ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በደሴቲቱ ማዳጋስካር ከዘጠኝ ቀናት በፊት የተካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ የመጀመሪያ ውጤቶች እንዳሳዩት፣ በተወዳዳሪነት ከቀረቡት 33 ዕጩዎች መካከል አንዱም ለድል የሚያበቃውን ድምፅ ባለማግኘቱ በሀገሪቱ እአአ የፊታቸን ታህሳስ ፣ 2013 ዓም ሁለተኛው ዙር ምርጫ ይደረጋል።

click here for pdf
በቅዱሳት መጻሕፍት ዕውቀትና በቤተ ክርስቲያን ትምህርት የበሰሉ፣
ዘረኝነትንና ጠባብነትን እስከ መጨረሻው የተዋጉ፣
የፍቅር መሥፈርታቸው ሰው መሆን ብቻ የሆነ፣
ቤተ ክርስቲያን የቤተ መንግሥቱ ጥገኛና ተቀጽላ እንዳትሆን በብርቱ የተጋደሉ፣
ለእምነታቸውና ለአቋማቸው ሲሉ ከነገሥታቱ ጋር ፊት ለፊት የተገዳደሩ፣
ከእሳት፣ ከግርፋት፣ ከአራዊት፣ ከዘንዶ፣ ከግዞት፣ ከስደት ጋር ተጋፍጠው እምነታቸውን ያስከበሩ፣
ነገሥታቱ በተሳሳተ መንገድ ሲሄዱ እንደ ዮሐንስ መጥምቅ ያለ ፍርሃት የገሰጹ፣
በመላዋ ኢትዮጵያ ለስብከተ ወንጌል የተሠማሩ፣
ቤተ መንግሥትን ለሥልጣንና ለጥቅም ሲሉ ከተጠጉ ሥጋውያን ካህናት ጋር በእምነትና በጽናት ያደረጉት ትግል፤
ምንኩስና መንኖ ጥሪት(ሀብት ንብረትን መተው) ነው ብለው የተሰጣቸውን የማባበያ ገንዘብ፣ ወርቅና ርስት ላለመቀበልና       ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን ለመጠበቅ ያደረጉት ተጋድሎ፣

የአራት የእምነት ኃያላን አበው

                             (አቡነ በጸሎተ ሚካኤል፣ አቡነ ፊልጶስ፣ አቡነ አሮን፣ አቡነ አኖሬዎስ) ታሪክ
ከበቂ ታሪካዊ ማብራሪያ፣ የፎቶ ግራፍና የሥዕል ማስረጃዎች፣ የቦታና የሰዎች ስሞች መዘርዝሮች ጋር፣

የመካከለኛው ዘመን ኢትዮጵያ ሃይማኖታዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ባሕላዊ ታሪክ በሰፊው የተዳሰሰበት፣
        ጠፍተው የነበሩ ቦታዎችን በአሠሣ በመፈለግ፣ የጠፉ መረጃዎችን ከየገዳማቱና አድባራቱ በማፈላለግ፣ በቀደምት ሊቃውንት            የተጻፉትን በማጣቀስ፣ የተዘጋጀ የጥናት መጽሐፍ፣

በመጽሐፉ ውስጥ

• የአቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ የአቡነ ኤዎስጣቴዎስ፣ የአቡነ ዜና ማርቆስ፣ የአቡነ ኢየሱስ ሞአ፣ የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ፣
• በአሥራ ሁለት አህጉረ ስብከት ለስብከተ ወንጌል የተሠማሩት የአሥራ ሁለቱ ንቡራነ ዕድ ታሪክና የሥምሪት ሀገረ ስብከት            በስፋት ቀርቧል፤
• በመካከለኛው ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሰፊ ቦታ ያላቸው ግብጻውያን ጳጳሳት – የአቡነ ዮሐንስ፣           የአቡነ ያዕቆብ፣ የአቡነ ሰላማ መተርጉምና የአቡነ በርተሎሜዎስ ታሪክ ቀርቧል፤
• በደቡብ ኢትዮጵያና በኦሮሚያ ጥንት የነበሩትን የስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴዎች ያሳያል፤
• አቡነ ፊልጶስ ዛሬ ስላለችው ቤተ ክርስቲያን ከ600 ዓመታት በፊት የተነበየውን ትንቢት ያዩበታል

ነገሥታቱና መኳንንቱ ሲያሳድዷቸውና መከራ ሲያበዙባቸው፤ ከነገሥታቱ ጋር የተጠጉ የቤተ መንግሥት ካህናትና መነኮሳት ሲያሳብቁባቸውና ተንኮል ሲሠሩባቸው፤ እግዚአብሔር ደግሞ ቅድስናቸውንና እምነታቸውን በተአምራት ሲገልጥላቸው ያያሉ፡፡

                            አራቱ ኃያላን – ከአሥራ አምስት ቀን በኋላ በገበያ ላይ ይውላል

Ethiopia Zare (አርብ ጥቅምት 23 ቀን 2006 ዓ.ም November 1, 2013):- ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል በእስር ላይ የሚገኘውን የብእር ሰው፣ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ ባለቤቷን እስክንድር ነጋን ተለይታ ከምትኖርበት ዋሽንግተን ዲሲ የሀገሯን የመጨረሻ ስንብት በሚመለከት ለህሊና እስረኞች ለሆኑት ታሳሪዎች ያስተላለፈችው መልእክት ይፋ ተደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopia Zare (አርብ ጥቅምት 23 ቀን 2006 ዓ.ም November 1, 2013):- ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል በእስር ላይ የሚገኘውን የብእር ሰው፣ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ ባለቤቷን እስክንድር ነጋን ተለይታ ከምትኖርበት ዋሽንግተን ዲሲ የሀገሯን የመጨረሻ ስንብት በሚመለከት ለህሊና እስረኞች ለሆኑት ታሳሪዎች ያስተላለፈችው መልእክት ይፋ ተደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኦህዴድ ከወረዳ ጀምሮ ያሉ አባላቱን እየገመገ ሲሆን፣ ግምገማው በእርስ በርስ ሽኩቻና መጠላላፍ እየተካሄደ ነው። ከድርጅቱ አመራሮች መካከል አንዱ ለኢሳት እንደገለጹት ድርጅቱ ህልውና አደጋ ውስጥ ወድቋል።የዝምድና አሰራር እንዲሁም በቡድን ተደራጅቶ አንዱ ሌላውን የሚያጠቃበት ሁኔታ በሰሞኑ ግምገማ በስፋት የታየ ሲሆን፣ አብዛኛው ከታች እስከ ላይ ያለው …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አለማቀፉ የገንዘብ ተቋም ባወጣው የ2004-2005 ግምገማ ኢትዮጵያ ድህነትን ለመቅረፍ የምታደርገውን ጥረት አድንቋል። በኢኮኖሚው ረገድ ስኬት እየታየ መሆኑን፣ አገሪቱም የ7 በመቶ እድገት ማስመዝገቡዋን የገለጸው አይ ኤም ኤፍ፣ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር መንግስት የወሰደውን እርምጃንም አድንቋል። የአቶ መለስ ሞት በፈጠረው መደናገጥ ሁሉም የውጭ ምንዛሬ ለመግዛት መገደዱን በዚህም ሳቢያ የተፈጠረው የምንዛሬ …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክልሉ ለረጅም አመታት ኖረው በተለያዩ ምክንያቶች ከአካባቢው እንዲለቁ የተደረጉ አንዳንድ ሰዎች ለኢሳት እንደገለጹት ፣ መስተዳድሩ እንኳንስ የሌሎችን አካባቢዎች ህዝብ መብት ለማክበር ቀርቶ የክልሉን ነዋሪዎች መብት ማክበር አልቻለም ብለዋል። ከሌላ ክአካባቢዎች የመጡ በተለይም የአማራ ተወላጆች ሶማሊያ መናገር አትችሉም እየተባሉ ከስራ መባረራቸውን የገለጹት እኝህ ነዋሪዎች፣ በንግድ ስራ የሚተዳደሩና በጅጅጋ …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ ሌተናንት ጄኔራል ሆነው የተሾሙት በሱዳን የሚገኘውን እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስር በመሆን  በጸጥታ መስከበር ስራ ላይ የተሰማራውን የኢትዮጵያ ጦር የሚመሩት ምናልባትም ጀኔራል ሳሞራ የነሱን ሊተኩ ይችላሉ የሚባሉት ሌተናንት ጀኔራል ዮሀንስ ገብረመስቀል ተስፋማርያም በአዲስ አበባ የገነቡዋቸው የንግድ ህንጻዎች በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዋጋ እንደሚያወጡ ለእርሳቸው ቅርብ የሆኑ ሰዎች …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሀኪሙላ መሱድ የሚባለው የፓኪስታን ታሊባን መሪ የተገደለው በአሜሪካ ሰው አልባ የጦር ጅቶች መሆኑን አለማቀፍ ሚዲያዎች ቢዘግቡም እስካሁን ከአሜሪካ መንግስት በኩል የተሰጠ ማረጋገጫ የለም። ግለሰቡ በአሜሪካ ከሚፈለጉ አሸባሪዎች ማካከል አንዱ ነው። አሜሪካ ግለሰቡ ያለበትን ለጠቆመ 5 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል ገብታ ነበር። የመሱድ ምክትል ባለፈው ግንቦት ወር በተመሳሳይ …

ትላንት ዘሄግ ኔዘርላንድ ውስጥ ያስቻለው ዓ/ዓቀፉ የወንጀል ፍ/ቤት በኬኒያው ፕ/ት ኡሁሩ ኬኒያታ ላይ የተያዘውን የክስ ሂደት እስከሚቀጥለው የካቲት ወር ድረስ ለሶስት ወር ማራዘሙን ኣስታወቀ። የኣፍሪካ ህብረት ግን በቂ ኣይደለም እያለ ነው።

እንግዳችን የኤሌክትሪላል ኢንጂነሪንግ ምሩቅ ነው። በተማረበት ሙያ ሥራ አግኝቶ ነበር ይሁንና በፍላጎት ወደ ንግድ ሥራ ነው የገባው። ለምን? ስለዚህ ወጣት ማንነት እና ከሌሎች አራት ባልደረቦቹ ጋ ተደራጅቶ ስለሚሠራው ያስረዳናል።

በአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት የተዘጋጀው የ5 ሳምንት ስልጠና የመጀመሪያው ክፍል (1) እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ ረጅም የነፃነት ዘመን ሲኖራት በስልጣኔ ግን ብዙም እንዳልገፋችም። ስለዚህ ስልጠና ክፍል አንድ “ኢትዮጵያ ምን ስትሰራ ነበር?” የሚል ጥያቄ አንስቶ ሁለት አብይ ክሎች ያሉት ሰፊ ታሪካዊ መልሶች ሰጥቷል። በመቀጠል ክፍል አንድ (2) የሰላማዊ ትግልን እድገት አስመልክቶ ከክርስቶስ ልደት በፊት አንስቶ ዛሬ እስካለንበት ዘመን […]

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክንያቱ በውል ባይታወቅም ካለፉት 4 ቀናት ጀምሮ በከተማዋ ከፍተኛ ፍተሻ እየተካሄደ እንደሆነ የዘጋብያችን መረጃ ያመለክታል። በተለይ ዛሬ በከተማዋ መውጫና መግቢያ በሮች ላይ ሰዎች ከመኪናዎች እና ባጃጆች ላይ እንዲወርዱ እየተደረገ በጥብቅ ተፈትሸዋል። አንዳንድ ወገኖች  መንግስት ጸረ ሰላም እና አሸባሪዎች በከተማዋ ገብተዋል የሚል ወሬ እንደሚያስወራ ሲገልጹ፣ ሌሎች ነዋሪዎች ደግሞ …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዓመት 50ሺ የኮንዶምኒየም ቤቶችን ለመገንባት የያዘው ዕቅድ ከባድ ትችትን ያስከተለበት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዓመት ከ 100ሺ በላይ የቤቶች ግንባታ ለማከናወን ፊቱን ወደቻይና ኩባንያዎች ማዞሩ ተሰማ፡፡ አስተዳደሩ ከ800ሺ በላይ የኮንዶምኒየም ፣ ከ 136 ሺ በላይ የ40 በ60 ቤት ፈላጊ ነዋሪዎችን የመዘገበ ሲሆን ከዚህ ፍላጎት ጋር በማይጣጣም መልኩ …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ በከፍተኘው ፍርድ ቤት ባለው የአስተዳደር ቊንጮ ማለትም በዋናው ፕሬዚዳንት በዳኛ ውብሸት ሽፈራውና በምክትሉ ማሃል ያለው አለመስማማት እየጨመረ በመሄዱ የፍርድ አሰጣጥ ሂደቱን እያበላሸው መሆኑን ውስጥ አዋቂዎች ገለጹ ። አሁን ባለው አሰራር ተሰሚነት ያለው የኢሃዴግ አባል የሆነው ምክትሉ ሲሆን ፣  ፕሬዘዳንቱ የኢሃዴግ አባል ባለመሆኑ ተሰሚነት አጥቷል ይላሉ …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቅዱስ ሲኖዶሱ ሰሞኑን ሲያደርግ የነበረውን ምልዓተ ጉበኤ ሲያጠናቅቅ ባወጣው የአቋም መግለጫ ፣ በውጭ አገር ከሚገኙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ጋር ተጀምሮ የነበረው እርቀ ሰላም ወደ ፊት እንዲቀጥል እና ቤተክርስቲያን አንድነት እንዲጠናከር ወስኗል። የኦሮቶዶክስ ሀይማኖት ተከታዮች ቆጠራ እንዲካሄድና  የቤተክርስቲያኒቷ ታሪክ በደንብ ተጠንቶ እንዲቀርብም ወስኗል። ከፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ተወክለው የመጡ …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ እና በአማራ ክልሎች ያሉ አርሶ አደሮቹ ለኢሳት እንደተናገሩት ውጤታማ ባልሆኑበትና በግዴታ እንዲገዙ በተጠየቁት የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ እዳ እየተዋከቡ ነው። እዳችንን መክፈል አልቻንም የሚሉት አርሶ አደሮች መንግስት መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል። ግብርና ሚኒስቴር ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያ ጥቅም ላይ የዋለውን ዳፕ የተባለውን ማዳበሪያ ውጤታማ አልሆነም በሚል እንደሚቀይር ማስታወቁ ይታወቃል። …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቁም ነገር አዘል በሆኑ ቀልዶቹ የሚታወቀው ኮሜዲያን አብረሀም ከጀርባ ህመም ጋር በተያያዘ ሲሰቃይ ቆይቷል። ከጥቂት ወራት በፊት ወደ አውሮፓ በመምጣት በጀርመን አገር ህክምናውን ተከታትሎአል። አብርሀም በማእደ ኢሳት ዝግጅት ላይ ቀርቦ ለኢትዮጵያ ህዝብና የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ የረዱትን ወገኖች ማመስገኑና ጤናውም መሻሻልእያሳየ እንደሆነ መግለጹ ይታወሳል ፡፡ ከዲስከ መንሸራተት ጋር  …

ባሰላው ባሰላው እንቢ አለኝ እንዝርቱ፣ ከታችም አይደለ ከላይ ነው ጥመቱ። የጎንደር ሕዝብ እንጉርጉሮ ኦክቶበር 28 እንደ ሃገሩ አቆጣጠር ጠዋት ጉልበተኛ ነፋስ ከባሕር ተነስቶ በደቡብ እንግሊዝ በኩል አድርጎ እያቆራረጠ ወደ ሰሜን ተፈተለከ። የባሕሩ ሰይጣን የላከውን ጉልበተኛውን ነፋስ የፈራው አዳሜ ፈረንጅ ሁሉ ተርበትብቶ እኛንም በሬዲዮንና በቴሌቪዚዮን ሲያርበተብተን ሰነበተ። “ይህንን ቀን ከቆመ የተቀመጠ፣ ከተቀመጠም የተደበቀ ነው የሚያልፈው። ደፍሮ […]

በአዲስ ግንኙነት ዓለምን መቀየር በሚል መሪ ሃሳብ በታላቋ ብሪታንያ ዋና ከተማ ሎንዶን ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየዉ የዘጠነኛዉ የዓለም ዕስልምና ምጣኔ ሃብት መድረክ ዛሬ ተጠናቋል።

« በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያዊ ሕጻናት ስሞችን ስንመለከት በአብዛኛዉ ኢትዮጵያዊ ይዘት እንደሌላቸዉ እንረዳለን፤ አብዛኞች ስሞች ቅላጼያቸዉ ለጆሮ እንዲጥሙ እንጂ ፤ ታሪኩ ምን ማለት ነዉ ብለን ጠይቀን ለልጆቻችን ስም ስንሰጥ አንታይም። ይህ ደግሞ የባህል ወረራ እንዳያመጣብን እሰጋለሁ» ያሉን

ቅ/ሲኖዶስ ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪካዊነትና ቀዳሚነት እውነታውንና ትክክለኛውን የሚገልጽ ጽሑፍ እንዲዘጋጅ መመሪያ ሰጠ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት ለምልአተ ጉባኤው ስብሰባ የሰጠው ሽፋን ‹‹የጉርሻ ያህል ነው›› በሚል ተነቀፈ ‹‹ጉባኤው አገር አቀፍ ብቻ ሳይኾን ዓለም አቀፍም ነው፤ የምንሰጠው ትምህርት ነው፤ የምንወድቀው የምንነሣው ስለ ሀገር ጉዳይ ነው፤ ቤተ ክርስቲያን በዐይን የሚታይ በእጅ የሚጨበጥ ታሪክ ነው …

በአገልግሎት ጥራት /በሰው ተኮር ነፍስ የማዳን አገልግሎት/ ምእመናንን ማብዛትና ማጽናት፣ ቤተ ክርስቲያንን ከባይተዋርነትና ጠባቂነት ወደነበራት ሚና መመለስ፣ አስተምህሮዋን ከማይቃረኑ ጋራ ዓለም አቀፍ አጋርነትን በማጠናከር የሰላምና አንድነት ተምሳሌት ማድረግ፣ ለሙስና ችግሮች በንስሐ መንገድ መፍትሔ ማበጀት የቤተ ክርስቲያናችን ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማሕቀፍና ቊልፍ ጉዳዮች ኾነዋል፡፡ በቡድን እየተደራጁ የመንግሥትን ወቅታዊ አጀንዳዎች በአሉታዊ መንገድ የሚጠቀሙ አሉባልተኞችና ሙሰኞች እንዲሁም በቤተ ክህነቱ …

Prof. Al Mariam ፕ/ር ዓለማየሁ ገብረማርያም ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም፦ ነጻነት ለሀገሬ)
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ሕገመንግሥት በሕግ ከለላ ጥላ በቁጥጥር ስር የሚውሉ ዜጎችን አስመልክቶ የሚከተሉትን መብቶች ያጎናጽፋል። “በሕግ ከለላ ጥላ በቁጥጥር ስር የዋለ ማንኛውም ሰው በሕግ አግባብ መብቱ ተጠብቆ ይያዛል። ማንኛውም ሰው በሀሰት ለመረጃ ጠቀሜታ ተብሎ በማስገደድ እንዲያምን ወይም የተባለውን እንዲቀበል አይገደድም። ማንኛውም በማስገደድ የተገኘ መረጃ ተቀባይነት አይኖረውም።” ይላል አንቀጽ 19(2)(5)። እውነታው ሲታይ ግን ይህ የይስሙላ ሙበት የተጻፈበትን ወረቀት ዋጋ ያህል የለውም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

 

ኢትዮጵያዊያን በፍርዱ ረክተዋልወ/ሮ ሙሉመቤት ረታ (በሲያትል ኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር)

በእኔ አስተያየት ፍትህ ተበይኗል፤ ዳኛዋም ሆኑ ፍርድ ሰጭዎቹ (ጁሪዎቹ) በትክክል ጉዳዩን አይተው ወስነዋል ብየ አምናለሁዶ/ር ሸክስፒር ፈይሳ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት 20  ቀን 2006 ዓ.ም. October 30, 2013)፦ ከሁለት ዓመት በፊት ሃና ዊሊያምስ የተባለችውን ታዳጊ በቅዝቃዜ ደጅ ላይ በማዋልና በማሳደር አሰቃይተው ገድለዋል የተባሉት አሳዳጊዎቿ ኬሪ ዊሊያምስና ባለቤቷ ላሪ ዊሊያምስ የ37 ዓመትና የ29 አመት ጽኑ እስራት የተወሰነባቸው ሲሆን በሲያትል አካባቢ የሚኖሩ ትዮጵያዊያን በፍርዱ መደሰታቸውን በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥቅምት ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሪፖርተር ዛሬ ባወጣው ዘገባ በአገሪቱ የሚገኙ ሶስቱ ታላላቅ ስሚንቶ ፋብሪካዎች በአመት 12 ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ የማምረት አቅም ቢኖራቸውም በገበያ ውስጥ የሚገኘው ስሚንቶ ድምር ከ5 ሚሊዮን አይበልጥም። አብዛኛውን ስሚንቶ የሚገዛው መንግስት ሲሆን፣ የግሉ ዘርፍ ድርሻ ቀዝቃዛ መሆኑ ተዘግቧል። የሼክ ሙሀመድ አላሙዲን ንብረት የሆነው ደርባን ኩባንያ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ በኩንታል …

ጥቅምት ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የጥሬ ቆዳና ሌጦ ኤክስፖርት ባለፉት አምስት ዓመታት የተሻለ ገቢ ያስገኘ ቢሆንም ግብይቱ ኃላቀር፣ሰንሰለቱ የተንዛዛና ከፍተኛ የግብይት ወጪዎች የሚታዩበት እንዲሁም በምርት ጥራት በኣለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነቱ እጅግ አነስተኛ መሆኑን ከንግድ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ አመለከተ፡፡ የጥሬ ቆዳና ሌጦ ኤክስፖርትን በማቆም እሴት የተጨመረባቸውን የተለያዩ የቆዳ ውጤቶች ለውጪ ገበያ በመላክ የተሻለ የውጪ …

ጥቅምት ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የከተማዋ ነዋሪዎች እንደሚሉት በልመና የሚተዳደሩ አረጋውያን ቁጥር ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሯል። አረጋውያኑም ከክልል ከተሞች ወደ አዲስ አበባ እንደሚጎርፉ ነዋሪዎች ይናገራሉ። መንግስት የገጽታ ግንባታ በሚል አረጋውያንን ሰብስቦ ወደ ክልል ቢበትናቸውም፣ አረጋውያኑ ተመልሰው በምጣት በልመናው ቀጥለዋል። አንድ ነዋሪ እንዳሉት ቀድሞ ” አብያተ ክርስቲያናት ቅጥር ግቢ ውስጥ አይለመንም ነበር፣ አሁን ግን …

ጥቅምት ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በዘውዲቱ ሆስቲታል መድሀኒቱን ለመቀበል ከሳምንታት በላይ ሲጠባበቁ የነበሩ የስኳር ህመምተኞች በመጨረሻ መድሀኒት የለም መባላቸውን ለኢሳት ገልጸዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚሰጠው እርዳታ መቋረጥ ለችግሩ መፈጠር ምክንያት ነው ቢባልም፣ አንዳንድ ወገኖች ደግሞ የችግሩ ምንጭ መድሀኒቱ አየር ባየር ስለሚሸጥ ነው ብለዋል። ህመምተኞች እንደሚሉት መድሀኒቱን በግላቸው ገዝተው ለመጠቀም ዋጋው የሚቀመስ አይደለም። ብዙዎቹ መድሀኒቱን …

ጥቅምት ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የ42 አመቷ ካሪ ዊሊያምስ የ13 አመቷን ታዳጊ ሐና ዊሊያምስን በረሀብና በብርድ በመቅጣት ህይወቷ እንዲያልፍ ማድረጓን ፍርድ ቤቱ አረጋግጧል። የገዳዩዋ ባለቤት በ28 አመታት እንዲታሰር ተፈርዶበታል። ሌላው የ10 አመቱ የማደጎ ታዳጊ ኢትዮጵያዊም ለሌሎች አሳዳጊዎች እንዲሰጥ ተደርጓል። ፍርዱን የሰጡት ዳኛ ከፍተኛ የሚባለው ቅጣት ማስተላላፋቸውን ተናግረዋል። ሁለቱም ሰዎች ከሁለት አመታት በፊት መታሰራቸው …

የሃዋሣ ዩኒቨርሲቲና የከሰሣቸው ጋዜጠኞች የችሎት ውሎ

የሃዋሣ ዩኒቨርሲቲ በመሠረተባቸው ክሥ ሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡት የኢትዮ-ምህዳር ጋዜጣ ሁለት አዘጋጆች ወደ ዋናው ጉዳይ ገብተው እንዲከራከሩ ብይን ተሰጠ።

ሃዋሳ የሚገኘው የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩን የማየት መብት እንደሌለው ያቀረቡት መከራከሪያም ተቀባይነት አላገኘም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሁለቱ የጋዜጣው አዘጋጆችና ጉዳዩን ለመከታተል አብሯቸው የነበረው ባልደረባቸው እዚያው ሃዋሳ ከተማ በባጃጅ በመጓዝ ላይ እንዳሉ ባጋጠማቸው አደጋ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቀዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

“የአፄ አብርሃም ያዬህን ጽሑፍ አንብበን ስንጨረስ ነገር ማብላላታችንን ትተን ዝም ብለን መጋደም አልቻልንም፡፡ ዘመናችን ብዙ የሚሠራበት ሣይሆን ብዙ የሚወራበትና የሚጻፍበት መሆኑን እናውቃለንና አግራሞታችን ወሰን አልነበረውም፡፡ ጥሎብን ‘ሌላ ሥራ የላቸውም ወይ?’ እስክንባል ድረስ በዬቀኑ ብዙ እናነ(ብ)ባለን፤ ይህም ሲሆን በምንታዘበው ሁሉ እናነባለን፡፡ ሕዝባችንን የሚጠቅም ነገር ለማከናወን የዛሬ አሥራ ሁለት ዓመት ገደማ ብዙ ብንጥርም የአማራ ኤሊቶች እያወኩን ጥረታችን […]

እረፍት አደርግ ብየ ከማህበራዊ መገናኛ መድረኩ ገለል ባልኩባቸው እንደ ብርሃን ፍጥነት በሚወረወሩት ባለፉት ጥቂት ቀናት ከበርካታ ወዳጆቸ በርካታ መልዕክቶች ይደርሱኛል ። ብዙው መልዕክት ደግሞ የሚያጠነጥነው በጅዳ እና በአካባቢው በተፈናቃይ የኮንትራት ሰራተኞች አሰቃቂ ስቃይ ላይ ያተኮራል …ለነገሩ የአብዛኞቹ መልዕክቶች ብቻ ሳይሆኑ ከመልዕክቶች ጋር የሚላኩልኝ መረጃዎች እረፍት የሚነሱ ናቸው! … አዎ ተንቀሳቃሽ ምስል ጭምር በመረጃነት የታጨቀባቸውን የመልዕክት […]