Author: Daniel Kibret www.danielkibret.com
ራትን ቁርስ ላይ
የተሰበሰበ ድንች (ካለፈው የቀጠለ)
‹የተሰበሰበ ድንች›
click here for pdf
‹‹ግዴለሽም እንደምንም ብለሽ ንገሪኝ›› አለቻት፡፡
መጀመሪያ ሰው ነኝ
‹ሐተታ ዘርአ ያዕቆብ›
የማያለቅስ ልጅ
![]() |
| ፎቶ – ሐራ ተዋሕዶ |
ሁለተኛው ደግሞ ለሌሎች አካላት ቁጥጥር ስለሚመች ነው፡፡ ጌታችን አስቀድሞ ኃይለኛውን ማሠር እንዳለው መሪውን የያዘ ቤተ ክርስቲያኒቱን አን ልቡ ለመዘወር ይመቸዋል፡፡
‹‹የነ እንትና ታቦት››
የአውስትራልያ ትምህርት በረከቶች ለአፍሪካ፡- ዕድሎችና ተግዳሮቶች(ሪፖርታዥ)
|
ኃይለ ልዑልና ዶ/ር ብርሃነ ከቀድሞው የአውስትራልያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኬቪ ሩድ ጋር
|
የፉት ስክሬይ ማኅበረሰብ የሥነ ጥበብ ማዕከል የቦርድ አባል፣ አነስተኛ ቁጥር ያላቸውን የአውስትራልያ ማኅበረሰቦች የሚያካትተው Ethnic Communities’ Council of Victoria ሊቀ መንበር፣ የአፍሪካ የሐሳብ ማዕከል (African Think Thank) ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ማኅበረሰቡን እያገለገለ ነው፡፡ ለዚህና ለሌሎቹ አገልግሎቶቹ የዊኒስተን ቼርቺል ፌሎው – ሽልማት(2008)፣ የዊልያምሰን ማኅበረሰብ አመራር መርሐ ግብር- ሽልማት(2009)፣ የጋራ ብልጽግና አገሮች የሚኒስትሮች አማካሪ ኮሚቴ ለአፍሪካ – ሽልማት(2012)፣ እጅግ የተዋጣለት የማኅበረሰብ መሪ – ሽልማት(2011)፣ እንዲሁም በብዝሐ ባሕል የተዋጣለት ሥራ ለሠሩ የአውስትራልያ ሰዎች የሚሰጠውን (Meritorious service in the community) ሽልማት ከቀድሞው የቪክቶርያ ገዥ(Premier) በ2004 ተቀብሏል፡፡
በዓለም አቀፍ ትምህርትና ሥልጠና፡ ዕድሎችና ተግዳሮቶች
ዘንድሮ በሜልበርን ከተማ ቪክቶርያ ዩኒቨርሲቲ ኣዳራሽ የተካሄደው የአፍሪካ አውስትራልያ ማኅበር ዋና አጀንዳ በትምህርትና ሥልጠና ላይ ያተኮረ ነበር (Doing Business in Africa: Opportunities in International Education and Training)፡፡
በዚህ ጉባኤ ላይ ከቪክቶሪያ ግዛት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከኩባንያዎችና አፍሪካ ላይ ከሚሠሩ ተቋማት የመጡ ተወካዮች ሐሳቦቻቸውን፣ ሥራዎቻቸውንና ያጋጠማቸውን ነገር አቅርበው ነበር፡፡ በተለይም ባለ ሥልጣናቱ አውስትራልያ ከአፍሪካ ጋር እስከ ዛሬ የነበራት ግንኙነት ማዕድንን የተንተራሰ እንደነበርና ከ65 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሆነ የአውስትራልያ ኢንቨስትመንት በአፍሪካ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ ዓለም አቀፍ የትምህርት ግንኙነት ለአውስትራልያ 4ኛው የገቢ ምንጭ መሆኑንና ከ50 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በየዓመቱ ለሀገሪቱ ሲያስገኝ ከ100 ሺ ሰዎች በላይ ደግሞ በሥሩ ተሠማርተው ገቢ እያገኙበት መሆኑን ነግረውናል፡፡ አውስትራልያ ትምህርት አሰጣጧን በማስተካከል፣ የተሻለ ልምድ ካላቸው ሀገሮች ደረጃዎችን በመውሰድ፣ ለተማሪዎች የሚሻሉ መንገዶችን በመዘርጋት በዓለም ከሚመረጡ የትምህርት ተቋማት ወገን የሆኑ ተቋማትን ለመመሥረት መቻሏን ነግረውናል፡፡ ‹በዓለም ላይ የትምህርት ልዕለ ኃያል ሀገር – super power in Education› ብለዋታል፡፡ የትምህርት ጥራትና ደረጃ አካዳሚያዊ ነጻነትን፣ በባለሞያ የሚመራ የትምህርት ሥርዓትንና ገለልተኛ የሆነ ገምጋሚ አካልን እንደሚፈልግ ተናግረዋል፡፡ እኔም የሀገሬን ከፍተኛ ተቋማት እንዳስብ አድርገውኛል፡፡
በተለይም ከትምህርት ተቋማት የመጡት ባለሞያዎችና ባለሥልጣናት በአንድ ነገር ላይ ተስማምተው ሲናገሩ ነበር፡፡ በከፍተኛ ትምህርት ላይ የበጀት፣ የሰው ኃይልና የአሠራር ድጋፍ በማድረግ የአውስትራልያ መንግሥት በየጊዜው የተሻለ ሥራ ቢሠራም ሁለት ነገሮች ግን ለውጤቱ እጅግ በጣም አስፈላጊ ሆነዋል፡፡ እነዚህ ሁለት ነገሮች ደግሞ የሚገኙት ከተማሪዎች ነው፡፡ እነርሱም ፍላጎትና የተፎካካሪነት ስሜት(Interest and Competitiveness)፡፡ የምዕራቡ ዓለም ተማሪዎች የተሻለ ትምህርትና የትምህርት መሣሪያዎች ቢሟሉላቸውም ፍላጎትና ተፎካካሪነትታቸው ግን የእስያ ተማሪዎችን ያህል መሆን አልቻለም፡፡ በዚህም የተነሣ በአነስተኛ ወጭና ባልተሟሉ ሁኔታዎች ውስጥ የሚማሩት የእስያ ተማሪዎች የተሻለ ፍላጎትና የተሻለ ተፎካካሪነት ስለሚያሳዩ በተሻለ በጀት ከሚማሩት የምዕራቡ ተማሪዎች ይልቅ በውጤትማነት የተሻሉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የተከበሩ ፊል ሀኔውድ የተባሉ የሥነ ትምህርት ባለሞያና የአውስትራልያ ዓለም ዐቀፍ የትምህርት ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ እንዳሉት ለተማሪዎች ውጤታማነት ወሳኞቹ ነገሮች ከውስጥ የሚመነጩት ሁለቱ ኃይሎች – ፍላጎትና የተፎካካሪነት ስሜት ናቸው፡፡
የአፍሪካ ተማሪዎች ለትምህርት ያላቸው ፍላጎትና ተፎካካሪነት የተሻለ በመሆኑ በአውስትራልያ ትምህርት ቤቶች በተመደበላቸው ትምህርት ጊዜ በመጨረስ የአፍሪካ ተማሪዎች ውጤታማ ሆነዋል፡፡ የሀገሬው ተማሪዎች የመጨረስ ዐቅም 70 ከመቶ ሲሆን የአፍሪካ ተማሪዎች ግን 94 በመቶ ነው፡፡
ይህንን ልምድ በመያዝም በስኮላርሺፕ ብቻ ከመገናኘት ይልቅ ከአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆን ለመሥራት እየጣሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እስካሁንም 20 የአውስትራልያ ዩኒቨርሲቲዎች ከ51 የአፍሪካ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ግንኙነት በመመሥረት ይህንን ሥራ ለማስፋፋት እየሠሩ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር በተመለከተ ከቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች ድጋፍ ያለፈ ሪፖርት አልሰማሁም፡፡ በዚህ ረገድ ኬንያና ናይጄርያ የአንበሳውን ድርሻ መያዛቸው ነው የተነገረው፡፡
የአፍሪካ ተማሪዎች የበጀትና ትምህርት አመራር ድጋፍ ከተሰጣቸው የተሻለ ፍላጎትና ተፎካካሪነት አላቸው፡፡ በመሆኑም የአውስትራልያ ዩኒቨርሲቲዎች ከአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት በአውስትራልያ የትምህርት ደረጃና ጥራት የሚሰጡ መርሐ ግብሮችን በአፍሪካ ለመዘርጋት እየተሞከረ ነው፡፡ ይኼ ሁኔታ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች መልካም ዕድል በመሆኑ ዩኒቨርሲቲዎቹ የሚጠየቁትን ዝግጅት ከኤምባሲው በመውሰድ በጋራ ለመሥራት ቢነሡ ሀገራቸውን ለመጥቀም ይችላሉ፡፡ ተማሪዎቻችንን እንዲህ ባለ ዕድልና ዓለም አቀፍ ድጋፍ እንጅ በስብሰባ ብቻ ብቁ ዜጋ ማድረግ አይቻልምና፡፡
ሚሲስ ጃኩሊን ዝዋምቢላ የተባሉ በዚምባብዌ የቀድሞ የአውስትራልያ አምባሳደር እንደገለጡት የአውስትራልያ ዩኒቨርሲቲዎች ገንዘብና የሰው ኃይላቸውን ይዘው፣ በአውስትራልያ ደረጃ ከአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት አራት መሠረታዊ ችግሮች ገጥመዋቸዋል፡፡ የመጀመሪያው ብዙዎቹ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች ሳይሆኑ የማስተማሪያ ዩኒቨርሲቲዎች (lecturing rather than research) መሆናቸው ከዓለም የጥናት ሥራዎች አስተዋጽዖ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች 1% ብቻ እንዲያበረክቱ አድርጓቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አብዛኞቹ የሚያሠለጥኑት ለመንግሥት ሥራ(educating for public sector) እንጂ መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት በሚችሉ መስኮች አይደለም፡፡ ሦስተኛ ሆኖ የተነሣው የአፍሪካ ብዙዎቹ ዩኒቨርሲቲዎች የራሳቸውን ችግር ሊፈታ የሚችል፣ ራስ ተኮርና ራስ ፈጠር የሆነ መንገድና ደረጃ በመከተል፣ ዘላቂና ወጥ የሆነ፣ ብሔራዊ ቀለም ያለው የትምህርት ፖሊሲና ስትራቴጂ ከመቅረጽና በርሱም በቁርጠኛነት ከመመራት ይልቅ አውሮፓ ተኮር(Euro centric) መሆናቸው ነው፡፡ አራተኛው ብዙዎቹ ሀገሮች ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቂ በጀት ለመስጠት ባለመቻላቸው በአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃና በዩኒቨርሲቲዎች መካከል ያለው ልዩነት የሰርተፊኬቱ ደረጃ ብቻ እንዲሆን ማድረጉ ነው፡፡ በአንድ ጥናት ላይ እንደተመለከተው ከአፍሪካ ዓመታዊ ገቢ(GDP)1% ብቻ ለከፍተኛ ትምህርት ይመደባል፡፡
ፕሮፌሰር ዴቪድ ሞሪሰን የተባሉ የሞርዶክ ዩኒቨርሲቲ የጥናት ምክትል ቻንስለር አውስትራልያ በሚከተሉት ጉዳዮች በአፍሪካ ትኩረት እንደሰጠች ገልጠዋል (በአውስትራልያ ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር ለምታስቡ ተማሪዎች ወይም በጋራ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር ለመሥራት ለምትፈልጉ ተቋማት)፡፡ በአርብቶ አድር ልማት፣ በእርሻና ማዕድን፣ ለእናቶችና ሕጻናት ደኅንነት የዐቅም ግንባታ፡፡ እነዚህን ጉዳዮች በተመለከተ ከአውስትራልያ ተቋማት ጋር አብረው ከሚሠሩ ወይም ከሚያጠኑ ጋር ለመቀናጀት መርሐ ግብር አላቸው፡፡ ‹‹ትልቁ ችግር›› አሉ ፕሮፌሰሩ ‹‹የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ምርምር ላይ ትኩረት ስለማይሰጡ የጥናት ባሕላቸው ዝቅተኛ ነው(underdeveloped research culture)፡፡ በዚህም ምክንያት የአውስትራልያ ተቋማት እንዲደረግ የሚፈልጉት ጥናትና የአጥኝው ዐቅም አለመጣጣም ይከሰታል፡፡ እኒህ የጥናት ባለሞያ ደጋግመው እንደገለጡት ‹የአንዲት ሀገር የመፍጠር ዐቅም በሳይንስ መሠረቷ የተጽዕኖ ዐቅም ይወሰናል(the country’s ability to innovate is influenced by the size of its science base)፡፡››
በአሁኑ ጊዜ 4.5 ሚሊዮን ዓለም አቀፍ ተማሪዎች በየሀገሩ ይገኛሉ፡፡ አብዛኞቹ የአፍሪካ ተማሪዎች በፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካና ሳዑዲ ዐረቢያ ነው የሚማሩት፡፡ በአውስትራልያ ከሚማሩ ዓለም ዐቀፍ ተማሪዎች መካከል ቻይናውያን 27.4፣ ሕንዶች 10.4፣ ቬትናማውያን 5.1 በመቶውን ይዘዋል፡፡ በአውስትራልያ ትምህርት ቤቶች ለመማር ከሚያመለክቱት መካከል አፍሪካውያን ከ1 – 15 ከሚገኙ ዋና አመልካች ሀገሮች ውስጥ የሉበትም፡፡ ለዚህ ዋና ምክንያቱ ቪዛ ለማግኘት ያለው ጣጣ፣ በቂ የመኖሪያ ወጭ ሽፋን አለመኖር(10 በመቶዎቹ ብቻ በተማሪዎች መኖሪያ ይኖራሉ)፣ አውስትራልያ እስያ ላይ በማተኮሯ፣ በአፍሪካ የሚገኙ ትምህርት ኤጀንሲዎች ስለ አውስትራልያ ትምህርት ዕድሎች በቂ ግንዛቤ የሌላቸው መሆኑ፣ ቻይና ለአፍሪካ የተሻለ ስኮላርሺፕ በመስጠቷ መሆኑ ተገልጧል፡፡ በአውስትራልያ ለመማር የሚያስቡ ይኼንን ገጸ ድር ቢያዩት ተመክረዋል –
www.studyinaustralia.gov.au
ከ2012 ጀምሮ ከ8000 በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በአውስትራልያ ዩኒቨርሲቲዎች ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ መካከልም 1500ዎቹ የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ሲሆኑ 40ዎቹ የዶክትሬት ዲግሪ እየሠሩ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት በሁሉም የአውስትራልያ የትምህርት ተቋማት 14000 አፍሪካውያን ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው፡፡ የአውስትራልያ መንግሥትም በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት 5000 የማስትሬትና የአጫጭር ኮርሶች ዕድል ለአፍሪካውያን ማዘጋጀቱ ተገልጧል፡፡ ለአጫጭር ኮርሶች ይህንን ድረ ገጽ በማየት መጠቀሙ መልካም ነው –
www.australiaawardsafrica.org
ለቢዝነስ ጉዳዮች ደግሞ ወደዚህ ይዙሩ
www.dfat.gov.au
በጉባኤው ከነበሩት አቅራቢዎች ለአፍሪካውያን ስኮላርሺፕ ትልቁ ተግዳሮት ሆኖ የተነሣው ለትምህርት የሚመጡ ተማሪዎች ወደ ሀገራቸው ያለመመለሳቸው ችግር ነው፡፡ በዚህ ምክንያትም የስኮላርሺፕ ዕድላቸው የተንጠለጠለባቸው ሀገሮች አሉ፡፡ አንዳንድ የጉባኤው ተሳታፊዎች በኮሪደር ወሬ ኢትዮጵያ ከእነዚህ አንዷ መሆኗን ነግረውኛል፡፡
ነፍሱን ይማረውና ጋዳፊ በአንድ የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ላይ ‹የአደጉትን ሀገሮች የአየር መበከል፣ የጦርነትና የፖለቲካ ችግር እንደምንካፈለው ሁሉ የእነርሱን ሀብትና ዕድገትም መካፈል አለብን‹ ብሎ ነበር፡፡ ናይጄርያውያንና ኬንያውያን ከአፍሪካ፤ ሕንድ፣ ቻይናና ቬትናም ከእስያ የአውስትራልያን የትምህርት ስጦታና ዕድል በሚገባ እንደሚጠቀበሙት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የትምህርት ተቋማትና በአውስትራልያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ዳያስጶራ ተጋግዘን ዕድሉን ብንጠቀምበትና ለሀገራችን ሰው ብናፈራበት መልካም ይመስለኛል፡፡ በተለይም በሀገር ውስጥ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችና መካከለኛ ተቋማት ከአውስትራልያ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ለመሥራት የተዘጋጀውን መርሐ ግብር ተሻምቶ በመጠቀም በትንንሹ ዳቦ ከምንራኮት ትልቁን እንጀራ እንቁረስ፡፡ ወደ 310 ሚሊዮን ዶላር ለስኮላርሺፕ መንግሥት መመደቡን አብሥረዋል በጉባኤው ላይ፡፡ መልካም ዕድል፡፡
ሜልበርን፣ አውስትራልያ
‹ቀራንዮ፣ መድኃኔዓለም፣ ካህናቱ›
አርሴማ
|
ዐጽሟ ያረፈበት አርመን የሚገኘው ቤተ ክርስቲያን
|
![]() |
|
በመቃብሯ ላይ የሚገኘው ሥዕል
|
ፍቅር፣ ቁልፍና ድልድይ
![]() |
|
የፓሪሱ የፍቅር ድልድይ
|
| ሳውዝ ባንክ የእግረኞች ማቋረጫ |
ጨረቃና ጨለማ
እምቢታ (የቃቄ ወርድወት)
ሰነቦ
|
ዓባይ በረሐ መግቢያ ላይ
|
|
ይንሸራተታል ተጠንቀቁ
|
|
ሰቀላ ማርያም ደን
|
|
ውረድ- ወደ ሰነቦ
|
|
የመቅደሱ ግንብ
|
|
ወደ ዋሻው በዐለት ፍላጭ ላይ ጉዞ
|
|
የዋሻው ውስጥ መንገድ
|
|
የሌሊት ማኅሌት
|
|
በጨለማው ውስጥ ወደ ጠበሉ ጉዞ
|
|
ካህኑ ወደ ጠበሉ ሲገቡ
|
|
በውኃው ላይ ወደ ጠበሉ ጉዞ
|
|
ተጠማቂው በገመድ ታሥሮ ወደ ጠበሉ ኩሬ ሲገባ
|
|
ተራራውን ከታች ወደ ላይ ሲያዩት
|
|
በተስፋ፣ ከታች ወደ ላይ
|
|
ሸለቆው ከሩቁ
|
|
ተራራው ላይ ደረስን
|
ጳጉሜን – አምስት፣ ስድስት፣ ሰባት
ዝሆን (ክፍል ሦስትና የመጨረሻው)
ዝሆን (ክፍል ሁለት)
ዝሆን
| የዝሆን ሥዕል፣ ወሎ ገነተማርያም ቤተ ክርስቲያን |
|
የዝሆን ሥዕል፣ ወሎ እመኪና ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን
|
| የዝሆን ኩምቢ |
ዝሆን ሚዛናዊ ነው፡፡ ዝሆን በዓለማችን ትልቁ አጥቢ እንስሳ ነው፡፡ ክብደቱ እስከ ስድስት ሺ ኪሎ ግራም ይደርሳል፡፡ ይህንን ያህል ክብደቱን እስከ 3.3 ሜትር በሚደርሰው ቁመቱ ውስጥ ይይዘዋል፡፡ ይህንን ሁሉ ክብደት የያዘው ዝሆን ቅጠል በል መሆኑ የተነሣ የዛፎቹን ቁመት ተከትሎ ቀጭኔ በአንገቷ የምትደርስበት ቦታ ድረስ መድረስ የግድ ይለዋል፡፡ እዚህ ላይ ትልቁ ጥያቄ እንዴት? የሚለው ነው፡፡
| የዝሆን አመራር |
ሕግና ሥርዓት – በሐበሻ አሜሪካ
ንሥር (ክፍል ሁለት)
ንሥርም እንዲህ ትልሃለች፡- በግላዊ ሕይወትህ፣ በንግድህም ሆነ በሌላው ኑሮህ ከሰዎች ጋር መወዳጀት፣ አብሮ መሥራትና መንገድ መጀመር ያለብህ ለዓላማቸው ምን ያህል ጽኑና ቆራጥ፣ ትጉና አይበገሬ መሆናቸውን አረጋግጠህ መሆን አለበት፡፡ ሳታረጋግጥ መግባት ትርፉ ፀፀት ነው፡፡ እንኳን ሌሎችን ራስህንም ለአዲስ ተልዕኮ ከማሠማራትህ በፊት ፈትነው፡፡
ንሥር
እንደገና እንጋባ(የመጨረሻ ደብዳቤ)
ጳውሎስ ኞኞ (1926-1984)
ኡመተ ፈናን ኡመተ ቀሽቲ ዲሬ ዳዋ
እንደገና እንጋባ
ድኻው ምን አረገ
የታጋዩ የልጅ ልጅ
የሁለት ፈረሶች ጥያቄ
‹ትዕግሥት› – የቴሌ ሶፍትዌር
የዓመቱ በጎ ሰው መጽሔት
የ2006 ዓም የበጎ ሰው ሽልማት አሸናፊዎች ተሸለሙ
ያልሰማኸው ነገር
‹‹የዓመቱ በጎ ሰው›› የመጨረሻዎቹ ዕጩዎች
- ሙላቱ አስታጥቄ
- ተስፋየ አበበ
- አባባ ተስፋየ ሳሕሉ
- ይልማ ሀብተየስ
- ታደሰ መስፍን
- ዶ/ር ተዋበች ቢሻው
- ዶ/ር በላይ አበጋዝ
- ወ/ት ሮማን መስፍን
- ሲ/ር ዘቢደር ዘውዴ
- ወ/ሮ አበበች ጎበና
- ቤተልሔም ጥላሁን
- ዶ/ር ኢንጅነር ዳንኤል ቅጣው
- ዶ/ር ወሮታው በዛብህ
- አሶሴሽን ኦፍ ዉሜን ኢን ቢዝነስ
- ካፒቴን ሰሎሞን ግዛው
- አቶ ዓለሙ አጋ
- አቶ ሀብተ ሥላሴ ታፈሰ
- ሼህ አብዱላሂ ሸሪፍ
- ዶ/ር ዘረ ሠናይ ዓለም ሰገድ
- የኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ማኅበር
ሃይማኖታውያን ያልሆኑ የግእዝ ጽሑፎች (ግንቦት 2006 ዓም አኩስም ትግራይ)
- የድንጋይ ላይ ጽሑፎች፡- በድንጋይ ላይ የተጻፉት የግእዝ ሥነ ጽሑፎች በአኩስም አካባቢ የተገኙትንና የነገሥታቱን የጦርነት ታሪኮችንና ሌሎች ዘገባዎችን የያዙትን ጽሑፎች ይመለከታል፡፡ የተገኙት የድንጋይ ላይ ጽሑፎች ከአራተኛው መክዘ(ቅልክ) እስከ 8ኛው መክዘ(ድልክ) የሚደርሱ ናቸው፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ጥንታዊው የሚባለው የድንጋይ ላይ ጽሑፍ በመጣራ ኤርትራ በሐውልቲ የተገኘው(5ኛው መክዘ ቅልክ) ጽሑፍ ነው፡፡
- የብራና ላይ ጽሑፎች፡- ሁለተኛው የግእዝ ሥነ ጽሑፍ የብራና ሥነ ጽሑፎች መልክ ነው፡፡ የብራና ላይ የግእዝ ጽሑፍ ከ6ኛው መክዘ እስከ አሁን ዘመን የቀጠለ ሲሆን በማይክሮፊልም በተነሡት የብራና መጻሕፍት ቁጥር የሄድን እንደሆነ ቁጥራቸው እስከ 12,000 ይደርሳል፡፡ በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ አደጋ ጠፍተው የቀሩትን፣ በየቦታው ተደብቀውም አድራሻቸው ያልታወቁትን ሳይጨምር ማለት ነው፡፡ እስካሁን በተገኘው መረጃ ጥንታዊው የሚባለው የብራና የግእዝ መጽሐፍ በእንዳ አባ ገሪማ የሚገኘው ወንጌል ሲሆን የተጻፈውም በ6ኛው መክዘ ነው፡፡
- የወረቀት ላይ ጽሑፎች፡- ሦስተኛው የግእዝ ሥነ ጽሑፍ መልክ በወረቀት የታተሙ መጻሕፍት ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት በብራና የሚገኙትን የግእዝ መጻሕፍት ተደራሽ ከማድረግ አንጻር የቀረቡ እንጂ አዳዲስ ድርሰቶች አይደሉም፡፡ የግእዝ የታተሙ መጻሕፍት ታሪክ ጉተንበርግ የግእዙን ዳዊት ጀርመን ላይ ካሳተመበት ጊዜ ይጀምራል፡፡ ይህም የአራት መቶ ዓመታት ታሪክ ይኖረዋል፡፡
- ሃይማኖታውያን፣
- በዋናነት ሃይማኖታውያን ያልሆኑ ጉዳዮችን የያዙና
- ደብዳቤዎች
- የግእዝ ቋንቋ በአሁኑ ጊዜ የቤተ ክርስቲያን መገልገያ ቋንቋ በመሆኑ
- አብዛኞቹ የግእዝ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች ሃይማኖታውያን በመሆናቸው እና/ወይም
- ሃይማኖታውያን ስላልሆኑት የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች በብዛት ባለመነገሩና ባለመታተማቸው
- ከሀገር ውጭ
- ከሀገር ውስጥ
- ፊሳሎጎስ፡- ፊሳሎጎስ ከግሪክ ወደ ግእዝ በ6ኛው መክዘ የተተረጎመ መጽሐፍ ነው፡፡ ፊሳሎጎስ በብዙ ቋንቋዎች የታወቀ መጽሐፍ ሲሆን የስሙ መጠሪያ ‹ፊዚዮሎጎስ› ከሚለው የግሪኩ ስም የመጣ ሆኖ በ200 ዓም አካባቢ በእስክንድርያ ውስጥ በግሪክ ቋንቋ የተጻፈ ነው፡፡ መጽሐፉ 48 ምእራፎች ሲኖሩት 42ቱ በእንስሳት፣ 2ቱ በዕጽዋት፣ 4ቱ ደግሞ በማዕድናት ላይ መሠረት ያደረጉ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ምእራፍ አንድ እንስሳ፣ ዕጽ ወይም ማዕድንን በማንሳት፣ ጠባዩንም በመተንተን ከመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ጋር አጣምሮ የሚያቀርብ ነው፡፡
- ፈውስ ሥጋዊ፡- ይህ መጽሐፍ በአብዛኛው የሚታወቀው ፈውስ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ በሚል ነው፡፡ ነገር ግን ሁለቱ መጻሕፍት የተለያዩ ናቸው፡፡ ፈውስ መንፈሳዊ ምናልባት ከ13-16ኛው መክዘ ባለው ጊዜ ወደ ግእዝ የተተረጎመ መንፈሳዊ መጽሐፍ ነው፡፡ ዓላማውም በኃጢአት የቆሰለችን ነፍስ በመንፈሳዊ ሕክምና ማከም ነው፡፡ ፈውስ ሥጋዊ ግን በትክክል እስካሁን ያልተጠና ምናልባት ግን ከ17ኛው መክዘ በፊት የተደረሰ(ከሀገር ውስጥና ከውጭ ምንጮች) መጽሐፍ ይመስለኛል፡፡ በውስጡ ለሥጋዊ ሕመም ፈውስ ሊሰጡ የሚችሉ የተለያዩ የዕጽዋትንና የእንስሳትን ውጤቶች የያዘ ነው፡፡
- መጽሐፈ አዕባን፡- እስካሁን ባለኝ መረጃ መሠረት ስለዚህ መጽሐፍ ጥናት አልተደረገም፡፡ አንድ ኢትዮጵያዊ ብቻ በዚሁ ስም አንዲት አነስተኛ መጽሐፍ አሳትሟል፡ የተጠቀመው ይህንን ምንጭ ይሁን ወይም ሌላ አልተገለጠም፡፡ መጽሐፉ ለልዩ ልዩ ተግባር ሊውሉ የሚችሉ ድንጋዮችን በተመለከተ የተጻፈ የጂኦሎጂ መጽሐፍ ነው፡፡ አልፎ አልፎም ድንጋዮቹ በምን ዓይነት አካባቢ እንደሚገኙ ይናገራል፡፡ በኋላ ዘመን የድንጋይ ትርጉምና ጥቅም ተብሎ የተተረጎመውና በEMML 6815 የምናገኘው ከዚህ የተወሰደ ሳይሆን አይቀርም፡፡
- ዜና እስክንድር፡- ይህ መጽሐፍ በጥንታዊው ዓለም ታሪክ የተጻፈውን የታላቁን የግሪክ ንጉሥ የእስክንድርን ታሪክ በግእዝ የሚያቀርብ ነው፡፡ መጽሐፉ ምንጩ ግሪክ ሲሆን ከግሪክ ወደ ሶርያ፣ ከሶርያ ወደ ዓረብኛ፣ ከዓረብኛ ወደ ግእዝ የተተረጎመ ነው፡፡ የተተረጎመውም በ16ኛው መክዘ ምናልባት በ11ኛው የደብረ ሊባኖስ አበ ምኔት በዕጨጌ ዕንባቆም የመናዊ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለ፡፡ መጽሐፉ ሲተረጎም ርእሱ ‹‹ሑረቱ ለእስክንድር›› የሚል ነበር፡፡
ሀገር አቀፍ የግእዝ ዐውደ ጥናት
|
ከልዩ ልዩ ቦታ የተጋበዙ ምሁራንና ሊቃውንት
|
በዐውደ ጥናቱ ላይ ልዩ ልዩ ጽሑፎች ቀርበው ነበር፡፡
|
ዶ/ር ሥርግው ገላው፣ ፕ/ር ባየ ይማም እና ዶ/ር ኃይሉ ሀብቱ
|
|
መ/ር ደሴ ቀለብ፣ ዶር ታየ አሰፋ እና ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ
|
|
መሪጌታ ልሳነ ወርቅ ገብረ ጊዮርጊስ
|
|
የጋዜጠኞችና የአዘጋጆች ቡድን
|
የበጎ ሰው ሽልማት መርሐ ግብር
‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››
መሟላት
ዴር ሡልጣን፡- ዐሥር ነገሮች (ክፍል አምስትና የመጨረሻው ክፍል)
የ2006 የበጎ ሰው ሽልማት ደረሰ
- የሀገራዊ ዕርቅና ሰላም ዘርፍ
- የበጎ አድራጎት(ሰብአዊነት) ዘርፍ
- የኪነ ጥበብ/ ሥነ ጥበብ ዘርፍ
- ግብርናና ኢንዱስትሪ ዘርፍ
- መንግሥታዊ ኃላፊነትን በብቃት የመወጣት ዘርፍ
- ቅርስ ጥበቃ፣ ባሕልና ቱሪዝም ዘርፍ
- ሳይንስና ቴክኖሎጂ/ ጥናትና ምርምር ዘርፍ
ዴር ሡልጣን፡- ዐሥር ነገሮች(ክፍል አራት)
![]() |
|
የአርመን ሙዝየም ሕንጻ
|
ዴር ሡልጣን፡- ዐሥር ነገሮች(ክፍል ሦስት)
![]() |
|
ከመቶ ዓመታት በፊት ወደ ኢየሩሳሌም የመጡ አባቶች
|
- ከቅዱሳን ቦታዎች በረከት ለማግኘት፣
- ፍጹም የሆነ ምናኔን ለመኖር፣
- ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ዕውቀትን ለመገብየትና
- የኢትዮጵያውያንን ቅዱሳት መካናት ለመጠበቅ፡፡
ዴር ሡልጣን፡- ዐሥር ነገሮች(ክፍል ሁለት)
- ብሔራዊ ኮሚቴ ማቋቋም
- የጋራ የጉዞ ከሚቴ
- የጋራ የመታሰቢያ ቀን
ዴር ሡልጣን፡- ዐሥር ነገሮች
በኢየሩሳሌም ገዳሞቻችንም የሚታየው ይኼው ነው፡፡ ለማንኛውም ነገር ምክንያቶቹ ግብጻውያን ናቸው፡፡ ስለ ራሳችን ድክመት የሚያወራ የለም፡፡ ራሱን የሚወቅስም አልተገኘም፡፡ ብዙ ችግሮቻችን ግን ግብጻውያን ባይኖሩም የሚኖሩ ናቸው፡፡ ከጠባያችን፣ ከአሠራራችንና ከአካሄዳችን የሚመነጩ ናቸው፡፡ የግብጻውያኑ ችግርም መፍትሔ ያላገኘው እኛ ስለያዝነው ይመስለኛል፡፡ ነገሩን ጠበቅ አድርገን በመያዝ ብርቱ ሃይማኖታዊ፣ ዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ጫና ለማሳረፍ የምናደርገው ጥረት አለመኖሩ፡፡ የዴር ሡልጣን ነገር ትዝ የሚለን ለትንሣኤ በዓል ጊዜ መሆኑ፤ ከዚያ በቀር ይህን ጉዳይ ሥራዬ ብሎ የያዘ አንድም ቤተ ክህነታዊ አካል አለመኖሩ፡፡ ግብጾችኮ ጉዳዩን በፓርላማ ደረጃ በብሔራዊ ኮሚቴ ነው የሚከታተሉት፡፡ እኛኮ እንኳን ፓርላማ ቤተ ክህነት የሚያውቀው ኮሚቴ የለም፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም ቢሆን ከኢየሩሳሌም ገዳማት በሚቀርብ ጥያቄ ይወያያል እንጂ የኢየሩሳሌም ገዳማትን ጉዳይ በዝርዝር አጥንቶ፣ የድርጊት መርሐ ግብር ቀርጾ፣ አካል አቋቁሞ፣ ከሚመለከታቸው ጋር ኅብረት መሥርቶ ዘላቂና ተከታታይነት ያለው ሥራ አይሠራም፡፡ አብዛኛው የኢየሩሳሌም ገዳማትን የሚመለከተው አጀንዳም ‹‹አቡነ እገሌ ይነሡ አይነሡ›› በሚለው ላይ የሚያተኩር ነው፡፡



























