደ ሲኦል ለመውረድ አዘንብላ የነበረችበትንም ዘመን ስናስብ በልብ ስብራት እንመታለን፡፡
የታሪክ ሂደት ያመጣቸውን የትናንት ነገሮች ዛሬ አንቀይራቸውም፡፡ ሆነዋልና፡፡ ነገር ግን እንማርባቸዋለን፤ ከትናንት ወስደንም ለዛሬ እንጠቀምባቸዋለን፡፡ የዛሬ ማንነታችን መገንቢያም እናደርጋቸዋለን፡፡ በተቃራኒውም ያለፉትን ዘመናት ጠባሳዎች እየነካካን ቂምን ማመርቀዝ፣ ጥላቻን ማጎንቆል፣ ልዩነትን ማስፋት፣ ፍቅርንም ማደብዘዝ እንችላለን፡፡ ሁለቱም በእኛ ምርጫ ላይ የተመሠረቱ ናቸው፡፡ ምርጫው ለእህሉ ወይስ ለአረሙ ትለፋለታለህ? የሚለው ነው፡፡ 
ታሪካቸውን ለዕድገታቸውና ለሰላማዊ መስተጋብራቸው የተጠቀሙት ግን ከአረሙ ይልቅ ለእህሉ ጊዜና ጉልበታቸውን ያፈሰሱት ናቸው፡፡ ገበሬ ዓመት በሙሉ የሚለፋው አረም ለማብቀል አይደለም፡፡ አረም ለመብቀል ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያ፣ ጉልጓሎ፣ አያስፈልገውም፡፡ ወንፈልና ደቦ አይሰበስብም፡፡ ጉልበትና ጊዜውን አያባክንም፣ ወዝና ላቡን አያንጠፈጥፍም፡፡ ለአረም አንድ ነገር በቂ ነው፡፡ ስንፍና ብቻ፡፡ ገበሬ ከሰነፈ ምንም ሳይደክም አረም እርሻውን ከዳር ዳር ይወርስለታል፡፡ በሬ ሳይጠምድ፣ እርሻ ሳይውል፣ ሌሊት ሳይነሣ፣ ማታ ሳይገባ፣ ዝናብ ሳይመታው፣ ፀሐይ ሳይከካው፣ ብርድ ሳይገርፈው፣ ወላፈን ሳይጠብሰው አረም እንዲሁ ይበቅልለታል፡፡ ገበሬ ለአረም አይለፋም፡፡
የገበሬን ጥበብ፣ የገበሬን ድካም፣ የገበሬን ጉልበት፣ የገበሬን ማዳበሪያ፣ የገበሬን ትዕግሥት፣ የገበሬን ሐሞት፣ የገበሬን ልምድ፣ የገበሬን  ጊዜ፣ የሚፈልገው እህሉ ነው፡፡ ወንፈልና ደቦ የሚሰበስበው ለእህሉ ሲል ነው፡፡ በሬ የሚጠምደው፣ ሞፈር የሚቆርጠው፣ ቀንበር የሚነድለው፣ ጎተራ የሚያዘጋጀው፣ አውድማ የሚለቅልቀው ለእህሉ ሲል ነው፡፡ አረም በስንፍና የሚበቅለውን ያህል እህል የሚበቅለው በጉብዝና ነው፡፡ እህል ያለ ገበሬው ጥበብ፣ ዕውቀት፣ ጉልበትና መሣሪያ ከምድር አይወለድም፡፡ አረም ግን አዋላጅ አይፈልግም፡፡ አረም በራ ተወልዶ በራሱ ያድጋል፡፡   
በታሪክ መስክ ላይ የተሠማራ ትውልድም ጊዜውን ማጥፋት፣ ጉልበቱን መሠዋት፣ ጥበቡን ማፍሰስ፣ ዕውቀቱን መከስከስ፣ ያለበት ለአረሙ አይደለም፡፡ ጥላቻው፣ ቂም በቀሉ፣ መቆራቆሱ፣ መናከሱ፣ መለያየቱ፣ መጠፋፋቱ፣ ይኼ የትውልድ አረም ነው፡፡ በስንፍና ብቻ ሊበቅል የሚችል፡፡ በታሪካችን ውስጥ በቅሎ የነበረው እህል ፍቅራችን ነበረ፣ አንድነታችን ነበረ፣ መዋለዳችን ነበረ፤ መዋሐዳችን ነበረ፤ ሥልጣኔያችን ነበረ፤ ጀግንነታችን ነበረ፤ ነጻነታችን ነበረ፡፡ ትኩረታችንን እህሉ ላይ ካደረግነው አረሙን እንቋቋመዋለን፡፡ መቋቋምም ብቻ ሳይሆን እናጠፋዋለን፡፡ አረሙን ማጥፋት ያለብን አረም ስላልነበረ አይደለም፣ አረምን ለመሸፋፈን ሲባልም አይደለም፡፡ አረም ስለማይጠቅመን ነው፡፡ በሀገራችን እንክርዳድ የተሰኘው አረም ሳይለቀም ቀርቶ ከስንዴ ጋር ገብቶ ጠላ የሆነ እንደሆነ ያሳብዳል፡፡ ለዚህም ነው፡-
እንክርዳድ እንክርዳድ የተንከረደደ
ስንዴ መስሎ ገብቶ ስንቱን አሳበደ
የተባለው፡፡
አሁን አሁን በሀገራችን ጉልበት እየጨረስን ያለነው አረሙን ለማብቀል ይመስላል፡፡ አንዲት ጽጌረዳን ከማብቀልና ፈንድታ አበባዋ ሠፈሩን እንዲያውድ ከማድረግ ይልቅ አንድ ማሳ ሙሉ አረም ማብቀል በጣም ቀላል ነው፡፡ አረሙ ስንፍናን ብቻ ይጠይቃልና፡፤ ጽጌረዳዋን ለማብቀል ግን ከመሬቱ፣ ከሰማዩ፣ ከአየሩ፣ ከአራዊቱ፣ ከአላፊ አግዳሚው ጋር መጋደልን ይጠይቃል፡፡  
በታሪካችን ውስጥ የነበረውን እህል ዘሩን አምጥተን መዝራት፣ ዘርተን መከባከብ፣ ተከባክበንም ማሳደግ ይገባን ነበረ፡፡ ጥበባችንን፣ ዕውቀታችን፣ ገንዘባችንንና ጉልበታችንን ለእርሱ ማፍሰስ ይገባን ነበረ፡፡ አሁን ግን ድርሰቶቻችንን፣ ሚዲያዎቻችንን፣ ሐውልቶቻችንን፣ ትርክቶቻችንን፣ ዲስኩሮቻችንን፣ ንግግሮቻችንን፣ የፖለቲካ ፕሮግራሞቻችንን የምናባክነው አረሙን ለማብቀል ሆኗል፡፡ አረምኮ ይህንን ሁሉ አይፈልግም ነበር፡፡ አረምን ለማብቀል ሥርዓተ ትምህርት መቅረጽ፣ ዩኒቨርሲቲ መገንባት፣ የፖለቲካ ፓርቲ ማደራጀት፣ ሚዲያ መዘርጋት፣ ብዕርና ወረቀት ማባከን፣ ምስትርናና ዱክትርና መድረስ አያስፈልግም ነበረ፡፡ አረም እንዲሁ ይበቅላልኮ፡፡
የፖለቲከኞቻችን ብስለት፣ የምሁሮቻችን ብቃት፣ የትውልዱ ምጥቀት፣ የተቋሞቻችን ሥልጠት፣ የሐሳቦቻችን ጥልቀት፣ የሚዲያዎቻችን ፍጽመት፣ የሥልጣኔያችን ርቀት፣ የጥበበኞቻችን ልህቀት የሚታወቀው ባበቀልነው እህል እንጂ ባበቀልነው አረም ብዛት አይደለም፡፡ ለአረምማ እነዚህ ሁሉ አያስፈልጉትም፡፡ እነዚህ ያስፈለጉት ሲቻል አረሙን ቀድሞ ለመከላከል፣ ካልሆነም የበቀለውን አርሞ እህሉን አህል ለማድረግ ነበር፡፡ ለማስተማር እንጂ ለማደንቆር ምን ትምህርት ቤት ይሻል? ለማዳን እንጂ ለማሳመም ምን ሆስፒታል ያስከፍታል? ለፍትሕ እንጂ ለወንጀል ምን ዳኝነት ያስፈልጋል? ለመግባባት እንጂ ላለመግባባት ምን ቋንቋ ያስፈልጋል? ለልዕልና እንጂ ለውርደት ምን ኪነ ጥበብ ያሻል? ለዓለም ዓቀፋዊ እሴቶች እንጂ ለጎጠኝነት ምን ጥበብ መፍሰስ ያሻዋል? ለማጥገብ እንጂ ለማስራብ ምን ፖሊሲ ያስፈልጋል? ለሥልጣኔ እንጂ ለስይጣኔ ምን ፓርቲ ማቋቋም ያስፈልጋል? ለጽድቅ እንጂ ለኃጢአት ምን የእምነት ተቋም ያሻል?
የኛ ጥበብ፣ ዕውቀት፣ ገንዘብና ጉልበት አረም ላይ እየፈሰሰ ነው፡፡ የገበሬ ጉብዝና በአረም ብዛት እንደማይለካው ሁሉ የትውልድ ጉብዝናም በአረም አይለካም፡፡ ‹እንኳንስ ዘንቦብሽ እንዲያውም ጤዛ ነሽ› እንዲሉ እንኳንና የእኛ ጥበብና ገንዘብ፣ ጉልበትና ጊዜ ተጨምሮበት አረም በራሱም ሀገር ያጠፋል፡፡
እንዲህ እርሻው ሁሉ አረም እስኪወርሰው
የለም ወይ የለም ወይ የለም ወይ ባር ሰው
ተብሎ የለ፡፡
አረም አያዋለዱ ሀገርን ለማሠልጠን መመኘት፣ ተኩላን እያረቡ የበግ ሥጋን እንደመመኘት ያለ ነው፡፡
በገበሬዎቻችን ታሪክ ውስጥ በ16ኛው መክዘ በሀገራችን ተከስቶ በነበረው የሃይማኖት ጦርነት ጊዜ ከ20 ዓመታት በላይ ገበሬው ተረጋግቶ በእርሻ ላይ ስላልነበር አገሩን አረም ወርሶት ነበር ይባላል፡፡ በዚያ ጊዜ ከሀገራችን ገጽ የጠፉ የእህል ዓይነቶች አሉ፡፡ ለዘር ተብሎ የተቀመጠው ወይ በቀጠና ምክንያት ተበልቶ፣ አለያም ቤቱ ሲቃጠል ተቃጥሎ፣ ካልሆነም የተቀበረበት ቦታ በዘመን ብዛት ጠፍቶ ሳይተኩ የቀሩ የእህል ዘሮች አሉ፡፡ የካሕሳይ ገብረ እግዚአብሔርን ኅብረ ብዕር ያነበበ ሰው ከሚያያቸው የእህል ዘሮች መካከል ብዙዎቹ ስማቸውን ትተው ጠፍተው የቀሩት እንዲህ ባሉ ዘመናት ነው ይባላል፡፡ አረሙ ግን አልጠፋም፡፡ እንዲያውም ተመችቶት ነበር፡፡
በታሪካችንም ውስጥ እየጠፉና እየመነመኑ የመጡ በጎ እሴቶች፣ ባሕሎች፣ ልማዶችና ወጎች አሉ፡፡ አገር ችግር ላይ ስትወድቅ እህሉን የሚያመርተው ሲያጣ፣ ዘሩ ይጠፋል፡፡ ያንን ዕድልም አረሙ ይጠቀምበታል፡፡ ምድሩም እህል ተዘርቶበት የማያውቅ ይመስላል፡፡  
አሁን ለዚህ ትውልድ ጥያቄው አንድ ነው፤ ለአረሙ እንድከም ወይስ ለእህሉ? እህሉን በማምረት ብርታትህን ታሳያለህ ወይስ አረሙን በማብቀል ስንፍናህን? የኢትዮጵያ መልክ የሚቀየረው ለዚህ ጥያቄ በምንሰጠው መልስ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የአገር መከላከያ ሚኒስቴርን ጨምሮ በ23 መንግሥታዊ ተቋማት ላይ ምርመራ እያካሄደ መሆኑንና በተወሰኑት ላይ ደግሞ ማስረጃ በማጠናቀር ክስ መመሥረቱን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ የተጠናቀቀውን በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጠው እስከ ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ያለውን ሒደት ብቻ በሚያሳየው መግለጫ፣ በመከላከያ ሚኒስቴር በተፈጸሙ ሁለት የሙስና ወንጀሎች ጥቆማ የደረሰው መሆኑን ገልጿል፡፡ ከእነዚህም አንዱ በመከላከያ ሚኒስቴር ሕግን ባልተከተለ መንገድ ከሁለት ሚሊዮን ዶላር በላይ ለግዥ ውሏል የሚል ነው፡፡ ኮሚሽኑ ለጋዜጠኞች ባሰራጨው ሪፖርት በዚህ ጉዳይ ላይ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስገንዝቧል፡፡ 

ሌላኛው በመከላከያ ተፈጸመ ተብሎ የተጠረጠረው ጉዳይ በመከላከያ ሚኒስቴር 171 ሬጅመንት፣ ዘጠኝ መኮንኖች ከመከላከያ ፋውንዴሽን በዝቀተኛ ዋጋ ለክፍለ ጦሩ አባላትና ለቤተሰቦቻቸው ፍጆታ የሚውል ስኳር ከነጋዴዎች ጋር በመመሳጠር ከ2.2 ሚሊዮን ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል ተብለው መጠርጠራቸው ነው፡፡ ኮሚሽኑ በተጠርጣሪ መኰንኖች ላይ ክስ መመሥረቱ ተጠቁሟል፡፡ 

ኮሚሽኑ ምርመራና ክስ ካቀረበባቸው መንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶች መካከል የኢትዮጵያ መድን ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ፣ የአዲስ አበባ ቤቶች ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት፣ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንና ጂንአድ ይገኙበታል፡፡

የኢትዮጵያ መድን ድርጅት የሳሪስ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ የነበሩ ግለሰብ፣ ከቀረጥ ነፃ ተሽከርካሪ ለማስገባት የመድን ሽፋን ዋስትና ማስያዣ ያስያዘ ግለሰብ እንዳለው በማስመሰል ለገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በመስጠቱ፣ እንዲሁም ሚድሮክ ጐልድ ያለመያዣ (ኮላተራል) 600,000 ብር ቦንድ ዋስትና በመስጠቱ ተጠርጣሪው ግለሰብ ክስ እንደተመሠረተበት ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች የሆኑ ተጠርጣሪዎች የባንክ ገንዘብ ማስተላለፊያ የሚስጥር ቁልፍ በመጠቀም፣ ለግለሰቦች ሰባት ሚሊዮን ብር እንዲተላለፍላቸው በማድረግ ተጠርጥረው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑንም ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጁባ ቅርንጫፍ ሠራተኞችና ኃላፊዎች 20 ሚሊዮን ብር አጭበርብረዋል ተብለው ተጠርጥረው ክስ እንደተመሠረተባቸው ተገልጿል፡፡

የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ በቅሎ ቤት ቅርንጫፍ ሠራተኞች በሐሰተኛ አካውንት ጣሊያን ኤምባሲ በሚል፣ 2.2 ሚሊዮን ብር እንዳለው አድርገው ሰነድ ካዘጋጁ በኋላ 700,000 ብር ወደ ሌላ ባንክ በማስተላለፍ ወንጀል ተጠርጥረው ምርምራ እየተካሄደባቸው ነው፡፡

በአዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት (ፕሮጀክት 15) ያላግባብ የጠጠር ግዥ በመፈጸም ሁለት ሚሊዮን ብር መጠን ያለው የሕዝብና የመንግሥት ንብረት ላይ ጉዳት አድርሰዋል በተባሉ ለጊዜው ቁጥራቸው ባልታወቁ ሠራተኞች ላይ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የአዲስ አበባ ቤቶች ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ከ1997 ዓ.ም. እስከ 2006 ዓ.ም. ድረስ የሳኒተሪ ዕቃዎች ግዥ በሕገወጥ መንገድ ግዥ እንዲፈጸም በማድረግ በ81 ሚሊዮን ብር ተጠርጥረው ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ 

ከእነዚህ ጉዳዮች በተጨማሪ ሁለት አስመጪ ነጋዴዎች ከኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በመመሳጠር 301.9 ሚሊዮን ብር በመመዝበር ተጠርጥረው ክስ ተመሥርቶባቸዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በእነ አቶ መላኩ ፈንታ መዝገብ ክስ ከተመሠረተባቸው የቀድሞ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣናት አንዳንድ የባለሥልጣኑ ሠራተኞችና ከፍተኛ ነጋዴዎች ላይ ተጀምሮ ከነበረው ምርመራ ጋር በተያያዘ፣ የአገር ውስጥ ግብርና የጉምሩክ ቀረጥ ባለመክፈል በተጠረጠሩ አምስት የግል ኩባንያዎች ላይ የኢንስፔክሽን ኦዲት በማስደረግ በተገኘው ማጣራት፣ 361.6 ሚሊዮን ብር ታክስ አለመከፈሉን ኮሚሽኑ በሪፖርቱ ገልጾ፣ ቀጣይ ምርመራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡

ከእነዚህ ውጪ ደግሞ የጅምላ ንግድ አቅራቢ ድርጅት (ጅንአድ) የሻሸመኔ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ፣ ከገቢያቸው በላይ ሀብት ይዘው መገኘታቸው ነው፡፡ ኃላፊው በሁለት ሆቴሎች፣ በመኖሪያ ቤቶችና በተሽከርካሪዎች ተጠርጥረው ጉዳያቸው በምርምራ ላይ እንደሚገኝ ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡ 

 

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

በተለምዶ አያት አደባባይ እየተባለ በሚጠራው አያት ቁጥር ሁለት ኮንዶሚኒየም አካባቢ፣ ባልተከደነ ቱቦ ምክንያት የአራት ዓመት ሕፃን ሕይወት መስከረም 5 ቀን 2008 ዓ.ም. አለፈ፡፡

በአካባቢው በሚገኙት ኮንዶሚኒየም ቤቶች ውስጥ በአብዛኛው የሚኖሩት በመልሶ ማልማት ከአራት ኪሎና ከተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ ነዋሪዎች ሲሆኑ፣ አደጋው የደረሰው ከእነዚህ መካከል አንዱ በሆኑት አቶ እንግዱ ዘለቀ ሕፃን ልጅ ላይ ነው፡፡

የሕፃኑ ሕይወት የተቀጠፈውም የቤቶቹ ግንባታ ባለመጠናቀቁና የተከፈቱ ቱቦዎች በመኖራቸው እንደሆነ ቤተሰቦቹ ለሪፖርተር ገልጸዋል…

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጋቢት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ዕጣ ያወጣባቸው 35 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ካርታ ተሠርቶ ባለመጠናቀቁ፣ ቤቶቹ ለደረሳቸው ዕድለኞች ማስረከብ አለመቻሉ ተጠቆመ፡፡ 

አስተዳደሩ በአራት ኪሎ፣ የካ አባዶ፣ ገላን፣ ቱሉ ዲምቱና በተለያዩ ቦታዎች 41 ሺሕ ቤቶችን አዘጋጅቶ ስድስት ሺሕ ያህሉን ለልማት ተነሺዎች፣ 35,000 የሚሆኑትን ደግሞ ለነባር ተመዝጋቢ ዕድለኞች በዕጣ እንዲደርስ ካደረገ በኋላ፣ እስከ ሰኔ 5 ቀን 2007 ዓ.ም. ከአስተዳደሩ ጋር ውል እንዲፈጽሙ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ 

ውሉን ከአስተዳደሩ የተለያዩ ወረዳ ጽሕፈት ቤቶች በመቅረብ (በየክፍላተ ከተሞቹ) ተዋውለው ከጨረሱ በኋላ 20 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ ሲፈጽሙ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ወራት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ጠርቶ የብድር ውል እንደሚፈራረሙ ገልጾላቸው እንደነበር፣ በዕጣ ዕድሉ የደረሳቸው ግለሰቦች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ 

የቤቶቹ ዕጣ ከወጣ ስድስት ወራት እንደሞላውና 20 በመቶውን ከከፈሉ አራት ወራት እንደሞላቸው የሚናገሩት አቶ በዛብህ ንጉሡ የተባሉ ዕድለኛ፣ ባንኩ በሁለት ወራት ውስጥ እንደሚጠራቸው የነገራቸው ጊዜ ከማለፉም በተጨማሪ፣ 11ኛው ዙር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ሊወጣ መሆኑን በመገናኛ ብዙኃን ሲሰሙ ሥጋት እንደገባቸው ገልጸዋል፡፡ ዕጣው እንደወጣላቸው ከታወቀ ጊዜ ጀምሮ አከራዮቻቸው ‹‹ነገ ጥሎት ለሚሄደው›› በማለት የኪራይ ዋጋ በእጥፍ እንደጨመሩባቸው የሚናገሩት አቶ በዛብህ፣ ባንክ በሁለት ወራት ውስጥ ውል ፈጽሞ ቤቱን እንደሚረከቡ ተስፋ በማድረጋቸው የተጨመረባቸውን የቤት ኪራይ በወቅቱ ችላ ቢሉም፣ አሁን ግን ባንኩ ዝም በማለቱ ግራ እንደገባቸው ተናግረዋል፡፡ 

ለእሳቸውና ለሌሎች ዕድለኞች የደረሰው መኖሪያ ቤት ሳይተላለፍ ስለሌላ ዕጣ ሲወራ ሲሰሙ ግራ በመጋባታቸው ወደ ባንክ ሄደው ሊጠይቁ ቢሞክሩም በቂ ምላሽ እንዳላገኙ የሚናገሩት አቶ በዛብህ፣ አስተዳደሩ ወይም ሌላ የሚመለከተው አካል ችግሩ ምን እንደሆነ እንዲያስረዷቸው ጠይቀዋል፡፡ 

እንደ አቶ በዛብህ ሁሉ አብዛኛዎቹ የዕድሉ ተጋሪዎች ከባንክ ጋር ውል አለመፈጸሙና ቤቱን አለመረከባቸው ግራ እንዳጋባቸው እየገለጹ መሆኑን የ65 ዓመት ዕድሜ እንዳላቸው የሚናገሩት ወይዘሮ ቀለሟ ተገኝም አስረድተዋል፡፡ ችግር ካለም የሚመለከተው አካል ግልጽ እንዲያደርግላቸው እሳቸውም እንደ አቶ በዛብህ ጠይቀዋል፡፡ 

በአሥረኛው ዙር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የደረሳቸው ዕድለኞች በየክፍለ ከተማው ከሚገኙ ከቤቶች አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች ጋር የመጀመርያውን የቤት ባለቤትነት ውል ከፈጸሙ በኋላ፣ 20 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ ለባንክ ከፍለዋል፡፡ 

የቤቱን ካርታ በመያዝ የብድር ውል ከዕድለኞቹ ጋር መፈጸም ያለበት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ለምን ውሉን እንዳልፈጸመ ከሪፖርተር ለቀረበለት ጥያቄ የባንኩ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ሲመልሱ፣ ‹‹ችግሩ የባንኩ አይደለም፡፡ ባንኩ ካርታ ተሠርቶ ከተሰጠው ትክክለኛነቱን በማረጋገጥ ውል ይፈጽማል፡፡ ነገር ግን በየሳይቱ ተሠርቶ የቀረበለት ካርታ በጣም ትንሽ ነው፡፡ በመሆኑም ካርታው ተሠርቶ ካልተሰጠው ውል መፈጸም አይችልም፤›› ብለዋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መስፍን መንግሥቱ በጉዳዩ ላይ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ካርታ የሚያዘጋጀው የመሬት አስተዳደር ነው፡፡ ‹‹እስካሁን ሰባት ሺሕ ካርታዎችን አዘጋጅቷል፡፡ በእርግጥ በተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተጠቀሱት ክፍተቶች አሉ፡፡ ክፍተቶቹን ለመሙላት በጋራ እየሠራን ነው፡፡ የመሬት አስተዳደር፣ የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት፣ የቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲና ሌሎችም ያሉበት ኮሚቴ ተዋቅሮ በመረባረብ እየተሠራ ነው፤›› ሲሉ አቶ መስፍን አስረድተዋል፡፡ 

ካርታው ሲሠራ ጥንቃቄ የሚፈልግ መሆኑንና አብዛኛው የዕድሉ ባለቤት የሚያቀርበው ሰነድ ደግሞ ከጋብቻ መኖርና መፍረስ፣ ከስም ስህተትና ከመሳሰሉት ጋር የተገናኘ በመሆኑ፣ እሱን ማስተካከሉ ጊዜ የሚወስድ መሆኑንም አቶ መስፍን አክለዋል፡፡ ባንክ አንድ ፊደል ቢጎድል ስለማይረከብ ሥራው ልዩ ጥንቃቄ የሚፈልግ መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ካርታውን በዋናነት የሚሠራው መሬት አስተዳደር መሥሪያ ቤት ሠራተኞች ወደ ሥልጠና መግባታቸውም ጫና መፍጠሩን ጠቁመዋል፡፡ 

ሌላው እያንዳንዱ ቤት የማን እንደሆነ የሚያረጋግጠው የዲዛይንና የቴክኒክ ሥራ በተለይ በየካ አባዶ፣ በአቃቂ ቃሊቲ፣ በገላንና ገነት መናፈሻ ሳይቶች ላይ ችግር በመፈጠሩ፣ እንደገና እየተከለሰ እንደነበር አክለዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን የአውቶካድ ኤክስፐርቶች በየሳይቱ በቋሚነት ተመድበው እየሠሩ በመሆናቸው ችግሩ እየተቀረፈ እንደሆነ አቶ መስፍን ተናግረዋል፡፡ 

ሁሉም ባለድርሻ ተረባርቦ በመሥራት እስከ መስከረም 30 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ ሁሉም ካርታ ተጠናቆ ለባንክ መሰጠት እንዳለበት አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሠራ በመሆኑ፣ ሥራው እንደሚጠናቀቅና ለዕድለኞቹ ቁልፍ ማስረከብ እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡ አዲስ ይወጣል ስለሚባለው 11ኛ ዙር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ጉዳይ የተጠየቁት አቶ መስፍን፣ ጎን ለጎን ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን ጠቁመው የወጡ ዕጣዎች ለዕድለኞች ሳይተላለፉ ሌላ ዕጣ እንደማይወጣ፣ ቀጣዩ ዕጣ መቼና በየትኛው ወር እንደሚወጣ አሁን መናገር እንደማይቻል አስታውቀዋል፡፡

 

የ44 ሚ. ብር ግብር ዕዳ ያለበት “ሪል ውሃ” ከፍተኛ ምርመራ እየተደረገበት ነው

    ቲ ጂ ኤም ዲ በሚል ስያሜ የተመሰረተው የ “ሪል ውሃ” አምራች ኩባንያ፤ ያለበት 44 ሚ.ብር የግብር ዕዳ በምርመራ ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ገለፀ፡፡ ኩባንያው ከ1999 ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም ድረስ ታደለ ዳለቻ በተባለ ግለሰብ ስራ አስኪያጅነት ሲመራ የቆየ ሲሆን ከ2002 እስከ 2003 ዓ.ም አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ይመሩት እንደነበር የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የትምህርትና ኮሙዩኒኬሽን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ፋሲካ በላይ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ በመቀጠል ድርጅቱ አቶ መሃመድ ለተባሉ ግለሰብ የተሸጠ ሲሆን የኩባንያው እንቅስቃሴ ሲጠና ቆይቶ፣ 44 ሚ ብር የግብር እዳ እንዳለበት መታወቁን ይህንንም እዳ ግለሰቡ እንዲከፍሉ የሚጠይቅ ደብዳቤ በ2005 ዓ.ም ከባለስልጣኑ መ/ቤት እንደተፃፈላቸው ምክትል ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ ግለሰቡ “ኩባንያውን ስገዛው ይሄ ሁሉ እዳ እንዳለበት አላውቅም’ የሚል ምክንያት አቅርበዋል” ያሉት አቶ ፋሲካ፤ አንድ ኩባንያ በሽያጭ ሲዘዋወር ክሊራንስ ሳይወጣበት ስለማይዘዋወር የሰውየው ምክንያት ተቀባይነት ያለው አልነበረም ብለዋል – አቶ ፋሲካ፡፡ በኋላ ግን ኩባንያውን የገዙት ግለሰብ ወደ ባለስልጣኑ በመቅረብ፤ “ያለበትን እዳ ቅድሚያ 25 በመቶ ከፍዬ ቀሪውን ቀስ በቀስ እከፍላለሁ” እያሉ ሲያዘናጉ ቢቆዩም፣ ኩባንያው ግን እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ማምረት አለማቆሙን ባለስልጣኑ ደርሶበታል ብለዋል ም/ዳይሬክተሩ፡፡ ኩባንያው ክስ ያልተመሰረተበት ጉዳዩ ውስብስብ በመሆኑ ነው ያሉት አቶ ፋሲካ፤ በአሁኑ ወቅት የግብሩ ዕዳ በከፍተኛ ምርመራ ላይ መሆኑን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡የሪል ውሃ ማምረቻ ድርጅት ከ190 በላይ ሠራተኞች ያሉት ሲሆን ያለፉትን ሁለት ወራት ደመወዝ ያልተከፈላቸው መሆኑንና የሪል ውሃ ማምረቻው የሚገኝበት የቡራዩ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ፅ/ቤትም ለዓመታት ከሰራተኞቹ ደመወዝ የሚቆረጠው የስራ ግብር አልደረሰኝም ማለቱን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዘግቧል፡፡

የመንገድ ላይ ንብረቶች ውድመት ተባብሷል

     በግጭት ምክንያት የሚደርሰው የመንገድ ንብረቶች ውድመት እየተባባሰ መምጣቱን በአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን የመንገድ መብት ጥበቃና አስተዳደር ገለፀ፡፡
አስተዳደሩ ያለፈው ዓመት የስራ አፈፃፀሙን አስመልክቶ ከትላንት በስቲያ በሰጠው መግለጫ በበጀት ዓመቱ በ569 የመንገድ ንብረት ላይ አደጋዎች ደርሰው ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን የጠቆመ ሲሆን ከነዚህም አደጋዎች ውስጥ 244 ያህሉ አደጋዎች በቀለበት መንገድ ላይ መከሰታቸውንና የንብረቶቹ ውድመት በገንዘብ ሲተመን፣ ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነም የአስተዳደሩ ንዑስ የስራ ሂደት መሪ አቶ አስመላሽ ኪዳነማርያም ተናግረዋል፡፡
ቀሪዎቹ 325 አደጋዎች በሌሎች ዋና ዋና መንገዶች ላይ የተከሰቱ ሲሆን ግጭቶች ያደረሱት ጉዳት በገንዘብ ሲተመን ከ3.6 ሚሊዮን ብር በላይ መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል፡፡
በአብዛኛው ለጉዳት የሚዳረጉት የመንገድ ላይ ንብረቶች የመንገድ ዳር መብራቶች፣ የእግረኛ  መከላከያ አጥሮች፣ የመንገድ ማካፈያ፣ መከላከያ ግንብና የትራፊክ ምልክቶች ሲሆኑ በግጭት ምክንያት ከሚደርስባቸው ጉዳትና ውድመት ባሻገር በህገ ወጥ ግለሰቦችም ስርቆት እንደሚፈፀምባቸው ተገልጿል፡፡ በበጀት ዓመቱ በግጭትና በስርቆት ምክንያት በመንገድ አካላቶች ላይ ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳት መድረሱንም አቶ አስመላሽ አብራርተዋል፡፡
እንደ አቶ አስመላሽ ገለፃ፤ ባለስልጣኑ በግጭት ጉዳት የሚደርስባቸውን ንብረቶች በክትትል ካሳ ከማስከፈልም በተጨማሪ በመንገድ ላይ በሚያጋጥሙ ህገ-ወጥ ተግባራት ላይ የቁጥጥርና የክትትል ስራ የሚያከናውን ሲሆን በዚህም ክትትልና ቁጥጥር በዋና መንገዶች ላይ የግንባታ መስሪያዎች ያከማቹ 105 ግለሰቦች ላይ የገንዘብ መቀጫ ጥሏል፡፡
የመንገድ ላይ ንግድ፤ በግንባታ ስም እግረኛ መንገድን ማጠር፣ ከባድ መኪናን ለረጅም ጊዜ አቁሞ መጥፋት፣ ህገወጥ ማስታወቂያዎችን መለጠፍ፣ ማንጠልጠልና መትከል፣ በባለስልጣኑ ከፍተኛ ቁጥጥር የሚደረግባቸው ሲሆን እነዚህን ህገ ወጥ ድርጊቶችን ባከናወኑ አካላት ላይ እርምጃ መውሰዱንም ኃላፊው አብራርተዋል፡፡
ህብረተሰቡ የመንገድ ላይ ንብረቶችን እንደራሱ ንብረት እንዲጠብቅና ህገ-ወጦችን እንዲጠቁም ባለስልጣኑ የግንዛቤ ስራዎችን የሚራ ሲሆን በህገ-ወጦች የሚፈፀሙ ጥፋቶችን እንዲጠቆም 917 ነፃ የስልክ መስመርን ማስተዋወቁንም ገልፀዋል፡፡
“ምንም እንኳ ባለስልጣኑ በመንገድ አካላት ላይ የደረሱ ውድመቶችን ካሳ ሙሉ በሙሉ ማስከፈል ቢችልም የግጭቱ መጠን ግን ከ2006 የበጀት ዓመት ጨምሯል ያሉት ኃላፊው፤ በ2007 የደረሱት የመንገድ ንብረት አደጋዎች ቀደም ካለው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ126 አደጋዎች ብልጫ ማሳየቱን ተናግረዋል፡፡
ባለስልጣኑ በ2008 የበጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ለመከወን የዓምናውን ልምድ መነሻ በማድረግ ቀመር ማውጣቱንም ኃላፊው ገልፀዋል፡፡

መስከረም ፯ (ሳባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የቀድሞው የህወሃት መስራችና በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ አባል የሆኑት ዶ/ር አረጋዊ በርሄ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ፣ ህወሃት ኢህአዴግ በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ ተዳክሞ የሚገኝበት ወቅት በመሆኑ፣ ከድርጅቱ የለቀቁ የቀድሞ አባሎቹን በማነጋገር ወደ ድርጅታቸው እንዲመለሱ ለማድረግ እየጣረ መሆኑን ገልጸዋል። ህወሃት/ኢህአዴግ በራሱ የውስጥ ችግር …

መስከረም ፯ (ሳባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ ውስጥ በንግድ እንቅስቃሴያቸው ከሚታወቁት አካባቢዎች መካከል አንዱ በሆነው ካዛንችስ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ የንግድ ቤቶች በብዛት የፈረሱ ሲሆን፣ መኖሪያ ቤቶችን ለማፍረስ እንቅስቃሴ በመጀመሩ ነዋሪዎች ስጋት ገብቷቸዋል። የመንግስት ቤቶችን ተከራይተው ይሰሩ የነበሩ የንግድ ድርጅቶች በከተማዋ ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ቦታዎች እንዲሰማሩ ቢደረግም፣ የግል የንግድ ቤት የነበራቸው …

መስከረም ፯ (ሳባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከያዝነው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል የተባለው ሁለተኛው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የወጭ ንግዱን ከ3 ወደ 12 ቢሊየን ዶላር ለማድረስ መታቀዱ አሁን ሀገሪቱ ባለችበት ተጨባጭ ሁኔታ እጅግ የተጋነነና ተግባራዊ ሊሆን የማይችል ነው ሲሉ ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ በተካሄደ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ያተኮረ ስብሰባ ላይ የተሳተፉ አንድ የኢኮኖሚ ባለሙያ አስተያየታቸውን …

መስከረም ፯ (ሳባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የዋጋ ቁጥጥር ውሳኔው አንዳንድ ት/ቤቶች አደናግጦአቸዋል፡፡ መመሪያው ፍትሐዊነት ጎድሎታል ያለውን የግል ትምህርት ቤቶች የክፍያ ሁኔታ ሰርኣት የሚያሲዝ ነው ቢባልም ፣ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ቅሬታቸውን እየገለጹ ነው። አዲሱ መመሪያ ከስርኣተ ትምህርት ውጪ ልዩ ልዩ የትምህርት ኣይነቶችን ማስተማርና ለዚህም ክፍያ መጠየቅ ይከለክላል፡፡ ክፍያ ሲጠየቅ ለ10 ወራት ብቻ መሆኑን፣ …

መስከረም ፯ (ሳባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ዓመት በኩዌት ሱላቢካት ከተማ ውስጥ የአሰሪዋን ልጅ የ19 ዓመቷን ወጣት ሲሃም ማህሙድ በስለት በመግደል ወንጀል ተከሳ የነበረችው የ22 ዓመቷ ኢትዮጵያዊት ወጣት ራቢያ ማህሙድ ላይ የተላለፈው የሞት ፍርድ ውሳኔ መፅናቱን የአገሪቱ ፍርድ ቤት አስታውቋል። ግድያውን ለመፈጸም ያበቃት ሟቿ መኝታ ክፍልዋ በተደጋጋሚ ጊዜ በመምጣት በር በመዝጋት ጥቃት …

መስከረም ፯ (ሳባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኮንጎ ብራዛቪል አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው በመላው የአፍሪካዊያን ጫወታ ላይ ኢትዮጵያዊያን ሯጮች ድል እየቀናቸው ነው። በ5 ሺ ሜትር የወንዶች የሩጫ ውድድር ጌትነት ሞላ የወርቅ ሜዳሊያ ሲያገኝ፣ ርቀቱን በ 13 ደቂቃ 21 ሰከንድ 88 ማይክሮ ሰከንድ ጨርሷል። ልዑልሲ ገብረስላሴ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል። በ1 ሺ500 ሜትር …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ «ደሚህት»ተብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ከተዋጊዎቻቸዉ ጋር ከጥቂት ቀናት በፊት ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋአል።

መስከረም ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መስከረም 16፣ 2008 ዓም በደቡብ ክልል በጌዲዮ ዞን ወናጎ ከተማ ከንግድ ቤት ጋር በተያያዘ የተፈጠረው ውዝግብ አድጎ ወደ ብሄረሰቦች ግጭት በማምራቱ በርካታ ሰዎች ጉዳት ሲደርስባቸው፣ የተለያዩ የንግድ ቤቶችም ተዘርፈዋል። የከተማው ባለስልጣኖች ሆን ብለው ቀስቅሰውታል በተባለው በዚህ ግጭት፣ የአንድ ብሄረሰብ አባላት ነን የሚሉ ሰዎች፣ የሌላ አካባቢ ብሄረሰቦች …

መስከረም ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተንከባካቢ ድርጅት፣ ሲፒጄ የምስራቅ አፍሪካ ተወካይ የሆኑት ቶም ሮድስ፣ የዞን 9 ጸሃፊዎች የዚህን አመት የአለማቀፍ የፕሬስ ነጻነት ሽልማት ማሸነፋቸውን ተከትሎ ለኢሳት እንደተናገሩት፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ሽልማት የሚገባቸው በርካታ ጋዜጠኞች አሉ ሲሉ ጋዜጠኞች ለፕሬስ ነጻነት እየከፈሉ ያለውን መስዋትነት አወድሰዋል። የዞን ዘጠኝ ጸሃፊዎችን ለመሸለም የፈለግነው በኢትዮጵያ …

መስከረም ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፊታችን መስከረም 24 ቀን በኢህአዴግ መቶ በመቶ የተያዘው ፓርላማ ስራ ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የአቶ ሃይለማርያም የጠ/ሚኒስትርነት ሹመት ካጸደቀ በሃላ በጠ/ሚኒስትሩ አቅራቢነት የሚካሄደው የካቢኔ ሹም ር አዲስ ነገር ይዞ አይመጣም ተብሎአል። ለግንባሩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ለአዲስአበባው ዘጋቢያችን እንደተናገሩት ግንባሩ በሙስናና በመልካም አስተዳደር ችግሮች በተጨማለቁ የካቢኔ አባላት …

መስከረም ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ድርጅትን እንዲያስተዳደር ለሁለት አመታት 21 ሚሊዮን 700 ሺ ዶላር ወይም ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ የተከፈለው ፓወር ግሪድ ይህ ነው የሚባል ስራ ሳያከናውን ተሰናብቷል። በአገሪቱ ውስጥ የሚታየው የመብራት መጥፋት ሊሻሻል ካለመቻሉ ጋር ተያይዞ፣ ቀድሞውንም ይህን ያክል ገንዘብ ማውጣት ለምን አስፈለገ የሚል ጥያቄ አስነስቷል። ስራ …

በመሀል አዲስ አበባ ለዘመናት ታጥረው በተቀመጡና ግንባታ ባልተካሄደባቸው ቦታዎች ላይ ጠበቅ ያለ ዕርምጃ እንደሚወስድ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሀል አዲስ አበባን በድጋሚ መገንባት ያስፈልጋል በማለት ነዋሪዎችን ማስነሳቱ ይታወሳል፡፡ አስተዳደሩ በርካታ ኪስ ቦታዎችን ለባለሀብቶች ቢሰጥም፣ ባለሀብቶቹ ግንባታ ከማካሄድ ይልቅ አጥረው የያዟቸው ቦታዎች በርካታ ናቸው፡፡ 

እነዚህ ሕግን ያልተከተሉ አሠራሮች በነዋሪዎች ላይ ቅሬታ እያሳደሩ መሆኑ በተገኙ መድረኮች እየተገለጸ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የ2007 ዓ.ም. የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ካካሄደ በኋላ፣ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ አሠራሩን ማጥበቅ እንደሚያስፈልገውና የወጡ ሕጐችን በብቃት ማስፈጸም እንደሚገባ መግባባት ላይ መድረሱን አስታውቋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኃየሎም ጣውዬ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ለመልሶ ማልማት ፕሮጀክቶች ተይዘው ወደ ግንባታ ያልተገባባቸው ቦታዎች ያለባቸውን ችግር በተቀናጀ መንገድ ለመፍታት በዓመቱ ወደ ሥራ ለመግባት ታቅዷል፡፡ በዚህ መስክ ያለውን ችግር አቶ ኃየሎም ሲያስረዱ፣ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ አስፈላጊውን ሥራ ቀደም ብሎ ማጠናቀቅ ቢችልም ለተወሰኑ ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት የማቅረብ ችግር አጋጥሟል፡፡ ‹‹ከዚህ በተጨማሪም ሙሉ በሙሉ ቦታው እስኪፀዳም ግንባታ በመጀመር በኩል መጓተት አለ፡፡ ይህንን ችግር ለመፍታት ከመሠረተ ልማት ተቋማት ጋር በጋራ መሥራት ይኖርብናል፡፡ መንግሥታዊ ተቋማትም በተሰጣቸው ቦታ ላይ ተነሺዎችን በማይጐዳ ሁኔታ ግንባታ እንዲካሄዱ እናደርጋለን፤›› ብለዋል፡፡ 

በርካታ አልሚዎች የወሰዷቸውን ቦታዎች አጥረው ማስቀመጣቸውን በተመለከተም፣ ‹‹በዚህ በኩል ያሉ ችግሮችን በመለየት ውል እንዳይራዘም በማድረግ መሬቱን ወደ መሬት ባንክ የማስገባት ሥራ ይሠራል፤›› በማለት አቶ ኃየሎም ተናግረዋል፡፡ መሥሪያ ቤታቸው ከወትሮው በተለየ ዘንድሮ ጠንካራ ዕርምጃዎችን እንደሚወስድ አስገንዝበዋል፡፡ 

በመልሶ ማልማት ሥራ ከተያዙት አንዱ የሸራተን አዲስ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ይገኝበታል፡፡ ለዚህ ቦታ በ2002 ዓ.ም. ነዋሪውን የማንሳት ሥራ ቢጠናቀቅም በዚህ ቦታ ላይ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ጋራዥ ባለመነሳቱ ብቻ ወደ ግንባታ ሳይገባ ቆይቷል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ተለዋጭ ቦታ የተሰጠው የራሱን ግንባታ ሳያካሂድ ከዚህ ቦታ ላይ የመነሳት ፍላጐት አላሳየም ተብሏል፡፡ ነገር ግን የአካባቢው ነዋሪዎች ቦታውን ከለቀቁ ከአምስት ዓመት በላይ ተቆጥሯል፡፡  

ከዚህ በተጨማሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማስፋፊያ፣ አሮጌው ቄራ ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት ማስፋፊያ፣ ተክለ ሃይማኖት መልሶ ማልማት፣ ሸበሌ ሆቴል ጀርባ መልሶ ማልማት ቦታዎች ይገኛሉ፡፡

እነዚህና ሌሎች በሒደት ላይ ካሉ የመልሶ ማልማት ቦታዎች ላይ ነዋሪዎች እንዲነሱ ቢደረግም፣ የተወሰኑ መኖሪያ ቤቶችንና መንግሥታዊ ተቋማትን ማንሳት ባለመቻሉ ቦታዎቹ ታጥረው ለዓመታት እንዲቀመጡ ምክንያት ሆኗል፡፡ ይህም የነዋሪዎችን ኑሮ አስቸጋሪ ከማድረጉም በላይ በተነሱበት ምክንያት ላይም ጥያቄ እያነሱ እንደሚገኝ እየተገለጸ ነው፡፡ አቶ ኃየሎም እንዳሉት በአሁኑ ወቅት ከመሠረተ ልማት ድርጅቶች ከኤሌክትሪክ፣ ከውኃ፣ ከቤቶች ልማት ጋር በተጠናከረ ሁኔታ በጋራ በመሥራት መሬቱን ነፃ በማድረግ ወደ ልማት ለማስገባት እየተሠራ ነው፡፡

‹‹አስቸጋሪ ሁኔታ እንኳ ቢፈጠር ግንባታውን ከሥር ከሥር ለማካሄድ ዕቅድ ተይዟል፤›› በማለት አቶ ኃየሎም የዘንድሮን ዕቅድ አስረድተዋል፡፡

ከንቲባ ድሪባ ኩማ በቅርቡ በሰጡት መግለጫ፣ 360 ሔክታር መሬት በመልሶ ማልማት ፕሮግራም ለማልማት ታቅዷል፡፡ ይህ ልማት የሚካሄደው እንደ አዲስ ሲሆን፣ ለቦታው ለቤቶች ልማት፣ ለቢዝነስና ለባለ ኮከብ ሆቴል የሚውል ነው፡፡  በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ90 ባለሀብቶች የተሰጠ መሬት ግንባታ ያልተካሄደበት በመሆኑ መናጠቁን ገልጸዋል፡፡

ከንቲባው እንዳሉት፣ በተካሄደው ግምገማ በአዲስ አበባ ከተማ መሬት ወስደው ግንባታ ያላካሄዱ አልሚዎች ከፍተኛ አቅም ያላቸው ናቸው፡፡ እነዚህ አልሚዎች ለምን ግንባታ እንዳላካሄዱ በሚመረመርበት ወቅት የከተማው አስተዳደር ችግር አንዱ ምክንያት ሆኖ ተገኝቷል፡፡ 

በዚህ ምክንያት አስተዳደሩ ያለበትን ችግር በመቅረፍ በዚህ ዓመት ወደ ግንባታ እንዲገባ ግፊት እንደሚደረግ፣ አልሚዎቹ ወደ ግንባታ የማይገቡ ከሆነ ግን ዕርምጃ ይወስዳል በማለት ከንቲባው አስረድተዋል፡፡ 

 

መስከረም ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢህአዴግ የቀድሞው የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ( ትህዴን) ሊቀመንበር አቶ ሞላ አስጎደም ለ14 ዓመታት የነበሩበትን ድርጅት ከድተው ለኢህአዴግ ባለስልጣናት እጃውን መስጠታቸውን ተከትሎ ገዢው ፓርቲ እየሰራ ያለው የቅስቀሳ ስራ በህዝብ ዘንድ የተለያዩ አስተያየቶችን እያስተናገደ ነው። የመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ትህዴን የአርበኞች ግንቦት7 አንድ የጦር ክፍል እንደሆነ አድርገው ማቅረባቸው፣ …

መስከረም ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሙስሊም የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ከሆኑት መካካል ኡስታዝ ያሲን ኑሩ፣ ሳቢር ይርጉ፣ አቡበከር ዓለሙ እና ገጣሚው ሙኒር ሁሴን ከእስር መለቀቃቸውን አስመልክቶ ድምፃችን ይሰማ ባወጣው መግለጫ፣ ሁሉም እስረኞች ካለምንም ቅድመ ሁኔታዎች እስካልተፈቱ ድረስ ትግላቸው እንደሚቀጥሉ በአጽንኦት ገልጿል። ድምፃችን ይሰማ ፣ ” ተፈቺዎቹም ይሁኑ ታሳሪዎቹ ጀግኖቻችን ሃይማኖታችን በተደፈረበት፣ …

መስከረም ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በለቡ መዝናኛ ውስጥ ከሴት ጓደኛዋ ጋር በመዝናናት ላይ የነበረችው ሰሎሜ ጉልላት የተባለችው የ20 ዓመት ወጣት ”አንቺ ሰው የማታናግሪው ለምንድ ነው?” በሚል ተልካሻ ምክንያት መሳሪያ የታጠቀው የፌደራል ፓሊስ አባል ተኩሶ ገድሏታል። ታጣቂው በወቅቱ እራሱንም ለማጥፋት ጭንቅላቱ አካባቢ ላይ ያቆሰለ ሲሆን፣ ሳይሞት በሕይወት መትረፉንና በሕክምና ላይ እንዳለ ለማወቅ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ የወንጀል ምድብ ችሎት በብርሃኑ ተክለ ያሬድ መዝገብ በተከሰሱ አራት የሰማያዊ አመራር አባላት ላይ ብይን ለመስጠት ዛሬ ቢሰየምም ለውሳኔው ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ።

በፍኖተ-ዴሞክራሲ ሬዲዮ ለቀረበው ውንጀላ የተሰጠ አጸፋዊ መልስ ሠሞኑን የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ንብረት የሆነው «ፍኖተ-ዴሞክራሲ» በመባል የሚታወቀው የሳተላይት ሬዲዮ ጣቢያ በዐማራው ነገድ ተወላጆች ላይ የጅምላ ክስ አቅርቧል። ክሱ «በአማራ ሕዝብ ስም ሌሎችን መዝለፍ የሚወገዝ ነው» በሚል ርዕስ ያዘጋጀውንመግለጫ ነሐሴ ፳፪ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. በሬዲዮ አስተላልፏል[1]፤ በጽሑፍ ደግሞ በተባባሪ ድረ-ገፆች «አሲምባ[2]» እና «ደብተራው[3]»አሠራጭቷል። ከሁሉም የሚያሣዝነው […]

ኢትዮጵያ ውስጥ እያደገ የመጣው የሰብዓዊ ዕርዳታ ፍላጎት ከሚሰጠው ምላሽ ጋር ሊጣጣም እንዳልቻለ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ – ኦቻ የአዲስ አበባ ፅሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡

(ሪፖርተር፤ ነአምን አሸናፊ፤ መስከረም ፪ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) የግብጽ ኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፖፕ እና የመንበረ ማርቆስ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎድሮስ ካልዕ፣ በመስቀል ደመራ በዓል አከባበር ላይ ለመታደም እና የአራት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ፣ መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም. ከቤተ ክርስቲያኒቱ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጋር በመኾን አዲስ አበባ ይገባሉ፡፡ ፓትርያርክ አቡነ ቴዎድሮስ አራት ቀናት …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

መስከረም ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን የባለስልጣናትን ሐብት ምዝገባ ለሕዝብ ይፋ ለማድረግ እንደተሳነው የኮምሽኑ ምንጮች አጋለጡ፡፡ ለጠ/ሚኒስትሩ ተጠሪ የሆኑትን የኮምሽኑ ኮምሽነር ዓሊ ሱሌይማን ትዕዛዝ ተቀብለው ብቻ የሚያስሩና የሚፈቱ በመሆናቸው በአዋጁ መሰረት ለህዝብ ይፋ መደረግ የነበረበት የባለለስጣናት የሐብት ምዝገባ በወቅቱ ለማከናወን ድፍረት ማጣታቸው ታውቆአል፡፡ የሐብት ምዝገባ ሥራን በኢንፎርሜሽን …

የኢትዮጵያ፤ የሱዳንና የግብፅ የጋራ ኮሚቴ ባለፈዉ መጋቢት ጥናቱን እንዲያደርጉ የመረጣቸዉ ሁለቱ ኩባንዮች የጥናት ዉጤታቸዉን ባለፈዉ ነሐሴ ማብቂያ ለኮሚቴዉ ማቅረብ ነበረባቸዉ

”ከሚያዚያ ወር ጀምሮ የ7ዓመት ግምገማ እያደረግን ቆይተናል። በዚህም ሞላ በፖለቲካ አመራር ድርጅቱን አዳክሞታል የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰናል። ሰራዊቱ የአመራር ለውጥ በሚፈልግበት ጊዜ ላይ በተካሄደው በዚሁ ግምገማ ሞላ ከፍተኛ ተቀውሞ ከድርጅቱ አመራሮችና አባላት ደርሶበታል። ” ”ይዞ የወጣው ታጋይ ቁጥሩ ተጋኗል። ያም ቢሆን ለስራ ተብለው(የኪነት ቡድኑ ለበዓል) የተታለለ ነው። በተቻለን መጠን አብዛኛውን መልሰናል። የተዋጋው ከእኛው ጋር ነው። […]

መስከረም ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፋይናንሻል ታይምስ እንደዘገበው ባለፈው ታህሳስ ወር 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዳላር ከግል ባንኮች የተበደረው መንግስት፣ ተጨማሪ በድር ለመውሰድ እንቅስቃሴ ጀምሯል። በሚቀጥለው ሳምንት የመንግስት ባለስልጣኖች ከአበዳሪ ተቋማት መሪዎች ጋር ለንደን ውስጥ ይገናኛሉ። ላዛርድ የተባለ የመንግስት የገንዘብ አማካሪ ድርጅት ባለስልጣኖቹን ከጀርመኑ ዶች ባንክና ከአሜሪካው ጄፒ ሞርጋን ሃላፊዎች ጋር እንደሚያገናኛው የዘገበው …

መስከረም ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቀድሞው የህወሃት አባልና በሁዋላም የአፋር ፓርቲ መስርተው የክልሉ ፕሬዚዳንት ሆነው ለ20 አመታት በስልጣን ላይ የነበሩት አቶ እስማኤል አሊ ሴሮ ከስልጣናቸው ከተነሱ በሁዋላ፣ የአብዴፓ ሊቀመንበር ሆነው በተመረጡት በአቶ ጠሃ ሙሃመድ ቡድንና በአቶ አሊ ሴሮ ቡድን መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል። የውዝግቡ መነሻ አቶ ጠፋ የክልሉ ፕሬዚዳንት ሊሆኑ …

መስከረም ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በንግድ ስራ የምትደዳረዋ ካሚል ሙሃመድ ታውኒ ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት አላት በሚል በኬንያ ልዩ ፖሊስ ተይዛ ለሶማሊና ለኢትዮጵያ መንግስታት ተላልፋ መሰጠቷን ተከትሎ ሰቆቃ እንደተፈጸመባት ተናግራለች። ቃሏን ለፍርድ ቤት ስታሰማ እንባዋ ያቋርጣት እንደነበር ቢቢሲ ዘግቧል። ወ/ት ትዌኒ የህክምናዋን ወጪ ለመሸፈን የኬንያ መንግስት የገንዘብ ካሳ እንዲሰጣት ፍርድ ቤትን ጠይቃለች። ፍርድ …