ህወሓት ጥቂት አባላትና ደጋፊዎች ይዞ ታላቂቷን ኢትዮጵያ ለማንበርከክ እና ሀብቷን ለመመዝበር  እናንተን መጠቀሚያ ያደረጋችሁ መሆኑን የምታውቁት ነው። እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ የተባሉ ድርጅቶች የራሳቸው ድርጅታዊ ነፃነት የሌላቸው የህወሓት አገልጋዮች መሆናቸው እነሱ ራሳቸው የሚነግሯችሁ ከመሆኑም በላይ እናንተም በዕለት ተዕለት ተግባራችሁ የምትታዘቡት ሀቅ ነው። እነዚህ ድርጅቶች ህወሓትን ለማስደሰት ሲሉ የራሳቸውን ሕዝብ የሚያስሩ፣ የሚገድሉ፣ የሚዘርፉ፣ ከቀየው […]

–ባለሥልጣኑ በጣቢያውና በኢትዮፒካሊንክ ላይ ያሳለፈው ውሳኔ ውድቅ ተደርጓል የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን በዛሚ 90.7 ኤፍኤም ራዲዮ ጣቢያ በሚተላለፈው ኢትዮፒካሊንክ ፕሮግራም ላይ የቀረበን አቤቱታ ምክንያት በማድረግ ሰኔ 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ለሬዲዮ ጣቢያው የጻፈው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያና ኢትዮፒካሊንክ የተባለው ፕሮግራም ላይ የሰጠው ዕግድ …

ብሮድካስት ባለሥልጣንና ዛሚ ራዲዮ የፈጠሩት ውዝግብ በባለሥልጣኑ ቦርድ ውሳኔ ተፈታ Read more »

ልደት እና ትምህርት ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ ሊቀ ጳጳስ ከአባታቸው ከመምህር ሀብተ ማርያም ደስታ ተክሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ በስሙ ቸርነት ታኅሣሥ 19 ቀን 1925 ዓ.ም. በድሮው አጠራር ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እየተባለ ይጠራ በነበረው እንሳሮ ወረዳ በአኹኑ አጠራር በሰላሌ አውራጃ በውጫሌ ወረዳ ልዩ ስሙ በርጋፈት ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተወለዱ፡፡ ዕድሜአቸው ለትምህርት ሲደርስ በታላቁ …

ኢሳት ዜና (ሃምሌ 13 2007 አም) የበክኔል ዩኒቭርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑትና በቅርቡ ከዚሁ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማእረግ የተቀበሉት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሳምንቱ መጨረሻ ኤርትራ መግባታቸው በኢትዮጵያውያን ዘንድ አብይ መነጋገሪያ ሆኖ ወጥቷል ፤ የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የመሪውን ትግል ቦታ መሄድ ይፋ በማድረግ ኢትዮጵያውያን በአቅማቸው መጠን በትግሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል። “እነሆ የአርበኞች ግንቦት ሰባት …

Magdalaወለላዬ ከስዊድን

አፄ ቴዎድሮስ ያሠሩትን መድፍ (ሴባስቶፖል) ወደ ተራራው አናት ለማውጣት እየተጣደፉ ነው። እሳቸው ጭምር በጉልበት እያገዙ ሲገፋ ውለው ረፋዱ ላይ ከሰፈር ደርሰው ሲመለሱ አንዱ መድፉን ከሚገፉት ተለይቶ ወደ ሰፈር ሲወርድ መንገድ ያገኙትና ቆም ብለው ወዴት ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ? ብለው ይጠይቁታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሐምሌ ፲፭ (አስራአምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ድርጅቶቹ ለፕ/ት ኦባማ በጻፉት ደብዳቤ ኬንያና ኢትዮጵያ በብሄራዊ ደህንነት ስም የሚያደርሱት የሰብአዊ መብት ረገጣ ፣ አለማቀፍ ህግጋትን መጣስ ብቻ ሳይሆን፣ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት የሚደረገውን ጥረት አደጋ ውስጥ እንደሚጥለው ገልጸዋል። ደብዳቤውን የጻፉት፣ አትላንታ ካውንስል፣ ካውንስል ኦን ፎሬን ሪሌሽን፣ ሂውማን ራይትስ ፈርስት፣ ከኒይ ግራጅዌት ሴንተር እና ሲቲ ኮሌጅ ኦፍ …

ሐምሌ ፲፭ (አስራአምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲቀርቡ ሲል የልደታ ፍርድ ቤት 19 ኛው የወንጀል ችሎት ወሰነ፡፡የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በምስክርነት እንዲያቀርብ ሲል ፍርድ ቤቱ ለሀምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥትዋል። አቶ አንዳርጋቸው …

ሐምሌ ፲፭ (አስራአምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዓለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት አይ ኦ ኤም በየመን አድርገው በሕገወጥ መንገድ ወደ ሳኡዲ አረቢያ ለመግባት ሲሞክሩ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች ታግተው የአካልና የሞራል ጉዳት የደረሰባቸውን ቁጥራቸው 3 ሺ 478 የሚሆኑ በጎፈቃደኛ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ወደ አገራቸው መመለሱን አስታውቀዋል። የ18 ዓመቱ ወጣት አልማይ ፍፁም ”በመኪና ተጭነን ወደ ሳዑዲ ድንበር እንደተቃረብን …

ሐምሌ ፲፭ (አስራአምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ዳይሬክተር ሆነው ያገለገሉት አቶ ጌታሁን ካሳ ”የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሰብዓዊ መብት ተቋም ሚናውና የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ላይ ይጋጠሙት ፈተናዎች” በተሰኘ ጥናታዊ የምርምር ሥራቸው ላይ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተቋም ነፃና ገለልተኛ ሆኖ፣ የሕግ የበላይነትን ከማረጋገጥ አኳያ ውጤታማ ሥራ ሠርቷል ማለት እንደማይቻል አመልክተዋል፡፡አቶ …

ከአርበኞች ግንባር ጋር የተዋሀደዉ የግንቦት ሰባት ሊቀመንበር ዶክተር ብርሃኑ ነጋና እና የፓርቲያቸዉ ከፍተኛ የአመራር አባላት ወታደራዊ ትግል ለማካሄድ ወደሚንቀሳቀሱባት ኤርትራ ጠቅልለዉ መሄዳቸዉን አንድ የንቅናቄዉ አመራር አባል አስታወቁ። ቁጥራቸዉ ይፋ ያልተደረገዉ የአርበኞች ግንቦስ ሰባት የአመራር አባላትን ይዘዉ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ወደኤርትራ …

ዶክተር ብርሃኑና የፓርቲያቸዉ አመራሮች የትግል ርምጃ – ዶይቸ ቬለ Read more »

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በርስ በርስ ጦርነት በምትታመሰው የመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን እየመለሰ መሆኑን አስታወቀ። እስካሁን ድረስ 1,429 በዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት 4,442 በኢትዮጵያ መንግስት ስደተኞች መመለሳቸውን ድርጅቱ አስታውቋል። በተጨማሪም በሚቀጥለው ሳምንት 284 ኢትዮጵያውያን በጀልባ ወደ ጅቡቲ ለማጓዝ አቅዷል … Listen

  ሮናልዶ እንዲህ ይላል… “ለኔ ለዚህ ስኬት መድረስ ትልቅ አስተዋፅኦ ያደረገልኝን የልጅነት ጓደኛዬን አልበርት ፎንትራኦን አመሰግነዋለሁ! በጊዜዉ እኔና እሱ ከ18 አመት በታች ለታዳጊ ሻምፕዮና በአንድ ክለብ አብረን እንጫወት ነበር…አንድ ቀን የሊዝበን አሰልጣኝ ወደ እኛ መጣና እንዲህ አለን:- “ዛሬ ብዙ ጎል ያስቆጠረ ወደ እኛ አካዳሚ ይገባል” አለን! በእለቱም ጨዋታውን 3ለ0 ስናሸንፍ ጎሎቹንም የመጀመሪያውን እኔ 2ኛውን ደግሞ […]

Sur Construction Ethiopiaየአርበኞች ግንቦት 7 ህዝብ ግንኙነት ጋዜጣዊ መግለጫ:- የአርበኞች ግንቦት 7 ጀግና የነፃነት ፋኖዎች በኢትዮጵያ መሬት ላይ በህዝቡ ጉያ ውስጥ ሆነው በወልቃይት የጀመሩትን ወታደራዊ ጥቃት አሁንም አጠናክረው በመቀጠል የህወሓትን አገዛዝ እያሽመደመዱት ነው፡፡ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የተባለውን በቁሙ ደርቆ የበሰበሰ ዛፍ ከስሩ ገዝግዞ ለመቁረጥ የተጀመረው ትግል ሰሞኑን በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ልዩ ልዩ አካባቢዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ከወታደራዊ ጥቅምና ደህንነት አንፃር ስማቸውን ለመግለፅ በማይቻልባቸው የጎንደር ዙሪያ ወረዳ ልዩ ልዩ አካባቢዎች ላይ በሚንቀሳቀሰው የህወሓት ፀረ-ሽምቅና ሚሊሻ ኃይል ላይ ደፈጣ በመጣል ደምስሰውታል፡፡

በአዘዞ እና ጠዳ ከተሞች መካከል ከሚገኘው መገጭ ወንዝ አጠገብ በግንባታ ስራ ላይ የነበረው የሱር ኮንስትራክሽን የድንጋይ መፍጫ ማሽነሪዎች እና ሌሎችን የግንባታ ቁሳቁሶች በአርበኞች ግንቦት 7 አርበኛ ታጋዮች ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ስራውን አቁሞ እንዲሸሽ ተገዷል፡፡ ሱር ኮንስትራክሽን የህወሓቶች የግል ንብረት የሆነው ኤፈርት በስሩ ካሉት ከ60 በላይ የንግድ ኩባንያዎች አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ሱር ኮንስትራክሽን ውድመት በደረሰበት አካባቢ የግንባታ ስራውን በብቸኝነት የያዘው እንደተለመደው ያልምንም ጨረታ ነው፡፡ በተያያዘ ዜና ከዚያው ጎንደር ዙሪያ ወረዳ ውስጥ የሚኖር አቶ ጎሸ ሽባባው የተባለ ገበሬ ለአርበኞች ግንቦት 7 አርበኛ ታጋዮች ስንቅ አቀብለሃል በሚል በህወሓት ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ውሎ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞበታል፡፡ አቶ ጎሸ ሽባባው አሁን በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ማክሰኝት እስር ቤት ውስጥ ይገኛል፡፡

በላይ አርማጭሆ አንገረባ ቀበሌ የአርበኞች ግንቦት 7 የውስጥ አርበኞች እና የህወሓት ጸረ-ሽምቅ ኃይል ለአንድ ሰዓት የዘለቀ ጦርነት አድርገዋል፡፡ ጦርነቱም የተካሄደው ሀምሌ 11 2007 ዓ.ም ሲሆን በአካባቢው ለአሰሳ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የህወሓት ፀረ-ሽምቅ ኃይል በውስጥ አርበኞች የተከፈተበትን ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት መቋቋም ስላልቻለ አንድ ሰዓት ከፈጀ የተኩስ ልውውጥ በኋላ ለጊዜው ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቁ በርካታ አባላቱ ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል፡፡ የሱዳን መከላከያ ኃይል የኢትዮጵያን ወሰን ጥሶ ገብቶ ከሆር ሁመር ገበሬዎች ጋር መታኮሱ ታውቋል፡፡ በተደረገው የተኩስ ልውውጥ 2 ገበሬዎች ለሞት ተዳርገዋል፡፡ በአካባቢው ሰፍሮ የሚገኘው ህወሓት መራሹ መከላከያ ሰራዊት የሱዳን መከላከያ ኃይል ድንበር ሰብሮ ገብቶ በገሬው ህዝብ ላይ የጦር ጥቃት ሲያደርስ እየተመለከተ እንዳላየ በዝምታ አልፎታል፡፡

ከአርበኞች ግንቦት 7 የጥቃት ማግስት ጀምሮ የተለያዩ የነጻነት ሐይሎች ጦርነት እያካሄዱ እንደሚገኙ ከወያኔ ወታደራዊ ግንኙነት ክፍል የወጣ መረጃ አመለከተ። መረጃዉ እንደሚጠቁመዉ ኦነግና የኦጋዴን ነጻ አዉጪ ሀይሎችም ተመሳሳይ የሆነ ሽምቅ ዉጊያ ተያይዘዉታል። የአሜሪካዉ ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማን መምጣት ምክንያት ባደረገ መልኩ ኢትዮጵያ ምንም አይነት የጦርነት አዋጅ እንደማታዉጅ ወታደራዊ ደህንነቱ ለየ እዝ ባለስልጣናቱ ሚስጢራዊ ትዕዛዝ በማሳለፉ የእዝ አመራሮችን […]

  አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ የወሰነው የልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በምስክርነት እንዲያቀርብ ለሀምሌ 29/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጠ፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሀምሌ 13/2007 ዓ.ም ልደታ ፍርድ ቤት ቀርበው የመከላከያ ምስክር እንዲሆኑ ፍርድ ቤቱ ወስኖ የነበር […]

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ተኛው ወንጀል ችሎት በሽብር ከተከሰሱት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች መካከል አብዛኛቹ በአቃቤ ሕግ ማስረጃ ላይ ያቀረቡትን መቃወሚያ ውድቅ አደረገ። ካሁን ቀደም በዋለው ችሎት ሰባት ተከሳሾች አቃቤ ሕግ ያቀረባቸዉን የክስ ማስረጃዎች ተቃውመዉ ፍርድ ቤቱ ከመዝገቡ እንዲያስወጣላቸዉ በጠበቃቸው አማካይነት …

በእስር ላይ ያሉ የተቃዋሚ መሪዎች “ተቀባይነት የሌላቸው” ያሏቸው ማስረጃዎች ይነሱልን ጥያቄ – VOA Read more »

ሐምሌ ፲፬ (አስራአራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት እንደ አዲስ ባገረሸው የምስራቅ እዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላትና የሃረሪ ክልል ፖሊሶች ግጭት 4 ፖሊሶች በመከላከያ አባላት ታፍነው መወደሳቸውንና እስካሁን የደረሱበት አለመታወቅን የሃረር ወኪላችን ገልጿል። የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ከሁለቱ ሃይሎች የተውጣጡ መሪዎችን ለማነጋገር ሙከራ ቢያደርጉም አልተሳካላቸውም። በሃረሪ ፖሊስና በምስራቅ እዝ የፖሊስ አባላት መካከል ያለው ግጭት …

ሐምሌ ፲፬ (አስራአራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአርባምንጭ ምንጮች እንደገለጹት ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የፌደራል ፖሊስ አባላት በየአንዳንድ ኪሎ ሜትር ርቀት ፍተሻ ሲያደርጉ የታየ ሲሆን፣ አንዳንድ ሰዎች ላቀረቡት ጥያቄ የተሰጣቸው መልስ ” ግንቦት7″ ከተማው ውስጥ ገብቷል የሚል ነው። በከተማውና በዙሪያ ወራዳዎች የሚታየው ፍተሻና ቁጥጥር መጨመሩን ፣ ህዝቡም ግራ ተጋብቶ እንደሚገን ምንጮች …

ሐምሌ ፲፬ (አስራአራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእነ ዘላለም ወርቅአገኘሁ የክስ መዝገብ ከ1 እስከ 6ኛ እንዲሁም የ9ኛ ተከሳሽ ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ በደንበኞቻቸው ላይ በቀረበባቸው የክስ ማስረጃ ላይ ያቀረቡት ባለ 10 ገፅ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ጠበቃው አቶ ተማም አባቡልጉ ተከሳሾቹ ሀምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ተይዘው ከሶስት ወር …

ሐምሌ ፲፬ (አስራአራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኦባማ በአፍሪካ ለሚያደርጉት ጉዞ በተለይ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸው አገሪቱ በሰብአዊ መብት ጥሰቶችና በዲሞክራሲያዊ የስልጣን ሽግግር የሌላት በመሆኑ ከዓለምአቀፍ ማኅበረሰቡ ኢትዮጵያን መጎብኘት ማቆም እንዳለባቸው በማሳሰብ ከፍተኛ ወቀሳ እየተሰነዘረባቸው ነው። በአፍሪካ ስላለው የሰብዓዊመብት አያያዝ ላይ ፕሬዝዳንቱ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል።በአንፃሩ ለፀጥታና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ዓላማ ይዘው ወደ አፍሪካ አህጉር የሚያቀኑት ኦባማ …

በሺህዎች የሚቆጠሩ አፍሪቃውያን ስደተኞችን የሚረዱት የ40 ዓመቱ አባ ሙሴ እጎአ ለ2015 የኖቤል የሰላም ሽልማት ከታጩት ሰዎች መካከል አንዱ መሆናቸው ተዘግቧል ። አባ ሙሴ ለዚህ ሽልማት መታጨታጨታው ክብሩ ለርሳቸው ብቻ ሳይሆን ለአፍሪቃውያንም ጭምር ነው ይላሉ ። አባ ሙሴ ዘርዐይ እዚህ አውሮፓ …

አባ ሙሴ እና የበጎ አድራጎት ሥራቸው – ዶይቸ ቬለ Read more »

መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ እስር ላይ የቆዩት እነ ወይንሸት ሞላ ሰኔ 15/2007 ዓ.ም በቄራ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት እንዲፈቱ ከተፈረደላቸው በኋላ ሰኔ 22/2007 አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆባቸው ነበር፡፡ ይሁንና የልደታ ፍርድ ቤት ዛሬ ሀምሌ 14/2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት የቄራ ፍርድ ቤት በእነ ወይንሸት ላይ የወሰነውን ውሳኔ በማፅናት አቃቤ ህግ የጠየቀውን ይግባኝ ውድቅ አድርጎታል፡፡ […]

በእነ ዘላለም ወርቃገኘው የክስ መዝገብ ከ1-6ኛ እንዲሁም የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት ተማም አባቡልጉ በደንበኞቻቸው ላይ በቀረበባቸው የክስ ማስረጃ ላይ ያቀረቡት ባለ 10 ገፅ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ጠበቃው ተከሳሾቹ ሀምሌ 1/2006 ዓ.ም ተይዘው ከሶስት ወር በኋላ ጥቅምት 7/2006 ዓ.ም ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተገኘ የተባለ መረጃ ከአቃቤ ህግ ማስረጃዎች ማስረጃ ዝርዝርነት እንዲወጣ፣ ተከሳሾቹ […]

ከርበኞች ግንቦት 7 የጥቃት ማግስት ጀምሮ የተለያዩ የነጻነት ሐይሎች ጦርነት እያካሄዱ እንደሚገኙ ከወያኔ ወታደራዊ ግንኙነት ክፍል የወጣ መረጃ አመለከተ። መረጃዉ እንደሚጠቁመዉ ኦነግና የኦጋዴን ነጻ አዉጪ ሀይሎችም ተመሳሳይ የሆነ ሽምቅ ዉጊያ ተያይዘዉታል። የአሜሪካዉ ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማን መምጣት ምክንያት ባደረገ መልኩ ኢትዮጵያ ምንም አይነት የጦርነት አዋጅ እንደማታዉጅ ወታደራዊ ደህንነቱ ለየ እዝ ባለስልጣናቱ ሚስጢራዊ ትእዛዝ በማሳለፉ የእዝ አመራሮችን […]

የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ መኳንንት ብርሃኑ መኖሪያ ቤታቸው ተክብቦ በፖሊስ እየታደኑ መሆኑንን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አመልክተዋል፡፡ የአቶ መኳንንት ቤት በፌደራል ፖሊስ መከበቡ የታወቀ ሲሆን፣ አቶ መኳንንት ግን ለሳምንት ያህል ቤታቸው እንዳልገቡ ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል፡፡ ቤታቸው የካ ክፍለ ከተማ ኮተቤ አካባቢ የሚገኘው አቶ መኳንንት ብርሃኑ፣ መኖሪያ ቤታቸው እሳቸውን ለመያዝ በታዘዙ ፖሊሶች ተከብቦ ይገኛል ተብሏል፡፡ ፖሊስ አቶ […]

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው እየታየ የሚገኙት የዞን 9 ጦማርያን ዛሬ ሐምሌ 13/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ሐምሌ 1/2007 ዓ.ም ‹‹ክሳችሁ ተቋርጧል›› በሚል ከእስር ከተፈቱት ተለይተው በእስር ላይ የሚገኙት በፍቃዱ ኃይሉ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አቤል ዋበላ ዛሬ ለ31ኛ ጊዜ […]

አገዛዙ 11ኛዋ ሰአት ላይ በደጋፊወቹ ክፉኛ እየተሞገተ መሆኑ ተሰማ! የወያኔ ስራ አስፈጻሚዎች በደጋፊዎቹ ክፉኛ እየተሞገተ መሆኑን ከውስጥ አወቅ ምንጮች ያገኘናቸው የግምገማ መርጃወች አመላከቱ።የስር አቱ ደጋፊዎችና ታማኝ የሚባሉ ካድሬወች ያነሱት ነጥብ ሲጨመቅ እንደሚከተለው ቀርቧል። “በተለይ ለእኛ ስለ ወቅታዊ ሁኔታወች ስውር የሆነብን ምክንያት ምንድን ነው፧ እኛም የፓርቲያችን እና የአገራችን ጉዳይ ያገባናል። እርስ በእርሳቸው የሚጣረሱ ዜናወችና መረጃወችስ እንዲደርሱን […]

የአሜሪካው ፕ/ት ባራክ ኦባማ ይህን የተናገሩት ” በአሜሪካና በኤርትራ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን ለመወጋት የምታደርገውን ጥረት እያደናቀፉ በመሆኑ የእርስዎ መንግስት የኢትዮጵያን መንግስት ለመርዳት ምን ያክል ዝግጁ ነው ተብሎ ከኢቢሲ ጋዜጠኛ ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ ነው። ጋዜጠኛው የድርጅቱን ስም በግልጽ ከመግለጽ ቢቆጠብም፣ ፕ/ት ኦባማ የሰጡት መልስ ፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም ለአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ምክትል ሃላፊ […]

ሐምሌ ፲፫ (አስራሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአርበኞች ግንቦት7 ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ “ለነጻነት፣ ለፍትህና ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል መሬት ላይ ወርዶ መምራት ይገባል” በሚል እምነት በከፍተኛ ውጣ ውረድ ከአሜሪካ ኤርትራ መግባታቸው እንደተሰማ በአርበኞች ግንቦት7 ሰራዊት ውስጥ ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን ፣ አስመራ በሚገኘው የድርጅቱ ጽህፈት ቤት አቀባበል ያደረጉላቸው ሻለቃ አክሊሉ መዘነ ተናግረዋል።በዋና ጽህፈት …

ሐምሌ ፲፫ (አስራሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ህውሃት 40ኛ ዓመቱንና ኦህዴድ 25ተኛ አመቱን ባከበሩበት ማግስት፣ ብአዴንም 35ተኛ አመቱን ከሁለቱ ድርጅቶች ባላነሰ ለማክበር በብዙ መቶ ሚሊዮን ብር የሚቆጠር ገንዘብ መመደቡን የብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ባደረጉት ዝግ ስብሰባ መነጋገራቸውን ምንጮች ጠቅሰዋል። ከሀምሌ ወር, 2007 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም ጋዜጠኛ የብአዴንን ታሪክ ለማወቅ የሚረዱትን መጽሃፍት በማሰባሰብ እንዲያነብና …

ሐምሌ ፲፫ (አስራሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው የሚገኙት የዞን 9 ጦማርያን ሐምሌ 13/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። በእስር ላይ የሚገኙት በፍቃዱ ኃይሉ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አቤል ዋበላ ለ31ኛ ጊዜ ፍርድ …

‹‹የታሰርኩት ቤተሰቦቼን በእሳት አቃጠሉብኝ ብዬ ስለከሰስኩ ነው›› አቶ አንጋው ተገኝ በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ በሽብርተኝነት የተከሰሱት 16 የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ለሀምሌ 17/2007 ዓ.ም ለብይን ተቀጠሩ፡፡ አመራሮቹ ሀምሌ 1/2007 ዓ.ም በጠበቆቻቸው በኩል የክስ መቃወሚያና የዋስትና ጥያቄ አቅርበው የነበር በመሆኑ ዛሬ ሀምሌ 13/2007 ዓ.ም አቃቤ ህግ ለጥያቄው መቃወሚያ እንዲያሰማ ቀጠሮ ተሰጥቶት የነበር ቢሆንም ሳይቀርብ […]

. የትጥቅ ትግሉ ያሰጋው ወያኔ የጎንደር ህዝብን እያሰቃየ መሆኑ ተነገረ፡፡ . ‹ባራክ ኦባማ ሲመጣ ሰልፍ ለመጥራት እያደራጁ ነው በሚል የተከሰሱት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ጉዳይ ፍርድ ቤቱ ለሶስተኛ ጊዜ አላይም ማለቱ . አንድ ሣምንት የዘለቀው የልኳንዳ ቤቶች አድማ እደቀጠለ ነው፤ . የስዊድን ጠቅላይ ሚኒስትር  ከአዲስ አበባ መልስ ወደ ሆስፒታል አመሩ። . የወያኔ መንግስት በአሜሪካ ፍርድ ቤት  ተከሰሰ አሰግድ […]

የቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬሽን (ኢትዮ ቴሌኮም) ዋና መሥሪያ ቤት ዋና መሐንዲስና የደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ሁለት ሥራ አስኪያጆች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው፣ ሰኔ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 18ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የመሠረተባቸው ተጠርጣሪዎች፣ የዋናው መሥሪያ ቤት ዋና መሐንዲስ የነበሩት አቶ ተክለ ማርያም ለአከ ተክለ ማርያም፣ የኮርፖሬሽኑ የደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ምክትል ሥራ አስኪያጅና የማርኬቲንግ ኃላፊ የነበሩት አቶ መስፍን ሙርጋና የደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ጌታቸው ተረፈ አየለ ሲሆኑ፣ በግል ሥራ የተሰማሩ አቶ ግርማ ተስፋዬ የተባሉ ግለሰብም በክሱ ተካተዋል፡፡ 

ተከሳሾቹ የማይገባ ጥቅም ለማግኘትና ለሌላ ሦስተኛ ወገን ጥቅም ለማስገኘት በማሰብ፣ በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሯል፡፡ ክሱ እንደሚያስረዳው፣ አቶ ተክለ ማርያም ያላቸውን የቴክኖሎጂ ዕውቀት፣ ልምድና ክፍተት በመጠቀም በግል ሥራ ከሚተዳደሩት አቶ ግርማ ጋር ከአዲስ አበባ ወደ አዳማ (ናዝሬት) ይሄዳሉ፡፡ አዳማ እንደደረሱ ለሕገወጥ ዓላማ ማስፈጸማያ የሚውል ቤት በደላላ አማካይነት አቶ ታደሰ ጅማ ከሚባሉ ግለሰብ ይከራያሉ፡፡ የቤቱን ውል ከመፈጸማቸው በፊት ቤት አከራዩ አቶ ታደሰ ጂማ 30 ቀጥታ የስልክ መስመሮችን ከቴሌ ማስገባት እንዳለባቸው ይስማማሉ፡፡ አቶ ተክለ ማርያም አብረዋቸው የሚሠሩ የውጭ አገር ዜጎች እንዳሉም ለአከራዩ አቶ ታደሰ እንደነገሯቸው ክሱ ያብራራል፡፡ 

ከውጭ አገር የሚመጡት ኢንቨስተሮች በመሆናቸው ለስልኩ ወጪ ክፍያ ምንም ሥጋት እንዳይገባቸው ለአቶ ታደሰ ተነግሯቸው፣ የስልክ መስመሮቹ ከገቡ በኋላ ኅዳር 21 ቀን 1995 ዓ.ም. በንግድ ሥራ የሚተዳደሩት ሁለተኛ ተከሳሹ አቶ ግርማ ተስፋዬና አቶ ታደሰ የቤት ኪራይ ውሉን መፈጸማቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ አቶ ተክለ ማርያም ሳተላይት መቀበያ መሆኑን እያወቁ ከአቶ ግርማ ጋር በመመሳጠር በተከራዩበት ቤት ዲሽ በመትከል፣ አገሪቱ ከዘርፉ ልታገኝ የሚገባትን ገቢ እንድታጣ በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ 

አቶ ግርማ የተባሉት ተከሳሽ ቤት አከራዩን አቶ ታደሰን በዜግነት ጥቁር አሜሪካዊ እንደሆኑ በመግለጽ ከተዋወቋቸው በኋላ፣ አብረዋቸው ከነበረ ኤም ዴቪድ ከሚባል ነጭ አሜሪካዊ ጋር ያስተዋውቋቸዋል፡፡ ወደ ተከራዩት ቤት በመውሰድ በአከራይ ተከራይ ውል ላይ ካስፈረሟቸው በኋላ፣ ስልክ ላስገቡበት 16,500 ብር ለቴሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት እንደከፈላቸው ክሱ ይገልጻል፡፡ 

ለሕገወጥ ድርጊት የሚውሉ ዘመኑ ያፈራቸውን ዕቃዎች በኤርፖርት ታክሲ ጭነው አዳማ በመውሰድ፣ በታኅሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ዲሹን መትከላቸውንም ክሱ አክሏል፡፡ በመሆኑም በወንጀሉ በመሳተፍ በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ይገልጻል፡፡ 

የቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅና የማርኬቲንግ ኃላፊ የነበሩት አቶ መስፍን ሙርጋም፣ ቤት ያከራዩት አቶ ታደሰ 30 ቀጥታ መስመር እንዲገባላቸው ጥያቄ ሲያቀርቡ፣ የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ተረፈ ማኅተም ሳያደርጉ የመሩትን ደብዳቤ ‹‹ለምን?›› ብለው ምክንያቱን ሳያረጋግጡ የቀረበውን ጥያቄ በማፅደቃቸው፣ በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ አቶ ጌታቸውም ኮርፖሬሽኑ ያወጣውን የደንበኞች አገልግሎት አፈጻጸም መመርያ በመጣስ፣ ስልኮቹ ለምን ዓላማ እንደሚውሉ ሳይጠይቁና ሳያጣሩ በተዋረድ ላሉ ኃላፊዎች በመምራትና በማፅደቃቸው፣ በሕዝብና መንግሥት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስና አላግባብ ሥልጣንን መገልገል ወንጀል እንደተከሰሱ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ 

ሁሉም ተጠርጣሪዎች በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ በግብረ አበርነት በፈጸሙት ሥልጣንን ያላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በሌሉበት ስለተከሰሱ፣ ኮሚሽኑ ተከሳሾቹን አፈላልጎ ለሐምሌ 21 ቀን 2007 ዓ.ም. እንዲያቀርብ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 18ኛ ወንጀል ችሎት አዟል፡፡ 

 

በታኅሳስ ወር 2007 ዓ.ም. ኢትዮ ቴሌኮም ኤሪክሰን ለተባለው የስዊድን ኩባንያ ሰጥቶ ከነበረው የቴሌኮም ማስፋፊያ አራት ፕሮጀክቶች መካከል፣ መዘግየት አይቼበታለሁ ያለውን የአንዱን ፕሮጀክት (ሰርክል) ውሉን ሰርዞ ሁዋዌ ለተባለው የቻይና ቴሌኮም ኩባንያ መስጠቱን አስታወቀ፡፡ 

ኤሪክሰን ከማስፋፊያ ፕሮጀክቶች መካከል አራት ‹ሰርክሎች›ን ለመሥራት ተዋውሎ የነበረ ቢሆንም፣ በተለይ ደቡብ ደቡብ ተብሎ በተለየው የማስፋፊያ ፕሮጀክት አንዱን ‹ሰርክል› በውሉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ማጠናቀቅ ባለመቻሉ መነጠቁን፣ የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ አብዱራሒም አህመድ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

አቶ አብዱራሒም ለሁዋዌ በቀጥታ የተሰጠውን ፕሮጀክት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ ሁዋዌ ከዚህ በፊት የወሰዳቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በተሻለ አፈጻጸም ተግባራዊ ማድረግ በመቻሉ ከኤሪክሰን ተነጥቆ የተሰጠው መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡ 

‹‹ሁዋዌ በአዲስ አበባ ያከናወናቸውን የማስፋፊያ ሥራዎች ከውሉ ቀድሞ መጨረስ በመቻሉ፣ በቀጥታ እንዲሰጠው ተወስኗል፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡

የኤሪክሰን ፕሮጀክትን አስመልክተው አቶ አብዱራሒም ሲገልጹ፣ ፕሮጀክቱ በሰኔ ወር መጨረሻ ላይ አጠናቆ ማስረከብ ባለመቻሉ፣ የመጀመርያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አካል የነበረውን የቴሌኮም ማስፋፊያ ሥራ ማጓተቱን ጠቁመዋል፡፡ 

‹‹ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ሁዋዌ ስድስት ‹ሰርክሎች›ን እያከናወነ ሲሆን፣ በእስካሁን አፈጻጸሙ በጣም አመርቂ የሚባል ውጤት እያየንበት ነው፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡ እነዚህም የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች የሰሜን፣ የሰሜን ምሥራቅ፣ የሰሜን ምዕራብ፣ የምሥራቅና የአፋር ቀጣናዎች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በመላ አገሪቱ የሞባይል አገልግሎት ኔትወርክ ተደራሽነትን  ለማስፋፋት ባወጣው ጨረታ፣ ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች ሁዋዌና ዜድቲኢ ያሸነፉ ቢሆንም፣ ዜድቲኢ በስምምነቱ መሠረት እንቅስቃሴ ባለመጀመሩ ከወሰዳቸው ስድስት የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች አራቱ ለስዊድኑ ኤሪክሰን የቴሌኮም ኩባንያ መተላለፋቸው  በወቅቱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ታኅሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. በሒልተን ሆቴል ኢትዮ ቴሌኮምና ኤሪክሰን ባደረጉት የቬንደር ፋይናንሲንግ ፕሮጀክት ማስፋፊያ ስምምነት፣ የቻይናው ዜድቲኢ ቴሌኮም ኩባንያ ከአገሩ አቻው ሁዋዌ ቴሌኮም ኩባንያ ጋር ከተካፈለው የ800 ሚሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ውስጥ፣ አራቱ ለኤሪክሰን መሰጠታቸውን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

ዜድቲኢና ሁዋዌ በመላው ኢትዮጵያ ያሉትን 13 ‹ሰርክሎች› ወይም የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ሲካፈሉ፣ ሁዋዌ አዲስ አበባን ጨምሮ ሰባት ‹ሰርክሎች›ን ሲወስድ ዜድቲኢ ስድስት ‹ሰርክሎች›ን ለመሥራት መዋዋሉ ይታወሳል፡፡

 

የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ማውጫ ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉ ተጠቆመ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. 40/60ን ጨምሮ 40 ሺሕ የሚሆኑ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ እንደሚያወጣ የገለጸ ቢሆንም፣ የዕጣ ማውጫውን ቀን ላልተወሰነ ጊዜ ማስተላለፉ ተጠቆመ፡፡ 

ዕጣ ይወጣላቸዋል ከተባሉት የጋራ መኖሪያ ቤቶች በተለይ ለመጀመሪያ ጊዜ በዕጣ ይከፋፈላል የተባለው 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት፣ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት አለፍ ብሎ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊትና ሰንጋ ተራ የሚገኙት ሕንፃዎች ግንባታ የተጠናቀቀ ቢሆንም፣ አብረው መጠናቀቅ የነበረባቸው መሠረተ ልማቶች ባለመጠናቀቃቸው የዕጣ መውጫው ጊዜ እንዲራዘም መደረጉን ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

የአስተዳደሩ ካቢኔና ቦርድ ተሰብስቦ ውሳኔ አለማሳለፉም ለዕጣው አለመውጣት ሌላው ምክንያት መሆኑን የጠቆሙት ምንጮች፣ የአስተዳደሩ ከፍተኛ ሹማምንት በሕዝብ መገናኛ ብዙኃን ሳይቀር ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚተላለፉ ቤቶች እንዳሉ ሲገለጽ ከርሞ፣ ቃላቸው አለመጠበቁ ‹‹ለምን?›› የሚል ጥያቄ እያስነሳ መሆኑንም አክለዋል፡፡

የመሠረተ ልማት አለመሟላት እንደ ምክንያት ሊወሰድ እንደማይችል የሚናገሩት ምንጮች፣ በአሥረኛው ዙር ዕጣ ከወጣባቸው 35 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል የአብዛኞቹ ሳይቶች መሠረተ ልማታቸው ገና ያልተጀመረ በመሆኑ ነው፡፡ 

ለሪፖርተር አስተያየት የሰጡ የተወሰኑ የ40/60 ተመዝጋቢዎች፣ ሙሉ በሙሉ ክፍያ የፈጸሙ ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው ገልጸው፣ አሁን ግን ዋጋው በጣም ሊጨምር ስለሚችል ሙሉ በሙሉ የከፈሉም ቢሆኑ ተጨማሪ ክፍያ እንደሚጠየቁ መስማታቸው አሳስቧቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ሁሉም በዕጣው ተካተው ዕድለኞች በዕጣ እንደሚያገኙ፣ የቤቶቹን መገንባት ያዩ ሌሎች ተመዝጋቢዎች በመሀል ሙሉ በሙሉ መክፈላቸውም ስላሳወቁ፣ ሲጀመር አጠናቀው ከከፈሉት ጋር ሊቀላቀሉ መሆኑንና ሌሎች ወሬዎችን እየሰሙ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተባለው ጊዜም ዕጣ አለመውጣቱ እንዳሳሰባቸው ይናገራሉ፡፡

የ20/80 ተመዝጋቢዎች በበኩላቸው ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ዕጣው ሰኔ 30 እና እስከ ነሐሴ መጨረሻ ድረስ ወጥቶ ዕድለኞች የቤት ባለቤት እንደሚሆኑ የተነገረበት ወቅት የምርጫ ጊዜ በመሆኑ፣ ሕዝቡን ለመያዝ ነው የሚል ግምታቸውን ዕውን እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡ ይህ ባይሆን ኖሮ ዕጣው በተባለው ጊዜ መውጣት ነበረበት ሲሉም ይከራከራሉ፡፡ 

ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ዕጣ እንደሚወጣ በአስተዳደሩ ከፍተኛ ሹሞች ከገለጹ በኋላ ለምን ዕጣውን እንዳላወጡ ወይም ያልወጣበትን ምክንያት እንዲገልጹ፣ የአዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤትንም ሆነ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲን ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡ 

ነገር ግን አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ባልደረባ እንደሚሉት፣ ዕጣው ያልወጣው በሁለት ምክንያቶች ነው፡፡ የመጀመሪያው የአስተዳደሩ ካቢኔና ቦርድ ተሰብስቦ ውሳኔ ባለማስተላለፉ ሲሆን፣ ሌላው በታሰበበት ወቅት ይጠናቀቃሉ የተባሉ መሠረተ ልማቶች ባለመጠናቀቃቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዋናነት የ40/60 የቤት ፕሮግራም የመጀመሪያ ከመሆኑ አንፃር ሁሉም ነገር ተጠናቆ፣ ዕጣው በወጣበት ዕለት ለባለዕድለኞች ወዲያውኑ ቁልፍ ለማስረከብ በመታሰቡ መሆኑን አክለዋል፡፡

   

 

በአልሸባብ ተመልምለው የሕዋስ (ሴል) አባላት ናቸው የተባሉ ኢትዮጵያ ውስጥ በተመረጡ ቦታዎችና በመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ላይ የሽብር ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር የዋሉ የተባሉ አምስት ተጠርጣሪዎች፣ ኢትዮጵያውያን፣ ሐምሌ 6 ቀን 2007 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 (1/ሀ)ን በመተላለፍ በዋና ወንጀል ተካፋይ በመሆን፣ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 38 (1 እና 2) በመተላለፍ ወንጀል ለመፈጸም አድማ በማድረግና የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ (4)ን በመተላለፍ የሽብር ድርጊት ለመፈጸም የማቀድ፣ የመዘጋጀት፣ የማሴርና የማነሳሳት ሙከራ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል ብሎ ክስ የመሠረተባቸው፣ በድሪ የሱፍ ሮባ፣ አነስ ኡስማን ዑመር፣ አህመድ ኑር ሳኒ፣ መሐመድ አህመድ ኡስማንና እስማኤል አደም መሐመድ ናቸው፡፡

ዓቃቤ ሕግ ለፌዴል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው ክስ እንደሚያስረዳው፣ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡ 

ተከሳሾቹ ከአልሸባብ ጋር በመስማማትና አባል በመሆን ከሶማሊያ ግዛት ወደ ኢትዮጵያ የሚላኩ ተቀጣጣይ ፈንጂዎች መሥራት የሚችሉ የአልሸባብ የፈንጂ ሥራ ባለሙያዎችን ለመቀበል፣ ለፈንጂ መሥሪያ የሚሆን ቤት ለመከራየት ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ክሱ ያስረዳል፡፡

በድሪ የሱፍ ሮባ የተባለው ተጠርጣሪ በሽር ቱሬ በሚባል የአልሸባብ አመራር በ1999 ዓ.ም. በአባልነት ከተመለመለ በኋላ፣ ሞቃዲሾ ውስጥ በሚገኘው አቡሐረሬ ተብሎ በሚጠራው መስጊድ ውስጥ ለስድስት ወራት ወታደራዊና የፖለቲካ ትምህርት ሥልጠና መውሰዱን ክሱ ያስረዳል፡፡ ተጠርጣሪው በ2002 ዓ.ም. ወደ መቋዲሾ በመሄድ ለአልሸባብ አባል የሚሆኑ ወጣቶችን በመመልመል ለሥልጠና እዚያ እንዲሄዱ ሲያዘጋጅ እንደነበርም በክሱ ተጠቁሟል፡፡ 

ግለሰቡ ጥቃት ለመፈጸም ከሞቃዲሾ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት የሚመጡትን የህዋስ አባላት መኖሪያ ቤት ተከራይቶ ለማስቀመጥ፣ የተመለሱትን ወጣቶች በኃላፊነት ለመምራት፣ መረጃ እየሰበሰበ ለአልሸባብ አባላት እንዲልክ የተሰጠውን ተልዕኮ ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሯል፡፡

አብዱልአዚዝ አልዩ (አቡ ያሲን) የተባለ የአልሸባብ አመራርና የፈንጂ ባለሙያ በ2006 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ገብቶ ባሌ ሮቤ ከተማ ውስጥ መልምሎ በህዋስ ያራጃቸውን ስድስት አባላት፣ አንደኛ ተከሳሽ እንዲመራቸው ኃላፊነት መውሰዱንም ክሱ ያስረዳል፡፡

ሻሸመኔ ከተማ ውስጥ ‹‹ቁርዓን አስተምራለሁ ወይም የቁርዓን መምህር ነኝ›› በሚል ሽፋን አባላትን መመልመልና ማደራጀት እንዳለበት በሽር ቱሬ ከሚባለው የአልሸባብ አመራር ተልዕኮ መቀበሉንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ ጠቅሷል፡፡ አገር ውስጥ ባሉ የተለያዩ ባንኮችም ገንዘብ ይላክላቸው እንደነበር የገንዘቡን መጠንና የባንኮቹን ስም ጠቅሶ ዓቃቤ ሕግ በክሱ አካቷል፡፡

በኅዳር ወር 2007 ዓ.ም. በጊኒር በኩል ወደ ኢትዮጵያ ይገባል ለተባለው የአልሸባብ አመራር አብዱላዚዝ፣ በነገሌ ቦረና በኩል በታኅሳስ ወር 2007 ዓ.ም. ፈንጂ ይዘው የሚገቡትን አባላት አንደኛ ተከሳሽ ሻሸመኔ በሚገኘው ቤቱ አሳርፏቸው ፈንጂ የሚሠራበትን ማቴሪያል እንዲያዘጋጅና የማፈንጃ ዒላማዎችን እንዲያጠና ተልዕኮ ተቀብሎ ይንቀሳስ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡ ሻሸመኔ፣ አሰላና ባሌ ሮቤ ከተሞች ውስጥ ባንክ ቤትና ፖስታ ቤት መኖር አለመኖሩን አጥንቶ እንዲቆይም ትዕዛዝ ተሰጥቶት እንደነበር አክሏል፡፡ ተጠርጣሪው የሽብር ቡድኑ አደራጅና አመራር በመሆን ተሳታፊ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በዝርዝር ገልጿል፡፡ 

ሁለተኛው ተጠርጣሪ ተከሳሽ አነሰ ኡስማንም እንደ አንደኛ ተከሳሽ በተለይ ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ ውስጥ በመንቀሳቀስ አባላት በመመልመል፣ በተለይም አራተኛና አምስተኛ ተከሳሾችን መልምሎ ወደ ሶማሊያ ሥልጠና ሊልክ ሲል በቁጥጥር ሥር መዋሉን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ ሦስተኛ፣ አራተኛና አምስተኛ ተከሳችም በሁለተኛ ተከሳሽ ከተመለመሉ በኋላ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሥልጠና ለመውሰድ ወደ ሶማሊያ ለመሄድ በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው በክሱ ተገልጿል፡፡

ተከሳሾቹ ክሱ በችሎት ከተነበበላቸው በኋላ በራሳቸው ጠበቃ ማቆም እንደማይችሉ በመግለጻቸው፣ የተከላካይ ጠበቃ ጽሕፈት ቤት ጠበቃ እንዲመደብላቸው ትዕዛዝ በመስጠት ፍርድ ቤቱ ለሐምሌ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

 

በምስራቃዊ ኢራቅ ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን በጣለው የቦምብ ጥቃት ቢያንስ 120 ሰዎች መገደላቸውንና 130 የሚሆኑ ደግሞ መቁሰላቸው ተገለፀ። ከኢራቅ ዋና ከተማ 35 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውና የሺዓ እስልምና ተከታዮች በሚኖሩባት የካን ባኒ ሳድ ከተማ በመኪና ላይ የተጫነው …

ኢራቅ ዋና ከተማ ባግዳድ በአይሲስ የቦምብ ጥቃት 120 ሰዎች ተገደሉ Read more »

(ክንፉ አሰፋ ቶሮንቶ) ሰብለ (ሚሚ) ዲትሪች ለመጨረሻ ግዜ የታየችው እ.ኤ. አ. ጁላይ 10 2014 (ባለፈው አመት) ነበር። የሶስት ልጆች እናት የነበረች የዚህች ኢትዮጵያዊት በድንገት መሰወር ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖ ሰንብቷል። ለአመት የጠፋችው ይህች ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሴት በህይወት እንደማትኖር በርካቶች ቢጠረጥሩም፣ ማንንም ሳታማክር በድብቅ ወደ ሃገርዋ ገብታለች የሚሉ አልጠፉም። አለም አቀፍ ፖሊስ በአለም ዙርያ ፍለጋውን ተያያዘው። ሰብለ-ቀብር […]

ጌታቸው በቀለ፣ ጉዳያችን ብሎግ ኢትዮጵያ የገባችበት ብድር ከፍተኛ ቢሆንም የመሰረታዊ ፍላጎቶችን በዋና ከተማ ደረጃም ማዳረስ አልቻለችም በቢልዮን የሚቆጠር ዶላር የት ገባ? አንዲት ሀገር ከጠቅላላ ምርቷ 30 ከመቶው ከለጋሽ ተቋማትና ሃገራት የሚገኝ ብድር ላይ ከተመሰረተ ከፍተኛ የዕዳ ቀውስ ውስጥ እየገባች መሆኗን …

ሀገራችን ከመሸጧ በፊት መድረስ የዜጎች ግዴታ ነው! Read more »