ጀርመን በበርሊን ባዘጋጀችው እና ትናንት በተካሄደው ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ የስቴድየም ውድድር በሶስት ሺህ እና በአንድ ሺህ አምስት መቶ ሜትር ሩጫ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ታሪኩ በቀለ እና መኮንን ገብረ መድህን አንደኛ እና ሁለተኛ በመውጣት አሸናፊ ሆነዋል። ኬንያዊው ዴቪድ ሩዲሻም አስራ ሶስት …

ኢትዮጵያውያን በበርሊኑ አትሌቲክስ ውድድር Read more »

የኤኮኖሚክስ እና የአካውንቲንግ ምሁራን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ባቀረቡት የአምስት ዓመት የኤኮኖሚ መርሀ ግብር ሳይንሳዊ የኤኮኖሚ ግብዓቶች ላይ ያልተመሰረተ መሆኑን አመለከቱ። ምሁራኑ የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ ጠቅላይ ሚንስትሩ ባቀረቡት መንገድ ሊያድግ የሚችልበት የተመቻቸ ተጨባጭ ሁኔታ አለመኖሩን ገልጸዋል። ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

የተመድ ከአስር ዓመታት በፊት ባስቀመጠው የአምአቱ የልማት ግብ በዋነኝነት የድሆቹን ሀገሮች የጤና፣ የትምህርት ሁኔታን ለማሻሻል እና ድህነትን ለመቀነስ አቅዷል። የተመድ ከአስር ዓመታት በፊት ባወጣው የአምአቱ የልማት ግብ መሰረት በድሆቹ የዓለም ሀገሮች ውስጥ የሚታየውን የህጻናት ሞት እስከሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በጉልህ የመቀነስ …

የአምአቱ የልማት ግብ እና አንጎላ Read more »

አክራሪ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አል-ሸባብ «የደነበሸ» ያለዉን የርዳታ እሕል እሰበሰበ ማቃጠሉን አስታወቀ።ቡድኑ ከርዕሠ-ከተማ መቃዲሾ ሰብስቦ ያቃጠለዉ አምስት መቶ ከረጢት እሕል የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ድርጅት (WFP) ያከፋፈለዉ በቆሎና ስንዴ ነበር።የአል-ሸባብ የሞቃዲሹ አገረ-ገዢ ሼኽ አሊ መሐመድ ሑሴይን እንዳስታወቁት እሕሉ ለምግብ የሚዉልበት ጊዜ …

ሞቃዲሾ-አልሸባብ «የተበላሸ» እህል ቀበረ Read more »

በአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አባላት መካከል ከዚህ ቀደም የተነሳው ውዝግብ ፍርድ ቤት እያሟገተ ነው። ዛሬ ያስቻለው የአዲሰ አባባ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፓርቲውን ጽህፈት ቤት ንብረት በኃይል ለመውሰድ ሞክረው ነበር ተብለው በተከሰሱ አባላት ላይ የተሰጠውን ምስክርነት አዳምጧል። ዘገባውን ለማዳመጥ እዚህ …

የአንድነት ፓርቲ ፖለቲከኞች የፍርድ ቤት ሙግት Read more »

ከሰባት ዓመት በላይ ኢራቅ ከቆዩት የአሜሪካ ተዋጊ ጦር ኃይል አባላት የመጨረሻዎቹ ትናንት ኢራቅን ለቀው ወጥተዋል ። የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የኢራቅ ጦርነት ማብቃቱን ትናንት በይፋ አስታውቋል ። በርካታ ኢራቃውያን የአሜሪካን ጦር ሀገራቸውን ለቆ በመውጣቱ የተቀላቀለ ስሜት ነው ያደረባቸው ። …

የአሜሪካን ጦር ከኢራቅ መውጣት ያሳደረው ስጋት Read more »

ለኢትዮጵያ አማራጭ የመረጃ አግልግሎት ለመስጠት የተቋቋመውና ከኔደርላንድ የሚያሠራጨው ESAT በሚል ምኅጻር የታወቀው የኢትዮጵያ የሳቴላይት ቴሌቭዥን አገልግሎት ሥራውን ከጀመረ 4ኛ ወሩን ቢይዝም በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ፤ ለ 3ኛ ጊዜ ተቋርጧል። ይሁንና ከመጪው ሳምንት ጀምሮ እንደገና በተጠናከተረ መልኩ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ፤ …

ESAT አሁን እንደገና በአዳዲስ መሥመሮች እንደሚያሠራጭ አስታወቀ Read more »

የቀድሞዉ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ለገሰ ቢራቱ እንደሚሉት በምክር ቤት ዉስጥ ሰወስት መቀመጫዎች ብቻ ያለዉ ቅንጅት ከምርጫ ቦርድ የተቀበለዉ አርባ የምክር ቤት መቀመጫዎች ያሉት በማስመል ነዉ የኢትዮጵያ ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ባለፈዉ ግንቦት ለተደረገዉ ምርጫ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወሰደዉ የገንዘብ ድጎማ …

የአየለ ጫሜሶ ቅንጅት የወሰደዉ ገንዘብና ወቀሳዉ Read more »

የዜና አውታሮች ባለፈው ሳምንት ማለቂያ ላይ እንደዘገቡት፤ ዓርብ፣ ከቀትር በኋላ፤ በግብጽና እሥራኤል ድንበር ላይ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ፣ ሰዎችን ካገር -አገር በሚያሻግሩ ቡድኖችና በፈላስያን መካከል ፣ ተካሄደ በተባለ የተኩስ ልውውጥ 4 ኤርትራውያን ተገድለዋል።

20 ከመቶ የኤኮኖሚ ዕድገት ። ለአውሮፓውያን ይህ ህልም ብቻ ነው። አፍሪቃ ውስጥ ግን በተለይ ድፍድፍ ነዳጅ ዘይት በገፍ ትቸበችብ በነበረችው በአንጎላ ይህ ከጥቂት ዓመታት በፊት ህልም ሳይሆን ተጨባጭ ሀቅ እንደነበረ የሚካድ አይደለም ።

ኢትዮዽያ በስዊድን ያለውን ኤምባሲዋን መዝጋቷን ጠቃላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከትላንት በስቲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጪያ ላይ ማስታወቃቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ኤምባሲው ተልዕኮውን ሊወጣ ባለመቻሉ መዘጋቱንና ከዚያ ይልቅ በብራዚል መክፈት እንደሚሻል ገልጸዋል። የሲውዲን መንግስት ይህ የኢትዮዽያ መብት ነው ሲል ምላሽ ሰጥቷል። …

ኢትዮጵያና ስዊድን Read more »

የኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርሰቲያን ኢትዮዽያና አሜሪካ የሚገኙትን ሁለቱን ሲኖዶሶች ለማስታረቅ የተደረገው ሽምግልና ገና ሳይካሄድ ቅድመ ሁኔታ ቀርቦበት ተሰናክሏል።

በሳዉዲ ዐረቢያ በጄዳ ከተማ ካለመጠለያ እና ካለምግብ፡ ወደአገራቸዉ የሚመለሱበትን ዕለት በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ችግር አሁንም መፍትሄ ባላገኘበት ድርጊት ስቃያቸው እየከፋ ሄደ።

የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን በእንግሊዘኛው ምህፃር UNHCR የሶማሊያ ስደተኞች ከሳውዲ አረቢያ በጅምላ በግዳጅ ወደ ሶማሊያ መባረራቸውን ለማስቆም የሚረዳ የመፍትሄ ሀሳብ ለሳውዲ አረቢያ መንግስት ማቅረቡን አስታወቀ ።

ባለፈው ቅዳሜ ረፋድ ላይ አዲስ አበባ ውስጥ ኮልፌ በሚባለው አካባቢ በደረሰው የመኪና አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከዚህ ቀደም ከተገለፀው ከፍ ሊል እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል ።

ትምህርት ለአፍሪቃ እድገት ቁልፍ ሚና አለው። በማዳመጥ መማር የተሰኘዉ የዶቼ ቬለ መረሃ ግብር በመገናኛ ብዙሃን የርቀት ትምህርት በሁሉም የአህጉሪቱ ክፍሎች እውቀትን ለማዳረስ በጥረት ላይ ይገኛል።