የምሥራቅ አፍሪቃ አፍሪቃ ሃገራት ፤ የኢትዮጵያ ኬንያና ዩጋንዳ መሪዎች፤ 11 ወራት በእርስ በርስ ጦርነት ላይ የሚገኙትን የደቡብ ሱዳን ተቃናቃኝ መሪዎች ለመሸምገል ዛሬም አዲስ አበባ ውስጥ ጉባዔ አካሂደዋል።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአባይ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት እቅድ እንደሚያሳየው ግድቡ ሲጠናቀቅ 1600 ኪሎሜትር ስኩየር  መሬት የሚሸፍን ውሃ የሚተኛበት ሲሆን፣ የዚህ መሬት አካል 90 በመቶው በደን የተሸፈነነ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ አንጻራዊ በሆነ መልኩ የተሻለ የደን ሽፋን አለው የሚባለው ግድቡ የሚሰራበት የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቢሆንም፣ ከ200 ኪሎ ሜትር ያላነሰ ስፋት ያለው …

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ተጠናክሮ የቀጠለው የገዢው ፓርቲ አፈና መንግስት ራሱ ያስታጠቃቸውን ታጣቂዎች ትጥቅ እስከማስፈታት መድረሱን ምንጮች ገለጹ በትግራይና በአማራ ክልሎች ባለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው አፈና ቀጥሎ ጥቅምት 26 ቀን 2007 ኣም የሰላም ታጋይ እየጠባለ የሚታወቅ ወጣት ሽሻይ አዘናው በመቀሌ ከተማ በትግራይ ክልል የፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ገ/ህይወት ካህሳይ …

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ በኢትዮጵያ እና በአረብ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት እንዲሁም መንግስት ወደ አረብ አገራት በሚላኩ ዜጎች ጉዳይ ሊፈጽመው ያሰበው ስምምነት ምን ደረጃ ላይ  እንደደረሰ ግምገማ ተካሂዶ ነበር። መንግስት ተጓዝ ሰራተኞችን በሚመለከተ ያወጣው ህግ በአረብ መንግስታት እውቅና የተነፈገው ሲሆን፣ የአረብ አገራት ባለስልጣናት ኢትዮጵያውያን …

ጥቅምት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዩኒቨርስቲው ውስጥ በሚታየው ተደጋጋሚ የሃይል መቆራረጥና የውሃ እጥረት ተማሪዎች ትምህርታቸውን በአግባቡ ለመከታተል አልቻሉም። ከውሃ እጥረት ጋር በተያያዘ ከጽዳት ጋር ለተያያዙ በሽታዎች ሊደራጉ እንደሚችሉ ተማሪዎች ፍርሃታቸውን ገልጸዋል።

«ባርያዉ» በሚል መጠርያዉ የሚታወቀዉ ወጣት ሰመረ ካሳ በመድረክ በሚያቀርባቸዉ አዝናኝና አስተማሪ ቀልዶቹ ተወዳጅነቱ ታዋቂነቱ እየጎላ መጥቶአል። በዕለቱ ዝግጅታችን ባርያዉን ከነቀልዱ ይዘን «ሂስ የማኅበረሰብ አረም መንቀያ መሳርያ ነዉ» ያሉንን ምሑራን ጋብዘን የሂስን ምንነት ለማየት ቀርበናል።

ከ 50 የሚበልጡ የደቡብ ሱዳን ዜጎች፤ የሰብዓዊ ተቋማትና ፤ ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት እንዲሁም የደቡብ ሱዳን ጎረቤት ሃገራት የተመድ የፀጥታ ምክር ቤት በደቡብ ሱዳን ላይ አስቸኳይ የጦር መሳርያ ማዕቀብ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረቡ።

የአፍሪቃ ሕብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት እንኮሳዛና ድልሚኒ ዙማ ፤ ኢቦላ የተከሠተባቸውን የምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት ፤ ሴራሊዮንና ላይቤሪያን ተዘዋውረው ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ ፤ ለርዳታ ለመሠማራት ቃል የገቡትን

የቀድሞው የየመን ፕሬዚዳንት አሊ አብደላ ሳሌህ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ገር ለቀህ ውጣ አልችኝ ሲሉ ምሬት -አዘል ቃል ቢሰነዝሩም ዩናይትድ ስቴትስ ፣ ሳሌህ ያሉትን አለማድረጓን ገልጻለች። ባለፈው ሳምንት ዩናይትድ ስቴትስ፤

የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ የዝግጅት ክፍል አባላት ወደ ቂሊንጦና ቃሊቲ እስር ቤቶች በማቅናት እስረኞችን ጠይቀዋል፡፡ እስረኞቹ ያስተላለፉትን መልዕክት ነገረ ኢትዮጵያ እንደሚከተለው ጠቅለል አድርጋ አቅርባዋለች፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ አይቀርም›› እስክንድር ነጋ በማህበራዊ ድረ-ገጽም ሆነ በሌሎች አጋጣሚዎች መልካም ልደት ለተመኛችሁልኝ ሁሉ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ የቡርኪናፋሶው አምባገነን መውደቁን በመስማቴ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ይህ ለእኔ ውድ የልደት ቀን ስጦታየ […]

የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል እና የሰሜን ጎንደር የዞን ሰብሰቢ አቶ አግባው ሰጠኝ በገዢው ፓርቲ ሀይሎች ታፈነ
ትናንትና ምሽት አካባቢ ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍኖ የተወሰደው የዞኑ አስተባባሪ እስከአሁን ሰዓት ድረስ ያለበትን ቦታ ማወቅ አልተቻለም፡፡ ትናንት ማምሻውን በሲቪል እና መሳሪያ በታጠቁ የገዢው ፓርቲ ሀይሎች ቤቱ ተበርብሮ ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍኖ መወሰዱን በዞኑ ያሉ የፓርቲው አካላት አረጋግጠዋል፡፡
ከሰማያዊ ፓርቲ የጎንደር ዞን አስተባባሪ አቶ አግባው ሰጠኝ በተጨማሪም ወደ ስድስት(6) የሚደርሱ የአንድነት እና መኢአድ ፓርቲ አባላትም ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍነው መወሰዳቸው ተረጋግጧል፡፡
በሌላ በኩል በጎንደር ባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ከፍተኛ ክትትልና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሆነ የዞኑ ተጠሪዎች አመልክተዋል፡፡

የ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› ህዝባዊ ትግል ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር እንቅስቃሴ በፓርቲዎች ትብብር በህዳር ወር ይጀመራል!
ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም ትብብር የመሰረትን ዘጠኝ ፓርቲዎች ስለምስረታችን በሰጠነው መግለጫ የስምምነታችን ‹‹ … ዘላቂ ግብ ማንም ተጎጂ የማይሆንበትና ሁላችንም ተጠቃሚ የምንሆንበትን አቅጣጫ የተከተለ እንደመሆኑ ገዢው ፓርቲ/መንግስት እኔ ከሥልጣን ከለቀቅሁ በቀጣይ በሚመጣው ለውጥ አገር ትበታተናለች በማለት ህዝብን ከሚያስፈራራበት፣ ካድሬዎቹን ፣መከላከያ ሠራዊቱንና የፀጥታና ደህንነት ኃይሉን ተቃዋሚዎች ካሸነፉ አንድም ለወህኒ ካነሰም ‹‹ለልመናና የጎዳና ተዳዳሪነት›› ትዳረጋላችሁ… በሚል ሽብር ከሚነዛበት ፕሮፖጋንዳና አካሄድ እንዲመለስና እንዲታረም ዕድል የሚሠጥ›› መሆኑን ፣ ለትብበሩ አባላት ‹‹ ከምንም እና ከማንም በላይ ቀዳሚው አገርና ህዝብ ›› መሆኑንና በህዝባዊ ሠላማዊ ትግል በምትገነባው ሉዓላዊነቷ የተከበረ ዲሞክራሲዊት ኢትዮጵያ ‹‹ በሁለት ጽንፎች የተወጠረው የአገራችን የአሸናፊ-ተሸናፊ የጠቅላይ ሥልጣን ፖለቲካ ልምድ እንደሚቀየርና በከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ በህዝቦች መካከል ያለውን አብሮነት ለመበጣጠስ የተዘራውን አጥፊ ዘር ማድረቅ፣ የተሰራጨውን መርዝ ማርከስ ›› መቻሉን መግለጻችን ይታወሳል፡፡

አካሄዳችንን በሚመለከትም ‹‹…ለጋራ ዓላማችን እውን መሆን ያለፈው አካሄዳችን የትም እንዳላደረሰንና እንደማያደርሰን ከውድቀታችን ልምድ ቀስመን በአዲስ አስተሳሰብና የአመራርና አሰራር ሥርዓት ለማይቀረው ሥር ነቀል ሁለንተናዊ ለውጥ በግልጽነት በተጠያቂነት መርህ በጽናት ለመታገልና ለማታገል የደረስንበትን ስምምነት ስናበስር ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚመጣውን አገራዊና ህዝባዊ ኃላፊነት በመገንዘብ ›› መሆኑን ገልጸን ለዓላማችን ማስፈጸሚያ ተመጋጋቢና ተደጋጋፊ የአጭርና የረጅም ጊዜ የዕቅድ አቅጣጫ ማስቀመጠችንንም ገልጸን ነበር፡፡ የዛሬው መግለጫችን ዓላማም ባስቀመጥነው የአጭር ጊዜ ዕቅድ – ምርጫ 2007 ላይ ትኩረት ያደረገና ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ፕሮግራም በተከታታይ የሚካሄደውን ህዝባዊ ሠላማዊ ትግል የመጀመሪያውን ዙር የአንድ ወር እንቅስቃሴ መርሀ-ግብር ከባለቤቱ ዘንድ ማድረስ ነው፡፡

በዚህ መግለጫ በአገራችን ነባራዊና ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊና ማኅበራዊ እውነታዎች ዝርዝር ውስጥ ለመግባት አይሞከርም ፣ በየቤታችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚታየውን ፣በአራቱም የአገሪቷ አቅጣጫዎች በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ሥቃይና የሰላምና ፀጥታ ፣የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት… ላይ የደረሰውንና የፈጠረውን ሥጋት ማንሳት ‹‹ ቀባሪን የማርዳት›› ሙከራ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ትኩረታችን በምርጫና በመጪው ምርጫ 2007 ላይ ይሆናል፡፡

ሁላችንም እንደምናውቀው በመጪው ግንቦት ወር አምስተኛው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ ይካሄዳል ተብሎ ስለሚጠበቅ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀውን የጊዜ ሰሌዳ እንደተለመደው ለማወያየት በሚል ለማሳወቅ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ስብሰባ መጥራቱ ይታወሳል፡፡ ከዚህ ስብሰባ አስቀድሞ የዚህ ትብብር አባላትን ጨምሮ አስራ ሁለት ፓርቲዎች ለቦርዱ ጥቅምት 5 ቀን 2005

‹‹ 1ኛ/ ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ያቀረብናቸው ጥያቄዎቻችን እንዲመለሱ፤

2ኛ/ ገዢውን ፓርቲና አጋሮቹን ጨምሮ ሁሉም ህጋዊ ፓርቲዎች በጋራ ተገናኝተው በምርጫና የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ላይ የሚወያዩበት የጋራ መድረክ እንዲዘጋጅ ››

የሚሉ የጋራ ጥያቄዎችን በማቅረብ ‹‹የእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ማግኘት ማለት ለሠላማዊ የሥልጣን ሽግግር / የነጻ፣ ፍትሃዊና ተኣማኒና አሳታፊ የምርጫ ውድድር ሥርዓት/ ሠላማዊ ትግል/ ዕድል ከመስጠትና የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ከማረጋገጥ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው፡፡ ማለትም በሌሎች አምባገነን መንግስታትና ሥርዓቶች በጦር መሣሪያ ኃይልና በደህንነት አቅም በመመካት በሥልጣን ላይ ለመቆየት ያሳዩትን እምቢተኝነትና ማንአለብኝነት ተከትሎ የተከሰቱ ህዝባዊ እምቢተኝነትና በውጤታቸውም የተከተሉ ቀውሶችን በጋራ በመከላከል ከአሸናፊ/ተሸናፊ ጠቅላይ የፖለቲካ ሥልጣን አስተሳሰብ በመውጣት ለዲሞክርሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሠረት የመጣልና ለዘላቂ ሠላምና ልማት ዋስትና መስጠት ማለት ነው፡፡ በዚህ ማንም ተጎጂ አይሆንም፡፡›› ብለን ሌላው አማራጭ ደግሞ ‹‹በተቃራኒው እነዚህ ጥያቄዎች ባልተመለሱበት የሚደረግ የምርጫ ተሳትፎ ለኢህገመንግስታዊነትና ኢዲሞክራሲያዊነት ዕውቅና በመስጠት አገሪቷንና ህዝብን ወደባሰ አዘቅት መወርወር በመሆኑ በታሪክና ትውልድ ፊት የሚያስጠይቅ ይሆናል፤በዚህ ማንም ተጠቃሚ አይሆንም፣ በዚህ መተባበርም ከተጠያቂነት አያተርፍም፡፡›› ብለን የእኛ ምርጫ የመጀመሪያው በመሆኑ ቦርዱ ‹‹ ከምርጫ የጊዜ ሰሌዳ በፊት ባለበት አገራዊና ህዝባዊ ኃላፊነት መሠረት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠውና ተገቢ ምላሽ በመስጠት ሚዛናዊነቱን. ከወገንተኝነት የጸዳ፣ በምርጫ ህጉ በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት መሰረት የሚሰራ መሆኑን እንዲያረጋግጥ በድጋሚ አበክረን እንጠይቃለን፡፡›› በማለት አሳውቀናል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በስብሰባው ወቅት ( እዚህ ላይ ይህ ዓይነቱ ስብሰባ በ2005 አዳማ ላይ ስለምርጫ 2005 የጊዜ ሰሌዳ ፓርቲዎች በአንድ ላይ ተሰብስበን 33ቱ ‹‹ከጊዜ ሠሌዳው በፊት የፖለቲካ ምህዳሩ ይስተካከል›› የሚል ፔቲሽን ከተፈራረሙ በኋላ ባለው ጊዜ ቦርዱ ፓርቲዎችን በሦስት ቦታ በመከፋፈል እንጂ በአንድ ላይ የማይጠራ መሆኑን ያጤኑኣል) በሦስቱም የስብሰባ ቦታዎች የተገኙ ከኢህአዴግና አጋሮቹ እንዲሁም የኢህአዴግ ቀለብ የሚሰፈርላቸው የ‹‹ስለት›› ልጅ የሆኑ ለአጃቢነት የታጩ ፓርቲዎች በቀር ሁሉም የተቃውሞ ጎራ ፓርቲዎች በተመሳሳይና ተደጋጋፊ መንገድ ከላይ የቀረቡትን ጥያቄዎች የሚያጠናክሩ ተጨባጭ ማሳያዎችን በማቅረብ፣በማብራራትና የጥያቄዎቹን ምክንያታዊነትና ባልተመለሱበት ሊፈጠር የሚችለውን ችግር ለቦርዱ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡ ቦርዱም እነዚህን ጥያቄዎች በዝርዝር እየመዘገበ መሆኑን በኦዲዮ ቪዥዋል መሳሪያዎችም እየተቀረጹ መሆናቸውን በመግለጽ ለቦርዱ ስብሰባ ቀርበው መልስ እንደሚሰጣቸውና መፍትሄ እንደሚበጅላቸው፣ይህንንም ተገናኝተን እንደምንነጋገር ቃል ገብቶ ስብሰባዎቹ ተጠናቀው ነበር፡፡

በተገባው ቃል መሰረት የሚሰጠውን መልስና የሚበጀውን መፍትሄ በመጠባበቅ ላይ እያለን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች በጥያቄኣችን ላይ ያነሳነውን ለገዢው ፓርቲ ያላቸውን ‹‹ ወገናዊነትና የጉዳይ ፈጻሚነት ሚና›› ፍንትው አድርጎ በሚያሳይ መልኩ የጊዜ ሰሌዳውን ማጽደቅ ብቻ ሣይሆን በምርጫ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ የተመሰረቱትን ጥያቄዎቻችንን የቢሮ ጥያቄዎችና አስተዳደራዊ ጉዳዮች በማስመሰል አሳንሶ በማቅረብ ፕሮፖጋንዳ በመስራት በለመደው መንገድ ለመቀጠል መወሰኑን አውጀዋል፡፡ በዚህም ሳያበቃ በትብብር በጋራ ለመስራት በምናደርገው ግንኙነትና በተፈራረምነው ስምምነት መሰረት በቀጣይ ለምንቀሳቀሰውም ቦርዱ በህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር (ከዚህ በፊት ተመሳሳይ መግለጫ ይሰጡ የነበሩት የኢህአዴግ አባልና የደብረ ብርሃን ከተማ ዕጩ የምርጫ ተወዳዳሪ የነበሩ መሆኑን እያስታወስን) በኩል ‹‹ በዚህ ትብብር አማካይነት ነገ ወደ ሥራ ሲገቡ ችግር ቢያጋጥማቸው ቦርዱ ሊቆምላቸው የሚችልበት የሥራ አግባብ የለም ››፣ በዚህም ተጠያቂ ‹‹ እንደግለሰብም ሆነ እንደፓርቲ ራሳቸው ነው የሚሆኑት›› የሚፈጠረው ችግርም ‹‹ከህግ ማክበር ጋር ›› የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል በመግለጽ (ሪፖርተር ጥቅምት 29 ቀን 2007) ለማን መሆኑን ባናውቅም (ለኢህአዴግ ይህን መምከር ስድብ ይሆናልና) በማስፈራሪያ መልዕክት የታጀበ የወንጀል ክስ ኃሳብና ጥሪ አስተላልፏል፡፡

ከላይ የገለጽናቸው ሁሉ በጋራ ትግላችን ላይ ለማሳረፍ የተፈለገውን የፖለቲካ ጫናና አንድምታውን የመረመረው የትብብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ‹‹ ጽድቁ ቀርቶ በወጉ በኮነነኝ ›› እንዲሉ በህገ መንግስቱና በምርጫ አዋጁ የተቀመጠው መብታችን መጣስ/መጨፍለቅ፣ ቦርዱም ሆነ በሥሩ ያሉት መዋቅሮች ነጻና ገለልተኛ ያለመሆን፣ የምርጫ ሜዳው (የተፎካካሪ ፓርቲዎች በእኩል በህዝብ ውስጥ የመንቀሳቀስ መብት፣የአማራጭ ኃሳብ ማራመጃ ሚዲያ ፣ የመራጩ ህዝብ ዲሞክራሲዊ መብትና ሳይሸማቀቅ በነጻ የመምረጥ መብት፣ የምርጫ አስተዳደሩ፣…) በሚመለከት ለምናቀርባቸው ጥያቄዎች መልስ የማይሰጥ፣ቦርድ በህግ ‹‹ጥፋት›› ለሆነ ድርጊት ከለላ ሊሰጠን እና መከታ ሊሆነን መከጀሉ (መቼ፣ለማን፣እንዴት፣ተደርጎ እንደነበር በጥያቄ ታልፎ) ምጸት መሆኑን ተረድቷል፡፡ የቦርዱም አካሄድ ከተለመደውና በድህረ ምርጫ 2002 ግምገማ ከደረስነው ድምዳሜ ‹‹የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል›› ከሚለው አልፎ ‹‹ ተዘግቷል›› ወደሚል ድምዳሜ የሚያሸጋግር ሆኖ መገኘቱን በተጨባጭ አረጋግጠናል፡፡ ዛሬ ላይ የእምነት ነጻነት ጠያቂዎች፣ጋዜጠኞች፣ጦማሪያን፣የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና አባላት፣ አልፎም ከገዢው ፓርቲ የተለየ ኃሳብ ያላቸው ዜጎች በአፋኝ ህጎች በፈጠራ ወንጀል ተከሰው የት እንደሚገኙ ከእኛ አልፎ የዓለም ህዝብ ያውቀዋል፤ አንድም በወህኒ ያሊያም በስደት፡፡

ስለዚህ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለማስከፈት ትግሉን የ ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል የፕሮግራም መርህ ለመግፋት ወስኖ የመጀመሪያውን ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ የአንድ ወር ዕቅድ አዘጋጅቶኣል፡፡ በዕቅድ ዝግጅቱ የፕሮግራሙ የአፈጻጸም ስልት ፣የጊዜ ሰሌዳ፣ የቦታ ሽፋን፣የፋይናንስ ምንጭ፣ ዓላማዎች፣ትኩረት የሚደረግባቸው ጉዳዮችና መንግስታዊና የህዝብ ክፍሎች፣ዋና ዋና ተግባራት ፣በተጨማሪም በታሳቢነት በአፈጻጸም ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች/ደንቃራዎችና ሥጋቶች እንዲሁም ለፕሮግራሙን ስኬት አጋዢ ሁኔታዎች እንዲካተቱ ተደርጓል፡፡

በዚህ መሠረት ይህ ዙር የሚያተኩርባቸው ዋና ዋና ተግባራትም–
1. በየቤተ እምነቱ ጸሎት ፕሮግራም እንዲደረግ ጥሪ ማድረግና አባላት እንደየእምነታቸው ተሳትፎ ማድረግ፤
2. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግ፤
3. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ፤
4. ለመንግሥታዊ ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት፤
5. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት፤
6. የህዝብ ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ፤ ናቸው፡፡

እዚህ ላይ ሊታወቅ የሚገባው አቢይ ጉዳይ ይህን ዕቅድ ስናዘጋጅ ነጻነታችንና መብታችን ከገዢው ፓርቲ ለምነን የምናገኘው ሣይሆን በእያንዳንዳችን እጅ ውስጥ መሆኑንና በማመን እኛ የዕቅዱ አስተባባሪዎች እንጂ የጉዳዩ ዋነኛ ባለቤት፣ የዕቅዱ ፈጻሚና ዋና ተዋናይ እያንዳንዱ/ዷ ኢትዮጵያዊ/ት ዜጋ ነው/ናት በሚል ሙሉ እምነት ላይ ቆመን መሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ ለዚህ ዕቅድ ተፈጻሚነት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ/ት በጋራ/በትብብር ከጀመርነው ሠላማዊ ትግል ጎን በመቆም ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ አይኖርምና በምርጫ ሥም ሠላማዊ የነጻነት ትግሉን ማዘናጋት ያብቃ// ማለትና ለዕቅዱ ተፈጻሚነት የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ራስን ከባርነት ነጻ የማውጣት፣አገርን ከጥፋት የመታደግ የዜግነት ግዴታ መሆኑ ግልጽ እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡

በመጨረሻም ከላይ በገለጽናቸው ተጨባጭ ሁኔታዎች ውስጥ የሚደረግ ምርጫ ገዢው ፓርቲ በጉዳይ ፈጻሚው የምርጫ ቦርድ በኩል በተለመደው መንገድ በምርጫ ሥም ለመሥራት የተያያዘውን ቧልት ራቁቱን በማስቀረት ለ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ የምርጫ ሜዳውን እንዲያስተካክል በሠላማዊ ትግል አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማሳረፍ በእኛ በኩል አስፈላጊውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈልና እስከ መጨረሻው በጽናት ለመቆም የተዘጋጀን መሆኑን እያረጋገጥን ፡-

1ኛ/ የችግሩ ገፈት ቀማሽና የጉዳዩ ቀዳሚና ዋነኛ ባለቤት የሆናችሁ በአገር ቤት ያላችሁ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ አገራችን ከገባችበት ፈተና ህዝባችን ከሚደርስበት ሥቃይ ለማውጣት የራሳችን የዜግነት ክብር ባለቤት ለመሆን ያለን ምርጫ በጽናትና ቆራጥነት የተባበረና የተቀናጀ ሠላማዊ ትግል ስለሆነ ለዚህ ፕሮግራም ስኬት ሁለንተናዊ የፋይናንስ ፣የማቴሪያል፣የጊዜና ጉልበት፣ የዕውቀትና ሙያ፣ የትግል አስተዋጽኦ (በማድረግ የዜግነት ግዴታችሁን እንድትወጡ) እንድታደርጉና እንቅስቃሴኣችንን በመከታተል የአመራርና አፈጻጸም እገዛችሁ እንዳይለየን ፤

2ኛ/ ከአገዛዝ ሥርዓቶች ጋር የተያያዙ የተለያዩ ችግሮችና ፈተናዎች ለስደት የተዳረጋችሁ፣በውጪ ለመኖር የተገደዳችሁ ባላችሁበት ሆናችሁ የአገራችሁ ጉዳይ እንቅልፍ የሚነሳችሁ ኢትዮጵያዊ የዲያስፖራ አባላት በሙሉ ከላይ የእናንተ ተሳትፎ ከትብብርና ድጋፍ ያለፈ አገራዊ ኃላፊነት የመወጣት ነውና በአገር ቤት ላሉት ካቀረብነው በተጨማሪ ድምጹ ለታፈነውና የሰቆቃ ህይወት ለሚገፋው ወገናችሁ ድምጽ ሆናችሁ የዲፕሎማሲውን ትግል በኃላፊነት ስሜት እንድታከናውኑ፤

3ኛ/በትብብሩ ያልታቀፋችሁ በተለይም በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋችሁ በተለያየ ምክንያት የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረማችሁም ሆነ የአገርና ህዝብን ጉዳይ ከፓርቲ ጥቅምና ዓላማ በላይ ስለሆነ በጋራ ለመሥራት ዝግጅቱና ቁርጠኝነቱ ያላችሁ ሌሎች ሠላማዊ የተቃውሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ትግሉ እንድትቀላቀሉ እና/ወይም የፕሮግራሙ አካል እንድትሆኑ፤

4ኛ/ የዓለም አቀፉና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት መንግስታት ተለዋዋጭና ኃላፊ፣ ህዝብ ግን ቋሚ ነውና በግንኙነታችሁ የህዝብ ለህዝብ ዘላቂ ጥቅምንና ታሪካዊና ፖለቲካ አንድምታን ከግምት እንድታስገቡ፤ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

በተቀናጀ የጋራ አመራር የተባበረ ህዝባዊ ሠላማዊ ትግል በእኩልነት ላይ የተመሠረተች ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን//

ጥቅምት 25/2007፣ አዲስ አበባ

የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች የአሁኑ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ሰመጉ ባወጣው 132ኛ ልዩ መግለጫ በክልሉ በመንገሽና ጎደሬ ወረዳዎች ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የተገደሉ የ60 ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በሪፖርቱ እንደቀረበው 27 የአማራ፣ 27 የመዠንገር፣ 2 የከፋና 4 የኦሮሞ ተወላጆች ተገድለዋል። እንዲሁም 16 የአማራና 6 የመዠንገር ተወላጆች የአካል ጉዳት ሲደርስባቸው፣ 36 የአማራ ተወላጆች ተፈናቅለዋል። 4 የአማራ ተወላጆችም የደረሱበት አለመታወቁ በሪፖርቱ ተጠቅሷል።
ከተገደሉት ሰዎች መካከል የዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ የመዠንገር ተወላጅ የሆኑት ዳኛ ፀጋዬ ጌታሁን ሲገኙበት፣ መካሻ መንግስቱ የተባሉ ሰው ደግሞ እስከነባለቤታቸው ተገድለዋል።
ሰመጉ በግጭቱ መነሻ ዙሪያ የተናገረው ነገር ባይኖርም፣ በተለያዩ አካባቢዎች የብሄረሰቦች ግችት እየተስፋፋ ቢመጣም መንግስት ይህን አሳሳቢ ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት እያደረገ ያለው ጥረት ከችግሩ ክብደትና እየደረሰ ካለው ጉዳት አንጻር ሲታይ ጨርሶ የሚመጣጠን አይደለም ብሎአል። መንግስት ተመሳሳይ ግጭቶች እንዳይፈጠሩ ዘላቂ መፍትሄ ማበጀት ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ጉዳይ ነው የሚለው ሰመጉ፣ በመዠንገር ዞን ለተፈጠረው ሰብአዊ እልቂትና መንስኤ የሆኑ ምክንያቶችንና ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ግልሰቦችንና ቡድኖችን አጣርቶ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል።
ሰመጉ ባወጣው መግለጫ ላይ መንግስት የሰጠው አስተያየት የለም። መኢአድ የተገደሉ ዜጎችን ቁጥር ከ540 በላይ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል።

Image

Image

Image

ዜጎች መታሰራቸው እየቀጠለ ነው። በተለይም የአንድነት ፓርቲ አባላት (በጎንደር፣ በትግራይ፣ በመቱ፣ በአዲስ አበባ ፣ በወላይታ ….) ። ብዙዎች ከፍተኛ ደብደባ እየደረሰባቸው ነው። ሕወሃት ፣ በሕዝብ እንደተጠላ ስላወቀ የአንድነት ፓርቲ እንዲዳከም ወይም ከምርጫው ዉጭ እንዲወጣ እየሰራ ነው። አንድነት ሊያሸንፈው እንደሚችል ስላወቀ። የድርጅቶች መተባበር አስፈላጊ በመሆኑ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር ተስማምቶ የቅድመ ዉህደት ስምምነት ፈርሞ ነበር። ሁሉም ነገር […]

በዚህ የምርጫ ወቅት እየተቃረበ ባለበት ወቅት ስርዓቱ የመንግስትን ተቋማት ተገን አድርጎ የአንድነት አባላትን በመላ ኢትዮጵያ በማሰርና በማዋገብ ላይ ይገኛል። ለጥቅምት 25/2007 ዓ.ም. አጥቢያ ላይ በምዕራብ አምርማጭሆ አብርሃ ጅራ ከተማ የሚገኙ የአንድነት አባላት አቶ አንጋው ተገኝ የአካባቢው የአንድነት ሰብሳቢ፣ አቶ አባይ ዘውዱ እና አቶ እንግዳው ዋኘው የተባሉ የአካባቢው የአንድነት አመራር አባላት የፌደራል ፖሊሶች የቤታቸውን በር ገንጥለው […]

በመቀሌ የአንድነት አባል የሆነው ወጣት ሺሻይ አዘናው በዛሬው ዕለት ጥቅምት 26 2007 ዓም በመንግስት የድህንነት አካላት ከሚሰራበት መስሪያቤት የወሰዱት ሲሆን ከዚያ ወደ ቤቱ በመውሰድ ቤቱን ፈትሸው እዚያ ያገኙትን ወረቀት ሁሉ አፋፍሰው ከያዙ በኋላ በሽፍን ላንድኩረዘር መኪና ወደ አልታወቀ ቦታ ይዞውት ሄደዋል። ወጣት ሽሻይ አዘናው ቀደም ሲል አንድነትን ከመቀላቀሉ በፊት የአረና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበረ ሲሆን፤ […]

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሰሜን ጎንደር ዞን በፓርቲው አባላት ላይ በዘመቻ የሚደረገውን እስርና እንግልት በመቃወም መግለጫ አወጣ

በዛሬው ዕለት ጥቅምት 26 ቀን 2007 ዓ.ም ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት የአንድነት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዳንኤል ሺበሺ ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ም/አፈ ጉባኤ የሺዋስ አሰፋ ፣ የአረና ፓርቲ የአመራር አባልና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህር አብርሃ ደስታ እንዲሁም የአ/አ ዩኒቨርስቲ የማስትሬት ተማሪ ዘላለም እና በተመሳሳይ መዝገብ […]

Image

በኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ ታሪክ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት በህገ መንግስት እውቅና ያገኘውና በይፋ ፓርቲ መመስረት የተቻለው በኢህአዴግ ዘመን ነው፡፡ ይህ መቸም እንደ ጅምር ሊያስመሰግን የሚገባ ተግባር ነው፡፡ ምንም እንኳ ኢህአዲግ ለነፍሱ ብሎ ባያደርገውም፡፡ ሁኔታዎች አስገድደውት ያደረገው እንደሆነ ቢታወቅም በይፋ መደራጀት መቻልን እንደ ትልቅ ለውጥ ነው የምወስደው፡፡
ቁም ነገሩ ግን ኢህአዲግ የፈቀደልንን ህገ መንግስታዊ (ከጫካ ስለሆነ የመጣው ያለመፍቀድ እድልም ነበረው) የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ተጠቅመን ለውጥ ለማምጣት ተንቀሳቅሰናል ወይ? የሚለው ነው፡፡ ለእኔ መልሱ አይደለም የሚል ይሆናል፡፡ ከአዛውንቱ ዶክተር አስራት ወልደዬስ በቀር አንድም እንኳ ህዝብ አስተባብሮ መሬት ያረፈ ትግል ያደረገ እና ኢህአዲግን የተገዳደረ ፓርቲ ፈጽሞ የለም፡፡ ከጠብ-መንጃ ጋር ፊት ለፊት በባዶ እጅ የተጋፈጡት ቆፍጣናው ምሁር አስራት ውልደዬስ እድሜያቸውና ክብራቸውን በማይመጥን ሁኔታ ለእስር ተዳርገው ለሞት ቢበቁም ከእርሳቸው በኋላ ለምልክት እንኳ የተንቀሳቀሰ የፓርቲ መሪም ሆነ ፓርቲ አላየሁም፡፡
ለዚህም እንደ ማሳያ የሚሆነው አንድም እንኳ የፓርቲ መሪ ለእስርም ሆነ ለሞት ሲዳረግ ታይቶ አለመታቁ ነው፡፡ በአካልም ሆነ በመንፈስ አንዳች ጉዳት ደርሶባቸው አለማወቁ ነው፡፡ በነገራችን ላይ የግድ ለምን አልታሰሩም ወይም አልሞቱም የሚል መንቻካ ሀሳብ ለማንሳት ሳይሆን ከኢህአዲግ አምባገነንነት አንጻር ምንም አይነት እርምጃ ያለመውሰዱ የመሪዎቹን ልክ ያሳያል ለማለት ነው፡፡ ሁሉንም የግፍ ገፈት የሚጨልጡት አባላትና ዜጋው ነው፡፡ ቆፍጣናዋን እንስት ብርቱካን ሚዴቅሳን ግን መርሳት ከቶ አይቻልም፡፡
በኢህአዲግ ክፍተት ወይም እንዝላልነት በአጋጣሚ የተገኘው የ1997 ዓ.ም ተሞክሮም ቢሆን በፖለቲከኞች ልፋት ያልመጣ መሆኑ ለክርክር የሚቀርብ አይደለም፡፡ የመለስ ዜናዊ ‹‹እንከን አልባ ምርጫ እንደርጋለን›› ፉከራን ተከትሎ ገርበብ ያውን በር ነጻነት የተጠማው ህዝብ በርግዶት ከመግባቱ በቀር ይህን አስተዋጽኦ አደርጌያለው የሚል ካለ ለክርክር ፈቃደኛ ነኝ፡፡
ምን ይሻል???
እስካሁን የነበረውን ‹‹የእናቴ ቀሚስ ጠለፈኝ›› ማስተባበያ ወደ ጎን ብለን ህዝቡ ድረስ በመውረድ ማደራጀት፤ የነጻነትን ጣዕም እንዲያውቅ ማንቃት፤ ዲሞክራሲን በተግባር ማለማመድ፤ ህዝቡ የሥነ ልቦና ለውጥ እንዲያመጣ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለውድቀታችን ሁሉ ኢህአዲግን መክሰስ ግን እንደ ቋንጣ የደረቀና አዋጭ ቢዝነስ አይደለም፡፡ በነገራችን ላይ ለፖለቲካችን መበላሸት ኢህአዲግ ሰፊ መዳፍ የለውም የሚል የሞኝ አስተሳሰብ የለኝም፡፡ የእኔ መከራከሪያ የኢህአዲግ ባህሪ የታወቀ ስለሆነ እርሱን ወደ ጎን ትተን እና እረስተን ህዝቡ ጋር መድረስና ህዝባችን ማንቃት የሚል ነው፡፡ ምክንያቱም የነቃ ህዝብ ለጭቆና ስለማይች፡፡ በተቃራኒው ያልሰለጠነና ያልነቃ ህዝብ ‹‹ቢጭኑት አህያ ቢጋቡት ፈረስ›› ከመሆን አያልፍምና፡፡
‹‹መንግስት የቆመጠው ቆማጣ አይባልም›› ብሎ የሚተርትን ህዝብ መንግስት መቁመጥ መብቱ አለመሆኑን ማስረዳት ይኖርብናል፡፡ በተቃራኒው ህዝብ በመንግስት ላይ ያለውን የበላይነት አንጽሮ መንገርና ሀሳብ ማስታጠቅ ይጠበቃል፡፡ ነገር ግን አብዛኛዎቹ የሀገራችን ፖለቲከኞች ኢህአዲግን ከመክሰስ እና ሰሞነኛ ነገር ከማራገብ ያለፈ ስር ነቀል ለውጥ የምንፈልግ አይመስለኝም፡፡
‹‹ኢህአዲግ ገዳይ ነው፤ ኢህአዲግ ያስራል ፤ ያፈናቅላል፤ ያሰድዳል፤ የመንግስትን በጀት ለድርጅት ይጠቀማል፤ ይዋሻል…..ብላ ብላ ከሚል ማላዘን ያለፈ ተጨባጭ አማራጭ የለንም፡፡ አለን የምንለው እንኳ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ አይደለም ሀገርን ያክል ትልቅ ነገር ይቅርና መንደር ለመምራት የሚያስችል አቅም ያለው ፓርቲ ማግኘት ጨረቃ ላይ እንደመውጣት ያለ ከባድ ነው፡፡
‹‹የኢህአዲግ የትምህርት ፖሊሲ የተሳሳተ ነው›› የሚል ተቃዋሚ አማራጭ የማቅረብ ግዴታ አይኖርበትም፡፡ እውነታ ግን ባ ተቃውሞ ብቻ ነው፡፡ የእያንዳንዱን ፓርቲ ገመና ቀርባችሁ ስታዩት ከበርሜል ጩኸት አይለይም፡፡ ባዶ ‹‹የእንዲህ ሆነብን›› ጩኸት!! ታዲያ በዚህ ሁኔታ እንዴት ለውጥ ማምጣት ይቻለል?? በነገራችን ላይ ‹‹ኢዴፓ›› መስተካከል ያለበት እንዳለ ሆኖ ማንም ፓርቲ ሊስተካከለው የማይችል ዝርዝር የትንታኔ ሰነድ ባለቤት ነው፡፡
መፍትሄው
መፍትሄው እራሳቸውን በሸንበቆ አጥር ከልለው በጸጉር ስንጠቃ አባዜ የተበታተኑ ፓርቲዎችን ወደ አንድ ጎራ እንዲፈሱ በማድረግ ግዙፍ የሆነ እና አማራጮችን ማቅረብ የሚችል የተቃውሞ ጎራ መፍጠር ብቻ ነው፡፡ ደግሞም ይህን ለማድረግ የሚያግድ አንዳች እንኳ ምክንያት የለም፡፡ ምን አልባት እንደ ዘመነ መሳፍንት ሁሉ በዬ መንደሩ አለቃ ሆነው የከረሙት የፓርቲ አመራሮች ይህ እንዳይሆን አይታገሉም ማለት አይደለም፡፡
ነገር ግን ኢህአዲግን ከመታገላችን በፊት እነዚህን ‹‹የመንደር አውራዎች›› ልክ ማስገባት ለነገ የማይባል ስራ መሆን ይኖርበታል፡፡ መነጋገሪያችን መሆን ያለበትም ፍትህ የተጠማውን ህዝባችን መታደግ የሚችል ፋና ወጊ ፓርቲ እንዴት መመስረት ይቻላል የሚል መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ ደግሞ ለዛሬ እንጅ ለነገ መባል አይገባውም፡፡

በተባበረ ክንድ ወደ ነጻነት የምንጓዝበት ቀን ሩቅ አይሆንም!!
…………….እናቸንፋለን……!!!

አቶ ሀብታሙ አያሌው ግራ እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ችሎቱን ተቀምጦ ለመከታተል መገደዱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ተከሳሾች ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው ::
7 ሙስሊም ወንድሞች እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም ተሳትፈዋል›› የተባሉ ተከሰዋል ::

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በሽብር የተከሰሱት አራቱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ዛሬ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት የዋስትና ጉዳያቸውን ለማየት ለህዳር 2/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ሀብታሙ አያሌው፣ የሽዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታና ዳንኤል ሺበሺን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ከቀናት በፊት መመስረቱ የሚታወስ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ የዋስትና ጉዳያቸውን አይቶ ብይን ይሰጣል ቢባልም የተከሳሽ ጠበቆች አጭር የጊዜ ቀጠሮ በጠየቁት መሰረት ለህዳር 2/2007 በአምስት ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ከ1-5ኛ እና የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ የተከሳሾች የዋስትና ጉዳይ ከመታየቱ በፊት በተከሳሾች ላይ የቀረበው ማስረጃ የገጽ ብዛት ተጠቅሶ ለጠበቃዎቹ እንዲደርሳቸውና የአቃቢ ህጎቹ ስም እንዲጠቀስ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡
ጠበቃው የዋስትና ጉዳዩን በተመለከተ በቃል ጥያቄውን ማድረስ እንደሚችሉ ገልጸው፣ ነገር ግን ጊዜ ተሰጥቷቸው በጽሑፍ ለዳኞቹም ለአቃቤ ህጎቹም ማቅረብ እንደሚችሉ ለችሎቱ በጠየቁት መሰረት ለቀጣይ ቀጠሮ በጽሑፍ አዘጋጅተው እንዲቀርቡ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ በበኩሉ ያለውን የሰነድ ማስረጃ ከክሱ ጋር አያይዞ ማቅረቡን በመግለጽ የሰው ማስረጃዎችም እንዳሉት አስረድቷል፡፡
አቶ ሀብታሙ አያሌው ግራ እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ችሎቱን ተቀምጦ ለመከታተል መገደዱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ አቶ ሀብታሙ አያሌው 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ሌሎች ተከሳሾች ደግሞ 1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ፣ 3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ፣ 4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ፣ 5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ፣ 6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ፣ 7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን፣ 8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ፣ 9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ፣ እና 10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ 7 ሙስሊም ወንድሞች እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም በዋና ወንጀል አድራጊነት ተሳትፈዋል በሚል አቃቤ ህግ ዛሬ ክስ እንደመሰረተባቸው ታውቋል፡፡
ተከሳሾቹም፡-
1ኛ. ተከሳሽ ጃፋር መሀመድ
2ኛ. መሀመድ ኑሩ
3ኛ. መሐመድ ሰሊም
4ኛ. ኑረዲን ጀማል
5ኛ. መሀመድ አባብያ
6ኛ. አኑዋር ጃኒ
7ኛ. ጀማል አብዱ ናቸው፡፡
= በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርት =

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የምርጫዉን ውጤት የገመገሙልን በባልቲሞር ሞርጋን ስቴት ዮኒቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ መምህር ዶክተር ጌታቸዉ መታፈሪያ የፕሬዚደንት ኦባማ የአገርና የዉጪ ፓሊሲዎች ላይ ከፍተኛ እንድምታ ይኖረዋል ብለዋል። ከፊታችን ጥር ወር ጀምሮ በሁለቱም ምክር ቤቶች ማለትም በመምሪያዉና በመወሰኛዉና ክፍሎች የአብላጫ ድምጽ የሚኖራቸዉ ሬፑብሊካዉያን ሲቃወሙዋቸዉ የነበሩ ለምሳሌ እንደ ፕሬዚደንት ኦባማ የጤና ጥበቃ ሕግ ያሉትን ሊሽሩ እንደሚችሉ ተናግረዋል። የሆነ ሆኖ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ድምጽን በድምጽ የመሻር ስልጣን እንዳላቸዉ ይታወቃል።

 

በሕዋ ለመመራመርም ሆነ ለመንሸራሸር፣ የሚደረግ ጉዞ፣ በምድር ላይ እንደምናውቀው የተለያየ የማጓጓዣ ዘዴ ፍጹም ቀላል አይደለም። በሕዋ ጎዞ የማይታሰብ የተለያየ ችግር ሊያጥም እንደሚችል በማሰብ ማሰላሰል ፤ አማራጭ መላዎችን ሁሉ መሻቱ ተገቢ ነው።

በቻይና የመጠጥ ዉኃ ምንጭ በደንብ በተመጣጠነ ሁኔታ ለኅብረተሰቡ አልተከፋፈለም። በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል ከሚገኘዉ የመጠጥ ዉኃ አገልግሎት ይልቅ በደቡባዊ የሀገሪቱ ክፍል በብዛት ተዳርሷል።

በዩኤስ አሜሪካ ትናንት በተካሄደው አጋማሽ የምክር ቤት ምርጫ ሬፓብሊካውያን በሁለቱም የምክር ቤት ክፍሎች አሸነፉ። በሕግ መምሪያው ምክር ቤት አብላጫውን ድምፅ የያዙት ሬፓብሊካውያን 100 መንበሮች ባሉት በሕግ መወሰኛው ምክር ቤትም ውስጥ 52 መንበሮችን በማግኘት አብላጫውን ድምፅ መያዝ ችለዋል።

በብዙ የኢትዮጵያ ከተሞች እየታየ ያለው የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በዕለት ተዕለት ኑሮው እና ስራ ላይ ከፍተኛ ችግር እንዳስከተለባቸው ዜጎች በምሬት ገልጸዋል። በሕዝቡ ኑሮ ላይ አሉታዊ ጫና የፈጠረውን የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግር ለመቀነስ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ብዙ ስራ መሰራቱንና ይህንኑ ጥረቱን መቀጠሉን የኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ገልጾዋል።

የአፍሪቃን ኤኮኖሚ ዕድገት ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል እንዲቻል በተለይ ትኩረቱ በከፍተኛው ትምህርት ዘርፍ ላይ ማረፍ እንደሚገባው በአዲስ አበባ የተመ የአፍሪቃ ኤኮኖሚ ኮሚሽን ውስጥ ለአራት ቀናት የተካሄደው ጉባዔ አሳሰበ።

ጥቅምት ፳፭ (ሃያ አምት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባዔ  የአሁኑ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ( ሰመጉ) ባወጣው 132ኛ ልዩ መግለጫ በክልሉ በመንገሽና ጎደሬ ወረዳዎች ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የተገደሉ የ60 ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል። በሪፖርቱ እንደቀረበው 27 የአማራ፣ 27 የመዠንገር፣ 2 የከፋና 4 የኦሮሞ ተወላጆች ተገድለዋል። እንዲሁም 16 የአማራና 6 የመዠንገር ተወላጆች …

ጥቅምት ፳፭ (ሃያ አምት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፉት ሁለት ቀናት ጀምሮ መንግስት በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የተቃዋሚ አመራሮችን በመያዝ እያሰረ ነው::  በትግራይ ክልል በምዕራባዊያን ዞን ቃፍታ ሁመራ ወረዳ ዳንሻ ከተማ የአረና ፓርቲ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ዘነበ ሲሳይ ጥቅምት 25፣ 2007 ዓም ከቤታቸው ተነጥለው በመወሰድ ሲታሰሩ፣  በተመሳሳይ ቀን በሁመራ የአረና የቁጥጥር ኮሚቴ አባል የሆኑት …

ጥቅምት ፳፭ (ሃያ አምት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ በመሰረተባቸው አቶ ዘላለም ወርቅነህ፣  ሃብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ የሽዋስ አሰፋና በሌሎች 5 ተካሳሾች ላይ ዋስትናን በተመለከተ ሊሰጥ የነበረውን ውሳኔ አራዘመ። ፍርድ ቤቱ የሁሉም ጠበቆች ተዘጋጅተው ባለመቅረባቸው ውሳኔውን ለህዳር 2 ፣ 2007 ማራዘሙን አስታውቋል። እስረኞቹ በሽብር …

ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

እንደ መግቢያ፡- በመዝገበ ቃላት አተረጓጎም መሠረት “ዲሞክራሲ ማላት በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት ማለት ሲሆን የመጨረሻውም ሥልጣን በሕዝብ ቁጥጥር ስር ያለ፣በቀጥታ በራሳቸው ወይም እነርሱ በወከሉት ወገን ብቻ በሥራ የሚተረጐምና በነፃ ምርጫ ስርዓት የተመረኮዘ ነው” ይላል፡፡ በአብርሃም ሊንከን አባባል “ዲሞክራሲ ከሕዝብ የወጣ ፣በሕዝብ የተመረጠና ለሕዝብ የሚያገልግል መንግስት ነው፡፡”በማለት የሰጠው ትርጓሜ በአብዛኛው ተቀባይነት ያገኝ ሃሳብ ነው፡ሦስቱ መሠረታዊ የመንግስት ምሶሶዎች ተብለው የሚታወቁት ማለትም ሕግ አውጪ፣ሕግ አስፈጻሚ እና ሕግ ተርጓሚ በሁለት መንገድ ሥራቸውን ያከናውናሉ፡፡እነኚኽም አካሄዶች ቀጥተኛ እና የተወካይ ዲሞክራሲ ተብለው ተለይተው ይታወቃሉ ፡፡
ቀጥተኛ ዲሞክራሲ ዜጎች የሚመርጧቸው ምንም ዓይነት ተወካይ አይኖራቸውም፡፡ይህ ማላት ግን አስተዳዳሪ ወይም መሪ የላቸውም ማለት አይደለም፡፡በማናቸውም ጉዳዮች ውሳኔ የሚወስነው በቀጥተኛ የህዝብ ተሳትፎ ነው፡፡ለየትኛውም የህዝበ ውሳኔ ጉዳዮች ፣ዜጎች በጋራ ተሰባስበው በመመክር በአንድ ዓይነት ስምምነት፣ ውይም በድምፅ ብልጫ ውሳኔ የሚያስተላልፉበት ስርዓት ነው፡፡የዲሞክራሲ እናት በመባል የምትታውቀው አቴንስ ከ4 ሺህ እስከ 7ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ስብሰባ በማካሄድ ነበር ቀጥተኛ የሆነ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ተግባራዊ ታደርግ የነበረችው፡፡ይሁን እንጂ ከሕብረተሰብ ብዛት እና ከውስብስብነቱ አኳያ ለቀጥተኛ ዲሞክራሲ ተግባራዊነት የሚሰጠው ጥቅም ውስን በመሆኑ ብዙም ሳይጓዝ እንዲቀር ተደርጓል፡፡በአሁን ወቅት በዓለማችን በአብዛኛው ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የዲሞክራሲ ዓይነት የተወካዮች ዲሞክራሲ ነው፡፡እንዲህ ዓይነቱ ዲሞክራሲ ዜጎች የፖለቲካ ውሳኔዎችን የሚወስንላቸው ተወካዮቻቸውን በመምረጥ ነው፡፡ተመራጮችሁም በበኩላቸው የመረጣቸውን ሕዝብ ወክለው ውስብስብ መንግስታዊ ሥራዎችን እውቀታቸውን፣ጊዜያቸውን እና ጎልበታቸውን ሰውተው ግልጋሎት ይሰጣሉ፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ፡- ከቀጥተኛ ዲሞክራሲ ይልቅ የተወካዮች ዲሞክራሲ ውጤቱ አጥጋቢ ባይሆንም፣ ተግባራዊ ለማድረግ ሙከራዎች ከዚህ ቀደም ተደርጓአል፡፡በተለይ በቀዳማዊ ንጉሳችን ኃይለ ስላሴ የተወካዮች ዲሞክራሲ ወደ አገራችን በማስገባት የዲሞክራሲ በዓላችን እንዲዳብር የተደረገው ጥረት እና ውጤት በታሪክ በአውንታዊ ጎን ተፅፎ የሚኖር ነው፡፡ይሁን እንጂ የተወካዮቹ አመራረጥ እና የሥራ ሂደታቸው ሲለካ ውጤቱ ምን እንደነበር ለታሪክ አዋቂዎች ቢተዉ የተሻለ ይሆናል፡፡ከዚህ ባለፈ በደርግ የተካሄደው የብሔራዊ ሸንጎ እና የኢሕአዴግ የ4 ዙር አገር አቀፍ ምርጫ ለዜጎች ከሰጠው ፋይዳ ይልቅ የአምባገነን ሥርዓት ለማስቀጠል የሰጠው ጥቅም የበዛ ነው፡፡
ከምርጫ 1997 ዓ.ም ወዲህ፣ ገዥው መንግሰት የምርጫን መቃረብ ተከትሎ መንገዶችን ይሰራል፣ የጋራ መኖራይ ቤት ገንብቶ በዱቢ እና በረጅም ወራት ክፍያ ለተጠቃሚዎች ያስተላልፋል፣ለመንግሰት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ያደርጋል፣በአንድ ለአምስት አደረጃጀት በመጠቀም የምረጡኝ ዘመቻ ይጀምራል፣አብዮታዊ ዲሞክራሲ ስልጠናና ጥምቀትን ያካሂዳል፣ዘላቂነት የሌላቸው ጊዚያዊ የሥራ እድሎችን በመፍጠር የሥራ አጦችን ካርድ ይነጥቃል፤ይህ ሣይሆን ሲቀር ኢ-ፍህታዊ ጥቅማ-ጥቅምን በመስጠት ደጋፊን ያበዛል፡፡ በተጨማሪም መቼም የማይፈፀሙ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በየቦታው የመሠረት ድንጋይ በመጣል ዳንኪራ ያስጨፍራል፣ከዚህም በላይ የሆነበትን ደግሞ ቃል ይገባል ፡፡እነዚህና መሰል የሆኑ ሁሉ ነገሮችን ማከናወኑ ለምርጫ ካርድ እንጂ ለዘለቂታዊ ልማት አይደልም፡፡የምርጫ ወቅት ሲቃረብ መንግስት ደፋ ቀና ደፈ ቀና የሚለበት ሥራ ሁሉ ለይስሙላ እንጂ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ እንደሌለው ላለፉት አራት ዙር በተደረጉ ምርጫዎች ለማረጋገጥ ይቻላል ፡፡ በይበልጥ ደግሞ የፊታችን ግንቦት ወር ይካሄዳል የሚባለው ምርጭ በገዥው መንግሰት ቀጥተኛ ተፅኖ ስር በወደቀው ምርጫ ቦርድ እና ፣በመንግስት በኩል መንገስት ስል ኢሕአዴግ ወይም ወያኔ ለማለት እንደተፈለገ ግንዛቤ ይወሰድልኝ፡፡ምክንያቱ ደግሞ ገዥው ፓርቲ እና መንግስት ባልተለያዩበት ሥርዓት ውስጥ በመሆናችን ነው፡፡ስለሀኖም በእነዚህ ሁለት ሃይሎች ተፎካካሪ ወይንም አማራጭ በሆኑ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ይህ-ቀረሽ የማይባል ጫና እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ችግሩ ደግሞ ቀጥተኛ በሆነ መንግድ የሚፈፀም ስለመሆኑ ከዚህ በታች በመጠኑ ለማመላከት ይሞከራል፡፡
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በፓርቲዎች፡-
በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች በሚከተሉው መልኩ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ “ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና ሰብዓዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፡፡በተለይም ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡”የሚል ነው ፡፡
ይህ እጅግ በጣም ጠንካራ የሆነ ዜጎች በፖለቲካ የመደራጀት መብታቸውን የሚያስከበር ዓለም አቀፍ ሕግ ነው፡፡አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገመንገስት ይህን ህግ በመቀበል አካቶ ይገኛል፡፡እርግጥ ነው ህገመንግስቱ በራሱ ማሻሻይን የሚፈልጉ በርካታ አንቀፆች አሉት፡፡በዚህ አጋጣሚ ሰማያዊ ፓርቲ ዜጎችን በጋራ አግባብቶ በዘላቂነት ሊያገለግል የሚችል እና ለሕገመንግሰት መሠረት ወይም ምሶሶ የሚሆን “የዜጎች ቃል-ኪዳን ሰነድ ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ”የተሰኘ ሠነድ በማዘጋጀት ለህዝብ ይፋ ማድረጉ የሚታወቅ ነው፡፡ለዚህም መልካም ጅማሮ ለሰማያዊ ፓርቲ አድናቆት ሊቸረው ይገባል፡፡ወደጉዳያችን ስንመለስ በዓለም አቀፍ እዲሁም በኢትዮጵያ ሕግ የፖለቲካን ዓላማ ለማስፈፀም ሕግን መሠረት ያደረገ አደረጃጀት የተፈቀደ ነው፡፡ይሁን እንጂ ይህን መሰረት ያደረገ አደረጃጀት ኖራቸው በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተቃወሚ ፓርቲዎች፤ ሰብዓዊና ዲሞክራሳዊ መብቶች ይከበሩ፣የሕግ የበላይነት ይረጋገጥ፣ህዛባዊ መንግሰት ይመስረት በማለታቸው እና ለተግባራዊነቱ በመንቀሳቀሳቸው ብቻ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ለሞት፣ለእስራት፣ለስደት እና ለእንግልት እየተዳረጉ ይገኛሉ፡፡
ይህም በመሆኑ አብዛኛው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላቶቺ ታስረዋል፣የመንግሰት ታጣቂ ሃይሎች በግልፅ እና በስውር በፓርቲ አባላት ወከባና እንግልት እየፈፀሙ ይገኛሉ፣ጠንካራ የሚባሉ የተቃዋሚ ሃይሎች የቀን-ተቀን ሥራቸውን የሚያከናውኑበት ቢሮ መከራየት እንዳይችሉ አከራዩች በቀበሌ ካድሬዎች ማስፈራሪያ እና ዛቻ ይደርስባቸዋል፣ከብዙ ልፋት እና እንግልት በኋላ በሚያገኙት ቢሮ የፓርቲ አባላቶች ወደ ቢሮ ሲገብ እና ሲወጡ እየጠበቁ የመንግሰት ደንነቶች ወከባ ከፍ ሲልም ትንኮስ እየፈፀሙ ይገኛሉ፣ ፓርቲዎች ዋንኛ የተቋቋሙለትን ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችላቸውን ማናቸውም እንቅስቃሴዎች ከደጋፊዎቻቸው ጋር በመሆን በነፃነት አደባባይ ወጥተው ቅስቀሳ እንዲሁም ተቃውሞ ማድረግ የሞት ሽረት ትግል ነው፡፡በተለይ ደግሞ አዲስ ተመዝጋቢ አባላት የአባልነታው የእጩ ቀናት መቁጠር ከመጀመራቸው በፊት በመንግሰት ታጣቂ እና በካድሬዎች የሚደርስባቸው ማስፈራሪያ እና ዛቻ ልጉድ ነው፡፡ከምንም በላይ ደግሞ የአባላትን ወራዊ መዋጮ እና ድጋፍ የፓርቲዎች የፋይናስ አቅም አይነተኛ መንግድ ነው፡፡ሆኖም ግን ይህ ገንዘብ በራሱ በቂ አይደለም፡፡ይህም በመሆኑ የፓርቲ አባላት ሣይሆኑ ደግፍ መስጠት ለሚፈልግ ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ በልብ ሙሉነት ገንዘባቸውን እንዳይለግሱ ጫና ይደረግባቸዋል፡፡የጉዳዩ አሳሳቢነት ምን ያኸል እነደሆነ ለማሳያ አነድ ምሣሌ መጥቀስ ይቻልል፤አቶ የሺዋስ አሰፋ፣አቶ አብታሙ አያሌው፣አቶ ደንኤል ሽበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ በማእከላዊ እስር ቤት በዋንኛነት የሚደረግባቸው ምርመራ “የፓርቲያችሁ የገንዘብ ምንጭ ምንድነው ? ማነው በቋሚነት ድጋፍ የሚያደርግላችሁ ?ገንዘቡ የት ነው የሚቀመጠው” የሚሉት ዘወትር የተለያየ የምርመራ ዘዴዎች በመጠቀም የሚጠየቁት ጥያቄ ነው፡፡ነገሩን ይበልጥ አስገራሚ የሚያደርገው ከላይ የተገለፁት የፓርቲ አባለት የተያዙት “በሽብር ወንጀል በመጠርጠር ነው”በማለት ገዥው መንግስት ገልፆአል ሆኖም በምርመራ ወቅት ግን የሚጠየቁት የፓርቲ ገንዘብ ወጪና ገቢ ነው፡፡ በአጠቃላይ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በመሆን ብቻ ነጋዴው ከንግዱ፣ተማሪው ከት/ት፣ሰራተኛው ከስራው፣ገበሬው ከእርሻው፣አርብቶ አደሩ ከከብቶችሁ እየተፈናቀለ ይገኛል፡፡
ስለዚህም ተፈካካሪን የተቃወሚ ፓርቲን በእንዲህ መልኩ እያዳከመ እና አንዳንዶችን በጭራሽ ከወደቁበት እንዳይነሱ እያደረገ ይገኛል፡፡በእንዲህ መልኩ ከሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ጋር ኢሕአዴግ ተፎካካሪ በመሆን ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው እንዴት ሊባል ይቻላል ?
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በምርጫ ቦርድ ፡-
በየደረጃው ትክክለኛ ምርጫ እንዲካሄድ ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 102 ላይ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ሹመታቸው ከመንግስት መልካም ፍቃድ የመነጨ ሲሆን አሰራራቸውም ለገዥው መንግስ በእጅጉ በጣም ያደላ ነው፡፡ስለዚህም ምርጫ ቦርድ ህገመንግስቱን መሠረት አድርጎ ነጻ እና ገለልተኛ ነው ለማለት ከበድ ድፍረትን የሚጠይቅ ነው፡፡የስከዛሬውም የምርጫ ቦርድ የሥራ አንቅስቃሴ ለገዥው መንግስት ያለው ታማኝነት እና አገልጋይነት በድብቅ ሣይሆን በአደባባይ “እዩልኝ፣ስሙልኝ” እያለ በራሱ ላይ መስክሮ የእኛን መስክርነት ከሰጠን አመታት ተቆጠሩ፡፡ከወረዳ የምርጫ አስፈፃሚ ጀምሮ እስከላይ ያለው የምርጫ ቦርድ ሃላፊ፣ በገዥው መንግሰት ቀጥተኛ ተፅእኖ ስር መሆናቸው ግልፅ እና አሻሚ ያልሆነ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ላይ ከዘህ በላይ ማሣያዎችን ለማመላከት መሄድ ዉሃ ቅዳ ዉሃ መልስ ይሆናል ነገሩ፡፡
በመሆኑም ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በአገራችን የለም፡፡ ሃቁ ይህ ሆኖ ሣለ ከተፈካካሪ የተቃወሚ ፓርቲዎች ጋር ኢሕአዴግ ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው ማለት እንዴት ይቻላል ?
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በነፃ በጋዜጠኛ ላይ ፡-
ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ የመግለፅ ነፃነት አለው፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 29 ተፅፎ ይገኛል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት ገደብ ሊጣልበት እንደሚችል በህገ መንግስቱ ላይ ተገልፆ የተቀመጠ ሲሆን ገደብ ግን መሠረታዊ የሆነውን መረጃን የመስጠት እና የማግኘት እንዲሁም አስተሳሰብ ላይ ወይም አመለካከት ላይ ውጤት እንደማይኖረው በህገመንግስቱ ተገልፆ ይገኛል፡፡
ይሁን እንጂ አሳብን በነፃ ማሰብና ማንሸራሸር በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ አሳብን ለመግለፅ ይቅርና ከገዥው መንግስት ፍላጎት እና አሳብ ውጪ ማሰብ በራሱ ለእስራት እና ለእንግልት ይዳርጋል፡፡ጋዜጠኞችን በማሰቃየት፣በማሰር እና እንዲሰደዱ በማደረግ ኢትዮጵያ በዓለማችን መጥፎ ሪከረድ አስመዝግባለች፡፡በአሁን ወቅት ከ17 የማያንሱ ጋዜጠኞች በእስር ቤት እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡፡21 የሚሆኑ ጋዜጠኖች በስደት መከራን እየተቀበሉ ነው፡፡መንግስትን ተችቶ የፃፈና ፁሁፉ የወጣበት ጋዜጣ ወይም መፅሔት ጨምሮ ሁሉም ተጠራርጎ ቃሊቲ የሚገባበት ወይም አደገኛ ዛቻና መስጠንቀቂያ የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡በውጪ አገር የሚገኙ የተለያዩ ሚዲያዎችም ቢሆኑ፣በአገር ውስጥ ተደማጭ እና ተነባቢ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ አፈና እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
ስለዚህም ነፃ አሳብ የሚንሸራሸርባቸው ነፃ ጋዜጦችና መፅሔቶች ምን ያህል አሉ ? በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው አገራዊ ምርጫ ተፈካካሪ ፓርቲዎች የምረጡኝ ዘመቻ ቅስቀሳ የሚያደርጉት በይትኛው ነፃ ጋዜጣ እና መፅሔት ነው ? ህሊናውን እና ሙያውን ብቻ መሠረት አድርጎ የሚሰራ ጋዜጠኛ ምን ያህል አለ ? እርግጥ ይህ ፁሑፍ የቀረበበት ሚዲያ ጋዜጣ በቀጣይ የሌሎች ጋዜጣ እና ጋዜጠኞች እጣ ፈንታ እንደማይደረሰው በምንም እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡በምንም!!
እናም ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ጋዜጠኛ እና የእትመት ውጤት ሣይኖር መርጫ እንዴት ይታሰባል፡፡አገራችን በጋዜጠኛ ድርቅ እንድትመታ ገዥው መንግሰት ሆነ ብሎ ያደረገው መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ይህ በሆነበት ሁኔታ ኢሕአዴግ ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው ማለት በራስ ላይ እንደመተኮስ ይቆጠራል ፡፡

ከላይ በመጠኑ የዚህ ፁሑፍ አቅራቢ ለመዳሰስ የሞከራቸው እና ሌሎች ተመሳሳይ ምክንያቶችን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !

ጎንደር ፦ የህዝቦችን መብቶች የማይወክሉ የወያኔ ሰንደቅ አላማዎች ከሚውለበለቡበት ወረዱ ::
#Ethiopia #Gonder #Kimant #ESAT #MinilikSalsawi #Freedom

– በሰሜን ጎንደር ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘጉ:: ESAT
– በሰሜን ጎንደር ዞን 130 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው አልተገኙም።
– በአድማው የመንግስት መስሪያ ቤቶች ይካተታሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የቅማንት ተወላጆች ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ በተጠራ የስራ ማቆም አድማ በዞኑ የሚገኙ ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ካለፈው አርብ ጀምሮ የተዘጉ ሲሆን፣ መንግስት እስከ መስከረም 30 መልስ የማይሰጥ ከሆነ፣ ተቃውሞው ግብር ባለመክፈል እንደሚቀጥል አስተባባሪዎቹ ለኢሳት ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በርካታ አስተባባሪዎች ተይዘው የታሰሩ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው እስከ መስከረም መጨረሻ መልስ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።

እስካሁን ከ130 ሺ ያላናሱ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው የቀሩ ሲሆን፣ ሌሎች ትምህርት ቤቶችና የመንግስት መስሪያ ቤቶችም በአድማው ይቀጥላሉተብሎ ይጠበቃል። በተዘጉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚውለበለቡ ሰንደቃላማዎች እንዲወርዱ ተደርጓል። ሰንደቃላማዎች እንዲወርዱ የተደረገበት ምክንያት የህዝቦችን መብቶች የሚወክሉ አይደሉም በሚል ነው።

Image

ትናንትና ምሽት አካባቢ ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍኖ የተወሰደው የዞኑ አስተባባሪ እስከአሁን ሰዓት ድረስ ያለበትን ቦታ ማወቅ አልተቻለም፡፡ ትናንት ማምሻውን በሲቪል እና መሳሪያ በታጠቁ የገዢው ፓርቲ ሀይሎች ቤቱ ተበርብሮ ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍኖ መወሰዱን በዞኑ ያሉ የፓርቲው አካላት አረጋግጠዋል፡፡

ከሰማያዊ ፓርቲ የጎንደር ዞን አስተባባሪ አቶ አግባው ሰጠኝ በተጨማሪም ወደ ስድስት(6) የሚደርሱ የአንድነት እና መኢአድ ፓርቲ አባላትም ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍነው መወሰዳቸው ተረጋግጧል፡፡

በሌላ በኩል በጎንደር ባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ከፍተኛ ክትትልና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሆነ የዞኑ ተጠሪዎች አመልክተዋል፡፡

ጋዜጠኛ አንተነህ መርዕድ

በዙህ ጉዳይ ላይ ለመጻፍ በሁለት ምክንያቶች ከራሴ ጋር ብዙ ታግያለሁ። መጀመርያ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም አይደለም ለራሳቸው፤ ለሌላም የሚተርፍ አንደበት አላቸውና ራሳቸው መልስ  ይስጡ በማለት ሲሆን ሁለተኛው ምክንያቴ ደግሞ ትልልቅ አገራዊ ጉዳይ እያለ በዚህ ጠባብ ነገር መጠመድ ለማን ይበጃል በሚል ነበር።በሁለቱም ትክክል አልነበርሁም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡ ‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ […]

የአንድነት ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች መዋቅሩን የዘረጋ ድርጅት ነው። ወደ አምስት ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ በሚኖርባት አዲስ አበባ ፣ ፓርቲው እስከታች በመዝለቅ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድርጅታዊ መዋቅሩን ዘርግቶ የሚንቀሳቀስ ነው። – የአዲስ አበባ ምክር ቤት የተቋቋመው በአዲስ አበባ ከሚገኙ 23 የምርጫ ወረዳዎች በተወከሉ ስድስት ስድስት አባላት ነው። በአጠቃላይ 138 አባላት አሉት። – በ23ቱም የምርጫ ወረዳዎች ፣ […]

“በሽብር” ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የፓርቲ አመራሮች ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት፣ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ፣ የሺዋስ አሰፋ የሰማያዊ ፓርቲ ም/አፈ ጉባኤ፣ መምህርና የአረና ፓርቲ የአመራር አባል አብርሃ ደስታ እንዲሁም የአ/አ ዩኒቨርስቲ የማስትሬት ተማሪ ዘላለም እና ተመሳሳይ መዝገብ የተከሰሱ ሌሎች 5 ግለሰቦች ነገ ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ልደታ በሚገኘው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡ […]

የምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ የአንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ የነበረው አቶ ደረጀ ክበበው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ አቶ ደረጀ በጠና ታሞ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ትላንት ጠዋት በአዳማ ከተማ ቀበሌ 07 በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ያረፈ ሲሆን የቀብር ስነስርዓቱ በትላንትናው ዕለት ከቀኑ በ 7፡00 ሰዓት አዳማ በሚገኘው መድኃኒአለም ቤ/ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ ፓርቲው በአቶ ደረጀ ክበበው ሞት […]

– የመከላከያ እና ፖሊስ ሰራዊቱ ላይ አለመተማመኑ እየጨመረ መጥቷል። – የደህንነት አባላቱ መረጃን በግል ጥቅም በመለወጥ እየሰሩ ነው የሚል ግምገማ ቀርቦባቸው ተንጠዋል። – የሃገሪቱን ጉዳይ በተመለከተ ለበታች “ተከታይ ” ባለስልጣናት መረጃ መስጠት ቆሟል። – የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ አይደሉም ። በኢትዮጵያ ውስጥ መጭው ጊዜ በህዝቡ ዝምታ ተከትሎ በስርአቱ […]