በተያዬ ጊዜ ሰማያዊ ፓርቲን የሚመለከት በርካታ ጽሁፎችን ለማየት ሞከርኩ ሁሉም ሰማያዊ ፓርቲን የሚወቀሱ ሆነው አገኘኋቸው፡፡ እኔ በእርግጥ ሰማያዊ ፓርቲ በተደጋጋሚ ብቻውን በመሄድ የዚህን ሀገር ትግል እንደሚለውጥ ሲናገር መስማቱ የዕለት ተዕለት ጉዳይ ሆኖ ቢሰነብትም ቅሉ በእነርሱ ከመቀየም ፓረቲውን ወደፓረቲ ደረደጃ እንዲድግ ቢሰራ ጥሩ ነው እላለሁ፡፡ ይህንን የሰማያዊ ፓርቲ የተናጠል ጉዞ ደግሞ በርካቶች የጠሉት ይመስላል፡፡ እኔ ግን […]

ማንነታቸው ግልጽ ያልሆኑ የደህንነት ሰራተኞች፣ ለአዲስ አበባ አስተዳደር ባስተላለፉት መመሪያ መሰረት፣ ሚያዚያ 19 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲያደርግ እውቅና ሊሰጥ እንደሆነ፣ ከአዲስ አበባ አስተዳደር አካባቢ ያሉ ምንጮቻችን ገለጹ። አስተዳደሩ ሚያዚያ 19 ቀን ሰልፉን ለማድረግ፣ አስቀድሞ የአንድነት ፓርቲ ደብዳቤ ቢያስገባም፣ በዚያ ቀን ሌሎች ዝግጅቶች ስላሉ ለሚያዚያ 26 ቀን ለሰልፉ እውቅና እንደሚስጡ ባሳወቁት መሰረት፣ የአንድነት ፓርቲ […]

ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር 9 ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮችን ይዛ ቀርባለች፡፡

በተለያየ ምክንያትጋዜጣዋን ኮፒ በዕለቱ ያላገኛችሁ ይኸው መረጃ ይደርሳችሁ ዘንድ በፒዲ ኤፍ ለቀናታል
PDF ያንብቧት!

ፕ/ር አለማየሁ፣ ፕ/ር መሳይ፣ አቶ ታዲዮስ ታንቱ፣ ግርማ ሞገስ፣ ታምራት ታረቀኝና ሌሎችም ጥልቅ ትንታኔ ሰጥተውባታል፡፡ ጋዜጣዋ በርዕሰ አንቀጽዋ በፋሲካው ስለ ነጻነት፣ ፍትህ፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን አስበን እንድንውል ትመክራለች፡፡
በጎንደር የሚፈርሱት 30 ሺህ ቤቶች፣ ኢትዮጵያውያን ዛሬም ‹‹አገራችሁ አይደለም ውጡ!›› እየተባሉ መሆናቸውን፣ አርሶ አደሮች መሬታቸውን ያለ ካሳ መነጠቃቸውንና ሌሎች ትኩስ ወሬዎችን አካትታለች፡፡ ሰለሞን ተሰማ ጂ ለዚህ ትውልድ ‹‹ጥራኝ ጎዳናው፣ ጥራኝ መንገዱ›› እንደሚያስፈልገው ይተነትናል፡፡
በላይ ማናዬ በአገልግሎት እጥረትና በሎሎችም ችግሮች ውስጥ ያለውን ህዝብ ‹‹አይ አንተ ህዝብ ትግስትህ!›› በሚል የችግሩን ጥልቀትና የህዝቡን በዝምታ መገዛት ያስነብበናል፡፡ ጌታቸው ሺፈራው ‹‹የዘመኑ የፖለቲካ ሰማዕታቶች››ን ስለ ፖለቲካው ፋሲካ ቅርበትና ርቀት በአንደበታቸው የሚናገሩትን ጽፏል፡፡

የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ደረጀ መላኩ ስለ ኢትዮጵያ ስትራቴጃዊ ጠቀሜታና ከአሜሪካ ጋር ስላላት ግንኙነት ጥልቅ ትንታኔ ሰጥቶባታል፡፡ ሳሙኤል አበበ ‹‹ማጅራት መችው ፖሊስም የህዝብ ነውን?›› በሚል ‹‹ፖሊስ የህዝብ ነው!›› የሚሉትን ይሞግታል፡፡ ሌሎች ጉዳዮችም ተዳስሰውባታል!

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (ከአዲስ አበባ)

ልዕለ ኃያሏ ሀገረ-አሜሪካን ዛሬ ለተጎናፀፈችው የሕግ የበላይነት የተከበረበት ሥርዓት መሰረት የጣሉት እነ ቶማስ ጃፈርሰን በነፃነት አዋጃቸው ላይ ‹‹ሁሉም ሰዎች በእኩልነት የተፈጠሩ ናቸው›› በማለት ሲደነግጉ፤ እንግሊዛዊው ደራሲ ጆርጅ ኦርዌል ደግሞ “Animal Farm” በሚለው መፅሐፉ፣ ጉልበታም ‹‹ገዥ›› አድርጎ በሳላቸው ገፀ-ባሕሪያት አማካኝነት ‹‹…አንዳንድ እንስሳት (ሰዎች) ግን የበለጠ እኩል ናቸው›› ይለናል። በርግጥ ሁለቱም አይነት አስተዳደሮች መሬት ወርደው ዓለማችንን ዲሞክራት እና አምባ-ገነን በማለት በሁለት ጎራ የከፈሉ የመሆናቸው ጉዳይ አከራካሪ አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

አንድ በሀርቫርድ የኒቨርሲቲ ያጋጠመኝን ነገር መግቢያ ላድርገውና ልቀጥል፤ በአንድ ሴሚናር (የጥናት ውይይት) ላይ አንድ ጥቁር አሜሪካን ፕሮፌሰር ወደአሜሪካ በባርነት በመጡት አፍሪካውያን ላይ የተፈጸመውን ግፍ በመዘርዘር አስረድቶ አሁን ለእነሱ ልጆችና የልጅ ልጆች ካሣ መከፈል አለበት የሚል ክርክር አነሣ፤ ካሣውን የመክፈል ግዴታ የሚጣለው ማን ላይ ነው? ካሣውንስ የመቀበል መብት የሚሰጠው ለማን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ሳናነሣ ብዙ ሌሎች ጥያቄዎች ይኖራሉ፤

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከ ሁለት ሺ ዓመታት በፊት በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የተገለጠው ኢየሩሳሌምን ለመሳለም የሚደረገው ጉዞ ዛሬ የሺዎች ጉዞ ሆኗል፡፡ በእግር ተጉዘው ኢየሩሳሌም ለመድረስ ሱዳንን፣ ግብጽና የሲና በረሃን ያቋርጡ የነበሩት፤ ያለበለዚያም በመካ በኩል ተሻግረው በዮርዳኖስ በኩል ይገቡ የነበሩት አባቶቻችን ክብር ይግባቸውና፣ በኢየሩሳሌም ያቆዩትን ቦታ ለመሳለምና የትንሣኤ በዓልንም በትንሣኤው ቦታ ለማክበር ኢትዮጵያውያን ከሰባ ሺ ብር በላይ እየከፈሉ ይጓዛሉ፡፡

ከዛሬ ሃምሳ ዓመት በፊት የኢትዮጵያውያን ምእመናን የኢየሩሳሌም መታሰቢያ ድርጅት በአዲስ መልክ የኢየሩሳሌምን ጉዞ ሲጀምር በአንድ ድርጅት ብቻ ይከናወን የነበረው ጉዞ፣ ዛሬ ከሃያ በላይ በሚሆኑ አጓጓዦች በኩል ከመላው ዓለም ኢትዮጵያውያን ይሰባሰባሉ፡፡ ከሃምሳ ዓመታት በፊት ከኢትዮጵያ በሚመጡ ተሳላሚዎች የተጀመረው ጉዞ ዘንድሮ ከ27 ሀገሮች በመጡ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደሚከናወንበት ደረጃ ደርሷል፡፡ ከዓመታት በፊት በአብዛኛው በሽማግሌዎችና በእናቶች ብቻ ይደረግ የነበረው ጉዞ ዛሬ ከሦስት ወር ጽንስ እስከ 94 ዓመት አዛውንት ተካትተውበት የሚደረግ ሆኗል፡፡

ከዐሥር ዓመታት በፊት የትንሣኤ በዓል በዴር ሡልጣን ሲከበር በአንደኛው የገዳሙ አጥር ጥግ ተሰባስበው ይታዩ የነበሩት ተሳላሚዎች ዛሬ ግቢው ጠቧቸው፣ መንገዶችን አጨናንቀው፣ ጠጠር መጣያ እስከ ማሳጣት ደርሰዋል፡፡ ወይም አንድ የእሥራኤል ጋዜጠኛ እንዳለው ‹‹ነጭ ጎርፍ በፍኖተ መስቀል በኩል ሲፈስ የሚታይበት ተአምር›› ላይ ደርሰዋል፡፡ ድንበር የለያያቸው ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ዜግነት ሳያግዳቸው፣ ሃይማኖት አገናኝቷቸው በአንድ የሚያመልኩበት፣ አንድ ማዕድ የሚቆርሱበት፣ የዘመድ ወግ የሚያወጉበት ሥፍራ ሆኗል፡፡

ይህ ሁሉ እግዚአብሔር የሰጠን ዕድል ቢሆንም ከተጠቀምንበት ነገር ያልተጠቀምንበት ይበልጣል፡፡ የዚህ ዋነኛ ምክንያቱ ደግሞ አስተሳሰባችን ከጠላት ተኮር ሥነ ልቡና ባለመላቀቁ ነው፡፡ ልክ ነው ግብጻውያን አሁንም በዴር ሡልጣን ገዳማችን ላይ ግፍ ይፈጽማሉ፡፡ አሁንም ችግር ይፈጥራሉ፤ አሁንም ገዳሙ እንዳይጠገን ይከላከላሉ፤ ህልውናችን ያበሳጫቸዋል፤ ብዛታችን ያንገበግባቸዋል፡፡ በግብጻውያን ምክንያት የተቀበልናቸው ብዙ መከራዎች አሉ፡፡ እንዳንሠራ የታገድናቸው ነገሮች አሉ፡፡ ግን የሁሉም ነገር መነሻና መድረሻ ግብጻውያን ናቸው ብለን መደምደም አንችልም፡፡ አንዳንዴም ‹‹እኛን የጨረሰን የራሳችን ጠማማ ነው›› እንዳሉት ዛፎች ለግብጻውያን ችግር ፈጣሪነት መነሻ እኛው ሆነን እንገኛለን፡፡

ታሪክ እንኳን እንደሚያስተምረን የዴር ሡልጣን ዋናው በር በግብጻውያን እጅ የቀረው ቁልፉ ለኢትዮጵያውያን እንዲሰጥ በተወሰነ ጊዜ በንጉሥ ምኒሊክ ተወካይና በገዳሙ ተወካይ መካከል ‹‹ቁልፉን መረከብ ያለብን እ ኔ ነኝ›› በሚል በተነሣው ውዝግብ ምክንያት ነበር፡፡ ዛሬ በየዓመቱ በስቅለት ቀን መብራት ይዘን እንለፍ አንለፍ የሚለው ውዝግብ የተፈጠረበት አንዱ ምንያት የኛው ጳጳስ በሰጡት ፈቃድ ነው፤ በገዳሙ በር አጠገብ ያሉት የብረት ቅስቶች የተገነቡት የኛው ጳጳስ በሰጧቸው ፈቃድ ነው፡፡

ግብጻውያን ጠንካራ ብሔራዊ ኮሚቴ አቋቁመን የዴር ሡልጣንን ነገር ዓለም ዐቀፋዊ አጀንዳ እንዳናደርገው አላገዱንም፤ ግብጻውያን በየዓመቱ የሚመጡ ምእመናንን በሚገባ እንዳናስገነዝብ አላገዱንም፤ ግብጻውያን እያንዳንዱ አጓጓዥ እንደ አይጥና ድመት እንዲተያይ አላደረጉም፤ ግብጻውያን በኢትዮጵያና በግብጽ ቤተ ክህነት በኩል ድርድር እንዳይጀመር አላደረጉም፤ ግብጻውያን ለሀገሩ የሚመጥኑ አባቶችን እንዳንመድብ አልያዙንም፤ ግብጻውያን ስለ ገዳማችን ተገቢውን መረጃ እንዳናስተላልፍ እጃችንን አልቆለፉንም፤ ግብጻውያን ምእመናን ተሳላሚዎችን አስተባብረን ሥራ እንዳናሠራ አላሳገዱንም፡፡

ጠላት ሁለት ጊዜ ይጎዳሃል፡፡ የመጀመሪያው በጠላትነቱ የሚሠነዝረው ጥቃት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በእርሱ እያመካኘህ ችግርህን ወደ ውስጥ እንዳታይ ማድረጉ ነው፡፡ ከሁለቱም የሚከፋው ሁለተኛው ነው ይባላል፡፡ የሁሉም ነገር ምክንያትና ሰበብ ጠላትህ ይሆናል፡፡ ሰዎችም በቀላሉ ይቀበሉሃል፡፡ አንተም ለማስረዳት ብዙ አትቸገርም፡፡ ለራስህም የችግርህ ሁሉ ምንጭ አድርገህ ትቀበለውና ሌሎች ነገሮችን አትመለከትም፡፡ አመለካከትህ ጠላት ተኮር ይሆናል፡፡


በኢየሩሳሌም ገዳሞቻችንም የሚታየው ይኼው ነው፡፡ ለማንኛውም ነገር ምክንያቶቹ ግብጻውያን ናቸው፡፡ ስለ ራሳችን ድክመት የሚያወራ የለም፡፡ ራሱን የሚወቅስም አልተገኘም፡፡ ብዙ ችግሮቻችን ግን ግብጻውያን ባይኖሩም የሚኖሩ ናቸው፡፡ ከጠባያችን፣ ከአሠራራችንና ከአካሄዳችን የሚመነጩ ናቸው፡፡ የግብጻውያኑ ችግርም መፍትሔ ያላገኘው እኛ ስለያዝነው ይመስለኛል፡፡ ነገሩን ጠበቅ አድርገን በመያዝ ብርቱ ሃይማኖታዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ጫና ለማሳረፍ የምናደርገው ጥረት አለመኖሩ፡፡ የዴር ሡልጣን ነገር ትዝ የሚለን ለትንሣኤ በዓል ጊዜ መሆኑ፤ ከዚያ በቀር ይህን ጉዳይ ሥራዬ ብሎ የያዘ አንድም ቤተ ክህነታዊ አካል አለመኖሩ፡፡ ግብጾችኮ ጉዳዩን በፓርላማ ደረጃ በብሔራዊ ኮሚቴ ነው የሚከታተሉት፡፡ እኛኮ እንኳን ፓርላማ ቤተ ክህነት የሚያውቀው ኮሚቴ የለም፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም ቢሆን ከኢየሩሳሌም ገዳማት በሚቀርብ ጥያቄ ይወያያል እንጂ የኢየሩሳሌም ገዳማትን ጉዳይ በዝርዝር አጥንቶ፣ የድርጊት መርሐ ግብር ቀርጾ፣ አካል አቋቁሞ፣ ከሚመለከታቸው ጋር ኅብረት መሥርቶ ዘላቂና ተከታታይነት ያለው ሥራ አይሠራም፡፡ አብዛኛው የኢየሩሳሌም ገዳማትን የሚመለከተው አጀንዳም ‹‹አቡነ እገሌ ይነሡ አይነሡ›› በሚለው ላይ የሚያተኩር ነው፡፡

በፓትርያርኮች ደረጃ በግብጽ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መካከል ውይይት ሲደረግም የኢየሩሳሌም ገዳማችን ጉዳይ አጀንዳ ሆኖ የተነሣበት ጊዜ የለም ማለት ይቻላል፡፡ ቢያንስ ውይይት ለመጀመር፣ ችግሩን ለመፍታትና አንዳች የስምምነት ደረጃ ላይ በየእርከኑ ለመድረስ የሚያስችል መግባቢያ እንኳን የለም፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በቅርቡ ወደ ግብጽ ይሄዳሉ፡፡ እስከ አሁን ባለኝ መረጃ ዴር ሡልጣን የአጀንዳቸው አካል የሆነ አይመስለኝም፡፡ ለግብጻውያን ግን ዴር ሡልጣን ከዓባይ ቀጥሎ ከኢትዮጵያን ጋር ላላቸው የዲፕሎማሲ ግንኙነት አንዱ አጀንዳቸው ነው፡፡

ይህንን በዚህ እንተወውና ለመሆኑ ወደ ኢየሩሳሌም ገዳማት የምንመድባቸው አባቶች መመዘኛቸው ምንድን ነው? የሃይማኖት ትምህርት፣ የእምነት ጽናት፣ ለጸሎትና ለአገልግሎት ያላቸው ፍላጎት፣ ለመማር ያላቸው ትጋት፣ ከአካባቢው ጋር ተዛምደው ለመኖር ያላቸው ዝግጁነት፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ አምባሳደር ለመሆን ያላቸው ችሎታ ይታያል? ከዐሥር ዓመታት በላይ ተቀምጠው ዐረብኛና ዕብራይስጥ የማይችሉ ከሆነ ኢየሩሳሌም መኖር ጥቅሙ ምንድን ነው? አገልግሎቱ ሲሆን ከሀገር ቤት ካልበለጠ ካልሆነም እንደ ሀገር ቤቱ ካልሆነ በኢየሩሳሌም ገዳማት መኖሩ በአሜሪካ ከመኖር ልዩነቱ ምንድን ነው? በኢየሩሳሌም ገዳማችን ደረጃውን የጠበቀ፣ አባቶችን ለዓለም አቀፋዊ አገልግሎት የሚያበቃ ትምህርት ቤት ከሌለን ኢየሩሳሌም መመደብ ከሥጋዊ ዕድል በዘለለ ጥቅሙ ምንድን ነው? የራሳችን የቅብዐ ቅዱስ ማዘጋጅ፣ የዕጣን መቀመሚያ፣ የንዋያተ ቅድሳት ማዘጋጃ፣ የመስቀል መሥሪያ፣ ከሌለን ኢየሩሳሌም መመደብ ጥቅሙ በዶላር ደመወዝ ማግኘት ነው ማለት ነው፡፡

የኢየሩሳሌም ገዳማችን ቤተ ክርስቲያናችን ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ጋር ያላትን ግንኙነት የሚያጠናክሩ፣ ከአካባቢው ባለ ሥልጣናት ጋር በሚገባ ተግባብተው የገዳማችንን መብት የሚያስከብሩ፣ በልዩ ልዩ ሞያ ሠልጥነው ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን ተስፋ የሚሆኑ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን ለማወቅ የሚመጡትን ምሁራን በደረጃቸው የሚያናግሩ፣ በማንኛውም መድረክ ተገኝተው ቤተ ክርስቲያንን ሊወክሉ የሚችሉ፣ ልዩ ልዩ የገቢ ምንጭ ፈጥረው የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን የሚረዱ ተቋማትን የማያፈሩ ከሆነ መነኮሳቱ ‹‹አረዳ ጠባቂ›› ከመሆን ያለፈ ለቤተ ክርስቲያን በቁዔታቸው ምንድን ነው? መቼም ይህንን ሁሉ ያላደረግነው በግብጻውያን ምክንያት ነው አንልም፡፡


በዚህ በትንሣኤ ሰሞን ከዐሥር ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ምእመናን በኢየሩሳሌም ተገኝተው ነበር፡፡ ነገር ግን እነርሱን በአንድ ጉባኤ ለማስተባበር፣ ስለ ገዳማቱ ሁኔታ በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር፣ ፕሮጀክት ቀርጾ ያንን እንዲተገብሩ ለማድረግ፣ ምእመናኑን ለማስተማርና ለማነጽ፣ ጥረት ሲደረግ አላየሁም፡፡ ከዚያ ይልቅ የሀገር ቤቱ አሠራር አልለቀን ብሎ አንዳንድ ቁራጭ ጧፍ ለመሸጥ ነበር መከራ ስናይ የከረምነው፡፡ ውኃ አዙሮ ለመሸጥ ነበር ጥረት ሲደረግ የነበረው፡፡ ምእመናኑን በሚገባ አስረድቶ፣ ዘላቂ ነገር እንዲሠሩ አወያይቶ፣ ለልጅ ልጅ የሚተርፍ ነገር ከመሥራት ይልቅ አንድ ሺ ጧፍ ሽጦ አንድ ሺ ዶላር ለማግኘት መድከሙ በዋናው አልጋ ላይ መተኛት ሲቻል በትራሱ ላይ እንደ መተኛት ነው፡፡

ተሳላሚ ምእመናኑም ራሳቸውን እንደ ቱሪስት ቆጥረው ተሳልሞ ለመጓዝ ከመትጋት ባለፈ የገዳሙን ሁኔታ ለማወቅ፣ ዘላቂና ችግር ፈች ሥራ ለመሥራት፣ አልከፈት ያለውን የቤተ ክህነት በር በሚገባ አንኳኩቶ ለማስከፈት አልቻልንም፡፡ አጓጓዦቹም ምእመናኑ ተገናኝተው፣ ተዋውቀውና ተወያይተው፣ በአንድ ኢትዮጵያዊ መንፈስ አንድ ሥራ እንዲሠሩ ጥረት ሲያደርጉ አይታዩም፡፡ እንዲያውም ተጓዦቻቸው ባለመተዋወቅና በመፈራራት የጎሪጥ እንዲተያዩ ያደርጓቸዋል፡፡

እነዚህን ለምሳሌነት የጠቀስኳቸው በግብጻውያን ብቻ እያመካኘን በመቀመጣችን ያልሠራነው ሥራ ምን ያህል ዋጋ እያስከፈለን መሆኑን ማየት እንድንችል ነው፡፡ ግብጻውያን ርስታችንን ከመንጠቃቸው በላይ በእነርሱ እያመካኘን የኛን ሥራም እንዳንሠራ አድርገውናል፡፡ አሁን ለዴር ሡልጣን መልካም ዘመን ነው፡፡ ኢትዮጵያ በግብጽ ላይ አንገቷን ቀና አድርጋለች፣ የአካባቢው የፖለቲካ ምሕዳር እየተቀየረ ነው፡፡ ምእናንም በብዛት ወደ ኢየሩሳሌም እየመጡ ነው፡፡ ከመላው ዓለምም ተሳላሚዎች እየበዙ ነው፡፡ ይህንን እግዚአብሔር የሰጠንን ዕድል ካልተጠቀምን እንነጠቃለን፡፡ ስለዚህ በአዲስ አስተሳሰብ፣ በአዲስ መንፈስና በአዲስ መንገድ መነሣት አለብን፡፡

እንዴት? በቀጣይ ዐሥር ነገሮችን እጠቁማሁ፡፡

ዴር ሡልጣን፣ ኢየሩሳሌም

“የተነጠቁ መብቶቻችን እናስመልስ” በሚል መሪ ዓላማ ስማያዊ ፓርቲ ያደረገው ጥሪ የተከበረ ግብ ቢሆንም፤ ውጥንቅጥና ውስብስብ በሆነው፡ ሕወሃት በፈንጂ ባጠረው የተግል ጎዳና የሰማያዊ ፓርቲ ብቸኛ ጉዞ መምረጡን በክፍተኛ ኃዘንና ቅሬታ እንድመለከተው ተገድጃለሁ። ጥያቄው ስማያዊ ፓርቲን የመቀበልና አለመቀበል ጉዳይ መደረግ የለበትም። መግለጽም ካስፈለገ፡ ለሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አድናቆት አለኝ። ይህንንም በተደጋጋሚ በዚህ ድህረ ገጽ ላይ አስረግጬ መስክሪያለሁ። በኢትዮጵያና […]

“የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።…” የምትለዋ አሰልቺ የቴሌ መልእክት ያላጋጠመው ቢኖር ወደ ኢትዮጵያ ስልክ ደውሎ የማያውቅ ሰው ብቻ መሆን አለበት። ኮ/ል መንግስቱ ሃይለማርያም ወደ ቀድሞ ወዳጆቻቸው መደዋወል ጀመሩና በመሃል ተስፋ ቆረጡ አሉ። አስር ለሚያህሉ አርሶአደሮች እና የሰራዊቱ አባላት ዘንድ ደውለው አልተሳካለቸውም። ለሁሉም ጥሪ ያገኙት ምላሽ “የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።” የሚል ሲሆንባቸው ራሳቸውን ነቀነቁ። ሰው […]

የዓለምን የጦር አቋም የሃገሮች ደረጃ የሚያወጣው “ግሎባል ፋየርፓወር” ዌብሣይት የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል ከሰሃራ በስተደቡብ ባለው አፍሪካ እጅግ ብርቱው መሆኑን አስታውቋል፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ቦኮ ሐራም የተሰኘው እስላማዊ አክራሪ ቡድን ናይጀሪያ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት ከባድ ጥቃቶችን ሲሰነዝር ቆይቷል። የናይጀሪያ ምርጫ በተቃረበበት በአሁኑ ወቅት ሰሞኑን ከፍተኛ እልቂት ያስከተለ የቦንብ ጥቃትም ሰንዝሯል። ለመሆኑ ቦኮሐራም ማን ነው? ከሽብርተኛ ቡድኑ ጀርባ የሰሜንና የደቡብ ናይጀሪያ ባላሥልጣናት እንቅስቃሴ ምን ይመስላል?

ለችግሩ መባባስ ምዕራቡ ዓለም ተጠያቂ የሚያደርጋት ሩስያ በኬቭ መንግሥት ላይ ወቀሳዋን አጠናክራለች ። ሩስያ የዩክሬን መንግሥት መገንጠል ከዩክሬን እንገንጠል በሚሉ ኃይሎች ላይ ፣ያለፈው ሳምንቱን ስምምነት በመጣስ ኃይል እየተጠቀመች ነው ስትል እየከሰሰች ነው ።

ከግጭቱ በኋላም በአዋሽና በሌሎች አካባቢች ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ወደ ከኢትዮጵያ ወደ ጅቡቲ ከጅቡቲም ወደ ኢትዮጵያ የሚወስደው መንገድ ተዘግቶ እንደነበርም ነዋሪዎች ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።የኢትዮጵያ ፌደራል ጉዳዮች መስሪያ ቤት በበኩሉ ሰዎች መሞታቸውን የሚያመለክት መረጃ እንዳልደረሰው አስታውቋል ።

ህገ መንግሥቱን የሚያረቁት ተወካዮች በሃገሪቱ ስር እየሰደደ የሄደውን ፖለቲካዊና ጎሳዊ ግጭቶች በተለይ በምስራቅ የሃገሪቱ ክፍል የሚቀርበውን የተጠናከረ የራስ ገዝ አስተዳደር ጥያቄ ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚኖርባቸው ተመልክቷል ። ረቂቁ እንደተጠናቀቀ ለህዝበ ውሳኔ ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል ።

Ethio-telecom sucks!ክንፉ አሰፋ

“የደወሉላቸው ደንበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም። …” የምትለዋ አሰልቺ የቴሌ መልዕክት ያላጋጠመው ቢኖር ወደ ኢትዮጵያ ስልክ ደውሎ የማያውቅ ሰው ብቻ መሆን አለበት። ኮ/ል መንግሥቱ ኃይለማርያም ወደ ቀድሞ ወዳጆቻቸው መደዋወል ጀመሩና በመሃል ተስፋ ቆረጡ አሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያየ አህጉር የምትኖሩ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችኹ፣ በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችኹ፣ እንዲኹም የሕግ ታራሚዎች ኾናችኁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፤ እርሱ ሕያው ኾኖ ሕያዋን መኾናችንን በትንሣኤው ላበሠረን ለጌታችን ለአምላካችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ እንኳን በሰላም …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በምሥራቅ ዩክሬይን መፍቀሬ ሩሲያውያን ኃይላት በስሎቭያንስክ የሠዓት ዕላፊ ገደብ አወጁ። በአዋጁ መሰረት ማንኛውም ሰው የሠዓት ዕላፊው ገደብ ሳይጠናቀቅ ወደ ውጭ ወጥቶ መንቀሳቀስ አይፈቀድለትም።

በምሥራቅ ዩክሬይን መፍቀሬ ሩሲያውያን ኃይላት በስሎቭያንስክ የሠዓት ዕላፊ ገደብ አወጁ። በአዋጁ መሰረት ማንኛውም ሰው የሠዓት ዕላፊው ገደብ ሳይጠናቀቅ ወደ ውጭ ወጥቶ መንቀሳቀስ አይፈቀድለትም።

በመኾኑም ታጋዮቹ የመንግሥትነት ሥልጣንን ሲቆናጠጡ ቤተ ክርስቲያንን የማጥቃት የቀደመ ሕልማቸውን አሐዱ አሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከዚህ ቀደም ይዛ የነበረውን መሬት መንጠቅ፣ በግፍ የተነጠቀቻቸውን ቤቶችና ሕንፃዎች አሟልቶ አለመመለስ፣ ቤተ ክርስቲያኗ በማኅበረ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በተለይም የማስታረቅና ግጭቶችን በሰላም የመፍታት ተልእኮዋን በመንጠቅ አዲስ ለተመሠረቱት ፖሊቲካዊ ማኅበራት መስጠት፤ ከዚኽም ባሻገር ከትጥቅ ትግል አንሥቶ በስለላና በሌሎች ተግባራት ህወሓትን ሲያገለግሉ የነበሩ ‹‹ታጋይ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በቦር፣ ጆንግሌይ የሚገኘውን የተመድ ሰፈር አጥቅተው ቢያንስ 50 ሰዎች ገደሉ። በዚሁ ቢያንስ 5000 ሰዎች ከለላ ባገኙበት ሰፈር በተጣለው ጥቃት ከቆሰሉት መካከልም ሁለት የተመድ ሰላም አስከባሪዎች ይገኙባቸዋል።

(አዲስ ጉዳይ፤ ቅጽ ፰ ቁጥር ፪፻፲፪፤ ሚያዝያ ፳፻፮ ዓ.ም.) ዲያቆን ዳንኤል ክብረት እስከ አሁን በታተሙ ቅዱሳት መጻሕፍትም ኾነ ለጥምቀት በታተሙ ካኔቴራዎች ላይ በኤፌሶን ፬÷፬ ላይ ያለው ጥቅስ ከነመገኛው ተጠቅሶ ከመታተሙ በቀር አንድ ሀገር የሚል የለውም፡፡ ከእውነታ አንጻር ይህን ጥቅስ መጥቀስ በራሱ ስሕተት ነው፤ የሌለን ነገር እንዳለ አድርጎ ማቅረብ ነውና፡፡ ‹‹ጥቁር ድመትን በጨለማ ውስጥ መፈለግ አስቸጋሪ …

የፋሲካ በዓል መከበር ያለበት ሌሎችንም በማሰብ መሆኑን ብዑዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አሳሰቡ፡፡

በክርስቶስ ሞት ቤዛነት እግዚአብሄር የሰውን ልጅ የታረቀበት ነው ብለዋል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ።

ለዝርዝሩ ፓትርያርኩ በዓሉን አስመልክቶ የሰጡትን ቡራኬና ያስተላለፉትን መልእክት የተከታተለን እስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

ኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ላይ የሚታየው ስደተኞችን እያፈሱ የማሰር እንቅስቃሴ ዛሬ ጋብ ያለ ቢመስልም ሶማሊያዊያን ስደተኞች ወደ ዳዳብ፣ ኢትዮጵያዊያን ወደ ካኩማ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑ ተሰምቷል፡፡

ኪቱዪ ሻሪአ የሚባል ለስደተኞቹ ጥብቅና የሚቆም እና የሚሟገት ድርጅት ባልደረባና ጠበቃ የሆኑት አቶ ኡጁሉ ኦቻላ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የእየሱስ ክርስቶስ ስቅለት የሚታስበበት የስቅለት በዓል ዛሬ በመላው አለም በሚገኙ ክርስቲያኖች በሙሉ ተከብሮ ዋለ ። በዓሉ በተለይም በሺህዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች በተገኙበት በእየሩሳሌም ክርስቶስ መስቀል ተሸክሞ እንደተጓዘበትና ስቃይና መከራ እንደተቀበለበት በሚታመንበት መንገድ መስቀል ተሸክሞ በመጓዝ ተከብሯል ።

የሩሲያን ጨምሮ የዩክሬን የዩናይትድ ስቴትስና የአዉሮጳ ኅብረት ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ጄኔቭ ላይ ትናንት ባካሄዱት ዉይይት አማካኝነት የደረሱበት መግባባት በቀዉስ በተወጠረችዉ ሀገር የተባባሰዉን ሁኔታ ለማርገብ ያስችላል እየተባለ ነዉ።

ስቅለትከሆሳዕና እስከ ማዕዶት

ሰሎሞን ተሰማ ጂ.

በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል ተከብሮ የሚውለው፣ በዕለተ እሑድ ነው። ጌታችንና መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳው በዕለተ እሑድ-መጋቢት 29 ቀን ነው። የግዕዝ ቋንቋ ሊቃውንት እንደሚተረጉሙት ከሆነ፣ “ትንሣኤ ማለት-መነሳት ማለት ነው።” ሞትን ድል አድርጎ፣ ከሙታን ተለይቶ መነሳት ማለት ነው። “ሕይወት ማግኘት፣ ነፍስ መዝራት፣ ሕልው መሆን” ማለት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሶስት ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው በአዲስ አበባ የተለያዩ ሆስፒታሎች ገብተዋል “ረብሻውን ያነሱት ህዝብን የማይወክሉ ወሮበሎች ናቸው” የከተማው ኮሙዩኒኬሽን “ባህርዳር በተካሄደው የስፖርት ውድድር ላይ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ አድልዎ ተፈጽሟል” በማለት የተቧደኑ ወጣቶች፣ ባለፈው ሐሙስ የሱሉልታ ከተማ ነዋሪ የሆኑ በርካታ የአማራ ተወላጆች ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ በድብደባ በርካታ ሰዎች ከመጐዳታቸውም በተጨማሪ፤ ቤት ንብረት ላይም ጥፋት እንደደረሰ የተናገሩት ጉዳት […]

የሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን ሰልፍ ለማድረግ ላሰገባዉ የማሳወቂያ ደብዳቤ ፣ ከአዲስ አበባ አስተዳደር ምላሽ እንዳገኝ ሰማያዊ ፓርቲ ገለጸ። የአስተዳደሩ ደብዳቤ፣ ሰልፉን በታሰበው ሚያዚያ 19 ቀን፣ ማድረግ እንደማይቻልና ለሌላ ቀን እንዲያስተላልፈው የሚጠይቅ ሲሆን፣ የሰማያዊ ፓርቲ ግን፣ ለሰልፉ መራዘም የቀረቡት ምክንያቶች በቂ አይደሉም በሚል፣ ቀኑን እንደማይለወጥ፣ ባስገባው ሁለተኛ ደብዳቤ ለአስተዳደሩ አሳዉቋል። የሰማያዊ ፓርቲ በላከው ሁለተኛ ደብዳቤ፣ […]

ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)

የ1994 የሩዋንዳ የጭፍጨፋ እና የእልቂት ጸጸት በ2014 የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ሰማይ ላይ እያንዣበበ ነው!

ባለፈው ሳምንት የሩዋንዳ ህዝብ እርስ በእርስ የተራረደበትን 20ኛውን ዓመት የሩዋንዳ የዘር ፍጅት መጥፎ ገጽታ ለማስታወስ የሀዘን ሳምንት አውጆ ድርጊቱን በመራር ሀዘን ዘክሮታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ካሳ

ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ እንደጠራ አነበብኩ። ገረመኝ። መጋቢት 28 ቀን በአንድነት ፓርቲ ሰልፍ ይደረጋል ተብሎ ተጠብቆ ነበር። የአዲስ አበባ አስተዳደር ሕጉን ባፈረሰ መልኩ በመጋቢት 28 ቀን ሰልፍ ማድረግ እንደማይቻል ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ …