ሻእቢያ ያገታቸውን ታጋዮቻችንን ለፕሮፓጋንዳ ሊጠቀምባቸው እያስገደዳቸው ነው ሲሉ የአማራ ንቅናቄ (አዲሃን)ምንጮች ገለጹ:: ‪

ሻእቢያ ያገታቸውን ታጋዮቻችንን ለፕሮፓጋንዳ ሊጠቀምባቸው እያስገደዳቸው ነው ሲሉ የአማራ ንቅናቄ (አዲሃን)ምንጮች ገለጹ:: ‪

Minilik Salsawi : የኤርትራ መንግስት በህገወጥ መንገድ ያገታቸውን እና የሰወራቸውን ታጋዮቻችንን በአስቸኳይ እንዲለቅ እንጠይቃለን በማለት በተደጋጋሚ መግለጫ ያወጣው የአማራ ንቅናቄ አይን ያወጣው ሻእቢያ ያገታቸውን አባሎቼን ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታው በማስገደድ ሊጠቀምባቸው ነው ማለቱን የንቅናቄው የውስጥ ምንጮች ከሰሜን ጎንደር ገልጸዋል::

ሕዝቦች ትክክለኛ መረጃ የማግኘት መብታቸው እየተገደበ ነው የሚሉት የንቅናቄው ምንጮች ከ70 በላይ የሚሆኑ የድርጅታችን አመራሮች እና ታጋዮቻችን በኤርትራ ወህኒ ቤቶች እየተሰቃኡ ከመሆኑም በላይ እንዲሁም በሺዎች የሚቆተሩ ኢትዮጵያውያን በእስር የማቀቁ ባሉበት ሁኔታ ሻእቢያ የነጻነት አባት በመምሰል በኢትዮጵያውያን ስም የሚሰጠውን ፕሮፓጋንዳ ምንም ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ ንቅናቄውን ዋቢ በማድረግ ጠቁመዋል::

– የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ በተደጋጋሚ የሰጣቸውን መግለጫዎች ዚህ ሊንክ ላይ ያግኙታል::

Please wait, video is loading…

– በድምጽ እዚህ ላይ ይጫኑት :

phpBB [video]

አስመራ የታገቱት የአማራ ንቅናቄ አባላት በሻእቢያ ከባድ እንግልት እየደረሰባቸው ነው::የሚለው ንቅናቄው በዚህ ዙሪያ መግለጫ ያወጣል ተብሎ የተጠበቀ ነው::

Image