Image

መሐሙድ የሱፍ የተወለደው በ1980ዓ.ም ከሶማሌ ክልል ርእሰ-መዲና ጅጅጋ 500 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውዶሀን ከተማ ነው፡፡ ለቤተሰቡ ሰባተኛ ልጅ ሲሆን፤ አምስት እህቶችእና ሦስት ወንድሞች አሉት፡፡ በጅጅጋ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ መዝለቁቢሳካለትም፤ ከዚህ በላይ ግን ሊቀጥል አልተቻለውም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኢትዮጵያመንግስት የደህንነት ሠራተኞች የ1999ዓ.ም የግንቦት ሃያ በዓል በጅጅጋ ከተማ ስታዲዬም በተከበረበት ዕለት፣ የኦጋዴን ነፃአውጪ ግንባር (ኦብነግ) በሰነዘረው የቦንብ ጥቃት ተሳትፈሃል በሚል ለእስር በመዳረጉነው፡፡ ይህንን ተከትሎምከምድራችን አስከፊ ማሰቃያዎች መካከል ግንባር ቀደም በሆነውና የክልሉ

ነዋሪ “ጄል-አዳብ” (የገሃነም እስር ቤት) እያለ በሚጠራው ማጎሪያ ውስጥ እጅግ በጣም የከፋ ምድራዊ መከራ እንደተቀበለሀዘን በተጫነው ድምፅ ይናገራል፡፡ በሠውነቱ የተለያዩ ክፍሎች ላይ እንደ ፍም ቀልተው የሚታዩት ጠባሳዎቹም ያሳለፈውንሥቃይ አፍ አውጥተው ይመሰክራሉ፡፡ ለአራት ወራት ያህል አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻው ተቆልፎበት፤ ሃያ አራት ሠዓታትሙሉ እጆቹ በካቴና ተቀፍድደው፣በቀን ከአምስት ጊዜ በላይ ለምርመራ እየተጠራ ያለዕረፍት ከባድ ስቅየት (ቶርቸር)ሲፈፀምበት ቆይቷል:፡ በመጨረሻም ለአንዲትም ቀን የፍርድ ቤት ደጅ ሳይረግጥ፣ ለኦብነግ አባላት አንድ ፓኬት ሲጋራሲያቀብል እጀ-ከፈንጅ ተይዟል በሚል ክስ የጅጅጋ ዞን ፍርድ ቤት በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን እዛው እስር ቤት ሆኖከኢትዮጵያ ሬዲዮ የዜና እወጃ እና ከቪኦኤ ሶማሊኛ ፕሮግራም ሠምቷል፡፡

ከፍርዱ በኋላም በተመሳሳይ ወንጀል ከተከሰሰ አንድ እስረኛ ጋር በካቴና ተጠፍሮ በቀን አንድ እንጀራ ለሁለት ተካፍሎእንዲበላ እንደ ውሻ እየተወረወረለት 60 ቀናትን አሳልፏል፡፡ መሐሙድ በተለይም በእንቅልፍ ወቅት እርሱ ወይምየሰንሰለት ደባሉ የተገላበጠ እንደሆነ ካቴናው የሚያደርስበትን የመለብለብ ቃጠሎ ሲያስታውስ ዓይኖቹ በእንባ ይሞላሉ፡፡በአሁኑ ወቅት በዝዋይ ማጎሪያ ከባድ ጥበቃ ለሚደረግባቸው ብቻ በተመደበ ‹‹ዘጠነኛ ቤት›› ውስጥ አስራ አንድ ሶማሊኛተናጋሪዎችን ጨምሮ በድምሩ ሰላሳ አራት ሰዎች ጋር ከዛሬ ነገ የግፍ ፍርዱ ተፈጻሚ ሊሆንብኝ ይችላል በሚል ሰቀቀንእየባነነ በስጋት ተጠፍንጎ መኖር ከጀመረ እነሆ ሰባት ዓመት ሊደፍን ሦስት ወራት ብቻ ቀርተውታል፡፡

የተዋረደው የፍትሕ ሥርዓት!. . .

ርግጥ ነው ይህ በጨረፍታ ያቀረብኩት አሳዛኝ ታሪክ የመሐሙድ የሱፍ ብቻ አይደለም፡፡ ሌሎች ሰባት ‹‹አባሪዎቹ››ስቃዩንም ሆነ የሞት ፍርዱን ይጋሩታል (በነገራችን ላይ በአንድ መዝገብ የተወነጀሉት እነዚህ ስምንት የሞት ፍርደኞች፡-መሐድ ኢብራሂም፣ አረብ ሰዋኔ ዱልባንቲ፣ ሐሰን መሐመድ ዑስማን፣ ሐሰን መሐመድ ዓሊ፣ ሙክታር መሐመድ ዓብዱላሂ፣ከድር ሽኩር ሙሳ እና ካሚል ዓብዱልናስር እንኳን በጋራ መንግሥት ላይ ሊያሴሩ ቀርቶ እርስ በርስም የተዋወቁት እስር ቤትውስጥ ነው፡፡ ከጅጅጋ ወደ ዝዋይ ‹‹ዘጠነኛ ቤት›› ተዘዋውረው በርካታ ዓመታትን ያሳለፉትም በጭካኔው ወደርእንደማይገኝለት የሚነገረው የክልሉ ፕሬዚዳንት አብዲ

በአደራ እንዲቀመጡ በመተላለፋቸው መሆኑን ነግረውኛል፡፡) እንደ መሐሙድ ሁሉ እነርሱም ፍርድ ቤት ቀርበውአያውቁም፤ ምንም ዓይነት የሰውም ሆነ የሰነድ ማስረጃ አልተቆጠረባቸውም፡፡ እዚህ ጋ የማነሳው አሳዛኝ ገጠመኝከመካከላቸው አንዳቸውም ራዲዮ ስላልነበራቸው የተጣለባቸውን የሞት ፍርድ ውሳኔ የሠሙት፣ ዜናው ከተላለፈ ከበርካታቀናት በኋላ ሬዲዮ ካላቸው እስረኞች መሆኑ

ነው፡፡ ይህ እጅግ አሳፋሪና አስደንጋጭ መንግሥታዊ ውንብድና በደንብ ይብራራ ዘንድ ለተከሳሶቹ ከተሰጣቸው ባለ አንድገፅ የክስ ቻርጅ የሁለቱን ብቻ በአዲስ መስመር እጠቅሳለሁ፡-‹‹በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ አቃቤ ሕግና ፍትሕቢሮ በሶማሌ ክልላዊ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት

ጅጅጋ

የዐ/ሕግ/መ/ቁ 90/2000

ዝዋይ እስር ቤት ያለው

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከሳሽ፡- ዐ/ሕግ

ተከሳሽ፡- ሐሰን መሐመድ ዑስማን (ሐንን መድቤ)

ዕድሜ፡- 21

ሥራ፡- ተማሪ

አድራሻ፡- ጅጅጋ ከተማ፡- 06 ቀበሌ

ወንጀል

በ1996ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ.መ.ሥ.ሥ.ህ.ቁ. 240(3) እና 251(መ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣

የወንጀል ዝርዝር

ተከሳሽ ከመስከረም 1999 ዓ.ም. ጀምሮ እራሱን ኦ.ብ.ነ.ግ. እያለ ከሚጠራው ተቃዋሚና አሸባሪ ድርጅት ጋር በራሱፈቃድ

በዚሁ በጅጅጋ ከተማ ከላይ በተጠቀሰው ዓመተ-ምህረት አባል በመሆን በጫካ በዚሁ አካባቢ ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋርበከተማም

ሆነ በጫካ በመገናኘት በኢኮኖሚ ረገድ የሚያስፈልጋቸውን፡- ጫማ፣ ልብስ የመሳሰለውን እዚያው ድረስ ሄዶ በማቀበልአብሮ

ሲንቀሳቀስ በመቆየቱ ተከሶ ቀርቧል፡፡››

ሁለተኛው የክስ ቻርጅ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፡-

‹‹በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ አቃቤ ሕግና ፍትሕ ቢሮ

በሶ/ክ/መ/ ጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት

ጅጅጋ

የዐ/ሕ/መ/ቁ 90/2000

ከሳሽ፡- ዐ/ሕግ

ተከሳሽ፡- መሐድ ሼክ ኢብራሂም

ዕድሜ፡- 28

ሥራ፡- የለውም

አድራሻ፡- ጅጅጋ ከተማ፡- ቀበሌ 05

1ኛ ክስ

ወንጀሉ

በ1996 ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ/መ/ህ/ ቁ. 241 እና 251(መ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣

የወንጀሉ ዝርዝር

ተከሳሹ በ1998 ዓ.ም. ወራትና ቀኑ በውል ካልታወቀ ጊዜ ጀምሮ እራሱን ኦ.ብ.ነ.ግ. እያለ ከሚጠራው ተቃዋሚ የፖለቲካ

ድርጅትና አሸባሪ ጋር በራሱ ፈቃድ አባል በመሆን ከዚህ ሕገ-መንግሥቱን ከሚፃረር ድርጅት በቀጥታ ፌዴሬሽኑእንዲከፋፈል፣ ክልሉን

የመገንጠል ዓላማ ለማሳካት ይህንኑ ድርጅት ከዚሁ በጅጅጋ ከተማ ለጊዜው ካልተያዘ ግብረ-አበሩ ጋር በመሆን ይህንኑአሸባሪ ድርጅት

በሚያስፈልገው ማቴሪያል ሁሉ፡- ጫማ፣ የፖሊስ የደንብ ልብስ፣ መድሃኒት. . . የመሳሰለውን በማቀበሉ፡፡

2ኛ ክስ

ወንጀሉ

በ1996ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ/መ/ህ/ ቁ. 36 (ለ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣

የወንጀሉ ዝርዝር

ተከሳሹ ከ1996 ዓ.ም. ጀምሮ የተለያዩ መ/ቤቶች ማለትም፡- የክልሉ ት/ቢሮን፣ የቀብሪ-ደሐር ት/ቢሮን፣ እንዲሁም የMSF

እና የተለያዩ መሥሪያ ቤቶችን እና የትምህርት ተቋማትን ማህተም በማስመሰል አትሞ እና የኃላፊዎችን ፊርማ ዓይነትአስመስሎ

በማስፈር ሐሰተኛ ሰነድ አዘጋጅቶ በመገኘቱ ተከሶ ቀርቧል፡፡››

(ሁሉም የክስ ቻርጆች ማኅተም እና አንጋው አፈወርቅ ምንተስኖት የተባለ የክልሉ ዐቃቤ ሕግ ፊርማ አላቸው)

እነሆም ያለአንድ ምስክር፣ ያለምንም የሰነድ ማሰረጃ፣ አንድም ቀን ችሎት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃል ሳይጠየቁ እና

ሳይከራከሩ (ያውም የዞን ፍርድ ቤት) በነዚህ በስም በጠቀስኳቸው በስምንቱ ኢትዮጵያውን ላይ የሞት ቅጣትን የመሰለየመጨረሻ

ውሳኔ እንደቀልድ አስተላልፎባቸዋል፡፡ (በነገራችን ላይ ሌሎች 13 የኢትዮጵያ-ሶማሌ ተወላጆችም በተመሳሳይ የሐሰትውንጀላ የዕድሜ

ልክ እስር ተፈርዶባቸው ዝዋይ ይገኛሉ፡፡ የሚገርመው ጉዳይ ደግሞ ም ቢሆኑ መጀመሪያ ተጠርጥረው በተያዙበት ወንጀልአይደለምየተጠየቁት፡፡ ጉዳዩ ጭራሽኑ በምርመራም ወቅት አልተነሳም) መቼም በዚህ መልኩ በተቀናበረ የውሸት ክስ ከ20-27 ዓመት የሚገኙ

ወጣቶችን በሲኦላዊ እሳተ-ነበልባል ስቅየት ውስጥ እንዲያልፉ ከማድረግም በዘለለ፣ ብሩህ ቀናቸውን አጨልሞ ላይመለሱወደመቃብር

የሚሸኝ ቅጣት ሲጣል ከመመልከት የበለጠ የትኛውንም ዜጋ የሕሊና ስቃይ ውስጥ ከትቶ፣ አንገት አስደፍቶ፣ በቁጣ ቀስቅሶ

ወደአደባባይ የሚያወጣ ገፊ-ምክንያት አለ ብዬ አላምንም፡፡

ማነው ተጠያቂው?

በእነዚህ ንፁሃን ኢትዮጵያውያን ላይ ‹በጄል-አደብ› የደረሰባቸው በነውረኝነት የታጀለ ኢ-ፍትሐዊ ፍርድ እና ስቅየት፣

የሥርዓቱን እውነተኛ ማንነት ገሃድ የሚያወጣ ተጨባጭ ተግባር መሆኑ ባይካድም፡ ይህንን አረሜናዊ ድርጊት በፊት-አውራሪነት

የመሩት፡- ኮሎኔል ሞኒ መንገሻ በጊዜው የክልሉ የፀረ-ሽብር ግብረ-ኃይል ዋና ኃላፊ የነበረ አሁን ወደአዲስ አበባ ተቀይሮ‹ሕገ-ወጥ

የሠው ዝውውር ወንጀል መከላከል› ኃላፊ፣ ቢኒያም የተባለ የክልሉ የደህንነት ኃላፊ፣ ሻለቃ ዘገየ በክልሉ የፌዴራል ፖሊስኃላፊ፣

ወልደአራዌ የክልሉ ፖሊስ ም/ኮሚሽነር፤ እንዲሁም ሻለቃ ወንድሜ፣ ሻለቃ በለጠ እና ታሰረ የተባሉ ኃላፊነታቸውንለይተው

የማያስታውሷቸው ግለሰቦች መሆናቸውን ግፉአኖቹ በተሰበረ ልብ፣ ምሬት በሞላው ድምፅ፣ ተስፋ በቆረጠ ስሜትሲተርኩልኝ ዓይኖቼ

ላይ የተቋጠረው የእንባ ከረጢት ገንፍሎ እንዳይፈስ ብርቱ ትግል ማድረጌን አልሸሽግም፡፡

የሆነው ሆኖ እነዚህ የሥርዓቱ ሹማምንት የፍርድ ቤት ደጅ ሳይረግጡ፣ የሞት ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ባደረጓቸው

ምስኪኖች ላይ የማሰቃያ ጥበቦቻቸውን በሙሉ ከሞከሩባቸው በኋላ፡- ‹‹ሞት እንፈርድባችኋለን!!›› እያሉ ያስፈራሯቸውናይዝቱባቸው

ነበር፤ እነርሱም፡- ‹‹እናንተ ፍርድ ቤት ናችሁ እንዴ?›› ብለው በግርምትና ባለማመን ሲጠይቋቸው፣ ማናአህሎኝነትያሳበጣቸው የፀጥታ

ኃላፊዎች እንዲህ በማለት አስረግጠው መልስ መስጠታቸውን ሰምቻለሁ፡-

‹‹አዎን! ፍርድ ቤት ማለት እኛ ነን!!››

በርግጥ ከዚህ ሁሉ መከራ በኋላ የተላለፈባቸው ውሳኔ፣ ያውም በሞት እንዲቀጡ የሚል መሆኑን ስናስተውል የዛቻውን

መነሾ መረዳቱ አዳጋች አይሆንብንም፡፡ በአናቱም በምርመራ ወቅት ዕድል ፊቷን ያዞረችበትን ተጠርጣሪ እዛው እስረኛ ፊትበሽጉጥ

ግንባሩን በርቅሰው እንደ መናኛ ነገር ሜዳ ላይ ይዘረጉት እንደነበረ የዓይን እማኞች ይመሰክራሉ፡፡

በጥቅሉ ይህ ሁነት በሀገሪቱ አለቅጥ የተንሰራፋውን የፍትሕ እጦት፣ የሠብአዊ መብት ጥሰት፣ ዳኞች ከሕግ ይልቅ ከቤተ-

መንግሥት በሚላክላቸው የፍርድ ውሳኔ ንፁሃኑን ለምድራዊ ስቃይ ከመዳረግም አልፈው ተርፈው በጭካኔሕይወታቸውንም

እንደሚነጠቁ በቂ ማስረጃ ይመስለኛል፡፡

‹‹ጄል-አዳብ››

የክልሉ ኗሪዎች ‹‹ጄል-አዳብ›› (የገሃነም እስር ቤት) እያሉ የሚጠሩት የጅጅጋው ማሰቃያ ቤት ክፍሎች የተሠሩት አራትመቶ

ታሳሪዎችን እንዲይዙ ታስቦ ቢሆንም፣ አብዛኛውን ጊዜ ከአራት ሺህ በላይ ታሳሪዎች እንደሚታጎሩበት አረጋግጫለሁ፡፡ይህም አንድ

ሰው ከአንድ ሰዓት በላይ በእንቅልፍ ማሳለፍ እንዳይችል አድርጎታል፡፡ ምክንያቱም ቦታውን ለተረኛው የመልቀቅ ግዴታአለበትና፡፡

ምናልባት እንቅልፍ ቢጥለው እንኳ ተረኞቹ ቀስቅሰው (ጎትተው) ያስነሱታል፡፡

ከ‹‹ጄል-አዳብ›› በሕይወት ተርፎ የሚወጣ ሰው ዕድለኛ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ በዚህ ቦታ ከቤተሰብ ጋር መገናኘት ጭራሽ

አይሞከርም፡፡ ማሰቡ እንኳ እንደ ቅንጦት ነው የሚታየው፡፡ በእስር ቤቱ አጥር ሦስት መቶ ሜትር ክልል ርቀት ዙርያ ውስጥመገኘትም

ለከባድ ስቃይ (አንዳንዴም ለሞት ቅጣት) ይዳርጋል፡፡ በሃያ አራት ሰዓት አንዴ፣ አንድ እንጀራ ለሦስት እየተቃመሱለአምስት ዓመት

በዛ እስር ቤት ያሳለፈ ምስኪን አጋጥሞኛል፡፡ ይህ ወጣት በ2004ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ሦስት ዓይነት ተላላፊ በሽታ(ተቅማጥ፣

ሰውነትን የሚያሳክክና ጉሮሮን አሳብጦ ለአዕምሮ መቃወስ የሚዳርግ) ተከስቶ በቀን እስከ አስራ አራት ሰው ድረስ ይሞትእንደነበር

ያስታውሳል፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ሕክምና ብሎ ነገር አልነበረም፡፡ እንዲያውም በግልባጩ የክልሉ አስተዳዳሪዎችጭካኔያቸውን (ኢ-

ሠብአዊነታቸውን) ወለል አድርገው የሚያሳብቁ ድርጊቶች መፈፀማቸውን አላቋረጡም፡፡ ለማሳያ ያህልም እስረኛው ከሌሊቱስድስት

ሰዓት ላይ በአንድ ድምፅ እንዲህ የሚል መፈክር እንዲያሰማ መገደዱን እዚህ ጋ መጠቀስ ይቻላል፡-

‹‹መለስ ዜናዊ ሐኖላዶ!›› (መለስ ዜናዊ ለዘላለም ይኑር!)

‹‹አብዲ ሑመድ ዑመር ሐኖላዶ!››

‹‹ኢትዮጵያ ሐኖላዶ!››

ኦብነግ ሐዳኦዶ!›› (ኦብነግ ይውደም!)ሌላው አስገራሚ ጉዳይ ቤተሰብ ታሳሪ ልጁ በሕይወት ይኑር ይሙት የሚያውቀውከማጎሪያው በስንት ጊዜ አንዴ የሚፈታ

ሰው ሲገኝ ብቻ የመሆኑ እውነታ ነው፡፡ እናም ድንገት በአንዲት ‹ዕድለኛ› ቀን አንድ ታሳሪ ከ‹‹ጄል-አዳብ›› የተለቀቀእንደሆነ ወሬው

ከመቅጽበት ይዛመትና ለሳምንታት አሊያም ለወራት የእስረኛው ቤት በእንግዶች እስከ አፍ-ገደፉ ጢም ብሎ ይውላል፡፡የተለመደ

ነውና እሱም ያለመታከት የቀረበለትን ጥያቄ በሚከተለው መልኩ ሲመልስ ይከርማል፡-

‹‹ኦ!… እገሌ ከሞተ እኮ ሁለት ዓመት አለፈው›› ፤ “እገሌማ ሲያሳዝን! ካረፈ ገና አንድ ወሩ ነው”፤ “ኦ! እገሌ ለወደፊቱ

እግዜር ይጠብቀው እንጂ እስካሁን በሕይወት ይገኛል…” ወዘተ ወዘተ. . .

አንዳርጋቸው እንዴት ከወያኔ እጅ ሊገባ እንደቻለ ዛሬም ድረስ ግልፅ መረጃ የለም። የተለያዩ መላ ምቶችን እየሰማን፣ እያነበብን ቆይተናል። አንዳርጋቸውን በቅርብ ከሚያውቁት አንዱ እንደመሆኔ እኔም ካለኝ መረጃ በመነሳት የራሴን ግምት መውሰዴ አልቀረም። የኔን ግምት ይፋ ከማድረጌ በፊት ሌሎች የሚሉትን ለመስማት በሚል እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ ሳልፅፍ ቆይቼ ነበር። አሳማኝ መረጃ ሳይፃፍ ወይም ሳይገለፅ ጊዜው ስለረዘመ እነሆ! እኔም የግል አስተያየቴን ለማኖር ወሰንኩ… (ቅዳሜ ለንባብ ይበቃል)

በቦረና ዞን ገላን ወረዳ የአንድነት አባላት መታሰራቸውን ከአከባቢው በደረሰን ሪፖርት አረጋግጠናል። የታሳሪዎቹ ስም ዝርዝር አቶ በድሉ መንግስቱ በቦረና ዞን ገላን ወረዳ ሰብሳቢ፣ አቶ ቆንጨሪ ሳፋይ አባል አቶ ንጉሴ ገልገሎ አባል አቶ ብርሃኑ ሳፋይ አባል ሲሆኑ፤ ሰብሳቢው አቶ በድሉ መንግስቱ የታሰሩት የመንግስትን ስም አላግባብ አጥፍተሀል ተብለው ነው። በተያያዘ ዜና በምስራቅ አሩሲ የኦሆዴድ አባል፣ የጢዮ ወረዳ የሲቪል […]

ኢትዮጵያችን ከምትታወቅባቸው ዘርፈ ብዙ ገዥ- ወለድ ችግሮች መካከል ስደት አንዱ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ዜጎቻችን በሀገራቸው ላይ ሰርተው የመኖር ዋስትና በመነፈጋቸው፤ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው እናስተዳድራችኋለን በሚሉ ገዥዎች በመጨፍለቁ የተሸለ ነፃነትና ኑሮ ፍለጋ እግራቸው በመራቸው መሰደድ የተለመደ ሁኗል፡፡ ገዥው ፓርቲም ከራሱ የስልጣን ቆይታ በስተቀር ሀገራዊ አደጋ እየሆኑ የመጡና የዜጎችን ስነ-ልቡና የሚጎዱ ሁነቶችን እንደማንኛውም ዜጋ አድማጭ ከመሆን በዘለለ ችግሩን […]

የታሰሩ እንዲፈቱ በፖለቲካ ድርጅቶች ላይ የሚደረገው ወከባና ጫና እንዲቆም በመግለጫው ጠይቋል::
http://www.andargachewtsige.com/?p=343

Image

በሰሜን ምሥራቅ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ውስጥ እየደረሰ ያለዉ ጥቃት ማሕበረሰቡን ከፍተኛ ስጋት ላይ እደጣለዉና መፍትሄ አልባ እንዳደረገዉ ተገልፆአል። የሲቪሉ ማሕበረሰብ ድርጅቶች አማፅያን የሚያደረሱት ጥቃት ለመከላከል የዓለም አቀፉን ርዳታ ጠይቀዋል።

በ  
የአንድ ዓመት ዕድሜ ያለውን ህፃን ልጇን ተሰድቤበታለሁ፤…

ዛሬ ዛሬ ከረጅም አመታት ጀምሮ በሃገራችን የተነሳው የሴቶች መብት ይከበር የሚለውን ይህዝብ ጥያቄ ለመቃረን እስኪመስል ድረስ ከባለፉትም ጊዜያቶች በባሰ ሁኔታ የሴቶች መብት እየተጣሰ ይገኛል። ከዛም አልፎ ተቆርቋሪ አካል የሌላቸው የሃገራችን ሴቶች ህይወታቸው አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል። ለዚህም በየጊዜው ወደ ተለያዩ አፍሪካና አረብ ሃገራት በተለይም በሱዳን በየመን የሚፈልሰው የኢትዮጵያውያን ሴቶ ች ቁጥር መጨመር ማረጋገጫ ነው። በተለያዩ […]


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
ብዙዎቻችን በስርቅርቅ ድምጻቸው እናውቃቸዋለን፡፡ እጅግ በተዋጣለት የኦርኬስትራ ቅንብር በመታጀብ የተጫወቷቸው ጥዑም ዜማዎች  በአዕምሮአችን ላይ ተቀርጸዋል፡፡ እኔ ጸሐፊው ሙዚቃቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁበትን አጋጣሚ አላስታውስም፡፡ ሆኖም የነርሱን ዘፈን በምሰማበት ጊዜ ሁሉ ሶስት ነገሮች ይታወሱኛል፡፡
   የመጀመሪያው ከተማችንን (ገለምሶን) ለሁለት ከፍሎ የሚያልፈውን አውራ ጎዳና ተከትለው ከተደረደሩት ሻይ ቤቶች ይንቆርቆር የነበረው የእንስቶቹ ዝማሬ ነው፡፡ በተለይም የሻይ ቤቶቹ ባለቤቶች በበርካታ የህብረተሰብ ክፍል እንደ ህብረ-ዜማ ይዘፈን የነበረውን “መሼና መሼና”ን እየደጋገሙ ማጫወታቸው የየዕለቱ ትዕይንት ሆኖ እንደቆየ አስታውሳለሁ፡፡ ሁለተኛው አይረሴ አጋጣሚ የተከሰተው በትምህርት ቤት ቆይታዬ ነው፡፡ በ1980 የአምስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ከለገዳዲ ሬድዮ ጣቢያ የሚተላለፈውን “የህብረተሰብ ትምህርት በሬድዮ” ለማዳመጥ በሄድንበት አንድ ጠዋት “ተማሪዎች፤ የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆነችውን ሱዳንን ታውቋታላችሁ?” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ትምህርት ተሰጠን፡፡ የሬድዮ ትምህርቱን የሚያቀርበው ባለሙያ “ሱዳን፣ በአፍሪቃ ትልቅ ሀገር ናት፤ ስፋቷ ወደ አንድ ሚሊዮን ስኩዌር ማይልስ ይጠጋል፤ ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው” እያለ በሚያስተምርበት ጊዜ በየአፍታው እንደመሸጋገሪያ አድርጎ የተጠቀመው እንስቶቹ “ለውነል መንጋ” እያሉ የሚያዜሙትን ተወዳጅ ዘፈን ነበር፡፡ ያንን ዘፈን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት በዚያች ዕለት ነው፤ ከዚያ በኋላ ከጭንቅላቴ ላወጣው አልቻልኩም፡፡
  ሶስተኛው አጋጣሚ በ1984 በአንዲት የማክሰኞ ምሽት ነው የተከሰተው፡፡ በዕለተ ማክሰኞ ሲገበያይ የሚውለው የከተማችን ህዝብ የቀኑን ድካም ለማራገፍ ሲል ምሽት ላይ እራቱን ከበላ በኋላ ሆጃና ሻይ አፍልቶ ለበርጫ መሰየሙ የተለመደ ነገር ነው፡፡ እኔም በዚያች የማክሰኞ ምሽት አብዱልቃዲር ከተባለ ዘመዳችን ሱቅ ሄድኩና ከጥቂት ጓደኞቹ ጋር በርጫውን ሲያስኬድ አኘሁት፡፡ አብዱልቃዲር ለበርጫው ማሟሟቂያ የመረጠው የእንስቶቹን ተወዳጅ ካሴት ነው፡፡ በተለይም ደግሞ “ኡሸ ሰጊራ፣ ኪፋያ ዐለይና” የተሰኘውን ዘፈን ይደጋግመው ነበር፡፡ እኔም የአብዱልቃዲር ሁናቴ አስገርሞኝ ስለእንስቶቹ እንዲያጫውተኝ ጠየቅኩት፡፡ እርሱም የዘፋኞቹን ማንነትና የሙዚቃ ጉዞአቸውን እያዳነቀ ተረከልኝ፡፡ እንግዲህ በዚያች አጋጣሚ ነው ስማቸውን ለመያዝ የበቃሁት፡፡
*****
አዎን! የኢትዮጵያን ሙዚቃ አውቃለሁ የሚል ሰው ሶስቱን የሱዳን ድምጻዊያን በደንብ ነው የሚያውቃቸው፡፡ እነዚህ እንስቶች እህትማማቾች ናቸው፡፡ ትክክለኛ ስማቸውም “ሐያት”፣ “አመል” እና “ሃዲያ” ነው፡፡ በዓለም ዙሪያ በደንብ የሚታወቁት ግን “አል-በላቢል” በተሰኘው የቡድን ስማቸው ነው (በዐረብኛ “አል-ባቢል” ሲባል “ዘማሪ ወፎች” እንደማለት ነው)፡፡ በምስራቅ አፍሪቃ የሙዚቃ ታሪክ የነርሱን ያህል የሚታወቅ የሴት ድምጻዊያን ቡድን የለም፡፡
“አል-በላቢል” በሰሜን ሱዳን በዋዲ-ሃልፋ ከተማ ነው የተወለዱት ነው፡፡ የአፍ-መፍቻ ቋንቋቸው “ኑቢያ” ነው፡፡ ሙዚቃን በዋዲ ሃልፋ ቢጀምሩትም ከእውቅና ማማ ላይ የወጡት ግን በካርቱም ከተማ ነው፡፡ በተለይም እንስቶቹ እ.ኤ.አ ከ1974-እስከ 1982 በነበረው ዘመን በሱዳን ሙዚቃ ላይ ነግሰው ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ያወጧቸው “መሼና”፣ “ሙትዓሉ ዐለይና”፣ “ሸባብ አንኒል”፣ “ዑሸ ሰጊራ”፤ “ለውነል መንጋ”፣ “ሒልዊን ሐለዋ”፣ “ጣኢረል ጀንና” የመሳሰሉት ዘፈኖቻቸው ዘመን ተሻግረው እስከ ዛሬም ድረስ ይደመጣሉ፡፡
  የአል-በላቢል አዕዋፋት ዝና በምድረ-ሱዳን ብቻ አልታቀበም፡፡ ከካይሮ እስከ ሞምባሳ፣ ከበርበራ እስከ ባማኮ (ማሊ) ባሉት የአፍሪቃ ከተሞች የሚኖሩ የሙዚቃ አፍቃሪዎች በስራቸው ተማርከውላቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ፣ በግብጽ፣ በሶማሊያ፣ በጅቡቲ፣ በቻድ፣ በኬንያ፣ በናይጄሪያ፣ በአልጄሪያ፣ በማሊና በሌሎችም የአፍሪቃ ሀገራት ሙዚቃዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአውሮጳና በአሜሪካም ተዟዙረዋል፡፡
*****
ሆኖም ሶስቱ እንስት ከ1986 በኋላ የሙዚቃ ስራቸውን በአንድ ላይ ለመቀጠል አልቻሉም፡፡ ትልቋ “ሐያት” እና ሁለተኛዋ ሃዲያ በጋብቻ ምክንያት ሱዳንን በመልቀቃቸው ብዙዎች ያደነቁላቸው የቡድን ስራቸው በመንገድ ላይ ቀረ (ሐያት በአሜሪካ፣ ሐዲያ ደግሞ በባህሬን ይኖሩ ነበር)፡፡ ሆኖም የሱዳን ህዝብ እንዲሁ አልተዋቸውም፡፡ እንስቶቹ በአንድ ላይ ተሰባስበው ስራቸውን እንዲሰሩ በልዩ ልዩ መንገድ ጫና ሲያደርግባቸው ነበር፡፡ እነርሱም ለህዝቡ ውዴታ በመሸነፋቸው በድጋሚ በመሰባሰብ የሙዚቃ ስራቸውን ማቅረብ ጀምረዋል፡፡
    ታዲያ አል-በላቢል በድጋሚ የቡድን ስራቸውን በጀመሩበት የአውሮጳዊያኑ 1998 አጋማሽ ላይ የለቀቁት “ኩልለ-ኑጁም” የተሰኘው አልበም በዓለም ዙሪያ በእልፍ አዕላፍ ቅጂዎች ነው የተሸጠው፡፡ የሱዳን የሙዚቃ ኤክስፐርቶች በዚያ አልበም የተካተቱትን ስራዎች ከሀገሪቱ የምንጊዜም ተወዳጅ ዜማዎች መካከል ደምረዋል፡፡ በተለይም የአልበሙ መጠሪያ የሆነው “ኩልላ-ኑጁም” የተባለው ዜማ ከሱዳን አልፎ በውጪው ዓለም (በጀርመን) ለሽልማት አብቅቶአቸዋል፡፡ የአውሮጳ ህብረት በበኩሉ ታህሳስ 11/ 2013 ባዘጋጀው ልዩ ዝግጅት እህትማማቾቹ ለሱዳን ሙዚቃ እድገት ላደረጉት አስተዋጽኦ ዓለም አቀፍ ሽልማት ሸልሞአቸዋል፡፡ እንስቶቹ የምታዩትን ፎቶግራፍ የተነሱት ሽልማቱን በተቀበሉበት ወቅት ነው፡፡
*****
አል-በላቢልን በሌላ ቀን እንዘይራቸዋለን፡፡ ለዛሬ ግን በኛ ሀገር በስፋት የሚታወቀውን “መሼና”ን እንገባበዝና እናብቃ፡፡
 መሼና መሼና መሼና
ቢጠሪቀል ሑብቢ መሼና
አዕዛቡ ያ ናር አልጊና
መሼና መሼና መሼና…
(እህትማማቾቹ መሼናን ሲዘፍኑ ለማየት የሚከተለውን ሊንክ ይክፈቱ)፡፡
—–
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 4/2007
ገለምሶ-ምስራቅ ኢትዮጵያ
—-
The writer, Afendi Muteki, is a researcher and author of the ethnography and history of the peoples of East Ethiopia.  You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click the following link to go to his page.

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክር ቤቱ ህዳር 30/ 2007 ዓም ባወጣው መግለጫ “በሀገራችን ህዝባዊ ሥርዓት ለማምጣትና በህግ የበላይነት የሚያምን መንግስት ለመመስረት በምናደርገው ትግል ሁሉ የሚጠበቅብንን መስዋእትነት ለመክፈልና ሀገራዊ ግዴታችንን ለመወጣት ዝግጁ” ነን ብሎአል። “ሰማያዊ ፓርቲን ጨምሮ ዘጠኝ ትብብር የፈጠሩ ፓርቲዎች በህዳር ወር ያወጡት መርሐ ግብር አንድ አካል የሆነውን የ24 ሰዓት የተቃውሞ የአደባባይ …

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንዳንድ ተጓዞች ለኢሳት እንደገለጹት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚታየው ፍተሻ ጨምሯል። ከዲላ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ ተሳፋሪ ለኢሳት እንደገለጸው ፖሊሶቹ ተሳፋሪውን ወዴት ነው የምትሄዱት? ለምንድነው የምትሄዱት በማለት ከመጠየቅ ጀምሮ የሰዎች ኪሶች በመግባት ፍተሻ ያደርጋሉ። በሽተኞችንና ህጻናትን የታቀፉ እናቶች ሳይቀሩ ፍተሻ በሚል ፖሊስ ጣቢያ ታጉረው መዋላቸውን …

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ወደ የመን ሲጓዝ የነበረ ጀልባ ሰጥሞ ከ79 ያላነሱ ኢትዮጵያዊያን ያለቁ ሲሆን እስካሁን ከ14 ያልበለጡ ሰዎች ብቻ አስከሬን መገኘቱን ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት ገልጿል። የሟቾች ቁጥር አስቀድሞ በመገናኛ ብዙሃን እንደተገለጸው ሳይሆን 79 መሆኑን ግሩም አክሎ ተናግሯል። በሌላ በኩል ደግሞ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕጋዊ ጉዞን ከአንድ ዓመት በላይ አግዶ …

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት  አስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት በካውች ማሞና ኦብዱል ኦቻር የሚባሉትን ባለስልጣኖች አውርዷቸዋል። ግለሰቦቹ ያለመከሰስ መብታችን የተነሳው በህገወጥ መንገድ ነው በማለት ወደ አዲስ አበባ ተጉዘው የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትን ለማግኘት ሙከራ ቢያደርጉም፣ ደህንነቶች ይዘው አስረዋቸዋል። ባለስልጣኖቹ ከውጭ ሃይሎች ጋር ትገናኛላችሁ በሚል መከሰሳቸውን የአኝዋ ሰርቫይቫል ዋና ሃላፊ አቶ ኒካው …

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጋቢያችን በአራት ኪሎ፣ በቦሌ፣ በካዛንቺስ፣ በልደታ አካባቢዎች የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎችን ተዘዋውሮ እንደተመለከተው በብዙዎቹ ማደያዎች በዛሬው እለት ነዳጅ ቢኖርም ነዳጅ ለመቅዳት የተሰለፉ ተሸከርካሪዎች በመብዛታቸው ረጃጅም ሰልፎች መታጣቸውንና የትራፊክ መጨናነቅ መከሰቱን መታዘብ ችሎአል፡፡ በዓለም ገበያ ላይ የነዳጅ ዋጋ መቀነስን ተከትሎ ከትላንትና ህዳር 30 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ ንግድ ሚኒስቴር መጠነኛ …

ዛሬ የኖቤል መሥራች አልፍረድ ኖቤል የሞተበት ዕለት መታሰቢያ ሲሆን የሚታሰበውም ለዓለም ሰላም ጉልሕ አስተዋጽዎ ለሚያደርግ ለሚያደርጉ የኖቤል የሰላም ሽልማት በመሰጠት ነው። የሚሰጠውም በኖርዌይ መዲና በኦስሎ ሲሆን ፤በተለያዩ የሳይንስ ዘርፎች ፤ ውጤታማ ለሆኑ ድግሞ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ነው ሽልማቱ የሚሰጠው።


(አፈንዲ ሙተቂ)
——
በኢትዮጵያ የታሪክ ሂደት የተፈጠሩ የፖለቲካ ድርጅቶችና ሽምቅ ተዋጊ ቡድኖች በትግል ዘመናቸው ከወደቁ ሰማዕቶቻቸው ሁሉ አግዝፈው የሚመለከቱት አንዳንድ ጀግና አላቸው፡፡ ለምሳሌ የተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ ( ጀብሃ) ትልቁ ሰማዕት “ዑመር እዛዝ” ይባላል፡፡ የህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ሻዕቢያ) ታላቅ ሰማዕት ደግሞ “ኢብራሂም አፋ” ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) ትልቁ ሰማዕት “ተስፋዬ ደበሳይ” ነው፡፡ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) “ታላቁ ሰማዕት” ኤሌሞ ቂልጡ ይባላል፡፡ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላት በበኩላቸው እንደ ትልቁ ሰማዕት የሚያዩት ሃየሎም አርኣያን ነው፡፡
Hayelom Ar’aya
  ታዲያ ሃየሎም ከሌሎቹ ሰማዕታት የሚለይበት አንድ ጠባይ አለ፡፡ ይህም በጀግንነቱ በህወሓት ብቻ ሳይሆን የህወሓት ቀንደኛ ጠላት በሚባሉ ግለሰቦችና ቡድኖች ጭምር የሚወደስ መሆኑ ነው፡፡ እርግጥ ስለሃየሎም ጀግንነት በስፋት መጻፍ የጀመረው እርሱ ከተገደለ በኋላ ነው፡፡ ሆኖም ሃየሎም በህይወት እያለ እንኳ ስለጀግንነቱ ሲሰጡ የነበሩ የምስክርነት ቃሎችን በልዩ ልዩ የፕሬስ ውጤቶች ላይ አንብበናል፡፡ ለምሳሌ የቀድሞው የኢህዴን ሊቀመንበር ያሬድ ጥበቡ (ጌታቸው ጀቤሳ) “መስታወት” በተሰኘ መጽሔት ላይ በጻፉት አንድ ጽሑፍ ሁሉንም የኢህአዴግ መሪዎች በፈሪነት ከፈረጇቸው በኋላ ሃየሎም አርኣያን ብቻ በጀግንነት አወድሰዋል፡፡ በኤርትራና በትግራይ ሲዋጉ የነበሩ የደርግ የጦር መኮንኖችም በተለያዩ መጽሔቶች ስለሃየሎም ኣርኣያ ጀግንነት ሲያወሱ ነበር፡፡
 በመሆኑም በሃየሎም የጦር ሜዳ ጀግንነትና በወታደራዊ ጥበብ አዋቂነቱ ላይ ጥርጣሬ የሚቀርብ አይመስለኝም፡፡ ሆኖም የሃየሎምን አሟሟት ያየ ሰው “ሰውዬው ሰማዕት ነው ሊባል ይችላልን?” የሚል ጥያቄ ሊያቀርብ ይችላል፡፡ ምክንያቱም በተለምዶ ሰማዕታት የሚባሉት በትግሉ ሂደት ሲዋጉ የወደቁ ሰዎች ናቸውና፡፡ ሃየሎም የተገደለው ግን የትጥቅ ትግሉ ካበቃ ከአራት ዓመታት በኋላ በተከሰተ ጸብ ነው፡፡
 የኢህአዴግ ሰዎች “ሃየሎም በሰላም ጊዜ በሚደረገው ትግል መሃል የወደቀ ጓዳችን በመሆኑ ሰማዕት ነው” እንደሚሉ ይታወቃል፡፡ ከሰማዕታቱ መካከል የተናጥል ሃውልት ያቆሙትም ለርሱም ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ወገኖችስ በሰማእትነቱ ላይ ምን ይላሉ? በጉዳዩ ላይ ያላቸውን አቋም እንዲነግሩን እንጠብቃለን፡፡
*****
ሃየሎም አርኣያ ህወሓት (በኋላም ኢህአዴግ) ባካሄዳቸው ዋና ዋና ዘመቻዎች ላይ የመሪነት ሚና ነበረው፡፡ ከነዚያ ዘመቻዎች መካከል ከስሙ ጋር ተቆራኝቶ የቀረው በየካቲት ወር 1978 የተካሄደው “ኦፕሬሽን አግአዚ” ነው፡፡ ይህንን ኦፕሬሽን የሚመለከት ጽሑፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ያነበብኩት በሚያዚያ 1985 በታተመው “እፎይታ” መጽሔት ላይ ነው፡፡ ተራኪው ደግሞ ሃየሎም አርኣያ ራሱ ነበረ፡፡
 ታዲያ ጽሑፉ በጣም የሚያስደምም በመሆኑ ብዙዎች ታሪኩን በመጠራጠር “ሰውዬው የተናገረው ልብወለድ ነው እንጂ እውነተኛ ነገር  አይደለም” ብለው ነበር፡፡ በዘመኑ ከኢህአዴግ በታቃራኒነት የተሰለፉት የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣናት “ኦፕሬሽን አግአዚ” በትክክል የተፈጸመ ዘመቻ መሆኑን መናገር ሲጀምሩ ግን የሃየሎም ትረካ እውነተኛት ሊረጋገጥ በቅቷል፡፡ በዚህ ረገድ የመጀመሪያውን ምስክርነት የሰጡት ጓድ መንግሥቱ ኃይለማሪያም እራሳቸው ናቸው (በ1994 የታተመውን የሌ/ኮ/ መንግሥቱ ኃይለማሪያም ትዝታዎችን ያስታውሱ)፡፡ በማስከተልም “ነበር” የተሰኘውን ተወዳጅ መጽሐፍ የጻፉት ገስጥ ተጫኔ (ዘነበ ፈለቀ) “ኦፕሬሽን አግአዚ” በትክክል መፈጸሙን አረጋግጠዋል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡
   “ኦፕሬሽን አግአዚ” በመቀሌ እስር ቤት ታስረው የነበሩ ከሶስት ሺህ የሚበልጡ የህወሐት ታጋዮችንና ደጋፊዎችን የማስለቀቅ ተልዕኮ ነበረው (ኦፕሬሽኑ የተሰየመለት “አግዓዚ” የሚባለው ታጋይ ከህወሐት መስራቾች አንዱ ነው፤ “አግዓዚ” የትግል ስሙ ሲሆን እውነተኛ ስሙ “ዘርዑ ገሠሠ” ነበር)፡፡ እንደ ጄኔራል ሃየሎም አርኣያ አገላለጽ ኦፕሬሽኑን ለማካሄድ የሚያስፈልገው ቅድመ ዝግጅት ለስድስት ወራት ያህል ተካሄዷል፡፡ በኦፕሬሽኑ የሚሳተፉ ኮማንዲስቶች በሚስጢር ነው የሰለጠኑት፡፡ ሆኖም ሰልጣኞቹ በስልጠናው ላይ በነበሩበት ወቅት ስለኦፕሬሽኑ ምንም መረጃ አልነበራቸውም፡፡ በመሆኑም እነዚያ ሰልጣኞች ለስልጠናው ወደተዘጋጁት የአሸዋ ቤቶች በሚወሰዱበት ጊዜ ከፊሉ “ይህ የመቀሌ ቤተ መንግሥት ነው” ይሉ የነበረ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ “አይ! የአየር ማረፊያው ነው” እያሉ ልዩ ልዩ መላምቶችን ይደረድሩ ነበር፡፡
  “ኦፕሬሽን አግአዚ” በታቀደለት ጊዜ ተካሄደ፡፡ የህወሓት አሸማቂዎችም ማንም ባልጠበቀው ሁኔታ ወደ መቀሌ እስር ቤት በመግባት የሚፈልጓቸውን ታሳሪዎች በሙሉ አስለቀቁ፡፡ በማግስቱ ወሬው በአዲስ አበባ ሲሰማ በሊቀመንበር መንግሥቱና በጦር ጄኔራሎቻቸው ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ ተቀሰቀሰ፡፡ መቀሌ ያሉ የጦር መሪዎችም ለአስቸኳይ ግምገማ ተጠሩ፡፡ በግምገማው ማብቂያም “ለኦፕሬሽኑ መሳካት ትልቁን ሚና የተጫወተው በአካባቢው የነበረው አብዮታዊ ጦር አዛዥ የነበረው ብ/ጄኔራል ታሪኩ ዐይኔ ያሳየው እንዝህላልነት ነው” ተባለ፡፡
  የደርግ መንግሥት ባለስልጣናት ታሪኩን ሲጽፉ “የህወሓት ጦር በእስር ቤቱ ላይ ወረራ በፈጸመበት ወቅት የእስር ቤቱ ሃላፊ ወደ ጄኔራል ታሪኩ በመደወል “በወንበዴ ተወርሬአለው፤ ባሉኝ ጠባቂዎች መከላከል ስለማልችል ረዳት ጦር በአስቸኳይ ይላኩልኝ” በማለት ሲጠይቀው ጄኔራል ታሪኩ “እኔ መደበኛ ወታደር እንጂ የእስር ቤት ጠባቂ ዘበኛ አይደለሁም” የሚል የሹፈት መልስ ሰጥቶት ከቤቱ ገብቶ ተኝቷል፤ የአንድ አብታዊ ጦር ዋና ዓላማ ሀገሩን ከውጭ ወራሪዎችና ከውስጥ ወንበዴዎች መከላከል ሆኖ ሳለ ጄኔራል ታሪኩ ረዳት ጦር ለወህኒ ቤቱ እንዳይደርስ በማድረጉ ወያኔ ታሳሪዎቹን በቀላሉ ለማስመለጥ ችሏል፤ በዚህም ጄኔራሉ የወንበዴዎቹ ዓላማ ተባባሪ ሆኗል” ይላሉ፡፡
 በተለይ ግን ጓድ መንግሥቱ ኃይለማሪያም “ኦፕሬሽን አግአዚ”ን በምሬት ነው የሚያነሱት፡፡ ጓድ መንግሥቱ “ወያኔ በዚያ ድንገተኛ ወረራ ሊያመልጡ የማይገባቸውን ወንጀለኞች ለማስለቀቅ ችሏል” በማለት ለጋዜጠኛ ገነት አየለ አንበሴ ነግረዋታል፡፡ ሆኖም ለወንበዴዎቹ ድጋፍ ሰጥተዋል በተባሉት ጄኔራል ታሪኩ ዐይኔ ላይ መጥፎ እርምጃ አልተወሰደም፡፡ ጓድ መንግሥቱ ይህንንም ሲያብራሩ “የታሪኩ ጓደኛ የሆኑ የጦር መሪዎች በአማላጅነት ወደኔ መጥተው “ጓድ ሊቀመንበር! ታሪኩን በዚሁ ብቻ ከምንመዝነው ወደ ኤርትራ ይላክና ችሎታውን ያሳይ” ስላሉኝ እኔም ቃላቸውን በመቀበል ወደ አፋቤት ልኬዋለሁ” ብለዋል (ሆኖም ጄኔራል ታሪኩ ወደ አፋቤት ቢቀየርም ከአራት ዓመታት በኋላ ተረሽኗል)፡፡
እነ ሃየሎም አርኣያ በበኩላቸው በጄኔራል ታሪኩ ላይ የቀረበውን ክስ አይቀበሉም፡፡ ሃየሎም ስለጉዳዩ ሲናገር “ጄኔራሉ ጦሩን ለማንቀሳቀስ ያልቻለው በእንዝህላልነት ሳይሆን የኛ ጦር በመቀሌ ከተማ የተለያዩ ስፍራዎች የማዘናጊያ ውጊያዎችን በመክፈቱ መደበኛው ወታደር በነዚያ ውጊያዎች ስለተወጠረ ነው፤ እኛም የማዘናጊያ ውጊያዎቹን ሽፋን በማድረግ ያለምንም ስጋት እስረኞቹን ለማስለቀቅ ችለናል” ብሏል፡፡ 
   “ኦፕሬሽ አግዓዚ”ን በተመለከተ አከራካሪ ሆኖ የዘለቀ አንድ ጉዳይ አለ፡፡ ይህም ኦፕሬሽኑን ለማካሄድ የወሰደውን ጊዜ የሚመለከት ነው፡፡ ጄኔራል ሃየሎም አርኣያ “ኦፕሬሽኑ የተካሄደው በአስራ አምስት ደቂቃ ውስጥ ነው፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ስራችንን ሙሉ በሙሉ መጨረስ እንደምንችል ያወቅነው ስልጠናው በሚካሄድበት ወቅት ነው” ብሏል፡፡ የደርግ ባለስልጣናት ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ዘርዘር ያለ ነገር ባይጽፉም ኦፕሬሽኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ መፈጸሙን በደፈናው ያምናሉ፡፡  (በነገራችን ላይ የ“ኦፕሬሽን አግአዚ”ን ታሪክ መሰረት ያደረጉ ሁለት ፊልሞች ተሰርተዋል፤ አንደኛውን ፊልም ያዘጋጀው ታዋቂው አርቲስት ኪሮስ ኃይለ ሥላሤ ሲሆን የሁለተኛውን ፊልም አዘጋጅ ማንነት በትክክል አላውቅም፤ ሆኖም ሁለቱ አዘጋጆች “ኦሪጂናሌው ታሪክ የኔ ነው” በሚል ውዝግብ ፈጥረው እንደነበረ አስታውሳለሁ)፡፡
*****
ሃየሎም አርኣያ የተገደለው በየካቲት ወር 1988 ነው፡፡ ታዲያ የርሱ ሞት ከፍተኛ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ ነበር፡፡ በኦፊሴል የወጣው የኢትዮጵያ መንግሥት መግለጫ አሟሟቱን ሲያስረዳ “ጄነራል ሃየሎም አርኣያ ጀሚል ያሲን ከሚባል ኤርትራዊ ወጣት ጋር በተፈጠረ ጸብ ተገድሏል” ነው ያለው፡፡ ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ግን የሞቱን ምክንያት ሲያስረዱ “ኤርትራ በሓኒሽ ወደቦች ምክንያት ከየመን ጋር በተጣላችበት ወቅት ሃየሎም አርኣያ “ከኤርትራ መንግስት ጋር ያለን ግንኙነት እንደማንኛውም ኢንተርናሽናል ግንኙነት መታየት አለበት፤ በተለይም በወታደራዊ መስክ ያለን ግንኙነት በሀገራችን ላይ አደጋ የሚጋብዝ መሆን የለበትም፤ ከኤርትራ ጎን ሆነን የምንዋጋበት ምክንያት ሊኖር አይገባም” የሚል አቋም በማራመዱ የሻዕቢያ ጥይቶች ሰለባ ለመሆን በቅቷል” ብለው ነበር፡፡ እነዚህ ወገኖች “የሃየሎም አርኣያ ገዳይ ኤርትራዊ መሆንም ይህንኑ ያረጋግጣል” በማለትም አክለዋል፡፡ ከዚህም አልፎ “በስልጣን ላይ የነበረው የአቶ መለስ ዜናዊ አመራር የግድያው ተባባሪ ነው” የሚሉ በርካታ ሰዎች አሉ፡፡
  ሃየሎምን ተኩሶ የገደለው ወጣት ጀሚል ያሲን ከመሞቱ በፊት ከእፎይታ መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለ-መጠይቅ “በምሽቱ ሐሺሽ ወስጄ ነበር፤ በሐሺሽ ተገፋፍቼ ነው የገደልኩት እንጂ የተለየ ጠብ ኖሮን አይደለም” የሚል ቃል ነው የተናገረው፡፡ ሃየሎም በሞተበት ወቅት በአጠገቡ የነበሩት ሰዎችም “ወጣት ጀሚል በስካር ጥንብዝ ብሎ ሃየሎምን በባለጌ ስድቦች ይሳደብ ነበር፤ ሃየሎም ለረጅም ጊዜ ከታገሰው በኋላ ትዕግስቱ ሲያልቅበት ሁለት ጥፊ አቀመሰው፣ በዚህ የተናደደው ጀሚል ሽጉጡን ከመኪናው ውስጥ አምጥቶ ገደለው” የሚል ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡
  መንግሥታት በርካታ ጉዳዮችን ሚስጢራዊ ማድረጋቸው የተለመደ ቢሆንም የሃየሎም ሞት ሙሉ በሙሉ ሚስጢራዊ ሆኖ ቀርቷል ለማለት ምንም ዋስትና የለንም፤ እንዲህ የምንለው ከበርካታ ማዕዘናት በመነሳት ነው፡፡ ለምሳሌ የህወሐት (ኢህአዴግ) ባለስልጣናት በየጊዜው ፓርቲውን ለቀው ይኮበልላሉ፡፡ ሆኖም ከነዚያ ባለስልጣናት መካከል አንዳቸውም ቢሆኑ “ሃየሎም ሻዕቢያ በሸረበው ሴራ ነው የተገደለው” በማለት ሲናገሩ አልሰማናቸውም፡፡ ከአቶ መለስ ጋር ተጋጭተው ከድርጅቱ የወጡትና ከመለስ በላይ ሃየሎምን በቅርበት የሚያውቁት አቶ አረጋዊ በርሀም አቶ መለስን በሃየሎም ግድያ ሲከሷቸው አልተሰሙም፡፡ ከህወሐት ጋር ታሪካዊ ጠላት ሆነው የዘለቁት አቶ አብረሃም ያየህም “ኤርትራ ኢትዮጵያን የወረረችው በአቶ መለስ ዜናዊ አደፋፋሪነት ነው” እያሉ ቢጽፉም ለሃየሎም ሞት ሻዕቢያንም ሆነ አቶ መለስ ዜናዊን ተጠያቂ ሲያደርጉ አላየናቸውም፡፡ ከህወሓት ያፈነገጡት እነ ተወልደ ወልደማሪያምና ስየ አብረሃም ለሻዕቢያ ወረራ በየጊዜው የአቶ መለስን ቡድን ተጠያቂ ማድረጋቸው እንደተጠበቀ ሆኖ የሃየሎምን ግድያ ከኤርትራ ጉዳይ ጋር  ሲያገናኙት አልተደመጡም፡፡
ሻዕቢያ ሃየሎምን አስገድሎት ሊሆን ይችላል የሚሉ ሰዎች በበኩላቸው “ሴራውን ይገልጻሉ” የሚሏቸውን አንዳንድ ምልክቶችን ይደረድራሉ፡፡ ለምሳሌ ሃየሎም ከሞተበት ዕለት ጀምሮ የኤርትራ ሚዲያዎችና ዌብሳይቶች ሰውዬውን በጀግንነቱ ሲያደንቁት እንጂ በአሉታዊ መልኩ ሲያነሱት አይታዩም፡፡ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በሚካሄድበት ወቅት እንኳ የኤርትራ ሬድዮ “የአቶ መለስ አገዛዝ ሃየሎምን የመሰለ የጦር ጀግና ያስበላ የወንበዴ ቡድን ነው” ይል ነበር፡፡ እናም በርካታ ሰዎች “እነዚህ የኤርትራ ሚዲያዎች ሃየሎምን የሚያደንቁት የግድያው ሚስጢር እንዳይወጣ ለማፈን ቢሆንስ?” የሚል የጥርጣሬ ጥያቄ ያቀርባሉ፡፡
 በኛ በኩል “ተጨባጩ እውነታ ይህ ነው” ብለን ምስክርነት መስጠት አንችልም!! በግድያው ዙሪያ በኢንተርኔትም ሆነ በፕሬስ ሲጻፍ የነበረው ሁሉ ጥርጣሬ እንጂ ሐቅ ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ጥርጣሬ እውነትም ሊሆን ይችላል፤ ውሸትም ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም የታሪክ ተመራማሪዎች  አንድ ቀን ሐቁን ያሳውቁናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን!! በዚህ አጋጣሚ የማንክደው ነገር ቢኖር ሃየሎም አርኣያ የጦር ሜዳ ጀግና የነበረ መሆኑን ነው፡፡
—-
  አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 7/2007
ገለምሶ-ሀረርጌ

በሰሜን ምሥራቅ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ውስጥ እየደረሰ ያለዉ ጥቃት ማሕበረሰቡን ከፍተኛ ስጋት ላይ እደጣለዉና መፍትሄ አልባ እንዳደረገዉ ተገልፆአል። የሲቪሉ ማሕበረሰብ ድርጅቶች አማፅያን የሚያደረሱት ጥቃት ለመከላከል የዓለም አቀፉን ርዳታ ጠይቀዋል።

የአሜሪካው የስለላ ተቋም «CIA» በሽብርተኝነት ተጠርጣሪ እስረኞችን በምርመራ ወቅት በከፍተኛ ሁናቴ ማሰቃየቱን የሚያጋልጠው ሠነድ በስተመጨረሻ ይፋ ሆኗል። የሰብአዊ መብት ተሟጋቿ ሎውራ ፒተር ሠነዱን፦ «ለበርካታ አሜሪካውያን እጅግ አስደንጋጭ ነው» በማለት ገልፀዋል።

በተለይ አዲስ አበባ ከተማ በሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎችና የሴቶች ጥቃት ፖሊሶችና የሕግ ተርጓሚዎች ተገቢዉን ድጋፍ እንደማያደርጉ ይባስ ብለዉም ወንጀሉን የሚያባብሱ ተግባራት እንደሚፈጽሙ ተገለጸ።

ከአፍሪቃው ክፍለ ዓለም ፣ ሞሮኮ፣ ለኃይል ምንጭ ፣ ከነዳጅት ዘይት ይልቅ ለፀሐይ ሙቀትና ብርሃን የላቀ ግምት የሰጠችበት እንቅሥቃሤ በአወንታዊነት ሲጠቀስ፣ ዩጋንዳ ለተፈጥሮ ተስማሚ ነው ያለችውን በኤሌክትሪክ የሚሽከረከር አውቶሞቢል መሥራት ብቻ

‹‹አገዛዙ የወሰደውና ወደፊት የሚወስደው ከእስካሁኑ የባሰ አረመኔነት እርምጃ ይበልጡን ያጠናክረናል›› የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ትናንት ህዳር 30/2007 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ትግሉን ያጠናክራሉ ያላቸውን ውሳኔዎችን አስተላለፈ፡፡ ብሄራዊ ምክር ቤቱ ያስተላለፋቸው ውሳኔዎች ‹‹ህወሓት/ኢህአዴግ በፈፀመው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እና እስር ምክንያት ክፍተት ሳይፈጠር የፓርቲው እንቅስቃሴ እንዲቀጥልና ትግሉም እንዲጠናከር የሚያስችሉ ናቸው›› ሲሉ የብሄራዊ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰይድ […]

ህዝብን በማይሽር ቁስል አየጎዱ በፕሮፓጋንዳ ማከም አይቻልም:: የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጥያቄና የኮሚቴው መፈታት ጥያቄ በአስቸኳይ ሊመለስ ይገባል:: ሙስሊም ወገኖቻችን ለሃገራቸው እና ለነጻነታቸው ምን ያህል ቀናኢ መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል:: ወቅሰን ወቅሰን ወንጅለን ወንጅለን የሰለቸን ለመስማትም የታከተን ነገር ቢኖር ያለፉት ስርአቶች ላይ እና ሌላው ላይ ማሳበብን አንዱን ከአንዱ ለማፋጀት ማፈራረጅን መጠቋቆምን የመሳሰሉት ኢሕአዴጋዊ ባህርያት ናቸው::ወያኔ ኢሕኣዴግ የጭንቅ ነገር […]

በመቀሌ ዞን የአንድነት አመራር አባል የነበረው ወጣት ሺሻይ አዘናው ጥቅምት 22 በደህንነት ኃይሎች ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ በመቀሌ በሚገኝ አንድ እስር ቤት ኮማንደር ሰዓረ በሚባል የፖሊስ አዛዥና እርሱ በሚመራቸው ፖሊሶች ከፍተኛ የሆነ ድብደባ ተፈፅሞበታል። ከዚያ በኋላ የት እንዳለ ሳይታወቅ ተሰውሮ ቢቆይም፤ በአሁኑ ሰዓት ማዕከላዊ እየተባለ በሚጠራው የማሰቃያ እስር ቤት እንደሚገኝና በዚህም ቦታ በተከታታይ ለአራት ቀናት ሌሊት […]


አፈንዲ ሙተቂ
——
ዶ/ር ሃይሌ ፊዳ በፎቶግራፉ ላይ የምትመለከቱት ነው፡፡ ፎቶውን የሰጡን አንጋፋው ደራሲ አበራ ለማ ናቸው፡፡ ጋሼ አበራን እያመሰገንን በሃይሌ ፊዳ አሟሟት ዙሪያ የተጠናቀረውን ይህንን ጽሑፍ ጀባ ብለናችኋል፡፡
                                                                          *****
ኮ/ል መንግሥቱ ሀይለማሪያም “ሀይሌ ፊዳ የተገደለው በገበሬዎች ነው” ባይ ናቸው፡፡ ከጋዜጠኛና ደራሲ ገነት አየለ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ የሀይሌ ፊዳን ሞት እንዲህ በማለት አስረድተዋል፡፡
ገነት፡ ሀይሌ ፊዳስ? በነሐሴ 1970 ተይዞ ከአንድ ዓመት በኋላ ነገር ከበረደ፤ ሁሉ ነገር ከተረጋጋ በኋላ ነው የተገደለው፡፡ በዚያን ጊዜ የኃይሌ ፊዳ በህይወት መኖር መንግሥትን ያሰጋ ነበር?
መንግሥቱ፡ መቼ ነው የሞተው ሀይሌ ፊዳ?
ገነት፡ በሀምሌ 1971 ነው::
መንግሥቱ፡ ማነው የገደለው?
ገነት፡ እኔ ምን አውቃለሁ? አስከሬኑ ከቀድሞው የራስ አስራተ ካሣ ግቢ ነው ተቆፍሮ የወጣው፡፡ እዚያ ነው የተገኘው፡፡
መንግሥቱ፡ ሀይሌ?
ገነት፡ አዎን! ሀይሌ ፊዳ፡
መንግሥቱ፡ እዚያ ምን ሲሰራ?
ገነት፡ እዚያ ነው አስከሬኑ የተገኘው፡፡
መንግሥቱ፡ እኔ አላውቅም፡፡
ገነት፡ መሞቱንም አያውቁም? እርሱንም እዚህ ከመጡ በኋላ ነው የሰሙት?
መንግሥቱ፡ መኢሶኖች እኮ ጥለውን ሄደዋል፡፡ የሶማሊያ ጥቃት አይሎ ሲመጣ የሻዕቢያዎች ጎራ ስለጠነከረ ከዚህ ከደከመ መንግሥት ጋር ምን እንሰራለን ብለው አይደል እንዴ ጥለው የነጎዱት? በነሱ ሃሳብ እኛ በመዳከማችን ወደፊት ከኛ ጋር በመቀጠል የስልጣን ጥማታቸውን የሚያረኩበት መንገድ ስለማይኖር ልዩ ልዩ ምክንያት ሲያቀርቡ ቆይተው በመጨረሻ ፈርጥጠዋል፡፡ በዚህን ጊዜ እነ መስፍን ካሱ ወደ ሲዳሞ፡ እነ ሀይሌ ፊዳ ወደ ወለጋ ሲሄዱ አግኝቶ ገበሬ ነው የከሰከሳቸው፡፡
ገነት፡ እዚያ ነው የተገደሉት?
መንግሥቱ፡ በሙሉ!
(ገነት አየለ አንበሴ፡ የሌተና ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም ትዝታዎች፡ 1984፣ ገጽ 207-208)
                                                                          *****
ሊቀመንበር መንግሥቱ “የሀይሌ ፊዳን መሞት ሰው ነው የነገረኝ” ነው የሚሉት፡፡ ነገር ግን ሀይሌ በነሐሴ 1969 ከተያዘ በኋላ በደርግ ምርመራ ክፍል ሲሰቃይ ቆይቶ እንደተገደለ ይታወቃል፡፡ ለዚህ ማስረጃ የሆነውንና ሀይሌ ከመሞቱ በፊት የሰጠውን ባለ 36 ገጽ የምርመራ ቃል በልዩ ልዩ መንገዶች ታትሞ አንብበነዋል፡፡ ከሀይሌ ጋር በአንድ ክፍል ታስረው የነበሩ ጓዶችም ሀይሌ በዚያ ወር እንደተገደለ ተናግረዋል፡፡ የደርግ የቅርብ ሰው የነበሩት አቶ ገስጥ ተጫኔ (ዘነበ ፈለቀ) “ነበር” በሚል ርዕስ በጻፉት ባለሁለት ቅጽ መጽሐፍ የምርመራ ቃሉን ከማተማቸውም በላይ ሀይሌ ከሱሉልታ ኬላ ተይዞ ወደ ደርግ ጽ/ቤት በመጣበት ወቅት በብሄራዊ ቤተመንግሥት እንዳዩት መስክረዋል፡፡
    
  በዚህም መሰረት “ሊቀመንበር መንግሥቱ ሀይሌን በእርግጥ ገድለውታል ወይ?” የሚለው ጥያቄ ለአሁኑ ዘመን አይሰራም፡፡ “መንግሥቱ ሀይሌን ለምን ገደሉት?” የሚለው ግን አሁንም ያከራክራል፡፡ ገነት አየለ እንደገለጸችው ሀይሌ በተገደለበት ወቅት ነገሮች ሁሉ በጣም በርደዋል፡፡ የሶማሊያ ወራሪዎች ከምስራቅ ኢትዮጵያ ከተባረሩ አንድ ዓመት አልፎአቸዋል፡፡  ሻዕቢያና ጀብሃ በሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ክፉኛ ተደቁሰው ወደ ሱዳንና ወደ ሳሕል በረሃ ገብተዋል፡፡ ከነዚህ ሁለት ክስተቶች ቀደም ብሎም ሀገር ያተራመሰውና ሺዎችን የቀሰፈው የቀይ ሽብር ዘመቻ ደርግ በሚፈልገው መልኩ ተጠናቋል፡፡ አብዮታዊው መንግሥት ከዚያ በፊት ያላየው ሰላምና እርጋታ በሀገሪቱና በሁሉም የስራ መስኮች ሰፍኗል፡፡ ታዲያ በዚህ ሰላማዊ ወቅት ሀይሌ ፊዳን ማስገደሉ ለምን አስፈለገ?
  
  
በርካታ ተመልካቾች የየራሳቸውን ግምት አስቀምጠዋል፡፡ አንዳንዶች ነገሩን ከቂም በቀል ጋር ያያይዙታል፡፡ “መንግሥቱ አንድ ቀን የገላመጠውን እንኳ የማይምር ቂመኛ ነው” -ይላሉ እነዚህ ወገኖች፡፡ የተወሰኑት ደግሞ መንግሥቱ በችሎታና በእውቀት ከርሱ የሚበልጥ ሰው ከታየው ወደፊት ስልጣኔን ይነጥቀኛል በሚል እንደሚያስገድለው ያወሳሉ፡፡ እነዚህኛዎቹ ክርክራቸውን ሲቀጥሉ “መንግሥቱ ሀይለማሪያም ሀይሌ ከእስር ቢለቀቅ ወይም ቢያመልጥ የራሱን ቡድን አደራጅቶ ወይ አንዱን ጄኔራል ተጠግቶ ከስልጣኔ ሊያሽቀነጥረኝ ይችላል” የሚል ፍራቻ ነበረው” ባይ ናቸው፡፡
     
   ከሁለቱ ወገኖች የሚለይ አስተያየት የሚሰጡ ጸሐፊያንና የታሪክ ሰዎችም አሉ፡፡ እነዚህኛዎቹ እንደሚሉት ኮሎኔል መንግሥቱ ሃይለማሪያም በሀይሌ ጉዳይ ላይ የሞት ውሳኔ ያሳለፉት እርሳቸውን ያስደነገጠ አንድ አደገኛ ክስተት ስለተፈጠረ ነው፡፡ እስቲ ታሪኩን አብረን እንየው፡፡
                                                                          *****
     ሊ/ር መንግሥቱ ለጉብኝት ወደ ኩባ ይጋበዛል፡፡ ከጓድ ፊደል ካስትሮ ጋር ጉብኝትና ስብሰባውን ማካሄድ ይጀምራል፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ለስራ ጉዳይ ወደ ውጪ ሀገር በመሄዱ ህይወቱ ለጥቂት የተረፈችው የመኢሶኑ ዶ/ር ነገደ ጎበዜ አዲስ አበባ መግባቱ ይነገረዋል፡፡ “እንዴት መጣ?” ብሎ ቢጠይቅ “የደቡብ የመንን ፓስፖርት ይዞ፤ ከደቡብ የመን ልዑካን ጋር ተቀላቅሎ” ሆነ መልሱ! (ደቡብ የመን አሁን ከሰሜን ጋር ተዋህዳለች)፡፡ “ዶ/ር ነገደ ተይዟል ወይ?” ብሎ ሲጠይቅ አለመያዙ ተነገረው፡፡ ያለበትን ቦታ ጠይቆ የተሰጠውን መልስ ሲሰማ ደግሞ ሊ/ር መንግሥቱ በድንጋጤ ፈዝዞ ቀረ!
                                                                          *****
 በርግጥ ዶ/ር ነገደ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ ነገር ግን መጥፎ አጋጣሚ ሆኖ ድሮ ከሚያውቀው የኤርፖርት ደህንነት ሃላፊ ጋር አይን ለአይን ተገጣጠመ፡፡ ደህንነቱ ነገሩን ወዲያኑ ለደርጎች አስታወቀ፡፡ ደርጎችም ነገደ ጎበዜን ለመያዝ ተንቀሳቀሱ፡፡ ሆኖም ዶ/ሩ ኩባ ኤምባሲ ገብቶ ተደበቀ፡፡ ሁኔታው ለጓድ ፊደል ካስትሮ ሲነገራቸው ካስትሮ አማላጅ ሆኑና በነገሩ ውስጥ ገቡ፡፡ በርሳቸው ተማጽኖም ዶ/ር ነገደ ከኤምባሲው ወጥቶ ወደ አውሮጳ ተመለሰ፡፡
  
   ይህ ድርጊት የተከሰተው የሶማሊያ ወረራ ካበቃ ከጥቂት ወራት በኋላ ነበር፡፡ ደርጎች ነገሩን እንደ ኩዴታ ነው የወሰዱት፡፡ ለዚህም ነው በውስጣቸው ከፍተኛ መሸበር የተፈጠረው፡፡ እርግጥ ሀገራቱ ኩዴታ እናድርግ ቢሉ የማስፈጸም አቅሙ ነበራቸው፡፡ በወቅቱ የ”ሶማሊያን ወረራ ለመቀልበስ በተደረገው ዘመቻ አብዮታዊ አጋር ሆኖ የመጣው የኩባ ሀያ ሺ ሜካናይዝድ ጦርና የየመን ሁለት ሺህ መድፈኛ ጦር ኢትዮጵያ ውስጥ ስለነበሩ እነርሱን ይዘው አንድ ነገር ማድረግ ይችሉ ነበር ተብሎ ይገመታል፡፡ የዘመኑ ሀያል ሶሻሊስት ሀገር የሆነችውን ሶቪየት ህብረትንም ለእርዳታ ቢጠሯት “በጄ” ከማለት የምትመለስ አይሆንም-ከመንግሥቱ ይልቅ ኩባና ደቡብ የመን ይበልጡባታልና፡፡ ሆኖም የዶ/ር ነገደን መምጣት ብቻ በማየት “ኩዴታ” ተጠንስሷል ለማለት ይከብዳል፡፡
     ሊ/ር መንግሥቱ በዚህ መረጃ ላይ በመመርኮዝ “ኩዴታ” እንደታቀደባቸው አሰመሩበት፡፡ ሀገራቱ ፈጸሙብኝ ላሉት በደል ደግሞ ቀጥተኛ ምላሽ ከበዳቸው -ምክንያቱም የክፉ ቀን ወዳጆች ናቸውና፡፡ በሌላ በኩል ግን ሊቀመንበሩ ቁጭታቸውን መዋጥ አቃታቸው፡፡    ለምን ቢባል እንኳንስ እንዲህ ዓይነቱን ምልክት አግኝተው ይቅርና በጥርጣሬ ብቻ ብዙዎችን ቀስፈዋልና፡፡ የቀይ ሽብሩ ትርዒት ሳይደመር የተፈጁትን ሰዎች ቤት ይቁጠረው፡፡ ሌ/ኮ/ አጥናፉ አባተን “ለሀገራችን ሶሻሊዝም አይጠቅማትም፤ እንደ ዩጎዝላቪያ የቅይጥ ኢኮኖሚ መርህ መከተል አለብን” በማለታቸው ብቻ አስገድለዋቸዋል፡፡ “ለኤርትራ ጥያቄ ሰላማዊ መፍትሔ ያስፈልጋል” ያሉ በርካታ ጓዶቻቸውን አስረሽነዋል፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ ቄስ ጉዲና ቱምሳ እና ሼኽ ሰይድ ቡደላ (የአብሬት ሼኽ) የመሳሰሉ የሀይማኖት አባቶች ያለ አንዳች ምክንያት ተገድለዋል፡፡ ከዚህ አንጻርም ለዶ/ር ነገደ ጎበዜ ድፍረት የሚሰጡት ቅጣት ከፍተኛ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ግን ዶ/ር ነገደ አልተያዘም፡፡ ስለዚህ ቁጭቱ በምን ይውጣላቸው?
    እንግዲህ በአንዳንዶች እምነት ዶ/ር ሀይሌ ፊዳ የተገደለው በዚህ እርግጠኛነቱ ባልታወቀ የዶ/ር ነገደ ጎበዜ “ኩዴታ” ጦስ ነው፡፡ ኩባና የመንን መበቀል ሲያቅታቸው ቁጭታቸውን በግቢአቸው ባጎሩት እስረኛ ላይ ተወጡት፡፡ ሀይሌን በአንድ ቀዝቃዛ ምሽት አሰናበቱት፡፡
                                                                          *****
     በቅርብ ጊዜ የተገኙ መረጃዎች ግን ከላይ የቀረበውን ታሪክ ዋጋ ቢስ አድርገውታል፡፡ እነዚህ መረጃዎች እንደሚሉት ዶ/ር ነገደ ጎበዜ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው የመጡት በሊቀመንበር መንግሥቱ እውቅና ነው፡፡ ለምሳሌ ዶ/ር መረራ ጉዲና በቅርቡ ባሳተሙት መጽሓፋቸው “ነገደ ጎበዜ በመንግሥቱና በኩባዊያን እውቅና መምጣቱን ነግሮኛል” በማለት ጽፈዋል፡፡ ከአሜሪካ የስለላ ምንጮች የተገኘው መረጃም ይህንኑ ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ደርጎች “መፈንቅለ መንግሥት ሊካሄድ ነበር” እያሉ ወከባ ይፈጥሩ የነበረው ህዝቡንና የተቃዋሚውን ክፍል ለማደናገርና የበለጠ ጸጥ ለማድረግ ነው ማለት ነው፡፡ የሀይሌ ፊዳ ግድያም ከመፈንቅለ መንግሥቱ ጋር አንዳች ግንኙነት አልነበረውም፡፡
  
     በአንጻሩ ደግሞ ሀይሌ ፊዳ የተገደለበት ሀምሌ 1971 በውል ሊመረመር የሚገባው የታሪክ ወቅት ሆኖ ሳለ ምሁራን በጥልቀት ሳያስሱት መቅረታቸው ይገርማል፡፡ ይህ ወር መንግሥቱ ከቀይ ሽብርና ነጭ ሽብር የተረፉ በርካታ ተቃዋሚዎቹን፣ አማካሪዎቹንና ታዋቂ ግለሰቦችን በድብቅ የገደለበት ጊዜ ነበር፡፡ እነ አቡነ ቴዎፍሎስን ጨምሮ የኢህአፓው ብርሀነ መስቀል ረዳ፣ የመኢሶኖቹ ከበደ መንገሻ፣ ንግሥት አዳነ፣ ደስታ ታደሰ፣ መስፍን ካሱ ወዘተ… በዚሁ ጊዜ ነበር የተገደሉት፡፡ “የማዕከል” ጥያቄ ደርጎችን ያናቆረው በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ ኢማሌድህ የሚባለውን የማርክሲስቶች ህብረት ከመሰረቱት አምስት ድርጅቶች (አብዮታዊ ሰደድ፣ መኢሶን፣ ወዝሊግ፣ ኢጭአት እና ማሌሪድ) መካከል መንግሥቱ ከሚመሩት “ሰደድ” ጋር በመድረኩ ላይ የቀረው የማሌሪድ መሪ ተስፋዬ መኮንን የታሰረውና የማሌሪድ ግብአተ ሞትም የተፈጸመውም በዚህ ወር ነበር፡፡ ስለዚህ ያ ታሪካዊ ወቅት የምሁራን እይታ ሊያርፍበት ይገባል፡፡
——
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 21/2006

የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ስብስብ የሆነው መድረክ የኢህአዴግ አገዛዝ በህዝባችን ህገመንግስታዊ ነጻ የመምረጥ መብት ላይ የሚፈጽማቸውን የመብት ረገጣዎች እንዲያቆም፣ በሃገራችን ነፃ ፣ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ተአማኒነት ያለው ምርጫ እውን እንዲሆና የምርጫ ሜዳውም ለሁሉም እኩል የተመቻቸ እንዲሆን ለመጠየቅ ለታህሳስ 5 ቀን 2007 ዓም የተቃውሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ መጥራቱን አስታውቋል። መድረክ ለኢህአዴግ አገዛዝ የውይይትና የድርድር ጥያቄዎችን በተደጋጋሚ ቢያቀርብም፣ አገዛዙ …

ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ የሽግግር ካውንስል ለኢሳት በላከው መግለጫ የአፓርታይድ ስርአትን እአካሄደ ያለው የወያኔ አገዛዝ በሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላይ የወሰደው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ ሊወገዝ ይገባዋል ብሎአል። የኢኮኖሚ እድገት አምጥቻለሁ እያለ ፕሮፓጋንዳ የሚነዛ መንግስት ፣ በስልጣን ላይ ለመቆየት ብቸኛ መተማመኛው ሃይል መሆኑን አሳይቷል ያለው የሽግግር ካውንስል፣ ሁሉም የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎችና የአለማቀፉ ማህበረሰብ ድርጊቱን እንዲያወግዙ …

ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ የጸጥታ ሃላፊ እንደገለጹት በደቡብ እና በቤንሻንጉል ክልሎች አጎራባች ወረዳዎች አሉ ችግሮችን ለመፍታት አንዳንድ ሙከራዎች ቢደረጉም፣ ከሶማሊ ክልል ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት አለመቻሉን ገልጸዋል። በደቡብ ክልል በአንዳንድ ወረዳዎች የድንበር ችግር መኖሩን የገለጹት ሃላፊው፣ ችግሩን ለመፍታት እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል። ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ጋር ያለውን የድንበር ውዝግብ ለመፍታት ተደጋጋሚ ሙከራ መደረጉን …

ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በደራ ወረዳ ጉንዶመስቀል ከተማ ላይ አንድ ከተማ ውበቱ የተባለ ሰው ሃብታሙ ሺበሺ የተባለን ሰው መግደሉን ተከትሎ፣ ገዳይን ለመያዝ በተደረገ ጥረት ሰኞ ህዳር 29፣ 2007 ዓም በአካባቢው ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ተካሂዷል። ከተማ ውበቱ የተባለው ሰው በ1999 ዓም የሰዎች ለሰዎች የተባለውን ድርጅት ገንዘብ ከዘረፈ በሁዋላ …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ቅዳሜ በአል-ማካ የወደብ ከተማ አካባቢ ስደተኞችን የጫነች ጀልባ መስመጧን እና 70 ኢትዮጵያውያን መሞታቸውን የየመን አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ-ገፁ አስታውቆ ነበር። ይህ መረጃ እስካሁን አልተረጋገጠም

ህዝብን በማይሽር ቁስል አየጎዱ በፕሮፓጋንዳ ማከም አይቻልም:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎EthioMuslims‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ ሽብር ግድያ እስር ድብደባ እንግልት በጅምላ አፈሳ ዘረፋ ንጥቂያ እና ከፍተኛ የሆነ ኢሰብአዊነት እና ጭፍጨፋ በመንግስት ነኝ ባይ ሃይሎች በይፋ በአደባባይ ተፈጽሟል::ይህንን መንግስታዊ ሽብር የማይሽር ጠባሳ በመላው ኢትዮጵያውያን ላይ ጥቁር ነጥብ አስቀምጧል:: የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጥያቄና የኮሚቴው መፈታት ጥያቄ በአስቸኳይ ሊመለስ ይገባል::ሙስሊም ወገኖቻችን ለሃገራቸው እና ለነጻነታቸው ምን ያህል ቀናኢ መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል::
http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … ost_9.html

Image

የዛሬ አምስት ዓመት ኮፐንሃገን የተካሄደዉ የአየር ንብረት ለዉጥ ጉባኤ ብዙ ተብሎለትና ብዙ ተጠብቆበት ካለ ዉጤት መጠናቀቁ ብዙዎችን ግራ ያጋባ ብቻ ሳይሆን ተስፋም ያስቆረጠ መስሎ ነበር።

ድርጅቱ ቀደም ሲል ሆስፒታሉን አዲስ አበባ ዉስጥ ለመገንባት ጥያቄ ቢያቀርብም የከተማይቱ መስተዳድር ለሆስፒታሉ ማስገንቢያ የሚሆን መሬት ባለመፍቀዱ ትግራይ ዉስጥ ለማስገንባት ወስኗል።

ፈረንሳይ በሚኖሩ አይሁዶች በሚታየው ዘረኝነት እና በሚፈፀምባቸው ጥቃት አንፃር በርካታ ሰዎች ባለፈው እሁድ በፓሪስ አቅራቢያ በምትገኘው ክሬቴይ ሰልፍ ወጥተዋል።አይሁዶች ሀብታሞች ናቸው የሚል የቆየ አነጋገር እንዳለ ይሰማል። ይኸው አነጋገርም ዛሬም ድረስ ብዙ ጠላት አፍርቶባቸዋል።

ትናንት በተጀመረዉ ሥብሰባ ላይ የአፍሪቃ መንግሥታት ፍርድ ቤቱ ከዓለም አቀፍነቱ ይልቅ አፍሪቃዉያንን ለመክሰስና ለመቅጣት ያለመ ነዉ በማለት ወቅሰዉታል። ፍርድ ቤቱ ከተመሠረተ ጀምሮ የከሰሳቸዉ ወይም የቀጣቸዉ በሙሉ አፍሪቃዉያን ፖለቲከኞች ናቸዉ።