የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 27 እና 28/2007 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ሊያደርገው ላቀደው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግለት፣ ህዳር 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ መጠየቁ የሚታወስ ቢሆንም አስተዳደሩ በቁጥር አ.አ/ከፅ/10/30.4/55 ህዳር 19 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፈው የመልስ ደብዳቤ ለሰላማዊ ሰልፉ እውቅና አለመስጠቱን አስታውቋል፡፡

ትብብሩ ለሰልፉ የመረጠው ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን፣ አስተዳደሩ በበኩሉ የ24 ሰዓቱን ሰልፍ ላለማወቁ ምክንያት ነው ያለውን ሲያስቀምጥ፣ ‹‹የተጠየቀው ቦታ በልማት ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅና ትላልቅ የመንግስት ተቋማት እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ያሉበት ስለሆን ጥያቄውን ተቀብለን ለማስተናገድ የምንቸገር መሆኑን እየገለጽን፣ የአደባባይ ስብሰባውም ሆነ ሰላማዊ ሰልፉ እውቅና ያልተሰጠው መሆኑን እናስታውቃለን›› በማለት አስፍሯል፡፡

የትብብሩን ሰልፍ እያስተባበሩ ያሉት ፓርቲዎች አመራሮች ዛሬ ለአስተዳደሩ በጻፉት ደብዳቤ እንደጠቀሱት ደግሞ፣ የሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 3/1983 አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 2 “የከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት በዚህ አዋጅ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 1 የተመለከቱትን ሁኔታዎች በማገናዘብ ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ሥፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያየት ካለው ምክንያቱን በመግለፅ ይህንኑ ጥያቄው በደረሰው በ12 ሰዓት ውስጥ በጽሁፍ ለአዘጋጁ የማሳወቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሆኖም የከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው ምን ጊዜም ወይም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ማለት አይችልም” በማለት አስተዳደሩ እውቅና የመንፈግ ስልጣን እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
Image
በመሆኑም፡-
‹‹1ኛ. እውቅና እንዲሰጥ የተጠየቀ ማንኛውም አካል ከላይ የተደነገገውን በማገናዘብ ለሌላ ጊዜና በሌላ ቦታ እንዲደረግ ሃሳብ ከማቅረብ ውጭ ሰላማዊ ሰልፉ ምን ጊዜም ወይም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ለማለት ለመስሪያ ቤታችሁ ስልጣን ያልተሰጠ በመሆኑ፤
2ኛ. ሰላማዊ ሰልፉና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የሚከናወኑት በመሰረታዊነት ለትላልቅ የመንግስትና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ለማሳወቅ በመሆኑ በእነዚህ አካባቢ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ማድረግ በአዋጁ ያልተከለከለ በመሆኑ፤

ለጥያቄያችን የተሰጠን መልስ ከምክንያታዊነትና ህጋዊነት ውጭ ሰልፉ እንዳይካሄድ ለመከልከል ስለሆነ እንዲህ ዓይነቱን ኢ-ህጋዊ የሆነ ውሳኔና አሰራር ፈፅሞ የማንቀበል በመሆኑ አስቀድመን ባሳወቅነው መሰረት ሰላማዊ ሰልፉን በተጠቀሰው ቀን፣ ሰዓትና ቦታ የምናካሂድ መሆኑን እያሳወቅን በጽ/ቤታችሁ በኩል አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግልን በድጋሚ እናስታውቃለን›› ብሏል ትብብሩ ዛሬ ለአስተዳደሩ በጻፈው ደብዳቤ፡፡

ሰዎች በማንኛውም መንገድ ሸብረክ ሸብረክ የሚሉ ከሆነ መርህ አልባ መሆናቸውን ከማሳየት ውጭ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡ ባለፈው ሳምነት ፍኖተ ነፃነት ላይ ወጣቱ ፀሃፊ ኢዮኤል ፍስሃ ዳምጤ ለምን እንደምንፈራ ቁልጭ አድርጎ አሳይቶን ነበር፡፡ የገዢዎቻችን በትር የበረታብን በእነርሱ ጥንካሬ ሳይሆን ከፍርሃት በመጣ ዝምታችን እንደሆነ አስምሮበታል፡፡ መፍትሔውም ከፍርሃት መላቀቅና ዝምታውን ማፍረስ ነው፡፡ በዛሬው ፅሁፌ ማንሳት የፈለኩት ደግሞ ለምን […]

በእርግጥም “ እንዲህ እንደዋዛ ሲጠሩት ቀላል ይመስላል ቃሉ፤ እረ ሁላችሁም፤ አገር አገር በሉ፤ አገር አገር በሉ”። የምትለዋ ስንኝ በጋራ ስንላት ንዝረቷ ለጉድ ነበር። ተመኩሮዬን ያኔ ቆርጦ ሰልፉ ላይ የነበረ በቅርብ ፅፎ አስታወሰኝ። “ተርቲብ” የምትለዋን ቃል ትርጉም እስካሁን ስለማላውቅ ሙሉ መልክቱን በእርግጥ በትክክል አልረዳውም። ያም ሆኖ “ተርቲብ፤ አላህ ዋአክበር”። በጋራ ስትሉት ሲያምር። ምጥን ያለና ጉልበታም ነበር። […]


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
——
የልጅ እያሱ ሞት ይፋ የወጣው በህዳር ወር 1928 ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ወደ ማይጨው ከመዝመታቸው ሶስት ቀን አስቀድሞ ነው። በአሟሟታቸው ዙሪያ ከሚነገሩት መካከል
·        ልጅ እያሱ የተገደሉት ሀረር ውስጥ ነው::
·        ልጅ እያሱ የተገደሉት አዲስ አበባ ገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ውስጥ ሲሆን የተቀበሩትም ከቤተ መንግሥቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከሚገኘው ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ክልል ነው::
·        ልጅ እያሱ የቀብራቸው ስነ-ስርዓት የተከናወነው ደብረ ሊባኖስ ነው::
·        ልጅ እያሱ የተቀበሩት ሰንዳፋ ውስጥ ነው የሚሉት ይገኙባቸዋል።
የልጅ እያሱን አሟሟት አውቃለሁ በማለት እማኝነታቸውን ከሰጡ ግለሰቦች መካከል አገልጋያቸው የነበሩ አዛውንት ኢጣሊያኖች አቤቶ እያሱን ከጋራሙለታ እስር ቤት ለማስወጣት ሙከራ አድርገው እንደነበር በመግለጽ እንዲህ ይላሉ።
 
 “የኢጣሊያ ወኪሎች አባጤናን ከግራዋ እስር ቤት ለማስወጣት ከሞከሩ ጀምሮ ልዑልነታቸው በእስር ቤቱ ክልል እየተከዙ ወዲያ ወዲህ ይንጎራደዱ ነበር። አንድ ቀን ምሽት አንዲት አውቶሞቢል ወደ እስር ቤቱ መጣች። እርሳቸውም ይፈሩት የነበረው ሰው መኖር አለመኖሩን ጠየቁ። በቀጣዩ ቀን “የመጡት አባ ሐና ብቻ ናቸው” አልኳቸው። ነገር ግን ጥቂት ዘግይቶ ሁለተኛዋ አውቶሞቢል ሁለት ሰዎችን አሳፍራ መጣች። ከሁለቱ አንዱ ፊታውራሪ ነበር። እስኪጨልም ቆይተው እያደቡ ወደ እስር ቤቱ ተጠጉ። መዝጊያው ሰፋፊ ስንጥቆች ያሉት በመሆኑ ልዑልነታቸው በስንጥቆቹ ውስጥ አዘውትረው ምራቃቸውን ጢቅ ይሉ ስለነበር ሲያነጣጥሩባቸው ሳያዩአቸው አልቀረም። በተኮሱባቸው ጊዜ የመስኮቱን መቃኖች ጨምድደው ጨበጡ። ኃይለኛ ስለነበሩ ቤቱን በሙሉ ያናጉትና የሚናድ መስሎኝ ፈርቼ ነበር። ተንገዳግደው ወለሉ ላይ ሲወድቁ ሰማሁ። ሬሳቸው በባቡር ተጭኖ ወደ አዲስ አበባ ከመወሰዱ በፊት ሁለቱ ነፍስ ገዳዮች እንደ ባላዛር ሬሳቸው ላይ ተጎንብሰው አጓሩ። ሬሳቸው አዲስ አበባ እንደደረሰ ከፍተኛ ባለስልጣን ለባላምባራስ አበበ አረጋይ አስረከቡ። እንግዲህ ሬሳቸው ለዘላለም ያረፈበትን ቦታ የሚያውቁት ባላምባራስ አበበ አረጋይ ብቻ ናቸው። ይሁንና እኒሁ ሰው ደግሞ በ1953 በተሞከረው የመንግሥት ግልበጣ ጊዜ የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው ነበርና በአረንጓዴው የገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ታዛ ወለል ላይ ደማቸው ፈስሶ ሞቱ። አባ ሃና ጂማም ተመሳሳይ እጣ ገጠማቸው”።
    እንደ አዛውንቱ ምስክርነት ከሆነ አባ ሐና ጅማም ሆነ አበበ አረጋይ የልጅ እያሱን አስከሬን በተረካከቡበት ቦታ ላይ ስለተገደሉ ምስጢሩ አብሮ ሞቷል ማለት ነው።
ሌላኛዋ ለቤተ መንግሥቱ ቅርበት ያላቸው ሴት ደግሞ ለጎበዜ ጣፈጠ እንዲህ ብለው ነበር የተናገሩት (“አባ ጤና እያሱ” ከተሰኘው የጎበዜ ጣፈጠ ድርሰት የተወሰደ ነው)።
    “ዕለቱን አላስታውስም። ቢሆንም ልጅ እያሱ አርፈዋልና ቤተ መንግሥት እንድትመጡ የሚል መልዕክት ተላለፈ። እኛም ማልደን ወደ ቤተ መንግሥቱ ሄድን። አዲስ አበባ ውስጥ የምንገኝ ወይዛዝርትና መኳንንት ተሰብስበን ስንላቀስ ዋልን። ሬሳ ግን አልነበረም። እቴጌ መነን በጣም አዝነውና ተክዘው እንባቸውን ያፈሱ ነበር።  ጃንሆይ በርኖሳቸውን ገልብጠው ደርበው ወንድሜ ወንድሜ በማለት ያለቅሱ ነበር።”
ልጅ እያሱን በታሸገ ባቡር አሳፍሬ ወደ አዲስ አበባ ልኬአቸኋለሁ በማለት እማኝነታቸውን የሚሰጡት ብላቴን ጌታ ዶ/ር ሎሬንዞ ታዕዛዝ በበኩላቸው የቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን ቄስ የነበሩ ገ/መድህን የተባሉ ግለሰብ እንዲህ በማለት ነግረውኛል ይላሉ።
“በቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን ትይዩ የዱክ ቤት ይባል በነበረው ህንጻ ሰገነት ላይ አንድ እጆቹን በሰንሰለት የታበተ ሰው ከቀትር በኋላ ዘወትር ሲመላለስ እናየው ነበር። ነገር ግን ጃንሆይ ወደ ጦርነቱ ከመዝመታቸው በፊት ሌሊቱን ጸሎተ ፍትሐት እንድናደርግ ታዘዝን። ሆኖም የሟቹን ሰው የክርስትና ስም የሚነግረን አልነበረም። ከዚያ በኋላ ያ ሰውዬ ይመላለስበት ከነበረው ሰገነት ላይ አልታየም። እኛም የሞቱት ልጅ እያሱ እንደሆኑ ተረዳን።
(ምንጭ፡- ጎህ መጽሄት፣ ቅጽ 1 ቁጥር 5፣ ጥቅምት 1993፣ ገጽ 6/22)
—————–
ለዚሁ መጽሄት ቃለ-ምልልስ የሰጡት የልጅ እያሱ የልጅ ልጅ ፕሮፌሰር ግርማ ዮሐንስ እያሱ ቄስ ገ/መድሕን የተባሉት ሰው ከሰጡት ምስክርነት ጋር የሚጣጣም ቃል አሰምተዋል። ፕሮፌሰር ግርማ እንዳሉት ልጅ እያሱ በስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ባለው የዱክ ቤት (አሁን Law Faculty ዋና ህንጻ የሆነው) መታሰራቸው እውነት ነው። “አጼ ኃይለ ስላሴ ወደ ማይጨው ሀሙስ ከመዝመታቸው በፊት ማክሰኞ ሌሊት ልጅ እያሱ ተገድለው አሁን የዩኒቨርሲቲው የእግር ኳስ ሜዳ ከሆነውና ያኔ የቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን አጸድ ከነበረው ስፍራ ተቀብረዋል” ይላሉ ፕሮፌሰር ግርማ።
—————
አፈንዲ ሙተቂ
ሰኔ 22/2005
ሀረር- ምስራቅ ኢትዮጵያ

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

1- ሁለቱም በፈጣሪ አያምኑም ( የራሴ የሚሉት እምነት የላቸውም)
2- የጦር አዛዦቻቸው::ሂትለር በራሱ ግዜ ሮሚዮን ማርሻል አድርጎታል –መለስ ሳሞራን < ጀነራል> አድርጎታል
3-ሂትለር ሁለት ልጅ ነበረው::መለስም ሁለት ልጆች አሉት
4-ሁለቱም በጅምላ ህዝቦችን ጨርሰዋል (የዘር ማጥፋት ፈጽመዋል)
5-ሁለቱም insomnia ይሰቃዩ ነበር :; ( የመተኛት ችግር ከተኙም ቶሎ አለመንቃት)
6-ሁለቱም የሶሻሊዝም issue ነበራቸው:;ለዚህም ማሌሊትን ልብ ይልዋል
7- በዘር እና በጎሳ ላይ የተመሰረተ ፓርቲ በመፍጠርም ይታወቃሉ ::
8-ሂትለር ታላቅዋን ጀርመን ለመመስረት እቅድ የነበረው ሲሆን መለስ ደግሞ ታላቅዋን ትግራይን ..
9-E -ዲሞክራሲ ናቸው
10-ራሳቸውን በራሳቸው የፓርቲ እና የአገር መሪ አድርገው ሾመዋል Dagem Ahunem

Image

Eyasped Tesfaye…….(የግል ዕይታ)
‹‹……ሪቮሉሽን የአዳራሽ ዙሪያ አመፅ አይደለም፤ የሰፊው ህዝብ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ሰፊው ህዝብ ካልተሳተፈበት፣ ካልደገፈው፣ አይሆንም፤ አይፀናምም፡፡ የጥቂቶች አመፅ በሌሎች ጥቂቶች አመፅ ይገለበጣል፡፡ መሰረታዊ ለውጥ፣ በሰፊው ህዝብና በጨቋኝ መደቦች መካከል የሚካሄደው የትግል ፍሬ ነው፡፡….››ዴሞክራሲያ ቅፅ1 ቁ15
የኢትዮጲያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በ1993 ያሳተመው አማርኛ መዝገበ ቃላት አብዮት የሚለውን ቃል ‹‹በአንድ ነገር ክስተት ወይም ሂደት ውስጥ ያሉ ቅራኔዎች ተካረው ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሲደርሱ የሚፈጠር መሰረታዊ ለውጥ፤ አዲስ ከፍተኛና የተሻለ ነገር፤ ክስተትና ሂደት ወይም አስተሳሰብና እውቀት የሚከሰትበት፡፡›› የሚል ትርጓሜ ይሰጠዋል፡፡
አብዮት በተለያየ የታሪክ ወቅት እንዲሁም በተለያየ ቦታ ተከስቷል፣ እየተከሰተ ነው፤ ወደፊትም ይከሰታል፡፡ ከፈረንሳይ አብዮት እስከ ሩሲያው አቢዮት፤ ከላቲን አሜሪካ ሀገሮች እስከ ሩቅ ምስራቅ እስያ ብሎም እስከ አረቡ አብዮት፤ የአብዮት ንፋስ ያልነፈሰበት የአለማችን ክፍል የለም፡፡ በተለያዩ ቦታዎች የተካሄዱ አብዮቶች እንደወቅቱ እና እንደቦታው የራሳቸው የሆኑ መለያዎች ያሏቸው ይሁን እንጂ ሁሉም የሚጋሯቸው የወል የሆኑ ባህርያትም አሏቸው፡፡ ይኸውም ሁሉም አብዮቶች በጭቆና ማህፀን ውስጥ ተፀንሰው መወለዳቸው ነው፡፡
አብዮቶች ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ አሊያም ኢኮኖሚያዊ መነሾ ምክንያቶች ሊኖሯቸው ይችላል፡፡ ለምሳሌ ታሪካዊውን የፈረንሳይ አብዮት ያየን እንደሆነ ሶስቱም መነሾ ምክንያቶች እንደነበሩት እንረዳለን፡፡ የፈረንሳይ ህዝብ በፈላጭ ቆራጭ ንጉሳዊ አስተዳደር ስር ሆኖ መብቶቹን መገፈፉ የአብዮቱ ፖለቲካዊ መነሾ ሲሆን፤ በፈረንሳይ ህዝብ መካከል የነበረው የመደብ ልዩነት በተለይም አብዛኛው የፈረንሳይ የህብረተሰብ ክፍል በድህነት የሚማቅቅበት እና መብቱን የተነፈገበት ሶተኛው መደብ ውስጥ መካተቱ የአብዮቱ ማህበራዊ መነሾ ሆኗል፡፡ እንዲሁም ደግሞ በወቅቱ ፈረንሳይ በከፍተኛ የኢኮኖሚ ድቀት ውስጥ መገኘቷ እና በዜጎች ላይም ያለው የግብር ጫና ከፍተኛ መሆኑ የአብዮቱ ኢኮኖሚያዊ መነሾ ሆኗል፡፡
አብዮቶች አብዛኛውን ጊዜ በገዢው መደብ በኩል ሳይጠበቅ የሚከሰት ክስተት ነው፡፡ ለዚህም ነው የሩቁ የፈረንሳይ አብዮትም ሆነ የቅርብ ግዜው የአረቡ አለም አብዮት አለምን ያስደነቀው፡፡ አንዳንድ አብዮቶችን ትልልቅ የስለላ ተቋማት(ሲ.አይ.ኤ፤ ኬጂቢ) ሳይቀር ያልጠበቁት ክስተት እንደነበር ታሪክ ያስገነዝበናል(መሀመድ ሬዛን ያስወገደውን የኢራኑን አብዮት ልብ ይሏል)፡፡ ይህ የሚሆንበትን ምክንያት ቲሙር ኩራን የተሰኘው ፀሀፊ ‹‹sparks and praire fires: a theory of unanticipated political revolution›› በተሰኘው ፅሁፉ ላይ በአለማችን ላይ የተከሰቱትን ሶስት ዋና ዋና አብዮቶችን እንደምሳሌ በማንሳት ህዝብ የተቃውሞው ወገን እስኪጠናከር ድረስ በገዢው ወገን ላይ ያለውን ጥላቻ በውስጡ ደብቆ መያዙ አብዛኛውን ግዜ ገዚዎችን እንዲዘናጉ እንደሚያደርጋቸው ገልፆ አብዮቱ አንድ ግዜ ከፈነዳ በኋላ ለማስቆም አስቸጋሪ የሚያደርገውም በህዝብ ዘንድ ስር የሰደደ እና የቆየ ጥላች እና ቅራኔ መኖሩ እንደሆነ ያስረዳል፡፡
ለአብዮት መነሳት ምክንያቱ ከላይ የዘረዘርናቸው ቅራኔዎች(ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ) ቢሆኑም ከእነዚህ ሁሉ ቀድሞ የሚመጣው ግን የህብረተሰቡ የንቃተ ህሊና(enlightenment) ጉዳይ ነው፡፡ በላቲን አሜሪካ የተካሄዱት አብዮቶች ላይ ጥናት ያካሄዱት እንደ ዴቪድ ክሎስ ያሉ ምሁራኖች ለአብዮቱ መነሳት ዋና ምክንያት አድርገው የሚያቀርቡት የህብረተሰቡ ንቃተ ህሊና መዳበሩን እና በሌሎች ሀገራት የተካሄዱትን አብዮቶች ከራሱ ሀገር ነባራዊ ሁኔታ ጋር ማስተያየት እና ማገናዘብ መቻሉ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡
በሀገራችን በኢትዮጲያም ተከስቶ የነበረውን የ66ቱን አብዮት ያየን እንደሆነ በአለም ዙሪያ የነበረው ሁኔታ በወቅቱ የነበሩትን ወጣቶች ላይ ተፅእኖ ማሳደር መቻሉ እና የወጣቱ ንቃተ ህሊና የዳበረ መሆኑ ከነበረው ጭቆና ባሻገር ለአብዮቱ መነሳት አበይት ምክንያት ነበር፡፡
እነዚህን ከላይ የዘረዘርናቸውን የአብዮት መነሾዎች ይዘን የሀገራችን ነባራዊ ሁናቴ ካጤንን በኢኮኖሚው በፖለቲካውም ሆነ በማህበራዊው ዘርፍ ያለው ከፍተኛ የሆነ ምስቅልቅል እና ብሶት ለአብዮቱ መነሳት በቂ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ነገር ግን መረጃ የማግኘት መብቱን የተነፈገው ሰፊው የህብረተሰብ ክፍል መብቱን በማስከበር ዙሪያ ላይ ያለው የንቃተ ህሊና መዳበር በጥያቄ ውስጥ ያለ ጉዳይ ይመስለኛል፡፡
የቡርኪና ፋሶው የአብዮት ንፋስ በፍጥነት ወደ ቶጎ እና ጋቦን ተዛምቶ አምባገነን መንግስታትን ሲያንቀጠቅጥ ይህንን ጀብዱ የሰማው የኢትዮጲያ ህዝብ ምን ያህል ነው; ሰምቶስ ወስጡን የኮረኮረው እና መንፈሳዊ ቅናት ያደረበት ስንቱ ነው; የሚለው ጉዳይ ያሳስበኛል፡፡
በእኛ ሀገር አብዮት እንዲነሳ ካስፈለገ አብዮቱ መሪ ያሻዋል፡፡ በቡርኪና ፋሶም ሆነ አሁን በቶጎ እና በጋቦን የተነሳው ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ናቸው እየመሩት ያሉት፡፡ በእኛም ሀገር ባለው ተጨባጭ ሁናቴ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች አስተባባሪነት ውጪ በአሁኑ ሰዓት በራሱ የሚፈነዳ አብዮት ይኖራል ብሎ መገመት አስቸጋሪ ነው፡፡ ነገር ግን ተቃዋሚዎች
1ኛ፡- ለህዝብ ወቅታዊ መረጃዎችን በማቀበል እና በመተንተን የህዝብን ንቃተ ህሊና የሚያሳድጉበትን መንገድ መቀየስ ይኖርባቸዋል፡፡
2ኛ፡- በህዝብ ዘንድ ያላቸውን ቅቡልነት በማሳደግ የሚሞትላቸው ድርጅቶች መሆናቸውን ማረጋገጥ አለባቸው፡፡
Image

በኢትዮጵያ የሚፈጸመውን ወሲባዊ ጥቃት አሳሳቢ ነው ተባለ። በ17 ዓመቷ ታዳጊ ሐና ላላንጎ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈጽሞባት ህይወቷ ካለፈ በኋላ ድርጊቱ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል።

Image

ሠማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች የአንድነት መድረክ በመፍጠር ሰላማዊ ሰልፍ ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ/ም ለማድረግ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልፀው የሐገሪቱ ህዝብ በቦታው በመገኘት ድምፁን እንዲያሠማ ባሳወቁት መሠረት የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሠማ ጊዜያዊ ኮሚቴ እና የማህበሩ አባላት በሠላማዊ ሠልፉ ላይ ከሌላው የሐገራችን ህዝብ ጋር በመሆን ድምፃችንን እንደምናሠማ እየገለፅን ለሠላማዊ ሠልፉ መሣካት የበኩላችንን ደርሻም ለመወጣት ዝግጁ መሆናችንን ስንገልጽ በዚህ በጨለማ ዘመን ኃላፊነት ወስደው ይህንን ታላቅ ሠለማዊ ሠልፍ ላዘጋጁት የሠለማዊ ሠልፉ አዘጋጆች ምስጋናችንን በማቅረብ ነው፡፡
እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያን እያስተዳደሩ ሳይሆን እየገዙ ያሉት ብዙሀኑ ባለስልጣናት ከትምህርት አለም እርቀው ወደ ትግል የገቡ እና አሁንም ቢሆን በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እና የተሻለ ንቃተ ህሊና ያለው ሰው እንዳይፈጠር ትግል ላይ ናቸው በተለይ ለመምህራንና ባጠቃላይ ለትምህርት ስርአቱ ያላቸው ጥላቻ ላቅ ያለ ነው ይህንን እንኳን ስላልተማሩ ነው ብለን እንዳናልፈው የስርአቱ አመራሮች እና አጃቢዎች አለማወቃቸውንም ሊደብቁ ፍቃደኛ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ሟቹ መለስ ዜናዊ በህይወት ያለው ተፈራ ዋልዋ መምህራኑን ለማሰደብ አፋቸውን ከፍተው ባዶነታቸውን በነጻ ሲያስኮሞኩሙን ኖረዋል፡
እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ መምህር እንደሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ በወያኔ ጥርስ ውስጥ ከገቡት መካከል ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል፡፡ ገዢው የወያኔ ቡድን ጠንካራውን የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በማፍረስ ተለጣፊ ማህበር ከማቋቋም አልፎ ታላላቅ የማህበራችንን አመራሮች ከአሰፋ ማሩ ጀምሮ በመግደል በተለያዩ ጊዜያት ከኢትዮጵያዊው መምህር ሊነሱ የሚችሉ ተቃውሞችን ለማፈን ጥረት ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል በ2004 እንኳን የደመወዝ ጭማሪን ተከትሎ በተነሳው የመምህራን ጥያቄ መብታችን ይከበር ያሉ የማህበራችንን አባላት ከስራ ማባረር ጀምሮ ለእስር መዳረጉ የሚታወስ ሲሆን ይህም ሳያንስ በወቅቱ ከአንድ የሐገር መሪ ነኝ ከሚል ግለሠብ የማይጠበቅ ንግግር ከቀድሞው የሐገራችን አምባገነን ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ በሐገራችን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መስማታችን ይታወሳል ይህ በወያኔ አመራች ዘንድ ያለውን ከፍተኛ ንቀት እና ፍርሐት የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ውስጣዊ ፍርሀት የተነሳ በርካታ መስራት የሚችሉ እና ሀገሪቱን ሊቀይሩ ምሁራንን እንዲሰደዱ በማድረግ ያልተሰደዱትን ደግሞ በማሰር እና በማንገላታት የመምህርነትን ሙያን እንደማሰሪያ ብሎም አነስተኛ ደመወዝ በመክፈል የመምህራኑ አእምሮ በማጀት ወሬ እንዲጨናነቅ ማድረጉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡
ከሰሞኑም ይህንን ውስጣዊ ፍራቻውን ለካድሬዎቹ በመመሪያ መልክ በመስጠት በየት/ቤቱ የሚገኙ የገዢው ፓርቲ አባላት ያልሆኑ መምህራንን ስማቸውን ከተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በማያያዝ ማስፈራሪያ እና ዛቻ ሲያቀርብባቸው ሰንብቷል በተለይ የግንቦት ሰባት እና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ናቹህ በማለት በየእለቱ ዛቻ የሚደርስባቸው መምህራን ቁጥር እጅግ ከፍተኛ ነው በተለይ ከሰሞኑ የአባይ መዋጮ እንደአዲስ ለማስከፈል የሚደረገውን ጥረት ተከትሎ በተነሳው የመምህራን ጥያቄ በመምህራን ላይ የሚደርሰው መከራ እና ግፍ መጠኑ ጨምሯል፡፡
ስለሆነም የዚህ የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ለትምህርት ሚኒስቴር ጉዳዩን ቢያሳውቅም እልባት ሊያገኝ አልቻለም፡፡ የትምህርት ሚኒስቴሩም ለጉዳዩ እልባት ከመስጠት ይልቅ የአባዬን ወደእምዬ እንዲሉ በኮሚቴው አባላት ላይ ወቀሳ እና ማስፈራሪያ አቅርቧል ይኸውም ወትሮውም በትምህርት ሚኒስቴር ላይ አመኔታ ያልነበረውን ኮሚቴ ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ከሚታገሉ ሌሎች የሙያ ማህበራት እና ፓርቲዎች ጎን እንዲሠለፍ አድርጎታል በዚህም የተነሳ የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ኮሚቴ አባላት በሰልፉ ላይ እንደምንገኝ ቃል እየገባን ሌላው የሀገራችን መምህርም ከጎናችን በመሆን በሠላማዊ ሠልፉ ላይ ይገኝ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
የኢትዮጵያ መምህራን ድምጽ ይሠማ ጊዜያዊ ኮሚቴ
ህዳር 21/2007
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ማስታወሻ፡ ይህች ጽሁፍ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከተከሰሰባቸው ሁለት መጣጥፎች አንደኛዋ ናት። በመጭው ወር በአሶሳ የሚደረገውን የብሄር ቀን ድራማ እሳቤ በማድረግ – በርካታ አንባብያን በጠየቁት መሰረት እነሆ በድጋሚ ለንባብ አቅርበናል። – ክንፉ አሰፋ – “እኛ ጭቁን ብሄረሰቦች ከዚህ ቀደም በየሰው ቤት ተቀጥረን የምንሰራ፣ አሽከሮች እየተባልን ነበር የኖርነው። አሁን ግን ይኸውና ህገ-መንግስታችን መብታችንን ሰጥቶናል… ኑሯችንም ተሻሽሎ ዛሬ […]

በላይ ማናዬ

‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከፕሮ/ር አለማየሁ ገብረማርያም – ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

ለአራት አስርት ዓመታት እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው እና በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ከህዝብ ፍላጎት ውጭ በኃይል በስልጣን ወንበር ላይ ተፈናጥጦ የሚገኘው የወሮበላ የማፊያ ቡድን ኢትዮጵያን ለማጥፋት ቀጣይነት ያለው እና የማያቋርጥ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የባህል ጦርነት በመክፈት ዕቅድ አውጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢሕአዴግ አምባገነን መንግስት ነው::የአምባገነን መሰረቱ ደግሞ ፍርሃት ነው:: የህሊና እስረኛ የሆነው አንዷለም አራጌን ንግግር ያድምጡት::‪

Please wait, video is loading…

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የግብፅ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ ከተመሰረተባቸው ክስ በነፃ መሰናበታቸውን በመቃወም በመዲናይቱ ካይሮ ደም አፋሳሽ ግጭት መቀስቀሱ ተነገረ።ሙባረክን በነፃ ያሰናበተውን የግብፅ ፍርድ ቤት ለመቃወም ታህሪር አደባባይ በወጡ በሺህዎች የሚቆጠሩ ጸረ-ሙባረክ ሠልፈኞች እና ፖሊሶች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ቢያንስ ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል።

ይህ ፅሑፍ አብርሐ ደስታ በህወሀት ማፍያዎች ተይዞ እስር ቤት ከመግባቱ በፊት የፃፈው ነው፡፡ ስለትግራይ ህዝብ የተለያዩ ሠዎች የተለያዩ ፅሁፎችን ይፅፋሉ እንደዚህ እንደአብርሐ ደስታ ግን እስካሁን ሳነበው የሚመስጠኝ የለም
መልካም ንባብ

የትግራይ ህዝብ ከኢሕአዴግ መንግስት ምን ተጠቅሟል? የትግራይ ህዝብና መንግስት ምን አይነት ግንኙነት አላቸው? እነዚህንና ተያያዥ ጥያቄዎችን በተመለከተ አብርሃ በላይ ከመቀሌ አጥጋቢ መልስ ሰጥቷል:: አብርሃ እንደመነሻ ያደረገው ከአንድ የትግራይ ተወላጅ የቀረበለትን ጥያቄ ነው:: ጥያቄውም ይህ ነው:: “ኢህኣዴግን ትቃወማለህ፣ ግን ህዝብን ለለውጥ ኣነሳስተህ ከህወሓት የባሱ ፅንፈኛ የፖለቲካ ድርጅቶች ስልጣን ቢይዙስ ??? ስትቃወም ስለዉጤቱም ማሰብ ኣለብህ። በምትፅፋቸውን ነገሮች ለአዳንድ የትግራይ ጠላቶች መጋበርያ እየሆንክ ነው።”

መልስ
ሁሉም ዜጋ (የገዢው ፓርቲ ደጋፊም ተቃዋሚም) መጠየቅ ያለበት (የፖለቲካ ስርዓት ለውጥ ባህሪያዊ ሂደት መሆኑ ተገንዝቦ) በኢህኣዴግ እጅ ያለው ስልጣን (በለውጡ ሂደት) ‘ለማን ይሰጥ’ የሚለውን ነው። ሁለት ስልጣን ለመቀበል ያሰፈሰፉ ሃይሎች ኣሉ፤ (1) የኢትዮዽያ ህዝብና (2) ስልጣን በሃይል ለመያዝ የጓጉ የፖለቲካ ቡድኖች።
ኣንድ
እኔ ታድያ ‘ስልጣን ለኢትዮዽያ ህዝብ መሰጠት ኣለበት’ ከሚሉ ሰዎች ጎራ ነኝ (የምቃወምም ለዚህ ነው)። ምክንያቱም ስልጣን ለህዝብ ማስረከብ ዲሞክራሲን ማስፈን ነው። በዲሞክራሲያዊ መንግስት ህጋዊ ተቃዋሚዎች ይበረታታሉ፣ ኣማራጭ ፖሊሲያቸው ለህዝብ እንዲያቀርቡ ነፃ ሚድያ ይኖራል። ህዝቦች በነፃነት የፈለጉትን ፓርቲ ይመርጣሉ፤ ድምፃቸውም በገለልተኛ የምርጫ ቦርድና የፍትሕ ኣካላት መኖር ይከበራል። የህዝብ ድምፅ ከተከበረ ሲቪላዊ መንግስት የማቋቋም ዕድል ይኖራል። በዚ መንገድ በሃይል ስልጣን ለመያዝ የሚቋምጡ ሃይሎች ቦታ ኣያገኙም። ዓፈናው ከቀጠለ ግን ….
ዲሞክራሲ ማስፈን የብዙ ችግሮች መፍትሔ ይሆናል። የ’ኣፍርሶ መገንባት’ ስትራተጂ ዕዳ ይቀንሳል። ደም ማፋሰስ ያስወግዳል። ኧረ ሲንቱን …… ህወሓት/ኢህኣዴግ ኣሁን ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት ማድረግ የሚችለው ትልቁ ኣስተዋፅኦ ዲሞክራሲን በማስፈን ስልጣን ለህዝብ ማስረከብ ነው። የትግራይ ህዝብ ትግልም ለውጥ ኣመጣ እንላለን።
በኢትዮዽያ ታሪክ (እስከ ኣሁን ድረስ) ስልጣን የተያዘው በህዝብ ፍላጎትና ምርጫ ሳይሆን በጠመንጃ ኣፈሙዝ ነው። ፓርቲዎች ተጠናክረው ስልጣን መያዝ ከቻሉ ለመጀመርያ ግዜ ሰለማዊ የስልጣን ሽግግር ተግባራዊ ያደርጋሉ (የኢትዮዽያ የፖለቲካ ታሪክ ይቀይራሉ) ። ሰለማዊ ሽግግር ተደረገ ማለት ደግሞ ስልጣን ወደ ህዝብ ወረደ ማለት ነው። ህዝብ የስልጣን ባለቤት ከሆነ የመንግስት ኣካላት የሰው ጌቶች ሳይሆኑ የሰው ኣገልጋዮች ሆኑ ማለት ነው። በዚህ መልኩ የህዝቦች ነፃነት ተከበረ ማለት ነው፤ ቀጥሎም እኩልነት፣ ኣንድነት፣ መከባበር ይኖራሉ። እኛም ተዋደድን። ስለዚ ፓርቲዎች ሊከበሩ ይገባል።
ህወሓቶች የስልጣን ዕድሜ ማራዘም መፍትሔ እንዳልሆነ መገንዘብ ኣለባቸው። የተለያዩ ምክንያቶችን በማቅረብ ድጋፍ ማሰባሰብ ዘለቄታ ያለው የህዝብ ደህንነት ዋስትና ሊሆን ኣይችልም። የህዝብ ዋስትና ዲሞክራሲያዊ (ጠንካራ፣ ነፃና ገለልተኛ) ተቋማት ናቸው። መሪዎች ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ፤ ሲሄዱና ሲመጡ እንደ ድልድይ ሁኖው በማገልገል ለህዝብ ደህንነት ዋስትና (ወይ ጋሻ) የሚሆኑ እነዚህ የፍትሕ ተቋማት ናቸው።
ሁለት
ህወሓት /ኢህኣዴግ የያዘውን ስልጣን በፍቃደኝነት (በምርጫ) ለህዝብ ካላስረከበ በሃይል እስኪወርድ ድረስ በስልጣን ይቆያል ማለት ነው። ይህንን የሚያሳየን ህወሓት ስልጣኑን ለሌላ ታጣቂ (ተዋጊ) ሃይል እንጂ ለህዝብ ለመስጠት ፍላጎት የለዉም ማለት ነው።
ሌላ የታጠቀ ሃይል ስልጣን ከያዘ ሌላ ህወሓት /ኢህኣዴግ መጣ ማለት ይሆናል። ምክንያቱም ስልጣን በሃይል ለመያዝ ሰው መግደልን ጨምሮ ሌሎች የተወሰኑ ወንጀሎች ይሰራሉ፣ ግድያ ይኖራል። (ሃይል ስንጠቀም ወንጀሎችም ይኖራሉ ኣለበለዚያ ግን ለውጡ የመጣው በሃይል ሳይሆን በሰለማዊ መንገድ ነው ማለት ነው)። እነዚህ የተወሰኑ ወንጀሎች ለመሸፈን ሲባል ሌሎች ተጨማሪ ወንጀሎች ይፈፀማሉ። እነዚህ ወንጀሎች እንዳይጋለጡ ለማድረግ (ጉዳቸውን እንዳይወጣ) ስልጣን የያዘውን የፖለቲካ ቡድን የራሱ ዳኞች፣ ወታደራዊ መኮነኖች፣ የደህንነት ሃላፊዎች ወዘተ ይኖሩታል።
ከተሸናፊው የፖለቲካ ድርጅት ‘ደህንነታዊ ስጋት’ በመስጋትም የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በጠላትነት ይፈርጃል። እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎችም ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ ሌላ የኣደረጃጀት ኣማራጭና የፖለቲካ ስልት ያፈላልጋሉ። የሃገር ኣንድነትም ኣደጋ ላይ ይወድቃል።
ስልጣን ላይ የወጣ ሃይል ድክመቱን ለመሸፈን ሲል የሚጠራጠራቸውን ህዝቦች ለመቆጣጠር (የመገንጠል ጥያቄን በሃይል ለመመለስ) እንዲችል ኣሻንጉሊት ድርጅቶችን ያቋቁማል። ይህንን ሁኔታ ሌላ ኢህኣዴግ ያደርገዋል። እኛ ደግሞ “ኣዲስ ንጉስ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ …” እንዘፍናለን።
ሦስት
በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ መንግስት ህዝቦችን የመጨቆን ዕድሉ ይቀንሳል። ምክንያቱም ፖለቲከኞቹ ከወንጀል ነፃ የመሆን ዕድል ኣላቸው። (ከወንጀል ነፃ ካልሆኑ ኣይመረጡማ) ወይም ከስልጣናቸው ለማውረድ ቀላል ይሆናል። እነሱም ከስልጣን መውረድን የሞትን ያህል ኣይፈሩም (በህዝብ የተመረጡ ናቸዋ)። ስልጣን ላለመልቀቅ ኣያንገራግሩም (ህዝቡ ሰልፍ ይወጣላ)። መሪዎቹ ሰልፍ ለወጣ ህዝብ እንዲገድሉ ወታደሮቻቸውን ኣያዙም። ምክንያቱም በፖለቲከኞችና ወታደሮች መሃከል (ህገ መንግስታዊ ከሆነ በቀር) ልዩ ግንኙት ወይ ትስስር ኣይኖራቸውም።
በህዝብ የተመረጡ መሪዎች ተጠያቂነታቸው ለመረጣቸው ህዝብ ይሆናል (የስልጣን ምንጫቸው ህዝብ ነውና)። ስልጣን የያዙት በሃይል ከሆነ ግን ተጠያቂነታቸው ለጠመንጃቸው ነው። የህዝብ ጉዳይ ኣያሳስባቸውም። ስለ ካድሬዎቻቸው እንጂ ስለ ህዝቡ ችግር ላይጨነቁ ይችላሉ።
ኣራት
ኢህኣዴግን መቃወም ለምን???
(1) ገዢው ፓርቲ ስልጣን ወደ ህዝብ እንዲመልስ ለማገዝ ያስችላል። ኢህኣዴግ የህዝብን ድምፅ ኣላከበረም፣ ህዝብ እየገዛ እንጂ እያስተዳደረ ኣይደለም ያለው። ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት እንፈልጋለን። የሁሉም ህዝቦች ደህንነትና ልማት የሚረጋገጠው ዲሞክራሲያዊ ነፃነት ሲፈቀድ ነውና።
(2) ኢህኣዴግ ችግሮቹን እንዲያርም ለማድረግ ነው። የመናገር መብት ያፍናል፤ ህወሓት በትግራይ ህዝብ ስም ሌሎች ህዝቦች ይጨቁናል፤ ለራሱ ጥቅም ሲባል ኣሻንጉሊት ድርጅቶች በማቋቋም የሚገዙትን ህዝብ የማይወክሉ መሪዎች በኣስገዳጅነት እንዲገዙ ያደርጋል። እነዚህ ህዝቦች ራሳቸው ይወክሉናል ብለው በመረጡዋቸው ድርጅቶች መተዳደር ኣለባቸው። ህዝቦች በሚወክሉዋቸው መሪዎች ሲተዳደሩ የትግራይ ህዝብ ቢጠቀም ‘ጂ ኣይጎዳም።
(3) ለውጥ ፈልገን ነው። ለውጥ የመፈለግ ኣባዜ የተፈጥሮ ጥሪ ነው። እያንዳንዱን ትውልድ የራሱ /ለራሱ የሆነ ለውጥ የማምጣት ወይም የማድረግ የግል የቤት ስራ ኣለው። የኣባቶቻችን ታሪክ ለኛ (የኛ) ሊሆን ኣይችልም። ስለዚ ለውጥ መፈለግ በራሱ ስሕተት ኣይደለም። ለለውጥ መነሳት የህይወት ግዴታችን ነው።
ኣምስት
የትግራይ ስጋት የሚመነጨው ከነዚህ ዲያስፖራ ፖለቲከኞች ከሚያራምዱት ኣስተሳሰብ እንደሆነ ተነግሮኛል። እነዚህ የ ‘ትግራይ ጠላቶች’ እንደሆኑ ተደርገው የሚታሰቡ ሃይሎች መነሻቸው ምንድነው ? ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው።
እነዚህ ሰዎች በኢህኣዴግ መንግስት በጠላትነት ተፈርጀው ‘ኣሸባሪ’ ተሰይመው ከሃገራቸው የተባረሩ ናቸው። ከሃገራቸው ከተባረሩ ታድያ እንዴት ለህወሓት ጥሩ ኣመለካከት ሊኖራቸው ይችላል? በህወሓት ዘመነ መንግስት ወደ ሃገራቸው እንዲገቡ ካልተፈቀደላቸው ሃገራቸውን ለመግባት ህወሓትን በሃይል ማስወገድ ግድ ሊላቸው ነው። ስለዚ ጥረታችው ኣይደንቀኝም።
ጥያቄው እነዚህ ሰዎች ለምን የትግራይን ህዝብ target ያረጋሉ የሚል ነው። መልሱ ግን ቀላል ነው። (1) ህወሓት ራሱ … ህወሓትና የትግራይ ህዝብ ኣንድ እንደሆኑ ኣድርጎ ይሰብካል (ድጋፍ ለመሰብሰብ)።
(2) የዲያስፖራው የፖለቲካ ስትራተጂ ተደርጎ ይወሰዳል። የትግራይን ህዝብ target ሲያደርጉ የትግራይን ህዝብ ፈርቶ ህወሓትን ከመደገፍ ይቆጠባል ከሚል ኣስተሳሰብና ከትግራይ ህዝብ ውጭ ያለው ኢትዮዼያዊ ‘በኣንድነት በመቆም’ ህወሓትን ከስልጣን ለማውረድ እንዲነሳ ታስቦ ነው።
(3) ተሳዳቢዎቹ ዲያስፖራ ኣራት ዓይነት ናቸው።
(ሀ) የፖለቲካ ብቃት የሚያንሳቸው (ህዝብና ገዢው ፓርቲ መለያየት ያቃታቸው ወይም መለያየት ያልፈለጉ)። እነዚህ በቀጥታም በተዘዋዋሪም ህወሓትን ያግዛሉ። የትግራይን ህዝብ ሲሳደቡ , የትግራይ ተወላጆችም ሳይፈልጉ ከህወሓት ጎን እንዲሰለፉ ይገደዳሉ። ግን ስጋት ሊሆኑ ኣይችሉም ስልጣን ኣይዙምና (በሃይል ካልሆነ በቀር)፤ የፖለቲካ ዕውቀት ፤ስለሚያንሳቸው ።
(ለ) ወደ ሃገራቸው እንዳይገቡ የተከለከሉ (በሰለማዊ መንገድ እንዲታገሉ በህወሓት ያልተፈቀደላቸው)። እዚ ላይ ስጋት ፈጣሪው ህወሓት ራሱ ነው።
(ሐ) በሻቢያ ተልከው ኢትዮዽያን ለመበጥበጥ ተከፍሎቸው የሚሰሩ (ኣብዛኞቹ ኤርትራውያን ናቸው)። ኢትዮዽያውያን ካልተባበርናቸው የትም ኣይደርሱም።
(መ) ከህወሓቶች ጋ ግንኙነት ያላቸው …. ይህንን ስትራተጂ ‘ዲያስፖራ ፖለቲከኞች ጥላቻ የሚሰብኩ ናቸው’ ተብለው እንዲፈረጁና የትግራይ ህዝብ እነሱን ፈርቶ ና ሰግቶ ከህወሓት ጎን እንዲሰለፍ ለማድረግ የታለመ ነው።
ስለዚህ ጥላቻን የሚሰብኩ ኣንዳንድ ፖለቲከኞች ሃገራቸውን እንዲገቡ ተፈቅዶላቸው በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ህዝባቸውን ለለውጥ እንዲያነሳሱ ቢደረግ የትግራይ ህዝብ የሚያዋሩዱበት ምክንያት ባልኖራቸው ነበር። ስለዚ የትግራይ ስጋት ሆን ተብሎ በህወሓት የተቀናበረ ነው።
ስድስት
ስጋቱ ቢኖርስ??? መፍትሔው በህወሓት እጅ ነው። ሥጋቱን ለመቀነስ ራሳችን የሌሎች ህዝቦች ስጋት ፈጣሪ መሆን የለብንም። እንደ ኣሰራርም :
(1) ህወሓት በትግራይ ህዝብ ስም ሌሎች ህዝቦች መጨቆን እንዲሁም ስጋት መፍጠር የለበትም። (ካልጨቆነ ስጋቱ ኣይኖርም)። ከዚህ ኣልፎም የትግራይ ህዝብ ከሌሎች የኢትዮዽያ ህዝቦች በሰላም መኖር የሚፈልግ እንጂ የህወሓት የጥላቻ ፖለቲካ እንደማይደግፍ በግልፅ መናገር ኣለበት። ይህ ካልሆነ ደግሞ መፍትሔው መደራጀት እንጂ ስልጣን የሙጥኝ ይዞ ህዝቦችን መጨቆን ኣይደለም።
(2) ህወሓት ዲሞክራሲን ማስፈን ሲገባው የታጠቁ ሃይሎችን ወደ ስልጣን መጋበዝ የለበትም። ህወሓት ህጋዊና ሰላማዊ የተቃውሞ ድርጅቶችን ሲያዳክምና ሲያፈርስ ስልታቸውን ቀይሮው የሃይል መንገድ ተከትለው ከስልጣን እንዲያወርዱት እየጋበዛቸው ነው። ይህ ኣካሄድ ደግሞ ህወሓት በሌሎች ህዝቦች እንዳደረገው ሁሉ ኣሻንጉሊት ድርጅት መስርተው የትግራይን ህዝብ ለመጨቆን ያስችላቸዋል።
ሰባት
“ለአዳንድ የትግራይ ጠላቶች መጋበርያ እየሆንክ ነው” የሚል ነገር ኣለ። የትግራይ ጠላት ማነው? እንደኔ እምነት: የትግራይ ህዝብ ጠላት ጭቆና ነው። ጠላቶቹ ጨቋኞቹ ናቸው። ድሮ ደርግ ነበር ጨቋኝ፣ ኣሁን ደግሞ ህወሓት። ስለዚህ የትግራይ ጠላቶች ጨቋኝ ገዢዎቹ እንጂ ሌሎች ብሄሮች ወይ ሌላ ሃይማኖት ተከታዮች ኣይደሉም።
ተጋሩ (የትግራይ ተወላጆች) የራሳቸው የፖለቲካ ኣቋም ይዘው ገዢውን መደብ ሲቃወሙ ‘ከጠላቶቻችን ኣብረዋል’ ወይ ‘ለጠላቶቻችን ያጋሉጥናል’ በሚል ሴራ በመንግስት ደጋፊዎች ይወቀሳሉ፣ ይገለላሉ። ግን እንዲህ ከተነቀፉኮ የትግራይ ተወላጆች የመቃወም መብት የላቸውም ማለት ነው። (ወይም እንዲቃወሙ ኣይፈቀድላቸውም ማለት ነው?)
በዚህ መልኩ (ተጋሩ የመቃወም መብታቸውን ከተገደበ) ‘ከትግራይ ወጥቼ ለትግራይ እቆማለሁ’ የሚል የህወሓት ድርጅት ፀረ ተጋሩ እየሆነ ነው ማለት ነው። ህወሓት ለትግራይ ቢቆም ኑሮ እኛ ተጋሩ የፈለግነውን የፖለቲካ ኣመለካከት እንድነራመድ ለምን ኣይፈቅድልንም? ደርግ ኣፈነን። ህወሓትም እንዲህ ካፈነን፣ ህወሓት ከደርግ (ለትግራይ ህዝብ) በምን ይሻላል? በምንስ ይለያል???
ህወሓት የመናገር መብታችን ካላከበረ፣ ሁሉም የትግራይ ሰው በእኩል ዓይን ካልታየ፣ በተግባሩና በስራ ኣፈፃፀሙ መመዘን ሲገባው በጎጠኝነት በስራው ግልፅ የሆነ ኣድልዎ ከተፈፀመበት፡ ከዚህ በላይ የህዝብ ጠላትነት ከየት ሊመጣ ነው? የትግራይ ህዝብ እንደማንኛውም ሌላ ህዝብ በነፃነት ሓሳቡ የመግለፅ መብት ኣለው፤ ሊከበርለትም ይገባል።
ህይወቱ ሙሉ ከጭቆና ነፃ ለመውጣት ሲታገል የኖረ ህዝብ የእኩልነት መብቱ ሲነፈግ እኛ ዝም ብለን ሳንቃወም ማየት ነበረብን? ብዙ መስዋእት የተከፈለበት የ17 ዓመት የትጥቅ ትግል በተወሰኑ ሰዎች ተጠልፎ ለግል ስልጣንና ጥቅም ሲውል እኛ ዝም ብለን ተመልካች እንድንሆን ነው የሚጠበቀው? ወይስ የራሳችን ሚና መጫወት ይኖርብናል!?
ስምንት
የኢህኣዴግ መንግስትን የተቃወመ ሰው ወይ የፖለቲካ ድርጅት የትግራይ ህዝብ ጠላት እንደሆነ ኣድርገው በማቅረብ የትግራይን ህዝብ ለማጭበርበር የሚሞክሩ የመንግስት ኣካላት እንዳሉም ይታወቃል። ግን ህወሓትን መጥላት የትግራይ ህዝብን መጥላት ኣያሰኝም። ህወሓትን መቃወም የትግራይ ህዝብን መቃወም ማለት ኣይደለም። ምክንያቶች
(1) ህወሓት (ገዢው መደብ)ና የትግራይ ህዝብ (ተገዢው ህዝብ) አንድ አይደሉም፤ ሊሆኑም ኣይችሉም። ፓርቲና ህዝብ አንድ ተደርጎ የሚወሰደው ለፕሮፓጋንዳ (የህዝብ ግንኙነት) ሥራ ነው። የትግራይ ህዝብ ከህወሓት በፊት ነበር፤ ከህወሓት በኋላም ይኖራል።
(2) ተቃዋሚን በጠላትነት ማየት የፖለቲካዊ ኣስተሳሰብ ችግር ውጤት ነው። መቃወም ተፎካካሪ (ኣማራጭ ሃይል) መሆን እንጂ ጠላትነት ኣይደለም። ዴሞክራሲ ኣሰፍናለሁ የሚል መንግስት ተቃዋሚዎችን በጠላትነት መፈረጅ ተገቢ ኣይደለም።
(3) ሰዎች ወይ ድርጅቶች ህወሓትን (እንደገዢ ፓርቲ) የመቃወም ተፈጥሮኣዊ መብት ኣላቸው። የትግራይ ህዝብ ህወሓትን ከፈለገ (በፍላጎቱ ) ይምረጠውና ትግራይን ያስተዳድር (መብቱ ነው)። ህወሓት ላልመረጠው ህዝብ ኣሻንጉሊቶችን በመፈብረክ ሌሎች ህዝቦችን በእጃዙር የመግዛት መብት ግን የለውም።
ህወሓት ለኢትዮዽያ ህዝቦች መሪዎች የመምረጥ መብት ማን ሰጠው? ራሳቸው እንዲመርጡ ለምን ኣይፈቀድላቸውም? ስለዚ ህወሓትን ለመቃወም በቂ ምክንያት ኣላቸው። ይህን ሁኔታ በመቃወማቸው ‘የትግራይ ህዝብ ጠላቶች’ ሊያሰኛቸው ኣይችልም። የኢትዮዽያ ህዝቦች የራሳቸውን ተወካዮች በነፃነት የመምረጥ ሙሉ መብት ኣላቸውና።
(4) ህወሓት ለትግራይ ህዝብ የቆመ ድርጅት ከሆነ ለምን እንድንደራጅ ኣይፈቅድልንም? መደራጀትኮ ሃይል ይፈጥራል። ለምንድነው ተደራጅተን ሃይል እንዳንፈጥር የሚያደርገን? ከዚህ በላይ ጠላትነት ኣለ እንዴ? ስለዚ ‘የትግራይ ህዝብ ጠላት ህወሓት ነው’ ማለት እችላለሁ።
(5) የትግራይ ህዝብ (ባይሳካም) አንድ ኣስተሳሰብ እንዲኖረው ጥረት ማድረግ ትውልድን መግደል ነው። ብዙ ሰዎች አንድ ዓይነት ኣስተሳሰብ እንዲይዙ ለማድረግ የብዙዎቹ ኣስተሳሰብ መግደል ግድ ይላል። ኣስተሳሰብ ታፈነ፣ ተገደለ ማለት ደግሞ ትውልድን ተገደለ ማለት ነው። ምክንያቱም የለውጥ ምንጭ ኣስተሳሰብ ነው።
(6) ደሞ የትግራይ ህዝብ ከህወሓት አገዛዝ ነፃ መውጣት ኣይፈልግም ያለ ማነው? በትግራይ ሁሉም ቢሮዎች (ከላይ እስከ ታች) በተወሰኑ ሰዎችና ቤተሰቦቻቸው ቁጥጥር ስር ነው። ማነው ትግራይ የነሱ ብቻ ናት ያለው? ትግራይኮ የሁላችን ናት? ወይስ የነሱ ባሮች (Slaves) ሁነን ለማገልገል ቆርጠን ተነስተናል?
ማንም ሰው የመደገፍም የመቃወምም ተፈጥሮኣዊ መብት ኣለው። የመቃወም መብት የህወሓት የግል ስጦታ ኣይደለም። ህወሓት ሲፈልግ የሚሰጠን ሲፈልግ ደግሞ የሚከለክለን የግል ሃብቱ መሆን የለበትም።
ዘጠኝ
የስርዓቱ ተጠቃሚዎች (በቤተሰባዊ ሙስና) ገዢውን ፓርቲ በሚቃወሙ ግለሰዎች ላይ ስም የማጥፋት ዘመቻ ከማካሄድ ኣይቦዝኑም። “የስርዓቱ ተጠቃሚዎች” ያልኩበት ምክንያት፡ ሕገ ወጥና ተቀባይነት የሌለው መንገድ በፈጠረው ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥገኝነታቸው በራስ የመተማመን ስሜታቸው ካላሽመደመደው በቀር ሃሳባቸውን በነፃነት በሚፅፉ ሰዎች ስም የማጥፋት ዘመቻ ማድረግ ኣስፈላጊነቱ ኣይታየኝም ከሚል እሳቤ በመነሳት ነው።
ህወሓቶች ለሚቃወማቸው ሰው ኣንድም ያስራሉ (ያዋክባሉ) ኣልያም ስም በማጥፋት ተግባር ይሰማራሉ። ለምን ስም ያጠፋሉ???
(1) በሙስና የበሰበሰ ስርዓት ተቃውሞ የሞትን ያህል ይፈራል። ምክንያቱም የግለ ሰዎች የተቃውሞ ፅሑፎች ድጋፍ ሊያሳጡት ይችላሉ። ድጋፍ ካጣ ስልጣን ሊለቅ ይችላል፤ ስልጣን ከለቀቀ የሰራውን ጥፋት ይጋለጣል።
(2) ጥቅሙ እንዲጎድልበት ኣይፈልግም (የእህል-ውሃ ጉዳይ ነው)። (“ኣብ ፃሕልና ኢድኩም ኣይትሕወሱ፤ ንሕና ክንበልዕ ንስኹም ጠጠው ኢልኩም ረኣዩ” ዝዓይነቱ።) ኣጥንት የያዘ ውሻ …… ይሆናል።
ህወሓት ተቃውሞ ሲያይልበት (ሁሉም ነገር ለብቻው ጠቅልሎ በመያዙ) ” እኔ ብቻ ኣይደለሁም የበላሁት፡ የትግራይ ህዝብም ኣብሮኝ በልቷል፤ ስለዚ እኔ ብቻ ተጠያቂ ኣልሁን፣ ከትግራይ ህዝብ ኣትነጥሉኝ” የሚል መልእክት ያለው ተግባር እያከናወነ ይገኛል።
የትግራይ ህዝብ ባልዋለበት (‘የማዩ የሰማዩ’) ሊያስወነጅለው እየሞከረ ነው (‘ጅብ ይበለሃል’ ከሚል ማስፈራርያ በተጨማሪ መሆኑ ነው)።
እኔ ግን እላለሁ፡ የህወሓት ሰዎች ባጠፉት ጥፋት የትግራይ ህዝብ ተጠያቂ ሊሆን ኣይገባም። እውነታውን መካድ የችግሩ መፍትሔ ኣይሆንም።
አስር
ሓሳብ በመግለፅ ብቻ ኣንድን ብሄር ወይ ፓርቲ ከስልጣን ለማውረድ ወይ ለማውጣት ኣይቻልም ። ሓሳባችን በነፃነት በመግለፃችን ከህወሓት ‘የባሱ’ ሃይሎች ስልጣን እንድይዙ ኣያስችልም ። እነዚህ ‘የትግራይ ጠላቶች ’ እየተባሉ የሚፈረጁ ግለሰዎች ተሳክቶላቸው ስልጣን ብይዙ እንኳ የራሳችውን ህዝብ ነው የሚያስተዳድሩ። ትግራይን የሚያስተዳዱርበት መንገድ የለም (እነሱም ትግራይን የማስተዳደር ስራ ‘ለኛ ይሰጠን’ ኣላሉም)። በህወሓት የሚሰጠን “እኔ ከሌለሁ ጅብ ይበላችኋል” ዓይነቱ ማስፈራርያ ግን ለትግራይ ህዝብ ያለው ንቀት የሚያሳይ ነው። ትግራይ የህወሓት ባለስልጣናት ብቻ ወልዳ የቀረች መኻን ኣይደለችም።
It is so!!!
ኣብርሃ ደስታ
Image

Image

– ክፍተኛ አነስተኛ እና ጥቃቅን በሚል ተከፍለው እየተሰለሉ ስልካቸው እየተጠለፈ መሆኑ ታውቋል::
– የሕወሓት ስጋት ውስጥ ውስጡን ክሻእቢያ ጋር ግንኙነቱን እንዲያጠናክር አድርጎታል::
– የኢትዮጵያ ሕዝብ ውስኝ የለውጥ ወቅት ላይ መሆኑን አውቆ አደባባይ በመውጣትወያኔን ሊያስወግድ ይገባል::
Minilik Salsawi
ከፊታችን አደጋ አለ በሚል ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የገቡት እና በመፍትሄፍለጋ ስብሰባዎች የተወጠሩት የሕወሃት ሰዎች ክከፍተኛ ባለስልጣናት ጀምሮ እንከ በታች ሹሞች ድረስ በብአዴንና በኦህዴድ ባለስልጣናት ላይ ክፍተኛ የማስፈራራት እና የማዋከብ ሽብር እየፈጸሙ መሆኑን አንድ ከፍተኛ የኢሚግሬሽን እና ደህንነት ባለስልጣን ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል::

በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ የሚገኙ የብአዴን እና የኦሕዴድ አባላት በግል እንዳይገናኙ እንዲሁም ከመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች ጋር እንዳይገናኙ ከፍተኛ የሆነ ክትትል እየተደረገባቸው ሲሆን በባለስልጣናት ደረጃ እያንዳንዱ እንቅስቃሴ የሚያጠና የደህንነት ቡድን የተመደበባቸው ሲሆን ስልኮቻቸውም እየተጠለፉ መሆኑን እኚሁ ባለስልጣን ተናግረዋል::

የብአዴንና የኦሕዴድ ሰዎችን ከፍተኛ አነስተኛ እና ጥቃቅን በሚል ተከፍለው በሕወሓት እየተሰለሉ ስልካቸው እየተጠለፈ ሲሆን እንደ በግ የሚታዘዝላቸው የደቡብ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ውስጥ ዘልቀው እንዳይገቡ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑ ታውቋል::ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የሆኑ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ከፍተኛ ባለስልጣናት መቀራረብ እና አብሮ መዋል የሕወሓት ሰዎችን ማሳሰቡን እና የደህንነት ክትትል እያደረጉባቸው እንደነበረና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከደመቀ መኮንን እና ከሙክታር ከድር ጀምሮ እስከ በታች የፌዴራል ባለስልጣኖች ላይ ከፍተኛ ስለላ እየተካሄደ ምንጮች መረጃ ሰተው እንደነበር ሲታወቅ ይህ በአሁኑ ወቅት በእጥፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ታውቋል::

ሁኔታዎች መልካም አይደሉም ከፊታችን አደጋ ተደቅኗል::ለውጥ ያስፈልጋል::የሚሉ የተቆጡ ድምጾች በስፋት በኢሕኣዴግ አባላት እየተሰሙ ያለበት አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው ሕወሓት በግል እና በጋራ ባለስልጣናቱ ላይ ከፍተኛ ማስፈራራት እና ዛቻ እያደረገባቸው መሆኑን የተናገሩት ምንጮቹ ኢሕአዴግን ለመናድ ብትሞክሩ ሃገሪቷ ትበታተናለች::እንደ ሱማሊያ መንግስት አልባ ሆና እንደ ሩዋንዳ ትበጠበጣለች እያሉ ከማስፈራራትም አልፎ በግል የተነከራችሁበት ሙስና አደባባይ እናወጣዋለን:: እኛን ማንም ሊጠይቀን አይችልም ቁልፉ እኛ ጋር ነው የሚሉ በኣደገኛ መርዞች የተሞሉ ማስፈራሪያዎች መሰንዘር ክጀመሩ እንደቆዩ ተገልጿል::

የኢትዮጵያን ህዝብ እንደ ሶማሌ እና ሩዋንዳ ማስብ ጅልነት ነው::የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ እንጂ ፍጅት ስለማይፈልግ ኢሕ አዴግ ሲፈርስ ሕወሓት እንደሚያስበው ሳይሆን ትልቅ ሰላም በሃገሪቱ ላይ ይሰፍናል ያሉት ምንጩ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ባለስልጣናት የየቀን ሪፖርት እና ግንኙነት በተመለከተ ማን ከማን ጋር እንደዋለ ማን እነማን ቤት እንደሄደ በመከታተል እየቀረበ ሲሆን የሃገሪቱን የደህንነት ቢሮ በጋራ የሚመሩት ጸጋዬ:ጌታቸውና ደብረጺሆን በየቀኑ ለትግሪኛ ተናጋሪ ደህንነቶች በአጫጭር ስብሰባዎች መመሪያ እያወረዱ ከመሆኑም በላይ አደጋ ውስጥ መሆናቸውን እየደጋገሙ እንደሚናገሩ ምንጮቹ አክለዋል::

በአሁን ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ ወሳኝ የትግል ወቅት ላይ መሆኑን በማወቅ የበሰበሰውን የወያኔ አምባገነን ስርአት ለመጣል በጋራ አደባባይ በመውጣት የሚያካሂደውን አብዮት የመከላከያ ሰራዊት የፖሊሱ እና የብአዴን እንዲሁም የኦሕዴድ ፓርቲ ለውጡን እንደሚደግፉት የህዝቡን መነሳሳት እየጠበቁ መሆኑን እና ሕወሓት ከመስጋቱ የመጣ ከሻእቢያ ጋር በውስጥ ግንኙነቱን አጠናክሮ መቀጠሉን እንዲሁም ለተመረጡ የኤርትራ ስደተኞች የደህንነት ትምህርት የተሰጠ እንደሚገኝ እኚሁ ባለስልጣን መረጃ አድርሰውኛል::‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

ህዳር 27 እና 28 ሰማያዊ ፓርቲ ከትብብሩ ጋር በመሆን ለነፃነት አደባባይ እንወጣለን፤ የማስተባበሩ ዝግጅት ቀጥሏል – በትግላችን ሰብዓዊ መብቶቻችንን እናስመልሳለን! ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር! ህዳር 20 2007

Image

Image

Image

Image

Image

Image

Image


ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
===ለመግቢያ ያህል====
    “የትግል ስም” ቃሉ እንደሚያመለክተው በትግል ዓለም ውስጥ ላለ ሰው ነው የሚያገለግለው፡፡ ታጋዩ በትግል ዓለም ውስጥ እያለ የሚጠቀምበት መጠሪያው ነው፡፡ ታጋዮች የትግል ስምን የሚጠቀሙት በልዩ ልዩ ምክንያቶች ነው፡፡ ዋነኛው ምክንያት ግን ታጋዩ በእውነተኛ ስም ሲጠቀም ሊደርስበት ከሚችል አደጋ ለመከላከል የሚል ነው፡፡
     
የትግል ስም እንደ ብዕር ስም በሚስጢራዊነት አይያዝም፤ ሰውዬው ድሮ የሚታወቅበትን ስም ተክቶ በስራ ላይ የሚውል ነው፡፡ ታጋዩ ወደ ትግል ዓለም ከገባ በኋላ የሚያገኛቸው የትግል ጓዶች በትግል ስሙ ነው የሚጠሩት፡፡ በመታወቂያም ሆነ በሌሎች ሰነዶች ጥቅም ላይ የሚውለውም የትግል ስም ነው፡፡ በተጨማሪም ታጋዩ ትግሉን በድል ካጠናቀቀ በኋላም በአብዛኛው በትግል ስሙ መገልገሉን ሲቀጥልበት ይታያል፡፡
   የትግል ስምን ለመጀመሪያ ጊዜ በጥቅም ላይ ያለው ማን እንደሆነ አይታወቅም፡፡ ሆኖም የሩሲያ ኮሚኒስቶች በትግል ስም በብዛት በመጠቀም ቀዳሚዎች ናቸው፡፡ ለምሳሌ እንደ ቭላድሚር ሌኒን፣ ጆሴፍ ስታሊን፣ ሊኦን ትሮትስኪ፣ ሉሊ ማርቶቭ ያሉ ስሞች በሙሉ የትግል ስሞች ናቸው፡፡ በሌሎች ሀገሮች የነበሩ ኮሚኒስቶችም በትግል ስም በብዛት ይጠቀሙ ነበር፡፡ ሆ ቺ ሚን፣ ኪም ኢል ሱንግ፣ ቼ ጉቬራ የመሳሰሉ መጠሪያዎች የትግል ስሞች ናቸው (የቼ ጉቬራ ትክክለኛ ስም “ኧርነስቶ ጉቬራ” ነው፤ የኪም ኢል ሱንግ ትክክለኛ ስም “ኪም ሱንግ ቹ” ነው)፡፡
====የትግል ስም በኢትዮጵያ===
   የትግል ስምን ለመጀመሪያ ጊዜ በስራ ላይ ያዋለው ኢትዮጵያዊ ማን እንደሆነ በትክክል አይታወቅም፡፡ ሆኖም ከተማሪዎች ንቅናቄ የፈለቁት ወጣቶች የፋኖነት ህይወት በጀመሩበት ዘመን በብዛት ስራ ላይ እንደዋሉት ይታወቃል፡፡ ታዲያ እነዚያ ፋኖዎች የትግል ስምን የሚጠቀሙበት ምክንያትና ስሙን በስራ ላይ የሚያውሉበት ዘይቤ አንድ ወጥ አልነበረም፡፡ በህቡዕ እና በትጥቅ ትግል መንግሥትን ለመለወጥ የሚታገሉ ድርጅቶች ከተመሰረቱ በኋላ በጣም ጎልብቶ የመጣው የትግል ስም አጠቃቀም ልማድም እንደ ፓርቲው ይለያያል፡፡ ከዚህ በማስከተልም በቀደምት ድርጅቶች ውስጥ ይሰራበት የነበረውን ልማድ በአጭሩ እናወሳለን፡፡
1.      ጀብሃ እና ሻዕቢያ
ጀብሃ እና ሻዕቢያ የትግል ስምን የመጠቀም ባህል የነበራቸው መሆኑ አልተመዘገበም (ወይም አላነበብኩም)፡፡ ሆኖም ሁለቱም ፓርቲዎች የሚስጢር ስም የመጠቀም ባህል የነበራቸው መሆኑ በስፋት ይታወቃል፡፡ በተለይም ታጋዮቹ ለየት ያለ ተልዕኮ በሚፈጽሙበት ወቅት በሚስጢር ስም እንዲጠቀሙ ይደረጋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በጀብሃና ሻዕቢያ ዘንድ ታጋዩን በቅጽል ስም መጥራት በጣም የተለመደ ነው፡፡ ለምሳሌ የጀብሃው “መሐመድ ቺክኒ”፣ የሻዕቢያዎቹ “ወልደ ዲንክል”፣ “ተክላይ አደን”፣ “ሀይሌ ጀብሀ” ይጠቀሳሉ፡፡ “የማነ ጃማይካ” የሚባለው የህወሐት ታጋይም ከድሮ የሻዕቢያ አባል በነበረበት ዘመን ሲጠራበት በነበረው ቅጽል ነው የሚታወቀው፡፡   
2.     ህወሐት
ህወሐት በትግል ስም የመጠቀም ሰፊ ልማድ አለው፡፡ በትጥቅ ትግሉ ዘመን ፓርቲው እያንዳንዱ ታጋይ በትግል ስም እንዲጠቀም ያደርግ ነበር፡፡ እነዚያ ታጋዮች ከትጥቅ ትግሉ ፍጻሜ በኋላም በትግል ስማቸው መጠራታቸውን ቀጥለዋል፡፡ በዚህ ረገድ ከፓርቲው የተገለሉትም ሆነ በፓርቲው ውስጥ ያሉት ተመሳሳይ መንገድ እየተከተሉ ነው፡፡
ህወሐቶች የትግል ስም የሚመርጡት ስማቸውን ሙሉ በሙሉ በመቀየር አይደለም፡፡ የታጋዩ የልደት ስም ብቻ ነው የሚለወጠው እንጂ የአባቱ ስም አይቀየርም፡፡ ከታዋቂ የህወሐት ሰዎች መካከል የሚከተሉትን ከትግል ስማቸው ጋር መጥቀስ ይቻላል፡፡
1.      እምባዬ መስፍን= ስዩም መስፍን
2.     ዘርዑ ገሠሠ= አግዓዚ ገሠሠ
3.     መሐሪ ተኽለ= ሙሴ ተኽለ
4.     አምሀ ጸሐየ= አባይ ፀሐየ
5.     ዮሐንስ ገ/መድህን= ዋልታ ገ/መድህን
6.     ስዕለ አብርሃ= ስዬ አብርሃ
7.     ወልደስላሤ ነጋ= ስብሐት ነጋ
8.     ለገሰ ዜናዊ= መለስ ዜናዊ
9.     ራስወርቅ ቀጸላ= አታኽልቲ ቀፀላ
10.    ገሰሰው አየለ= ስሁል አየለ
11.     መሐመድ ዩኑስ= ሳሞራ ዩኑስ
12.    ዮሐንስ እቁባይ= አርከበ እቁባይ
13.    ሐዱሽ አርኣያ= ሀየሎም አርኣያ
    ህወሐቶችም እንደ ሻዕቢያ ታጋዮቻቸውን በቅጽል ስም የመጥራት ልማድም አላቸው፡፡ ለምሳሌ ከህወሐት ታጋዮች የሚበዙት ሙሉጌታ ገ/ህይወትን “ጫልቱ”፣ ሰለሞን ተስፋዬን “ጢሞ”፣ ጄኔራል አበበ ተክለ ሀይማኖትን “ጀቤ”፣ ጄኔራል አብርሃ ወልደማሪያምን “ኳርተር”፣ ካሳ ገብረመድህንን “ሸሪፎ”፣ አብረሃ ታደሰን “መጅሙእ”፣ ጸጋይ በርሄን “ሀለቃ”፣ ጄኔራል ታደሰ በርሄን “ጋውና” እያሉ ነው የሚጠሩት፡፡ ግንቦት 20/1983 ከአዲስ አበባ ሬድዮ ጣቢያ “የዘመናት የህዝብ ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሰራዊት…” በማለት ያወጀውን ታጋይ በእውነተኛ ስሙ የሚያውቁት ጥቂቶች ናቸው፡፡ የታጋዩ ቅጽል ስም “ላውንቸር” ስለመሆኑ ግን ብዙዎቻችን እናውቃለን፡፡
 
    ከዚህ በተጨማሪ ህወሐትና ሻዕቢያ ታጋዮቻቸውን “ወዲ እገሌ” (የእገሌ ልጅ) እያሉ በሰሜኑ የሀገራችን ስም በሚሰራበት ባህላዊ ዘይቤ መጥራትን ያዘወትራሉ፡፡ በኦፊሴላዊ ደብዳቤዎች ጭምር “ወዲ እገሌ” የሚለውን ልማድ ሲጠቀሙ ይስተዋላል (በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት ይፋ የሆኑትን የአቶ ኢሳያስና የአቶ መለስን ደብዳቤዎች አስታውሷቸው)፡፡
3.     መኢሶን
የመኢሶን ሰዎች በትግል ላይ በነበሩበት ወቅት በልደት ስማቸው ነው የሚጠቀሙት፡፡ ሆኖም ከዋነኛ ስማቸው በተጨማሪ በሚስጢር ስምም ይገለገሉ እንደነበር ከልዩ ልዩ ሰነዶች የተገኘው መረጃ ያረጋግጣል፡፡ በዚህ መሰረት የመኢሶን መስራቾች ከሚታወቁበት የሚስጢር ስሞች የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡
a.     ሀይሌ ፊዳ= መላኩ
b.     ነገደ ጎበዜ= ነጋልኝ
c.     አብዱላሂ ዩሱፍ= አደም
d.     አንዳርጋቸው አሰግድ= ወልዴ
e.     ፍቅሬ መርዕድ= ሳሙኤል
f.      ከበደ መንገሻ= ነጋ
g.     ሲሳይ ታከለ= አሸናፊ
h.     ንግስት አዳነ= አይዳ
i.      ተረፈ ወልደጻዲቅ= ሚካኤል
ታዲያ እነዚህ ስሞች ሚስጢራዊ ደብዳቤ በሚጻፍበት ወቅት ወይም ሚስጢራዊ ስብሰባ በሚካሄድበት ጊዜ ብቻ ነው የሚያገለግሉት፡፡ መኢሶኖች በመታወቂያም ሆነ በፓስፖርት የሚገለገሉት በዋነኛ ስማቸው ነው እንጂ በሚስጢር ስም አይደለም፡፡
4.     ኢህአፓ
ኢህአፓዎችም በትግል ላይ ሳሉ ዋነኛ ስማቸውን በመተው በፓርቲው በሚሰጣቸው ስም ይገለገሉ ነበር፡፡ ፓርቲውን ወክለው በሚገኙበት መድረክ ሁሉ በዚያው ስም ነበር የሚጠቀሙት፡፡ ለታጋዮቹ የትግል ስም የሚሰጥበት ዘይቤ ግን አንድ ወጥ አይደለም፡፡ አንዳንድ ታጋዮች የልደት ስማቸውን ብቻ ይለውጡና ሌላ ቅጥያ ሳያስከትሉበት በዚያው ይጠራሉ (ለምሳሌ “ጋይም” እና “አያልነሽ”ን መጥቀስ ይቻላል)፡፡ አንዳንዶች ግን የአባታቸውን ስም ጭምር ይለውጣሉ፡፡ ከዚህ ሌላም ብዙዎቹ የኢህአፓ ታጋዮች ከትግሉ ዓለም ከተገለሉ በኋላ ወደ ቀድሞ ስማቸው ሲመለሱ ይታያል፡፡ ከኢህአፓ አባላት የትግል ስሞች የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡
a.     ክፍሉ ታደሰ= ታዬ አስራት
b.     መላኩ ተገኝ= ያፌት
c.     ገብረ እግዚአብሄር ወልደሚካኤል= ጋይም
d.     የዓለም ገዥ ከበደ= አያልነሽ
e.     መርሻ ዮሴፍ= በላይነህ ንጋቱ
  
በነገራችን ላይ ድሮ የኢህአፓ ታጋዮች የነበሩት የአሁኖቹ የኢህዴን/ብአዴን ዋነኛ ባለስልጣናት በትግል ስማቸው ነው የሚጠሩት፡፡ እንደምሳሌም መብራቱ ገ/ህይወት (በረከት ስምኦን)እና ፍቅሩ ዮሴፍን (ህላዌ ዮሴፍ) መጥቀስ ይቻላል፡፡ ጌታቸው ጀቤሳ በበኩሉ ለረጅም ጊዜ በትግል ስሙ ሲጠቀም ከቆየ በኋላ ከኢህዴን ሲወጣ “ያሬድ ጥበቡ” የተሰኘውን እውነተኛ ስሙን መጠቀምን መርጧል፡፡
5.     ኦነግ
 
 ከላይ የጠቀስኳቸው ድርጅቶች የትግል ስምን በስራ ላይ የሚያውሉበት ዋነኛ ምክንያት የታጋዮቻቸውንና ደህንነት ለማስጠበቅ በሚል ነው፡፡ በተለይም ታጋዩ በተወለደበት አካባቢ ለውጊያም ሆነ ለሌላ ተልዕኮ የሚሰማራ ከሆነ በዋነኛ ስሙ ቢጠቀም ህይወቱ አደጋ ላይ ይወድቃል ተብሎ ስለሚታመን ነው በትግል ስም እንዲጠቀም ሲደረግ የነበረው፡፡ በተጨማሪም ታጋዩ በትግል ስም ቢጠቀም በወላጆቹና በሌሎች ዘመዶቹ ላይ አደጋ እንዳይደርስባቸው ለመከላከል ይረዳል የሚል ምክንያት ከድርጅቶቹ ይቀርብ ነበር፡፡
    የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ባህል ግን ከዚህ ይለያል፡፡ በዚህ ድርጅት ውስጥ ያለ ታጋይ የትግል ስም እንዲጠቀም የሚደረገው በዋነኛነት ለታጋዩ ደህንነት ተብሎ አይደለም፡፡ ከታጋዩ ደህንነት በላይ ለድርጅቱ አንድነት ጠቃሚ ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው፡፡ የኦነግ ሰዎች ታጋዮቻቸው በትግል ስማቸው ቢጠቀሙ ሀይማኖትና ክፍለ ሀገርን አስታክኮ የሚመጣ መከፋፈልን ለመከላከል ይረዳል በማለት ያምናሉ፡፡ አንድ ታጋይ በስሙ ብቻ ተለይቶ ጥቃት እንዳይደርስበት ለመታደግም ጠቃሚ ነው በማለት ያስረዳሉ፡፡ 
     በዚህም መሰረት የኦሮሞ ስም የሌለው ታጋይ (አሕመድ፣ አብደላ፣ አበበ፣ ከበደ ወዘተ… በመሳሰሉት የሚጠራ) ወደ ድርጅቱ ሲመጣ ቀዳሚ ስሙን ይተውና በኦሮሞ ስም እንዲጠራ ይደረጋል፡፡ የታጋዩ የአባት ስም ኦሮምኛ ካልሆነ እርሱንም ይቀይራል፡፡ ታዲያ ታጋዩ የአባቱን ስም የሚመርጠው በዘፈቀደ አይደለም፡፡ የዘረግ ሀረጉን ወደላይ ሲቆጥር መጀመሪያ የሚመጣበትን የኦሮሞ ስም (የኦሮሞ ስም ያለው ቅመ-አያት የሚጠራበትን) ነው እንደ አባቱ ስም የሚገለገልበት፡፡ የአባቱ ስም ኦሮምኛ ከሆነ (ለምሳሌ እንደ ዮሐንስ ለታ) የራሱን ስም ብቻ ነው የሚቀይረው፡፡ ታጋዩ ይዞት የመጣው ሰው ሙሉ በሙሉ ኦሮምኛ ከሆነ ግን በስሙ ላይ የሚደረግ ለውጥ የለም (እንደ ምሳሌም ባሮ ቱምሳ፣ ኢብሳ ጉተማ፣ አባቢያ አባጆብር የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል)፡፡ ሆኖም ጥቂት የኦነግ ሰዎች ይህንን ልማድ አልተከተሉም፡፡ ከዚህ አሰራር ጋር በማይጣጣም መንገድ ነው የትግል ስማቸውን የመረጡት፡፡ እንደ ምሳሌም በተከታታይ የኦነግ ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡትን በሪሶ ዋቤ፣ ገላሳ ዲልቦ እና ዳውድ ኢብሳን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ድርጅቱን ከውጪ ሀገር የተቀላቀሉትም እንደ አዲስ የትግል ስም ሲሰጣቸው አይታይም (ለምሳሌ ጣሃ አብዲ፣ በያን አሶባ ወዘተ.. ይጠቀሳሉ)፡፡ ከታዋቂ የኦነግ ሰዎች መካከል የጥቂቶቹ የትግል ስም እንደሚከተለው ነው፡፡
a.     አብዱልከሪም ኢብራሂም= ጃራ አባገዳ (ከኦነግ በልዩነት ወጥቶ “የኦሮሞ ነጻነት እስላማዊ ግንባር” የተሰኘውን ድርጅት ቢመሰርትም ከኦነግ መስራቾችም አንዱ ነበር)
b.     መገርሳ በሪ= በሪሶ ዋቤ
c.     ዮሐንስ በንቲ= ገላሳ ዲልቦ
d.     ፍሬው ኢብሳ= ዳውድ ኢብሳ
e.     ቃሲም ሑሴን= ነዲ ገመዳ
f.      ዮሐንስ ለታ= ሌንጮ ለታ
g.     አብረሃም ለታ= አባጫላ ለታ
h.     ዮሐንስ ኖጎ= ዲማ ኖጎ
i.      አብዱልፈታህ ሙሳ= ቡልቱም ቢዮ
j.      ጀማል ሮበሌ= ጉተማ ሀዋስ
————-
መጋቢት 28/2006
አፈንዲ ሙተቂ

በሕገወጥ መንገድ ተታልለው ከሃገር ከወጡ በኋላ በታንዛኒያ እሥር ቤቶች ውስጥ ቆይተው እንደነበር የገለፃቸውን 435 ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች ወደ ሃገር እየመለሰ እንደሆነ የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል፡፡

ኀዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም ከፌደራልና ከክልሎች ለተውጣጡ የጸጥታና ደህንነት ሃላፊዎች እንደተናገሩት መንግስት አራት የጸጥታ ችግሮች አጋጥመውታል፡፡ የመጀመሪያው የሽምቅ ውጊያ የሚያደርጉ ሃይሎች የፈጠሩት ስጋት ነው ያሉት ዶ/ር ሽፈራው እነዚህን ሃይሎች እና ሽብርተኞችን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ፈተና መሆኑን ሲገልጹ፣ ከሃይማኖት ጋር ተያይዞ የሚፈጠረውን የአክራሪነት አደጋ ሙሉ …

ኀዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በቀድሞው የመከላከያ ኢታማጆር ሹም ሌተናንት ጄኔራል ጻድቃን ገብረትንሳይ የቦርድ ሰብሳቢነት የሚመራው ራያ ቢራ በቀድሞ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትና ህወሃትን ተጠግተው በሚነግዱ ነጋዴዎች ከፍተኛ አክስዮን የተመሰረተ መሆኑን ምንጮች ይገልጻሉ። ማይጨው ከተማ ላይ የተገነበው ፋብሪካው 600 ሚሊየን ብር የተከፈለ ካፒታል አለው። ከራያ ቢራ አክስዮን ባለድርሻዎች መካከል   ሌተናንት ጄኔራል ጻድቃንን …

ኀዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢትዮጵያውያኑ ኦስሎ በሚገኘው የእንግሊዝ ኢምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት ገዢው ሃይል የወሰደውን እርምጃ ከማውገዝ በተጨማሪ የኢንግሊዝ መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ስላሉበት ሁኔታ ወቅታዊ መረጃ እንዲሰጥ ጠይቀዋል። የዲሞክራሲ ለውጥ በኢትዮጵያ ባዘጋጀው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ አቶ አንዳርጋቸው የፍትህ ተምሳሌት፣ የነጻነት በር ከፋች ነው የሚሉ መፈክሮች ተሰምተዋል። ኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን …

ኀዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ወኪላችን እንደገለጸው የመንግስት ታጣቂዎች ወደ ሰማያዊ ብርሃን ቤተክርስቲያን በመሄድ ማፍረሳቸውን ለማወቅ የተቻለ ሲሆን አንድ ፓስተር እስከባለቤታቸውና ሌላ አገልጋይ ታስረዋል። የሃረር አብያተ ቤተከርስቲያናት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ዮሴፍ አምደማርያም ታስረው ሲፈቱ ሌላው የቤተክርስቲያኑዋ ፓስተር አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ። ቤተክርስቲያኗ በአገር አቀፍ ደረጃ ተመዝግባ የምትንቀሳቀስ መሆኗ ታውቋል። የክልሉ አፍራሽ …

ኀዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የገዢው መንግስት በምርጫ 2007 ያለውን ተቀባይነት ለማጠናከር በማሰብ የተለያዩ የህብረተሰቡን ክፍሎች በየክፍለ ከተማው በማሰባሰብ የተሰሩ ስራዎችን በማቅረብ ለመመስገን ሙከራ ቢያደርግም፤ተሰብሳቢዎች ግን ምንም እንዳልተሰራና ተሰራ የተባለውም ችግር ያለበት እንደሆነ  ተናግረዋል፡፡ የመንገዶች መበላሸት ያሳሰባቸው ነዋሪዎች በአካባቢው ላሉ አመራሮች የስራውን የጥራት ጉድለት ቢያሳውቁም የተስተካከለ ነገር እንደሌለ ገልጸዋል፡፡  “በ2006 የተሰራው …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››
Image
ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ዛሬ (ህዳር 19/2007 ዓ.ም) እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት ሰሞኑን እያካሄዱት ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማስመልከት እስክንድር ነጋን፣ አንዱዓለም አራጌን እና ሌሎችንም ሊጠይቁ በቦታው ተገኝተው ነበር፡፡

በጠዋት ቂሊንጦ የሚገኙ ወዳጆቼን ጠይቄ አብረውኝ ከነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ነበር ወደ ቃሊቲ ያመራሁት፡፡ ቃሊቲ የተገኘው ሰው ሁሉ መጠየቅ የሚፈልገውን ሰው እና ሙሉ አድራሻውን እያስመዘገበ ሳለ በመሐል እኔም እስክንድርን መጠየቅ እንደምፈልግ ነግሬ ተመዘገብኩ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ግን ስማችሁ ከዚህ ቀደም ያልተመዘገባችሁ አሁን መግባት አትችሉም መባሉን መዝጋቢ ፖሊሱ አረዳን፡፡ እኔ እና ትንሽ ሰዎች መግባት ስንችል አብዛኛው ሰው ግን መግባት እንደማይችል ተነገረን፡፡

በዚህ ሁኔታ እስክንድር ጋር ደርሰን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ አንድ የአንድነት ፓርቲ አባል ሰሞኑን ፓርቲያቸው እስረኞችን በተመለከተ በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ ለእስክንድር ያብራራለት ጀመር፡፡ እስክንድር በተለመደ ጥሞናው ሲያዳምጠው ቆይቶ፣ በግሉ የተሰማውን እና መሆን ቢችል ያለውን ነጥብ ተናገረ፡፡ በመሐል ወጣቱ የአንድነት አባል ወደ እስክንድር ጠጋ ብሎ ሌሎች ተጨማሪ ጉዳዮችን ሲነግረው ድንገት አንድ የፖሊስ አዛዥ ጨዋታቸውን እንዲያቆሙና እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እንዲገባ፣ ወጣቱ የአንድነት አባል ደግሞ ወደ ውጪ እንዲወጣ በትዕዛዝ ማጣደፍ ያዘ፡፡

ይህኔ እስክንድር ለስለስ ባለ አነጋገር ምንም እንዳላጠፋን በመግለጽ ፖሊሱ መረጋጋት እንዳለበት አስረዳ፡፡ የፖሊስ አዛዡ ግን ጭራሽ ብሶበት ወጣቱ በቶሎ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹ፖለቲካ ማውራት አቁሙ› የሚል ሆነ፡፡ ይህን ተከትሎ እስክንድር ድንገት በኃይለ ቃል ተናገረ፡፡ ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው!›› አለ እስክንድር በስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡

በግሌ እስክንድር እንዲረጋጋ፣ ሁኔታው ግን ያልተገባ እንደሆነ ገለጽኩ፡፡ ፖሊሱ ግን ሊረጋጋ አልቻለም፡፡ እስክንድርን ይዞት ሄደ፡፡ ‹‹በርቱ! እንቅስቃሴያችሁ ህጋዊና ሰላማዊ ይሁን እንጂ ትግላችሁን ቀጥሉ!›› ሲል እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እየገባ ተናገረ፡፡ የፖሊስ አዛዡም ከእስክንድር ጋር የነበረንን ቆይታ ሰዓቱ ሳይደርስ ገታው፡፡ የእስክንድር ያገባኛል ባይነት አስደመመኝ፡፡ እስር ቤት ሆኖም፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም እስክንድር ስለ ሀገሩ እንደሚያገባው በስሜት ተናገረ፡፡ መብቱን መቼም ቢሆን አሳልፎ እንደማይሰጥ አስረገጠ፡፡

ስለ ያገባኛል ባይነት ሳስብ በጠዋት ቂሊንጦ ያገኘኋቸውን የዞን 9 ጦማሪዎች አስታወስኩ፡፡ ‹ስለሚያገባን እንጦምራለን!› ይላሉ ወጣቶቹ ጦማሪያን፡፡ ከአብርሃ ደስታ ጋር አብረው ያገኘኋቸው እነ በፍቃዱ ኃይሉ እና አጥናፍ ብርሃኔ ብዙ ጉዳዮችን እያነሱ አወጉኝ፡፡ ‹‹ህወሓት አንድ ወይም ሁለት ነባር የህወሓት ባለስልጣናትን በሽብር ከከሰሰ ስርዓቱ እንዳበቃለት እቆጥራለሁ፡፡ ምክንያቱም ሽብር ማታለያ መሆኑ ይቀራል›› አለኝ በፍቃዱ ኃይሉ፡፡ አብርሃ ደስታ ቀበል አድርጎ ‹‹እናት አልጋነሽ በሽብር ስትከሰስ በጣም ብዙ ሰው ተቃውሞ ነበር›› አለ፡፡ አጥናፍ በበኩሉ ‹‹ቄስና ሸህ ሽብርተኛ እየተባለ አይደለም እንዴ›› በማለት ጠየቀ፡፡

አብርሃ ደስታ አንድ ነገር በኃይል እንደሚቆጨው ተናገረ፡፡ ምን እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹ብዙ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሳላደርግ መታሰሬ ይቆጨኛል!›› አለ፡፡ በፍቃዱ በበኩሉ፣ ‹‹እኔም የገባኝ ነገር ያለውን የሰላማዊና ህጋዊ የመስሪያ ልክ አለመስራታችን ነው፡፡ አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው እንዲህ ለሚያስሩን ስንት ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን እንኳ ሳናደርግ በትንሽ ነገር በርግገው እዚህ ሲያስገቡን ይቆጨኛል›› በማለት ሀሳቡን ቀጠለ፡፡ ‹‹በእርግጥ አንድ ሰው አሁን መጠንቀቅ ያለበት የሚሰራው ስራ ህጋዊ መሆን አለመሆኑን እንጂ፣ ይህን ካደረኩማ ያስሩኛል የሚለውን መሆን የለበትም፡፡ እነሱ ከፈለጉ ያስሩሃል፤ ስለዚህ መብትህን ተጠቅመህ መታሰሩ ይሻላል እንዲሁ ምንም ሳይሰሩ ከመግባት›› ሲል አብርሃ ሀሳቡን አካፈለ፡፡

ቂሊንጦ ከእነ በፍቃዱ ጋር ስንጨዋወት ስለእስክንድር ነጋ ትሁትነት፣ አስተዋይነት፣ ሰላማዊነት እያነሱ ሰላምታ እንዳደርስላቸው ጠየቁኝ፡፡ እኔም እስክንድር ነጋን ሳውቀው በትሁትነቱ፣ በአስተዋይነቱና በሰላማዊነቱ ነው፡፡ ዛሬ በነበረው ሁኔታ ግን ክፉኛ ተበሳጭቶ ነበር የተመለከትኩት፡፡ ያ ፈገግታው ከፊቱ ብን ብሎ ጠፍቶ ‹‹ያገባኛል!›› ሲልበት የነበረውን ስሜት ግር አለኝ፡፡ ካልነኩት የማይነካ ሰው ሲነኩት ትንታግ ነው፡፡ እስክንድር እዛ ስሜት ውስጥ የገባው ተገድዶ ነበር፡፡ ሊጠይቁት የመጡትን ሰዎች አብዛኞቹን አላስገባም ማለታቸው ሳያንስ ከገቡትም መካከል የምታወራውን እኔ ልምረጥልህ በሚል ግብዝነት አባርረዋል፡፡ እስክንድር ይህን አይቶ ዝም ማለት አልቻለም፡፡ ስለሆነም እንዲህ አለ፤

‹‹…እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው! ስለሀገሬ ያገባኛል!››

ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ የሠፈሩ እና ከአሁን ቀደም የዜግነት ጥያቄያቸዉ አጠራጣሪ በመሆኑ ወደ ሀገራቸዉ መመለስ ፈቃድ ያላገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ አንጎላዉያን ወደ ሃገራቸዉ እንዲመለሱ የሚችል ስምምነት መፈረሙ ተገለፀ።

በእስራኤል የአይሁዳውያን ምኩራብ ላይ ጥቃት ከተሰነዘረ በኋላ እየሩሳሌም የግጭት ስጋት ውስጥ ተዘፍቃለች። የዶይቼ ቬሌ ወኪል የሆነችው ታኒያ ክራመር በዘገባዋ ለአንዳንዶች አሁን በከተማዋ የሚታየው ስጋት ሁለተኛውን ህዝባዊ አመጽ ወይም ኢንቲፋዳ ያስታውሳል ትላለች።እሸቴ በቀለ ዘገባውን እንዲህ አሰናድቶታል።

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በዓመት አንዴ አዲስ አበባ ውስጥ ይካሄዳል። የዘንድሮው ማለትም 14ኛው የሩጫ ውድድር እንዴት አለፈ? አረንጓዴ እና ቀይ ቲሸርት ለብሰው ባለፈው እሁድ በሺ የሚቆጠሩ ፣ በተለያየ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገነኙ ኢትዮጵያውያን ፣ አዲስ አበባ የሚኖሩ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላትና

በአፍሪቃ እና በእስያ የሚገኙ የአሸባሪ ቡድኖች በተደጋጋሚ እስላማዊ መንግሥት ብሎ ራሱን የሚጠራዉን አሸባሪ መንግሥት ሲቀላቀሉ ተስተዉሎአል። ፅንፈኛዉ ቡድን «እስላማዊ መንግሥት» ከፅንፈኛዉ አልቃይዳ ቡድን ይልቅ የአሸባሪነት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠሉ ነዉ የተመለከተዉ።

የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃን ጨምሮ ከአርባ በላይ የሚሆኑ የፓርቲው አባላት ቃሊቲ እስር ቤት ውስጥ ታገቱ፡፡ አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች በሚል መሪ ቃል ከህዳር 14 ጀምሮ እያካሄደያለው የማህበራዊ ሚዲያ ንቅናቄ አካል የሆነውን የህሊና እስረኞችን የመጎብኘት መርሀ-ግብር ለመሳተፍ ወደ ቃሊቲ እስር ቤት ያቀኑት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃ […]

ነሐሴ 21/2003 ዓ/ም ከምሠራበት ቦታ በስልክ ተጠርቼ በተለምዶ ማዕከላዊ ተብሎ ከሚጠራው የፌዴራል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ተወስጄ ከአንዲት ትንሽ ጨለማ ክፍል ውስጥ ከተወረወርኩ በኋላ በማግስቱ አራዳ ወረዳ ፍ/ቤት ቀርቤ የሃያ ስምንት ቀን የምርመራ የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆብኝ ተፈቅዶላቸው ያም ሲያልቅ እንደገና ሌላ ቀጠሮ ተጠይቆ ተፈቅዶላቸው፣ የማይመለከቱኝን ጥያቄዎች ስጠየቅና ስመልስ ቆይቼ ጥቅምት 3/2004 በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ ቤት 3ኛ […]


 ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
አንጋፋውን ሱዳናዊ ድምጻዊ ዐብዱልከሪም አል-ካብሊን ከዚህ ቀደም ተዋውቀነው ነበር፡፡ ታዲያ የዚህን ጎምቱ ሰው ድምጽ ዛሬ ከአንድ ጓደኛዬ “አይፓድ” ውስጥ ሰማሁትና በሃሳብ ወደ ልጅነቴ ወሰደኝ፡፡ እናም ከርሱ ጋር “ሸዛ ዛሂር” እያልኩ ሳንጎራጎር “ስለዚህ ዘፈን ለምን አንድ ነገር አልጽፍም?” የሚል ሃሳብ መጣብኝ፡፡ እነሆ ጻፍኩላችሁ!!
*****

Abdul-Keriem Al-Kabli, the legendary Sudanese music icon.

አል-ካብሊ ከሌሎች ሱዳናዊያን ድምጻዊያን ከሚለይባቸው ባህሪዎች አንዱ አብዛኛውን ጊዜ ሙዚቃዎቹን በራሱ የሚጽፋቸው መሆኑ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በሙዚቃዎቹ ውስጥ ከሱዳን የዐረብኛ ዘይቤ ይልቅ ብዙ ጊዜ የጥንቱን “ዐረቢያ አልፉስሓ” (Classical Arabic) የሚጠቀም መሆኑ ነው፡፡ ሦሥተኛው ደግሞ ግጥሞቹን በሚጽፈበት ጊዜ ጥንታዊ የሆኑትን “ቀሲዳ”፣ “ቡርዳ” እና “ሙዓለቃት” የሚባሉት የዐረብኛ የስነ-ግጥም ዘይቤዎችን የሚጠቀም መሆኑ ነው፡፡
ከአል-ካብሊ ዘፈኖች መካከል በጣም የሚደነቀው “ሸዛ ዛሂር” ይባላል፡፡ “ሸዛ ዛሂር” የሚደነቀው በጥንቱ ዐረቢያ ፉስሓ የተገጠመ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን ዜማውም በጣም ማራኪ በመሆኑ ነው፡፡ የዘፈኑ አዝማች በኢራኖቹ “ሩባኢያት” ስልት የተጻፈ ሲሆን ተከታዮቹ ግጥሞች ግን በዐረብኛው “ሙዓለቃት” ስልት ነው የተጻፉት፡፡
 *****
“ሸዛ ዛሂር” በጣም የተደነቀው ግን በግጥሞቹ ውበት ሳይሆን በመልእክቱ እና ደራሲው ግጥሙን ሲጽፍ በተከተለው ለየት ያለ ተምሳሌታዊ (allegorical) ዘይቤ ነው፡፡ ግጥሙ ሲጀምር “ሸዛ ዛሂር” ይላል፡፡ “አበባው ፈነዳ… መዓዛው ምድሩን ሞላ” እንደማለት ነው፡፡ ታዲያ በዘፈኑ ውስጥ በአበባ የሚያስመስለው ሰው ሴት ሳትሆን ወንድ ነው፡፡ ወንድን አበባ እያሉ ማሞገስ አለ እንዴ?… በሌላ ቦታ አይታወቅም፡፡ አል-ካብሊ ግን አደረገው፡፡
   አል-ካብሊ የወደደውን ወንድ ሲያሞግስ “ወአንዙሩ ላ አራ በድረን አንተ ለይለተል በድሩ” ይለዋል፡፡ “ወደ ሰማይ ሳንጋጥጥ ሙሉውን ጨረቃ ለማለት አልቻልኩም፤ ምክንያቱም ያንተ ብርሃን ጨረቃውን አጨልሞታል” እንደማለት ነው፡፡ በተጨማሪ ደግሞ “አንተ ረሒቁን ለና” እስከማለት ደርሷል (“አንተ የኛ Nectar ነህ” እንደማለት ነው፤ Nectar ወፎችና ንቦች የሚቀስሙት የአበባ ጣፋጬ ክፍል ነው፤ በአማርኛ ምን ይባላል)፡፡
አል-ካብሊ ከዚህም ርቆ ይሄድና የወደደውን ሰውዬ “ለደቱ አል-ኸምረ ዐን ሸፈቲ፤ ለዐለ ጀማለከል ኸምሩ” ይለዋል፡፡ “አንድም የመጠጥ ብርጭቆ ወደ ከንፈሬ አላስጠጋሁም፤ ነገር ግን ውበትህ “ኸምር” ሆኖ አስክሮኛል” ማለቱ ነው፡፡ ለመሆኑ ሰውዬው ምን ነክቶት ነው ወንድን እንዲህ የሚያሞግሰው (አንዳንዱ ሰው ምናልባት… Gay ሳይሆን አይቀርም ይል ይሆናል….ቂቂቂቂ)
የሰውዬውን ማንነት ከኋላ ትመጡበታላችሁ፡፡ አሁን የዘፈኑን ግጥም ተመልከቱ፡፡
(አዝማች)
ሸዛ ዛህሪን ወላ-ዛህሩ
ፈዐይነ ዚሉ ወን-ነህሩ
ረቢዑ ሪያዲና ወላህ
አሚን አህ ፊከ አን-ነሽሩ
—–
ወሐዘ ነሁሩ የብሱሙሊ ዐኒ-ድ-ዱንያ ወየፍተሩ
ወአንዙሩ ላ አራ በድረን አአንተ ለይለተል በድሩ፡፡
—–
ወቢሂ ሱክሩን ተመለከኒ ወዐጀቡን ከይፈ ቢሂ ሱክሩ
ረድቱ አል-ከእሳ ዐን ሸፈቲ ለዐለ ጀማለከል ኸምሩ፡፡
—-
ነዐም አንተ ረሒቁን ለና ወአንተ ሲሕሩ ወልኢጥሩ
ወአንተ ሲሕሩ ሙቅተዲረን ወገይረል ሀይ ወሀዋ ሲሕሩ፡፡
ኹዙ ዱኒያ ቢዐጅማኢሀ ሐቢቡን ዋሒዱን ዙኽሩ
ኢዛ ጃአት መጣሊኡሁ ፈኩሉ ሰማኡና በድሩ፡፡
ኹዙ ዱኒያኩሙ ሃዚሂ ፈዱኒያዋቱና ኩስሩ፡፡
ኹዙ ዱኒያኩሙ ሃዚሂ ፈዱኒያቱና ኩስሩ፡፡
*****
የአል-ካብሊ ግጥም ቅኔያዊ ፍቺ በመጨረሻው ስንኝ ላይ ነው የሚገኘው፡፡ “ኹዙ ዱኒያኩሙ ሃዚሂ ፈዱኒያቱና ኩስሩ” ማለት “ዱኒያ ይህቺ ናትና እዩዋት፤ መጨረሻ ላይ ተሰባሪ ናት” ማለት ነው፡፡ እውነትም ዱኒያ ተሰባሪ ናት፡፡ አል-ካብሊ ግን ሰውዬን አድንቆት ሲያበቃ “ዱኒያ ተሰባሪ ናት ብሎ” ዘጋው፡፡ ከፊት የተናገረውን መቃረን ይሆናል አይደል…?
ነገሩ ወዲህ ነው፡፡ አል-ካብሊ እንዲህ ያደነቀው ሰው ጓደኛው ነበረ፡፡ ይህ ጓደኛው ገጣሚ ሲሆን በጣም ውብ የሆኑ ግጥሞችን በመጻፍ ይታወቃል፡፡ አንድ ቀን ግን ሳይጠበቅ “ጭጭ” አለ፡፡ ምንም ሳይታመም ነፍሲያው ወጣች፡፡ አል-ካብሊ በዚህ ድንገተኛ አደጋ ተደናገጠ፡፡ ልቡ ተሰበረች፡፡
ጓደኛው ከተቀበረ ከጥቂት ቀናት በኋላ በሐዘኑ የተጎዳው አል-ካብሊ በምሽት ከቤቱ ወጥቶ ሰማይ ሰማዩን ማየት ጀመረ፡፡ ሰማዩን እያየ ሟች ጓደኛውን ሲያስታውስ ይህ ግጥም መጣለት፡፡ ወዲያውኑ “ሸዛ ዛሂር”ን ጻፈውና መጫወት ጀመረ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ በአንድ አልበም ውስጥ አካተተው፡፡ ግጥሙ በሱዳኖች ዘንድ ሲሰማ ዐጂብ ተባለ፡፡ የሙዚቃ ገምጋሚዎች በበኩላቸው የአል-ካብሊ የምንጊዜም ምርጥ ዘፈን በማለት ሰየሙት፡፡
*****
አል-ካብሊ “ሸዛ ዛህር”ን ከጻፈው በኋላ እንደ መግቢያ የሚጠቀምበት አጭር እንጉርጉሮም አክሎለታል፡፡ ዘፈኑ ለገጣሚው ጓደኛው የተጻፈ መሆኑን በግልጽ የሚያሳውቀው በዚህ እንጉርጉሮ ውስጥ ነው፡፡ ይህ እንጉርጉሮ በተለምዶ “ማለሁ” እየተባለ የሚጠራው ነው (አል-ካብሊ እንጉርጉሮውን “ማለሁ” በማለት ነው የሚጀምረው፤ ዐረብኛ እንዲህ ሲባል “ለምን ሲል ነው?” የሚል ዘይቤአዊ ፍቺ አለው)፡፡ ታዲያ አል-ካብሊ ብዙ ጊዜ ዘፈኑን ከእንጉርጉሮው በመለየት ነው የሚጫወተው፡፡ አንዳንዴ ግን ሁለቱንም በአንድ ላይ ይዘፍናቸዋል፡፡ ሁለቱ ግጥሞች ሲዘፈኑ የተለያየ የድምጽ ውጣ-ውረድን ስለሚጠይቁ ማንም ዘፋኝ ነኝ ባይ በአንድ ላይ ሊዘፍናቸው ይቸገራል፡፡ እኔ ባለኝ ልምድ ግን አንድ ሰው ሁለቱንም በአንድነት ዘፍኖአቸው ተሳክቶለት አይቼአለሁ፡፡
አዎን! ዓሊ ቢራ ነው፡፡ ዓሊ በ1998 የእንቁጣጣሽ በዓልን በማስመልከት በሸራተን አዲስ በተዘጋጀው የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ እንጉርጉሮውንና ሸዛ ዛህርን አንድ ላይ ዘፍኖአቸዋል፡፡ የዓሊ ቢራ አዘፋፈን ውብ መሆኑን ለማየት በዩ-ቲዩብ ላይ የተጫነውን ቪዲዮ ይመልከቱ፡፡
(ቪዲዮውን ለማለት የሚከተለውን ሊንክ ክፈቱ)፡፡
በነገራችን ላይ ዓሊ ቢራ “ሸዛ ዛህር”ን ብቻ ሳይሆን ሌሎች የሱዳን ዘፈኖችንም ሲጫወት በጣም ይሳካለታል፡፡ የዚህ ስኬት አንደኛው ምክንያቱ ደግሞ ዓሊ ግጥሞቹ የተጻፉበትን “ዐረቢያ አል-ፍስሓ”ን በትክክል መናገር የሚችል መሆኑ ነው፡፡ (ዐረቢያ አል-ፉስሓ ሃያ ስምንቱን የዐረብኛ ድምጾች በትክክል ማውጣትን ይጠይቃል)፡፡
*****
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 18/2007

ኀዳር ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ትብብሩ ህዳር 18 ለመስተዳድሩ ባስገባው የእውቅና ጥያቄ ፣ የተቃውሞ ሰልፉን በመስቀል አደባባይ ከህዳር 27 እስከ ህዳር 28፣ 2007 ዓም ለማካሄድ ማቀዱን ገልጿል። የእውቅና ደብዳቤውን ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ሊቀመንበርና የትብብብሩ ም/ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርጌሎ፣ አቶ ግርማ በቀለ ከኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና …

ኀዳር ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አርበኛ ጋሻው ሽባባው በሰሜን ጎንደር ዞን አዳርቃይ ወረዳ ከመንግስት ታጣቂ ሃይሎች ጋር ለ4 ወራት ሲፋለም በቁጥጥር ስር መዋሉን ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛው ወንጀል ችሎት የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም ድርጊቱ የ4 አመት ከ8 ወር እስራት እንደፈረደበት ገልጿል። አርበኞች ግንባር በወቅቱ ባደረገው ተደጋጋሚ ጥቃት ከ60 ያላነሱ የመንግስት ወታደሮችን መግደሉን …

ኀዳር ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የብአዴን አመራሮች ሰሞኑን በዞኑ ባካሄዱት የወጣቶችና ሴቶች ጉባኤ ላይ ፣ የአካባቢው ወጣቶች የጸረ ሰላም ሃይሎች መሳሪያ ከመሆን እን  ዲቆጠቡ ጠይቀዋል። ወጣቶቹ በግፍ የታሰሩ የአካባቢው የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የሆኑት አንጋው ተገኝ፣ አባይ ዘውዱና ሌሎችም አባላት ታፍነው መወሰዳቸውን ተቃውመዋል። በተለይ የጋብላ እና የዘመነ መሬቅ ወጣቶች እውን ዲሞክራሲ የሚባለው …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ናሚቢያን ላለፉት 24 ዓመታት የመራት የደቡብ ምዕራብ አፍሪቃ ሕዝባዊ ድርጅት በእንግሊዘኛ ምኅጻሩ SWAPO በዘንድሮው የናሚቢያ የምክር ቤት እና የፕሬዚዳንት ምርጫ የማሸነፍ ዕድሉ ሰፊ እንደሆነ ተገምቷል። ሆኖም በአንዳንድ የፓርቲው አባላት ዘንድ ይኽ መነቃቃት ደብዛዛ መሆኑ ተጠቅሷል።

በ 70 ዎቹ ዓመታት በፖፕ ሙዚቃ ጥበቡ፣ በዓለም የሙዚቃ መድረክ ከፍተኛ ዝናን ያተረፈዉና የስልምና ሐይማኖትን በመቀበሉ የሚታወቀዉ ምዕራባዊዉ ዝነኛ ሙዚቀኛ በጀርመን የሙዚቃ መድረክ ዳግም ብቅ ሊል መሆኑ ከተገለፀ በኋላ የብዙሃን መገናኛን ቀልብ ስቦ ይገኛል።