ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ዛሬ በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለ አሸባሪ ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎችን በፖለቲካ አመለካከታቸው፣ መንግስት በመተቸታቸው በግልጽ በመጻፋቸውና በአደባባይ በመናገራቸው ከዚህም አልፎ በጥርጣሬ በተለይም በብሄረሰብ ማንነታቸው እያሳደደ የሚያፍን የሚያሰቃይና የሚገል የሽብር ተቋም ካለ ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ መሬት ላይ ሰላማዊ ዜጎችን ኢላማ ያደረገ የተቃውሞ ሃይል በተግባርም ሆነ በአስተሳሰብ ከወያኔ ውጪ አንዳች ሃይል የለም።

አፋኙ የወያኔ ስርአት በተለየም የህዝቡን ሀብትና ንብረት እየዘረፉ የሚቀማጠሉት የህወሃት መሪዎችና ሎሌዎቻቸው የተቃውሞ ድምጽ በሰሙ ቁጥር እንደሚሸበሩና እንቅልፍ አጥተው እንደሚያድሩ ይታወቃል። አፍነውና ዘርፈው ገለው የሚገዙት ህዝብ ግፍ በዛብኝ ብሎ በተናገረ ቁጥር የሚሸበሩት እነሱ ብቻ እንጂ ህዝቡ አይደለም።
በኢትዮጵያ ምድር ያለው አሸባሪ ወያኔ ብቻ መሆኑን ሺ ምሳሌዎችን ጠቅሶ ማስረዳት ይቻላል። ሶስት አመት ሙሉ የሰላም እጃቸውን እየዘረጉ ከልመና ባልተለየ ሁኔታ መብታቸውን የጠየቁና ድምጻችን ይሰማ ያሉት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማንንም ዜጋ አላሸበሩም። የተገላቢጦሽ እነሱ አሸባሪ ተብለው የግፍ ሰቆቃ ይፈጸምባቸዋል።

ጋዜጠኞችና ጦማሪዎቹ መንግስት ያወጣውን ህግ እንዲያከብር ስለጠየቁ በአደባባይ ስለጻፉ ግፍ ይፈጸምባቸዋል። እነሱ ያሸበሩት ሀገርና ህዝብ የለም። ከመንገድ ላይ ጎትተው እንደ እባብ ቀጥቅጠውና ፈነካክተው በማግስቱ ፍርድ ቤት ያቀረቧት ወየንሸት ሞላ የተባለች ባለ ተስፋ ወጣት የወያኔ አረመኔዎች በሙስሊሙ ህዝብ ላይ የሚሰሩትን ጭፍጨፋ እግር ጥሏት ከማየትና ከመታዘብ ውጪ ያሸበረችው ሰው፣ ሀገር የለም። በየወህኒ ቤቱ እና አፈና ጣቢያው ታስረው የሚቀጠቀጡት የኦሮሞ ልጆች ለጥያቄያቸው መልስ ሲጠብቁ ከመጨፍጨፍ ያለፈ የፈጸሙት እብሪት የለም። በየክልሉ ቀና ብለህ ባለስልጣን ተናገርክ፣ ጥያቄ ጠየቅክ፣ ባለስልጣን ደፈርክ፣ ተሰብስበህ አየንህ ወዘተ እየተባለ የሚገረፈው እንደ እንስሳ እየተገደለ የሚጣለው ገበሬ የሰራው ወንጀል የለም። አሸባሪም አይደለም! በየቦታው ቦንብ እየቀበረ አፈንድቶ ንጹሃንን ገድሎ ሊያፈነዱ ሲሉ ፈንድቶባቸው ራሳቸውን ገደሉ ብሎ በአደባባይ የሚሳለቀው አሸባሪው ህወሃት እንጂ ንጹሃኑ አይደለም።

የኛ መሪ አንዳርጋቸው ከልጅነት እድሜው ጀምሮ ራሱን ለህዝብ ነጻነት የሰጠ አርበኛ እንጂ አሸባሪ አይደለም። በተመሳሳይ ውንብድና ከጎረቤት ሀገር ድረስ በአለም አቀፍ የወረበሎች ውንብድና መንገድ ወያኔ እያፈነ የገደላቸው አሮሞዎችና፣ ሱማሌዎች፣ አኙዋኮች፣ አማሮችና ሌሎችም ነጻነት ከመፈለግ ውጪ ያሸበሩት ህዝብና ሀገር የለም።
በኢትዮጵያ ምድር የነጻነት ድምጽና ኮሽታ በሰማ ቁጥር የሚሸበረው ህወሃትና በለሟሎች ብቻ ናቸው። ይህ የነጻነት ድምጽ ደግሞ እየጎላ መሄዱ የማይቀር ነውና ወያኔ ሰፈር ሽብር ይሆናል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ወጣት፣ ሴት፣ ሽማግሌ፣ ገበሬ እና በየቦታው ያላችሁ የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ! አሸባሪህ ወያኔና ወያኔ ብቻ መሆኑን አውቀህ በገዛ ሀገርህ ላይ ነጻነት በተመኘህና በጠየቅህ ጊዜ ሁሉ ለሽብር ጥቃቱ ኢላማ ያደረጉህን ወያኔ ተባብረን ከላያችን ለማውረድ ተነስ! በያለህበት እምቢ በል! ለወያኔ የሚጠቅም የመሰለህን ነገር ሁሉ አታድርግ! አትተባበር! ሸቀጣቸውን አትግዛ! ወያኔዎችን ከማህበራዊ ሂወትህ አግል! የቻልክ ሁሉ ደግሞ የነጻነት አርበኞችን ዛሬ ነገ ሳትል አሁን ተቀላቀል!!! ነጻነታችን ያለው በእጃችን ላይ መሆኑን አትዘንጋ። ግንቦት 7 ሁልጊዜም ከመቼውም ጠንክሮ ከጎንህ ነው።

የወያኔን ሽብር በተባበረ ሃይል እናቁመው!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
ግንቦት7

የትግራይ ስብስቡ በጂጁ ሆቴል እቅዳቸው የህወሓትና የደህንነት ሰዎች ባሉበት ኣውጥተዋል ::
ሕወሓት በትግራይ ከዚህ ቀደም በሚደረጉ ምርጫዎች ካለምንም ተወዳዳሪ በብቸኝነት ተወዳዳሪ ሲመጣ ደሞ ስም በማጥፋት እና በጉልበት በመደቆስ በብቸኝነት ምርጫዎችን እያሸነፈ ላለፉት 23 አመታት ዘልቋል። ካለፉት 6 አመታት በኋላ አረና ትግርያ ብሎ የሚጠራ ተቀናቃኝ የፖለቲካ ፓርቲ ተመስርቶ በትግራይ ውስጥ እንቅስቃሴውን እያስፋፋ ባለበት ሰአት በመጭው ምርጫ እሸነፋለሁ ሕዝቡ በድምጹ ይጥለኛል የሚል ከባድ ስጋት ስላለበት ከአረና ፓርቲ ጋር ይመሳሰላልኛል ያለውን ተለጣፊ ፓርቲ ለመመስረን እንቅስቃሴ መጀመሩን ታውቋል።

http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … -post.html

የማለዳ ወግ … ጥሩ ምግባር ሁሌም ያስመሰግናል ! * አይታክቴውን የመረጃ ምንጩን ፣ ጋዜጠኛውንና ድምጻዊዋንም ላመስግን ! ለእኔ ለፈጣሪ በታች በጎ ለሚሰሩ የሰው ዘሮች በሙሉ የሚሰጥ ምስጋና ቃል ይስበኛል። ብዙ ጊዜ የመልካምና የበጎ ምግባር ፋና ወጊዎች ስራ ተመልክቸና መስጦኝ ለቀሪው አርአያ ፣ ለወደፊቱ ብሩህ ተስፋ ምንጭ ነው ብየ ካሰብኩና ካመንኩበት የምስክርነት ቃሌን የምሰጠው ምስጋና በማቅረብ […]

የአሜሪካዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒሰትር ሚስተር ጆን ኬሪ በቅርቡ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸዉ የሚታወስ ነዉ፡፡ በዚህ ጉብኝታቸዉ ወቅትም በኢትዮጵያ እየደረሰ ባለዉ የሰባዊ መብት ጥሰት ላይ ብዙም ሳይሉና የተቀዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን በሁኔታዉ ላይ ሳያነጋግሩ በመሔዳቸዉ ብዙዎችን ሳያሳዝን አልቀረም፡፡ በእርግጥ የእርሳቸዉ አመጣጥ በእርስ በእረስ ጦርነት በመታወክ ላይ ያለችዉን የደቡብ ሱዳን ችግር በመፍታት ላይ ያተኮረ ቢሆንም ቅሉ የኢትዮጵያዉያንን ችግርም ሳይቃጠል […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለአፍሪቃ እድገት እና ብልፅግና ትልቅ ሚና ይጫወታሉ ያሏቸውን ከተለያዩ የአፍሪቃ ሀገራት የተውጣጡ 500 ወጣት አፍሪቃውያንን ዘንድሮ ወደ ሀገራቸው ጋብዘው ነበር።

ምዕራብ አፍሪቃ ዉስጥ የኤቦላ ተሕዋሲ የገደላቸዉ ሰዎች ቁጥር ከሰባት መቶ ልቋል። በተጠቀሰዉ አካባቢ በተሕዋሲዉ ክፉኛ የተጎዱት ሃገራት የኤቦላ ወረርሽኝን ለመቋቋም ጠንካራና አዲስ መመሪያዎችን ተግባራዊ ማድረግ ጀምረዋል።

የደቡብ ሱዳን መንግስትና አማፂያን አቋርጠዉት የነበረዉን የሰላም ንግግር የፊታችን ሳምንት እንደሚጀምሩ አደራዳሪዎች አስታዉቀዋል። የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት ማለትም IGAD አደራዳሪዎች ዛሬ እንደገለጹት በያዝነዉ ሳምንት ይጀመራል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረዉ የሁለቱ ወገኖች የሰላም ንግግር የፊታችን ሰኞ ይጀመራል።

ጉዳዩ፥ ከአንድነት ፓርቲ ሶስቱ ፕሬዘዳንታዊ እጩዎች የተሰጠ የጋራ መግለጫ ውድ ወገኖች፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትሕ ፓርቲ በዴሞክራሲ ሂደትና ባህል አጥብቆ ያምናል። በአጭር እድሜው ፓርቲው አባላቶቹ በነጻነት የአሳብ ፍጭት አድርገው አሳባቸውን እንዲገልጹ በማድረግ ሶስት ፕረዚዳንቶችን ግልጽና ተጠያቂነት በተሞላበት ሁኔታ መርጧል። ፓርቲያችን መሪዎቹን የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ ባህሉን ይጠብቃል። የፓርቲያችን አባላቶችና ደጋፊዎች የዚህ ባህል ደጋፊ ብቻ ሳይሆኑ ሐዋሪያትም እንዲሆኑ […]

የአንድነት ቦስተን ድጋፍ ድርጅት፣ ለአመታት አገር ቤት የሚደረገዉን ሰላማዊ ትግል የሚደግፍ ድርጅት እንደ መሆኑ፣ በቅርቡ በአንድነትና በመኢአድ የሚደረገዉን የዉህደት እንቅስቃሴ በደስታና በጉጉት እየተከታተለው ነው። የአመራር አባላትን ለመምረጥ የሚደረገዉ አስደሳች ዴሞክራሲያዊ ዉይይትና ቅስቀሳ ፣ አንድነት ምን ያህል የዲሞክራሲ ባህል እያዳበረ እንዳለ አመላካች ከመሆኑም በተጨማሪም ያኮራን ነገር ነው። የእጩ ፕሬዘዳንት ምርጫ ላይ ድምጽ የሚሰጡትና የሚወስኑት፣ አገር ቤት […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በጣም ወሳኝ የሆነ ስራ ሲሰራ ነበር፡፡ እሱም ውህደት ነው፡፡ የአንድነት/መኢአድ ውህደት ወሳኝና መሰረታዊ ድርድሮችን አልፎ የቅድመ ውህደት ፊርማው ከተቀመጠም ከወር በላይ ሆነው፡፡ ከፊርማው በኋላ ውህደት አመቻች ኮሚቴ ተዋቅሮ በአጭር ጊዜ ነገሮችን መልክ ለማስያስ የቻለ ሲሆን ውህደቱም የሁለቱ መስራች የጉባዔ አባላት በተገኙበት ነሐሴ 3 እና 4 ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ታዲያ […]

በቀላሉ ሊሰሩ ከሚችሉ የሙዚቃ መሣሪያዎች አንዱ ዋሽንት ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ በገጠሩ አካባቢ ሰዎች ገና ከልጅነታቸው ጀምሮ ነበር ከቀርቀሀ የተሰራች ዋሽንታቸውን ይዘው ሙዚቃ ሲጫወቱ የሚስተዋሉት።

የሐገሪቱን የሥልክና የኢንተርኔት አግልግሎት በብቸኝነት የሚቆጣጠረዉ ኢትዮ-ቴሌኮም በየጊዜዉ ለሚነሱት ወቀሳዎችና ለሚፈጠሩት ችግሮች ምክንያት የሚላቸዉን ቴክኒካዊ ሠበቦች መደርደሩ አልቀረም።ችግሩ ግን የመቃለል እዝማሚያ አልታየበትም።

የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ ለሰባተኛ የስልጣን ዘመን ዳግም ከተመረጡ ዛሬ አንድ ዓመት ደፈኑ ።አምና በአብላጫ ድምጽ ተመርጠው በፕሬዝዳንትነት የቀጠሉት ሙጋቤ አሁንም በዚምባብዌ ነጮች የመሬት ባለቤት እንዳይሆኑ በያዙት አቋም እንደፀኑ ነው።

የእስራኤል የጋዛ ድብደባ ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል ። እስራኤል ተጨማሪ ተጠባባቂ ጦር ወደ ጋዛ አዝምታለች ። የፍልስጤም ደፈጣ ተዋጊዎችም ወደ ደቡባዊ እስራኤል ሮኬቶችን መተኮሳቸውን ቀጥለዋል ። ስደተኞች በተጠለሉበት በጋዛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ትምሕርት ቤት ላይ የደረሰውን ጥቃት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና አሜሪካን አውግዘዋል ።

ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

በቅርቡ የኣሜሪካ ፌደራል ኣቪየሽን ኣስተዳደር(FAA) በዓለም ላይ ለበረራ ኣደገኛ የሆኑትን መስመሮች በካርታው ላይ ከቦ ኣስጠንቅቆ የነበረ ሲሆን በሪፖርቱ ላይ እንደሚታየው እነዚህን ኣደገኛ ቦታዎች በሁለት ከፍሏቸዋል። ኣንደኛው መስመር ኣደገኛነት ያለው ክልል (potentially hostile region) ሲሆን ሁለተኛው ክልል ግን በረራን ጨርሶ የከለከለ(Flight prohibited) ክልል ነው። ኣደገኛነት ኣላቸው ተብለው ኣብራሪዎች ከግምት እንዲያስገቡ የተመከሩባቸው ክልሎች ኬንያ፣ኣፍጋኒስታን፣ኢራን፣ሶሪያ፣ ማሊ፣የመን፣ ኮንጎና ግብጽ […]

«ኤዲያ፤ ሰማያዊ ፓርቲ ቤት የተነሳውን እሳት እንደምንም ብለን ስናደፋፍነው አሁን ደግሞ አንድነት ፓርቲ ቤት ሌላ እሳት ተነሳ ….እርስ በርስ እየተጠዛጠዙ ፌስቡክን አጨናነቁት እኮ፡፡ ምናለ ዙከምበርግ ልክ የውስጥ ስልክ መስመር ወይም የውስጥ ሚሞ እንዳለ ሁሉ ለውስጥ ጉዳይ ብቻ የሚሆን ሌላ የፌስቡክ አይነት ቢፈጥርላቸው» ይሄን የጻፉት ከበደ ካሳ የሚባሉ የአገዛዙ ካድሬ ናቸው። የመኢአድ እና የአንድነት ዉህድ ፓርቲ […]

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም

ለእኔ ፖሊቲካና የግለሰብ ጠባይ እንደውሃና ዘይት የማይደባለቁ ነገሮች ይመስሉኛል፤ አጼ ምኒልክ ‹‹አመልህን በጉያህ›› ያሉት ለዚህ ሳይሆን አይቀርም፤ ዘይትና ውሀ በባሕርያቸው የሚለዩትን ያህል ፖሊቲካና ግለሰብም የባሕርይ ልዩነት አላቸው ማለት ነው፤ የወያኔ መሪዎች ምንም ነገር የማይሰምርላቸው፣ ከመጀመሪያውኑ እነዚህን ሁለት የማይደባለቁ ባሕርዮች አደባልቀው በመንሣታቸው ነው፤ ፖሊቲካ ለማኅበረሰቡ መቆርቆር ነው፤ ለሕዝቡ መቆርቆር ነው፤ ለአገር መቆርቆር ነው፤ የፖሊቲካ መነሻም ይኸው መሆን አለበት፤ ዓላማውም የማኅበረሰቡ፣ የሕዝቡ ልማት እንጂ ጥፋት አይደለም፤ የነበረውንና ያለውን ማጥፋት የፖሊቲካ ዓላማ ሊሆን አይችልም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አቶ ግርማ ሰይፉ

የመንግሰትን ቀጣይ እርምጃ የሚያሳዩ ተከታታይነት ያላቸው በግል ሚዲያዎች ላይ የሚደረጉ ዘመቻው ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ መልክቶች እየታዩ ነው። በቀጣይ ለሚቀርበው ዶክመንተሪ ተጋባዥ አንግዳ ሆኜ ለቆርጦ ቀጥሉ ኢቲቪ ቃለ ምልልስ እንደሰጣቸው ጥያቄዎቹ ደረስውኝ ተመልክቸዋለሁ። የጥያቄዎቹን ዝርዝር እንተወው እና ዓላማው ግን ባለፈው ከቀረበው ዘጋቢ ፊልም የተለየ ነገር የለውም። በነገራችን ላይ ባለፈው የቀረበውም ዘጋቢ ፊልም ላይ እንድሳተፍ ተጠይቄ እንደማይሆን ገልጨላቸው ነበር። ውሳኔዬ ትክክል መሆኑን ዘጋቢ ፊልሙን ካየሁ በኋላ ገብቶኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በቅርቡ ከአንድነት ጋር ዉህደት ይመሰርታል ተብሎ የሚጠበቀዉ መኢአድ ፣ የዉህዱን ፓርቲ ለመምራት እጩ መሆን የሚፈልጉ የድርጅቱ አባላት፣ ስማቸዉን እንዲያቀርቡ፣ የመኢአድ የዉህደቱ አመቻች ጉባኤ አሳወቀ። ከቀረቡ እጩዎች መካከል መኢአድ በድርጅቱ ልማዳዊ በሆነው አሰራር መሰረት፣ የመኢአድ ጠቅላላ ጉባኤ፣ መኢአድን ወክሎ ለዉህዱ ፓርቲ ተወዳዳሪ የሚሆነውን አንድ እጩ ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል። በተመሳሳይ ሁኔታ በአንድነት ፓርቲ ዉስጥም እጩዎች መቅረባቸው ይታወቃል። […]

ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ፣ ጊዜያቸዉን ወስደው ፣ በአንድነት ዉስጥ እየታየ ያለዉን በሌሎች ድርጅቶች ያልተለመደ፣ ዲሞክራሲያዊ ፉክክርን በመቀላቀል፣ የድርሻቸዉን ለማበርከት በርካታ ጽሁፎችን አስነብበዉናል። ለዚህም ያለኝን ምስጋና እና አድናቆት መግለጽ እወዳለሁ። ከርሳቸው ጋር በግል የተለዋወጥናቸው ሐሳቦች እንደተጠበቁ ፣ በአደባባይ ፣ በፌስ ቡክ ላቀረቡልኝ አንዳንድ ጥያቄዎች ግን ፣ እኔም በአደባባይ መልስ ለመስጠት እሞክራለሁ። «ምርጫ በአንድነት ዉስጥ ፤ ለአቶ በላይ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የኢትዮጵያ እና የቻይና ግንኙነት ረዘም ያለ ዘመናትን ያስቆጠረ ነው። የሁለቱ ሃገራት ግንኙነት የበለጠ የተጠናከረው እና የዛሬ መልኩን የያዘው ግን ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ነው።

ባለፈዉ ዓመት ከሩሲያ ጋር የ326 ቢሊዮን ዩሮ የንግድ ልዉዉጥ ያደረጉት የአዉሮጳ ሐገራት በማዕቀቡ የወለፊንድ ዉጤት ባንድ ወይም በሌላ መንገድ መነካታቸዉ አይቀርም።ከዩናይትድ ስቴትስና ከቻይና ቀጥሎ ከሩሲያ ጋር ከፍተኛ የንግድ ልዉዉጥ ያላት ጀርመን ደግሞ ከሕብረቱ አባል ሐገራት ሁሉ ቀዳሚዋ ናት።

ለአፍሪቃ ሕብረት፤ ለአፍሪቃ ምጣኔ ሐብት ኮሚሽን ወዘተ እየተባለ በርካታ አፍሪቃዉን የሚመላለሱ፤ የሚስተናገዱባት ኢትዮጵያ እስካሁን የወሰደችዉ የጥንቃቄ እርማጃ ሥለመኖር-አለመኖሩ በይፋ የሰመነዉ የለም። ኬንያ ግን ወደ ሐገሯ በሚገቡ መንገደኞች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ጀምራለች።


አገራችን ኢትዮጵያ በጥሩ ልትጠራባቸው የምትችላቸው ጉዳዮች እንዳሉ ሆነው በድህነት በሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ በሙስና እና ሃሳብን ነጻነት በመግለጽ መብት የተለመዱ የምናፍርባቸው ጉዳዩች ሆነው መቀጠላቸው እሙን ነው፡፡ ሃሰብን በነጻነት መግለጽን አስመልክቶ ሶስት ወራትን ከፈጀ ምርመራ በኋላ በብዙ የፓሊስ ድብብቆሽ ሂደት የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ባለፈው አርብ ክስ መመስረቱም አብሮ ይታወሳል

ጓደኞቻችን ከታሰሩ ጊዜ ጀምሮ መንግሰት ያቀረበውን ውንጀላ አስመልክቶ በተለያየ ወቅት ሃሳባችንን ለመግለጽ አስበን ምናልባት የምንሰጠው ሃሳብ አሁንም በመንግሰት እጅ የሚገኙት ጓደኞቻችን ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽእኖ በመፍራት እነዲሁም ለመንግሰት እድሉን በመስጠት ኦፌሻል ክሱን እስክናይ ድረስ በጠቅላላ ሃሳቦች ላይ አስተያየት ከመስጠት ውጨ ብዙም ሳንል ቆይተናል፡፡ አሁን ግን ክሱ አንድ የዞን 9 ጦማሪን ጨምሮ በይፋ በመመስቱ እነዲሁም በክሱ ላይ ተጠቀሱት ክሶች አንዳቸውም እውነት ባለመሆናቸው ክሱን አስመልክቶ ዘርዘር ያለ ማብራሪያ መስጠት እነዳለብን ተሰምቶናል፡፡

  ክሱ በአጭሩ

በአስሩ ተከሳሾች ላይ የተጠቀሱት የክስ አይነቶች ሁለት ሲሆኑ አንዱ የሽብር ተግባርን ማቀድ ማሴር ማነሳሳትና መፈጸም ሲሆን (የጸረ ሽብር ህጉ አንቀጽ አራት) ሁለተኛው ህገ መንግሰታዊ ስርአቱን በሃይል መናድ( የወንጀለኛ መቅጫ ህጉ አንቀጽ 238) የሚሉ ናቸው ፡። ክሱ ላይ በፓርላማ በሽብተኝነት ላይ ከተፈረጁ ድርጅቶች ቀጥታ ትእዛዝ በመቀበል በህቡእ በመደራጀት የሽብር ተግባር ላይ መሰማራት እና የመሳሰሉት ክሶች በዝርዝር ቀርበዋል፡፡ ከሶቹ ሲጠቃለሉ

1. ከግንቦት ሰባት ጋር እና ከኦነግ ጋር ግንኙነት መፍጠር ትእዛዝ መቀበል

2. ስሙ ባልተጠቀሰ የህቡእ መደራጀት እና ስራ ክፍፍል መፍጠር
3. Security in a boxን ጨምሮ ስልጠና መውሰድ
4. አመጽ ቡድኖችን ማደራጀትና አመጽ ማነሳሳት  የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ከግንቦት ሰባት ጋር እና ከኦነግ ጋር ግንኙነት መፍጠር ትእዛዝ መቀበል
ከዚህ በፊትም እነደተናገርነው  ማንኛቸውም የዞን9 ጦማርያን በፓርላማ በሽብር ከተፈረጁ ወገኖች ጋር ምንም ግንኙነት የለንም፡፡  ብዙ  የዞን9 ነዋሪያንንም አንደሚረዱት አብዛኛዎቹ የዞን9 ጦማርያን እነዚህ አካላት ላይ በሚያደርጉት ከፍተኛ ትችት እየታወቁ ጉዳዩን ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር ለማያያዝ መሞከር ፣መንግስት የፈረጃቸውን ድርጅቶች እነደፈለገ ማንንም ሰው ለመክሰስ አንደሚጠቀምበት ከማሳየት ባለፈ ትርጉም የማይኖረው ነው፡፡ ለማጠቃለል ያህል ማንኛቸውም የዞን9 አባላት አገር ውስጥም ሆነ ውጪ አገር ያለ የፓለቲካ ደርጅት አባላት አይደሉም፡፡ ይህንን የሚያሳይ መረጃም መንግሰት ለማቅረብ አንደማይችልም አናውቃለን፡፡ ( የማስረጃ ዝርዝር ላይ ወደታች የምንመለስበት ይሆናል)
ስሙ ባልተጠቀሰ የህቡእ መደራጀት እና ስራ ክፍፍል መፍጠር
በክሱ ላይ ስሙ ያልተጠቀሰ የህቡእ ሽብር ድርጅት በመመስረት ተከሰናል፡፡ በመሰረቱ መንግስት ዞን9 የሚለውን ስም አንድም ቦታ በክሱ ላይ ለመጠቀም ያልፈለገው የጦማርያኑን ቡድን ይበልጥ ታዋቂ እነዳይሆን ለማድረግ አንደሆነ አንገምታለን፡፡ ይህ አስቂኝ ክስ አንድም ቦታ ላይ የዞን9 ስም ባያነሳም በደፈናው በህቡዕ መደራጀት ብሎ ከሶናል፡፡ በመሰረቱ መንግሰት እኛን ለማግኘት ምንም አይነት የደህንነት ስራ እነዳላስፈለገው አናውቃለን፣. ምክንያቱም ሁሉም የዞን ፱ ጦማርያን ስማቸውና ፎቶአቸውን ማስቀመጣቸው ቋሚ የምንስማማበት እሴት ስለነበር ነው፡፡ የምንጽፈው ነገር በተናጠል ሃላፊነትን አንድንወስድ አንዲሁም ሌሎችን ሃሳብ መግለጽን ለማበረታታት በማሰብ በአደባባይ  እነዲታይ የወሰነውን የጦማርያንን ስብስብ ‹‹ህቡዕ›› ብሎ መጥራት ማንን ለማሞኘት አንደሆነ ግልጽ አይደለም፡፡ ዞን፱ ድብቅ እነዳልሆነ እያንዳንዱ ጽሁፍም በተናጠል ሃላፊነቱን የሚወስድ ጸሃፊ የቡድን ጽሁፎች ሲሆኑ ደሞ የቡድን ሃላፌነት አንደምወስድ ማንም የጦማራችን አንባቢ ያውቀዋል፡፡ መንግስት የዞን፱ አይነት ጦማሮችንም ሆኑ የአንተርኔት አንቅስቃሴዎቸን የሚመዘግብበት አሰራር አለመኖሩ ደሞ የእኛ ጥፋት ተብሎ ሊቆጠር አይችልም፡፡ተሰብስቦ መጦመርን የሚከለክል ምንም አይነት የህግ ክልከላም የለም፡፡ በመሆኑም ተሰብስበን መጻፋችን  ራሳችንን ገልጸን ሃሳባችንን መግለጻችን የጣስነው ምንም ሕግ የለም፡፡ፓሊስም ሆነ መንግሰት ሶስት ወር በፈጀ ምርመራው ህቡዕን ትርጉም ትርጉም በሚገባ አለማወቁም ጉዳዩን አስተዛዛቢ ባስ ሲልም መሳለቂያ ያደርገዋል፡።  
Security in a boxን ጨምሮ ስልጠና መውሰድ

Security in a box ኢንተርኔት ላይ የሚገኝ የኢንተርኔት አንቅስቃሴን በጥንቃቄ ለማድረግ የሚረዳ ኦፕን ሶርስ የስልጠና ማንዋል ሲሆን ይህንን ስልጠና መውሰድ በምንም መልኩ ወንጀል ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ የስልጠና ማንዋል ለማንኛውም የሰብአዊ መብትና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት የሚያሳስባቸው ሰዎች አንዲያገኙት ሆኖ የተዘጋጅ  ፍሮንት ላየን ዲፌንደርስ እና ታክቲካል ቴክ የተባሉ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማት ያዘጋጁት ስልጠና ነው፡፡ በመሰረቱ ይህንን ስልጠና ወንጀል አድርጎ ከማቅረብ በፊት ጎግል ላይ አስገብቶ መፈለግና ውጤቱን ማየት ከአንደዚህ አይነት አሳፋሪ ክስ ያድን ነበር፡፡ ይህ በበጎ መልኩ አንረዳው ካልን የፍትህ አካላቱ ከቴክኖሎጂ ጋር ያላቸውን ከፍተኛ ርቀት የሚያሳይና መንግሰትም በሰፊውና በቅንጅት ሊሰራበት የሚገባ ክፍተት ሲሆን ከዚያ ባለፈ ካየነው ደሞ መንግሰት እሱ የማያውቀውን ማንኛውንም ነገር ያለምንም የህግ ክልከላ  ወንጀል ብሎ ለመፈረጅ ያለውን ጉጉት ያሳያል ያ በራሱ ደሞ መንግስትን ራሱን ህገ ወጥ እነደሚያደርገው ያለምንም የህግ እውቀት ማሰብ ብቻ ለሚችል ሰው የሚገለጥ ሀቅ ነው፡፡
በዚህ አጋጣሚ ወንጀል ተብለው የተለያዩ ስልጠናዎች በሚል የተጠቀሱት የኮምኒኬሽን ስልጠና የስትራቴጂክ ስልጠና የአድቮኬሲ ስልጠና የመሳሰሉት መሆናቸውን ለመጥቀስ አንወዳለን፡፡ በመሰረቱ በተለያዩ ድርጅቶች ግብዣ ስልጠና መውሰድና የሰብአዊ መብት ፎረሞች ላይ መገኘትን ወንጀል የሚያደርግ ህግ አለመኖሩን መንቀሳቀስም የዜጎች ሰብአዊ መብት መሆኑን ለአቃቢ ህግ ህግና ፓሊስ ካላወቁ ማን ሊያውቅ ነው ??

የተደራጁት የአመጽ ቡድኖችን ማደራጀት  እና 48 ሺህ ብር ለአመጽ ማከፋፈል
መንግሰት የአመጽ ቡድኖችን ማደራጀት በሚል ያቀረበውን ክስ ለመመለስ ያህል አንድ ጥያቄ ብቻ አንጠይቃለን? የታሉ የተደራጁት ቡድኖች?  ምንም የተደራጀ ቡድን በሌለበት ይህንን ክስ ማቅረብ በፍትህ ስርአቱ ማፌዝ ካልሆነ በስተቀር ሌላ ምን ይባላል? በ48 ሺህ ብር የአመጽ ማነሳሳት ክሱን ከብሩ ማነስ በላይ ይበልጥ አስቂኝ የሚያደርገው የማስረጃው ዝርዝር ላይ ያለው ማስረጃ እና ክሱ የተለያዩ መሆናቸው ነው፡፡ ክሱ 48,000 ብር ከውጪ በመቀበል በማለት በደፈናው ላኪውን ሳይጠቅስ ያለፈው እና ለሽብር ተግባር የተባለው አርቲክል 19 ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ለታሰሩ ጋዜጠኞች ቤተሰቦች የሚደረግ ድጋፍ ሲሆን በወቅቱ ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ ባንክ ስለሚሰራ ተቀብሎ ለጋዜጠኛ ርዩት አለሙ ቤተሰቦች እስር ቤት መመላለሻ ተብሎ የተሰጠ ድጋፍ ነው፡፡
የተያያዘው የባንክ ደረሰኝም ያንን የሚያሳይ ሲሆን ክሱ ላይ በይፋ መጥቀስ ያልተፈለገው ለምን ይሆን? (ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹን መታሰር ተከትሎ መንግስት ፋይል የከፈተበትን ከሰብአዊ መብት ተቋማት ነን ከሚሉ ድርጅቶች የሃሳብና የገንዘብ ድጋፍ በመቀበል ሶሻል ሚዲያን በመጠቀም አመጽ ማነሳሳት የሚለውን ክስ ተከትሎ የተባበሩት መንግሰታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ ከአለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራ መስራት ወንጀል ሊሆን አይገባም በሚል ርእስ እስሩን የሚያወግዝ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል)

ማስረጃው ሲገመገም
እስካሁን በእጃችን የደረሰውን የማስረጃ ዝርዝር በሶሰት ከፍለን ማየት አንችላለን ፡፡ ከማስረጃ ዝርዝሩ ውስጥ አብዛኛውን ቦታ የሚይዘው በተለያየ ወቅት የተጻፉ የጦማርያኑ ጽሁፎች ሲሆኑ ጋዜጠኞቹ ላይ ደሞ ጭራሽ የመረጃ ዝርዝር ለማቅረብም አልተቻለም፡፡(አቃቤ ህግ የሁሉንም የበይነ መረብ ዘመቻዎች መግለጫ እና እቅድ እንደማስረጃ አቅርቧል)  በሁለተኛ ደረጃ የቀረቡት የተለያዩ የጉዞ ትኬቶች አለም አቀፍ ስብሰባ ማስታወሻዎች አንዲሁም ፕረዘንቴሽኖች  ሲሆኑ ሁሉም ጦማርያኑ ያደረጓቸው አለም አቀፍ ጉዞዎችን የሚያሳዩ የተሳተፉባቸው ሰብአዊ መብትና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት የተመለከቱ የአፍሪካ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ የተደረጉ ጉዞዎችን ናቸው፡፡

በማስረጃ ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት የሽብር ተግባር የተደረጉ ጉዞዎች ተብለው መሆኑ ይበልጥ ክሱን አሳፋሪ ያደርገዋል፡፡ መንግሰት ጉዞዎቹ የተደረጉትም ሆነ የስልጠና ግብዣዎቹ የመጡት ከአለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት አንደሆነ እያወቀና እና ማስረጃው ላይም በግልጽ እየታየ የሽብር ቡድኞች ብሎ ግንቦት ሰባትና ኦነግን ጣልቃ ማስገባቱ አስገራሚ ነው፡፡ (የፍርድ ሂደቱ ላይ እነዚህ ተቋማት ጋር የተደረጉ ግንኙነቶቸን አንዴት ብለው በፓርላማ ከተፈረጁ የሽብር ተቋማት ጋር እነደሚያገናኛቸው አብረን የምናየው ይሆናል)  በሶስተኛ ደረጃ የተቀመጡት ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ የተደረጉ የስልክ ልውውጦች ሲሆኑ በፍርድ ቤት ሂደቱ ውስጥ በዝርዝር የምናያቸው ይሆናል፡፡  በመጨረሻም ተከሳሽ ቤት ተገኘ የተባለውና ፓሊሶች ራሳቸው ያመጡት ከግንቦት ሰባት ጋር የተገናኙ ዶክመንቶች እና የአባላት መጽሄት ሲሆን በፍተሻው ወቅት ፓሊሶች ራሳቸው ፍሪጅ በስተጀርባ አገኘን ብለው በፍተሻ ወቅት ከፍተኛ አለመግባባት ተፈጥሮ የራሳቸውን ምስክሮች ብቻ አስፈርመው መሄዳቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

እንዲሁም ፓሊስ 18 የሰው ማስረጃ ለማሰማት የስም ዝርዝር ማስገባቱን እና የስም ዝርዝሩም እጃችን ላይ የሚገኝ ቢሆንም ከፍርድ ቤት ለሚመጣው የፍርድ ውጤት ሳይሆን በአጠቃላይ የፍትህ ስርአትን ማክበር ሃላፊነት ስላለብን ብቻ እዚህ ጽሁፍ ውስጥ ላለማካተት ወስነናል፡፡

እንደማጠቃለያ

የዞን፱ ጦማርያን ከዚህ በፊትም በተለያየ ወቅት አንደተናገርነው የመንግሰት ይህን ሁሉ ጊዜ ወስዶ ይዞ የመጣው ማስረጃ የአደባበይ ጽሁፎች እና በተለያየ ወቅት የተደረጉ የአደባባይ ሁነቶች( public events) ጥርቅም መሆኑ የክሱን ፓለቲካዊነት ያረጋገጠ ነው፡፡ ጦማርያኑ የፍርድ ቤት ስርአቱን የተለያዩ አለም አቀፍ የወንጀል ስነስርዓት ደረጃን በጠበቀ መልኩ ህጉን አክብረው የሚከታተሉ ሲሆን እኛም ሂደቱን በተቻለ መጠን ለዞን ፱ ነዋሪያን ለማሳየት ለማሳወቅ የምንጥር መሆኑን ለማሳወቅ አንወዳለን፡፡ በተደጋጋሚ ተፈትኖ የወደቀው የአገራችን ፍርድ ቤት እና የፍትህ ስርአት ገለልተኝነት ይህንን እድል በመጠቀም ራሱን ለማሻሻል መፍቀዱን እነዲያሳይና ፍርድ ቤቱ ማስረጃዎቹን አይቶ ክሱን እነዲዘጋ ጥሪ እያደረግን ይህንን በማድረግ የአገሪቱን የፍትህ ሂደት አንድ ደረጃ የማራመዱን እድል ዳኞች እንዲጠቀሙበት መንግስትን ከወራት በፌት የሰራውን ስህተት ለማስተካከል እድሉ ዛሬም ያልመሸ መሆኑን ለማስታወስ አንወዳለን፡፡

የታሰራችሁ ጦማርያንን እና ጋዜጠኛ ወዳጆቻችን ለከፈላችሁት መስዋእትነት ውለታችሁ አለብን፡፡ እንኮራባችኋለን!!  

ማስረጃ ተብለው የቀረቡ ሰነዶች ለፈገግታ ያህል

ዞን ዘጠኝ ላይ የታተሙ ጽሁፎች

  1. ነጻነትና ዳቦ – በናትናኤል ፈለቀ
  2. ሳንሱር ዋጋ ያስከፍላል – በናትናኤል ፈለቀ
  3. ስደትና ፍቅር – በሰለሞን አብርሃም(ከአውሮጳ)
  4. ዋኤል ጎኒሞ ኢትዮጵያዊ ቢሆን ኖሮ ….? – በበፍቃዱ ሃይሉ
  5. ልማታዊ ጋዜጠኝነት ወይስ ይሁንታን ማምረት? – በእንዳልካቸው ሃይለሚካኤል
  6. እኛና ሶማልያ – በናትናኤል ፈለቀ
  7. ድምፃችን ይሰማ – በእንዳልካቸው ሃይለሚካኤልና እና በፍቃዱ ሃይሉ
  8. እንዴት እንደመጥ – በማህሌት ፋንታሁን
  9. የመለስ ውርስ እና ራዕይ – በሶሊያና ሽመልስ
  10. የቅድመ ምርመራ ቅድመ ምርምራ – በማህሌት ፋንታሁን
  11. ትግራይና ሕዋሐት ምንና ምን ናቸው ? -በበፍቃዱ ሃይሉ
  12. ህግ ምርኩዝ ነው ዱላ በዘላለም ክብረት

ከበፍቃዱ ብሎግ(www.befeqe.com) የተገኙ

  1. ከ21 አመት በኋላ ዴሞክራሲ ሲሰላ
  2. ኢትዮጵያ ውስጥ የመንግስት መመሪያ በማክበር መሥራት ይቻላል?
  3. አብዮት ወረት ነው
  4. የእህአዴግ ‹‹ትርፍ›› እና ኪሳራ
  5. የኢትዮጵያ መንግስት መጠላቱን የሚያሳብቁ ምልክቶች
  6. ከእከሌን አሰሩት እስከ እከሌን አገዱት
  7. ሰማኒያ ሚሊዮን እስከምንደርስ እንታገላለን
  8. “ድር ቢያብር” ለአምባገነኖች ምናቸው ነው ?
ከሌሎች ብዙ ዝርዝሮች በጥቂቱ

  1. “ኢትዮጵያዊ ማንነት ከሌለ ትግሬያዊ ማንነት የለም” – (በአብርሃ ደስታ ጽሑፍ ከፌስቡክ የተወሰደ) /በበፍቃዱ ቤት የተገኘ/
  2. “መንግስት የለም ወይ ?” የምንና ምን አይነት መንግስት(የመስፍን ነጋሽ ጽሑፍ ከፌስቡክ የተወሰደ ) /በበፍቃዱ ቤት የተገኘ/
  3. የሁለተኛው ዘመቻ ዕቅድ ( ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አሁኑኑ)
  4. የ2ኛው ዘመቻ ጋዜጣዊ መግለጫ (ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አሁኑኑ)
  5. ዳዊት ሰለሞን ስለአዲሱ የጋዜጠኞች ፎረም ፕሬዚዳንት ፌስቡክ  ላይ የፃፈው እና አጥናፍ ለበፍቄ ኢሜል የደረገለት ጽሑፍ
  6.  “ፍርሃታችን የት ያደርሰናል ?” በሚል በኤልያስ ገብሩ ተጽፎ በፍቄ ላፕቶፕ ውስጥ የተገኘ(ለዕንቁ መጽሄት ተዘጋጅቶ ያልታተመ ጽሑፍ)
  7. የ3ኛው ዘመቻ ጋዜጣዊ መግለጫ ( ዴሞክራሲን በተግባር እናውል የሰላማዊ ሰልፍ መብታቸን ይመለስ)
  8. “ሰልፍና ሰይፍ ” በሚል በበፍቄ ተጽፎ ነገር ግን ያልታተመ ጽሁፍ ከላፕቶፑ
  9. የ1ኛው ዘመቻ ጋዜጣዊ መግለጫ(draft ሕገ መንግሰቱ ይከበር)
  10. የ4ኛው ዘመቻ ዕቅድ( ኑ ኢትዪጲያዊ ህልም አብረን እናልም)
  11. ጋዜጠኛ አስማማው ለድምፃችን ይሰማ የፌስቡክ ገጽ ያዘጋጀቸው ጥያቄዎች ከኢሜሉ (ለአዲስ ጉዳይ መጽሄት)
  12. ስለ ዞን 9 ዘመቻዎች globalvoicseonline.org ላይ የታተሙ ጽሑፎች
  13. በናትናኤል በኩል ለርዕዮት ዓለሙ ቤተሰቦች ከ Article 19 የተላከ 48,170.25(ብር) የዌስተርን ዩኒየን ኮፒ
  14.  “የተቃውሞ ሰልፉ ዕድሎች እና ተግዳሮቶች” በሚል አዲስ ጉዳይ ላይ የታተመ ጽሁፍ (draft)
  15. ማሒ ስለ ርዕዮት ዓለሙ እና ስለ አዲስ ዘመን “አዝማሚያ ጥናት ” በቀልድ የጻፈችው ጽሑፍ፡፡
  16. የዞን 9 ወደፌት ለመስራት የታቀዱ ሶስት ፕሮጄክት ፕሮፓዛሎች ( ምርጫ 2007 ሪፓርት የማድረግ ስራ፣ የኢትዮጲያ የነጻነት ኢንዴክስ ማዘጋጃት ስራ ፣ ገጠሪቷ ኢትዮጲያ ላይ ለመስራት የታሰበ ዶክመንተሪ እቅድ)
  17. እና ሌሎችም ትርኪሚርኪዎች (ለምሳሌ የዳንኤል ብርሃነ ጽሑፍ፣ የናቲ የ10ኛ ክፍል ግጥም)

#Ethiopia #FreeZone9Bloggers #FreeEdom #FreeTesfalem #FreeAsmamaw #FreeAllPoliticalPrisoners

     

     

     

     

    ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ እንዲሁም የኮንግረስ አባላት ጋር አፍሪካ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ስላላት ግንኙነት፣ የወጣቶች ሚና፣ አልፎም በአፍሪካ የወደፊት ዕድገትና ፈተናዎች ዙሪያ ትናንት ሲወያዩ የዋሉት 500 የአፍሪካ ወጣቶች ዛሬ ደግሞ ለውጥ እንዴት ሊያመጡ እንደሚችሉ ሲነጋገሩ ውለዋል፡፡

    ወጣቶቹ የለውጥ መሪዎች እንደሆኑ፤ ለዚህም የተጠናከረ ድጋፍ እንዳላቸው ፕሬዝደንት ኦባማ ገልፀዋል።

    በዛሬው ዕለት ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ስልታዊ ውይይቶችን እርስ-በርስ ሲያካሂዱ ነው የዋሉት።

    በሌላ በኩል ደግሞ ከኢትዮጵያዊያኑ ተሣታፊዎች አንዱና በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የተጀመረውና በዚህ ዓመት በታላቁ ደቡብ አፍሪካዊ መሪ ኔልሰን…

    ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

    ይኼ የመጨረሻዬ ደብዳቤ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ወይ እንደገና እንጋባለን አለበለዚያም እኅትና ወንድም ሆነን እንቀጥላለን፡፡ አሁን ‹እኅትና ወንድም ሆኖ መቀጠል›› ሲባል ቀላል ነገር ይመስላልኮ፡፡ የተለያዩ ባልና ሚስቶች ‹እኅትና ወንድም› ሆነው ለመቀጠል ሦስት ነገሮች ሳያስፈልጋቸው አይቀርም፡፡ ጠላትነትን ማጥፋት፣ ሌላ ዓይነት ወዳጅነትን መቀጠልና በአዲሱ መንገድ የሚመጡትን አስከፊ ነገሮች ሁሉ ለመቀበል መቻል፡፡ አንዳንድ ተጋቢዎች ሲለያዩ በጋብቻ ምትክ ጠላትነትን ተክተው ነው፡፡ እንዲያውም አንዳንዶቹ እንኳን ከዚህ በፊት አንድ ሆነው የኖሩና አንድ ሆነው ያደሩ፣ የተዋወቁም አይመስሉ፡፡ አንዱ ሌላውን ሲያስበው ያንገሸግሸዋል፡፡ ‹‹በለው በለው፣ ግደለው ግደለው› የሚለው ስሜት ይመጣበታል፡፡ ከፍቺ በኋላ ለሚፈጠሩ አሰቃቂ ወንጀሎች አንዱ ምክንያትም ይኼው ነው፡፡ ንብረት ክፍፍል ላይ ‹‹ይህንንማ አትገኛትም፣ አያገኛትም›› እየተባባሉ ምርኮ ስብሰባ የሚያስመስሉትም ለዚህ ነው፡፡

    ‹ሌላ ዓይነት ወዳጅነት› ያልኩሽ ቢያንስ ለመጠያየቅ፣ ተገናኝቶም ቢሆን ሻሂ ለመጠጣት፣ ስለ ልጆች ለመነጋገር፣ ቤተሰቦቻቸውን ለመጠያየቅ መግባባት ላይ መድረስ ማለት ነው፡፡ በትዳሩ ጉዳይ ለጊዜው ባይግባቡም ሌላ የሚያግባባቸው ነገር አያጡም፡፡ ትዳሩ ቢፈርስ እንኳን ትውውቁና ዝምድናው እንዲቀጥል ለማድረግ መጣር አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡ አንዳቸው ስለሌላቸው ክፉ ላለማውራት፣ ምሥጢሮቻቸውንም ጠብቀው ለመኖር መስማማት ኑሮን ሰላማዊ ለማድረግ ሳይጠቅም አይቀርም፡፡ ይኼ ነገር ለሁለቱም ሰላማዊ ኅሊና ይሰጣቸዋል፡፡ ከጠብ ስሜት፣ ከበቀል መንፈስ፣ ያድናቸዋል፡፡ ስለ ሌላ ሰው በክፉ ማሰብ ከሚታሰብለት ሰው በላይ ክፉ አሳቢውን ይጎዳዋል፡፡ ለስንት በጎ ነገር ሊጠቀምበት የሚችለውን የኅሊና ጉልበት ለማይጠቅም ጠብና ሐሜት፣ ጥላቻና ክፋት እንዲጠቀምበት በማድረግ ውሳጣዊ ሰላሙን ያሳጣዋል፡፡ በሌላም በኩል ደግሞ በሰላም ተለያይተው በሰላም የሚኖሩ ተፋቺዎች በጠብ ከተለያዩት ይልቅ እንደገና ለመጋባት የቀና መንገድ ይኖራቸዋል፡፡ ለፍቺ ያበቃቸው ቁስል እንዲድን ዕድል ሰጥተውታልና፡፡ ከፍቺ በኋላ በክፉ በመፈላለግ ቁስሉ ይበልጥ እንዲያመረቅዝ አላደረጉትምና፡፡

    በአዲሱ መንገድ የሚመጡትን አስከፊ ነገሮች ሁሉ ለመቀበል ዝግጁ መሆን ሲባል መለያየቱ የሚያመጣቸውን አሳዛኝና አስከፊ ነገሮችም ለመቀበል ዐቅም ማግኘት ማለት ነው፡፡ ተለያይቶ መኖሩን፣ የሀብት መካፈሉን፣ የአንደኛው ወገን ከሌላ የጾታ ጓደኛ ጋር መታየቱን፣ ከልጆች መለየትን የመሰሉ ነገሮችን ‹አስፈላጊ ሰይጣን› ናቸው ብሎ ለመቀበል መቻል ነው፡፡ ይህንን ለመቀበል ዐቅም ያጡ ተፋቺዎች ትልቁን ትዳር አፍርሰው ለትንሹ ንብረት ሲሟገቱ፤ እንዴት እገሌን ከሌላ ጋር አየዋለሁ፣ እንዴት እገሊትን የእገሌ ሆና አያታለሁ እያሉ ደም ሲለብሱ፤ ቆይተውም ወደ በቀል መንገድ ሲገሠግሡ ይታያሉ፡፡ ለዚህ ነው ‹እኅትና ወንድም ሆነን እንቀጥላለን›› ያልኩሽ፡፡ እርሱም ዛሬ ዛሬ ለብዙዎቻችን እያስቸገረን ነውና፡፡

    የመጨረሻው ደብዳቤዬ ነውና ‹ባለቤቴ› ስለሚለው ነገር እነግርሻለሁ ያልኩትን ነግሬሽ ልጨርስ፡፡ በግእዙ ‹በዐለ ቤት› ማለት ‹የቤት ጌታ፣ የቤት አለቃ› ማለት ነው፡፡ ‹ቤት› ደግሞ በምሥራቃውያን ባሕል ብዙ ነገርን የሚይዝ ነው፡፡ ቤት ነገድ ነው ‹ቤተ እሥራኤል እንዲሉ› ቤት ሀገር ነው ‹ቤተ አምሐራ›› ብለው እንዲጠሩ፡፡ ቤት  በማኅደሩ አዳሪውን ጠርተው ‹ነዋሪ› ማለት ነው፡፡ ‹‹ቤቶች›› እንዲሉ፡፡ ቤት ‹የቅርብ ዘመድ› ማለት ነው፡፡ ‹ቤተሰብ› እንዲሉ፡፡ ቤት ወገንን ያሳያል ‹ሥራ ቤቶች›  ሲል የቤት ውስጥ ሥራ የሚሠረቱትን አንድ አድርጎ እንዲገልጥ፡፡ ባለ ይዞታነትንና ባለሀብትነትንም ይገልጣል፡፡ ‹ባለቤት› ሲል ባለሀብት ማለት እንደሆነው፡፡ ቤት ልብስም ይሆናል ‹ቤተ እግር› ሲል ካልሲ፣ ገምባሌ ማለት ነውና፡፡ ቤተ እድ ሲልም ‹እጀ ጠባብ፣ እጅጌ፣ ቀለበት› ማለት ነው፡፡ የተሸለመ እልፍኝ ማለትም ይሆናል፡፡ ‹ቤተ አንስት› ሲል የተሸለመ የተጌጠ ቤት ማለት ነው፡፡

    ባለትዳሮችም ‹ባለቤቴ› ሲባባሉ የቤቴ ጌታ፣ የቤቴ አለቃ፣ ወገኔ፣ ነገዴ፣ አብሮኝ የሚኖር፣ የቅርብ ዘመዴ፣ በአንድ አብረን የምንሠራ፣ የሀብቴ የንብረቴ ባለሀብት ባለይዞታ የሆነ፣ ጌጠየ፣ ሽልማቴ፣ ልብሴ፣ ሞገሴ፣ እልፍኜ› ማለት ነው፡፡ በሌላም በኩል ‹ቤተ› ማለት ‹አደረ፣ ኖረ› ማለት ነው፡፡ ባለቤቴ ማለት ደግሞ አብረን የምናድር አብረን የምንኖር፣ ልቤ መኖሪያዋ፣ ማደሪያዋ ልቧ መኖሪያዬ፣ ማደሪያዬ የሆነ ማለት ነው፡፡ አንዳንድ ሊቃውንትም ‹ጉዳዩን በቤት በኩል ብቻ ሳይሆን በ‹በዐል› በኩልም ይፈቱታል፡፡ ‹በዐለ› – ከበረ፣ ከፍ ከፍ አለ፡፡ በዐለ – ቻለ፣ ዐወቀ፣ ሠለጠነ፣ ገዛ ማለት› ነው፡፡ ‹በዐለ መድኃኒት› ሲል መድኃኒት ያለው የሚያውቅ ማለት ነው፡፡ ‹በዐለ ሥልጣን› ሲል ሥልጣን ያለው ማለቱ ነው፡፡  ‹በዐለ ቤት› ሲል ‹የቤቱ ሠራዒ መጋቢ› ማለቱ ይሆናል፡፡ ባለቤቴ የሚለው ነገር እኩል ሥልጣንን፣ እኩል ባለሀብትነትን፣ እኩል አለቅነትንና እኩል መብትን ያሳያል፡፡ በእኔ ላይ ሥልጣን ያለው፣ ሥልጣን ያላት፣ እኔን የምታውቅ፣ በእኔ ላይ የሠለጠነ፣ የሠለጠነች፣ ማለት ነው፡፡

    ለዚህ ይመስለኛል በባሕላችን ‹ከባለቤትዎ ጋር› እየተባለ ጥሪ የሚተላለፈው፡፡ ሰውየው ለብቻው ሙሉ አይሆንም፣ ሴትዮዋም ለብቻዋ ሙሉ አትሆንምና፣ ሥልጣንም የላትም የለውምና፣ ስጦታ እሰጣለሁ፣ ቃል እገባለሁ፣ ብትልና ቢል አይችልምና ሙሉ አድርገን እንጥራቸው ብለው ነው ‹ከባለቤትዎ ጋር› ብለው የሚጋብዙን፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ በአብርሐና አጽብሐ ዘመን ብቻ ነው ይባላል ሁለት ነገሥታት በአንድ መንበር የገዙት፡፡ ከአብርሐ አጽብሐ ወዲህ በትዳር ብቻ ይመስለኛል ሁለት ነገሥታት በአንድ መንበር የሚነግሡት፡፡ ይህንን በአንድ መንበር ሁለት ነገሥታት መንገሣቸውን ነው ‹ባለቤቴ፣ ባለቤቴ› እየተባባልን የምንጠራው፡፡

    አንዱ ለሌላው ታዛዥ፣ ተገዥ ሆኖ፤ እርሱም በሌላው ላይ ገዥ፣ አዛዥ ሆኖ፣ የመኖርን ስልት ለማምጣት ነው ‹ባለቤቴ› ማለት፡፡ በፈቃድ መገዛትን፣ በፈቃድም ራስን መስጠትን ለማመልከት ነው ‹ባለቤቴ› ማለት፡፡ አንዱ የኔና ያንቺ ችግር ‹ብቻችንን ባለቤት እንሁን› እያልን ይመስለኛል፡፡ ሥልጣናችንን ስንጠቀመው ሌላውን ባለ ሥልጣን እየረሳን ስለሆነ መሰለኝ ችግራችን፡፡

    እና እስኪ ከራስሽ ጋር ብቻ ተወያይና ለእኔም ባትጽፊልኝ ለራስሽ መልስ ስጭ፡፡ እኔ ለአንቺ፣ አንቺም ለእኔ ክፉ ብትሆኚ እንኳን የተሻልን ክፉዎች የምንሆን ይመስለኛል፡፡ ከማያውቁት መልአክ የሚያውቁት ሰይጣን ይባል የለ፡፡

    በይ ደኅና ሁኚ፡፡ ምንም ብንለያይ ደኅና መሆንሽ ሁላችንንም ይጠቅማልና፡፡ 

    © ሦስቱም ደብዳቤዎች በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ወጥተዋል