ያዩ እንደሚሉት በርግጥም ዘግናኝ ነዉ።የሰዉ አንገት በገጀራ ይቀነጠሳል።እጅ፥ እግር፥ በጎራዴ ይቆረጣል።ሌላ አካል በጩቤ ይጨቀጨቃል። መንገዶች በደም አበላ ጨቅይተዋል-እየጨቀዩም ነዉ።አስከሬን በየጉርጓዱ ይከመራል።ከተንቀሳቃሽ ሥልክ እስከ ምግብ፥ ከሐብል እስከ ብስክሌት ያሉ ቁሳቁሶች ይመዘበራሉ። ቤቶች፥ መደብሮች፥ ቁሳቁሶች፥ መሳጂዶች ይነዳሉ።

የካቲት 12 የሰማዕታት መታሰቢያ እለትን በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በመገኘት በተዘጋጀው ሻማ ማብራትና የፓናል ውይይት ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ በክብር ተጋብዘዋል!!!

እሮብ ከ10፡00 ሰዓት ጀምሮ

በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት /ከካሳንቺዝ ወደ አዋሬ መንገድ የአዋሬ አጥቢያ ወንጌላውያን ቤተክርስቲያ አካባቢ!

በመጀመሪያ በአቅርቡ በተከታታይ ለአንባቢያን ያቀረብኩዋቸውን ሁለት ጽሁፎች አንብበህና ጊዜህንም ወስደህ በዝርዝር ላቀረብከው የሙግት ሃሳብ ምስጋናዮ የላቀ ነው። ለነገሩ የጽሑፌም ዋና አላማ ጉዳዩን ሕዝብ እንዲያውቀው ብቻ ሳይሆን በተነሱት ነጥቦችም ዙሪያ በአንባቢዎች ዘንድ የውይይት ሃሳብንም በማጫር ጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝም ጭምር ስለሆነ ያንተ ምላሽ እኔንም በዚሁ ጉዳይ ላይ በድጋሚ እንድመለስበት አድርጎኛል። ምንም እንኳን ባነሳሃቸው በርካታ ሃሳቦች ፍጹም […]

“ለወደቀ ዛፍ ምሣር ይበዛብታል” እንደሚሉ ሆኖ ነው መሰል አገራችንን እትዮጵያንና ሕዝቧን ከያቅጣጫው የገጠማቸው ችግር ከመቼውም የበለጠ የሚያስደነግጥና፤ ሊታመንም በማቻልበት ሁኔታ በጆሮ ለመስማት እንኳ የሚቀፍና የሚዘገንን ነው። በአባቶቻቸን፤ በአያቶቻችንና በቅድመ አያቶቻቸን ደም ፍሳሽና አጥንት ክስካሽ ተፈርቶና ተከብሮ የነበረው ዳር ድንበሯ ዛሬ “የምትፈግ ገብተህ እግርህን ዘርግተህ ተዝናንተህ ፈንጪበት፤ ሁሉም በጅህ ሁሉም በደጅህ ይሁንል” የተባለ ይመስላል። የቤልጅየምን የቆዳ […]

የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለተኛውን የ“ሚሊዮኖች ድምፅ” ህዝባዊ ንቅናቄ ስራ አስፈጻሚው ተግባራዊ እንዲደርግ ወሰነ፡፡ ብሔራዊ ምክር ቤቱ ዛሬ የካቲት 10 ቀን 2006 ባደረገው አስቸኳ ስብሰባ በሶስት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ከነዚህ ውሳኔዎች መካከል ሁለተኛው ዙር የ“ሚሊዮኖች ድምፅ” ህዝባዊ ንቅናቄ ይገኝበታል፡፡ የፓርቲው ፕሬዝደንት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሁለተኛው ዙር የ“ሚሊዮኖች ድምፅ” […]

በትላልቅ የኢትዮጵያ ከተሞች፣ በተለይ በአዲስ አበባ የመኖሪያ ቤቶች ችግር እንዳለ ብዙ ሲነገር ይሰማል። የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ከሕዝቡ ፍላጎት ጋ ያልተጣጣመበት ምክንያቱ እና መፍትሔው ምን ሊሆን ይችላል? ስለጉዳዩ የሚከታተሉ ሰዎችን አወያይተናል።

አስፈላጊውን ግብር እና ቀረጥ እስከከፈልን ድረስ የጸጥታ አስከባሪዎች ስራ እና የህገመንግስቱ ትርጉም ይነገረን::
ምንሊክ ሳልሳዊ ፦ዞር ብለን ካለፍነው የኢትዮጵያ የፍትህ ታሪክ እንዳነበብነው ከወላጆቻችን እና ከቅርብ መካሪዎቻችን እንደሰማነው የፊውዳሉ ንጉሳዊ ስርኣትም ይሁን የወታደራዊው ደርግ አገዛዞች በፍትህ አካላት ላይ ፖለቲካን ተገን አድርገው ፍትህን ያዛቡበት ቦታ አልተጠቀሰም :: የፖለቲካ ባላንጣዎቻቸውን ፍትህን ለሃሰት ተጠቅመው ማስረጃ ፈብርከው በየእስር ቤቱ በህገወጥነት አላጎሩም:: እነዚህ ሁለት ሰው በላ እና አራጅ መንግስታቶች የማንንም ህዝብ መብት በፍትህ ስም አልተጋፉም በፍርድ ቤቶች ላይ አዛዥ አልሆኑም::

ፍትህ ካለ ሰላም አለ:: ፍትህ ካለ የተደበላለቁ ስሜቶች ራሳቸውን ይገዛሉ:: ፍትህ ካለ የበላይ አካላት ለህዝብ ይታዘዛል:: ፍትህ ካለ ዲሞክራሲ ይጎለብታል:: ፍትህ ካለ ማንኛውም ሰው በነጻነት ይዘዋወራል:: ፍትህ ካለ እያንዳንዱ ሰው የራሱን መብት ያቃል;የሌላውንም ያከብራል … ፍትህ ካለ የጸጥታ ሃይሎች የወጡበትን አብራክ አይረግጡም የእናት ሃገር ማህጸንን አያደሙም ህዝብን አያስለቅሱም ወዘተ….. ስለዚህ ፍትህ ላይ ማተኮር የእያንዳንዱ ዜጋ ግዴታ ነው::

አሁን ግን እያየነው ያለው ፍትህ ከሁለቱ መንግስታት በተለየ ሁኔታ ህዝብን በፖለቲካ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ መስክ ቁም ስቅሉን እያሳየው ነው:: የሃገሪቱ ህገ መንግስት ከሚፈቅደው ውጪ እና ውጪ በፖለቲካ መስክ የአይናቸው ቀለም ያላማረ ተቃዋሚዎች ይደበደባሉ ይታሰራሉ ይገረፋሉ በፍርድ ቤት በሃሰት መረጃ ከህግ ትእዛዛት ውጭ የረዥም አመት እስር ይከናነባሉ:: እንደ መንግስት ባለስልጣናት ሳይሰርቁ ደፋ ቀና ብለው ያፈሩት ንብረት ይወረሳል::ከዛም አለፍ ካለ በአደባባይ ይረሸናሉ:: በደህንነት ሃይሎች ይገደላሉ:: ይህ የሚያሳየው የጸጥታ ሃይሎች ከህግ በላይ ሆነው ፍትህን መግደላቸው ነው:: የፖለቲካ ድርጅቶች እንዳይንቀሳቀሱ የጸጥታ ሃይሎች እንቅፋት ከመሆን አልፈው ወደ አንድ ፓርቲ ያደላ ኮንትሮባንዳዊ ፖለቲካ እየፈጸሙ ነው:: በፓርቲዎች ላይ ወከባ እየደረሰ ነው:: የጸጥታ ሃይሎች ደሞዝ የሚከፈላቸው ከህዝብ ኪስ ሆኖ ሳለ የሚያዋክቡት እና ፍትህ የሚያጎድሉበት የሚያስለቅሱት ግን ይኸው ደሞዝ የሚከፍላቸውን ህዝብ ነው::

ህገ መንግስት አዋጅ መመሪያ አያለ መንግስት የሚያወጣው እና ፓርላማ አጸደኩ የሚለው ለህዝቡ ምንም የሰጠው ትርጉም የለም ጠቀሜታውም ዜሮ ነው ህዝቡ በኑሮ ውድነት እየደቀቀ ባለበት ሰአት ላይ ጥቂት ሰዎች ገነው በኢኮኖሚ መበልጸጋቸው በማህበራዊው መስክ የሚደረገውን ህብረተሰባዊ ጠቀሜታዎችን ማሳጣታቸው የፍትህን በአደባባይ መሰቀል ያመለክታል:: ይህ ሁሉ ተያይዞ የጸጥታ ሃይሎች ህዝብን አይዞህ ባይነታቸውን ትተው የባለስልጣናትን ወንበር እየጠበቁ ነው:: ስለዚህ ለመንግስት አስፈላጊውን ግብር እና ቀረጥ እስከከፈልን ድረስ የጸጥታ አስከባሪዎች ስራ እና የህገመንግስቱ ትርጉም ይነገረን::ፍትህ ላይ እናተኩር::

ጋዜጠኞች ቁጭ ብለው የሞሪኒሆን ፈረስ ሲጠብቁ ገንዘቤ 3 ሪኮርዶችን ሰበረች:: ከአድዋ ድል ቀጥሎ የኢትዮጺያ ሰንደቅ አላማ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ ያደረገው አትሌቲክስ ነው:: አትሌቶቻችን በሄዱበት ውድድር ሁሉ ድልን ተጎናፅፈው አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን አለም ላይ ከፍ አድርገው ያውለበልቡታል::

እንግሊዞች እግር ኳስን በፍቅር ይወዱታል:: አለም ላይም ሊጋቸው ተወዳጅ እንዲሆን በሚዲያቸው በመጠቀም ተፅኖ አሳድሮዋል:: በአትሌቲክስም ከሀገራቸው አንድ አትሌት ትንሽ ውድድር ካሸነፈ ብዙ ያወሩለታል:: አለም ላይ ያሉ ተርጓሚ ጋዜጠኞችም እዬንኑ ግነት አግንነው ያወሩታል::

በእንግሊዝ ሚዲያ ቀኝ ከተገዙ ሀገራት መካከል የኢትዮጺያ ሚዲያ አንዱ ነው:: ስለ ቀነኒሳ 2ኛ መውጣት ይልቅ ስለ ሞፋራ ሰባተኛ መውጣት ብዙ ይወራለታል:: “የእንግሊዝ ሚዲያ ጅራፉን ያነሳል የኢትዮጺያ ሚዲያ ጅራፉን ያጨዋል”

ገንዘቤ ዲባባ ሰሞኑን አለም ላይ በ15 ቀን 3ሪኮርዶችን እንደ ከረሜላ ኮረሻሽማለች:: የኢትዮጺያ ኔትዎርክ ሳይስተካከል እሷ 3 ሪኮርዶችን ጨፈላልቃለች:: ገንዘቤ በኢትዮጺያ ሚዲያ ሽፋን በበቂ ሁኔታ አልተሰጣትም ብዬ አስባለው:: የሞሪኒሆ ስለ ፈረስ ወሬ በትንታኔ እየቀረበ የገንዘቤ 3 ሪኮርዶች እንደ ዜና ብቻ ቀርበው ሲታለፉ ያስተዛዝባል:: ኢትዮጺያ ውስጥ የእግር ኳስ ጋዜጠኞች እንጂ የስፖርት ጋዜጠኞች ዬሉም የሚለውን ያረጋግጣል::

“ውድድሩ የግል ነው ሀገርን አይወክልም” የሚል ክርክር ሊመጣ ይችላል…. ግን ደደቢት እኮ በአፍሪካ ቻምፒዮንስ ሊግ ሲሳተፍ የግል ውድድር ነው ሲጠራ የኢትዮጺያው ደደቢት ተብሎ ነው:: በአትሌቲክስም ተመሳሳይ ነው:: “ኢትዮጺያዊቷ (ዲባባስ ፋሚሊ) ገንዘቤ ዲባባ አለም ላይ ነገሰች” ነው የሚባለው::

ገንዘቤ እንደ ምንያህል በጋዜጣ “እንግሊዛዊ ብሆን የኢትዮጺያ ሚዲያ ብዙ ያወራልኝ ነበር” ብትል የእግር ኳስ ጋዜጠኞች እኮ ተሰደብን ብለው በማህበራቸው በኩል መግለጫ ያወጡ ይሆናል:: ምነው ባለች ያስብላል::

ገንዘቤ አቦ እንኳን ተወለድሽ…. እንኳን ሰባበርሽ…. እንኳንም ደስ አለሽ…. ኢቲ ፉፋ

“ሪኮርዱ ቦሌ ፈረሱ ጉለሌ”
የቡና ቁርስ – በEphrem Amare

ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በራሳቸዉ እጅ የጻፉት ማኒፌስቶ በግልጽ እንደሚያሳየን እነዚህ ዘረኞች ጫካ ገብተዉ የትጥቅ ትግል እንዲጀምሩ ያነሳሳቸዉ በአማራ ህዝብ ላይ ያላቸዉ ጥላቻና መሰረተ ቢስ ቂም በቀል ነዉ። ይህ ጥላቻቸዉ ደግሞ አማራዉን በመግደልና ግዛቱን ሲያሻቸዉ ከራሳቸዉ ክልል ጋር በመቀላቀል አለዚያም ለጎረቤት አገሮች በመሸለም ብቻ ሊቆም ወይም ሊገታ አልቻለም። እነሆ የአማራው ህዝብ የወያኔ ዘረኞች ዋነኛ ዒላማ ሆኖ የአገዛዙን የግፍ ፅዋ ያለማቋረጥ መጋት ከጀመረ ድፍን 23 አመታት ተቆጠሩ። ፋሽስቱ ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ብሔራዊ ስሜት በማምከን ፣ የዘመናት ተገዥነቱን ለማረጋገጥ በቅድሚያ የአማራን ሕዝብ ማንነት ማጥፋት ፣ የአማራን ሕዝብ ስነ ልቦናዊ ጥንካሬ መስለብ እና አንገቱን ማስደፋት አስፈላጊ መሆኑን በጽናት ያምናል። ይህ በመሆኑም ፣ በአማራ ህዝብ ላይ በወያኔ የሚፈፀመው ግፍ እና በደል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ስር እየሰደደና እየከፋ በግልፅም በስውርም በተቀነባበረ መንገድ ቀጥሏል።
ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ብሔራዊ ስሜት በማዳከም፣ ለዘመናት ሥልጣን ላይ ለመቆየት ያገለግለኛል ብሎ ዘመቻ ከከፈተባቸው ብሄረሰቦች አንዱና ዋንኛው የሆነው የአማራ ህዝብ በራሱ ማንነት እንዲያፍርና ብሄራዊ ኩራቱ እንዲሟሽሽ ላለፉት 23 አመታት በግብር ከፋዩ ህዝባችን ገንዘብ በሚተዳደሩ የመንግሥት መገናኛዎች ሳይቀር ከፍተኛ የስነ ልቦና ዘመቻ ተካሂዶበታል። በአማራ ሥም አማራውን የወያኔ አገር የማፍረስ አጀንዳ አስፈጻሚ ለማድረግ የተሾሙበት ተላላኪዎች በህወሃት አለቆቻቸው የተሰጣቸውን ተልዕኮ ለመፈጸም በተለያዩ አጋጣሚዎች አማራውን የሚያዋርድና የሚዘልፍ አስተያየት በአደባባይ ሲሰጡ ሰምተናል አይተናል። ይህ ተግባራቸው ለአማራ ህዝብ ቅንጣት ታህል ክብርና ፍቅር ያልነበረው ዘረኛው አለቃቸው መለስ ዜናዊ ከዚህች አለም በሞት ከተሰናበተ ቦኋላም ተጠናክሮ ቀጥሎአል።
የህወሃት መሪዎች አማራው ላይ ያላቸው ጥላቻ ወደሥልጣን ከመጡ ቦኋላ የተፈጠረ ሳይሆን ገና በጫካ ትግል ላይ በነበሩበት ወቅት በጻፉት የድርጅታቸው የፖለቲካ መረሃግብር በግልጽ እንደተቀመጠው ለትግል ያነሳሳቸውም አማራ ብለው የሚጠሩት ብሄረሰብ እንወክለዋለን በሚሉት ብሄረሰብ ላይ አድርሰዋል በሚሉት የፈጠራ በደልና ቂም እንደሆነ አረጋግጠዋል። ላለፉት 23 አመታት አማራው ከሚኖርበት የራሱ ክልሉ ሳይቀር እንዲፈናቀል ተደርጎ እየደረሰበት ያለው በደል የዚህ የቆየ የወያኔ ቂም በቀል ውጤት መሆኑ ግልጽ ነው።
ሰሞኑን አለምነው መኮነን የተባለ ሆድ አደር የባንዳነት ተግባሩን በመፈጸም በአለቆቹ ፊት ግርማ ሞገስ ለማግኘት እመራዋለሁ የሚለውን የአማራ ህዝብ እጅግ በወረደና ጸያፍ በሆነ ቃላት ያን ያህል ሲዘባበትበት መደመጡ አማራውን ብቻ ሳይሆን መላውን የአገራችንን ህዝብ አስቆጥቶአል።
በእርግጥ አለምነው መኮንን አማራን በማዋረድ የመጀማሪያው የወያኔ ተላላኪ አይደለም። የህወሃቶቹን ቁንጮዎች ስድብና ዘለፋ ወደ ጎን ትተን በወያኔ የዘር ፖለቲካ አማራውን እወክለዋለው የሚለው ብአዴን ከፍተኛ አመራር እነ እነታምራት ላይኔ ተፈራ ዋልዋና በረከት ስሞን በተለያየ ወቅት ንቀትና ስድባቸውን አሰምተውናል። አለምነህ መኮንን እንደዚያ በወረደ ቃላት አማራውን ሲያዋርድ በስብሰባው አዳራሽ የነበሩ ህወሃት የፈጠራቸው የብአዴን ልጆች በሳቅ ካካታ ሲያጅቡት እንደነበረ እድሜ ለኢትዮጵያ ሳታላይት ቴለቪዥን ከአዳራሹ ሾልኮ ለህዝብ ጀሮ የደረሰው የኦዲዮ ድምጽ አጋልጦአል።
ሁላችንም፤ እንደምንገነዘበው ወያኔ የገዛ ብሄረሰባቸውን ረግጠው በመግዛት የጥፋት አላማውን እንዲያስፈጽሙለት በራሱ አምሳል ከፈጠራቸው ድርጅቶች አንዱ የሆነው ብአዴን በታሪኩ አንድም ለህዝቡ የቆመ መሪ አፍርቶ አያውቅም። ለራሳቸውና ከአብራኩ ለተገኙት ህዝብ ምንም አይነት ክብር የሌላቸው የብአዴን መሪዎች ጣሊያን አገራችንን በወረረችበት ወቅት ለሆዳቸው ሲሉ ከባዕድ ጋር ተሻርከው ህዝባቸውን ካስጨፈጨፉት ባንዳዎች የከፋ ተግባር በህዝባቸው ላይ እየፈጸሙ ነው።
ወያኔ ለም የሆነውን የአማራ ግዛት እንዳለ የኔ ነው ወደሚለው የትግራይ ከልል ሲወስድ፤ በአማር ክልል ወስጥ በቀሩት ለም ቦታዎች የህወሃት ታማኝ ካድሬዎችን ከያሉበት እያጓጉዘ ሲያሰፍር፤ የአገሬውን አርሶ አደር እያፈናቀለ ለራሱ ታማኞች ለም መሬት እየሸነሸነ ለሰፋፊ እርሻ አገልግሎት ሲያድል አማራውን እወክለዋለው የሚለው ብአዴን አንድም የተቃውሞ ድምጽ አሰምቶ አያውቅም። የብአዴን መሪዎች የወያኔን ተልዕኮ ከማስፈጸም አልፈው በሟቹ አለቃቸው በመለስ ዜናዊ ሥም እየማሉ በአገራችን ኢትዮጵያና በሚያስተዳድሩት የአማራ ህዝብና ክልል የሚፈጽሙት በደል ብዙ ነው። ልክ እንደ ብአዴን የዘረኛውን ወያኔ የጥፋት ፖሊሲ ለማስፈጸም ከሚተጉት አንዳንዶቹ አማራውን ከክልላቸው ለማጽዳት በቤኒሻንጉል፤ በቤንች ማጅና ጉራፈርዳ ወረዳ እርምጃ ሲወስዱና ንብረታቸውን ቀምተው ባዶ እጃቸውን ሲያባርሩዋቸው ብአዴን ቁጭ ብሎ ተመልካች ነበር። ከአማራ ክልል ጋር የሚዋሰነው ዳር ድንበራችን ላይ በተነሳው የባለቤትነት ጥያቄም ላይ የወሰደው አቋም በህዝብና በታሪክ ፊት ውሎ አድሮ የሚያስጠይቀው ነው።
እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደሚገነዘበው ፋሽስቱ ወያኔ በአገራችንና በህዝባችን ላይ እየፈጸመው ያለው አንዱን ዘር ከሌላው ጋር የማጋጨትና በተናጠል ደግሞ እያንዳንዱን ለይቶ የማዋረድና የማጥፋት ተግባር አሁን የተጀመረ ክስተት አይደለም። የቆየና ወያኔ ህዝባችንን ከፋፍሎ ለመግዛት ከመነሻው ሲጠቀምበት የነበረ ስልት ነው። ስለዚህ ወያኔ በራሱና በተላላኪዎቹ አማካይነት ላለፉት 23 አመታት በህዝባችን ላይ እየፈጸመ ያለውና የፈጸመው ግፍ፤ ውርደትና መከራ እንዲያበቃ ሁላችንም እጅ ለ እጅ ተያይዘን መነሳት ይኖርብናል። በወያኔ ከፋፋይ አጀንዳ እርስ በርስ እየተናቆርን የጥቃት ሰለባ የመሆናችንን እንቆቅልሽ ለማስቀረት ከኛ በላይ ሃይል ያለው አይኖርም።
በተለይ ግንባር ቀደም የወያኔ ሰለባ የሆነው የአማራ ህዝብ ወጣት በጫንቃው ላይ ተፈናጠጠው የወያኔን የጥላቻና የበቀል እርምጃ የሚያስፈጽሙትን ከአብራኩ የተገኙ ባንዳዎች ላይ የጥቃት ክንዱን መሰንዘርና ለክብሩ መቆሙን ማሳየት ያለበት ጊዜው አሁን ነው።
በብአዴን ሥር የተሰባሰቡ የአማራ ተወላጆች፤ በመከላኪያ ሠራዊቱ፤ በፖሊስና በደህንነት፤ በወጣት ማህበር፤ በሠራተኛ ማህበርና በተለያየ ሙያ ማህበር ብአዴን ራሱ ያደራጃቸው ሁሉ ለክብራቸውና ለኢትዮጵያዊ ማንነታቸው ሲሉ ከትግሉ ጎን በመሰለፍ የወያኔን ዕድሜ ለማሳጠር ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሚያካሂደውን ትግል እንዲቀላቀሉ ንቅናቄው ጥሪውን ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

ኢሕአዴግ የዘረጋቸው ትላልቅ ፕሮጅክቶች የሕዝቡ ተሳትፎ እንደሚጠይቁ የተገነዘቡት በርካታ የኢሕአዴግ ደጋፉዎችና አባላት፣ ኢሕአዴግ መሰረታዊ ማሻሻያዎችን እንድያደርግ፣ የፖለቲካ ምህዳሩን እንዲያሰፋ፣ እስረኞችን እንዲፈታ ዉስጥ ዉስጡን ጫና እያደረጉ እንደሆነ ከኢሕአዴግ አካባቢ ያሉ ምንጮቻችን ይገልጻሉ።

ትግራይን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች በኢሕአደግ ዘንድ ባሉ የመልካም አስተዳደር፣ የኢፍትሃዊነት ችግር ላይ፣ እንዲሁም አልቻል በተባለው የኑሮ ዉድነት የተነሳ፣ የሚነሱ ተቃዉሞዎች እየተበራከቱ መሆኑ ያዩ ኢሕአዴግን የሚደግፉ ወገኖች፣ ኢሕአዴግ የሕዝብን ጥያቄ እንዲያዳምጥ፣ ከሕዝብ ግር እንዲታረቅ ጥሪ እያቀረቡ ናቸው።
«የዛሬዎቹ ኢሕአዴጎች የዚህ የደሃ ሕዝብ እንባና ሮሮ የማያትያቸው ናቸው»
«እዚህ አገር ላይ መልካም አስተዳደር ድራሹኑን ጠፏቷል»
ኢሕአዴጎችን «እነዚህ ክፉ የጫካ ሹሞች ….»
«ሕዝቡ ተማሯል»
«አስተዳደሩ ተበላሽቷል። የአቶ መለስን የቀድሞ አባባል ልዋስና በስብሷል ማለት ይቻላል»
«እዚህ ክፍለ ከተማ ሕዝብ አስለቅሶ በሙሰኝነት ሲነሳ የሰማችሁት ግለሰብ፣ የድርጅት አባል ስለሆነ ተብሎ ወዲያኛው ክፍለ ከተማ ሲሾም ታዩታላችሁ። ይሄ ነገር ምንድን ነው ስትሉ ,አይ ግድ ለየም ሂሱን ወጧል የሚሉት አነጋገር አላቸው»
«የሕዝብ እንደራሴ ተብለው የተመረጡ፣ ፓርላምዉን ያጣበቡ ብዙ ናቸው። መቼ ነው ወደ መረጣቸው ሕዝብ ሄደው ምንድን ነዉ ችግሩህ ያሉት ?፡»
እነዚህ አባባሎች የተናገሩት አቶ ቢኒያም ከበደ ይባላሉ። የኢትዮጵያ ፈርስት ድህረ ገጽ አዘጋጅ ናቸው። እርሳቸው ገለልተኛ መሆናቸውን ቢናገሩም የገዢዉ ፓርቲ ኢሕአዴግ ደጋፊ እንደሆኑ የነገርላቸዋል። በተለይም ሟቹን ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊን በጣም እንደሚወዱና እንደሚያደንቁ በተለያዩ ጊዜ ሲገልጹ ተሰምተዋል።፡
አቶ ቢንያም በአሁኑ ጊዜ መኖሪያቸውን ከአሜሪካን ወደ አዲስ አበባ በማዞር ከዚያዉ ከአገር ቤት አልፊ አልፎ ዘገባዎች ያቀርባሉ።
በቅርቡ በድህረ ገጻቸው ላይ፣ ባልተጠበቀ መልኩ፣ በኢሕአዴግ ላይ ጠንካራ ትችት አሰምቶናል። አቶ ቢንያም ኢሕአዴግ እየበሰብሰ እንደመጣ በመናገር በአገሪቷ መልካም አስተዳደር ፈጽሞ እንደጠፋ፣ ህዝቡ በኢሕአዴግ ካድሬዎች እየተጎላላ እንዳለ ይናገራሉ። የዉሃ እጥረት ከፍተኛ ደረጃ በመድርሱ ጀሪካን እየያዝን ነው የምንወጣው ያሉት አቶ ቢኒያም፣ የመብራት ችግር በጣም አሳዛኝ መሆኑን ሲገለጹ፣ «መብራቱ አሥሬ እየበራና እየጠፋ፣ የምሽት ዳንስ ቤት ነዉ የሚመስለው» በማለት ነበር።
99.9 በመቶ የሚሆኑ በፓርላማ የሚቀመጡ የሕዝብ እንደራሴዎች ላይ ሳይቀር፣ አቶ ቢኒያም ያላቸውን ምሬት ገልጸዋል። « በቴንትድ (በጠቆረ) መስኮት መኪና ዉስጥ ተሸሸገው ፣ ከሕዝቡ የማይገናኙ፣ የተደበቁ፣ የሕዝብኑን ብሶት የማያዳምጡ ናቸው» ሲሉ የፓርላማ ተወካዮች ምን ያህል የማይረቡ መሆናቸውን አቶ ቢኒያም ለማስረዳትም ሞከረዋል።
ኢሕአዴግ የሕዝብ ጥያቄ የማይሰማና ሕዝብን የማያከብር ከሆን፣ ይሄ የመረረዉ ሕዝብ ቅጣቱን እንደሚያወርድ ያስጠነቀቁት አቶ ቢኒያም፣ ኢሕአዴግ አፋጣኝ ለዉጦች እንዲያመጣ፣ ለሕዝብ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥና ሕዝብን እንዲያከበር መክረዋል።

ለአቶ ያሬድ ኃ/ማርያም አንዳንድ መልሶች

ተከልሚካኤል አበበ – ቶሮንቶ

እንደመግቢያ፤ ያሬድና ጽሁፉ

1-         አቶ ያሬድ ሀይለማሪም (ያሬዶ) ለሰብአዊ መብት መሟገት አመል ሆኖበት (አመሉ፤ አዎንታዊ በሆነ መልኩ ማለቴ ነው)፤ ከጥቂት ቀናት በፊት አንድ ጽሁፍ አውጥቶ ነበር፡፡ ያንን ጽሁፍ ተከትሎ አንዳንድ በብእር ስም ጀርባ የተደበቁ ተቺዎች አበሳጩት መሰለኝ ሌላ ተከታይ ሁለተኛ ጽሁፉም ጽፎዋል፡፡ የኔ አስተያየት በመጀመሪያው ጽሁፍ ላይ ነው፡፡ ከሞላ ጎድል ጽሁፉ፤ ግንቦት ሰባት፤ ለኢትዮጵያ እንታገላለን ብለው ኤርትራ የገቡ ወጣቶች ላይ፤ ከኤርትራ መንግስት ጋር በመተባበር፤ ብዙ ግፍ እየፈጸመ ወይንም እያስፈጸመ ሲሆን፤ መገናኛ ብዙሀን ይሄ ግፍ ሲፈጸም እያዩ ዝም ማለታቸው፤ አግባብ አይደለም የሚል ነው፡፡ የያሬዶ ጽሁፍ ሸጋ ነበር፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

አዎ! የኢህአዴግ መንግስት የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት በMonopoly መቆጣጠሩ ይታወቃል። ለዚህም ምክንያት አለው። በህወሓት/ኢህአዴግ የፖለቲካ ኢኮኖሚ ፍልስፍና መሰረት ስልጣን የሁሉም ነገር መሳርያ ነው። ስለዚህ ስልጣንን መቆጣጠር ግድ ነው። ስልጣን ለመቆጣጠር ደግሞ ኢኮኖሚውን መቆጣጠር ያስፈልጋል። ለዚህም ነው ስልጣን ለመቆጣጠር ሲሉ ኢኮኖሚውን የሚቆጣጠሩት። ኢኮኖሚውን ለመቆጣጠር ትርፋማ የሆኑ ሴክተሮችና የኢኮኖሚን እንቅስቃሴ የሚቆጣጠሩ ተቋማት በmonopoly መያዝ ያስፈለገው። ትርፋማ ከሆኑ ሴክተሮች ኢትዮቴለኮምና […]

በሊቢያ እአአ የፊታችን የካቲት 20፣ 2014 ዓም አዲስ ምክር ቤት ይመረጣል። ከያካባቢው 20 አባላት፣ ባጠቃላይ 60 አባላት የሚጠቃለሉበት ይኸው ምክር ቤት በሚቀጥሉት ወራት ለሀገሪቱ አዲስ ሕገ መንግሥት የማርቀቅ ስራ ይጠብቀዋል። ይህ ስራው ቀላል እንደማይሆን እና የምርጫው ሂደትም በተረጋጋ ሁኔታ መከናወኑ እንደሚያጠራጥር ታዛቢዎች ገምተዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታየውን ሕገወጥየዱርእንስሳትአደንናንግድንበተመለከተ ከመላ ዓለም የተውጣጡ የመንግሥት፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች እና ጠበብት በዚህ ሳምንት ለንደን ብሪታንያ ስብሰባ አካሄዱ። ለተፈጥሮ ጥበቃ እና ለዱር አራዊት ህልውና የሚሟገቱት ጠበብት እንዳመለከቱት፣

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮና መኖርያ ቤት በሚገኝበት ታላቁ ቤተ መንግሥት አጥር ዙሪያ ገባው ላይ የሚገኘው የመስቀል ቅርጽ፣ የእስልምናና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ሃይማኖቶች መሪዎችን አነጋገረ፡፡
የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር ባለፈው ሳምንት ቅዳሜና እሁድ በሐዋሳ ባካሔደው የምክክር መድረክ ላይ ‹‹አገሪቱና መንግሥቱ የእኩልነትና የዜጎች መንግሥት ነው፤›› ያሉት የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸኽ ኪያር ሙሐመድ አማን÷ ከቀድሞው ሥርዐት አንጻር አሁን የሚያበረታቱ ነገሮች እንዳሉ ገልጸዋል፡፡

ይኹንና በሴኩላሪዝምም ቢኾን ፍጹምነት ባለመኖሩ ‹‹አገር የጋራ ነው ከተባለ በኋላ የጎደለ ነገር አለ፤›› በሚል አዘውትረው ጥያቄ የሚያቀርቡላቸው ሰዎች መኖራቸውን ሸኽ ኪያር ጠቅሰዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ ይቀርቡልኛል ካሏቸው ጥያቄዎች መካከል ‹‹ለምሳሌ፡- ታላቁ ቤተ መንግሥት በመስቀል ነው የተከበበው፤ ይህ መጥፎ ነገር ሊያመለክት ይችላል›› የሚሏቸው እንዳሉ ተናግረዋል፡፡
ታላቁን ቤተ መንግሥት የከበበውን መስቀል፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፊት ለፊት እንደቆመው የደርግ ሐውልት ያህል እንዲታይ በሚል ለጥያቄው መልስ እንደሚሰጡ የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፣ “በአክሱም አንዲት ጎጆ መስጊድ እንኳ ለመገንባት እንዴት አልቻልንም?” ተብለው ሲጠየቁ የዚህን ያህል ‹‹የቀልድ መልስ እንኳ ለመስጠት አልተቻለም፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹ነገሮችን ለማከም መቅደድ አለብን›› የሚል የዐረብኛ ብሂል እንዳለ የጠቀሱት ፕሬዝዳንቱ፤ ሁልጊዜ ጥላሸት መስለው ይታያሉ ያሏቸውን ችግሮች ለመፍታትና መልስ ለመስጠት ይቻላል ወይስ አይቻልም ሲሉ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል፡፡

በጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሸኽ ኪያር ጥያቄ ላይ ፈጥነው አስተያየት የሰጡት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ፣ ሸኽ ኤልያስ ያቀረቧቸው ነገሮች ሌሎች ስለጠየቋቸው እንጂ ራሳቸው ፕሬዝዳንቱ አምነውበት እንዳልሆነ ከአነጋገራቸው መረዳታቸውን ገልጸዋል፡፡
በጥያቄው ስለ መስቀልም ስለ አክሱምም መነሣቱን ያስታወሱት ፓትርያርኩ፣ ‹‹ሁለቱም የቆዩ ናቸው እንጂ አሁን የተፈጠሩ አይደሉም፤›› ሲሉ ተናግረዋል፤ ‹‹በዚህ ግቢ (ስብሰባው በተካሔደበት ሌዊ ሪዞርት ማለታቸው ነው) ያየናቸው ዋርካዎች ድሮ የነበሩ ናቸው፤ አሁንም ይጠቅማሉ፤ ከቆረጥናቸው ጉዳት ነው፤ ከኖሩ ይጠቅሙናል፤›› በማለት የቆየው ታሪክ መጠበቅ እንዳለበት በምሳሌ አስረድተዋል፡፡ ‹‹የመስቀሉ ቅርጽ የቆየ ታሪክ ነው፤ በታሪካዊነቱ ተከብሮ ተጠብቆ መኖር አለበት፤ በአክሱም ስላለው ነገር ከተነሣም የእኛም ጥያቄ ወደ ረጅምና ዝርዝር ነገር ይሔዳል፤›› በማለት የሁሉም ታሪክ በየራሱ መታወቅና መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

መከባበርም መቻቻልም እጅግ አስፈላጊ መሆኑን የገለፁት ፓትርያርኩ፣ “አገሩ የኹላችንም ነው፤ የነበረው ታሪክ ደግሞ በታሪካዊነቱ ተከብሮ መኖር አለበት” በሚል ለሸኸ ኪያር ጠያቂዎቹ ምላሽ መስጠት እንደሚቻል በፈገግታ የታጀበ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ የውይይቱ ተሳታፊ ከኾኑ ሌሎች የሃይማኖት ተቋማት መሪዎችም ሆነ የምክክር መድረኩን ከመሩት የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች የተሰጠ ምላሽና አስተያየት አልነበረም፡፡
የመስቀልና ዘውድ አምሳል በተቀረጹባቸው አጥሮች የተከበበው ታላቁ ቤተ መንግሥት፣ የምኒልክ ቤተ መንግሥት በመባል የሚታወቅ ሲሆን ንጉሡ በ1878 ዓ.ም ያሠሩት መንበረ መንግሥታቸው ነበር፡፡ የተለያዩ መኖርያ ቤቶችን፣ እልፍኞችንና አዳራሾችን እንዲሁም ቤተ ጸሎቶችን ያካተተው ቤተ መንግሥቱ÷ የታዕካ ነገሥት በኣታ ለማርያም ገዳም፣ የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እና የሥዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ይዋሰኑታል፡፡

በተለይ የዘውድ አምሳል በጉልላቱ ላይ የሚታይባት የበኣታ ለማርያም ገዳም የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ፣ የንግሥታቱ እቴጌ ጣዪቱና ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ እንዲሁም የልዕልት ፀሐይ ኃይለ ሥላሴ ዐፅሞች ያረፉበት ሲኾን የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮና መኖርያ የኾነው ከደርግ መንግሥት ጀምሮ ነው፡፡
ለሁለቱ የሃይማኖት መሪዎች መነጋገርያ የኾነው ጉዳይ መነሻ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ የግጭትና ሰላም ጥናት ረዳት ፕሮፌሰር በኾኑት ዶክተር ታረቀኝ አዴቦ የቀረበው ‹‹በአገራችን የሃይማኖት ተቋማትና ተከታዮች በሰላም አብሮ የመኖር ወርቃማ ተሞክሮና የማስቀጠል ፋይዳው›› የተሰኘ ፅሁፍ ነው፡፡

የአገራችን ሕዝቦች ‹‹እንኳን በብርሃን ዘመን በጨለማው ዘመንም ጭምር›› የሃይማኖት ብዝሐነትን በመሠረቱ ያለመግባባትና የግጭት መነሻ ሳያደርጉ በሰላም አብረው እንደኖሩ የሚያትተው የጥናት ጽሑፉ፣ በሰላም አብሮ መኖር÷ ብዝሐነትን እንደ ነባራዊ ኹኔታ የመቀበል፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ የትግል ስልት የመከተል፣ የብዝሐነቶች ነጻነትና እኩልነት መረጋገጥ አስተሳሰቦች ጥምረት መኾኑን ይገልጻል፡፡
የሃይማኖት መሪዎች በሰላም አብሮ የመኖር አርኣያ በመኾን ከቅድመ አያቶቻችን ጀምሮ ለዘመናት የቆየውን በሰላም አብሮ የመኖር ዕሴት በውስጣቸውም ይኹን በመካከላቸው፣ አስተሳሰቡንና ተግባሩን በማስፈን ለሚቀጥለው ትውልድ የማስተላለፍ ታሪካዊ አደራና የዜግነት ግዴታ እንዳለባቸው ያስገነዝባል- ጥናታዊ ፅሁፉ፡፡

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግሥት፣ ያለፈውን ታሪካዊ እውነታ ተቀብሎና ዕውቅና ሰጥቶ፣ የወቅቱን ነባራዊ ኹኔታ መሠረት አድርጎ ወደፊት በመቃኘት፣ በአገራችን ብዝሐነትን ተቀብሎ በተገቢው ኹኔታ ለማስተናገድ አቅጣጫ ያስቀመጠ ብቸኛው የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ነው የሚሉት ሌሎች የጥናታዊ ጽሑፍ አቅራቢዎች÷ መንግሥታዊ ሃይማኖትን ከሠየመው የንጉሣዊው ሥርዐት ሕገ መንግሥትና ፀረ – ኹሉ ከነበረው የወታደራዊ ሥርዐት ሕገ መንግሥት፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግሥት የሚለይባቸውን መርሖዎችና ድንጋጌዎች ዘርዝረዋል፡፡
የሃይማኖት ተቋማት ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችን ለተከታዮቻቸው የማስተማር ሓላፊነታቸውን በተጠናከረ መልኩ መወጣት ይኖርባቸዋል ያሉት ጽሑፍ አቅራቢዎቹ፣ የመንግሥትና የሕዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትና ሠራተኞችም ሴኩላሪዝምንና ሃይማኖት ነክ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በጥብቅ በመተግበር፣መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸውን ያረጋገጠውን ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ ማስከበር እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡

በሃይል ለመግዛት መሞከር የውድቀት ምልክት ነው!!
ለሂሊናቸው ሶይሆን ለሆዳቸው ብቻ የሚኖሩና ለታሪክ ደንታ ቢስ የሆኑ ሁሉ በኢህኣዴግ የተዛባ ሚዛን ልማታውያን ናቸው፡፡ ልማታዊ የሚል መዳልያ ከኢህኣዴግ የሚገኝ ትልቅ የክብር ሽልማት ነው፡፡

የጠ/ሚ ሃ/ማርያም ደሳለኝ ቆይታ ከልማታውያን ጋዜጠኞች
ልማታዊ ጋዜጠኛ፣ ልማታዊ ነጋዴ፣ ልማታዊ መመህር፣ ልማታዊ ሃኪም፣ ልማታዊ ቄስ፣ ልማታዊ ሼክ—- ልማታዊ የሚል መዳልያ ከኢህኣዴግ የሚገኝ ትልቅ የክብር ሽልማት ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ኣይነት ሽልማት የሚሰጣቸው የተወሰኑ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህም ኢህኣዴግ በህዝብ ላይ የፈለገውን አፈና ሲፈፅም ፣ የሃገር ኢኮኖሚ በሙስና ሲበዘብዝ ለምን ያማይሉ፣ ለሂሊናቸው ሶይሆን ለሆዳቸው ብቻ የሚኖሩና ለታሪክ ደንታ ቢስ የሆኑ ሁሉ በኢህኣዴግ የተዛባ ሚዛን ልማታውያን ናቸው፡፡

ሁላችን እንደ ተከታተልነው 04/06/06 ዓ/ም ከሁለት ሰዓት ዜና በኃላ ጠ/ሚ ሃ/ማርያም ደሳለኝ እነዚህ ኣብዛኛዎቻቸው ልማታውያን ጋዜጠኞች ጠርተው የቼዝ ጭዋታ (chess play) በማካሄድ ሰዓታቸውን ኣሳልፈዋል፡፡ በዛ ጭዋታ ላይ የነበሩ ጋዜጠኞች ኣብዛኛዎቻቸው ልማታውያን ስለነበሩ ሲያቀርብላቸው የነበሩ ጥያቄዎችም ልማታውያን ናቸው፡፡ ነገር ግን ኣንድ ሁለት የሚሆኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ጥያቄ በተለይ ስለ መብራት ማቋረጥ፣ ወሃ እጥረት፣ የሞባይል ኔትወርክ ችግር፣ ስለነጋዴዎች ስጋት፣ ስለኢኮኖሚያዊ ሁኔታና ስለሚቀጥለው ምርጫ ዝግጅት — ወዘተ መጠየቃቸውና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ኣራባና ቆቦ የሆነ መልስ እንደ ተሰጣቸው ጆራችን ሰምተዋል፡፡

ስለሚቀጥለው ምርጫ የተነሳ ጥያቄ ሲመልሱ
ተቋዋሚ ፓርቲዎች በሚቀጥለው ምርጫ ወደ ፓርላማ እንዲመለሱ ምን የታሰበ ነገር ኣለ? ለሚለው ጥያቄ ሲመልሱ “የሚወዳደር ኣካል ራሱ ኣዘጋጅቶ መቆየት ኣለበት ካልሆነ በኢህኣዴግ ለተቋዋሚ ፓርቲዎች የሚሰጥ ትሩፋት ኣይኖርም” የሚል አስገራሚ መልስ ሰጥተዋል፡፡
ጥያቄው ግልፅና የማያሻማ ነበር፡፡ የጋዜጠኛዋ ጥያቄ ኣሁን ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ (በጣም ጦቦ) ወይ ደግሞ ኢህኣዴግ በራሱ ልክ የሰፋው የፖለቲካ ምህዳር ትንሽ ይሻሻል ወይም ቀዳዳ ይፈጠርለት ይሆን? እንዲሁም ተቋዋሚዎች በሄዱበት ሁሉ እየተከታተሉ ማዋከብና በፈጠራ ክስ ማሰርና ማስፈራራት ይቀንስ ይሆን ማለ~ ነው እንጂ በምርጫ ጊዜ በየትም ሃገር በገዢ ባርቲ ለተቋዋሚ ፓርቲዎች እንደ ዳቦ የሚከፋፈል ትሩፋት ወይ የፓርላማ ወንበር እንደሌለና ሊኖርም እንደማይችል ጠፍቶባት ኣይደለም ጥያቄው ያቀረበችላቸው፡፡

“የሚወዳደር ፓርቲ ራሱ ኣዘጋጅቶ መቆየት ኣለባት” ብሎዋል ጠ/ሚ ሃ/ማርያም፡፡ ጥሩ ኣባባል ነው፡፡ ነገር ግን በምን መልኩ መዘጋጀት እነደሚችሉ ቢነግ[ቸው ጥሩ ነበር፡፡ ምክንያቱም፡

1/ ተቋዋሚ ፓርቲዎች ህገ-መንግስታዊ መብታቸው ተጠቅመው ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይወጡ በእርስዎና የእርስዎ ተከታዮች በተከለከሉበት ወቅት (ለምሳሌ ያኣንድነትና የሰማያዊ ፓርቲ ኣመራሮችና ኣባላት በክልሎችና በተለይ በኣዲስ ኣበባ ይህንን በመሞኮራቸው ስንቴ ታስረዋል ስንቴ ተደበድበዋል)፡

2/ ህዝብ በመሰብሰብ ኣላመቸውን ለማስተዋወቅ ፍቃድና መሰብሰብያ ኣዳራሽ ለጠየቁ ፓርቲዎች በእርስዎና በእርስዎ ተከታዮች ኣንዴ የሚጠብቅ የፖሊስ ሃይል የለንም በማለት ኣንዴ ደግሞ ስራችን እያስፈታችሁን ነው በሚል ተልካሻና ኣስገራሚ ምክንያት በሚከለከሉበትና በሚታሰሩበት ይባስ ብሎም 5 ኪሎ ስንዴና ኣንድ ሌትር ዘይት ከቀበሌ በሚሰጣቸው ኑሮዋቸው በሚገፉ በኣንድ ለ5 ኔትወርክ ያታቀፉ የቀበሌ ሴቶችና ምንም ያማያውቁ ከእድሜ በታች የሆኑ ልጆች ሰብስባችሁ እንሰዲሰድብዋቸውና እንዲደበድብዋቸው እያደረጋችሁ ባላችሁበት ጊዜ (ለምሳሌ የዓረና ፓርቲ አመራሮችና ኣባላት በታህሳስና በጥሪ ወር በሽሬ፣ በዓዲ ግራትና በሑመራ) ፈሪውን ህ.ወ.ሓ.ት/ኢህኣዴግ ያደረገውን ኣፈና፡

3/ በሃገራችን ፖለቲካ ላቅ ያለ እውቀት ያላቸውና ለፖለቲካዊ ለውጥ ቆራጥ ኣቋም ያላቸው የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በፈጠራ ክስ የፈረዳችሁባቸውና እያስፈራራችሁባቸው ባላችሁበት ጊዜ (ለምሳሌ በዚህ ሳምንት ያአንድነት ፓርቲ አመራሮች የሆኑ ኣቶ አስራት ጣሴና ወጣት ደራሲና ፖለቲከኛ ዳንኤል ተፈራ)፡

4/ የተቋዋሚ ፓርቲ አባላት የሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ከስራቸው በምክንያት እንዲባረሩና እንዲዋከቡ እያደረጋችሁ ባላችሁበት ጊዜ፡

5/ የሃገሪቱን መገናኛ ብዙሃን 24 ሰዓት በቁጥጥራችሁ ውስጥ ኣስገብታችሁ ለግለ ሰብና ለፓርቲዎች ስም ማጥፋት ዘመቻ በምታወልበት ሃገር፡

6/ ዜጎች የፈለጉትን ሃሳብ እንዳይገልፁና የፈለጉትን የፖለቲካ አቋም እንዳይኖራቸው በ1 ለ5 የስለላ ኔትወርክ ሰርታችሁ ነፃነቱ በነጠቃችሁት ህዝብ በአጠቃላይ መንግስት የመንግስት ስራ ትቶ የፓርቲ ስራ በሚሰራበትና መንግስት መንግስትነቱን ትቶ የተራ ሽፍታ ስራ በሚሰራበት ጊዜ እንዴት ኣድርገው ነው ተወዳዳሪ ፓርቲዎች ራሳቸው ለውድድር መዘጋጀት የሚችሉት?

ሌላው ጠ/ሚ ደጋግመው ሲሉት የነበረ ጉዳይ ስለ ምርጫ ሂደት ነው፡፡ “ምርጫው ልክ እንደ ቅድሙ ሁሉ ነፃ፣ ፍትሓዊ፣ ዲሞክራስያዊና በህዝቡ ላይ ተአማኒነት ያለው እንዲሆን እንደ መንግስት በቂ ዝግጅት እናደርጋለን” የሚል ኣስገራሚ ኣባባል ነበር፡፡

መቼ ነው ኢህኣዴጎች ከረጆ ከመስረቅ (ከመቀየር)፣ የተቋዋሚ ፓርቲ ታዛቢዎ ኣስፈራርቶ ከማባረር፣ ህዝብ በነፃነት እንዳይመርጥ ከማስፈራራትና ከመደለል እንዲሁም ከማደናገር ኣልፋችሁ ነፃ፣ ፍትሓዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ያካሄዳችሁት? መቼ ነው በህዝብ ላይ ተኣማኒነት ያተረፈ ምርጫ ከንግግር ኣልፎ በተግባር የተደረገው?

በ1997 ዓ/ም ኣንፈልጋችሁም ብሎ ድምፁ ለነፈጋችሁ የኣዲስ ኣበባ ህዝብ ጥይት ያጎረሳችሁት ረስታችሁታል ማለት ነው? የወጋ ቢረሳ የተወጋ ኣይረሳምና ጠ/ሚ ሃ/ማርያም በኣጠቃላይ ኢህኣዴጎች የምትናገሩትና የምትሰሩት ፍፁም ስለማይገናኝ ይህ ኣይነት ቁማር በመጨረሻ ላይ ለናንተም ጠቃሚ ስላልደለ የኢትዮጵያ ህዝብ ህገ-መንግስታዊ መብቱ ተጠቅሞ የፈለገውን ሃሳብ በነፃነት እንዲያራምድ፣ እንዲሰበሰብና ኣቋሙ በሰላማዊ ሰልፍ እንዲገልፅ ብትፈቅዱለት ጥሩ ነው፡፡ ካልሆነ ህዝብ ኣፍነህ ለመግዛት መመኮር የቱንዝያ፣ የግብፅና የሊቭያ የቀድሞ ዲክታተር መሪዎች መጨረሻ ላይ እንዳላማረባቸው ከዚህ ይማረን እያላችሁ ስትከታተሉት የነበረ የትናንት ሓቅ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ በጣም ትእግስተኛና ኣስተዋይ በመሆኑ እስካሁን ትእግስቱ ኣማጥጦ በመጠቀም የታገሰ ነው ያለው፡፡ ነገር ግን ትእግስት መጠን ኣለው፡፡ ስለዚ ትናንት ነገ ስለማይሆ ትእግስቱ ተማጥጦ እንዲያልቅ ባትገፋፉት ጥሩ ይመስለኛል፡፡
በሃይል ለመግዛት መሞከር የውድቀት ምልክት ነው!!

የአዲስ አበባ ዞን ሊቀመንበርና ስራአስፈፃሚዎችን ለመምረጥ የ3 አስመራጭ ኮሚቴ ኮሚቴ አባላት ምርጫ ተደርጓል፤ በመቀጠልም ለሊቀመንበርነት 3 አባላት ተጠቁመዋል፡፡ በዚሁ መሰረት አቶ ዳዊት ሰለሞን አቶ ትግስቱ አወሉ አቶ ዘካርያስ የማነ ብርሃን ለዕጩ ሊቀመንበርነት ተጠቁመዋል፡፡ 3ቱም ዕጩዎች እያንዳንዳቸው የ7 ደቂቃ የምረጡኝ ቅስቀሳ አድርገዋል፤ ለሊቀመንበርነት ጠንካራ ውድድር ከተደረገ በኋላ እና የድምፅ አሰጣጡ በምስጢር ከተካሄደ በኋላ በቆራጥ አመራራቸው በአንድነት […]

‹‹አገር የጋራ ነው ከተባለ በኋላ የጎደለ ነገር አለ››/ሼኽ ኪያር ሙሐመድ አማን/ ‹‹በታሪካዊነቱ ተከብሮ ተጠብቆ መኖር አለበት›› /ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ/ (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፫ ቁጥር ፯፻፴፭፤ ቅዳሜ፤ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፮) የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮና መኖርያ ቤት በሚገኝበት ታላቁ ቤተ መንግሥት አጥር – ዙሪያ ገባው ላይ የሚገኘው የመስቀል ቅርጽ የእስልምናና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ሃይማኖቶች መሪዎችን አነጋገረ፡፡ የፌዴራል …

በትላንትናው ዕለት በሁለት አመት ገደብ የአምስት ወር እስራት ተፈርዶባቸው እንዲለቀቁ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ቢሰጥም የቂሊንጦ ወህኒ ቤት አቶ አስራትን እስከ ሰኞ እንዳይለቅ መመሪያ እንደደረሰው ማንነታቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የቂሊንጦ ወህኒ ቤት ሃላፊ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡ በዛሬው እለት የአቶ አስራት ጣሴን ከእስር መውጫ ወረቀት ይዘው ቂሊንጦ የተገኙት የአንድነት ፓርቲ አባላት ከወህኒ ቤቱ ቀና ምላሽ አላገኙም፡፡ የወህኒ ቤቱ […]

የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ምክር ቤት ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ ባልቻ ሆስፒታል አቅራቢያ በሚገኘው ሶሊሽ ኢንተርናሽናል ሆቴል የምስረታ ጉባኤውን ደርጋል፡፡ ዞኑን በሊቀመንበርነት ለመምራት የጦፈ ፉክክር እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡ አንድነት ፓርቲ በሚመራበት የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ መሰረት ፓርቲውን ይበልጥ ለማጠናከር ሲባል የአዲስ አበባ ዞን ምክር ቤት የአደረጃጀት ለውጥ ሊደርግ ችሏል፡፡ በአደረጃጀት […]

‘Ethiopiawinet’ is an Amharic term equivalent to ‘Ethiopianism’. But, the context it is recently being discussed in social media is very different from it has been used in English and historical scripts. The old Ethiopianism (as written in the scripts) is more theological thought than political, and pan-Africanist concept than Ethiopian nationalist. The debate now ranges from denying the existence of it (as a self-standing identity) to worshiping it (as the only thought to save Ethiopian unity). The former is mainly opinion of ethno-nationalists who have concerns that the term might be used as pseudo-Abyssinian. They think the so-called ‘Ethiopianism’ is not inclusive of all but is just an identity built on the cultures and religion of Ethiopian highlanders. I am guessing the debate ends with a new definition of what Ethiopianism is (should be). It seems Ethno-nationalism (which I would like to call Ethnopianism) is its biggest challenge.

Encyclopedia Britannica described Ethiopianism as “religious movement among sub-Saharan Africans that embodied the earliest stirrings toward religious and political freedom in the modern colonial period. The movement was initiated in the 1880s when South African mission workers began forming independent all-African churches, such as the Tembu tribal church (1884) and the Church of Africa (1889). An ex-Wesleyan minister, Mangena Mokone, was the first to use the term when he founded the Ethiopian Church (1892). Among the main causes of the movement were the frustrations felt by Africans who were denied advancement in the hierarchy of the mission churches and racial discontent encouraged by the colour bar. Other contributing factors were the desire for a more African and relevant Christianity, for the restoration of tribal life, and for political and cultural autonomy expressed in the slogan “Africa for the Africans” and also in the word Ethiopianism.

“The mystique of the term Ethiopianism derived from its occurrence in the Bible (where Ethiopia is also referred to as Kush, or Cush) and was enhanced when the ancient independent Christian kingdom of Ethiopia defeated the Italians at Adwa in 1896.”

It was Garvey who first demanded ‘Africa for Africans’. A Study of Ethiopianism in Rastafarianism with a Focus on the Concept Of Ethiopia as Zion (by Jennifer Skowera) stated that ‘the man most responsible for bringing the ideals of Ethiopianism to Jamaica is Marcus Garvey. Barrett describes the man as “. . . the prophet of African redemption . . . [and through him] the spirit of Ethiopianism came into full blossom” (77).’

The term was  first coined in a desperate attempt of strengthening Africans and black people who were under colonization and slavery around the world. It is a huge ideal which conceived free and united Africa. That dream was big and isn’t fulfilled yet.

Every sane African loves the idea of United Africa and even most pragmatic politicians want to come to it through regional integration of the east, of the west, of the north, of the south and of the center. As compared to this dream, it is difficult to grasp that how African countries are splitting into many for little differences. In east Africa alone, the number of countries is doubled within two decades.

These things happen because immature but accidentally influential politicians misunderstand systematic-inequality as inability to co-exist. In the process of states making and independence, some people were disproportionately favored. However this doesn’t mean that [due to historical injustices,] the favored and disfavored ones can’t exist together, many a self-claimed freedom fighters come and plant hate among people. In this way, the dream of African Union walks two steps away as Africans walk to have it a step.

The case in Ethiopia isn’t different. Ethiopia is a small Africa where state fails to bond its people beyond tribal differences.

Discussions on Ethiopianism (as in unity and pride) give more sense to other Africans than us. That’s why we need to stop and realize that unity is not the enemy of equality. Unity isn’t becoming one but untied for better. Perhaps, it is because we aren’t united that dictatorship isn’t gone.

ዶር ያእቆብ ኃይለማሪያም፣ የአሰብ ወደብን በተመለከተ የጻፉት መጽሃፍ ሰባት ጊዜ እንደታተመ ከሲ.ቢ.ኤስ ራዲዮ ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ገለጹ። «ይህ የሚያመለክተዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ምን ያህል የአሰብ ጉዳይ እንደሚያንገበግበው ነዉ» ያሉት ዶር ያእቆብ፣ በአሰብ ዙሪያ ያሉትን ችግሮች በስላም መፍታት እንደሚቻልም ለማሳየት ሞክረዋል። የኤርትራ ሕዝብና የኢትዮጵያ ሕዝብ ወንድማማች ህዝብ እንደሆኑ የተናገሩት ዶር ያእቆብ፣ ጠቡና መለያየቱ የመጣዉ በመሪዎች […]

አቶ ብርሃኑ በርሄ ይባላሉ። እስከ 1994 ድረስ የሕወሃት አባል ነበሩ። የሕግ ባለሞያ ናቸው። በትግራይ ክልል የፍትህ ቢሮ ሃላፊ ነበሩ። « የፍህት ቢሮ አደረጃጀት እና አቃቢ ሕግ ከፖለቲክ ገለልተኛ መሆን አለባቸዉ » በሚል አማራጮችን አቀረቡ። « አቃቤ ሕግ ተጠሪነቱ ወይም ለካቢኔ ወይንም ለምክር ቤት መሆን አለበት» የሚል የጥናት ወረቀት አቀረቡ። ያቀረቡት ሃሳብ በሕወሃት አመራሮች ዉድቅ ተደረገ። […]

ኢሕአዴግ የዘረጋቸው ትላልቅ ፕሮጅክቶች የሕዝቡ ተሳትፎ እንደሚጠይቁ የተገነዘቡት በርካታ የኢሕአዴግ ደጋፉዎችና አባላት፣ ኢሕአዴግ መሰረታዊ ማሻሻያዎችን እንድያደርግ፣ የፖለቲካ ምህዳሩን እንዲያሰፋ፣ እስረኞችን እንዲፈታ ዉስጥ ዉስጡን ጫና እያደረጉ እንደሆነ ከኢሕአዴግ አካባቢ ያሉ ምንጮቻችን ይገልጻሉ። ትግራይን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች በኢሕአደግ ዘንድ ባሉ የመልካም አስተዳደር፣ የኢፍትሃዊነት ችግር ላይ፣ እንዲሁም አልቻል በተባለው የኑሮ ዉድነት የተነሳ፣ የሚነሱ ተቃዉሞዎች እየተበራከቱ መሆኑ ያዩ […]

የሱዳን መንግት ኢትዮጵያዉያን ከዘመናት ከኖሩበት ቦታ እንዲለቁ የሳምነት ማስጠንቀቂያ እይሰጠ እንደሆነ የአራን አመራር አባል አቶ አብርሃ ደሳት ገለጹ። «የሱዳን መንግስት በኢትዮ-ሱዳን ድንበር አከባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሳምንት ዉስጥ ቀያቸውን ለቀው እንዲወጡ ትእዛዝ መስጠቱ የሑመራና አከባቢው ኗሪዎች ለዓረና ትግራይ ፅሕፈትቤት አስታውቀዋል። የሱዳን መንግስት ትእዛዝ ያስተላለፈው መሬቱ የሱዳን ግዛት ሁኗል በሚል በምክንያት እንደሆነ አክለዋል።”” ሲሉ ነገር አቶ አብርሃ […]

አቶ ዳንኤል ተፈራ በዋስ መለቀቃቸው፣ አቶ አሥራት ጣሴም መፈታታቸውን አነበብኩ። መጀመሪያዉኑ እነዚህ የአመራር አባላት መከሰስ ብሎም መታሰር አልነበረባቸውም። ሆኖም ግን ኢሕአዴግ ነገሮችን በማርገብ እንዲፈቱ ማድረጉ በአዎንታዊነት ተቀብዬዋለሁ። አዎ «የኢሕአዴግ አመራር አባላትን ጥሩ አድርጋቹሃል » እላለሁ። ይህ አይነቱን፣ መቀራረብን የሚያመጣ፣ ፖለቲካዉ የበለጠ እንዳይከር የሚያደርግ ተግብራትን እንዲፈጸሙ ነበር የሁላችንም ፍላጎት። ኢሕአዴግ በአገራችን እያደረጋቸው ያለው የልማት እንቅስቃሴዎች ሰፋፊና […]

የትግራይ ህዝብና ታጋዮቹ የህ.ወ.ሃ.ት ትጥቅ ትግል የተጀመረበት ቀን ከ1967 ዓ/ም የካቲት ወር ጀምሮ እስከ 1983 ዓ/ም በየአመቱ ለምትመጣዉ የካቲት 11 ለማክበር በናፍቆት የሚጠብቁት ነበር። በአሉን ለማክበርም የሚበላ፣ የሚጠጣ፣ የሚለበስ ያላቸውን ሃብት በማሟጠጥ አስቀድመዉ ይዘጋጁበት ነበር የትግራይ ህዝብ ይቅርና በነፃ መሬት በጠላት ውስጥ በስደት በተለይ ደግሞ በ1977 ዓ/ም በድርቅ፣ በደርግና በሻዕቢያ ወረራ ወደ ሱዳን ተሰዶ በለጋሾች […]

በፍርድ ቤቱ ዉሳኔ መሠረት አቶ አስራት አምስት ወራት እስራት ተቀጥተዉ፥ በሁለት ዓመት ገደብ ተለቀዋል።የአቶ አስራት ጠበቃና ፓርቲያቸዉ ብይኑን ተቃዉመዉ ይግባኝ እንደሚጠይቁ አስታዉቀዋል

ወደ ዉቅሮ ከተማ ጎራ ብዬ ነበር። የትግራይ ክልል ዕጩ ዳኞችና ዓቃብያን ሕግ የሚሰለጥኑት በዉቅሮ ከተማ ነው። ዳኞቹ ከዩኒቨርስቲዎች በሕግ የተመረቁ ወጣቶች ናቸው። ዳኞችና ዓቃብያን ሕግ ሁነው ለማገልገል ስልጠና ይሰጣቸዋል። ስልጠናው ግን ስለ ዳኝነት ሳይሆን ስለ ህወሓታዊ ፖለቲካና ፕሮፓንጋንዳ ሁኖ ተገኝቷል። የሚሰለጥኑት ስለ ወያናይ ዴሞክራሲ (አብዮታዊ ዴሞክራሲ) ነው፤ ስለ ልማታዊ መንግስት ነው (ልማታዊ መንግስት በኢህአዴጋዊ ቋንቋ […]

እጎአ የካቲት 14 ቀን ማለትም ዛሬ በተለይ በምዕራብ ሀገራት የፍቅረኛሞች ቀን ይከበራል። በአዲስ አበባ እና አካባቢዋም ከአመት ዓመት ቀኑን የሚያከብሩት ፍቅረኛሞች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። ወጣቶቹ የት እና እንዴት ያከብሩታል? አከባበሩ ምን ይመስላል?

የተመድ መቅዲሹ አዉሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ የደረሰ ፍንዳታ ህይወት አጥፍቶ ጉዳት ቢያደርስም የሶማሊያ መንግስት እንዲህ ያለ ጥቃትን ለማስቆም የሚያደርገዉን ጥረት መደገፉን እንደሚቀጥል አስታወቀ። ዋና ፀሐፊ ባን ጊሙን በጥቃቱ ህወታቸዉን ላጡት ቤተሰቦችና ለተጎዱት ሃዘናቸዉን ገልጸዋል።

የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቡናን ኤክስፖርት ከማድረግ ጋር በተያያዘ በክትትልና ቁጥጥር፣ በመረጃ አያያዝ፣ ያለብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ቡናን ወደውጭ ኤክስፖርት ከማድረግ እና በሁሉም አካባቢ የቡና ድርጅቶችን መጋዘኖች ክምችት ቆጠራ በወቅቱ ባለማድረግ ላይ ክፍተቶች እንደሚስተዋሉ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ያጠናው አንድ ጥናት አመለከተ፡፡ ጥናቱ  ኤክስፖርት በማያደርጉ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ያለመውሰድ፣ በንግድ ፈቃድ …

የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የታክሲ ሹፌሮች አድማውን የመቱት አዲሱን የትራፊክ የቅጣት ደንብ በመቃወም ነው። በከተማው መሃል ላይ አሽከርካሪዎቹ ተሰብስበው የመኪና ጥሩምባ ማጮሃቸውን የገለጸው የኢሳት ወኪል፣ ከሰአዓታት በሁዋላ ታክሲዎቹ ከአደባባይ ላይ በመሰወራቸው ነዋሪዎች ታክሲዎችን ለማግኘት ሲቸገሩ ታይቷል። የገዢው ፓርቲ ሰዎችና ትራፊኮች፣ በመንገድ ላይ ያገኙትን ታክሲ በማስገደድ ሰዎችን እንዲጭን ለማድረግ ሞክረዋል። ፈቀደኛ ያለሆኑ …

የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጉርሻ ክፍያው ከየካቲት ወር መጨረሻ ጀምሮ እንዲሰጣቸው ተብሎ የጸደቀበትና የክፍያ ማዘዣው ከከተማ  አስተዳድሩ ለሁሉም ወረዳዎችና ክ/ከተሞች በያዝነው ሳምንት እንደተላለፈላቸው ለማዎቅ ተችሎአል። የጉርሻ ገንዘቡ ከ1 ሺ 700  እስከ 4 ሺ 000 ብር የሚደርስ ሲሆን አገልግሎቱም ለስልክ፣ ለቤት ኪራይ እና ለትራንስፖርት መደጎሚያ ታስቦ የሚሰጥ ነው። ክፍያው በፋይናንስ መክፍያ  ሰነድ …

የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ በሚካሄደው ድርድር በቅርቡ ከእስር የተፈቱት 7ቱ የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳታፊዎች ሆነዋል። ይሁን እንጅ ባለስልጣኖቹ ከሁለቱም ወገኖች ሳይሆኑ በገለልተኛነት በድርደሩ ላይ መገኘታቸውን ተናግረዋል። ገለልተኝነትን የመረጡበትም ምክንያት ሲናገሩ ደግሞ የጦር መሳሪያ የለንም የሚል ነው። የሳልቫኪር መንግስት ባለስልጣኖችን ያሰረው ከተቃዋሚው መሪ ሪክ ማቻር ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል ነበር። …

እንደመግቢያ፤ ያሬድና ጽሁፉ አቶ ያሬድ ሀይለማሪም (ያሬዶ) ለሰብአዊ መብት መሟገት አመል ሆኖበት (አመሉ፤ አዎንታዊ በሆነ መልኩ ማለቴ ነው)፤ ከጥቂት ቀናት በፊት አንድ ጽሁፍ አውጥቶ ነበር፡፡ ያንን ጽሁፍ ተከትሎ አንዳንድ በብእር ስም ጀርባ የተደበቁ ተቺዎች አበሳጩት መሰለኝ ሌላ ተከታይ ሁለተኛ ጽሁፉም ጽፎዋል፡፡ የኔ አስተያየት በመጀመሪያው ጽሁፍ ላይ ነው፡፡ ከሞላ ጎድል ጽሁፉ፤ ግንቦት ሰባት፤ ለኢትዮጵያ እንታገላለን ብለው […]