የምዕራባዉያን ማዕቀብና ሩሲያ

ባለፈዉ ዓመት ከሩሲያ ጋር የ326 ቢሊዮን ዩሮ የንግድ ልዉዉጥ ያደረጉት የአዉሮጳ ሐገራት በማዕቀቡ የወለፊንድ ዉጤት ባንድ ወይም በሌላ መንገድ መነካታቸዉ አይቀርም።ከዩናይትድ ስቴትስና ከቻይና ቀጥሎ ከሩሲያ ጋር ከፍተኛ የንግድ ልዉዉጥ ያላት ጀርመን ደግሞ ከሕብረቱ አባል ሐገራት ሁሉ ቀዳሚዋ ናት።