የብዙ ድርጅቶች ስብስበ የሆነው መድረክ በአዋሳ ከተማ ቅዳሜ ሰኔ 7 ቀን በጠራዉ ሰላማዊ ሰልፍ በርካታ ሕዝብ በመገኘት ድምጹን እንዳሰማ የደረሰን ዘገባ አመለከተ። መድረኩ ከጥቂት ሳምንታት በፎኢት በአዋሳ ሕዝባዊ ስብሰባ አድርጎ የነበረ ሲሆን ፣ በአዲስ አበባ የተቃዉሞ ሰልፍ ማድረጉ ይታወሳል።

“ሰዎቹ ለፖለቲካ ትርፍ ማስገኛ መጠቀሚያ እየሆኑ ነው::” የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር

ባለፈው ዓመት ለዓመታት ከኖሩበትና ሀብት ንብረት ካፈሩበት መኖሪያቸው እንደተፈናቀሉ በመግለጽ ይህን ተግባር ፈጽመዋል፣ አስፈጽመዋል ባሏቸው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴርና በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ቡለል ወረዳ ላይ ተፈናቃዮቹ በተወካዮቻቸው በኩል ክስ መስርተዋል፡፡

በዚህ መሰረት ዛሬ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ 8ኛ ፍትሃ ብሄር ምድብ በዋለው ችሎት የክስ መዝገቡ ተሰምቷል፡፡ ተፈናቃዮቹ በጠበቃቸው በዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም አማካኝነት እየተመሩ ክሱን እንዲያስኬዱላቸው ቄስ መስፍን አስፋውንና አቶ አቻምየለው ደሴን ወክለው አቤቱታቸውን ለፍርድ ቤቱ አሰምተዋል፡፡

ከሳሾቹ ከ15-20 ዓመታት ከኖሩበት ስፍራ ቤት ንብረታቸውን ጥለው እንዲፈናቀሉ መደረጋቸውንና ይህም ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ ወንጀል እንደተፈጸመባቸው አስረድተዋል፡፡ ክሱ የቀረበባቸው የፌደራል ጉዳዮችና የቡለል ወረዳም መልስ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከሳሾቹ ይኖሩበት በነበረው ቦታ ቤት ንብረት አላፈሩም፤ ሰዎቹ ለፖለቲካ ትርፍ ማስገኛ መጠቀሚያ እየሆኑ ነው ሲል ለችሎቱ አስረድቷል፡፡
የቡለል ወረዳ በበኩሉ ከሳሾቹ በወንጀል የሚፈለጉ እንደሆኑ ጠቅሷል፡፡ ችሎቹ ግራ ቀኙን አዳምጦ ሶስቱም አካላት ለክርክር ቀጠሮ ሰኔ 30 ድጋሜ ችሎት ፊት እንዲቀርቡ ወስኗል፡፡

ይህን የፍርድ ሂደት ለማስጀመር ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ ባካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የዜጎችን ከአመታት ከኖሩበት ቀየ መፈናቀል በማውገዝ ጉዳዩን ወደ ህግ ለማቅረብ ቃል በገባው መሰረት የተፈናቃዮችን ሁኔታ ቦታው ድረስ በመሄድና በመከታተል ለአሁኑ የህግ ሂደት እንዲደርስ ማስቻሉን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡ አሁንም ፓርቲው አጠቃላይ የፍረድ ሂደቱን በቅርበት እንደሚከታተል አቶ ዮናታን ጨምረው አስረድተዋል፡፡

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

እርስ በርስ መካሰስ፣ መጠላላት፣ መበላላት፣ የሌላውን ታሪክ ማጉደፍ፣ የሌሎችን ሰብዓዊ ክብር መንካትና ማዋረድ እንደ ጀብዱና አሸናፊነት በሚቆጠርበት፣ ጥላቻ፣ ጽንፈኝነትና መለያየት የአገራችን ፖለቲካ ፓርቲዎችና ፖለቲከኞቻችን ልዩ መለያ ሆኖአል፡፡

ኢትዮጵያን ወደ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ያሻግራል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት ተማሪ፣ ገበሬ፣ ወታደር፣ ምሑር፣ወዘተ በነቂስ ሆ ብሎ የተሳተፈበት አብዮት በአገራችን ላይ ጥሎት ያለፈው ጠባሳ እጅግ ከባድና መራር ነበር፡፡ እስከ አሁንም ድረስ በዚያን ዘመን ትውልድ አባላት ለውጥ አራማጆች ላይ የፈጠረው የልዩነት ገደል፣ ጥላቻና መራርነት ሳይናድ እዚህ ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡

የትናንት ትውልድ አባል የሆኑት አብዛኛው የዛሬዎቹ ፖለቲከኞቻችን የብዙ ወገኖቻቸውን ክቡር ሕይወት የቀጠፈውንና አገሪቷን ወደ አሰቃቂ እልቂትና ፍጅት የመራውን ፖለቲካዊ ቀውስ አስመልክቶ ይቅር ለመባባልና እርቅ ለማውረድ ከወሬ ባለፈ ተግባራዊ የሆነ እንቅስቃሴ ለማድረግ አልደፈሩም፡፡ ዛሬም ቢሆን ትናንት በአገራችን ላይ ለተከሰተው ሰብዓዊ እልቂት፣ ኢኮኖሚያዊ ውድመትና ማኅበራዊ ምስቅልቅል አንዱ አንዱን ተጠያቂ የማድረግ አባዜ ነው ጎልቶ የሚታየው፡፡

የፍቅርን፣ የሰላምንና የዕርቅን ባንዲራ ከፍ አድርጎ በማውለብለብ የኢትዮጵያችንን የዘመናት ፖለቲካዊ ስብራቷንና እያመረቀዘ ያስቸገራትን የቂም በቀልና የጥላቻ ቁስሏ ይሽር ዘንድ የፍቅርንና የይቅርታን ዘይት የሚያፈስላት እንደ ማንዴላ ያለ ብሔራዊ የፍቅር ጀግና ለማግኘት ገና አልታደለችም፡፡ እናም ያልሻረ ቁስሏን፣ ያልተፈወሰ ሕመሟንና ያልተጠገነ ስብሯቷን ይዛ በማንከስ እናት ኢትዮጵያ በእኛም ዘመን ወንድም ወንድሙን ትናንት በተፈጸመ ታሪክ ለበቀልና ለሞት የሚፈላለጉባት ምድር ሆና ዘልቃለች፡፡

በጥላቻ፣ በቂም በቀለኝነትና በጽንፈኝነት እግረ ሙቅ ውስጥ ለወደቀው የአገራችን ፖለቲካ መፍትሔው ከልብ የሆነና ከፍቅር የመነጨ ብሔራዊ እርቅ፣ መግባባትና በግልጽ መነጋገር እንደሆነ በግሌ በእጅጉ አምናለሁ፡፡ ይህን ጹሑፍ ለመጻፍ የተነሳሁበት ዋነኛው ምክንያትም በገዢው ፓርቲም ሆነ በተቃዋሚ ፖለቲከኞቻችን መካከል ተቀራርቦ በመግባባት መነጋገር ይቻል ዘንድ፣የአንድ አገር ልጆች በሐሳብ ልዩነትና ፖለቲካዊ አመለካከት ምክንያት በጠላትነት የምንፈራረጅበት የጨለማው ታሪክ ዘመናችን ያበቃ ዘንድ በመመኘት ነው፡፡

አሁንም ድረስ የአገራችን ፖለቲካ በጥላቻና በጽንፈኝት ሥር ወድቆ የሚማቅቅ መሆኑን ከበቂ በላይ የሆኑ ማሰረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በዕርቅና በፍቅር መንገድ ሊነሱ ቀና ቀና ያሉትንም ባለ ራዕዮች ከጠላቶቻቸው ቀድመው ወዳጆቻቸው ነን የሚሉት ራዕያቸውን አምክነው፣ ተስፋቸውን አድብዝዘው ከትግሉ መድረክ ገፍተዋቸዋል፡፡ እናም ዛሬም ድረስ የአገራችን የፖለቲካ ሰማይ ካረገዘው ከጥላቻ፣ ከጽንፈኝነትና ከቂም በቀል የጸዳ ለማድረግ ገና ከፊታችን እልህ አስጨራሽ የሆነ ረጅም ጉዞ የሚቀረን ይመስለኛል፡፡

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) :- የመንግስት ሹመኞችና ባለሟሎቹ የሙስናን በሽታውን ወደ ሕዝብ ነዝተውታል፡፡ ነጋዴው ማህበረሰብ እንደወትሮው ወጭ ገቢውን የሚያሰላው ከቀጥተኛ ወጭው ጋር ያተያያዘውን ግዢና ግብር ብቻ አይደለም፡፡ የቀን ጅብ ለሆኑ ሙሰኞች የሚሰጠውን ኮሚሽንና ውጣ ወረዱን ጭምር ነው። ………… ሕዝቡ የኑሮ ውድነት ከበደኝ! የእቃ ዋጋ ንረት አስመረረኝ! ግፍ በዛብኝ! ሸምቶ መቃመስ አቃኝ የሚል ምሬት ሲያሰማ.. ሹመኞች አፍ ለማስያዝንና ለማሸማቀቅ ይሽቀዳደማሉ፡፡ “በገበያ ስርዓት ነው የምንመራው የሚችል ይገዛል፡፡ ያልቻለ አይገዛም” ይባላል፡፡ ገፋ ሲልም “አጭበርባሪ ነጋዴ ስናሳድድ አንገኝም!” የሚል ማበረታቻ አከል መልስ ለሕዝቡ ይሰጣል፡፡
የተረጋጋ የነበረውን የግብይይት ስርዓት ያለበቂ መነሻና ጥናት የዋጋ ጣራ በማወጅ፣ ውቅያኖሱን ደብድቦ አሳውን የሚረብሽ ፖሊሲ ይዘረጋል፡፡ አለመረጋጋቱን ታኮ ነጋዴው እጥረትን፣ የጥራት ችግርን፣ ቅሸባን፣ ሚዛን ማጓደልን አይነተኛ የስራውና የትርፉ መሰረት ያደርገዋል፡፡ ሕዝብ፤ ሙስና እየነዳ ላመጣው ግፍ ለዋጋ ንረት፣ ለኑሮ ውድነት፣ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ ተዳርጓል፡፡
http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … -post.html

መጪው ጊዜ ለወያኔ ጨለማ ሆኖቦታል። መላ ሃገሪቱን በስለላ መረብ አጥሮታል።

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
የሃገሪቱ ግማሽ በጀት ላፓርላማቸው ሳያሳውቁ ለደህንነት እና ለስለላ ተግባር መድበዋል።
በአራት ቡድኖች ተከፍሎ በከፍተኛ የሕወሃት አመራሮች የሚመራ የደህንነት ቡድን በአገሪቱ በአዲስ መዋቅር ስራ መጀመሩን መረጃዎች ጠቁመዋል ፤ ኢሕአዴግ ውስጥ በተነሳው የብሩህ ተስፋ ክሽፈት የመጣ በባለስልጣናቱ ዘንድ ከፍተኛ የሆነ ድንጋጤ መከሰቱን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ውጥረት አመራሮችን አጣብቂኝ ውስጥ ከቷቸዋል። ባለፉት 23 አመታት በህዝብ እና በሃገር ላይ የተደረገው ከፍተኛ የሆነ በደል እና ዘረፋ በሕዝቡ ዘንድ ጥርስ እንዳስነከሰባቸው እና መጪው ጊዜ ይጨልምብናል ብለው ከፍተኛ ስጋት ስላደረባቸው በአራት ቡድኖች የተከፋፈለ በሕወሓት ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ እና በመላው ሃገሪቱ የተበተነ የድህንነት እና የስለላ ሃይል ማሰማራታቸው ታውቋል።

በአራት ቡድኖች ተከፍሎ በከፍተኛ የሕወሃት አመራሮች የሚመራ የደህንነት ቡድን በአገሪቱ በአዲስ መዋቅር ስራ የጀመረው በየአከባቢው ከመንደር እና ቀበሌ ጀምሮ እስከ ከተሞች የገጠር ወረዳዎች ዘልቆ በመግባት በወያኔ ላይ ደባ ይሰራሉ ይፈጸማሉ ይመከራሉ የተባሉ እያንዳንዱን የዜጎች እንቅስቃሴዎች ሪፖርቶችን በትጋት በመሰብሰብ ወደ መሃል አገር በመላክ መታፈን ያለባቸው መገደል ያለባቸው ደብዛቸው መጥፋት ያለባቸውን ሰዎች በተመለከተ ከበላይ በሚተላለፍለት ትእዛዝ መሰረት መፈጸም ዋናው ስራው ነው። ይህ የደህንነት እና የስለላ መዋቅር ከመሃል ሃገር ተነስቶ እስከ ኬንያ ዩጋንዳ የኤርትራ ደጋማ አከባቢዎች ደቡብ ሱዳን እና ሱዳን ጅቡቲ እና ሰሜን ሱማሊያን ያጠቃልላል።

ወያኔ የሚጠራው መጪው ምርጫ ሕዝቡ በ1997 እንዳደረገው አሁንም እንዲሁ ቂሙን በካርድ ይገልጽብናል በማለት የሚሰጋው ወያኔ መጪውን ምርጫ ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውን ተቃውሞ ከፍተኛ የሆነ የሃይል እርምጃ በመጠቀም ለማክሸፍ የሚያስችለው በየትኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ሊሆን እንደሚችል ስለላውን ተያይዞታል፡፤

አራቱ የደህንንት እና የስለላ ቡድኖችን የሚመሩት ከፍተኛ የሕወሓት አመራሮች የደህንነት ሹሞቹ ጌታቸው እና ኢሳያስ በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን እና በጎረቤት አገሮች ያለውን በደብረጺሆን ገብረሚካኤል የሚመራው ቡድን በደቡብ ኢትዮጵያ በብርጋዴር ጄኔራል ተክለብርሃን የሚመራው ቡድን በምእራብ ኢትዮጵያ እንዲሁም ባለፈው አውስትራሊያ ውስጥ በቡጢ የተዘረሩት አለቃ ጸጋዪ የሰሜኑን ክፍል እና የኤርትራ ደጋማ አከባቢዎችን የደህንነት እና የስለላ መዋቅር ለመምራት ከፍተኛ ገንዘብ ለስልጣን ማቆያቸው በመመደብ የገቡበትን ውጥረት ለማኮላሸት እየሰሩ መሆኑን ታውቋል።

በፓርቲው ውስጥ የሚነሱ ጥያቄዎች የካድሬዎች እንቢተኝነት የውጪ ሃይሎች ጫና የህዝብ እሮሮ እና አቤቱታ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ወያኔ ማጣፊያው አጥሮት የሃገሪቱን ግማሽ በጀት የሚሆነውን ለደህንነት እና ለስለላ ተግብር በማዋል ከፍተኛ የሆነ አደጋ በሃገር ላይ አውጆ ሕዝብን እያሸበረ ይገኛል።

‹‹ዕውቅናችን ሕጋዊ ነው፤ ቅሬታችን በአግባቡ አልተስተናገደም፡፡›› /የኅብረቱ አመራሮች/ በየሀገረ ስብከቱ ለተበራከቱት ማኅበራት መመሪያ እንዲዘጋጅላቸው ተጠይቋል (ኢትዮ-ምኅዳር፤ ቅፅ ፪ ቁጥር ፸፪፤ ረቡዕ፣ ሰኔ ፲፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የተደራጀው ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት›› የአገልግሎት ፈቃድ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ መታገዱ ተገለጸ፡፡ የእግድ ውሳኔው ለኹሉም ማኅበራት በማዕከል ተዘጋጅቶ …

…ዕለቱ የሁለት ሺ ሶስት ዓመተ ምህረት የመስቀል በዓል የተከበረበት ማግስት፤ ሰሜናዊቷ የኤርትራ አዋሳኝ ወልቃይት ገና ከእንቅልፏ ሙሉ ለሙሉ ባለመንቃቷ፣ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ ጎፈሪያቸው የተንጨ(ባረረ ፋኖዎች በውስጧ ካሉ ተቋማት ወደ አንዱ እያመሩ ስለመሆኑ የጠረጠረች አትመስልም፤ ከኤርትራ የተነሱት ፋኖዎች መዳረሻ በወረዳዋ ታዋቂ የሆነው አወርቅ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመሆኑ፤ ማንም ልብ ሳይላቸው ልክ እዚያው እንደደረሱ፣ ከፊሎቹ በሰለጠነ […]

በምሥራቅ አፍሪቃ በተለይም በአፍሪቃው ቀንድ በመከሠት ላይ ያለውን ድርቅ ለመቋቋም፤ የምሥራቅ አፍሪቃ በይነ መንግሥታት ፣ የኢ ጋ ድ ሃገራት መሪዎች፤ አዲስ አበባ ውስጥ ጉባዔ በማካሄድ ድርቁን መቋቋም በሚያስችሉ

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ሚንስትር ደ ኤታ ዚልበርሆርን እንደሚሉት ደግሞ የአፍሪቃ ዕድገት እንዲቀጥል ዕድገቱ የአፍሪቃዉያን በሙሉ መሆን አለበት።የሕዝቡን የምግብ፤የጤና እና የትምሕርት ፍላጎት ማሟላት-አንድ።መልካም አስተዳድር እና የመሠረተ-ልማት አዉታርን ማስፋፋት-ሰወስት።

በብራዚሉ የዓለም ዋንጫ ውድድር ፤ የጀርመንና የፖርቱጋል ብሔራዊ ቡድኖች፣ ከምድባቸው የመጀመሪያውን ግጥሚያ ዛሬ አካኺደዋል። ጀምረዋል። ስለሁለቱ ቡድኖች ሰሞኑን ብዙ ሲጻፍና ሲነገር ሰንብቷል። የእግር ኳስ ባለሙያዎች እንዴት ያዩታል? ቀድሞ

በዩናይትድ ስቴትስ ኮሎምቢያ ዩንቨርስቲ የሚደገፈው «አይ ሲ ኤ ፒ» በሚል የእንግሊዝኛ ምሕጻር የሚታወቀው ግብረ ሠናይ ድርጅት በምሥራቅ ኢትዮጵያ ለሚገኙ የጤና ተቋማት፣ የቴክኒክና የሕክምና መሣሪያዎች ድጋፍ

የአንጎሎ-አሜሪካን መሪዎች አዲሲቱ ኢራቅ በደም-አስከሬን፤ በሽብር፤ እልቂት፤ በጥፋት ዉድመት ቀለል ካለም እስረኞችን በማሰቃየት- ከድፍን ዓለም አንደኛ ሐብታም ሐገር ስትሆን-ሰዉዬዉም እንደ ሁሉም ዓለም አዩ።እንደ ሁሉም ኢራቃዊ ኖሩበት።አማረሩ።እንደ ሐይማኖት መሪ-አወገዙ፤ እንደ ወጣት ጥፋቱን-ሊያጠፋ ተነሳ።

በምሥራቅ አፍሪቃ በተለይም በአፍሪቃው ቀንድ በመከሠት ላይ ያለውን ድርቅ ለመቋቋም፤ የምሥራቅ አፍሪቃ በይነ መንግሥታት ፣ የኢ ጋ ድ ሃገራት መሪዎች፤ አዲስ አበባ ውስጥ ጉባዔ በማካሄድ ድርቁን መቋቋም በሚያስችሉ

 በእዩብ መሳፍንት 

ጦማርያንን እና ጋዜጠኞችን ጉዳይ ለማየት የተሰየመው ችሎት ለ4ኛ ግዜ የተቀጠረው ፖሊስ ምርመራዬን አልጨረስኩም፤ ያልተያዙ ግብራበሮቻቸው አሉ፤ እንዲሁም ማስረጃዬን አጠናቅሬ አልጨረስኩም በማለቱ ነበር፡፡ ከዚህ በፊት በነበሩት ሁሉም ቀጠሮዎች ፖሊስ ለተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ በምክኒያትነት ያቀረበው እነዚሁኑ ምክኒያቶች ነበር፡፡

ከሶስተኛው ቀጠሮ ጀምሮ ክሱ ወደ “ሽብርተኝነት” የዞረ በመሆኑ ጉዳያቸውና የቀጠሮ አሰጣጡ በዚሁ ህግ መሰረት መካሄድ አለበት፡፡ በፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ አንቀፅ 20/3/ መሰረት ፖሊስ ምርመራውን ለማጠናቀቅ የ28ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ሊሰጠው እንደሚችልና ይህ ግዜም በድምሩ ከ4 ወር ሊበልጥ እንደማይችል ይደነግጋል፡፡ የዚህ አንቀፅ ዋናው አላማውም ለፖሊስ በቂ የምርመራ ጊዜ መስጠትና ተጠርጣሪውም እንዳይጎዳ የፖሊስን የምርመራ ጊዜ መገደብ ነው፡፡
ፖሊስ የጠረጠረው ወንጀል ምንም ያህል ውስብስብ ቢሆን ከ4 ወር በላይ ሊፈቀድለት አይችልም፡፡ እስከዛሬ ቀን ድረስ ጓደኞቻችን ለ52 ቀናት የታሰሩ ሲሆን ፖሊስ ግን በነዚህ ቀናት ይህን ሰርቻለሁ ያለው አንድም ነገር የለም፡፡ አንድ አይነት ምክኒያት በመስጠት ብቻ ይጠይቃል ፍ/ቤቱም ይፈቅዳል፡፡ ባሁኑ ችሎት ለየት የሚለው ነገር ዳኛዋ ለፖሊስ ቀጠሮውን የሰጡት ከከባድ ማስጠንቀቅያ ጋር መሆኑ ነው፡፡ (ግዴላችሁም ሴት ዳኞች ሳይሻሉን አይቀሩም)


 

ፖሊስ የሽብር ህጉን አላማ በማሳት የምርመራ ጊዜውን በአግባቡ እየተጠቀመበት አለመሆኑን ከዚህ በላይ ማሳያ አያስፈልግም፡፡ በተደጋጋሚ ቀጠሮዎች አንድ አይነት የማይረባ ምክኒያት በማቅረብ ቀጠሮ ማራዘምን መጠቀም የክሱን ፓለቲካዊነት ያጎላዋል፡፡ ለዚህ ነው የፍትህ አካላት ፖሊስን ጨምሮ ከገዢው ፓርቲ ተፅኖ ነፃ አይደሉም የምንለው፡፡ የገዢዎችን ፊት እያየ የሚሰራ የፍትህ አካል መቼም ገለልተኛ ስራ መስራት አይችልም፡፡ ኢህአዲግም ከሀገር አንድነት በመቀጠል በእምብርክክ ያስኬደው እና ለፓለቲካዊ ጥቅሙ እየተጠቀመበት ያለው የፍትህ ስርአቱን ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ፖሊስ በማይረባ ምክኒያትም ቢሆን ባቀረበው ጥያቄ ሌላ የ28 ቀን ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ የሰው ክብር እና ሉአላዊነት (autonomy) በረከሰበት ሀገር የ28 ቀናት ተጨማሪ እስር ምንም ላይመስል ይችላል፡፡ ምክኒያቱም እውነተኛውን ነፃነት በተመለከተ እኔና የዞን ዘጠኙ አጥናፍ ሁለታችንም ታሳሪዎች ነን፡፡ የእስር ቤቱ ስፋት እና ያለንበት ዞን ቢለያይም፡፡
ከምሬቱ ወደ ህግ አስተያየቱ ስመለስ ፍ/ቤቱ የዛሬ 28ቀንም በዚሁ ሰንካላ ምክኒያት ተጨማሪ የግዜ ቀጠሮ አይሰጥም የሚል እምነት የለኝም፡፡ እኔም ገራም የሆነውን የጠበቃ አምሀን ቃል ልዋስና ሂደቱን በሚመለከት

“ብሩህ ነገር ይታየኛል ለማለት ባለመቻሌ አዝናለሁ”


ከአምባገነን ስርአት ፍትህን መጠበቅ ሞኝነት ነውና፡፡ ኢህአዴግ ማሰር እንጂ መፍታት የሚያስችል የሞራል የበላይነት የለውም፡፡ ተፈጥሮውም አይፈቅድለትም፡፡
ብዙ ወገኖች ጥሩ ዜና ጠብቀው ፍ/ቤት መገኘታቸውን ሳይ አዝኛለሁ ለእኔ የዋህነት እና የስርአቱን ባህሪይ ጠንቅቆ አለማወቀ ነው፡፡ በሚቀጥለውም ከዚህ የተሻለ ነገር ይጠበቃል ብየ አላስብም፡፡ የዚህን የአምባገነን ስርአት ባህሪ የታሰሩ ጦማሪያኑም በሚገባ ያውቁ ነበር፡፡ እኔ ጀግኖች ናቸው የምላቸው የሚደርስባቸውን እያወቁ ይህንን መንገድ በመምረጣቸው ነው፡፡
ውጤ ቱ ምንም ይሁን ምን አሁንም ቢሆን ጩኀታችንን መቀጠል ይኖርብናል፡፡ ዝም የሚያስብል ህሊና የለንምና፡፡ 

ማስታወሻ
በመጨረሻም ፅሁፉ በብስጭት፤ በቁጭት፤ በንዴትና እና በአቅም ማጣት የተፃፈ ስለሆነ ከህጉ ይልቅ በፖለቲካ ላይ ካተኮርኩ አትዘኑብኝ፡፡ (ለነገሩ ጉዳዩን ቀድሞ የቀላቀለው ራሱ ኢህአዴግ ነው) 

#FreerZone9bloggers #FreeEdom #FreeTesfalem #FreeAsemamaw #Ethiopia

ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በእንግዶች ተጨናንቋል፡፡ በአዲስ አበባ ለሚዘጋጀው ዓለም አቀፍ ጉባኤ የሚመጡ እንግዶች አሁንም አሁንም የፍተሻውን መሥመር እያለፉ ሌሎች አገልግሎቶችን ለማግኘት ይሰለፋሉ፡፡ ብዙዎቹ የሞባይል ስልክ ለማግኘት የተሰለፉ ናቸው፡፡ የቪዛ አገልግሎት ለማግኘት እንኳን ያንን ያህል አልተሰለፉም፡፡ አንዳንዶቹ ያማርራሉ፣ አንዳንዶቹም ያመራሉ፡፡

ሰልፉ እየተቃለለ መጥቶ ሁሉም እንግዶች ወደየማረፊያቸው ተጓዙ፤ ጉባኤው የሚጀመረው ነገ ነው፡፡

በማግሥቱ የሀገሩም የውጭውም ሰው በአዳራሹ ከተተ፡፡ መርሐ ግብሩ እስኪጀመር ድረስ ንዴትና ብስጭት፣ ቁጣና ርግማን የተቀላቀለባቸው ንግግሮች ከእንግዶቹ እዚህም እዚያም ይሠነዘሩ ጀመር፡፡ ‹‹እንዴት ለሀገራቸው ሰው ብቻ የሚሠራ ስልክ ይሰጣሉ፤ ነውር አይደለም እንዴ›› ይላሉ እዚህም እዚያም፡፡ አንዳንዱ ስልኩን መሬት ላይ ቢፈጠፍጠው ንዴቱ የሚበርድለት ይመስል አሥር ጊዜ ይሠነዝረዋል፡፡ ወዲያው አንድ አካባቢ ሰዎቹ ከበው ቆሙ፤ ቀጥሎም ቁጣ ቀላቅሎ የሚዘንብ የውግዘት ዝናብ አወረዱ፡፡

ለካስ ከጉባኤው አስተናጋጆች መካከል አንዱን አግኝተውት ነው፡፡ ‹‹እንዴት ከስልክ ዐቅም የሀገር ሰውና የውጭ ትለያላችሁ፤ ሌላ ሀገርኮ ስልክ በሳንቲም ከሱቅ የሚሸመት ነው፤ የኛ ሳይሠራ እንዴት የናንተ ብቻ ተለይቶ ሠራ›› ባለሥልጣን እንዳጀበ መኪና ጥያቄው ተከታትሎ ወረደ፡፡ ‹‹ተአምኁ በበይናቲክሙ›› እንደተባለ አስቀዳሽ አንገቱን በአራቱም አቅጣጫ አዞረ፡፡ የቴሌውን ሰው ከሩቁ አየው፡፡ ክበቡን ጥሶ መሄድ ስለከበደው ሞባይሉን አወጣና በማዶ ለሚያየው የቴሌ ሹም ደወለ፡፡ ‹‹የደወሉላቸው ደንበኛ ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጭ ናቸው›› ስትለው ደንግጦ ዘጋው፡፡ እንግዶቹ በእንግሊዝኛ የምትለውን ቢሰሙ ጭራሽ ያብዳሉ ብሎ ፈራ፡፡ ‹‹ይኼ ታላቅ ስብሰባ የሚደረግበት አዳራሽ ራሱ ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጭ ነው ማለት ነው›› አለና አፈረ፡፡ ታድያ የቱ ነው ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውስጥ የሆነው? ለመሆኑ ይኼ ቴሌ የመሠረታቸው ‹የአገልግሎት ክልል› እና ‹ከአገልግሎት መስጫ ውጭ የሆነ ክልል› በሕገ መንግሥቱ ዕውቅና ያገኙ ክልሎች ናቸው?ቴሌስ የራሱን ክልል መመሥረት ይችላል እንዴ? ስንት ባልና ሚስት ‹የት ሄደህ ነበር፣ የት ሄደሽ ነበር› እየተባባለ የተጣላው ያቺ የቴሌ ሴትዮ ‹‹ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጭ ናቸው›› እያለች የሌለ ነገር አውርታ አይደል እንዴ?

አስተናጋጁ ይቅርታ ጠየቀና የቴሌውን ሹም ሊጣራ ሄደ፡፡ ‹‹እርሱ የቴሌ ባለሞያ ነው፤ ጠይቁት›› ብሎ ሹልክ ብሎ  ከክበቡ ወጣ፡፡ ወደ መድረኩ ሲያቀና ‹‹እንኳን እኔ አለቆቹ የማያውቁትን ጥያቄ ያዘንቡብኛል እንዴ›› ወደ መድረኩ ሲወጣ የቴሌውን ሹም የከበቡት እንግዶች የላምበረትን አውቶቡስ ተራ ጠሪዎች የመሰለ መዓት ድምጽ ሲያወርዱበት ሰማ፡፡ ‹‹ቻለው እንግዲህ፤ ኔት ወርኩ ያልቻለውን እናንተ ቻሉት›› አለ በልቡ፡፡

‹‹እንዴት ትናንትና የገዛነው ስልክ እስከ ዛሬ አይሠራም፤ የተሳሳተ ሲም ካርድ ነው የሰጣችሁን፤ አታላችሁናል፤ ገንዘባችንን መልሱ›› እንደ ሲሚንቶ አቡኪ ከየማዕዘኑ እንደ አሸዋ የበዛ ጥያቄ ጣሉበት፡፡ ፈገግ ለማለት ሞከረ፡፡ ፈረንጅ ፈገግታ ይወዳል የሚባለው ትዝ ብሎት፡፡ ‹‹ችግራችሁ ይገባኛል፡፡ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ አገልግሎቱን እንድታገኙ እናደርጋለን፤ ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እንጠይቃለን›› ሲል አሁኑኑ መፍትሔ አምጣ የሚል ወጣሪ ገጠመው፡፡ የሚያደርገውን ሲያጣ ስልኩን አወጣና ‹‹አንዴ ኃላፊውን ላናግረው›› አለና ደወለ፡፡ ‹‹የደወሉት ቁጥር የተሳሳተ ነው›› ስትለው እንግዶቹ እንግሊዝኛውን እንዳይሰሙ ሰግቶ እዘጋለሁ ሲል ጭራሽ ድምጽ ማጉያውን ከፈተውና አሰማቸው፡፡ ሰሚዎቹ ጎል እንደገባበት ስታዲዮም አንድ ላይ ጮኹ፡፡

እያመመው ፈገግ አለና ‹‹ሶሪ›› ብሎ ቀና ሲል የስብሰባው መጀመር ገላገለው፡፡ እንግዶቹ ወደመቀመጫቸው ሲያመሩ እርሱም አንገቱን ደፍቶ ወደ ቢሮው ገባ፡፡ ‹‹ምን ዓይነት መከራ ነው፡፡ ባለፈው ጊዜ ከስድስት መቶ ቦታዎች ስድሳውን ሠርተን ጨርሰናል ተብሎ ተነገረ፤ ሰውም ‹ጤፍ እየዘራን ነውና ራብህን ቻለው ማለት ነው› ብሎ ተረተብን፡፡ አሁን ደግሞ ምን ሊባል ነው፡፡ ያ የመሥመር ስልክ ይሻለን ነበር፡፡ በሞባይል የተላከ ቴክስትና በፖስታ የተላከ መልእክት እኩል እየደረሱ ቴሌ ምን ያደርጋል?

ስልኩን አነሣና ወደ ዋናው ቢሮ ደወለ፡፡

‹‹ኧረ ሰው ሊበላን ነው አንድ ነገር ይደረግ›› አለ በማዶ ላለው ሰውዬ፡፡

‹‹ገና ምኑን አይተህ ከዘጠና ሺ በላይ የሆኑ ደንበኞች ያወጡት ሲም ካርድ ሊሠራላቸው አልቻለም፡፡ ሲስተሙ ተበላሽቷል››

‹‹ታድያ መፍትሔው ምንድን ነው?››

‹‹እኛም አለቆቻችንን ስንጠይቅ ‹በቃ ታገሡ በሏቸው› ነው ያሉን››

‹‹እነዚህኮ ነገ ተሰብስበው ወደ ሀገራቸው ይሄዳሉ››

‹‹አገራቸው ከገቡ በኋላ በአድራሻቸው እንልክላቸዋለን›› ሣቀ፡፡

‹‹ታድያ ለምን ሸጥንላቸው››

‹‹እና ኢትዮጵያ የሞባይል ሲም አትሸጥም ይባል? ይኼማ ለገጽታችን ጥሩ አይደለም››

‹‹የኢትዮጵያ ሞባይል አይሠራም መባሉስ ገጽታ ይገነባል?››

ስልኩ ተዘጋ፡፡

የጉባኤው የመጀመሪያ ክፍል አብቅቶ እንግዶቹ የሻሂ ግብዣ ላይ ናቸው፡፡ መድረክ አካባቢ የነበሩት ባለ ሥልጣናትም ወደ እንግዶቹ መጥተው አብረው ሻሂ መጠጣት ጀመሩ፡፡ ሁለት ባለ ሥልጣናት ክብ ሠርተው ወደሚገኙ እንግዶች መጡና ተቀላቀሉ፡፡ ሁለቱም ራሳቸውን አስተዋወቁ፡፡ አንደኛው የቴሌ ዋናው ሰው ነበሩ፡፡ ‹የሰው ሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል› እንዲል መጽሐፍ ሁሉም ዓይናቸውን በእርሳቸው ላይ ተከሉ፡፡ ሁሉም ቅሬታውን አዘነበ፡፡ ባለ ሥልጣኑም ራሳቸውን እየነቀነቁ ሰሙና ስልካቸውን አወጡ፡፡ ደወሉ፡፡

‹‹ቴሌፎኑ ለጊዜው ጥሪ አይቀበልም፣ ወይም ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጭ ነው›› ሲል ሰሙት፡፡ እንደገና ወደ ሥራ አስኪያጁ ሞከሩ ‹‹የደወሉት ቁጥር አገልግሎት ላይ ያልዋለ ነው፡፡›› የቴሌው ሥራ አስኪያጅ ቁጥር እንዴት አገልግሎት ላይ አልዋለም፤ እነዚህ ሰዎች ጠንቋይ ይመስል ለረሳቸው አያውቁም እንዴ›› ብለው ፈገግ አሉና ለመጨረሻ ጊዜ ሌላ ኃላፊ ጋ ደወሉ ‹‹ይህንን ጥሪ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ሂሳብ የለዎትም›› ስትል ደነገጡና ‹‹ዋት፣ ይኼኮ ካርድ የሚሞላበት ስልክ አይደለም፤ ምን ማለቷ ነው›› የከበቧቸው ሰዎች የሚሉት ነገር አልገባቸውም፡፡

‹‹የሚመለከታቸውን ላናግር ነበር፤ የኔም ስልክ ግን እንደናንተው አይሠራም፤ ከመታገሥ በቀር ሌላ አማራጭ የለንም›› አሉ፡፡

‹‹እስከ መቼ ነው ግን የምንታገሠው? ስብሰባውኮ ነገ ያልቃል››

‹‹ልክ ናችሁ ብዙ ስብሰባዎችም እንዲሁ በትዕግሥታችን ነው ያጠናነቅናቸው››

‹‹ታግሠን ግን ምን ይገኛል››

‹‹ስብሰባው ያልቅና አገራችሁ ትገባላችሁ፤ ያን ጊዜ ሲም ካርድ ለምን አልሠራም? ማለት ታቆማላችሁ፤ ጥያቄውን መመለስ ካልተቻለ ሌላው አማራጭ ጥያቄውን እንዳይጠየቅ ማድረግ ነው››

ምሽት ላይ ስብሰባው ሲያልቅ መሬቱን የሞላው የተወረወረ ሲም ካርድ ነው፡፡ ለጽዳት ሠራተኞች ግን ሠርግና ምላሽ ሆኖላቸዋል፡፡

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ብሔራዊ ምክር ቤት በትላንትናው ዕለት ተሰብስቦ በመኢአድና አንድነት እንዲሁም በዲሲፕሊን ኮሚቴ መመሪያ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ አንድነት ፓርቲና መኢአድ በተፈራረሙት ቅድመ ውህደት መሰረት የጉባኤ ጠሪ አብይ ኮሚቴ አዋቅሯል፡፡ በዚህም መሰረት ጉባኤው ጠሪው 7 አባላት ሲኖሩት ከ 7ቱ አባላት 5ቱ የሁለቱን ጉባኤ ለማመቻቸት የተሰየሙ ናቸው፡፡ እንዲሁም በፓርቲው የዲሲፕሊን ኮሚቴ መመሪያ […]

ሰኔ 1 ቀን 1997ዓ.ም፤ በአዲስ ከተማ ት/ቤት የተጀመረው ተማሪዎችንና ንጹሃን ዜጐችን በግፍ የመግደል እርምጃ ተከትሎ አብዛኛው ባለስልጣናት ልጆቻቸውን ከየት/ቤቱ በአጃቢ ያስወጡ ነበር። ወደ ካቴድራል ት/ቤት በሁለት ኮብራ ተጭነው የተላኩ 20 ልዩ የፌዴራል ፖሊሶች የጄ/ል ሰአረና የጄ/ል ብርሃነ (ወዲ መድህን) ሴት ልጆችን አጅበው ሄዱ። ሁለቱ ሴት ልጆች በማግስቱ አሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ ተመቶላቸው ዓርብ ሰኔ 3 ቀን […]

የእስከመቼ አዘጋጅ፤ ሰኔ ፯ ቀን ፳፻ ፮ ዓመተ ምህረት በአሁኑ ሰዓት በአብዛኛዎቹ ኢትዮጵያዊ የዜና መለዋወጫ መስኮች፤ “ትግሬዎች በዚህ መንግሥት ተጠቅመዋል? ወይንስ አልተጠቀሙም?” የሚለው ጉዳይ ዓይነታ መወያያ ሆኖ፤ መድረኮቹን ሁሉ አጣቦ ይዟል። በመጀመሪያ ደረጃ፤ አንድን ጉዳይ ኢትዮጵያዊ ታጋዮች ሲያነሱ፤ ከትግሉ ዋና ግብ አንጻር ነው። እንዲያው ለወግ ያህል ወይንም ቁጭትን ለመዘርገፍ የሚደረግ ውይይት፤ የታጋዮችን ቀልብ አይስብም። ይኼ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ባለፈዉ እሁድ አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ በአጭሩ አንድነት፤ እንዲሁም የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት በምህጻሩ መኢአድ ለዉህድት የሚያበቃቸዉን ቅድመ ዉህደት ስምንነት ተፈራርመዋል።

“‹‹የታሰራችሁ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖች የእኔ ጀግኖች ናችሁ። አከብራችኋላሁ።›› ብለህ ንገርልኝ አለኝ – ደጋግሞ።…” ከትናንት በስትያ ሰኔ 03 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ከቅርብ ጓደኛዬ እና የሙያ ባልደረባዬ ጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ ጋር ወደቃሊቲ ማረሚያ ቤት [እስር ቤትም ነው] አምርተን ነበር- ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆኑትን አቶ አንዷለም አራጌን ለመጠየቅ። የተለመደውን የፖሊስ ፍተሻ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ናይጀሪያን የጎበኙት የጀርመን የልማት ሚንስትር ጌርድ ሚውለር ባለፈው ሚያዝያ በሰሜናዊ ናይጀሪያ በቺቦክ መንደር በፅንፈኛው የሙ/ስሊም አክራሪ ቡድን የቦኮ ሀራም የታገቱትን ወደ 300 የሚጠጉ ልጃገረድ ተማሪዎችን

አንዷን ቅዳሜ በፍርድ ቤት
በዛሬው ችሎት ፖሊስ የሃያ ስምንት ቀን የምርምራ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቀደለት

ጽዮን ግርማ

ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፉ ብርሃነ Journalist Tesfalem Weldeyes, Zelalem Kibret, journalist Asmamaw H/ghiorgis, journalist Edom Kassaye, Natnael Feleke and Atnaf Berhane

ለአብዛኛው ወጣት አዲስ አበባ ላይ ”ቅዳሜ” ትርጉም አላት። የሣምንቱን የሥራ ቀናት በየፈርጁ ያሳለፈው ኹሉም ወጣት ”ቅዳሜ”ን ደግሞ እንደየምድቡ ይውልባታል። እንደሰማኹት ከኾነ ለዞን ዘጠኝ አባላትና ጓደኞቻቸውም ቅዳሜ ልዩ ቀን ናት። ለወጣቶቹ አብሮነት የጡመራ መድረኩ ቢያግዛቸውም ከዛ በላይ ግን ጓደኝነታቸው ቤተሰባዊነትን ፈጥሮላቸው አብዛኛውን ቅዳሜ እንደየቅርበታቸው አብረው ያሳልፋሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተክለሃይማኖት አካባቢ የሚገኙ የንግድ ሱቆች ብቻ ተለይተው ሊፈርሱ መሆኑን በአካባው ሚገኙ ነጋዴዎች ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡ ነጋዴዎቹ እንደሚሉት ከተክለ ሃይማኖት ጀምሮ እስከ ጥቁር አንበሳ የሚገኙ የመኪና ዕቃ መለዋወጫ፣ የጎማ መሸጫ እና ሌሎች የንግድ ሱቆች በአምስት ቀናት ውስጥ እንዲፈርሱ በመንግስት ተወስኗል፡፡ ከንግድ ቤቶቹ በስተጀርባ የሚገኙ የቀበሌ ቤቶች አብረው የማይፈርሱ መሆኑን የሚናገሩት ነጋዴዎቹ “እኛ ግብር ከፋዮች ሆነን ከሌላው […]

ሰኞ ግንቦት 18 ቀን 2006 ዓ.ም ማታ ራት ከበላ በኋላ ከዩኒቨርስቲ ግቢ ባልታወቁ ኃይሎች ታፍኖ የተወሰደው ወጣት መልካሙ አምባቸው ያለበት ሳይታወቅ ቀናቶች ማለፋቸው ያሳሰበው አንድነት ፓርቲ በየፖሊስ ጣቢያው ፍለጋውን ቢያጠናክርም ሊያገኘው ባለመቻሉ ግንቦት 29 ቀን 2006 ዓ.ም ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንት ጽ/ቤት በግልባጭ፡ – ለትምህርት ሚኒስቴር – ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚ ፋኩልቲ – ለአ/አ […]

የዞንዘጠኝ ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ ላይ ተጨማሪ 28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠ! 

ዛሬ አራዳ “ፍርድ ቤት” አንደኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት
ናትናኤል ፈለቀ
አጥናፍ ብርሃኔ
ዘላለም ክብረት
እንዲሁም
ጋዜጠኞቹ
ኤዶም ካሳየ
ተስፋዓለም ወልደየስ
አስማማው ሀይለጊዮርጊስ ላይ ተጨማሪ 28 “የምርመራ ቀናት” ሲፈቀድ ፣ ፍርድ ቤቱ የፍትህ ስርአቱ መፋጠን እንዳለበት እና ከዚህ በሁዋላ የፓሊስን ምክንያቶች እንደማይቀበል አስጠንቅቋልም ተብሏል። ሁሉም ታሳሪዎች በጥሩ መንፈስ ላይ እንደሆኑ በቦታው የነበሩ ወዳጆቻችን አስተውለዋል።

ማስታወሻ
የጦማርያኖቹ እና የጋዜጠኞች እስር ፓለቲካዊ መሆኑን እና ምንም ወንጀል አለመስራታቸውን እያስታወስን ዛሬ ፍርድ ቤት ለተገኙ ከ300 በላይ ለሚሆኑ የዞን ዘጠኝ ወዳጆች ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርባለን። 

#FreeZone9Bloggers #FreeEdom #FreeTesfalem #FreeAsemamaw #Ethiopia

(ሊያነቡት የሚገባ)

ከጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ (አዲስ አበባ)

ከትናንት በስትያ ሰኔ 03 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ከቅርብ ጓደኛዬ እና የሙያ ባልደረባዬ ጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ ጋር ወደቃሊቲ ማረሚያ ቤት [እስር ቤትም ነው] አምርተን ነበር- ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆኑትን አቶ አንዷለም አራጌን ለመጠየቅ። የተለመደውን የፖሊስ ፍተሻ አልፈን ወደ ውስጥ ስንዘልቅ የሰማያዊ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፈ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ፣ አቶ ሳሙኤል የተባሉ አባልና የ‹‹ነገረ ኢትዮጵያ›› ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው እስክንድርን ሊጠይቁ ቀድመውን ደርሰው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጸጋዬገ ብረመድኅን አርአያ

እንደ ልጄ የምቆጥረውና ከበኩር ልጄ ከዩሐንስ ጋር ያደገው ሳምሶን በሕክምና ኮሌጅ ይማር በነበረበት ዘመን በምሽቱ ሰዓት ላይ የ‹‹ፈገግታ ጊዜ›› በምንለው ግማሽ ሰዓት ያጫውተን ነበር፡፡ አዎን ሕይወት ውጥርጥር ባለበትና ጭንቀት ከቀበሌ ከሚወረወር ቀስት፣ ጭንቀት ከየካድሬውና ከየፖለቲካው ኅቡዕ ድርጅት ከሚወረወር ሌላ ቀስት፣ ጭንቀት፣ ከመስሪያ ቤት ጭንቀት፣ ከበላይ አካል ጭንቀት፣ ከበታች አካል ጭንቀት፣ ጭንቀት —- አንድ የድሮ ማስታወቂያ ሚኒስትር እንዳሉት ከላይ ከመሳፍንቱና ከመኳንንቱ በሚለቀቅብህ እሳት፣ ከታች ከሕዝቡና ከሠራተኛው ከሚነድድብህ እሳት የገና ዳቦ ትሆናለህ፡፡ ስለዚህ ‹‹በታይም አውት›› (ፋታ ልበለው) መልክ ከሳሚዬ ጋር የማደርገው የግማሽ ሰዓት ውይይት (ጨዋታ) ለእኔ “ማሳጅ” ነበር፡፡ መታሻ!

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይህን ፅሁፍ በሎሚ መፅሄት ላይ ባለፈው ሳምንት አወጣሁት፡፡ መፅሄቱ ላልደረሳችሁ ይኸው እዚህ ለጠፍኩት፡፡ በቅድሚያ እንኳን ወታደራዊ አምባገነኖች ተደምስሰው ‹‹ዴሞክራሲያዊ›› አምባገነኖች ለተተኩበት የግምቦት 20 በአል አደረሳችሁ፡፡ ዛሬ ዝምታ ሲበዛ ፍርሀት፣ ውሸት ደግሞ ሲደጋገም እውነት ይሆናልና የማውቀውንና የተሰማኝን ለአምባቢም ግልፅ ሊሆንለት የሚገባ ጉዳይን በወፍ በረር ላስቃኝ ወደድኩ፡፡ ለፅሁፌ መነሻ የሆነኝ ሎሚ መፅሄት አቤል ኤፍሬም በተባለ ግለሰብ የቀረበውንና […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በኢትዮጵያ ጥንታዊና ዘመናዊ የትምሕርት አሠጣጥ ሥርዓት እና በትምሕርት ጥራት ላይ ያተኮረ ዉይይት ሰሞኑን አዲስ አበባ ዉስጥ ተደርጓል።አዉደ-ኢትዮጵያ የተሠኘዉ የኢትዮጵያዉያን ምሑራን ማሕበር ባዘጋጀዉ ዉይይት ላይ ሥለ ትምሕርት አሰጣጥ ጥናት ያደረጉ ምሑራንና መምሕራን ተካፋዮች ነበሩ።