በአበራ ለማ (ደራሲ፣ ጋዜጠኛና ባለቅኔ)

አንጋፋው የዲሞክራሲና የለውጥ አርበኛ አበራ የማነአብ የሰባ ሁለት አመት አዛውንት ናቸው። ከዚህ እድሜያቸው ውስጥ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ባፈላማ ይዟቸው ሃያ አምስቱን አመታት ባለም በቃኝና ወህኒ ቤቶች ቀርጧቸዋል። ከዚህ ውስጥ ባመክሮ ጥቂት አመታት አራግፈው አስራ ስድስት አመት ከስምንት ወራት በህሊና እስረኝነት አሳልፈዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ካሳ
በፌስቡክ የሚጽፋቸውን እየሰበሰቡ አንዳንድ ድረ ገጾች ያስነብቡናል። በመቀሌ ነው የሚኖረው። ወጣት ነው። አብርሃ ደስታ ይባላል። የሚያምንበትን ከመናገርና ከመጻፍ ወደኋላ አይልም። በቅርቡ ከጻፋቸው አስተያየቶች አንዱ፣ ልቤን ማረከው። እኔም በዚያ ላይ ጨመር ለማድረግ ፈለኩ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሐዲስ ዓለማየሁ Haddis Alemayehuዳንኤል ክብረት
የዛሬ 600 ዓመት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የተባለ ኢትዮጵያዊ ደራሲ “አርጋኖን” የተሰኘ መጽሐፍ ይደርሳል። ይህንን መጽሐፍ የተመለከቱ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንትም እጅግ ያደንቁና ለንጉሡ ለዐፄ ዳዊት ያቀርባሉ። ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም መጽሐፉን ተመልክተው በማድነቅ በወርቅ ቀለም እንዲጻፍ አዘዙ። አባ ጊዮርጊስንም ሸለሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት ወደ ኋላ (ክፍል ሁለት)
ያሬድ ኃይለማርያም ከብራስልስ
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት በኢትዮጵያዊያን ላይ እያሰፈነ ስላለው የፍርሃት ባህል ቀደም ሲል ባሰራጨሁት የዚህ ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል ውስጥ ባለሙያዎች በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ ለፍርሃት ባህል መስፈን መንሰዔዎች ያሏቸውን ነጥቦች ዘርዝሬ ነበር። 

ሙሉውን አስነብበኝ …

በሀገር ቤት የሰላማዊ ትግልን የሚከተለው ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው እሁድ ዲሴምበር 15 ቀን 2013 እ.ኤ.አ. በዋሽንግተን ዲሲ ህዝባዊ ስብሰባ አካሂዶ ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ የፓርቲው ሊቀመንበር ያደረጉትን ንግግር ኢሳት ዘግቦታል። (ቪዲዮውን ለመመልከት የማጫወቻ ቁልፉን ይጫኑ!)

ኢትዮጵያ የሁሉም እኩል ሀገር ትሆናለች
ደመቀ በሪሁን
በዓለም ላይ በየጊዜው በርካታ የታሪክ አጋጣሚዎች ይፈጠራሉ። አንዳንዶች የተፈጠረውን አጋጣሚ በሚገባ በመጠቀም ለአገርና ለህዝብ የሚጠቅም ታላላቅ ሥራዎችን ይሠራሉ፤ ሌሎች በአንፃሩ የተፈጠረውን አጋጣሚ በማባከን ሀገርንና ህዝብን የሚጎዳ ታሪካዊ በደል ይፈጽማሉ። ወያኔ በኢትዮጵአ በተፈጠረው አጋጣሚ ለመንግሥት ሥልጣን በቅተሃል፣ የተፈጠረውን አጋጣሚ ለምንና እንዴት እየተጠቀምክበት እንደሆነ መመልከት ጠቃሚ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በልጅግ ዓሊ

የማንዴላን ሕልፈተ ሕይወት ተመልክቶ በዓለም ደረጃ የሚያስደንቅ ሁኔታ ስናይ ሰነበትን። ማንዴላ የሠራውን መስራት ሳይሆን እሱ የታሰረበትን ዓላማ በተጻራሪ የሚተገብሩ ሁሉ በቀብሩ ላይ ለመገኘት ከተደበቁበት ብቅ ብቅ ማለታቸው የሚስደምም ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

PM Hailemariam Deslegne ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝግርማ ካሳ

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ብዙዎች እንደ “እግዚአብሔር ሰው” ይቆጥሯቸዋል። በየቀኑ ፀሎት እንደሚያደርጉ፣ መጽሐፍ ቅዱስን እንደሚያነቡም ይናገራሉ። እርግጥ ነው፣ ሰዎች ፀሎት ሲያደርጉና መጽሐፍ ቅዱስ ሲያነቡ፣ መልካም ነው። ነገር ግን ፀሎት ማድረግና መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ፣ በራሱ የእግዚአብሔር ሰው ያሰኛል ብዬ አላስብም። ቄስ፣ ወንጌላዊ፣ ፓስታር፣ ጳጳስ … መሆን የእግዚአብሔር ሰው አያሰኝም። መስቀል ይዞ መዞር፣ በያሬዳዊ ዜማ ቅኔ መዝረፍ፣ በልሳን መፀለይ … የእግዚአብሔር ሰውነት መመዘኛ አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ነጻነት ለሀገሬ)
ኔልሰን ማንዴላ Nelson Mandela
ኔልሰን ሮሺስላሽላ ማንዴላ ለነጻነት የሚያደርጉትን ረዥሙን ጉዞ እ.ኤ.አ በ2013 መገባደጃ ወር ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ደመደሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

ባለፈው ሳምንት የምስራቅ ኢትዮጵያ ፖለቲካን ተጨባጭ እውነታዎችን ቃኝቼ ተከታዩን ክፍል በይደር አቆይቼው እንደነበረ ይታወሳል፤ እነሆም ዛሬ እንዲህ እቀጥላለሁ፡-
ሐረር እንደ ማሳያ
(መቼም ኢህአዴግ በብቸኝነት የሚኩራራበት የፖለቲካ ‹ስኬት›፣ ለዘመናት አንድ ሆኖ የኖረ ሕዝብን ‹ብሔር ብሔረሰቦች› በሚል ከፋፋይ የ‹ክርስትና ስም› እጥምቆ በአደባባይ ማስጨፈር ከሆነ ሰነባብቷል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

አማኑኤል ዘሰላም

በምርጫ ዘጠና ሰባት ወቅት የነበረውን ሁላችንም የምናስታወሰው ነው። ያኔ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፁን ለቅንጅት ቢሰጥም፣ ህወሓት/ኢሕአዴግ የሕዝቡን ድምፅ ነጥቆ እስከአሁን ድረስ በኃይልና በጡንቻ እየገዛ ነው። በሥልጣን ላይ ለመቆየት በቀዳሚነት አገዛዙ የወሰዳቸው አምስት እርምጃዎች ነበሩ። እነርሱም …

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነፃነት ዘለቀ – ከአዲስ አበባ

የግርማ ካሣን ጽሑፎች አልፎ አልፎ አነባቸዋለሁ። ሀገር ወዳድ መሆኑን ይጠቁማሉ – ጽሑፎቹ። ታታሪ ሰው ይመስለኛል፤ በጥረቱና በሀገር ፍቅር ስሜቱ እወደዋለሁ። ሁልጊዜ ሳይታክት ይጽፋል። ሳይታክቱ የሚጽፉ ብፁዓንነት የሚበዛባቸው ቢሆን ዕድለኞች ግን ናቸው። ብዙዎቻችን እየደከመን መጻፍ ቀርቶ ማንበባችንንም እያቆምን በምንገኝበት ሰዓት አዘውትሮ መጻፍ መታደል ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዘለቀ ረዲ

የተከበራችሁ አንባቢያን በተለመደው ግንኙነተችን መሰረት ዛሬ ከእዲስ አበባ ተነስቼ ገላን፣ ዱከም፣ ደብረዘይት፣ ቢዮዲማ፣ ሞጆ፣ ሙዳ፣ ኤጀርሳ፣ ቆቃ፣ ዐለምጤና፣ መቂ ዝዋይ አድርጌ ጉዳየን ጨርሼ ወደአዲስ አበባ ለመመለስ ያቀድኩ ቢሆንም በመንገዱ መጨናነቅ ሳቢያ በመጣሁበት መንገድ ተመልሼ አዲስ አበበ መግባት ከባድ እንደሆነ ስለገመትኩ በዚያ መመለስ ሰዓቴን እንደሚጨርስ ስለተረዳሁ በዝዋይ ቡታ ጅራ እዲስ አበባ መመለስን መረጥኩ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግንቦት ሰባት Ginbot-7ግርማ ካሳ

በቅድሚያ ሰላምታዬ ይድረሳችሁ። ከአምስት ዓመታት በፊት ከአንዳንዶቻችሁ ጋር፣ በቅርበት፣ በቅንጅት ድጋፍ ማኅበራት ውስጥ አብረን ሰርተናል። አብረን ለሰላም ለዲሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነት መስፈን፣ ለዜጎች ሰብዓዊ መብት መከበር፣ ለሕሊና እስረኞች መፈታት ስንጮህ፣ ስንሰራ፣ ስንደክም፣ ስንመክር ነበር። መሃከል መንገድ ላይ የፖለቲካ ስትራቴጂ ልዩነቶች ተፈጠሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይድነቃቸው ከበደ Yedenekachew Kebedeይድነቃቸው ከበደ
ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም ሕገ-መንግሥቱ የፀደቀበት ቀን ነው። ይህንንም ተከትሎ በመንግሥት አሳሳቢነት እልፍ ሲልም አስገዳጅነት ህዳር 29 በየዓመቱ ከተለያዩ ጎሳ የተወጣጡ ሰዎች ተሰባስበው በመንግሰት ሹማምንቶች ፊት በአደባባይ ከበሮ የሚደለቅበት ቀን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በዳዊትከበደወየሳ

ተጨማሪ ማስታወሻዎችና ከኢትዮጵያ የወሰዱት ሽጉጥ መጨረሻ

የነጻነት ታጋዩ ኔልሰን ማንዴላ በ95 አመታቸው ከዚህ አለም ሲለዩ፤ የተለያዩ አገሮች እንደየራሳቸው ግንኙነት የራሳቸውን ታሪክ ሲያወሩ ነበር። የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ሃዘናቸውን ሲገልጹ ከማንዴላ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት በመግለጽ ነበር። እኔ በምኖርበት አትላንታ ከተማ ዜናው ሲቀርብ፤ ኔልሰን ማንዴላ አትላንታ በመጡበት ወቅት፣ ከነአንድርው ያንግ ጋር ሆነው የማርቲን ሉተር ኪንግ ማዕከልን ስለመጎብኘታቸው ነበር – ዋናው ዜና። ሁሉም አገር ስለማንዴላ የየራሱ ትዝታ አለው። ኢትዮጵያውያንም ስለኔልሰን ማንዴላ የራሳችን ታሪክ እና ትዝታ አለን። እናም ማንዴላ የዛሬ 51 አመት ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ስለነበረው ጉዳይ በማውጋት ታሪካችንን እንጀምራለን።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopian foodፕ/ር መስፍን ወልደማርያም
አበሻ ድግስ ይወዳል፤ ድግስ የሚወደው መብላትና ማብላት ስለሚወድ ነው፤ ለመብላት የአበሻ ምክንያቱ ብዙ ነው። ልጅ ተወለደ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ ክርስትና ተነሣ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ አገባ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ ሞተ ብሎ መብላት ነው፤ አበሻ ሰው ቀብሮ ሲመለስ በንፍሮ ይጀምርና ቀስ በቀስ ወደሌላው ይተላለፋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኔልሰን ማንዴላ Nelson Mandelaመራራ ስንብት – ከመብራታችን ጋር …
ሥርጉተ ሥላሴ

በዘመነ ወያኔ የተከበሩ ማንዴላ የተስፋዬ ሀገር የሚሏትን ሀገርና ህዝብ፤ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵውያንን ሳያዩ አረፉ። ስለ ምን? ለጥቁሮች የተፈሪነት ፍጹም ልዩ ዓርማ የሆነችውን የሀገራችንን ቀደምትነት፤ ያን የአፍሪካዊ የጥቁር ገድል፤ የቅኝ ግዛትን ቀንበር በምኞት ያስቀረ የፈካ ታሪክ በዕብሪትና በበቀል የጣሰው የወያኔ ሓርነት ትግራይ ማንፌስቶ አልተመቻቸውም ነበርና።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሕዳር 25  ቀን 2006 ዓ.ም. Dec 5, 2013)አፓርታይድን ከምድረ ሳውስ አፍሪካ እስከመጨረሻው ለመገርሰስ በተደረገው ታላቅ ተጋድሎ በዋንኛነት ተጠቃሽ የነበሩትና የሰላም አባት በመባል አላማቀፋዊ ሽልማቶችን የተጎናጸፉት የደቡባዊት አፍሪካ የነጻነት አባት ኔልሰን ማንዴላ አረፉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ Dr. Berhanu Negaግርማ ካሳ

“የኢሕአዴግ መራሹ መንግሥት ለግንቦት ሰባት የእንደራደር ጥያቄ አቀረበ” ሲል ኢሳት ሰበር ዜና አሰማን። ዶ/ር ብርሃኑ ነጋንም በማቅረብ በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ እንዲሰጡም አድርጓል። ምንም እንኳን የቀረበውን ዘገባ ከሌላ ምንጭ ማጣራት ባይቻልም፣ ዜናው እውነት ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ግን ይሰማኛል። አገዛዙ ከኦብነግ፣ ኦነግ ከመሳሰሉ ጋር ድርድር እየጀመረ፣ የማቋረጥ ልማድ እንዳለው ታሳቢ በማድረግ። የግንቦት ሰባት “እንደራደር” ጥያቄም ከዚያ የተለየ አይሆንም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም Prof. Al Mariamፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ)
በአረብ አገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሠራተኞች ላይ የሚደረገው ህገወጥ የማሰቃየት እርምጃ በአስቸኳይ ይቁም! በአሁኑ ወቅት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሰራተኞች ላይ በሪያድና በአዲስ አበባ ከተሞች ባሉ ገዥ አካሎች እየተፈጸመ ያለው የሰብአዊ መብት እረገጣ ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያውያን/ት የዲያስፖራ ማህበረሰብ ለጉዳዩ ልዩ የሆነ ትኩረት እንዲሰጡትና ለወገኖቻቸው የማያቋርጥ ድጋፍ እንዲያደርጉ ምቹ አጋጣሚን ፈጥሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

 ተመስገን ደሳለኝ – ከአዲስ አበባ

…አውሮፕላኑ ቅዳሜ ጠዋት ሶስት ሰዓት ላይ ድሬዳዋ አየር ማረፊያ ደርሶ ከተርሚናሉ ስወጣ፣ ተጠራጥሬ ሰዓቴን ተመለከትኩ፤ የድሬ የጠዋት ፀሐይ ከተለመደው ንዳዷ ጋር የአዲስ አበባን የቀትር መራራ ፀሀይን ታስከነዳለች፤ እናም አጥበርባሪ ጨረሯን ያለምህረት ስትለቅብኝ፣ ጓደኛዬ መኪና ይዞ እቦታው እስኪደርስ መጠበቁ በገዛ ፍቃድ መለብለብ ስለመሰለኝ፣ በቀጥታ ከተደረደሩት ታክሲዎች አንዱን ይዤ ወደ ከዚራ አመራሁ፤ ድሬ የሄድኩት በዋናነት ከማህበራዊ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ምክንያት በመሆኑ ሊቀበለኝ የተዘጋጀውን ጓደኛዬን ደውዬ ከማውቃቸው የአንዱን ሆቴል ስም ጠቅሼ እዚያ እንድንገናኝ ነገርኩት፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

“ኢሕአዴግ ሃገሪቱን ወደ እርስ በርስ ጦርነት እንዳይከታት እሠጋለሁ” ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ

ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር ናቸው፡፡ ላለፉት 30 ዓመታት በአሜሪካ ኖረዋል፡፡ የየትኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆኑና ሆነውም የማያውቁት ዶ/ር ዳኛቸው በሀገሪቱ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ግን ምሁራዊ አስተያታቸውን በየጊዜው ይሰጣሉ፡፡ ከዶ/ር ዳኛቸው ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሎሚ አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ያደረገው ቆይታ ይህንን ይመስላል፡-

ሙሉውን አስነብበኝ …

ክንፉ አሰፋ
በሳውዲ የተነሳው የወገን ሰቆቃ ገና አልበረደም። ስቃዩ የበለጠ ሲከፋ እንጂ ሲቀንስ አላየንም። ለውጭ ምንዛሪ ማግኛ ሲባል ልክ እንደ ባርያ ንግድ በቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ በኩል የተላኩት ምስኪን ኢትዮጵያውያን ጉዳይ በገዥው ፓርቲ እንደታሰበው አልሆነም። እንዲያውም ሌሎች መዘዞችን አስከትሎ መጥቷል። ዲያስፖራው እንደገና ተነሳ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በሳዑዲ ዐረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለውን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት አስመልክቶ “ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ” ሊቀመንበር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር አድሃኖም ገብረየሱስ የጻፉትን ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ልከውልናል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሥርጉተ ሥላሴ Seregute Selaseለልጅ ተክሌ የተሰጠ ምላሽ

ሥርጉተ ሥላሴ

አረሙ ወያኔ በየትኛውም መስፈርት ኢትዮጵያዊነትን የመቀማት ሞራሉም ሆነ አቅሙም የለውም – በጣም በእርግጠኝነት!

ጤና ይስጥልኝ ሞገደኛው ተክሌ እንደምን ሰነበትክ? ደህና ነህ ወይ? የብዕር አጣጣልህ እንደ አቤ ቶኬቻው ውብ ስለሆነ ለረጅም ጊዜ እያደንኩ አነባለሁ። ጠረባህንም አክሎ። በጠረባህ ዙሪያ አንድ ቀን የምለው ይኖረኛል … ዛሬ ግን ልታገሰው ስላልቻልኩት ማለት ፈለግኩ … በሦስት ነገሮች ዙሪያ … እንዲህም እላለሁ … እኔው …

ሙሉውን አስነብበኝ …

በሳዑዲ ዐረቢያ ግፍ እየደረሰባቸው ያሉ ኢትዮጵያውያን Violence Against Ethiopians in Saudi Arabiaየማለዳ ወግ፦ የጅዳ ሸረፍያ እስከ ሽሜሲ የተሰማው የወገን ዋይታና እዚህ ያደረሰን መንገድ!

ነቢዩ ሲራክ

ፈታኙን ወቅት ለማለፍ …

የሳውዲ የምህረት አዋጅ አልቆ በሪያድ መንፉሃ ላይ አለምን ያሳዘነ ሰቆቃ ተፈጸመ … ስጋት ነግሶ፣ ኑሮ ከብዶን ጨንቆን ጠቦን ከርመናል! በዚህ ክፉ ቀን ወገን ወገኑን ለመርዳት ደፋ ቀና በማለቱ ረገድ የሃገሬ ልጅ ከጫፍ እስከ ጫፍ በቁጭት ስሜት ሲንቀሳቀስ የፖለቲካው ትኩሳት ወላፈን እያጓተተን አልሰነበትንም አይባልም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ቅዱስ ዮሃንስ

ትምህርት ዜጎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ በመቅረጽ ለራሳቸው፣ ለማህበረሰባቸውና ለሀገራቸው ጠቃሚ ዜጋ እንዲሆኑ የሚያግዝ የእውቀት ማሸጋገርያ ስልት ነው። ዛሬ በስልጣኔ የገሰገሱ የአለም ሀገራት የዕድገታቸው ዋነኛ መነሻ ትምህርት ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይሄይስ አእምሮ

ከጥቂት ሣምንታት ወዲህ በተለይ የኢትዮጵያን የወያኔ መንግሥት በሚቃወሙ የሚዲያ ማዕከላት ዘንድ ዋና መነጋገሪያ ሆኖ የሚገኘው በሳዑዲ የኢትዮጵያውያን መንገላታትና መሰቃየት እንዲሁም ከኢሰብዓዊነትም በወረደ ሁኔታ በግፍ መጨፍጨፍ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተክለሚካኤል አበበ (ቶሮንቶ-ካናዳ)

የሳኡዲ ግፍና የኛ ሰልፍ፤

እንደመግቢያ፤ የፋና ነገር

1.         ፋና፤ ኢትዮጵያዊ ካናዳዊት ነች፡፡ ቆንጆ ነች፡፡ እሱዋ እንደምትለው ከሆነ ፖለቲካ አትወድም፡፡ በአባይ ቦንድ ሽያጭና በመሰል የመንግስት መርሀ ግብር ዝግጅቶች ላይ ግን ቀድማ የምትገኝ ጎበዝ ነች፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ተቃዋሚዎች መፈክር ይዘው በኢህአዴግ ላይ ሲሰለፉ ስትመለከት ግን ደምዋ ይፈላል፡፡ ሰሞኑን በዚህ በሳኡዲአረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ግፍ ስላሳዘናት፤ ሳውዲዎችን ልክ ልካቸውን ልትነግራቸው ቆርጣ ተነስታለች፡፡ ስለዚህም በመጪው አርብ መሰል ጉዋደኞችዋን ይዛ ሰልፍ ልትወጣ ተፍ ተፍ ትላለች፡፡ በፋና እምነት በሳኡዲ በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ሰቆቃ፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር የለም፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ቴዎድሮስ አድሃኖም Tewodros Adhanomኤፍሬም ማዴቦ
የኢትዮጵያ ህዝብና እናስተዳድረዋለን የሚሉት አምባገነን ገዢዎቹ ተስማምተውና አንዱ ሌላውን አክብሮ የኖረበት አንድም የታሪክ አጋጣሚ የለም። የእስከዛሬው ታሪካችን ምዕራፍ በጥቅሉ ሲታይ ታሪካችን የሚቋጨው ህዝብ ተረገጠ፤ ተጋዘ፤ ገዢዎች ደግሞ ረገጡ፤ ገዙ፤ አሰሩ፤ አጋዙ እየተባለ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አሸናፊ ንጋቱ
በስልጣን ላይ ያለው የወያኔ መንግስት የዛሬ 22 ዓመት አንግቦት የነበረውን የዲሞክራሲ መፈክር በማየት ዲሞክራሲ የጠማው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ ጮቤ በመርገጥ ነበር የተቀበለው። ነገር ግን ይህ መፈክር ድራማ መሆኑ እየዋል እያደረ ነበር እየተጋለጠ የመጣው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም፣ ትርጉም፦ ነጻነት ለሀገሬ

ባለፉት አስርት ዓመታት በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች በአገራቸው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አህጉር በተለየ መልኩ ተንሰራፍቶ እየተፈጸመ ካለው ጭካኔና ርህራሄ የጎደለው አምባገነናዊ ስርዓት ለማምለጥ ሲሉ እግራቸው ወዳመራቸው አገር በመሰደድ ላይ ይገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አበራ ሽፈራው ከጀርመን
በተለይም ባለፉት 22 ዓመታት በሀገራችን ለተከናውኑት አበይት ችግሮች ሁላችንም እጆቻችንን ወደ ህወሓት እየቀሰርን ለችግሮቻችን መፍትሔ መስጠት አቅቶን ይባሱኑ ለከፍተኛ ስቃይና መከራ መዳረጋችንና፤ መፍትሔውን ከህወሓት እየጠበቅን ለችግራችን መባባስ አስተዋጽኦ በማድረጋችን ችግራችን እየተባባሰ ቀጥሏል። በምን መልኩ ነው አስተዋጽኦ አደረግነው?

ሙሉውን አስነብበኝ …

እሁድ ኖቨምበር 24 ቀን 2013 (እ.ኤ.አ.) በፍሎሪዳ ስቴትስ በምትገኘው ታምፓ ቤይ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት በሳዑዲ ዐረቢያ በሚገኙ የኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ኢሰብዓዊ በደል ከልብ እንዳስቆጣቸው ገልጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

PM Hailemariam Desalegn ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝግርማ ካሳ
በሕገ መንግሥቱ መሰረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰብሳቢ ናቸው። የጦር ኃይሎች ኤታ ማጆር ሹምን፣ ተቀዳሚ ጠቅላይ ሚኒስትርን፣ የሚኒስቴር ካቢኔዎችን፣ የፌደራል ፖሊስ አዛዦችን … የመሾምና የመሻር ሙሉ ሥልጣን አላቸው። ፓርላማውን በትነው አዲስ ምርጫ መጥራትም ይችላሉ። ፓርላማው በፈለገ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትሩን አውርዶ፣ ሌላ መሾም ይችላል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም ተጠሪነታቸው ለፓርላማው ብቻ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ቅዱስ ዮሃንስ

ፀረ -ሽብርተኝነት ለአምባገነኖች ሁለት ጥቅም ያስገኝላቸዋል። አንደኛ በፀረ- ሽብርተኝነት ስም ከምዕራባውያን ኃያላን ጎን በአጋርነት በመቆማቸው በጥሬ ገንዘብም ሆነ በዓይነት (ለምሳሌ በመሣሪያ፣ በፖለቲካ ድጋፍ) ዳጎስ ያለ ጥቅም ያገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት (የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር) Eng.Yilkal Getnet Chairman of Blue Party.ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
(የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር)

ሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እያደረሰች ያለውን ግፍና በደል በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ፓርቲያችን በወሰነው መሰረት ለሚመለከተው ክፍል አሳውቀን ነበር። መቼም ህዝባችን በጭቆና ውስጥ ስለኖረ በመብቱና በግዴታው መሀል ያለውን ድንበር በውል ካለመረዳቱ የተነሳ ሰልፉ እንዲደረግ ስለመፈቀዱ በተደጋጋሚ ስንጠየቅ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዓለማየሁ ዲባባ

የሳዑዲ ሕዝቦች በአንድ የታሪክ ዘመናቸው በኃይማኖት ልዩነት እርስ በእርሳቸው ተፋጅተው ወደ ኢትዮጵያ በተሰደዱ ወቅት ተቀብለናቸው አኑረናል፣ አስጠልለን መግበናል፣ አልብሰን አርዘናል። ከለላ እና ጥበቃ ሰጥተናቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፊልጶስ
የግፍ ጽዋው ሞልቶ፣ …
ሞልቶ፣ … ሞልቶ ፈሶ
ሰው መባል በሰው፣ ስዕብናችን አሶ
ከ’ጥናፍ – እስከ – አጥናፍ፣ ደማችን “‘ረክሶ”፤
ውቅያኖስ፣ ባህሩን፣ ወንዙን አደፍርሶ
እዩት ይ’ጣለላል፣ አስፋልቱን አልብሶ።
ግን እኮ፣ … እንኳ’ ደም
ውኃ ፈሶ፣ አይቀርም
ይዘገያል እንጂ፣ በሰፈሩት ቁና፣ መሰፈር አይቀርም።
“ዓለም የም’ጠፋው፣ ሰይጣናዊ ምግባር በሚፈጽሙ ሳይሆን፤ ምንም ሳያደርጉ ቀጭ ብለው በሚመለከቷቸው ሰዎች ነው።” /አልበርት አነስታይን/

ሙሉውን አስነብበኝ …

አበራ ሽፈራው ከጀርመን
በአረቡ ዓለም ከፍተኛ ተሰሚነትና የመላው ዓለም አይን ሁሉ በተለየ መልኩ በሚያያት ሳውዲአረቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰው አሰቃቂ ግፍና መከራ ለትውልድ የማይረሳ ክፉ ታሪክ ጥሎብናል፤ ዛሬም ሰቆቃው ቀጥሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

የዚህ ፅሁፍ ማጠንጠኛ የፖለቲካ አመለካከትን መተቸት አይደለም፤ ከዋና ዋና  ገራዊ አ ንዳዎች ወረድ ያሉ የጉልበታሙን ስርዓት የሥራ አፈፃፀሞችን ማብጠልጠልም አይደለም፤ የተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ስንክሳር መንቀስም… አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊ (አል- በሽ) መሆን ለፈተና፣ ለመከራ፣ ለሰቆቃ… መዳረጉ የወለደው ብሶት እንጂ፤ መመረር-ማምረር ነው፡፡ …ይህ የእኛ ዕጣ ፈንታ የሆነበትን ምስጢር መመርመር ነው፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢያሱ ዓለማየሁ

የኢሕአፓ 41 ዓመት መራራና ረጅም ትግል ረጅም ትግስትን ጠይቋል። አያሌ ፈተናዎችን ተቋቁሞና አልፎ ዛሬም ህልውናውን ጠብቆ በትግሉ ሜዳ ላይ መገኘቱ በቅድሚያ የአባላቱታሪክን ገርተውና ጽፈዋት ያለፉትም ሆነ በሕይወት ያሉትን ጽናትና ቆራጥነትየሚመለከት ነው። ኢሕአፓን ለመመስረትና መስርቶም ለማታገል በተደረገው ትግል በታሪክ አጋጣሚ ዋና ተካፋይ ሆኜ በመቆየቴ የሚሰማኝ ደስታና ክብርም ወደር የለውም። ሀቁ ይህ ድርጅት ከቶም ባልተመሰረተ የሚሉት ጠላቶች እንደ ነበሩትና እንዳሉት ሁሉ (በአብዛኛው ከስርዓቶቹ ጋር የተያያዙ) ቤዛችን ነው፣ የወኔያችን መከሰቻ ነው፣ የሀገር አለኝታችን ነው ድርጅታችን ነው የሚሉ ደሞ ብዙዎች ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተመስገንደሳለኝ

በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም በተፈጥሮ ሞት ነውና፡፡ በ1983 ዓ.ም ወርሃ ግንቦት በጠብ-መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ-መራሹ መንግስትም ቢሆን፣ በቀድሞዎቹ ገዥዎች ‹የብረት ጫማ› ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ-ስንብቱን በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነብዩሲራክ

ትናንት እንደ ቀልድ …
በያዝነው የፈረንጆች 2013 ዓም በወርሃ መጋቢት አጋማሽ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ” ህጋዊ ሰነድ ያልያዙትን አስወጣለሁ !” ብላ አወ ች ። ቀጠለና አፈሳ አሰሳው ተከተለ! አስፈሪው ያ ክፉ የጭንቅ ቀን በሳውዲው ንጉስ ሌላ የምህረት አዋጅ ተተክቶ ህገ ወጥ የተባሉትን ህጋዊ በሚያደርግ ህግ ተተካና የምህረቱ አዋጅ በያዝነው ህዳር መባቻ እንደሚያልቅ በተጠቆመው አዲስ የምህረት አዋጅ ተተካ !

ሙሉውን አስነብበኝ …

ምስጢሩ The Secretክፍል አምስት (ወለላዬ ከስዊድን)
ምስጢሩ ወደኛ እየቀረበ ይሆን?
የምስጢሩን መጽሐፍ እያሳጠርኩ በመጻፍ ላይ እያለሁ ምስጢሩን የሚያጠናክር ነገር ገጠመኝ። ከወዳጄ ያሬድ ክንፈ ጋር አልፈን አልፈን ውሃ የምንጎነጭባት ቤት አለች። እንደወትሮው በዛው ቤት ተገኝተናል። አንዲት ወጣት ስዊድናዊት ልታስተናግደን መጣች። ለጓደኛዬ የሞቀ ሰላምታ ሰጠችው። ስትስቅ ጉንጭና ጉንጮቿ ላይ የሚወጡት ጎድጓዳ ምልክቶች ዓይን ይስባሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ጌታቸው ካሳ

ኢሕአዴግን እንደ አንድ የሚመለከቱ፣ ሁሉን አባላቶቹን በጅምላ የሚፈርጁ ጥቂቶች አይደሉም። ነገር ግን ኢሕአዴግ ውስጥ የተለያዩ ቡድኖች አሉ። አንዱ የገነባውን አንዱ ያፈርሳል። አንዱ ሲያነሳ አንዱ ይጥላል። አንዱ ሰላማዊ ሰልፍ ሲፈቅድ፣ አንዱ በጎን የዜጎችን ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት ይጋፋል። አንዱ የታሰሩ የሕሊና እስረኖች እንዲፈቱ ሲፈልግ፣ ሌላው “እዚያው ቃሊቲ ይበስብሱ” ይላል። አንዱ በጎና ቀና ሕሊና ሲኖረው፣ ሌላው ደግሞ የጠመመና የጫካ አስተሳሰብ ያለው ሆኖ ይገኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አንዱዓለም ተፈራ

ዘግናኙ የስደተኛ ኢትዮጵያዊያን ግፍ በሳዑዲ አረቢያዊያን እጅ፤ ከፊታችን ተደቅኗል። ሁላችን በያለንበት፤ “ለምን? ምን አደረግን? መጨረሻው ምንድን ነው? መቼ ነው ይኼ ሁሉ የሚያበቃው?” እያልን እርስ በርሳችን እየተጠያየቅን ነው። እኛ ወደ የምንፈልገው መንገድ ካልገባን፤ ሌላ ሊይስገባን የሚችል ኃይል የትም የለም። በሳዑዲ አረቢያ የተደረገውን ኢሰብዓዊ ድርጊት፤ ሁላችን ኢትዮጵያዊያን በግል በራሷና በራሱ እንደተደረገ በደል አድርገን ወስደነዋል። ተገቢም ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ወገን ለወገን ደራሽ ነው

ሜሮን አድማሱ ከኖርዌይ
በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵዊያን በሚኖሩባት ሳውዲ ዐረቢያ በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ እያደረገችው ያለችው ኢሰብዓዊ ድርጊት ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ሲሆን፣ ከአንድ ኃይማኖት አለን ከሚል ሀገር የማይጠበቅ አሳፋሪ ተግባር ነው። በታሪክ እንደሰማነው የነብዩ መሐመድ ተከታዮች ሲሠደዱ ኢትዮጵያ በጊዜው ተቀብላ መኖሪያና ማምለኪያ ቦታ እንዳልሰጠቻቸው ሁሉ፤ ዛሬ ግን በኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ላይ እያደረሰችባቸው ያለው ስቃይና እንግልት ውለታ በይነቷን ያሳያል።

ሙሉውን አስነብበኝ …