ጽዮን ግርማ
ሦስተኛዋን ”እሁድ” - በአራዳ ምድብ ችሎት

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ተጠርጣሪዎቹን እሁድ ለሚሰየም ተረኛ ችሎት መቅጠሩን የተለመደ አድርጎታል። ከቀናት በፊት በሦስቱ ብሎገሮች ላይ በተሰጠው የዐሥራ አራት ቀናት የጊዜ ቀጠሮ መሠረት የቀጠሮው ቀን ዛሬ ነበር። ዛሬ በዚህ ፍርድ ቤት ተገኝቼ የነበረውን ሁኔታ መከታተል ባልችልም ምንጮቼ የነገሩኝን ዝርዝር እንዲህ ጽፌዋለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በውህደት ጉዳይ ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ጋር ሲደረግ የነበረው ውይይት በመጠናቀቁና ሁለቱ ፓርቲዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ስምምነት ላይ በመድረሳቸው ምክንያት የቅድመ ውህደት ፊርማ ስነ-ስርዓት ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ መወሰኑን የሚገልፅ ደብዳቤ ለአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) መላኩን የመኢአድ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነው ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡ […]

የ ምርጫ ዘጠና ሰባት ሕልፈት ሕይወት የ አዲስ አበባን ወጣቶች ከምርጫ ወደ በርጫ በብርሃን ፍጥነት ሲመራቸው ቅንጅትም ከመንፈስነት ወደ ፈስነት የሄደበት መንገድ እንዲሁ ተመሳስይ ነብር። ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ነብር ሆነው የነበሩት የተቃዋሚ ፓርቲ ፖለቲከኞች ከነብርነት ወደ ነበርንነት ፣ ቁልቁል ተንደርድረው ከዝግባነት ወደ ዘጋቢነት የተሸጋገሩበትን እጻዊ ( ምጸታዊ ጡዘት ) መንፈስ እና መንፈሰ ግስጋሴ ሳስበው ይገርመኛል። […]

የማለዳ ወግ … ካርል ሓይሰን ለሰብዕና የተጉ ብጹዕ ነበሩ ! ነፍሳቸውን ይማር ሰብዕናን መሰረት አድርገው በመላ አለም በበጎ የረድኤት እና ምግባረ ሰናይ ድርጅቶችን የመሰረቱ ብጹአን እንብዛም ባልበረከቱባት ምድር አልፎ አልፎ ብቅ እያሉ በሰብአዊ ስራቸው መንፈሳዊ ቅናት ሰሜታችን የሚያጎኑ አልጠፉም። …ግን አይበረክቱም ከቀረው አለም ምልከታ ትናንትም ሆነ ዛሬ በእኛ ሃገር ለእኛ ስለሆነውና የሚሆነውን አድርገው ስላለፉት የእኔ […]

የለውጥ አስፈላጊነት ላይና ወያኔ መራሹ መንግስት ይበቃው ዘንድ ባብዛኛው ዜጋ ከተቻለ የሚለው እንዳለ ብዥታ የለም። ይህ ፍላጎት የብዙ ስረአቱ ውስጥ ያሉ ዜጎችም ጭምር መሆኑን የተለያዩ መረጃዎችን ጨምቆ ግንዛቤ መውሰድ ይቻላል። በርግጥ የለውጡ አስፈላጊነት ላይ የሚስማሙና አይቀሬነቱን የሚያውቁ ነገር ግን ለውጡ የተረጋጋና ችግሮች ያልበዙበት እንዲሆን ይረዳል ብለው አገዛዙ ድርሻ በሚያደርግበት እንዲከወን የሚመኙ አሉ። ፈራ ተባ እያሉ […]

ብዙ የውጭ ሃገር ሰዎች ሃገራችንን ይወዳሉ። ከነዚህ ውስጥ አንዱ የኦስትርያ ተወላጅ የሆነው ካርልሃይንዝ ቦይም(Karlheinz Böhm ) ነበር። ነገር ግን ካርልሃይንዝ የዓለም ዜጋ(Weltbürger) ነኝ ብሎ ነበር የሚያምነው። ቢሆንም ካርልሃይንዝ 2003 የኢትዮጵያ የክብር ዜግነት ተቀብሏል። ይህንን ታላቅ ሰው ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁት ኢሊባቡር ውስጥ ጉመሮ ሻይ ተክል መጥቶ በነበረበት ወቅት ነው። በዚያ ወቅት የተነገረን የፊልም ተዋንያን መሆኑን ብቻ […]

·         ጳጳሳት የፓትርያርኩን የማኅበረ ቅዱሳን ደንብ ማሻሻያ ቅድመ ኹኔታ አልተቀበሉትም::

·         ‹‹ቅድመ ኹኔታው የማኅበሩን አገልግሎት የሚያቀጭጭና በሒደትም የሚያስቆም ነው›› /ታዛቢዎች/

(አዲስ አድማስ ጋዜጣ):- የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅን እንደ አንድ አጀንዳ የያዘው የዘንድሮው የሲኖዶሱ የርክበ ካህናት ጉባኤ ከረቂቁ ጋር በተያያዘ በፓትርያርኩና በሊቃነ ጳጳሳቱ መካከል በተፈጠረ ፍጥጫ መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡ የፍጥጫው መንሥኤ፣ በቅዱስ ሲኖዶሱ የተሠየመው የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደርያ ደንብ አጥኚ ኮሚቴ ያዘጋጀው የማሻሻያ ረቂቅ በዝርዝር ከመታየቱ አስቀድሞ ፓትርያርኩ ለውይይቱ እንደ ቅድመ ኹኔታ ያቀረቧቸው ነጥቦች በአብዛኛው የጉባኤው አባላት የገጠመው ተቃውሞ እንደኾነ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

የቅ/ሲኖዶሱን ስብሰባ በርእሰ ጉባኤነት የሚመሩት ፓትርያርኩ፤ በአጀንዳው ላይ የሚካሔደውን ውይይት ቀጣይነት ይወስናል በሚል ካቀረቧቸው ቅድመ ኹኔታዎች ውስጥ÷ ለአጥኚ ኮሚቴው መመሪያ የሰጡባቸው ‹‹ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችና ግዴታዎች›› አንድም ሳይቀነሱ በደንቡ እንዲካተቱና ረቂቁ ሕገ ቤተ ክርስቲያኑ ከጸደቀ በኋላ እንዲታይ የሚሉ እንደሚገኙበት ተመልክቷል፡፡
ፓትርያርኩ በቅድመ ኹኔታ አስቀምጠዋቸዋል በተባሉት ነጥቦች ስምምነት ላይ ከተደረሰ ስብሰባው ሊቀጥል እንደሚችል በመጥቀስ፣ ኃይለ ቃልም ተማኅፅኖም በተቀላቀለበት አኳኋን መጠየቃቸው ተዘግቧል፡፡
ይኹንና የሚበዙት ሊቃነ ጳጳሳት በቀጥታ እንደተቃወሟቸው፣ የተቀሩትም ድጋፍ ከመስጠት እንደተቆጠቡ ታውቋል፡፡ ፍጥጫው ቀጥሎ አቡነ ማትያስ ‹‹አቋሜ ይኽው ነው፤›› በሚል አጀንዳውን መዝጋታቸውን ሲያስታውቁም፣ ‹‹የማኅበረ ቅዱሳን ጉዳይ እንዲህ ተብሎ የሚተው አይደለም፤›› በሚል ከኹሉም ሊቃነ ጳጳሳት ጠንካራ ተቃውሞ እንደገጠማቸው ምንጮች ይገልፃሉ፡፡
የቅ/ሲኖዶሱ መደበኛ ስብሰባ የሚካሔደው ምልዓተ ጉባኤው ከጅምሩ ተስማምቶ ባጸደቃቸው የመነጋገርያ አጀንዳዎች መሠረት እንደኾነ በሊቃነ ጳጳሳቱ ተቃውሞ ተጠቅሷል፡፡
የማኅበሩ የመተዳደርያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ እንዲቀርብ ከታዘዘበት ከጥቅምት2005 .. ጀምሮ እየተንከባለለ ለኹለት ዓመታት መዘግየቱን ሊቃነ ጳጳሳቱ አስታውሰው፣ የተጓተተው አጀንዳ ‹‹የማኅበሩን አገልግሎት ያቀጭጫሉ፣ በሒደትም ያስቆማሉ›› በሚል በተተቹት የፓትርያርኩ ቅድመ ኹኔታዎች ሊዘጋ እንደማይችልና ተጨማሪ ጊዜ ሳይወስድ /ሲኖዶሱ ሊወያይበት እንደሚገባ በአጽንዖት በመናገራቸው፣ ጉዳዩ ሳይቋጭ ለቀጣዩ ቀን በይደር ተላልፏል፡፡
አጀንዳው ሰኞ፣ ግንቦት 18 ቀን2006 .. ጥዋት መታየት ሲጀምር፣ አጥኚ ኮሚቴው 37 አንቀጾችና 34 ገጾች አሻሽሎ ያዘጋጀው የማኅበሩ መተዳደርያ ደንብና የኮሚቴው ቃለ ጉባኤ በንባብ መሰማቱም ታውቋል፡፡ ፓትርያርኩ ‹‹ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችና ግዴታዎች›› በሚል ራሱን በቻለ ርእስ በደንቡ እንዲካተት ለአጥኚ ኮሚቴው ጥብቅ መመሪያ የሰጡበት ባለ24 አንቀጽ ሰነድም አብሮ እንዲነበብላቸው መጠየቃቸው የመጀመሪያው ቀን የፍጥጫ መነሻ እንደነበር ታውቋል፡፡
24 አንቀጾችና በአምስት ገጾች የተዘረዘሩት የፓትርያርኩ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችና ግዴታዎች÷ በአባላቱ በጎ ፈቃድ ተቋቁሞ ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ የሚገኘውን ማኅበር፤ ከሕገ ተፈጥሮው ውጭ የሚያደርግ፣ በቅ/ሲኖዶሱ ፈቃድ ከሚመራበት ደንብ በተፃራሪ ተቋማዊ ህልውናውን፣ የአመራር ምርጫውን፣ የአባላት አያያዙንና የሥራ ቦታውን ለውጭ ተጽዕኖ አሳልፎ የሚሰጥና አጣብቂኝ ውስጥ የሚያስገባ፣ በአርኣያነት የሚጠቀሰውን የፋይናንስ አሠራሩን ወደ ኋላ የሚጎትት መኾኑን እንደተረዱ ያብራሩ አንድ የቅ/ሲኖዶሱ አባል፣ ‹‹ቀጣዩ ቀንም የከበደ ነገር ይዞ እንደሚመጣ ግልጽ ነበር፤›› ይላሉ፡፡
በይደር የተያዘው አጀንዳ በቀጣዩ ቀን ማክሰኞ ጥዋት ተጀምሮ ለግማሽ ቀን የቀጠለ ቢኾንም ፓትርያርኩና ሊቃነ ጳጳሳቱ የመተዳደርያ ደንብ ማሻሻያውን በዝርዝር ለመመልከት የሚያስችል ስምምነት ላይ ለመድረስ እንዳልቻሉ ታውቋል፡፡
‹‹ፓትርያርኩ በቅድመ ኹኔታ ያስቀመጧቸውን ነጥቦችና በአጀንዳው ቀጣይነት ላይ የያዙትን አቋም አልቀየሩም፤ ሊቃነ ጳጳሳቱም ባጸደቅነው አጀንዳ መሠረት ቅድሚያ ሰጥተን መነጋገር ያለብን የሠየምነው አጥኚ ኮሚቴ አዘጋጅቶ ባቀረበው ረቂቅ ላይ ነው፤ መካተት ያለበት ነገር ካለም ማኅበሩን በሚያሠራ መልኩ እያገናዘብን በሒደት እናየዋለን እንጂ አጀንዳው በቅድመ ኹኔታ መታሰር የለበትም በሚል ለማስረዳት ጣሩ፤ በመጨረሻም ፓትርያርኩእንግዲያውስ ስብሰባውን ለመምራት አልችልምበማለታቸው የስብሰባው መቋጫ ኾኗል፤›› ይላሉሒደቱን ለአዲስ አድማስ የገለጹ የስብሰባው ምንጮች፡፡
የማኅበሩ ደንብ በመጀመሪያ ረድፍ ከሰፈሩት የቅ/ሲኖዶሱ መነጋገርያ ነጥቦች አንዱ እንደነበር ያስተዋሉ ሌሎች የስብሰባው ተከታታዮች በበኩላቸው፤ አጀንዳው ከቅደም ተከተሉ ወጥቶ እየተገፋ በመጨረሻ መነሣቱ በፓትርያርኩና በሊቃነ ጳጳሳቱ መካከል ይህ ዓይነቱ አለመግባባት ሊነሣ እንደሚችል ጠቋሚ ነበር ብለዋል፡፡ 
ተከታታዮቹ አክለውም፣ ፓትርያርኩ ስብሰባውን ለመምራት ፈቃደኛ ባይኾኑም በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ በተደነገገው የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት መሠረት፣ ምልዓተ ጉባኤው በማኅበሩ መተዳደርያ ደንብ ማሻሻያዎች ላይ የጀመረውን ውይይት ቀጥሎ ውሳኔ ለማሳለፍ የሚችልባቸው አግባቦች እንደነበሩ ገልጸው፣ /ሲኖዶሱ በግለጫው የመጨረሻው አጀንዳው ባደረገው የማኅበሩ ደንብ ላይውይይት ተደርጎበታልከማለት በስተቀር ስብሰባውን የቋጨበት አኳኋን ያልተለመደና አደናጋሪ ነው ብለዋል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን የዘመኑን ኦርቶዶክሳዊ ትውልድ አደራጅቶ ማንነቱን የሚያውቅበትንና በግብረ ገብ የሚታነፅበትን ትምህርተ ሃይማኖት ከማስተማር ባሻገር፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ተቋማት አገልግሎታቸውን በብቃት የሚወጡበትን ኹለገብ ሞያዊ ድጋፍ የመስጠት ሓላፊነት እንዳለበት በደንብ አጥኚ ኮሚቴው ማሻሻያ ረቂቅ ላይ መስፈሩ ታውቋል፡፡
ይኹንና ‹‹ጥበቃና ጥንቃቄ›› በሚል ፓትርያርኩ እንደ መመሪያ ያቀረቧቸው ድንጋጌዎችና ግዴታዎች እንዲሁም ከልዩ /ቤታቸው ማኅበሩን አስመልክቶ በየጊዜው የሚወጡ መመሪያዎች የማኅበሩን አገልግሎት የማቀጨጭ፣ በሒደትም አዳክሞ የማስቆም ውጤት ሊኖራቸው እንደሚችል ታዛቢዎች ያስረዳሉ፡፡
የማኅበሩ መተዳደርያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ፣ /ሲኖዶሱ የማኅበሩ ደንብ እንዲሻሻል ግንቦት 14 ቀን2004 .. ባካሔደው ስብሰባ÷ ማኅበሩ ከጊዜው ጋር የሚሔድ፣ አገልግሎቱና አደረጃጀቱ የደረሰበትን ስፋትና ዕድገት የሚመጥን፣ ለቤተ ክርስቲያን ኹለንተናዊ ልማት የሚጠቅም ድርጅታዊ መዋቅር እንደሚያስፈልገው ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት አምስት ሊቃነ ጳጳሳት፣ ገለልተኛ የሕግ ባለሞያዎችና የማኅበሩ አባላት በታከሉበት አጥኚ ኮሚቴ የጋራ ጥናት የተዘጋጀ መኾኑ ተመልክቷል፡፡
በግንቦት ወር1984 .. በበጎ ፈቃድ በተሰበሰቡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የተመሠረተው ማኅበሩ፤ እየተመራ ያለው /ሲኖዶስ 1994 .. ለሦስተኛ ጊዜ አሻሽሎ በሰጠው መተዳደርያ ደንብ ሲኾን አሁን የተሻሻለው ረቂቅ ተመርምሮ ባለመጽደቁ በነባሩ ደንብ እየተመራ ለመቀጠል እንደሚገደድ ተመልክቷል፡፡
Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የተመድ የስደተኞች ጉዳይ ተመልካች መስሪያ ቤት በሳምንቱ መጀመሪያ እንዳስታወቀው፣ በዚህ በተያዘው የግንቦት ወር ብቻ ከ66,000 የሚበልጡ ደቡብ ሱዳናውያን ከመንደሮቻቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፤ ከነዚህ መካከል 22,000 ወደ ጎረቤት ኢትዮጵያ ተሰደዋል።

ጳጳሳት የፓትርያርኩን የማኅበረ ቅዱሳን ደንብ ማሻሻያ ቅድመ ኹኔታ አልተቀበሉትም ‹‹ቅድመ ኹኔታው የማኅበሩን አገልግሎት የሚያቀጭጭ በሒደትም የሚያስቆም ነው፡፡›› /ታዛቢዎች/ ማኅበሩ የመተዳደርያ ደንቡ ማሻሻያ ረቂቅ እስኪጸድቅ በነባሩ ለመመራት ይገደዳል (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፫ ቁጥር ፯፻፶፤ ቅዳሜ ግንቦት ፳፫ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን መተዳደርያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅን እንደ አንድ አጀንዳ የያዘው የዘንድሮው …

በልጅግዓሊፍራንክፈርት

ብዙ የውጭ ሃገር ሰዎች ሃገራችንን ይወዳሉ። ከነዚህ ውስጥ አንዱ የኦስትርያ ተወላጅ የሆነው ካርልሃይንዝ ቦይም(Karlheinz Böhm ) ነበር። ነገር ግን ካርልሃይንዝ የዓለም ዜጋ(Weltbürger) ነኝ ብሎ ነበር የሚያምነው። ቢሆንም ካርልሃይንዝ 2003 የኢትዮጵያ የክብር ዜግነት ተቀብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት የቀድሞ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር እና ምክትል ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ ሌሎች ተከሣሾች ያቀረቧቸውን የክሥ መቃወሚያዎች በአብዛኛው ውድቅ አድርጓል፡፡

በፍርድ ቤቱ ባዘዘው መሠረት አቃቢ ሕግ የሚያሻሽላቸውን ክሦች የሚያቀርብበትን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ለዝርዝሩ የፍርድ ቤቱን ውሎ የተከታተለውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በወጣትና በጎልማሳነታቸዉ ዘመን በተጫዎቷቸዉ ፊልሞች ኦስትሪያና ጀርመን ዉስጥ ከፍተኛ አድናቆትና ያተረፉት በኧም ኢትዮጵያ ዉስጥ ችግረኞችን የሚረዳዉን ሜንሽን ፉር ሜንሽን የተሠኘዉን ግብረ-ሠናይ ድርጅት የመሠረቱና ለረጅም ጊዜ የመሩ በጎ አድራጊም ነበሩ

የናጄሪያዉ ቦኮ ሐራም፤ የማሊ ነዉጠኞች፤ በአካባቢዉ የሚንቀሳቀሱ የባሕር ወንበዴዎችንም ሆነ ሌሎች «ሠላም አዋኪ» ያሏቸዉ ሐይላትን ጥቃት ለመቋቋም የማሕበረሰቡ አባላት ብቻቸዉን አይችሉትም

በፈረንሣይዋ ጥንታዊት ከተማ ካን ውስጥ ዘንድሮ በተከናወነው ዓመታዊ የካን ፊልም ፌስቲቫል ለመታደም በፊልም ሙያ የተሰማሩ አምስት ኢትዮጵያውያን ወደ ስፍራው አቅንተው ነበር፤ አራት ሴቶች እና አንድ ወንድ።

በወጣትና በጎልማሳነታቸዉ ዘመን በተጫዎቷቸዉ ፊልሞች ኦስትሪያና ጀርመን ዉስጥ ከፍተኛ አድናቆትና ያተረፉት በኧም ኢትዮጵያ ዉስጥ ችግረኞችን የሚረዳዉን ሜንሽን ፉር ሜንሽን የተሠኘዉን ግብረ-ሠናይ ድርጅት የመሠረቱና ለረጅም ጊዜ የመሩ በጎ አድራጊም ነበሩ

አስ መሐመድ ከግመልና ፍየል ጠባቂነት እራሳቸዉን ለዉጠዉ ዶቢ በተባለ በረሐማ አካባቢ ጨዉ በማልማት ከፍተኛ ሐብት ለማፍራት የበቁ፤ ለበርካታ ኢትዮጵያዉያን የሥራ ዕድል የፈጠሩና ችግረኞችን የሚረዱ ባለሐብት ናቸዉ

የ2006 ዓም ‹‹የዓመቱ በጎ ሰው›› ሽልማት በሰባት ዘርፎች የመጨረሻዎቹ ዕጩዎች ታውቀዋል፡፡ በልዩ ልዩ ዘርፎች ዕውቀትና ተሞክሮ ያላቸው፣ በሞያው ለረዥም ዘመን ያገለገሉ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ ደራስያን፣ የዜማ ሰዎች፣ ሳይንቲስቶች፣ የባሕል ባለሞያዎች፣ የሚገኙበት 21 ዳኞች የመጨረሻዎቹን ሰባት ተሸላሚዎች ለመለየት ድምፅ እየሰጡ ነው፡፡ ዳኞቹ እርስ በርሳቸው የማይተዋወቁ ሲሆን በዘርፋቸው የራሳቸውን ድምፅ ብቻ ይሰጣሉ፡፡ የመጨረሻዎቹ ዕጩዎች የሚታወቁት በሚቀጥለው ሳምንት ውስጥ ነው፡፡
የሽልማቱ ዲዛይን የታዋቂው ሰዓሊ የእሸቱ ጥሩነህ ነው፡፡ ‹‹ጀ›› ፊደል ኢትዮጵያዊ ፊደል በመሆኑ ኢትዮጵያዊነትን የሚወክል ሲሆን ‹በ› ና ‹ሰ› የሚሉ ፊደላት ተቀጣጥለውበታል፡፡ ይህም የበጎ ሰው ሽልማትን የሚገልጥ ነው፡፡ ከላይ ደግሞ የ‹ሽ› ምልክት አለው፡፡ ይህም ሽልማትነቱን ያሳያል፡፡ ከላይ ያለው የፊደሉ ቅጥያ የቁልፍ መክፈቻ ምልክት ያለው ይኼም የተሸላሚዎቹን ቁልፍ ማኅበረሰባዊ ሚና ያመለክታል፡፡ ከፊደሉ ሥር የሚገኘው ደረጃ ደግሞ ተሸላሚዎቹ ደረጃ በደረጃ የደረሱበትን የሰብእና  ልዕልና ያሳያል፡፡

ዕጩዎች በየዘርፉ

ኪነጥበብ ዘርፍ

  1. ሙላቱ አስታጥቄ

  2. ተስፋየ አበበ

  3. አባባ ተስፋየ ሳሕሉ

  4. ይልማ ሀብተየስ

  5. ታደሰ መስፍን

 ማኅበራዊ አገልግሎት
 1.         ዶ/ር አበበ በጂጋ
2.       ዶ/ር ሚናስ ኅሩይ

3.       ቄስ አሰፋ ሰጠኝ(ትግራይ)

4.       ብጹዕ አቡነ ዮናስ(አፋር)

5.       ደበበ ኃይለ ገብርኤል

ርዳታና ሰብአዊ ሥራ

  1. ዶ/ር ተዋበች ቢሻው

  2. ዶ/ር በላይ አበጋዝ

  3. ወ/ት ሮማን መስፍን

  4. ሲ/ር ዘቢደር ዘውዴ

  5. ወ/ሮ አበበች ጎበና

ግብርና፣ ኢንዱስትሪና ኢንተርፕርነርሺፕ

  1. ቤተልሔም ጥላሁን

  2. ዶ/ር ኢንጅነር ዳንኤል ቅጣው

  3. ዶ/ር ወሮታው በዛብህ

  4. አሶሴሽን ኦፍ ዉሜን ኢን ቢዝነስ

  5. ካፒቴን ሰሎሞን ግዛው

መንግሥታዊ ኃላፊነትን መወጣት

1.         አምባሳደር ቆንጅት ሥነ ጊዮርጊስ

2.       ኢንጅነር ስመኘው በቀለ

3.       አቶ በድሉ አሰፋ

4.       አቶ ይርጋ ታደሰ

5.       አቶ አድማሱ ታደሰ

ቅርስ፣ ባሕልና ቱሪዝም

  1. አቶ ዓለሙ አጋ

  2. አቶ ሀብተ ሥላሴ ታፈሰ

  3. ሼህ አብዱላሂ ሸሪፍ

  4. ዶ/ር ዘረ ሠናይ ዓለም ሰገድ

  5. የኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ማኅበር

ጥናትና ምርምር

1.         አምባሳደር ዘውዴ ረታ

2.       ፕ/ር አሥራት ኃይሉ

3.       ፕ/ር ዓለም ፀሐይ መኮነን

                                            መርሐ ግብሩን ዳሽን ቢራ በዋናነት ስፖንሰር አድርጎታል

ኢሊሊ ሆቴል አዳራሹን በመስጠትና ለሌሎችም ተግባራት በመተባበር፣ ሸገር ሬዲዮና ኢቢኤስ ቴሌቭዥን የሚዲያ አጋር በመሆን፣ ጋዜጦችና መጽሔቶች ማስታወቂያዎችንና መረጃዎችን በነጻ በማውጣት እየተባበሩ ይገኛሉ፡፡

ከኢያሱ ዓለማየሁ

ነገርን ነገር ያመጣዋል እንዲሉ በቅርቡ አንዲት የተበሳጨች ኢትዮጵያዊ- የኢሕአፓ ታሪክ እያሉ መጽሃፍ ጻፍን በሚሉ ዋሾዎች በመናደድ–በስም ጠቅሳኝ የድርጅቱን ታሪክ ባለመጻፌ ወቅሳኝና ውቀሱት ስትል መልዕክትና ምሬት ፈረንጆቹ ፌስ ቡክ በሚሉት አማካይነት አሰምታለች። ወጣት ናት በሚል ግምት አንቺ ብያለሁና ከተሳሳትኩ ይቅርታ። ብስጭቷ ቢገባኝም ታሪክ መጻፍን በተመለከተ የተንደረደረችበት ግምትና ሌሎችም የሚያሰሙት ትችት በመሰረቱ የተሳሳተ ነው። ላብራራ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
——–
ቃር ቃር የሚለውን የሰሞኑ የጭንቀት ሰቀቀን በምንፈልገው መጠን  እንድንጫወት ባይፈቅድልንም በተገኘችው አጋጣሚ ሩሓችን “ኢስቲራሓ” እንድታደርግ ልንፈቅድላት ይገባል፡፡ በዛሬ ውሎአችን የሚያናፍሰን ደግሞ አንጋፋው ሱዳናዊ ድምጻዊ ሰይድ ኸሊፋ ነው፡፡ ጉዞ ወደ ቢላድ- አስ-ሱዳን! ጉዞ ወደ ኻርቱም! ጉዞ ወደ ኡምዱርማን! ጉዞ ወደ ከሰላ፣ ጉዞ ወደ ዋዲ ሀልፋ፣ ጉዞ ወደ ገዳሪፍ፣ ጉዞ አል-ኡቤይድ! ጉዞ ወደ ኮርዶፋን! ዳይ!!
———
ከየትኛው እንጀምር እንግዲህ! ሰውዬው በበርካቶቻችን አዕምሮ ውስጥ የገዘፈ ምስል ጥሎብን ያለፈ በመሆኑ “ከሀ እስከ ፐ” እያሉ ስለርሱ ማውራቱ ያስቸግራል፡፡ ለማንኛውም በካይሮ ከተፈጠረ አንድ ክስተት ብንጀምር ጥሩ ይመስለኛል፡፡
ዘመኑ ራቅ ብሏል፡፡ በ1940ዎቹ አጋማሽ ነው፡፡ እውቁ የካይሮ ዩኒቨርሲቲ ለዓለም አቀፍ ተማሪዎች በሰጠው የስኮላርሺፕ እድል በመጠቀም በርካታ ሱዳናዊያን በዩኒቨርሲቲው ይማሩ ነበር፡፡ ከነዚያ ወጣቶች መካከል አንዱ በሙዘቃ ትምህርት ቤት የተመደበ ጠይም ዘለግ ያለ ኮበሌ ነው፡፡ ያ ወጣት በቤተሰቡ ወደ ግብጽ የተላከው ህግ አጥንቶ ጥሩ ዳኛ እንዲሆን ነበር፡፡ እርሱ ግን በራሱ ፍላጎት ምርጫውን ወደ ሙዚቃ አዞረ፡፡ በመሆኑም በእውቁ የዐረብ ሙዚቃ አካዳሚ ሊማር ተመዘገበ፡፡ ወጣቱ ሱዳናዊ ሙዚቃን በሀገር ቤት ያንጎራጉር ነበር፡፡ በትምህርት ቆይታውም በሀርሞኒካ እየተጫወተ ጓደኞቹን ያዝናናል፡፡
   አንድ ቀን ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎቹ ባዘጋጀው ታላቅ የሙዚቃ ድግስ ላይ እንዲዘፍን የተጋበዘው ፈሪድ አል-አጥራሽ የተባለው የዘመኑ ታዋቂ ግብጻዊ ዘፋኝ በሰዓቱ ይመጣል ተብሎ ሲጠበቅ የውሃ ሽታ ሆኖ ይቀራል፡፡ አዳራሹን ከዳር እስከ ዳር ያጨናነቁት ተማሪዎች በትዕግስት ጠበቁ፡፡ ነገር ግን ፈሪድ አል-አጥራሽን የበላ ጅብ አልጮኽ አለ፡፡ በመጨረሻም በአዳራሹ የነበረው ታዳሚ በጩኸትና በፉጨት ንዴቱን መግለጽ ጀመረ፡፡ ታላቁን ዘፋኝ ሲጠባበቅ የነበረው መድረክም በንዴተኛ ተማሪዎች ረብሻ ትርምስምሱ ወጣ፡፡
  
   የዩኒቨርሲቲው መምህራንና ሰራተኞች የተማሪዎቹን ቁጣ ለማብረድ አልቻሉም፡፡ ይሁንና ከሱዳናዊው ወጣት ተማሪ ጋር ይቀራረብ የነበረው አንድ አስተማሪ ወጣቱን እየገፋ ወደ መድረኩ አስገባውና “ዝፈን” አለው፡፡ ወጣቱ ሙዚቃን ለራሱና ለጓደኞቹ መደሰቻ ያህል ነበር የሚጫወተው፡፡ ህዝብ በተሰበሰበት አዳራሽ ላይ ቆሙ መዝፈኑን ቢመኘውም በዚያ ዕድሜው በባዕድ ሀገርና በባዕድ ታዳሚ ፊት ምኞቴን አደርገዋለሁ የሚል ሀሳብ አልነበረውም፡፡ እስከዚያን ጊዜ ድረስ በህዝብ ፊት መዝፈንን አልተለማመደውም፡፡ ስለዚህ የአስተማሪው ግብዣ በፍርሃት ማጥ ውስጥ ወረወረው፡፡
ይሁንና ወጣቱ ግብዣውን “እምቢ” ብሎ ከመድረኩ ለመውረድ አልሞከረም፡፡ እንደዚያ ቢያደርግ በፈሪድ አል-አጥራሽ መቅረት የተቃጠሉት ተማሪዎች ቁጭታቸውን በርሱ ላይ የሚወጡ መሰለው፡፡ ከተማሪዎቹ ቁጣ ለመዳን ሲልም እንደ አቅሙ ዘፍኖ ከመድረኩ ለመውረድ ወሰነ፡፡ በመሆኑም በፍርሃት እየራደና እየተርበተበተ ማይክራፎኑን ጨበጠ፡፡ የአዳራሹ ጸጥታ “ረጭ” ሲልም በቀጭን ድምጽ “አል-ማምቦ ሱዳኒ” (የሱዳን ጭፈራ) እያለ ዘፋፈነ፡፡ በፈሪድ አል-አጥራሽ መጥፋት የበገኑት ተማሪዎች ድንገት በመድረኩ ላይ በተከሰተው ሱዳናዊ ወጣት የድምጽ ቅላጼ ተማረኩ፡፡ ወጣቱ ዘፈኑን ሲጨርስ በከፍተኛ የአድናቆት ጭብጨባ አዳራሹን ቀወጡት፡፡ ዘፈኑንም ደግሞ እንዲዘፍንላቸው ጠየቁት፡፡
ሱዳናዊው ወጣት የስድብ ናዳ እንጂ የአድናቆት ጭብጨባ አልጠበቀም ነበር፡፡ የተማሪዎቹ ምላሽ የአድናቆት ጭበጨባ ሲሆንበት ግን መንፈሱ መለስ አለለት፡፡ በፍርሃት መንቀጥቀጡንም አስወገደ፡፡ እናም ዘና በማለት “አል-ማምቦ ሱዳኒን” እየደጋገመ ዘፈነ፡፡ የአዳራሹ ታዳሚ ከፊት በበለጠ ጭበጭባና አድናቆት አሞገሰው፡፡
የሱዳናዊው ወጣት ገድል በዚያ መድረክ ብቻ አልተገደበም፡፡ ስለድምጹ ማማርና ስለ ቅላጼው የሰማው ሁሉ በድግስና በሙዚቃ ኮንሰርት እንዲዘፍንለት ይጋብዘው ጀመር፡፡ በዘመኑ በካይሮ የሚኖሩት ከመቶ ሺህ በላይ የሚሆኑ ሱዳናዊያንም ወጣቱን የሀገር አለኝታና መታወቂያ አድርገው ወሰዱት፡፡ በየአጋጣሚው በሚያዘጋጇቸው የሙዚቃ ድግሶችም ወጣቱን ቁጥር አንድ ምርጫ በማድረግ አስዘፈኑት፡፡
ያ ወጣት የሙዚቃ ትምህርቱን በሚገባ ካጠናቀቀ በኋላ በ1946 ገደማ ተመረቀ፡፡ በታሪክ ሙዚቃን በአካዳሚ ደረጃ ያጠና የመጀመሪያው ሱዳናዊ ሆኖ ተመዘገበ፡፡ ከምርቃቱ በኋላ ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡
———
ይህ ነው እንግዲህ የሰይድ ኸሊፋ የዘፈን ጥንስስ! በዚህ መንገድ ነው እንግዲህ ዝነኛው ሱዳናዊ የጥበብ ጉዞውን የጀመረው፡፡ ይሁን እንጂ ሰይድ ኸሊፋ በመነሻው ላይ በካይሮ የተቀዳጀውን ዝና በሀገሪቱ ለመድገም አልቻለም፡፡ እንዲያውም መጀመሪያ ላይ የሱዳን ህዝብ “ዘፈን ሳያውቅ እዘፍናለሁ ብሎ የተነሳ መደዴ” የሚል የጥላቻ ቅጽል ለጥፎለት ነበር፡፡ ይህም የተፈጠረበት ምክንያት ሰይድ ኸሊፋ ይዞት የመጣው አዲስ የአዘፋፈን ዘውግ እና የግብጽና የኑቢያ ሙዚቃዎች ውህድ የሆነው የዘፈኖቹ ቅኝት ለሱዳናዊያን ጆሮ እንግዳ በመሆኑ ነው፡፡ ሱዳናዊያን በወቅቱ የለመዱት የአንጋፋዎቹን የነ በሺር አባስንና የነ አሕመድ አል-ሙስጠፋን የአዘፋፈን ስልት ነው፡፡ በመሆኑም እንደ ካሊፕሶ እና ዲስኮ ሞቅ እያለ የሚጓዘው የሰይድ ኸሊፋ ዘውግ ለነርሱ አልጣማቸውም፡፡
  እያደር ግን ሁሉም ነገር መስተካከል ጀመረ፡፡ ሱዳናዊያን ከሰይድ ኸሊፋ ስልት ጋር ተላመዱ፡፡ ከጥቂት አመታት በኋላ “መደዴ ዘፋኝ” የተባለው ወጣት የሁሉም ሱዳናዊ አርቲስቶች ቁንጮ ሆኖ ተገኘ፡፡ በተለይም “ኢዘየኩም” የተሰኘው ነጠላ ዜማው በኦምዱርማን ሬድዮ ሲለቀቅ ሱዳናዊያን ከዳር እስከ ዳር በአንድ ልብ አደመጡት፡፡ ስለቤተሰብና ፍቅርና ክብር የሚዘምረውን ዘፈኑን የሱዳን ብሄራዊ ዘፈን እስኪመስል ድረስ ተቀባበሉት፡፡
በ1950ዎቹ አጋማሽ ላይ የሰይድ ኸሊፋ ዝና በአባይ ግርጌ ካሉት ግብጽና ሱዳን ተነስቶ የአባይ ምንጭ ወደሆነችው ወደ ኢትዮጵያ ተሻገረ፡፡ ኢትዮጵያዊያንም ዘፈኖቹን ከመስማት አልፈው በአማርኛ፣ በኦሮምኛና በሶማሊኛ ቋንቋዎች እየተረጎሙ ዘፈኑት፡፡ በዚህም መሰረት ምኒልክ ወስናቸው “ጃሩ አነ ጃሩ” የሚለውን ዘፈኑን “ትዝታ አያረጅም” በሚል ቀይሮት ተጫወተው፡፡ ጥላሁን ገሠሠ ደግሞ “ወጠነል ጀማል” የሚለውን ተወዳጅ ዜማውን በአማርኛ ቋንቋ “እዩዋት ስትናፍቀኝ” በማለት ተጫወተው፡፡
—–
1961፡፡ የማይረሳ ዓመት፡፡ ኢትዮጵያዊያን በድምጹ ብቻ የሚያውቁትን ታዋቂ ዘፋኝ ያዩበት ዓመት፡፡ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ መንግሥት ከሱዳን ሪፐብሊክ መንግሥት ጋር ባደረገው የባህልና የኢኮኖሚ ግንኙነቶች ማዳበሪያ ስምምነት መሰረት አንጋፋና ወጣት ድምጻዊያን የተካተቱበት የሱዳን የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጣ፡፡ ዝግጅቱንም በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ቴአትር (በአሁኑ ብሄራዊ ቴአትር) ማቅረብ ጀመረ፡፡ አሕመድ አል-ሙስጠፋ፣ በከር ሙስጠፋ፣ ኢብራሂም አውድ፣ ሳላህ ቢን ባዲያ እና ሌሎችም በታዳሚው ፊት ዘፈኑ፡፡ ከቆይታ በኋላ ግን ብዙዎች ሊያዩት የሚጓጉለት ሰይድ ኸሊፋ ወደ መድረኩ ተጋበዘ፡፡ አዳራሹ በአድናቆት ጭብጨባ ተናወጠ፡፡
ታዲያ ሰይድም ከህዝቡ ለተቸረው አድናቆትና ክብር አጸፋውን በአስገራሚ መልኩ መለሰ፡፡ በሁለት ሌሊቶች ውስጥ ያጠናቸውን የአማርኛ ቃላት ከዐረብኛ ጋር በማሰናኘት “ኢዘየኩም”ን እንዲህ ተጫወተው፡፡
 ኢዘየኩም ኬፍ ኢነኩም (2)
አነ-ሌ ዘማን ማ ሹፍቱኩም፡፡ (2)
“ጤና ይስጥልኝ እንደምን ናችሁ (2)
ከሱዳን መጣን ልናያችሁ” (2)
አነ ሌ ዘማን ማሹፍቱኩም፡፡
 በአዳራሹ የታደመው ኢትዮጵያዊ ተመልካች በሰማው ነገር እየተገረመ ጭብጨባውን አጠናክሮ ቀጠለ፡፡ በዚያች ቀን ተመልካቹን ለማስገረም ብቻ የተላከ ይመስል የነበረው ሰይድ ኸሊፋም ሌላ ዜማ ማከል አስፈለገው፡፡ እና ለሱዳናዊያን እንግዳ የሆነውን “ትዝታን” በተሰባበረ አማርኛ ተጫወተው፡፡ ተመልካቹም በሳቅ ፍርስ እያለ አጨበጨበለት፡፡
——-
አዎን! ሰይድ ኸሊፋ በኢትዮጵያዊያን ልብ ከነገሱ የሱዳን የኪነ-ጥበብ ፈርጦች መካከል ቀዳሚው ነው፡፡ “ሱዳን” ሲባልም ከሁሉ በፊት ለኛ ትዝ የሚሉን “ኢዘየኩም” እና የሰይድ ኸሊፋ የተሰባበረ አማርኛ ናቸው፡፡ ይህ አንጋፋ የጥበብ ፈርጥ በእጅጉ ከሚታወቅበት የምስራቅ አፍሪቃ ክልል ባሻገር በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአውሮጳ እና በአሜሪካ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ለመቀዳጀት በቅቷል፡፡ ለዚህ ይበልጥ የረዳው ደግሞ “ኢዘየኩም”ን በሄደበት ሀገር ቋንቋ ሁሉ ለመዝፈን የሚሞክር መሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም እኛ “ጤና ይስጥልን፣ እንደምን ናችሁ” እያልን የምንዘምረው “ኢዘየኩም” በሀውሳ፣ በሰዋሂሊ፣ በእንግሊዝኛ፣ በጀርመንኛና በፈረንሳይኛ ቋንቋዎችም አቻ ትርጉሞች አሉት፡፡ ይህም ሰይድ ኸሊፋ ሙዚቃን ከመጫወት አልፎ የሌሎችን ቋንቋና ባህል ለማጥናት የነበረውን ጉጉት በአጭሩ ያስረዳል፡፡
——
ሰይድ ኸሊፋ እንደ ብሄራዊ መዝሙር ከሚዘፍነው “ኢዘየኩም” ባሻገር በመቶ የሚቆጠሩ ሌሎች ዜማዎች አሉት፡፡ በሀገራችን አድማጮች ዘንድ ተወዳጅ ከሆኑት ዜማዎቹ መካከል “ኢንቲ ያ ጀሚላ”፣ “ሐቢበተል በለዲያ”፣ “ወሽወሾ ሀምሳ”፣ “ጃሩ አነ ጃሩ”፣ ዚድኒ ሚን ደለክ ሺወይያ”፣ “አል-ዋሒድ ኸሊ ዓለል ዋሒድ”፣ “ተዓሊ ተዓሊ”፣ “ሳምባ”፣ “መሽጉል ባለኪ”፣ “ሲደ-ንናስ ሐደር”፣ “አህላ ገራም”፣ “ያ ዒቅደል ሉሊ” የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ሰይድ ኸሊፋን በመላው ዓለም ተወዳጅ ያደረጉት ግን አራት  ዜማዎች ናቸው፡፡ እነርሱም  “ዘኑባ”፣ “ኢዘየኩም”፣ “አወድዳዕኩም” እና “አል-ማምቦ ሱዳኒ” የተሰኙት ናቸው፡፡
“ዘኑባ” የፍቅር ዜማ ነው፡፡ በዘፈኑ ውስጥ “ዘኑባ” የተባለላት ወጣት የኑቢያ ተወላጅ ናት፡፡ ሰይድ ለዚያች ወጣት “ሐረቀት ገልቢ መሐባታ” (ፍቅርሽ ልቤን አቃጠለው) እያለ ልመናውን ይደረድርላታል፡፡ “ዘኑባ ያ ቢንተል ኒል”ም ይላታል፡፡ “አንቺ ኒል (አባይ) ያበቀላት የኑቢያ ወጣት” ማለት ነው፡፡ ሰይድ ኸሊፋ ይህንን ዘፈን ወደ ኢትዮጵያ በመጣበት ወቅት “ዘነበች” እያለ በአማርኛ አዚሞታል፡፡ እርሱ “ቢንት ኢትዮጵያ፣ ዘነበች” እያለ ሲዘፍን ዘነበች ታደሰ (ጭራ ቀረሽ) ደግሞ ከርሱ ጎን ቆማ ትደንስ ነበር፡፡ 
   “ኢዘየኩም” የሰላምታና የናፍቆት መጠየቂያ ነው-ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት፡፡ ታዲያ ሰይድ በዚህ ዘፈን የተጠቀመው “ኢዘየኩም” የተሰኘው ቃል ሰላምታን ከመግለጽ ባሻገር ትልቅ ታሪካዊ ፍካሬን ተሸክሟል፡፡ “ኢዘይ” (እንዴት) የሚለው ቃል መሰረቱ ዐረብኛ አይደለም፡፡ ይህ ቃል ከጥንታዊው የኑቢያ ቋንቋ ተወርሶ ከዐረብኛ ጋር የተደባለቀ ነው፡፡ በግብፅና በሰሜን ሱዳን ጠረፍ በሚነገረው የዐረብኛ ዘዬ ውስጥ ጉልህ ሆኖ ይሰማል፡፡ በኻርቱም አካባቢ በሚነገረው የዐረብኛ ዘዬ ውስጥ ግን የለም፡፡ የሰይድ ኸሊፋን ዜማዎች ያጠኑ ተመራማሪዎች እንደሚናገሩት ሰይድ ይህንን ቃል በዘፈኑ ውስጥ የተጠቀመው የናፍቆት ሰላምታን ከማስተላለፍ በተጨማሪ የጥንቷ ኑቢያ በታሪክ ውስጥ የነበራትን ሚና ለማስታወስ በሚል ነው፡፡
“አወድዳዕኩም” የተሰኘው ዘፈኑ ደግሞ የ“ኢዘየኩም” ተቃራኒ ነው፡፡ ሰይድ ኸሊፋ በዚህ ዘፈን “ልለያችሁ ነው፤ ልሰናበታችሁ ነው” ነው የሚለው፡፡ ብዙ ጊዜ ሙዚቃውን ለታዳሚዎቹ ሲያቀርብ ሁለቱን ዘፈኖች መክፈቻና መዝጊያ ያደርጋቸዋል (ማለትም በ“ኢዘየኩም” የተጀመረውን ዝግጅት በ“አወድዳዕኩም” ይዘጋዋል)፡፡ ሁለቱን ዘፈኖች የሚዘፍንበት ስሜትም እንደ ዘፈኖቹ ይለያያል፡፡ “ኢዘየኩም”ን በፍልቅልቅ ፈገግታና በደስታ ተሞልቶ ነው የሚጫወተው፡፡ “አወድዳዕኩም”ን ግን ጭንቅ ጥብብ እያለ ልብን በሚነካ ስልት ያስኬደዋል፡፡ አንዳንዴም አልቅሶ ታዳሚውን ያስለቅሳል፡፡ ታዲያ ሰውዬው ሰይድ ኸሊፋ ነውና ሁለቱም ያምሩለታል፡፡ በፈገግታ ሲፍለቅለቅም ሆነ ጉንጮቹን በእምባ ሲያርስ ታዳሚውን የመነቅነቅ ሀይሉ ከፍተኛ ነው፡፡
——–
ከሰይድ ኸሊፋ ታላላቅ ዘፈኖች መካከል ጉልህ ሆኖ የሚጠቀሰው “አል-ማምቦ ሱዳኒ” ነው፡፡ ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት “አል-ማምቦ ሱዳኒ” በመድረክ ላይ የተጫወተው የመጀመሪያ ዜማው ነው፡፡ ሰይድ ኸሊፋ “አል-ማምቦ ሱዳኒን”ን በወጣትነቱ ሲጫወተው “እኛም ሀገር እንዲህ ዐይነት ተአምር አለና ተመልከቱ” ለማለት ያህል ነው፡፡ ከጊዜ በኋላ የዘፈኑ ግጥም በሙዚቃ ኤክስፐርቶች ሲጠና ግን በርካታ ተአምራትን አጭቆ የያዘ እንደሆነ ተደረሰበት፡፡  እስቲ ሙሉ ግጥሙን ልጻፍላችሁ፡፡
—– 
(አዝማቹ)
አል-ማምቦ ሱዳኒ
አልማምቦ ፊኪያኒ
ፊዑዲ ፊከማኒ
ወአጅመል አልሓኒ
ማምቡ….!
—-
(1ኛ ተከታይ ግጥም)
ያ ሐቢበ መሕላኪ
አል-ማምቦ ፊጊናኪ
አል-ለሕኑ ኸልላኪ
ቲትማየሊ ፊኹጣኪ
ዐላ-አንጋሚል ማምቡ
—-
አልማምቦ ሱዳኒ
(2ኛ ተከታይ ግጥም)
ያ ሐቢበ የዑዲክ
ያ ወርደ ፊኹዱዲክ
አድኔቲ መርዩዲክ
ሚን ቡክረ መውዑዲክ
የርጉስ በሃኪ ጀንቡ
—–
ዐላ አንጋሚል ማምቦ
—–
(3ኛ ተከታይ ግጥም)
ረንነት ኹጣኪ አል-ሓን
ያ ወርደ ፊ ቡስታን
አነ ቀልቢ ባት ሐይራን
ማካን ያሬት ማካን
ማዱግና ናር ሑብቡ
——
የውም ረግሰተል ማምቦ
——
(4ኛ ተከታይ ግጥም)
በረደን-ነሲም ያሌል
ያሡረይያ ናዲ ሱሄል
ኩል ኺል መዓህ ኸሊል
አነ ወሕዲ ጀመል-ሽሼል
ዐሰረል-ሀዋ ገልቡ
——
የውም ረግሰተል ማምቦ
—–
“ማምቦ” የላቲን አሜሪካ የጭፈራ ዐይነት የሚጠራበት ስም ነው እንጂ ኦሪጅናሌ የሱዳን ቃል አይደለም፡፡ ሰይድ ኸሊፋም ግጥሙን ሲጀምር በፈረንጆቹ ዘይቤ “ማምቦ” ብሎታል፡፡ በማሳረጊያው ላይ ግን ቃሉን ወደ ዐረብኛ በመጎተት “ማምቡ” አድርጎታል፡፡ ይህንንም ያደረገው አዝማቹን ከተከታዮቹ ግጥሞች ጋር ለማስማማት እንዲያመቸው ነው፡፡
  ተከታዮቹ ግጥሞች ባለ አምስት መስመር ናቸው (ስድስተኛው መስመር ዘፈኑን ለማሳመር የሚደጋገም መነባንብ ነው እንጂ የግጥሞቹ አካል አይደለም፤ ለዚህም ነው ለብቻው የጻፍኩት)፡፡ ከአምስቱ መስመሮች መካከል አራቱ በተመሳሳይ ፊደል ነው የሚያሳርጉት፡፡ በአምስተኛ መስመር ላይ ያሉት ሁሉም ስንኞች ግን “ቡ” በተሰኘው ፊደል ነው የሚያበቁት፡፡ ይህም ከአዝማቹ ጋር በሚጣጣም መልክ መሆኑ ነው (አዝማቹም ባለአምስት መስመር መሆኑን ልብ በሉ)፡፡
እንዲህ ዓይነት ግጥም በዘመናዊው ዐረብኛ ውስጥ የለም፡፡ በጥንታዊው ዐረብኛ (Classical Arabic) ግን የግጥሙን ውበት መጠበቅ ግዴታ ነው፡፡ ገጣሚዎች ስለስንኙ መልዕክት ብቻ ሳይሆን የግጥሙን ውበት በሚያበለጽጉ ቴክኒካዊ ጉዳዮችም ላይ ይጨነቃሉ፡፡ የያንዳንዱ ስንኝ ቃላትና ፊደላት ብዛት፣ ስንኙ ቤት የሚመታበት ሁኔታ፣ ከተከታይ ስንኞች ጋር ያለው ትስስር

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በፈረንሳይ የወደብ ከተማ ፤ ካሌ፣ ከተለያዩ ሃገራት ፤ ከኢትዮጵያና ኤርትራ ጭምር የመጡ ስደተኞች ቀልሰዋቸው የነበሩትን መጠለያ የፕላስቲክ ድንኳኖች ፖሊስ ያፈራረሳቸው መሆኑ ተገለጠ ።

« የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥታዊ መንግሥት ለጀርመን መንግሥት ከፍተኛ እርዳታ አድርጎ ነበር። በዝያን ግዜ እንደሚባለዉ ለጀርመን ወደ 200 ሽ ዶላር ርዳታ ኢትዮጵያ ሰታለች» ይላሉ ዶክተር አስፋዉ ወሰን አስራተ፤

በብሪታንያ በምሕፃሩ «ዩ ኬ አይ ፒ» በመባል የሚታወቀው የተባበረችው ብሪታንያ ነፃ ፓርቲ ባለፈው ሳምንት በሀገሩ በተካሄደው የቀበሌ እና የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ እንዲሁም፣ የአውሮጳ ምክር ቤት እንደራሴዎች ምርጫ በሚያስገርም ሁኔታ

የሩስያ፣ የካዛኽስታን እና የቤላሩስ መንግሥታት በመካከላቸው አንድ የኤኮኖሚ አንድነት ህብረት ለመመሥረት በዛሬው ዕለት ውል ተፈራረሙ። በካዛኽስታን መዲና አስታና የተፈረመው ይኸው ታሪካዊ የተባለው ውል ከስድስት

ከሰሞኑ የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ ያከበረው የኢየሩሳሌም መታሰቢያ ድርጅት፣ በአባልነት የሚመዘግባቸው ተሳላሚዎች ፣ በኢየሩሳሌም ቅዱሳት ቦታዎችን፣ የኢትዮጵያን አብያተ ክርስትያን እና ገዳማትን ጎብኝተው

የሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 20/2006 ዓ.ም ባደረገው የብሄራዊ ምክር ቤት ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ፡፡ ምክር ቤቱ በሊቀመንበሩ የቀረበውን የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ያጸደቀ ሲሆን ብሄራዊ ምክር ቤቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ ውሳኔዎችም ተላልፈዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በሊቀመንበሩ የቀረበለትን የስራ አስፈጻሚዎች የቦታ ሽግሽግም ተቀብሎ ያጸደቀ ሲሆን በሽግሽጉ መሰረትም አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ፣ አቶ ዮናታን ተስፋዬ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ፣ አቶ ጌታነህ ባልቻ የጥናትና ስትራቴጅ ኃላፊ እንዲሁም አቶ እያስፔድ ተስፋዬ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ ሆነው እንዲሰሩ አጽድቋል፡፡

ትምህርታቸው የአፈርና ቋጥኝ ፊዚክስ ፤በተለይም የእሳተ ገሞራ ጥናት ነው። ይሁንና ዛሬ ፣ እመኻል አውሮፓ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 21 ሰዓት ከ 56 ደቂቃ ለምርምር ፣ ከባይኖኩር ካዛኽስታን ፤ በሩሲያ ሶዩዝ የጠፈር መንኮራኩር ወደ ዓለም አቀፉ

 ክፍል አንድ
1.1 አጠቃላይ የግእዝ ሥነ ጽሑፋዊ ሀብት

የግእዝ ቋንቋ ከሁለት ሺ ዓመታት በላይ ጊዜ ያስቆጠረ የሥነ ጽሑፍ ሀብት ያለው ቋንቋ ነው፡፡ እስካሁን የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የግእዝ ሥነ ጽሑፍ በተጻፉበት ቁስ በሦስት መልኮች ቀርበዋል፡፡ በድንጋይ ላይ፣ በብራና ላይና በወረቀት ላይ፡፡

  1. የድንጋይ ላይ ጽሑፎች፡- በድንጋይ ላይ የተጻፉት የግእዝ ሥነ ጽሑፎች በአኩስም አካባቢ የተገኙትንና የነገሥታቱን የጦርነት ታሪኮችንና ሌሎች ዘገባዎችን የያዙትን ጽሑፎች ይመለከታል፡፡  የተገኙት የድንጋይ ላይ ጽሑፎች ከአራተኛው መክዘ(ቅልክ) እስከ 8ኛው መክዘ(ድልክ) የሚደርሱ ናቸው፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ጥንታዊው የሚባለው የድንጋይ ላይ ጽሑፍ በመጣራ ኤርትራ በሐውልቲ የተገኘው(5ኛው መክዘ ቅልክ) ጽሑፍ ነው፡፡

‹ዝ ሐውልት ዘአገበረ

አገዘ ለአበዊሁ ወሰ

ሐበ ሙሓዛተ አውዐ

አለፈነ ወጸበለነ›› የሚለው ነው፡፡

እነዚህ የድንጋይ ላይ ጽሑፎች አብዛኞቹ ዘገባዎችና ታሪኮች ሃይማኖታውያን አይደሉም፡፡

  1. የብራና ላይ ጽሑፎች፡- ሁለተኛው የግእዝ ሥነ ጽሑፍ የብራና ሥነ ጽሑፎች መልክ ነው፡፡ የብራና ላይ የግእዝ ጽሑፍ ከ6ኛው መክዘ እስከ አሁን ዘመን የቀጠለ ሲሆን በማይክሮፊልም በተነሡት የብራና መጻሕፍት ቁጥር የሄድን እንደሆነ ቁጥራቸው እስከ 12,000 ይደርሳል፡፡ በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ አደጋ ጠፍተው የቀሩትን፣ በየቦታው ተደብቀውም አድራሻቸው ያልታወቁትን ሳይጨምር ማለት ነው፡፡ እስካሁን በተገኘው መረጃ ጥንታዊው የሚባለው የብራና የግእዝ መጽሐፍ በእንዳ አባ ገሪማ የሚገኘው ወንጌል ሲሆን የተጻፈውም በ6ኛው መክዘ ነው፡፡

  2. የወረቀት ላይ ጽሑፎች፡- ሦስተኛው የግእዝ ሥነ ጽሑፍ መልክ በወረቀት የታተሙ መጻሕፍት ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት በብራና የሚገኙትን የግእዝ መጻሕፍት ተደራሽ ከማድረግ አንጻር የቀረቡ እንጂ አዳዲስ ድርሰቶች አይደሉም፡፡ የግእዝ የታተሙ መጻሕፍት ታሪክ ጉተንበርግ የግእዙን ዳዊት ጀርመን ላይ ካሳተመበት ጊዜ ይጀምራል፡፡ ይህም የአራት መቶ ዓመታት ታሪክ ይኖረዋል፡፡

 1.2 የሦስቱ የግእዝ ሥነ ጽሑፍ መልኮች ልዩ ባሕርይ
የድንጋይ ላይ ጽሑፎች

የድንጋይ ላይ ጽሑፎቹ የዘገባ መልክ ያላቸው፣ ታሪካዊ መረጃ የሚሰጡና በአብዛኛውም ሃይማኖታዊ ይዘት የሌላቸው ናቸው፡፡ ሃይማኖታዊ መረጃ ቢሰጡንም ነገሥታቱ ፈጣሪያቸውን ሲያመሰግኑ፣ ለፈጣሪያቸው የሰጡትን መሥዋዕት ሲገልጡ፣ ወይም የሙታን መታሰቢያ ሐውልቶቹ ደግሞ እግረ መንገዳቸውን በሚሰጡን መረጃ አማካኝነት ነው፡፡ የድንጋይ ላይ ጹሑፎቹ በሁለት ዓይነት አጻጻፍ የተጻፉ ናቸው፡፡ በጥንታዊና አናባቢ በሌለው ግእዝ ‹‹ሐወለተ፣ አከሰመ›› በሚለው መንገድና አናባቢ በተፈጠረለት ዘመናዊው ግእዝ የተጻፉ ናቸው፡፡ የድንጋይ ላይ ጽሑፎቹ በቅድመ አኩስምና በአኩስም ዘመን የተሠሩ ሲሆኑ የሚያንጸባርቁትም ያንኑ ዘመን ነው፡፡

የብራና ጽሑፎች

የብራና የግእዝ መጻሕፍት ከ6ኛው መክዘ ጀምረው እስካሁን የዘለቁና በሀገራችን የሥነ ጽሑፍ ዘመን በጥንታዊነትም ሆነ ለረዥም ዘመን በመዝለቅ ተወዳዳሪ የሌላቸው ናቸው፡፡ የብራና የግእዝ የጽሑፍ ሀብቶች ሦስት ዓይነት ናቸው፡፡

  1. ሃይማኖታውያን፣

  2. በዋናነት ሃይማኖታውያን ያልሆኑ ጉዳዮችን የያዙና

  3. ደብዳቤዎች

ሃይማኖታውያንየምንላቸው የተጻፉበት ዓላማ ሃይማኖትን ለማስተማር(ዶግማን፣ ቀኖናን፣ ትውፊትን፣ ታሪክን) ወይም ለአምልኮ ሥርዓት መፈጸሚያነት(ለጸሎት፣ ቅዳሴ፣ ውዳሴ፣ ዝማሬ፣ ሃይማኖታዊ ክዋኔ) የሆኑ ጽሑፎች ናቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን ጨምሮ አብዛኞቹ የግእዝ የብራና ጽሑፎች ሃይማኖታውያን ናቸው፡፡ እነዚህ ሃይማኖታውያን የግእዝ ጽሑፎች ሦስት እምነቶችን የያዙ ናቸው፡፡ የኦርቶዶክስ፣ የካቶሊክና የይሁዲነት፡፡ የኦርቶዶክስ እምነትን የሚገልጡ መጻሕፍት በብዛትም ሆነ በቀደምትነት የግእዝን ጽሑፎች ይይዛሉ፡፡ ከ16ኛው መክዘ በኋላ ደግሞ የካቶሊክ እምነትን የሚገልጡ የግእዝ የብራና መጻሕፍትን እናገኛለን፡፡ የይሁዲነትን እምነት የሚገልጡት ጽሑፎች በኢትዮጵያ ከሚገኙ የቤተ እሥራኤል ወገኖች ጋር የተያያዙ ሲሆኑ እስካሁን ባሉን መረጃዎች ከመካከለኛው ዘመን ወደ ኋላ የዘለሉ አላገኘንም፡፡

የታተሙ የግእዝ የጽሑፍ ሀብቶች

የታተሙት የግእዝ ጽሑፎች የብራና ጽሑፎች ቅጅዎች ናቸው፡፡ እስካሁን ድረስ በግእዝ የተጻፉ ኣዳዲስ ድርሰቶችን በኅትመት አላገኘንም፡፡ አብዛኞቹ የታተሙ የግእዝ ጽሑፎች ግእዝና አማርኛን፣ ግእዝና ትግርኛን፣ ግእዝና እንግሊዝኛን፣ ግእዝና ጀርመንኛን፣ ግእዝና ስፓኒሽን፣ ግእዝና ፈረንሳይኛን፣ ግእዝና ፖርቹጊዝን ጎን ለጎን ያደረጉ ሲሆኑ ለሁለት ዓይነት ተግባራት የታተሙ ናቸው፡፡ ለሃይማኖታዊ አገልግሎትና ለምርምር አገልግሎት፡፡ ለሃይማኖታዊ አገልግሎት የሚውሉት የግእዝ ኅትመቶች የሚታተሙት በአብዛኛው በኢትዮጵያና በኤርትራ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ትንሣኤ ዘጉባኤ አሳታሚ፣ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፣ ተስፋ ገብረ ሥላሴ፣ አኩስም ማተሚያ ቤት፣ ማኅበረ ቅዱሳንና የየአጥቢያው አብያተ ክርስቲያናት ሲያሳትሟቸው፤ በኤርትራ ዋናው አሳታሚ ማኅበረ ሐዋርያት ፍሬ ሃይማኖት ነው፡፡

ለምርምር የሚውሉት የግእዝ ኅትመቶች በአብዛኛው የሚታተሙት በውጭ ሀገር ዩኒቨርሲቲዎች በኩል ነው፡፡ እነዚህ ኅትመቶች በጥናታዊ መጽሔቶች ውስጥና ራሳቸውን ችለው በመጽሐፍ መልክ የሚወጡ ሲሆኑ ከግእዙ በተጨማሪ የመቅረቢያ ቋንቋውን ትርጉም፣ ስለ ጽሑፉ ዳራና የጽሑፉ ምሁራዊ ሐተታ ይቀርቡባቸዋል፡፡ አብዛኞቹም የተለያዩ ቅጅዎች ንጽጽር አሏቸው፡፡ በዚህ ረገድ የጣልያን፣ የእንግሊዝ፣ የጀርመን፣ የፈረንሳይና የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ብዙ ሥራ ሠርተዋል፡፡ ለጥናት የሚታተሙ የግእዝ ጽሑፎችን በማተም ቤልጅየም የሚገኘውን ፒተርስ አሳታሚ የሚያህለው የለም፡፡

በግለሰብ ደረጃ ከጥንቶቹ እንግሊዛዊው ዋሊስ በጅ፣ ጀርመናዊው ኤድዋርድ ኡልንዶርፍና ኢዮብ ሉዶልፍ፣ ጣልያናዊዎቹ ኮንቲ ሮሲኒ፣ ኤንሪኮ ቼሩሊና ጉይዲ፤ ፈረንሳዊዎቹ ሬኔ ባሴ፣ ዣን ፕሩሶ፤ ራሺያዊውቢ ቱራየቭ ይጠቀሳሉ፡፡ ከዘመናችን ደግሞ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌን የሚስተካከል የለም፡፡

ክፍል ሁለት

ሃይማኖታውያን ያልሆኑ የግእዝ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች

ስለ ግእዝ ሥነ ጽሑፍ ብዙ ጊዜ ሲነገር ከሃይማኖታውያን የጽሑፍ ሀብቶቹ ጋር በተያያዘ ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለውም በሦስት ምክንያቶች ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡

  1. የግእዝ ቋንቋ በአሁኑ ጊዜ የቤተ ክርስቲያን መገልገያ ቋንቋ በመሆኑ

  2. አብዛኞቹ የግእዝ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች ሃይማኖታውያን በመሆናቸው እና/ወይም

  3. ሃይማኖታውያን ስላልሆኑት የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች በብዛት ባለመነገሩና ባለመታተማቸው

ምንም እንኳን ከላይ የተገለጠው ግእዝን ከሃይማኖታዊ ድርሰቶች ጋር የማያያዝ ትርክት ጊዜ ጠገብ ቢሆንም በግእዝ ቋንቋ ተጽፈው የምናገኛቸው አያሌ ሃይማኖታውያን ያልሆኑ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች ግን አሉ፡፡ እነዚህ ሃይማኖታውያን ያልሆኑት የግእዝ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች ከሁለት ምንጮች የተገኙ ናቸው፡፡

  1. ከሀገር ውጭ

  2. ከሀገር ውስጥ

ከሀገር ውጭ የምንላቸው ከኢትዮጵያ ውጭ ተደርሰው ወደ ግእዝ ቋንቋ የተተረጎሙ ሲሆኑ እነርሱም ከግሪክ፣ ላቲን፣ ዓረብና ቅብጥ የተተረጎሙ ናቸው፡፡ ምንም እንኳን መገኛ ቋንቋዎቻቸው እነዚህ ቢሆኑም በእነርሱ በኩል ግን ከምሥራቅ ሕንድ እስከ ምዕራብ ሮም የሚደርሱ ድርሰቶችን አግኝተናል፡፡

ከሀገር ውስጥ የምንላቸው ደግሞ በኢትዮጵያውያን ደራስያን የተደረሱና በግእዝ ቋንቋ የተጻፉ ናቸው፡፡ እነዚህም በተለይ በመካከለኛው ዘመን ተጀምረው እስከ 18ኛው መክዘ የዘለቁ የግእዝ የሥነ ጽሑፍ ሀብቶች ናቸው፡፡ የዚህ ጥናታዊ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ይህ በመሆኑ በዚህ ጽሑፍ ላይ የተወሰኑትን እናያቸዋለን፡፡

  1. ፊሳሎጎስ፡- ፊሳሎጎስ ከግሪክ ወደ ግእዝ በ6ኛው መክዘ የተተረጎመ መጽሐፍ ነው፡፡ ፊሳሎጎስ በብዙ ቋንቋዎች የታወቀ መጽሐፍ ሲሆን የስሙ መጠሪያ ‹ፊዚዮሎጎስ› ከሚለው የግሪኩ ስም የመጣ ሆኖ በ200 ዓም አካባቢ በእስክንድርያ ውስጥ በግሪክ ቋንቋ የተጻፈ ነው፡፡ መጽሐፉ 48 ምእራፎች ሲኖሩት 42ቱ በእንስሳት፣ 2ቱ በዕጽዋት፣ 4ቱ ደግሞ በማዕድናት ላይ መሠረት ያደረጉ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ምእራፍ አንድ እንስሳ፣ ዕጽ ወይም ማዕድንን በማንሳት፣ ጠባዩንም በመተንተን ከመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ጋር አጣምሮ የሚያቀርብ ነው፡፡

ይህ መጽሐፍ በትውፊታዊው የኢትዮጵያ ትምህርት ውስጥ የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ማስተማሪያ ዋና ምንጭ ሆኖ ያገለገለ ነው፡፡

  1. ፈውስ ሥጋዊ፡- ይህ መጽሐፍ በአብዛኛው የሚታወቀው ፈውስ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ በሚል ነው፡፡ ነገር ግን ሁለቱ መጻሕፍት የተለያዩ ናቸው፡፡ ፈውስ መንፈሳዊ ምናልባት ከ13-16ኛው መክዘ ባለው ጊዜ ወደ ግእዝ የተተረጎመ መንፈሳዊ መጽሐፍ ነው፡፡ ዓላማውም በኃጢአት የቆሰለችን ነፍስ በመንፈሳዊ ሕክምና ማከም ነው፡፡ ፈውስ ሥጋዊ ግን በትክክል እስካሁን ያልተጠና ምናልባት ግን ከ17ኛው መክዘ በፊት የተደረሰ(ከሀገር ውስጥና ከውጭ ምንጮች) መጽሐፍ ይመስለኛል፡፡ በውስጡ ለሥጋዊ ሕመም ፈውስ ሊሰጡ የሚችሉ የተለያዩ የዕጽዋትንና የእንስሳትን ውጤቶች የያዘ ነው፡፡

  2. መጽሐፈ አዕባን፡- እስካሁን ባለኝ መረጃ መሠረት ስለዚህ መጽሐፍ ጥናት አልተደረገም፡፡ አንድ ኢትዮጵያዊ ብቻ በዚሁ ስም አንዲት አነስተኛ መጽሐፍ አሳትሟል፡ የተጠቀመው ይህንን ምንጭ ይሁን ወይም ሌላ አልተገለጠም፡፡ መጽሐፉ ለልዩ ልዩ ተግባር ሊውሉ የሚችሉ ድንጋዮችን በተመለከተ የተጻፈ የጂኦሎጂ መጽሐፍ ነው፡፡ አልፎ አልፎም ድንጋዮቹ በምን ዓይነት አካባቢ እንደሚገኙ ይናገራል፡፡ በኋላ ዘመን የድንጋይ ትርጉምና ጥቅም ተብሎ የተተረጎመውና በEMML 6815 የምናገኘው ከዚህ የተወሰደ ሳይሆን አይቀርም፡፡

  3. ዜና እስክንድር፡- ይህ መጽሐፍ በጥንታዊው ዓለም ታሪክ የተጻፈውን የታላቁን የግሪክ ንጉሥ የእስክንድርን ታሪክ በግእዝ የሚያቀርብ ነው፡፡ መጽሐፉ ምንጩ ግሪክ ሲሆን ከግሪክ ወደ ሶርያ፣ ከሶርያ ወደ ዓረብኛ፣ ከዓረብኛ ወደ ግእዝ የተተረጎመ ነው፡፡ የተተረጎመውም በ16ኛው መክዘ ምናልባት በ11ኛው የደብረ ሊባኖስ አበ ምኔት በዕጨጌ ዕንባቆም የመናዊ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለ፡፡ መጽሐፉ ሲተረጎም ርእሱ ‹‹ሑረቱ ለእስክንድር›› የሚል ነበር፡፡

እስክንድርን በተመለከተ በ14ኛው መክዘ እንደዚሁ አንድ ትርጉም ተከናውኖ ነበር፡፡ ‹‹ዜና እስክንድር›› የተባለው ይህኛው መጽሐፍ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ መጽሐፍ ለመጨረሻ ጊዜ የታየው በትግራይ አካባቢ በሚገኙ ገዳማት ውስጥ ነው፡፡ ዜና እስክንድርየእስክንድርን የጀግንነት ታሪክ በክርስትና የሞራል ትምህርት ውስጥ ለማሳየት የሚሞክር ሲሆን ዋናው ዓላማውም ነገሥታቱን፣ መኳንንቱንና ወታደሮችን ማጀገን ነው፡፡

5.       ፍትሐ ነገሥት፡- ፍትሐ ነገሥት ሁለት ክፍል አለው፡፤ ፍትሕ ሥጋዊና ፍትሕ መንፈሳዊ፡፤ ትኩረታችን በፍትሕ ሥጋዊ ላይ ነው፡፡ ፍትሐ ነገሥትን ያዘጋጀው በ13ኛው መክዘ ግብጽ ውስጥ የነበረው እብን- እል አሳል የተባለ ባለሞያ ነው፡፡ መንፈሳዊ ሕግጋቱን ከተለያዩ የቀኖና መጻሕፍት ሲወስድ ሥጋዊ ሕግጋቱን ደግሞ ከሮም፣ ከባዛንታይምና ከሌሎች ሀገሮች ሕግጋት ወስዷቸዋል፡፡

መጽሐፉ ወደ ግእዝ የተተረጎመው በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሀገሪቱ እስከዚያ ድረስ ትጠቀም የነበረው የኦሪቱን የሕግ መንገድ በመሆኑ ንጉሥ ዘርዐ ያዕቆብ ይህንን ሕግ ለመቀየር በማሰቡ ነው፡፡ ይህንን ሃሳቡን የነገረውና በወቅቱ ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ጴጥሮስ አብደል ሰይድ የተባለ ግብጻዊ ፍትሐ ነገሥትን ንጉሡ ከግብጽ እንዲያስመጣ መከረው፡፡ ጴጥሮስ አብደል ሰይድም በንጉሡ ተልኮ መጽሐፉን ካመጣው በኋላ ወደ ግእዝ ተረጎመው፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ግን ፍትሐ ነገሥት በሥራ ላይ ለመዋሉ ምንጭ የተገኘለት በዐፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን ነው፡፡ ፍትሐ ነገሥት ኢትዮጵያ ዘመናዊ ሕግ እስክትቀርጽ ድረስ የተጠቀመችበት ለ600 ዓመታት ያህል ያገለገለ የሕግ ምንጭ ነው፡፡

6.       ዜና ስክንድስ፡- ስክንድስ በክርስትና የመጀመሪያዎቹ ዘመን የነበረ የግሪክ ፈላስፋ ነው፡፡ እናትና አባቱ የፍልስፍናን ነገር እንዲያጠና ወደ አቴንስ ልከውት የተመራመረውን ነገር ነው መጽሐፉ የሚገልጥልን፡፡ ይህ መጽሐፍ በሁለት የምዕራብ ቋንቋዎች(ላቲንና ግሪክ)ና በሦስት የምሥራቅ ቋንቋዎች(ሲርያክ፣ዓረብኛና ግእዝ) ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያው መጽሐፍ ከዐረብኛ የተተረጎመ ይመስላል፡፡ ወደ ግእዝ የተመለሰውም በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን መሆኑን ይገልጣል፡፡

ግእዙ ሦስት ክፍሎች አሉት፡፡ የመጀመርያው ክፍል የስክንድስን ሕይወት ይይዛል፣ ሁለተኛው ደግሞ የ55 ፍልስፍናዊ ጥያቄዎችንና መልሶችን የያዘ ሲሆን ሦስተኛው ክፍል 108 ጥያቄዎችን እያነሣ ያትታል፡፡


7. መጽሐፈ ፈላስፋ ጠቢባን፡- ይህ ከ1503 – 1515 ዓም ባለው ዘመን የተተረጎመው መጽሐፍ በግእዝ ሊቃውንት ዘንድ እጅግ የታወቀ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ የግሪክና የሌሎች ሀገሮች ፈላስፎችን አባባሎችና ትምህርቶች የያዘ መጽሐፍ ነው፡፡


8. በርለዓም ወየወሴፍ፡- በርለዓም ወየወሴፍ የተለያዩ ምሳሌዎችንና ተረቶችን የያዘ የሕንድ መጽሐፍ ነው፡፡ የተወሰደውም ከትውፊታዊው የጉተማ ቡድሐ የሕይወት ታሪክ ነው፡፡ ታሪኩ የፍቅር ታሪክ ነው፡፡ የዚህ መጽሐፍ ቅጅዎች በአይሁድ፣ በማኒያውያን፣ በሙስሊሞችና በክርስቲያኖች ዘንድ ይገኛሉ፡፡


ዋዳጎስ የተባለ እጅግ ባዕለ ጸጋ የሆነ ኃይለኛ የሕንድ ንጉሥ በሕንድ የሚገኙ ክርስቲያኖችን ጨፈጨፈ፡፡ አንድ ቀን ዋዳጎስ የወሴፍ የሚባል ወንድ ልጅ ወለደ፡፡ ኮከብ ቆጠሪዎችና ጠንቋዮች ስለ ልጁ ዕጣ ፈንታ ሲጠየቁ ልጁ ወደፊት ክርስቲያን እንደሚሆንና የክርስቶስን ሃይማኖትንም ከፍ ከፍ እንደሚያደርግ ይናገራሉ፡፡ ይህንን በመፍራት ንጉሡ ልጁን በአንድ ቤተ መንግሥት ውስጥ ወስኖ አስቀመጠው፡፡ ኀዘን፣ ድክመት፣ ሞት የሚባሉትን ነገሮች እንዳያውቅ እርሱንም ከደስታ የሚያወጣውን ነገር እንዳያጋጥመው አደረገው፡፡


እያደገ ሲሄድ ግን መስፍኑ ከዚያ ቤተ መንግሥት ውጭ ያለውን ዓለምም ለማወቅ ፈለገ፡፡ ከቤተ መንግሥቱ ውጭም ኀዘን፣ በሽታ፣ ልቅሶ፣ ረሃብና ሞት መኖራቸውን ዐወቀ፡፡ ታዋቂው መናኝ መምህር በርለዓምም መስፍኑን አገኘው፡፡ ስለ እግዚአብሔርና ስለ ክርስትናም አስተማረው፡፡ ይህንንም ያስተማረው የተለያዩ ታሪኮችንና አባባሎችን በመጠቀም ነበር፡፡


መስፍኑ የወሴፍ ዓለምን ለመካድ ከበርለዓም ጋር ያለውንም ግንኙነት አባቱ ሳይሰማ ለማቆም ፈለገ፡፡ አባቱ ነገሩን ከመስማቱ በፊትም በርለዓም ከእርሱ ተለየ፡፡ ንጉሡም ነገሩን ሲሰማ እጅግ ተበሳጨ፡፡ የወሴፍን ወደ ጥንት እምነቱ ለመመለስም የቻለውን ሁሉ አደረገ፡፡ የመንግሥቱን አንድ ሦስተኛ ለመስጠት ቃል እስከ መግባትም ደረሰ፡፡ የወሴፍ ግን ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ በመጨረሻም ንጉሡ ራሱ ስሕተቱ ገባው፡፡ አማካሪዎቹ ሁሉ ክርስቲያን ከሆኑ በኋላም ንጉሡም ክርስትናን ተቀበለ፡፡


አባቱ ከሞተ በኋላ የወሴፍ መንግሥቱን ተወ፡፡ እጅግ ለሚያምነው ተከታዩ ዙፋኑን በመስጠትም መምህሩ በርለዓም ለመፈለግ ወደ በረሃ ሄደ፡፡ እዚያ በርለዓምን ሲያገኘውም ሁለቱም የምናኔ ሕይወታቸውን እስከ ዕለተ ሞታቸው ቀጠሉ፡፡


መጽሐፉን ያስተረጎመው ዐፄ ገላውዴዎስ ሲሆን የተረጎመው ደግሞ እጨጌ ዕንባቆም ነው፡፡ ትርጉሙም የተከናወነው በ1546 ዓም ነው፡፡ በርለዓም ወየወሴፍ ከሕንድ ተወስዶ በክርስቲያናዊ መንገድ የቀረበ የሥነ ምግባር ማስተማሪያ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ በሦስቱ ዋና ዋና እምነቶች (አይሁድ፣ ክርስትናና እስልምና) ተቀባይነት ያገኘ መጽሐፍ ነው፡፡


9. አቡሻክር

አቡ ሻክር ቢን አቢ ኤል ከሪም ቡጥሮስ ቢን አል ሙሐዲብ ያዘጋጀው የዓለምን ታሪክ የያዘ መጽሐፍ፡፡ የኖረው ከ1200/ 10 እስከ 1295 እኤአ  ካይሮ ውስጥ ነው፡፡ አቡሻክር የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ዲያቆንና የቅዱሳት መጻሕፍት ደራሲ ነበር፡፡ ከእርሱ መጻሕፍት መካከል በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ዘንድ እጅግ የታወቀው ‹‹ኪታብ – አት – ታዋሪህ›› የተባለውና የዓለምን ታሪክ በአጭር በአጭሩ የሚገልጠው ‹አቡሻክር፣ ሐሳበ አቡሻክር›› እየተባለ የሚጠራው መጽሐፍ ነው፡፡


ከ1626 እስከ 1630 ዓም ባለው ዘመን መካከል የተጻፈ አንድ አቡሻክር እንዲህ ይላል ‹‹ዝንቱ መጽሐፍ ብሩክ ዘደረሰ እግዚእ ትሩፈ ምግባር ማእምረ መጻሕፍት አቡሻክር ወልደ አቡእልከረም ጴጥሮስ መነኮስ እብንልመሐድብ ዘበትርጓሜሁ ወልደ ግሡጽ ወእመአኮ ወልደ ምሁር ዘእሙር በሪሺ ዘተሠይመ ዲያቆነ በቤተ ክርስቲያን ዘመዐልቃ፡፡ እንዘ ይነግር በእንተ ሐሳበ ዐለም፡፡››

የዐረብኛው መጽሐፍ የተጻፈው በ1250 ዓም ነው፡፡ በኢትዮጵያ አንድ የብራና መጽፈፍ ላይ መጽሐፉ የተጻፈው በ6750 ዓመተ ዓለም፣ በ655 ዓመተ ተንባላት (በእስልምና አቆጣጠር) መሆኑን ይገልጣል፡፡ ይህም በ1250 ዓም መሆኑን ያመለክታል፡፡


10.     በአርመንኛ የሚገኙ ቁጥሮች ትርጉም፡- ይህ መጽሐፍ እስካሁን አልተገኘም፡፡ የተጻፈው በ11ኛው የደብረ ሊባኖስ እጨጌ በአቡነ ዕንባቆም የመናዊ ነው፡፡ ከስሙ ለመገመት እንደሚቻለው የአርመንኛ ቁጥሮችን ኮድ የሚተረጉም ይመስላል፡፡ ስለ መጽሐፉ ፍንጭ የሰጠን አልቫሬዝ ነው፡፡


11.       የላቲን ቃላት ዝርዝር፡- ይኼኛውም መጽሐፍ የዕንባቆም መጽሐፍ ነው፡፡ እስካሁን ግን አልተገኘም፡፡ ከስሙ ለመገመት እንደሚቻለው የላቲን ቃላትን የሚዘረዝርና የሚተረጉም ይመስላል፡፡ አልቫሬዝ ዕንባቆም ላቲን እንደሚችል ይነግረናል፡፡ ምናልባትም ጥንታዊ መዝገበ ቃላትም ይሆናል፡፡


12.     በሮማን ዘየ(dialect) የተጻፉ ቁጥሮች ትርጉም፡- ይህ መጽሐፍ የዕጨጌ ዕንባቆም መጽሐፍ ሲሆን የሮምን ቁጥሮችን መንፈሳዊ/ የኮድ ትርጉም የያዘ ይመስላል፡፡ መጽሐፉ እስካሁን አልተገኘም፡፡


13. ዮሐንስ መደብር፡- ይህ መጽሐፍ በግእዝ ሊቃውንት ዘንድ እጅግ የታወቀ የታሪክ መጽሐፍ ነው፡፡ ዲያቆን ቅብርያል በ16ኛው መክዘ የነበረ ግብጻዊ ነው፡፡ ዐረብኛና ግእዝ ይችል ነበር፡፡ በሠራዊቱ አለቃ በአትናቴዎስና በእቴጌ ማርያም ሥና ትእዛዝ ‹‹ዮሐንስ መደብር›› የተሰኘውን የነቅዩስ ጳጳስ የዮሐንስን መጽሐፍ በ1594 ዓም በዐፄ ያዕቆብ ዘመን በአራተኛው ዓመት ተርጉሟል፡፡


በአንድ መጽሐፍ መጨረሻ ላይ እንዲህ ይላል ‹‹ወተርጎምና በአስተሐምሞ ብዙኅ ለዝንቱ መጽሐፍ እም ዓረቢ ለግእዝ አነ ምስኪን ምኑን በኀበ ሰብእ ወትኁት በውስተ ሕዝብ ወዲያቆን ቅብርያል ግብጻዊ ወልደ ሰማዕት ዮሐንስ ዘቀልዩቢ በትእዛዘ አትናቴዎስ ሊቀ ሠራዊት ዘኢትዮጵያ፡፡ ወበትእዛዘ ንግሥት ማርያም ሥና››


14. አንጋረ ፈላስፋ፡- ይህ የተለያዩ ፈላስፎችን አነጋገር የያዘ መጽሐፍ ነው፡፡ የአሪስቶትል(አርስጣጣሊስ)፣ የፕሉቶ (አፍላጦን) የሶቅራጥስ ና የሌሎችንም ፈላስፎች ንግግሮች ይዟል፡፡ መጽሐፈ ፈላስፋ ጠቢባን በመባልም ይታወቃል፡፡


15. ሐተታ ዘርዐ ያዕቆብ አኩስማዊ ወወልደ ሕይወት እንፍራንዛዊ፡- ይህ የ17ኛው መክዘ ኢትዮጵያዊ የፍልስፍና መጽሐፍ ሲሆን በሁለት ኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ነው፡፡ ዘርዐ ያዕቆብ በተባለ የአኩስም ተወላጅና ወልደ ሕይወት በሚባል የጎንደር (እንፍራንዝ) ተወላጅ፡፡ ሁለቱን ያገናኛቸው አመለካከት ነው፡፡ ዘርዐ ያዕቆብ በወቅቱ ይታሰብ ከነበረው የእምነት፣ የባሕልና የአስተዳደር አስተሳሰብ ወጣ ብሎ ነገሮችን በሰላ ዓይን ይመረምር ነበር፡፡ ደቀ መዝሙሩ ወልደ ሕይወትም ይህንኑ መሥመሩን ተከትሎታል፡፡


16. መጽሐፈ ማስያስ፡- አባ ማስያስ በጣና ገዳማት በ15ኛው መክዘ የነበሩ ኢትዮጵያዊ መነኮስ ናቸው፡፡ ስለ ዓለም ነገር ማወቅ ይፈልጉ ነበር፡፡ ይህንንም በጾምና በጸሎት ከፈጣሪያቸ&#481

አሁን በኢትዮጵያ ባለው በቋንቋ ላይ ብቻ የተመሰረተ፣ የብሄረሰብ ፌዴራል አወቃቀርን በተመለተ ከሶስት የኦሮሞ ምሁራን ጋር የአሜሪካን ድምጽ ራዲዮ ያደረገው መደመጥ ያለበት ዉይይት !

ዛሬ ከአገራችን አውራ ችግሮች መካከል ዋናው፣ የተደጋገሙ ውሸቶች ዕውነት የመሰሏቸው ቡድኖች የሚያጎኑት በጥላቻ ላይ የተመሠረተ የዘር ፖለቲካ እና አንድን ነገድ፣ በኢትዮጵያ ተፈጠሩ ለሚባሉ ችግሮች ሁሉ ተጠያቂ የሚያደርገው ነው ብዬ አምናለሁ። አይደለም የሚለኝ ከመጣም የሚለውን ለመስማት ዝግጁ ነኝ። የተደጋገሙ ውሸቶች ሀውልት ሲያስቆሙ እያዬን ነው። የአኖሌን ሀውልት ለአብነት መመልከት ነው። የከተሞችን ስም ሲያስለውጥ እያዬን ነው። አዲስ አበባን […]

ነገረ ኢትዮጵያ የግንቦት 20 ልዩ እትም ጋዜጣዋ የግንቦት 20 ‹‹ፍሬዎች›› ተዳሰውባታል፡፡

በተለያየ ምክንያትጋዜጣዋን ኮፒ በዕለቱ ያላገኛችሁ ይኸው መረጃ ይደርሳችሁ ዘንድ በፒዲ ኤፍ ለቀናታል
PDF ያንብቧት!

ታምራት ታረቀኝ የግንቦት 20 ሰለባ የሆኑትንና ሐኪም አጥተው የሞቱትን እውቁን ሐኪም ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያስታውሰናል፡፡
የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ስለ ግንቦት 20 ፍሬዎች የራሳቸውን እይታ ገልተውባታል፡፡
የመኢአድ ፕሬዝደንት አቶ አበባው መሃሪ፣
የሰማያዊ ፓርቲ ም/ሊቀመንበር አቶ ስለሽ ፈይሳ፣
የአረና የህዝብ ግንኙነት አቶ አብርሃ ደስታ
እንዲሁም የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ ሰሎሞን ስዩም ስለ ግንቦት 20 ይናገሩባታል፡፡
አቶ ታዴዎስ ታንቱ የግንቦት 20ን እንክርዳድ ለመመንገል ስለሚያስችለው ስልት ጽፈውባታል፡፡
ሰንደቅ አላማውና ግንቦት 20፣ ግንቦትና ግንቦታውያን፣ ግንቦት 20 የበላቸው ቀሽ ገብሩዎች፣ ግንቦት 20 እና ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነት….እና በርካታ ጉዳዮች ተዳስሰውበታል፡፡
መልካም ንባብ!

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በርሊን-ጀርመን የሚሩ ኢትዮጵያዉን ባንፃሩ ኢሕአዴግ ሥልጣን የያዘበትን ሃያ ሦስተኛ ዓመት በተቃዉሞ ሠልፍ ዘክረዉታል። ሠልፈኞቹ ባለፉት ሃያ ሦስት ዓመታት የኢትዮጵያዉን ሰብአዊ መብት መረገጡን፤