ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ

በዚህ ዓመት በኢትዮጵያ ሙስናን አስመልክቶ ይሀ ለሰባተኛ ጊዜ ያቀረብኩት ትችት በማዕድኑ ዘርፍ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ በሙስና ላይ ያቀረብኳቸውን ሌሎችን ትችቶች “Al Mariam’s Commentaries” የሚለውን ድረ ገጽ በማየት ግንዛቤ መውሰድ ይቻላል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

በኤሌክትሪክ መጥፋት ምክንያት የአገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ሥራ በተደጋጋሚ እንደሚስተጓጓልና በዕለት ተዕለት ኑሮም በኤሌክትሪክ ማብሰያዎች መጠቀም አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱን ዶቼቬለ የጠየቃቸው አስተያየት ሰጭዎች ተናግረዋል ።

ዉጭ የሚኖሩ የሶማሊያ ተወላጆች ወደሀገራቸዉ ከፍተኛዉን የዉጭ ምንዛሪ እንደሚልኩ ይነገርላቸዋል። ሰሞኑን ግን ታዋቂዉ የብሪታንያ ባንክ ባርክሌ ከሶማሊያ ጋ መስራት አልፈልግም በማለቱ የሶማሊያዉያን ገንዘብ መለዋወጫ ባንኮች ችግር ገጥሟቸዋል።

የኤሌክትሪክ መጥፋት ምክንያት የአገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ሥራ በተደጋጋሚ እንደሚስተጓጓልና በዕለት ተዕለት ኑሮም በኤሌክትሪክ ማብሰያዎች መጠቀም አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱን ዶቼቬለ የጠየቃቸው አስተያየት ሰጭዎች ተናግረዋል ።

የሳውዲ መንግሥት ለ ሁለተኛ ጊዜ የሰጠው የምህረት አዋጅ ቀነ ገደብ ካበቃበት ካለፈው እሁድ አንስቶ በተካሄደ የፖሊስ ክትትል ሁለት ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን ሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አስታወቁ ። እነዚሁ ነዋሪዎች እንዳሉት ባለፉት ሶስት ቀናት ከሞቱት ሌላ በርካታ ኢትዮጵያውያን ታፍሰዋል ።

የዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ መንግሥት እና አማፅያኑ «ኤም 23» ቡድን በምሥራቃዊ የሀገሪቱ አካባቢ የሚያካሂዱትን ውጊያ ለማብቃት በካምፓላ ዩጋንዳ ከብዙ ወራት ወዲህ የጀመሩት ድርድር ካለውጤት በተበተነበት ባሁኑ ጊዜ የኮንጎ ጦር በአማፅያኑ ላይ ሙሉ ድል ተቀዳጅቶዋል።

ባለፈዉ ሰሞን የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል ኮርፕሬሽን ከአንድ የዉጭ ኩባንያ ጋር ከከርሰ ምድር እንፋሎት ኃይል ለማመንጨት እና ከእንፋሎት የሚገኝን የኤሌትሪክ ኃይል ጥቅም ላይ ለማዋል ተስማምቷል። የመሬት ዉስጥ የእንፋሎት ኃይል ምንጭ ምንድን ነዉ?

ዳንኤልክብረት
ተስፋየ ገብረ አብ ‹የስደተኛው ማስተዋሻ› የተሰኘ መጽሐፍ ማውጣቱንና ባነበው መልካም እንደሆነ ገልጦ አንድ ወዳጄ ‹ስስ ቅጅውን› ከ ገረ አሜሪካ ላከልኝ፡፡ ከዚህ በፊት ሌሎች መጻሕፍቱን አንብቤያቸዋለሁ፤ በአጻጻፍ ችሎታው የምደሰተውን ያህል እንደ አበሻ መድኃኒት ነገሩን ሁሉ እርሱ ብቻ የሚያውቀው ምስጢር ስለሚያደርገው፤ በአንዳንድ ጉዳዮችም ሆን ብሎም ሊያናጋቸው የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ እሴቶች ያሉ ስለሚመስለኝ፤ ተስፋዬ ለምን እንደዚህ ይጽፋል? እያልኩ የምጠይቃቸው ነገሮች ነበሩ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

Normal
0

false
false
false

MicrosoftInternetExplorer4

/* Style Definitions */
table.MsoNormalTable
{mso-style-name:”Table Normal”;
mso-tstyle-rowband-size:0;
mso-tstyle-colband-size:0;
mso-style-noshow:yes;
mso-style-parent:””;
mso-padding-alt:0cm 5.4pt 0cm 5.4pt;
mso-para-margin:0cm;
mso-para-margin-bottom:.0001pt;
mso-pagination:widow-orphan;
font-size:10.0pt;
font-family:”Times New Roman”;
mso-fareast-font-family:”Times New Roman”;
mso-ansi-language:#0400;
mso-fareast-language:#0400;
mso-bidi-language:#0400;}

(ፕ/መስፍንወልደ ማርያም)

 

ወያኔና የነፖሊቲካ አጋሮቹ የሚያደርጉትን ለእነሱ የሚመች አከፋፈል ትተን አበሻን ለሁለት እንክፈለው፤ ሆድ ያለውና ሆድ የሌለው፤ ወይም የሚበላና የማይበላ፤ ዛሬ የምናገረው ሆድ ስላለው ወይም ስለሚበላው አበሻ ነው፤ አታውቁት እንደሆነ ተዋወቁት፤ በአጠቃላይ ስንመለከተው ግን የአበሻ ፍቅርም ሆነ ጠብ ለሆድ ነው፤ አበሻን የሚያጣላው፣ የሚያነታርከው፣ የሚያቧጭቀው የሆድ ነገር ነው፤ ለመብላት ነው፤ አንዳንዴም ሎሌውን ለማብላት ነው፤ ግብር ለማግባት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥቅምት ፳፮(ሃያ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ገዢው ፓርቲ መጪውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ለማክበር በጅጅጋ ከተማ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል። ለገዢው ፓርቲ ታማኞች ናቸው የተባሉና ” በተለምዶ ልማታዊ አርቲስትና ጋዜጠኞች እየተባሉ የሚጠሩ ታዋቂ ሰዎች አካባቢውን በመጎብኘት አድናቆታቸውን ሰጥተዋል። ኢሳት በክልሉ ያለውን ሁኔታ ከዘገበ በሁዋላ የተለያዩ ነዋሪዎች እና ጎብኝዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ክልሉን በቅርቡ አይታ …

ጥቅምት ፳፮(ሃያ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከምሽቱ 7 አካባቢ አንድ የውጭ አገር ዜጋ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ጀርባው አካባቢ በጩቤ ተወግቶ መገደሉን ለማወቅ ተችሎአል። ግለሰቡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰራተኛ ሳይሆን አይቀርም። ግድያውን ማን እንደፈጸመውና ለምን እንደተፈጸመ የታወቀ ነገር የለም። የክልሉን ፖሊስ ለማነጋገር ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም። ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን የምናቀርብ መሆናችንን እንገልጻለን።

ጥቅምት ፳፮(ሃያ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጥቅምት 20 ቀን 2006 ዓ.ም በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቀረበባቸውን የስም ማጥፋት ክስ ፍ/ቤት ቀርበው ምላሽ ለመስጠት ወደ ሐዋሳ ያመሩት የኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ባልደረቦች ከደረሰባቸው የባጃጅ ተሸከርካሪ አደጋ ጋር በተያያዘ በተለይ ኤፍሬም በየነ ላይ የከፋ ጉዳት መድረሱን ተከትሎ በመዋጮ ህይወቱን ለማትረፍ እየተደረገ ያለው ጥረት እስካሁን ውጤቱ አመርቂ አለመሆኑን አንድ የዕርዳታ አሰባሳቢ …

ጥቅምት ፳፮(ሃያ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ህወሀት በውስጡ የተነሳበትን መከፋፈል ለማስቀረት በእነ አቶ ስብሀት ነጋ የሚመራው ቡድን የቀድሞ ታጋዮችን በማሰባሰብ ህወሀትን ለማዳን በሚረባረብበት ጊዜ፣ በአቶ ስየ አብርሀ እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የተጀመረው ዘመቻ ግን እንደቀጠለ መሆኑ ታውቋል። አቶ ስየ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴያቸው በእጅጉ የተገታ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ( ኢቲቪ) ” የነቀዙ ሀይሎች” በሚል በእርሳቸውና በአቶ …

ጥቅምት ፳፮(ሃያ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሱዳን፣ ኢትዮጵያ እና ግብጽ መካከል በካርቱም የተካሄደው የአንድ ቀን ስብሰባ ያለውጤት ተጠናቋል። በኢትዮጵያና ግብጽ መካከል ልዩነቶች የተፈጠሩ ሲሆን፣ ልዩነቶችን ለማጥበብ ስለሚወሰደው እርምጃም አልተስማሙም። ብዙ ክብደት ተሰጥቶት የነበረው ስብሰባ በአንድ ቀን መጠናቀቁ በሁለቱ አገራት መካካል ያለው ልዩነት እየሰፋ መሄዱን የሚያሳይ ነው ተብሎአል። ምንም እንኳ ከአንድ ወር በሁዋላ አገራቱ …

ጥቅምት ፳፮(ሃያ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከወራት በፊት በግብጽ የተቀሰቀሰን አመጽ ተከትሎ በወታደራዊ ሀይሉ ጣልቃ ገብነት ከስልጣን የተወገዱትና በእስር ላይ የሚገኙት መሀመድ ሙርሲ  በካይሮ ጉዳያቸውን እንዲያስችል በተሰየመው ፍርድ ቤት ቀርበው የግብጽ ፕሬዳንት መሆናቸውን ተናገሩ። ሙርሲ፦የተከሰሱበት መንገድ ህገወጥ መሆኑንና እርሳቸው የግብጽ ህጋዊ ፕሬዳንት ሆነው መቀጠል እንዳለባቸው ነው ለዳኞች የተናገሩት። እንደ ቢቢሲ  ሪፖርት ሙርሲና ሌሎች …

እንዴት ነሽ ኢትዮጵያ፡ ስላም ነው? እንደዘበት ትቼሽ ወጥቼ ከቀረሁ ያለፈው መስከረም ገብርኤል ሃያ ዓመት ሆነኝ። ከጠቅላላ ዕድሜዬ ከሲሶው በላይ መሆኑ ነው። ጊዜው እንዴት ይሮጣል? ያኔ ትቼሽ ስወጣ ወደኋላ እንዳላይ ብዬ ድንጋይ ወርውሬ መውጣቴን ስለምታውቂ ምነው ይህን ያህል ዘመን ጠፋህ የምትዪኝ አይመስለኝም። ምን ላድርግ። አይንሽ እያየ አይገፉ መገፋት አስገፋሽኝ። ዘር አስቆጠርሽብኝ። መገፋቴን ለምን እንደማለት በመገፋቴ ከንፈር […]

በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ አዲስ የካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ እየተገነባ ነው። የኢትዮጵያ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ ቅዱስ ቶማስ አኳይናስ አሁን ለጊዜው በካቶሊክ ካቴድራል ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ነው ያለው።

የነፃ ትምህርት እድል አግኝተው በመጡባት ጀርመን ሲኖሩ ከ27 ዓመት በላይ ሆኗቸዋል ። የግብርና ውጤቶችን የምግብ ይዘትና ጠባይ አጥንቶ ለምግብነት ማዘጋጀት የሚያስችል ትምህርት ነው ያጠኑት ። የተማሩትም በበርሊኖቹ አሌክሳንደር ሁምቦልትና የቴክኒክ ዩኒቨርስቲዎች ነው ። ዶክተር አየለ ጉግሳ ይባላሉ

(ተመስገን ደሳለኝ)
ገራችን መንግስታዊ አስተዳደር የ‹‹ቁማር ህግ››ን ችግር መፍቻ አድርጎ መጠቀም የ መረበትን ጊዜ ለማስላት ንጉሰ ነገስት ዳግማዊ ምንሊክ እንደ”ተበሉበት” ከሚነግረን የሽኩሹክታ ታሪካችን አንስቶ አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት… እያልን ለመቁጠር እንገደዳለን፡፡ ይሁንና ባለሙያ (በንባብ የደረ ) ቁማርተኛ ፖለቲከኛ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛበት ድንገቴ ክስተት የ1966ቱ አብዮት ዋዜማ ነው ቢባል ወደ እውነታው ይጠጋል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ እስካለፈዉ ሳምንት ድረስ ባደረገዉ ጉባኤዉ የተለያዩ ዉሳኔዎች አሳልፏል።የቤተ-ክርስቲያኒቱ መሪዎች እንዳስታወቁት ለአስራ-አንድ ቀናት የተደረገዉ ጉባኤ ያሳለፋቸዉ ዉሳኔዎች የቤተ-ክርስቲያኒቱን አሠራራር ለማሻሻል የሚጠቅሙ ናቸዉ።

SHARE:

በአዲስ አበባ ስኬታማ ሰላማዊ ተቃውሞዎችን በማድረግ ጉዞውን የጀመረው ሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ ክፍላተ ሃገራት ያሉ መዋቅሮቹነ በመገምገምና አደረጃጀታቸውን በማጠናከር ላይ ይገኛል፡፡በዚህም መሰረት ባለፈው እሁድ በ24/2/06 በሰሜን ሸዋ የሚገኙ ወረዳዎችን በደብረ ብርሃን ከተማ በመገኘት የገመገመ ሲሆን በእለቱም የፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ጌታነህ ባልቻ በቦታው በመገኘት ስለ ፓረቲው አጠቃላይ ሁኔታና ጉዞ ገለፃ በማድረግ ስኬታማ ውይይት ከአባላት ጋር አካሂደዋል፡፡
በተመሳሳይም ከዛሬ ማክሰኞ 26/2/2006 አ/ም ጀምሮ ለ3 ቀናት በአርባ ምንጭ በወላይታ በአዋሳና ሆሳእና ከተሞች ላይ ከአባላት ጋር ውይይት የሚደረግ ሲሆን በቀጣይ ቀናትም በሌሎች ከተሞች ላይ ውይይቱ የሚቀጥል መሆኑ ታውቋል፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከመላው ኢትዩጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) ለመዋሃድ በምክር ቤቱ በማስወሰን በጽህፈት ቤቱ አማካኝነት ለመኢአድ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱ ሁለቱ ፓርቲዎች ለመዋሃድ በሚያስችሏቸው ሂደቶች ዙሪያ ለመነጋገር ኮሚቴ አቋቁመዋል፡፡ ፓርቲዎቹ ለመዋሀድ ለመዋሀድ የሚበቁበትን ሃላፊነት በመውሰድ የኮሚቴው አካል የተደረጉት ፓለቲከኞች በመጀመሪያው ቀን የውይይት ስብሰባቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የውህደት ውይይቱን ለማድረግ መስማማታቸውም ሂደቱን በመግባባት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን […]

ወጣቱ የነፃነት ሰላማዊ ታጋይ ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ ዋለ የፃፈው ‹‹ያልተሄደበት መንገድ›› ገበያ ላይ ዋለ፡፡ አንዷለም አርአያ ክብር ነው፡፡ ምሳሌና አርአያ ብናደርገው የምንጠቀምበት ምርጥ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ በቅርበት ስለማውቀው ብቻ እራሴን እንደ ዕድለኛ እቆጥራለሁ፡፡ ማርቲን ሉተር ኪነግንና ማህተመ ጋንዲን አንስቶ አይጠግብም፡፡ ስለፍቅር ሲል ሁሉን አሳልፎ መስጠት የሚችል፤ ስለ ኢትዮጵያ የሚሰስተው የሌለው ውድ ወጣት ነው፡፡ ለአላማው በፅናት መቆምን […]

click here for pdf

በይምርሐነ ክርስቶስ ጣራ ላይ የሚገኘው የዳዊት ኮከብ
ባለፈው ሳምንት ተስፋዬ ገብረ አብ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ያነሣቸውን ነጥቦች ማየት ጀምረን ‹የሦስቱን ተክለ ሃይማኖቶች› ጉዳይ ለዛሬ አቆይተነው ነበር፡፡ እንቀጥል፡፡

1)        የሰባተኛው መክዘ ተክለ ሃይማኖት

ተስፋዬ የጠቀሳቸው የሰባተኛው መክዘ ተክለ ሃይማኖት የሉም፡፡ እስካሁንም እንደርሱ ፈጠራቸውን የሚናገሩ እንጂ ማስረጃ ያመጡ አልተገኙም፡፡ ይህንን ነገር መጀመሪያ ያነሣው የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ገድለ ተክለ ሃይማኖትም ስለ ጽላልሽ (ኢቲሳ) ተክለ ሃይማኖት እንጂ ስለ ሰባተኛው መክዘ ሌላ ተክለ ሃይማኖት አይናገርም፡፡ ገድለ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ልዩ ልዩ ቅጅዎች ቢገኙም ሁሉም ግን በተወለዱበት ቦታ፣ በተወለዱበት ዘመን፣ በወላጆቻቸው ስም፣ በሠሯቸው ሥራዎችና በገዳማቸው ላይ የሚተርኩት ታሪክ ተመሳሳይ ነው(Encyclopedia Aethiopica, Vol., IV,.P.833) በአንድ ወቅት ታላቁን የታሪክና የኢትዮጵያ ጥንታውያን መዛግብት ሊቅ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌን ስለዚህ ጉዳይ ስጠይቃቸው ‹አለኝ ያለ ማስረጃውን ያምጣ፣ የለም የምንለው ፈልገን ልናመጣ አንገደድም›› እንዳሉት አለን የሚሉት እስኪያመጡ ድረስ የምናውቀውን ይዘን እንቀጥላለን፡፡

2) መራ ተክለ ሃይማኖት የሚባል ንጉሥ ነበረ፡፡ እንደ ደብረ ሊባኖስ ዘሺምዛና(ኤርትራ) እና ደብረ ሐይቅ መዛግብት ከሆነ መራ ተክለ ሃይማኖት የዛግዌ ሥርወ መንግሥት መሥራች ንጉሥ እንጂ ‹ቄስ› አልነበረም፡፡ የዛግዌን ዘመን በተመለከተ የተጻፉ የዛግዌ ቅዱሳን ገድሎች(ፔሩሾ የጻፈውን የገድለ ላሊበላ መቅድም መመልከት) ይህንን አይነግሩንም፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን የዛግዌን ታሪክ ያጠኑት ሊቃውንት(ለምሳሌ E. A. Wallis Budge, A History of Ethiopia, London, 1928; Sergew Hable Sellassie, Ancient and Medieval Ethiopian History) መራ ተክለ ሃይማኖት ቄስ ነበረ አይሉንም፡፡ የላስታ ትውፊትም ይህን አይናገርም፡፡ በላስታ አድባራትና ገዳማት የሚሳሉት ቅዱሳን አራቱ ነገሥታት ናቸው (ቅዱስ ላሊበላ፣ ቅዱስ ሐርቤ(ገብረ ማርያም)፣ ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስና ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ)፡፡ ከእነዚህም ክህነትና ንግሥናን እንደያዘ የሚነገረው ይምርሐነ ክርስቶስ ነው፡፡ ተስፋዬ እንዲሆን የሚፈልገውን ብቻ ነው የነገረን፡፡ 

ስለዚህም በገድለ ተክለ ሃይማኖት የሦስት ሰዎች ገድል ተቀላቅሏል የሚለን ማስረጃ አልባ ሕልም ነው፡፡ 

ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተጻፈው በገድላቸው ብቻ አይደለም፡፡ በብዙ ጥንታውያን መዛግብትም ጭምር እንጂ፡፡ በገድለ አቡነ ኢየሱስ ሞአ(ወሎ)፣ በገድለ አቡነ ፊልጶስ፣ በገድለ አቡነ አኖሬዎስ(ባሌ)፣ በገድለ አቡነ እንድርያስ(ደቡብ ጎንደር) በገድለ አቡነ ፊልጶስ ዘደብረ ቢዘን (ኤርትራ፣ እንዲያውም በ ደብረ ቢዘኑ(ኤርትራ) ገድለ አቡነ ፊልጶስ ወአቡነ ዮሐንስ ላይ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት አልፎ የእርሳቸውን ደቀ መዛሙርት ዝርዝር በሚገባ ይነግረናል፡፡ C. Conti Rossini, Gadla Filipos e il Gadla Yohannes,1901, P.156)፣ በገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ(ሰሜን ሸዋ)፣ በገድለ አቡነ ቀውስጦስ፣ በገድለ አቡነ ዕንባቆም(ወለጋና ምዕራብ ሸዋ)፣ በገድለ አቡነ ተክለ ሐዋርያት(ምዕራብ ሸዋ)፣ በገድለ አቡነ ተክለ አልፋ(ምሥራቅ ጎጃም)፣ በገድለ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ(ትግራይ)፣ በገድለ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ(ኤርትራ)፣ በገድለ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ(ምዕራብ ሐረርጌ)፣ ተጽፎ ይገኛል፡፡ እነዚህ በተለያዩ ዘመናት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተጻፉ ገድሎች በደብረ ሊባኖስ በ12ኛው መክዘ መጨረሻና በ13ኛው መክዘ መጀመሪያ ላይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የሚባሉ አባት ተነሥተው እንደነበረ ታሪካቸውን በአጭርም ሆነ በስፋት ይነግሩናል፡፡ ከኢትዮጵያውያንም ውጭ በ16ና17ኛው መክዘ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩት እነ ኢማኑኤል አልሜዳና ፓድሮ ፓኤዝ ወደ ኢትዮጵያ በመጡ ጊዜ ያገኙትን ነገር መነሻ ስለ ደብረ አስቦው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጽፈዋል፡፡ ሌላ ተክለ ሃይማኖት ስለመኖሩ ግን ያነሡት ነገር የለም፡፡

በርግጥ አልሜዳ ተክለ ሃይማኖትን በሰባተኛው ወይም በስምንተኛው መክዘ የተነሡ ናቸው ብሎ ገምቷል፡፡ ወደዚህ ግምት የወሰደው የኢትዮጵያውያንን ገድላት አጻጻፍ ባለቁ ነበር፡፡ ኮንቲ ሮሲኒ ‹‹ወደ ኢትዮጵያ ታሪክ ጥናት ይበልጥ ራሴን ባስገባሁ ቁጥር ሀገራዊውን ትውፊት ማወቅ እንዳለብኝ ይበልጥ እየተረዳሁ መጥቻለሁ፡፡ ይህንን ሀገራዊ ትውፊት፣ ከሕዝቦችን ንቅናቄ ታሪክና ከተከታታይ መሪዎቹ ታሪክ ጋር(ምንም እንኳን አንዳንዴ አፈ ታሪክም ቢሆን) እያወቅን በመጣን ቁጥር ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ ርግጠኛ የሆነ ግንዛቤ ይኖረናል›› እንዳለው(C. Conti Rossini, “Note di agiografia etiopica (Abiya- Egzi, Arkaledes e Gabra Iyesus),” Rassegna di studi orientali, 17(1938), 409-10. ) የኢትዮጵያን ባህል ና ትውፊት ካላወቁ የሚፈጠረውን ስሕተት ነው አልሜዳ የፈጠረው፡፡ ለምሳሌ አልሜዳ እንደ አንድ ማሳያ ያነሣው ‹በገድለ ተክለ ሃይማኖት ውስጥ ስለ ሙስሊሞች አልተገለጠም› የሚል ነው፡፡ የመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ገድሎች ግን ከክርስትና ውጭ ያሉትን ሕዝቦች ‹ተንባላት› እያሉ ነው የሚጠሯቸው፡፡ ሙስሊም ወይም እስላም የሚለውን ስም በሚገባ የምናገኘው የክርስቲያን ሙስሊም ግንኙነት እየሻከረ በመጣባቸው የመካከለኛው ዘመን የመጨረሻዎቹ ዓመታትና ከግራኝ አሕመድ ጦርነት በኋላ ነው፡፡ በገድለ አኖሬዎስ፣ በገድለ አቡነ አሮን፣ በገድለ አቡነ በጸሎተ ሚካኤልና በገድለ አቡነ ፊልጶስም በተመሳሳይ ሁኔታ ነው የሚገኘው፡፡

አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ከፖለቲካ ጋር የማያያዝ ነገር በተስፋዬ አልተጀመረም፡፡ ሌሎች አካላትም ሲያራምዱት የኖሩና የሚራምዱትም ነገር ነው፡፡ በዚህ ረገድ ያልተጠኑ ሦስት ነገሮች አሉ፡፡ አንደኛው የሰሎሞናዊ መንግሥት ምለሳ (Restoration) የሚባለው ነገር፡፡ ሁለተኛው በዚህ ምለሳ ላይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ነበራቸው የሚባለው ሚና እና የታሪኩ ምጮች ናቸው፡፡

የንጉሥ ሐርቤ የዳዊት ኮከብ ያለበት ማኅተም

እንደ እውነቱ ከሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ በአኩስም ዘመን የነበሩ ነገሥታት ራሳቸውን ሰሎሞናውያን ብለው የጠሩበት መረጃ የለንም፡፡ ለኢትዮጵያ ነገሥታት ግን ራሳቸውን ከኢየሩሳሌምና ከቅድስት ሀገር ጋር ማያያዝ የተለመደ ነው፡፡ በዚህ ረገድም የዛግዌ ነገሥታት ሰሎሞናውያን የማይሆኑበት ምክንያትም የለም፡፡ እንዲያውም ለሰሎሞናዊነቱ ከኋለኞቹ ነገሥታት ይልቅ የዛግዌ ነገሥታት ይቀርባሉ፡፡በውቅር ቤተ ክርስቲያኖቻቸውም ሆነ በማኅተሞቻቸው ላይ የዳዊትን ኮከብ በብዛት እናየዋለን፡፡ ወደ ኢየሩሳሌም በመሄድም የዛግዌ ነገሥታት ይበልጣሉ፡፡ ቅዱስ ላሊበላም የሮሐን አብያተ ክርስቲያናት ሲያንጽ ኢየሩሳሌምን እያስታወሰ ነው፡፡ በኋላ ዘመን ‹ሰሎሞናውያን› ከተባት የይኩኖ አምላክ ዘሮች ነገሥታት ወገን እንድም ንጉሥ ኢየሩሳሌም ሄደ ተብሎ አልተጻፈለትም፣ አልተነገረለትምም፡፡ የዛግዌ ነገሥታትን ግን ወደ ኢየሩሳሌም በመሄድ የሚተካከላቸው የለም፡፡

የአኩስምን ነገሥታት (በተለይ ዐፄ ካሌብና ዐፄ ገብረ መስቀል በወሎ አካባቢ አያሌ አብያተ ክርስቲያናትን ተክለዋል፡፡ የዛግዌ ነገሥታትም (በደብረ ሊባኖስ ዘሺምዛና ወንጌል እንደ ተገለጠው) ለኤርትራና ትግራይ ገዳማት ርስት ሰጥተዋል፡፡ የሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት መላሽ የሚባለው ይኩኖ አምላክም ቢሆን በእናቱ የቡግና ተወላጅ ነው፡፡ ውትድርና ተቀጥሮ የኖረውም ቡግና ነው፡፡ የተማረውም ወሎ ሐይቅ እስጢፋኖስ ነው፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞአ ትውልዳቸው ቡግና ስለሆነ ነው ይኩኖ አምላክ ወደ ሐይቅ ለትምህርት የሄደው፡፡ እርሱ ሲነግሥም መጀመሪያ ያሳነጸው የወሎዋን ገነተ ማርያምን ነው፡፡ አጽሙም የሚገኘው በወሎዋ አትሮንሰ ማርያም ነው፡፡ ይኩኖ አምላክ በሸዋ ውስጥ ስሙ እንጂ ቅርሱ ያለ አይመስልም፡፡

ይኩኖ አምላክ ወደ ሸዋ የወረደው እርሱ ሸዬ ስለሆነ አይመስልም፡፡ የዛግዌ ነገሥታት የበረታ ኃይል ከሚገኝበት ከወሎ አካባቢ ለመሸሽና የደቡቡን ኃይል ለማሰባሰብ እንጂ፡፡ ኮንቲ ሮሲኒ ከኤርትራ አግኝቶ ባሳተመው እንድ ጥንታዊ የብራና ጽሑፍ ላይ  ‹‹(የይኩኖ አምላክ ሠራዊት) ሰባቱ ጉደም ናቸው፡፡ እነርሱም ወግዳ – መለዛይ፣ ዲንቢ – ዳባራይ፣ ሙገር – እንደ ዛቢ፣ ወጅ – እነጋሪ፣ ወረብ – እነካፌ፣ ጽላላሽ እነ ጋፌ እና ሙዋይ – አውዣዣይ ናቸው፡፡ የእነርሱም አለቃ መለዛይ ከንጉሡ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ፤ ተዋግቶም ጠላቶቹን ድል ነሣ›› ይላል (Taddesse Tamrat, Ethnic Interaction and Integration In Ethiopian History: The case of The Gafat, JES, Vol. XXI,1988, P. 125)

ይኩኖ አምላክ የዛግዌ ነገሥታትን ሊያሸንፍ የቻለው በዚያ ዘመን በጥበበ ዕድ አንድነት በፈጠሩት(ሰባት ጉዳም) ጋፋቶች ርዳታ ነው፡፡ ምንጊዜም የመሣሪያ ኃይል ያለው ያሸንፋልና፡፡ ይኩኖ አምላክ ወደ ሸዋ ባደረገው መስፋፋት ወደ ክርስትና ተመልሶ ከደጋው ሸዋ ክፍል ጋር የነበረውን ጠላትነት ያጠፋውን የዳሞትን መንግሥት ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ተጠቅሞበታል፡፡ ልክ በኋላ ዘመን ዐፄ ምኒሊክ የደቡቡን ኃይልና ዐቅም በመጠቀም ገንነው እንደወጡት ማለት ነው፡፡ ይኩኖ አምላክ ወደ ሸዋ በመምጣት ኃይሉን በማደራጀቱ ሸዬ ሆኖ ቀረ፡፡ ልክ በኋላ የሸዋ ነገሥታት ወደ ጎንደር ሄደው ጎንደሬ ሆነው እንደቀሩት ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ‹ሰሎሞናዊ› የሚባል የተለየ መንግሥት አልነበረንም፡፡ ነገሥታቶቻችን ሁሉ ራሳቸውን ከኢየሩሳሌም ጋር ያያይዙ ነበር፡፡ ዐፄ ካሌብም ከናግራን ዘመቻ መልስ ዘውዳቸውን ኢየሩሳሌም ነው የላኩት፡፡ የዐፄ ገብረ መስቀል ልጅ ሙሴም መጀመሪያ ወደ ኢየሩሳሌም፣ በኋላም ወደ ሶርያ በመጓዝ በዚያ ገመንነው ገዳም መሥርተዋል፡፡ ገዳማቸውም ‹ሙሴ አል ሐበሽ ገዳም› ይባላል፡፡

የዛግዌ ነገሥታትም ሰሎሞናውያን የማይሆኑበት ምክንያት የላቸውም፡፡ በገድሎቻቸው ላይ ኢየሩሳሌምን አብዝተው የሚያነሡ፣ ማኅተሞቻቸው ሁሉ የዳዊት ኮከብ የሆኑ፣ በውቅር ቤተ ክርስቲያኖቻቸው የዳዊትን ኮከብ የቀረጹ የዛግዌ ነገሥታት እንዴት ሰሎሞናውያን አይሆኑም፡፡

የኢትዮጵያዊው የቅዱስ ሙሴ(የዐፄ ገብረ መስቀል ልጅ) ገዳም በሶርያ
በመሆኑም የጠፋና የተመለሰ የሰሎሞን መንግሥት አለ ብሎ ለመናገር ያስቸግራል፡፡ ሥርወ መንግሥታቱንም ‹የአኩስም፣ የላስታ፣ የሸዋ፣ የጎንደርና የሸዋ 2ኛ› ብሎ መክፈሉ የተሻለ ነው፡፡

ሲባል እንደኖረው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሲሦ መንግሥት ቢቀበሉ ኖሮ በገድለ አቡነ አኖሬዎስና በገድለ አቡነ ፊልጶስ ላይ እንደምናነበው እነዚህ ሁለት ቅዱሳን ወደ ደብረ አስቦ(የአሁኑ ደብረ ሊባኖስ) ሲመጡ ግንባር በምታክል መሬት ላይ አተር ዘርተው ሲሰበስቡ ባላገኟቸው ነበር፡፡ ደብረ ሊባኖስ ይበልጥ እየታወቀና በማዕከላዊ መንግሥት ቦታ እያገኘ የሄደው ከዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በኋላ ነው(ምናልባት ኤርትራ ይገኝ ከነበረው ከደብረ ሊባኖስ ዘሺምዛና ጋር ያለው ግንኙነት እየተዳከመ ሲመጣ)፡፡ ደብረ ሊባኖስ የሚለውን ስም ያገኘውም ያኔ ነው፡፡(Les chroniques de Zara Ya’eqob.,P. 91) አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከነገሥታቱ ጋር የተለየ ቀረቤታ ቢኖራቸው ኖሮ በዓለ ዕረፍታቸው ነገሥታቱና መኳንንቱ በተገኙ ነበር፡፡ ነገሥታቱ በደብረ ሊባኖስ መገኘት የጀመሩት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ካረፉ ከ100 ዓመታት ቆይተው ከዐፄ ይስሐቅ ዘመን (1406-1421 ዓም) በኋላ ነው፡፡ እንዲያውም የደብረ ሊባኖስ አባቶች በነበራቸው ጽኑዕ አቋም የተነሣ ከነገሥታቱ ጋር ባለ መስማማት ነው የሚታወቁት፡፡ 3ኛውን እጨጌ አቡነ ፊልጶስን፣ አሥራ አንዱን ንቡራነ ዕድና እጨጌ እንድርያስን ማስታወሱ ይበቃል፡፡

ከላስታ ወደ ሸዋ የመንግሥት ዝውውር ሲደረግ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሐይቅ እስጢፋኖስ በትምህርት ላይ ነበሩ(የሚጣቅ ዐማኑኤሉ ገድለ ተክለ ሃይማትና ገድለ ኢየሱስ ሞአ በዝርዝር እንደሚተርከው)፡፡ በዚህ የሥልጣን ዝውውር ላይ ይበልጥ ተሳታፊ የነበሩት አቡነ ኢየሱስ ሞአ ዘሐይቅ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ሐይቅ የዐቃቤ ሰዓትነት ሥልጣን ነበረው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሲሦ መንግሥት አግኝተዋል የሚለው ትረካ መንግሥት ወደ ጎንደር ከተቀየረ በኋላ(17ኛው መክዘ) በተጻፈው በብዕለ ነገሥት ላይ የተገለጠ ነው፡፡ ብዕለ ነገሥት የነገሥታትን ሀብት ለማሳየት የተጻፈ ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ነው ከይኩኖ አምላክ ጋር ቃል ኪዳን ገብተዋል ተብሎ የተጻፈው፡፡ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ግልጽ ነው፡፡ መንግሥት ወደ ጎንደር ሲዞር ደብረ ሊባኖስ ከማዕከላዊው መንግሥት ራቀ፡፡ በአካባቢውም ክርስቲያን ባልሆኑ ሕዝቦች ተከበበ፡፡ የጎንደር ነገሥታት ገዳሙን እንዳይረሱትም በብዕለ ነገሥት የአባታቸውን ይኩኖ አምላክን ቃል ኪዳን እንዲያስታውሱ የሚያደርግ ነገር ተጻፈ፡፡

እናም ተስፋዬም ሆነ ሌሎች እንደሚሉት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከቅድስና ሥራ በቀር የገቡበት ፖለቲካ የለም፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደ ደብረ አስቦ ሲገቡ ይኩኖ አምላክ በመንበሩ ላይ ነበር፡፡ ነገር ግን የጠበቃቸው ዘንዶ ይመለክበት የነበረ ዋሻ እንጂ ከሲሦ መንግሥት የተገኘ ግብር አልነበረም፡፡ ያንን ዋሻም ያገኙት ከጣዖት አምላኪዎች አስለቅቀው ነው፡፡ 28 ዓመት በደብረ አስቦ ሲቀመጡም የጎበኛቸው ንጉሥ አልነበረም፡፡ ደቀ መዝሙሮቻቸውም ከዝንጀሮ ጋር እየተሻሙ እህል ዘርተው ከማብቀል ውጭ የተለየ ርስት አልነበራቸውም፡፡ ደብረ ሊባኖስ ሲተከልም የአካባቢውን ሕዝቦች በማሳመን እንጂ በነገሥታቱ ድጋፍ አልነበረውም፡፡ ከይኩኖ አምላክ በኋላ የመጣው ያግብዐ ጽዮንና አምስቱ የያግብዐ ጽን ልጆች ለአቡነ ተክለ ሃይማትም ሆነ ለደብረ አስቦ ያደረጉት ነገር አልነበረም፡፡ ዐፄ ዐምደ ጽዮንና ዐፄ ሰይፈ አርእድም ከደብረ ሊባኖስ እጨጌዎች ጋር በሰላም አልኖሩም፡፡

አቡነ ፊልጶስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሲመጣ የአካባቢው ሰዎች ‹የገዳሙ መነኮሳት ሰው ይበላሉ›› ብለው ነው የነገሩት፡፡ ይህም ደብረ አስቦ በዚያ ዘመን የመነኮሳት ማኅደር እንጂ እንኳን ነገሥታቱ የአካባቢው ሰዎችም በቅጡ እንዳልቀረቡት ያሳየናል፡፡ የደብረ ሊባኖስ የመጀመሪያዎቹ አባቶችም በራሳቸው ጥረት በደብረ አስቦ ዋሻ ውስጥ ገዳም የተከሉ እንጂ በነገሥታቱ ድጋፍ ሲሦ መሬት የያዙ እንዳልነበሩ ያሳየናል፡፡ 

ከዐሥረኛው መክዘ ጀምሮ በነበረው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት በሰሜኑና በደቡቡ የሀገራችን ክፍል ምክንያት የነበረው ግንኙነት ተቋርጦ ነበር፡፡ ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት እንደሚገልጡትም የሰዎች ፍልሰት ከሰሜኑ የሀራችን ክፍል አሁን ሸዋ ወደሚባለው አካባቢ በየተወሰነ መጠን ብቻ ይከናወን ነበር፡፡ ይህንን ከሦስት መቶ ዓመታት በላይ ለሆነ ዘመን የተለያየ ሕዝብ እንደገና ያዋሐዱት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዳሞትን ከሸዋ ጋር ካገናኙ በኋላ ወደ ወሎ በመሄድ ሐይቅ ቆዩ፤ ቀጥለውም ወደ ትግራይ በመጓዝ ደብረ ዳሞ ገቡ፡፡ ለሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የምንኩስና ሕይወት ማንሠራራት አንዱ ምክንያት የሆኑትን አቡነ መድኃኒነ እግዚእን አመነኮሱ፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ደግሞ አምስቱን ከዋክብት(አቡነ አሮን ዘክቱር፣ አቡነ መርቆሬዎስ ዘዶባ፣ አቡነ ዘካርያስ ዘኬፋ፣ አቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘዳኅና፣ አቡነ ዳንኤል ዘጸዐዳ)ና ሰባቱን ከዋክብት በማመንኮስ(R. Basset, Etudes sur I historie d Ethiopie,.p 10) የሰሜኑን ገዳማዊ ሕይወት እንደገና ነፍስ ዘርተውበታል፡፡ በዚህም ምክንያት የሰሜኖቹ ወደ ደቡብ በመምጣት፣ የደቡቦችም ወደ ሰሜን በመሄድ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱ እንዲያንሠራራ አድርገውታል፡፡

ተስፋዬም ሆነ መሰሎቹ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ላይ የሚዘምቱት የእምነትም ሆነ የታሪክ ክርክር ስላላቸው አይደለም፡፡ ሀገሪቱ የቆመችባቸውን ተራዳዎች የመናድና እሴት አልባ የማድረግ ተልዕኮ ስላላቸው እንጂ፡፡ ይህ ተልዕኮ ደግሞ በዚህች በብዙ ቅዱሳን ጸሎት በታጠረች ሀገር ላይ ፈጽሞ የሚሳካ አይደለም፡፡ የሌለን ነገር የሚፈልግ አያገኝምና፡፡  

©ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው


ማስተዋሻ

አቡነ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከተ አንድ መጽሐፍ በማዘጋጀት ላይ ነኝ፡፡ ጻድቁ በጸሎታቸው ቢረዱኝ በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ ይወጣ ይሆናል፡፡ እናንተም ጸልዩበት፡፡


ለ10 ዓመታት (ከ፲፱፻፸፬ – ፲፱፻፹፬ ዓ.ም.) በስደት ለ15 ዓመታት (፲፱፻፹፬- ፲፱፻፺፱ ዓ.ም.)  በሐዋርያዊ አገልግሎት ቆይተውበታል፡፡ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ድጋፍ በኒውዮርክ ከተመሠረተውና የጃማይካ ተወላጆች ከሚገኙበት የኒውዮርክ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ቀጥሎ የመጀመሪያውን የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በዋሽንግተን ዲሲ (መካነ ሕይወት መድኃኔዓለም) አቋቁመዋል፡፡ የገለልተኛ አብያተ ክርስቲያን መዋቅርንና የሁለተኛ ሲኖዶስ ምሥረታን በመቃወም የእናት ቤተ ክርስቲያን …

ጥቅምት ፳፭(ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት የውጭ መከላከያ ደህንነት እንዲሁም የህግ፣ ፍትህ እና የአስተዳደር ጉዳዩች ቋሚ ኮሜቴዎች አባላት ሰሞኑን እንዲወያዩበት በተደረገው የመከላከያ አዋጅ 98 በመቶ የሚሆኑት ወታደራዊ አዛዦች ከአንድ ብሄር የሆኑበትን አወቃቀር እንደማይለውጠው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው መኮንኖች ተናግረዋል: የመከላከያ ሚኒስቴር ሹሞች በበኩላቸው አዋጁ እስከ ዛሬ የነበሩትን ህጎች ሁሉ የሚለውጥና …

ጥቅምት ፳፭(ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል ጋዜጠኞች እና በፖለቲካ ታማኝነት ተሹመው በሚያገለግሉ መሪዎች መካከል መተማመን የለም ሲሉ ጋዜጠኞች ለኢሳት ተናግረዋል፡፡ በጋዜጠኞች እና በአመራሩ መካከል ለተፈጠረው ልዩነት በርካታ ምክንያቶች ቀርበዋል። ጋዜጠኞቹ ለክልሉ ቴሌቪዥን ስርጭት ልዩ ምልክት ወይም ሎጎ ሁኖ እንዲያገለግል የተመረጠው የሰማእታት ሃውልት አርማ የአማራን ህዝብ የሚወክል አይደለም በማለት ተቃውሞ እያሰሙ ነው፡፡ …

ጥቅምት ፳፭(ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመላው ኢትዩጵያ ተግባራዊ እንዲደረግ በኢህአዴግ ጽ/ቤት በኩል ለ14 ቀናት የሚቆይ ሰልጠና ተቀርጾ ወደ ታች በመውረድ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡ ቅድሚያ እንዲያስተገብር ትዕዛዝ የተላለፈለት የአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች ስልጠናውን እየሰጠ ነው። ስልጠናው የኢትዩጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ  ወይም ኢህአዴግ የተጋድሎ ታሪክ  ላይ የሚያተኩር ሲሆን አርሶ አደሮች በኢህአዴግ …

ጥቅምት ፳፭(ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ ግንባታ ዘርፍ በየጊዜው እየናረ የመጣው የግብአቶች ዋጋ ንረት በተለይ በብድር የሚሰሩ በርካታ ግንባታዎችን እያስተጓጎለ እንደሚገኝ ታውቋል። ከመንገዶች ባለስልጣን የተገኘ መረጃ እንዳመለከተው የግንባታ ግብአቶች ዋጋ ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ ከ100 እስከ 237 በመቶ የዋጋ ንረት አሳይቶአል፡፡ መረጃው እንደአብነት ከዘረዘራቸው ግብአቶች መካከል ነዳጅ እ.ኤ.አ በ2009 ዓ.ም በሊትር 7.13 ብር የነበረው …

ሮም የታተመ የኢጣሊያ ጋዜጣ እንደዘገበዉ የሶሪያ ስደተኞችን እንረዳለን የሚሉ ሐይላት ከዘጠና አምስት ስደተኞች ላይ መቶ ሺሕ ዩሮ የሚያወጣ ወርቅ፥ሌላ ጌጣ ጌጥና ገንዘብ ዘርፈዋል።ዶን ሙሴ ዘርዓይ እንዳሉት ደግሞ አዉሮጳ የሚገቡ ስደተኞችን እንረዳለን የሚሉ፥ በተለይ የሚያስተረጉሙ ኤርትራዉን የስደተኞቹን ሚስጥር ለኤርትራ መንግሥት አሳልፈዉ ይሰጣሉ

የአሜሪካንን ምስጢራዊ መረጃዎች ያጋለጠው የቀድሞው የአሜሪካን የስለላ ድርጅት ባልደረባ ኤድዋርድ ስኖውደን፤ ባለፈዉ ሳምንት ሐሙስ ከታዋቂዉ የጀርመን ፖለቲከኛ ጋር ሞስኮ ላይ ሲገኛኝ ጀርመን ሁኔታዎችን ካመቻቸችለት በጀርመን ምክር ቤት ተገኝቶ ስለ አሜሪካ የስለላ ጉዳይ በግልፅ ለመናገር እንደሚፈልግ መናገሩ ይታወቃል።

የእስራኤል መንግሥት ከኢትዮጵያ የመጨረሻ ያላቸውን ተጓዞች ናቸው ባለፈው ነሐሴ 28 2013 ሀገሩ አስገብቶዋል። እሥራኤል እነዚህኑ አዲስ ገቦችን በተለያዩ የሀገሪቱ ከፊሎች ባዘጋጀቻቸው የመጠለያ ጣቢያዎች ያሰፈረች ሲሆን፣

የኢትዮ ምሕዳር ዋና አዘጋጅ ጌታቸው ወርቁ እና ዋና ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ሚልዮን ደግነው በኦሮሙያ ፖሊስ ለገጣፎ ውስጥ ታሰሩ። ወኪላችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር እንደገለጸልን፣ ጋዜጠኛ ሚልዮን ባለፈው ቅዳሜ፣

የኛ ነግር መልሶ መላልሶ ሆኗል። በገራችን አቆጣጠር በ1960ዎቹ የተማሩና የነቁ ወጣቶች አቢዮት ማካሄድ በጀመሩ ጊዜ የተነሱ ልዩነቶች አንዳንዴ ቅርጻቸውን በመጠኑ ይቀይሩ ይሆናል እንጂ ዛሬም ድረስ ባንድ ወይ በሌላ በኩል የልዩነትና የፍዳችን ምንጭ ሆነው ቀጥለዋል። እነዚህ ልዩነቶች መረቀቂያዎች፤ መጣያያዎች ቢያመች መገዳዳያዎቻችን ናቸው። ችግር የሆነው ጎራ ለይተው በነበሩ ፖለቲከኛች የሀሳብ ልዩነቶቹ መፈጠራቸው ወይ መኖራቸው አልነበረም። ወይ ልዩነት […]

የለውጥ አመራር ሂደቱን የሚያስቀጥል ዋና ሥራ አስኪያጅ ይፈለጋል የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን የዋና ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በጊዜያዊነት የሚመሩ ሓላፊ ተመደቡ፡፡ ሓላፊነታቸውን በድንገት ለቀው ወደ አሜሪካ ባቀኑት መጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት ምትክ የተመደቡት ጊዜያዊ ሓላፊ የክህነትና መንፈሳዊ ፍትሕ ዋና ክፍል ሓላፊ ንቡረ እድ አባ ዮሐንስ ገብረ ሕይወት ናቸው፡፡ የንቡረ እድ አባ ዮሐንስ ገብረ ሕይወት ጊዜያዊ ሓላፊነት እስከ …

በቅርቡ ከሰማናቸው ዜናዎች ውስጥ አንዱ‹‹በጋምቤላ በሕንዳዊው ኩባንያ ቨርዳንታ ሐርቨስት የተያዘው እርሻ በአካባቢው ሰዎች እሳት ተለቀቀበት›› የሚል ይገኝበታል፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች እርሻውን ማቃጠላቸው ስህተት እንደሆነ አምናለሁ፤ ነገር ግን በዚህ ጽሑፍ በነርሱ ቦታ ሳልሆን ልፈርድባቸው አልደፍርም፡፡ ይልቁንም በዚህ መረጃ ላይ ተመስርቼ ‹‹ለምን›› የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እሞክራለሁ፡፡
ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም የዛሬ ሁለት ዓመት (ኦክቶበር 16፣ 2011) ‹‹ቀጣዩ እሳት በምን ይመጣ ይሆን?›› በሚል ስጋታቸውን የጻፉት በዚያው ክልል ትልቅ የእርሻ ቦታ የገዛውን የካሩቱሪስታን ኩባንያ የመጀመሪያ ምርቱን የሰደድ እሳት ከበላበት በኋላ ነበር፡፡ ይህ በሆነ ልክ በሁለት ዓመቱ ነው ዘንድሮ ሌላኛው የሕንድ ኩባንያ እርሻ ላይ ነዋሪዎቹ እሳት የለቀቁበት፡፡
ብዙ የሚታወቀውና 300ሺሕ ሔክታር የእርሻ መሬት በየዓመቱ ተከፋፍሎ የሚከፈል 50 ሚሊዮን ብር ሊዝ የተከራየው ካሩቱሪስታን (ካራቱሪ) ነው፡፡ የግብርና ድርጅቶቹ የሥራ ማስኬጂያ ገንዘባቸውን የሚያገኙት ከዚሁ አገር በመሆኑ ኢንቨስትመንቱ በዚህ ረገድ የሚያስገኘው ጥቅም የለም፤ እንዲያውም ‹ካራቱሪ 62 ሚሊዮንብር የባንክ ዕዳውን መክፈል አልቻለም፡፡ ይባስ ብሎ የሠራተኞች ጡረታ ተቆራጭ እና የገቢ ግብር ለመንግሥት አላስገባም› ብሎ ሰንደቅ ጋዜጣ የዘገበው በቅርቡ ነበር፡፡ ከመሬት ሊዙ ይገኛል የሚባለው ጥቅም ‹‹የቴክኖሎጂ ሽግግር›› ነው፡፡ ነገር ግን የአካባቢዎቹን ነዋሪዎች እያበሳጨና በሌላም፣ በሌላም ከወዲሁ በተለይ ለነዋሪዎቹ አለመመቸቱን ምልክቶች ያሳያሉ፡፡
ይህን የእርሻ መቃጠል ስናነሳ በታሪክ ወደኋላ ተጉዘን ዘመነ መሳፍንት ላይ እንደርሳለን፡፡ በዘመኑ አቅም ያለው ሁሉ ባላባት የነበረበት እና ምስኪኑን ገበሬ በተደጋጋሚ እያስገበረ ያስመርር ነበርና የወቅቱ ገበሬ ገና ወታደሮች መምጣታቸውን ሲሰማ የገዛ መኸሩ ላይ እሳት ይለቅ ነበር ይሉናል የታሪክ ባለሙያዎች፡፡
ታሪክ ራሱን ደገመ!
ሰሞኑን አንድ ወዳጄ ያዋሰኝ በ2011 በFSS የታተመ የደሳለኝ ራሕመቶ ጥናት (LAND TO INVESTORS: Large-Scale Land Transfers in Ethiopia) መንግሥት የመሬት ልማት የሚለውን መቀራመት ችግሮች በአምስት አንኳር ነጥቦች ያስቀምጧቸዋል፡፡ እኔ በራሴ አገላለጽ እንደሚከተለው እዘረዝራቸዋለሁ፡-

1. የገጠር ኢኮኖሚ መዛባት
ለውጭ ባለሀብቶች የሚያደላው ይህ ስርዓት ግዙፍ የግብርና ፕሮጀክቶቹ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተጠቃሚዎች ከመሆናቸውም ባሻገር የትናንሽ ገበሬዎቹን ኢኮኖሚ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በማቃወስ የሀብት ልዩነቱን ይበልጥ ያሰፋዋል፡፡ ፉክክሩም ‹‹ባላቸውና በሌላቸው›› መካከል ይሆናል፡፡ በረዥም ጊዜ ሀብታሞቹ በኬሚካሎች ይዘቱን አራቁተው ሲሄዱ ድሀዎቹ ደረቅ መሬታቸውን ታቅፈው ይቀራሉ፡፡

2. የተጠቂነት ስሜት
የመሬት ነጠቃው /ኢንቨስትመንት የሚሰጥበት መንገድ/ ግልጽነት የጎደለው እና ያለነዋሪዎቹ ሙሉ ፈቃደኝነት የሚከናወን በመሆኑ፣ ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሱ በተጨማሪ ሰሚ እና ዋስትና የማጣት ስሜት /voiceless-ness and insecurity/ በነባሮቹ ማኅበረሰቦች ላይ ይፈጥራል፤ ስለሆነም ነዋሪዎቹ ‹‹ኢንቨስትመንቱን›› በቀና አይቀበሉትም ወይም ሊቀበሉት የሚያስችል ምክንያት የላቸውም፡፡
3. ‹‹የማያልፍለት ድኻ ሀብታም የመጋበዙ›› ጉዳይ
የውጭ ባለሀብቶች ምርታቸውን ስለሚያቀርቡለት አካል መደበኛም ሆነ ኢ-መደበኛ ስምምነት የለም፡፡ እንደምሳሌ የሕንድ ኩባንያዎች እዚህ ያመረቱትን ከፊሉ የአገራቸውን ‹‹የምግብ ክፍተት›› ለመሙላት፣ ከፊሉን ደግሞ ለሌሎች አገራት በጥሩ ትርፍ ለመሸጥ ነው መሬት ከኢትዮጵያ የገዙት፡፡ ኢትዮጵያ ግን በየዓመቱ የምግብ እጥረት የሚያጋጥማት እና ከውጭ እጆቿን ዘርግታ የምትለምን አገር ናት፤ (እጅ መዘርጋት መፍትሔ ይመስል!)
4. የቴክኖሎጂ ሽግግር ብሎ ነገር አለመኖር
የግዙፍ ግብርና ፕሮጀክቶች በባሕሪያቸው ትላልቅ ማሽነሪዎችን የሚጠቀሙ በመሆናቸው እና በበሬና ገበሬ ትከሻ አራሽ የገበሬ ቤተሰቦች ቴክኖሎጂ ሽግግር ያድርጉ ቢባል እንኳን ከነዚህ ግዙፍ ማሽነሪዎች ምንም ማግኘት አይችሉም፡፡ ስለዚህ አንዱ የመንግሥት መሬት በርካሽ የመቸብቸብ ግብ መቼም የተባለለትን አያመጣም፡፡
5. ሌሎች አማራጮች አልተቀመጡም
መንግሥት መሬት ለግዙፍ የግብርና ፕሮጀክቶች ማከራይትን እንደብቸኛ አማራጭ በመያዙ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች እንደተሞከረው መሬቱን፣ የደን እና የእንስሳት ይዘቱን እንደጠበቀ የገቢ ምንጭ ማግኛ አማራጭ መፈለግ ይቻል ነበር፡፡ በተለይም የጋምቤላ ደን እና የእንስሳት ይዘት /ecosystem/ በግዙፍ ግብርና ስም አደጋ ላይ ወድቋል፡፡ በረዥም የጊዜ ሒደት ወደማይመለስበት የደን ሀብት መራቆት ደረጃ ይደርሳል፡፡
እንግዲህ ገበሬዎቹን የሕንዶቹን እርሻ ለማቃጠል ያበቃቸው ከነዚህ ችግሮች አንድ ሁለቱ ብቻ ይሆናሉ፡፡ ነገር ግን ችግሮቹ ከዚያም የባሱ ናቸው፡፡

መንግሥት አያውቅም እንዳይባል ብዙ ምሁራን ብለውት፣ ብለውት ደክሟቸው ነው የተዉት፡፡ ስለዚህ አጥኚው (ደሳለኝ ራሕመቶ) እንደሚሉት ‹‹ill-conceived›› (በክፋት የተፀነሰ) ሐሳብ ስለሆነ፣ በእኔ እምነት መፍትሔው የስርዓቱን ክፋት በሠላማዊ ሁኔታ እስከገጥግ መታገል ነው፡፡

ብዙዎቻችሁ ከኢትዮጵያ ውጭ ምትኖሩ አንባብያን አዲሱን መጽሐፍ ባላችሁበት ለማግኘት ጠይቃችኋል፡፡ ያለው አማራጭ በ [email protected] ኢሜይል ላኩልን፡፡ በኢሜይላችሁ ያላችሁበትን አድራሻ አብራችሁ ላኩልን፡፡ የመላኪያውን ዋጋ ጠይቀን እንነግራችኋን፡፡ ከዚያም የመጽሐፉንና የመላኪያውን ዋጋ በባንክ በኩል ከላካችሁ መጽሐፉን በነጠላም ሆነ በብዛት እንልክላችኋለን፡፡ አስቀድመን በመላክም ከሀገር ቤቱ አንባቢ እኩል እንድታነቡ እናደርጋለን፡፡
መልካም ንባብ፡፡ 

ግምገማውን ተከትሎ የዋና ሥራ አስኪያጅ ሹመትና መዋቅራዊ ለውጡን ለማደናቀፍ በተለያዩ የመቀስቀሻ አጀንዳዎች አሉባልታ ሲነዙ፣ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያንን ለአድማ ሲቀስቀሱ በቆዩ ሓላፊዎች ላይ የሚወሰዱ ርምጃዎች ይጠበቃሉ፡፡ ለዋ/ሥ/አስኪያጅ ሹመት÷ በጎጠኝነትና በጥቅመኝነት የማግባባት እንቅስቃሴ እየተካሄደ ነው፤ ወደ ረዳት ሊቀ ጳጳሱ እና ወደ ፓትርያርኩ የጳጳስና የባለሥልጣን አማላጅ የላኩ፣ የድጋፍ ፊርማ በማሰባሰብ የተጠመዱም አሉ፤ ከብር 6.7 ሚልዮን በላይ በኾነ የገቢ …

የጋራ ማሕበር ለመመስረት የተስማማሙት ፖለከኞች እንደሚሉት የመጨረሻ አላማቸዉ ቢቻል ሁሉንም በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ተቃዋሚዎችን ይሕ ቢቀር ሰላሳ ሰወስት ፓርቲዎችን አስተባብሮ አንድ ጠንካራ ተቃዋሚ ጎራ ለመፍጠር ነዉ።ይሕ ምናልባት ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት በተቃዋሚዉ ጎራ የሚታየዉን መከፋፋል፥ መሰነጣጠቅና መጠላለፍ ለማስቀረት ይረዳ ይሆን?