ቦሌ ወሎ ሰፈር በግድግዳ ላይ ፅሁፎች እና በመፈክር አሽብርቃ አደረች፡፡ (PHOTOS)
ቦሌ ወሎ ሰፈር በግድግዳ ላይ ፅሁፎች እና መፈክር በተፃፈባቸው ወረቀቶች አሽብርቃ አደረች፡፡አቡ ዳውድ ኡስማን በአዲስ አበባ በቦሌ ወሎ ሰፈር የሚገኙ የውስጥ መንገዶች በግድግዳ ላይ ፅሁፎች እና መፈክር በተፃፈባቸው ወረቀቶች አሸበርቃ ማደሯን ምንጮች አስታወቁ፡:
በቦሌ ወሎ ሰፈር ውስጥ ለውስጥ በሚያስኬዱ መንገዶች የሚገኙ ግድግዳዎች እና መንገዶች የህዝበ ሙስሊሙን ሰላማዊ የመብት ትግል የሚያንጸባርቁ መልዕክቶች ተፅፎባቸው አንግተዋል፡፡
ከተፃፉት እና ከተበተኑት መፈክሮች መካከል
አሸባሪ አይደለንም፣ የታሰሩት ሙስሊሞች ይፈቱ,ኮሚቴው ይፈታ፣የሂጃብ
ገፈፋው ይቁም፣ትግሉ ይቀጥላል፣ ፍትህ ናፈቀን
የሚሉ እና በርካታ መፈክሮች በግድግዳ ላይ እና በወረቀቶች ተፅፈው መበተናቸው ታውቋል፡፡
ህዝበ ሙስሊሙ የጀመረውን ሰላማዊ ትግል በማጠናከር የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ድምፁን እያሰማ ይገኛል፡፡
ድል ለጭቁኑ የኢትዬጲያ ሙስሊም!!



More Photos
https://www.facebook.com/profile.php?id … nref=story