ፈርግሰን-ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ ያልታጠቀ ጥቁር ወጣትን የገደለዉ ነጭ ፖሊስ እንዳይከሰስ የከተማይቱ ፍርድ ሸንጎ መወሰኑ የቀሰቀሰዉ ሕዝባዊ ቁጣና ተቃዉሞ እንደቀጠለ ነዉ። ጀርመንም ቢሆን ፖሊሶች በቆዳ ቀለም ከፍተኛ የዘር መድሎ ያደርጋሉ በሚል በተደጋጋሚ ይወቀሳሉ።

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለአዳሩ ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ አስገባ
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ.ም ለሚደረገው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የእውቅና ደብዳቤ አስገባ፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የገባው ደብዳቤ በሰማያዊ፣ መኢዴፓ እና ኢብአፓ ተፈርሞ የገባ ሲሆን የእውቅና ደብዳቤውንም ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ሊቀመንበርና የትብብብሩ ም/ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርጌሎ፣ አቶ ግርማ በቀለ ከኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና የትብብሩ ፀኃፊ እና የመኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ ገንዘብ ያዥ አቶ ኑሪ ሙደሲር አስገብተዋል፡፡

የትብብሩ አመራሮች ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ በሄዱበት ወቅት የአቶ ማርቆስ ተወካይ ለሆኑት አቶ ፈለቀ አበበ ደብዳቤውን ለመስጠት ጥረት ቢያደርጉም ተወካዩ ‹‹የከንቲባ ጉዳዮች ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው የለም፡፡ እሱ ካልመራበት መቀበል አንችልም›› በሚል ደብዳቤውን አልቀበልም እንዳሏቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ ወደ አቶ አሰግድ ቢሮ ቢያቀኑም እንዳላገኙዋቸው ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ሆኖም የትብብሩ አመራሮች ደብዳቤ መስጠት እንጂ ደብዳቤ ማስመራት የሰራተኞቹ እንጂ የእነሱ ስራ እንዳልሆነ በመግለጽ ደብዳቤውን ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ታመዋል የተባሉት የአቶ ማርቆስ ተወካይ የሆኑት አቶ ፈለቀ ቢሮ በአራት ምስክሮች ፊት አስቀምጠው መምጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ አመራሮቹ የእውቅና ደብዳቤውን አቶ ፈለቀ ቢሮ አስቀምጠው ከመውጣታቸውም ባሻገር በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በፈጣን መልዕክት (ኢ ኤም ኤስ) በሪኮመንዴ ቁጥር eg157416502et መላካቸውን ገልጸዋል፡፡

የአዳር ሰላማዊ ሰልፉ ህዳር 27 ከጠዋቱ 3 ሰዓት ተጀምሮ ህዳር 28 ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የሚጠበቅ ሲሆን ቦታውም መስቀል አደባባይ ላይ እንደሚሆን መወሰኑ ታውቋል፡፡

የትብብሩ አመራሮች የእውቅና ደብዳቤውን ለማስገባት በሄዱበት ወቅት በቦታው የትብብሩ አመራሮች የሚያውቋቸው ደህንነቶች ባለ ጉዳይ በመምሰል ይመላለሱ እንደነበርና ፖሊሶችም ይከታተሉ እንደነበር ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
Image

አቶ አንተነህ መርዕድ የተባሉ ሰው ”ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ” በሚል ርእስ በዘሀበሻ ድህረገጽ ላይ ላቀረቡት መጻጽፍ የመልስ መንደርደሪያ የሚሆን ”ክህደትን ክህደት፣ የካደንም ከሀዲ ለማለት ድፍረት ይኑረን” በሚል ርእስ በኦክቶበር 8/2014 ለዘሀበሻ ድህረገጽ ልኬለት ባያወጣውም ሌሎች በድህረገጻቸው አውጥተውት አይቻለሁ፣ በዚህ አጋጣሚ እውነቱ እንዲነገር እድል ለሚሰጡ ድህረገጾች ምስጋናየን አቀርባለሁ። ባለፈው ጽሁፌ በቀጣይነት አቀርባለሁ ባልሁት መሰረት ለዛሬው የሚከተለውን ይዤ […]

ጦርነትትን ሰርተን ድል እናመጣለን የሚለው ስልጣን ላይ ያላው አካል አይዶሎጂ እንደሆነ ይታወቃል። ቦንብ አፈንድቶ ንፁሀን ዜጎችን ፈጅቶ የስልጣን እድሜን ለማራዘም በብዙ አኳያ ሲጠቀሙበት እንደነበረም የሚታዋቅ ነው። ያገራቸውን ሁኔታ በቅርበት የሚከታታለ ዜጎች መንግስት ያደርጋል ብሎ ለማመን ቢከብድም ለመናገር የማይቻልበት ሁኔታ ውስጥ ባይሆኑም ይህን ማወቅ ግን ነበረባቸው። ቦንብ እያፈነዱ ብዙ ጊዜ አስርና አምስት ንፁሀን ዜጎች ተቀጥፈዋል። ታዲያ […]


click here for pdf

ከለም ሆቴል ወደ ካዛንቺስ የሚሄድ ታክሲ ውስጥ ገብቼ ከኋላ ወንበር ተቀመጥኩ፡፡ ከጎኔ ሁለት በዕድሜ ወደ ሠላሳዎቹ አጋማሽ የሚሆኑ ሴቶች ተቀምጠዋል፡፡ ታክሲው ሲንቀሳቀስ ‹‹ለመሆኑ ምን ዓይነት ነገር ቢገጥምሽ ነው ለመንገር ያስቸግራል የምትይኝ›› አለቻት መካከል ያለቺዋ ወደ መስኮቱ ጥግ የተቀመጠችውን፡፡ እንደ ታክሲ መቼም ማኅበራዊ ኑሯችንን የምናውቅበት ምቹ መድረክ የለምና ጆሮዬን ጣል አደረግኩ፡፡ ‹‹ባክሽ ችግሩን ከመሸከሙ ችግሩን መግለጡ ይከብዳል›› አለች ያችኛዋ፡፡
 
አንድ ሊቅ ‹‹እጅግ አስቸጋሪው ችግር ሊገልጡት የሚያስቸግር ችግር ነው›› ያሉትን አስታወሰኝ፡፡ ምን እንደገጠማት ባላውቅም አንዳንድ ችግር ግን የሕመሙን ያህል መግለጫ ነገር አይገኝለትም፡፡ ሲናሩት ተራ ወይም ቀላል ይሆናል፡፡ ሰሚውም ‹‹አሁን ይኼ ችግር ነው?›› ይላል፡፡ ተናጋሪውም ንግግሩ ቀላል ስለሚሆንበት ከችግሩ በላይ ያመዋል፡፡

 ‹‹ግዴለሽም እንደምንም ብለሽ ንገሪኝ›› አለቻት፡፡

‹‹አንቺና ባለቤትሽ ስታወሩ እንዴት ነው?›› ስትል ጥያቄዋን በጥያቄ መለሰችው፡፡
‹‹እንዴት?በቃ ማውራት ነዋ፡፡››
‹‹ስታወሩ ምን ይሰማሻል?››
‹‹ፊዚክስ አደረግሽዋኮ›› አለች እየሳቀች፡፡
‹‹እኔ ግን ከእርሱ ጋር ሳወራ ያመኛል፡፡››
‹‹እንዴት? ይሰድብሻል፤ ይቆጣል፤ ምን ዓይነት ክፉ ቃል ቢናገርሽ ነው››
በመስኮቱ ጥግ ያለችው ሴት አንገቷን ስትነቀንቅ በዚህኛው መስኮት ነጸብራቅ በኩል አያታለሁ፡፡
‹‹ሁሉም አይደለም›› አለቻት፡፡ ጠያቂዋ የእፎይታ ትንፋሽ በረጅሙ ተነፈሰች፡፡
‹‹ታድያ ምድን ነው?›› አለች ጠያቂዋ፡፡
‹‹አየሽ ለመናገር አስቸጋሪ የሚሆነው አሁን ካልሻቸው ነገሮች አንዱን እንኳን ስላልሆነ ነው፡፡ እስካሁን ስም የወጣለት አይመስለኝም፡፡ ስድብ አይደለም፤ ቁጣ አይደለም፤ ማመናጨቅ አይደለም፤ ሽሙጥ አይደለም፤ ጭቅጭቅ አይደለም፣ ንትርክ አይደለም፤ ክርክር አይደለም፤ ሌላ ነው››
 
‹‹እንዴ እንትናዬ(ስሟን እያቆላመጠች) ምንድን ነው የሆንሽው? ምንድን ነው የሚያደርግሽ?››
 
‹‹የሁለታችን ወሬ ያማል፤ ጣዕም የለውም፡፡ እንጨት እንጨት የሚል፡፡ ምንም ነገር የሌለው፤ በቴፕ ተቀድቶ ብትሰሚው ባልና ሚስት እያወሩ ነው የማትዪው ዓይነት››
 
ወደራሴ ተመለስኩ፡፡ ‹የሚያም ንግግር› ብላ የጠቀሰችው ምንድን ነው? ስድብ ካልሆነ፣ ግልምጫ ካልሆነ፣ ቁጣ ካልሆነ፣ አግቦ ካልሆነ፣ ክርክር ካልሆነ፣ ጭቅጭቅ ካልሆነ፣ ንትርክ ካልሆነ፣ እንካ ሰላንትያ ካልሆነ፤ ታድያ ምንድን ነው?  ‹እንጨት እንጨት የሚል› ያለችው ምንድን ነው?
 
ሰውን ከሰው ጋር የሚያግባባው ዋናው ነገር ቋንቋ ነው፡፡ ካልተናገረ አይታይ ብልሃቱ፣ ካልታረደ አይታይ ስባቱ የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ ከአያያዝ ይቀደዳል፣ ከአነጋገር ይፈረዳል የሚልም ተጨምሮበታል፡፡ ግን መናገር ማለት ምን ማለት ነው? ንግግር ሁሉ መልእክት ያስተላልፋል? ንግግር ሁሉ ያግባባል? ሰው በቋንቋ እንደሚግባባው ሁሉ የማይግባባውም በቋንቋ ነው፡፡ ኤፍሬም እሸቴ ‹‹ቋንቋ መግባቢያ አይደለም›› የሚል ጽሑፍ ነበረው፡፡ ‹ቋንቋ ከሌላቸው እንስሳት በላይ ቋንቋ ያለው ሰው አለ መግባባት ከቻለ ቋንቋ ምኑን መግባቢያ ሆነው› ይላል፡፡ 
 
ቋንቋ ግን ብቻውን አያግባባም፡፡ ሐሳብ፣ ቃላት፣ ሰዋስውና ንግግር ብቻቸውን ሰዎችን አያግባቡም፡፡ ብቻቸውንም ውስጣችንን አይገልጡም፡፡ የእጆቻችን ወንጫፊዎች፣ የፊታችን ኩስታሬ፣ የዓይኖቻችን እንቅስቃሴ፣ የድምጻችን ቃና፣ የአንገታችን ንቅናቄ እንኳን ተጨምሮበት በሚፈለገው መጠን ሊያግባባን ዐቅም የሚያንሰው ጊዜ አለ፡፡ በመናገርና በመሰማት መካከል ልዩነት የሚፈጥረው፣ በማስረዳትና በመረዳት መካከል ያለውን ክፍተት የሚያሰፋውና የሚያጠበው፣ በሚወረወረው መልእክትና በሚፈጠረው ምላሽ መካከል ያለውን የተገቢነት ምጣኔ የሚለካው አንዱ ነገር – የቋንቋው ጣዕም ነው፡፡
 
ልክ እንደ ምግብ ጣዕም፡፡ አንድ ሰው አንድን ምግብ ለጤና ተስማሚ፣ የተመጣጠነ ምግብ የያዘ፣ በውድ ዋጋ የተገዛ ስለሆነ ብቻ አይመገበውም፡፡ እጅ የሚያስቆረጥም፣ ምላስ የሚያስቀረጥፍ፣ ሰሐኑን ብሉት ብሉት የሚያሰኝ የሚባልለት ሌላ ነገር ያስፈልገዋል – ጣዕም፡፡ ከአሠራሩ፣ ከይዘቱ፣ ከቁሌቱ፣ ከቅመሙ፣ ከውሕደቱ፣ ከአበሳሰሉ፣ ከቅንብሩ የሚመጣ፡፡ ለዚህም ነው መጋቢዎችና አስመጋቢዎች ከምግቡ ይዘት ባሻገር ለምግቡ ጣዕምና ለምግቡም አቀራረብ የሚጨነቁት፡፡ በምግብ ሂደት አንዱ ወሳኝ ነገር በምግቡና በበላተኛው መካከል ያለው ክፍተት ነው፡፡ በላተኛውን ወደ ምግቡ የሚወስደው፣ ያንን ምግብ እንዲመርጥ፣ ከመረጠም በኋላ ወዶትና ጣፍጦት እንዲበላ የሚያደርገው ነገር ነው – ይኼ በምግብና በበላተኛ መካከል ያለው ነገር፡፡ የገዛነውን ሁሉ ወደ ሆዳችን አንልከውምኮ፤ ገዝተነው የማንበላው ምግብ አለ፡፡ 
 
ከፍትፍቱ ፊቱ የሚለው ነገርኮ እንዲሁ አልመጣም፡፡ ያ ሁሉ ጣዕም ያለው ምግብ ቢዘጋጅ እንኳን ‹‹ብሉልኝ፣ ጠጡልኝ፣ በሞቴ፣ አፈር ስሆን፣›› እያለ ጠብ እርግፍ ብሎ የሚጋብዝ፣ ፊቱ ለምግብ የተፈጠረ ጋባዥ ካላገኘ ያቅራል ማለት ነው፡፡ ‹ሲያዩት ያላማረ ሲበሉት ያቅራል› እንዲሉ፡፡ እስኪ አስቡት እንደ ድሮ የአንደኛ ክፍል አለቃ፣ አርጩሜ ይዞ የተኮሳተረና ‹ብላ! አርፈህ ብላ! ውሰድ! ከቀይ ወጡ ውሰድ! አልጫ ጨመር! ዋ!›› የሚል አስተናጋጅ ከጎኑ የቆመበት ግብዣ ቢገጥማችሁ እንዴት ነው የሚበላችሁ፡፡ 
 
ንግግርም እንደዚያው ነው፡፡ ቀልዶች፣ ምሳሌዎች፣ ሰምና ወርቆች፣ አባባሎች፣ ግጥሞች፣ ተረቶች፣ ዘይቤዎች የተፈጠሩት ቃላት ቃላት ስለሆኑ ብቻ የልባችንን ስለማይገልጡት ነው፡፡ የንግግር ዜማ፣ የአወራር ዘይቤ፣ የአገላለጥ መንገድ፣ የነገር ክዋኔና  የአነጋገር ቃና ንግግሩ እንዲሰማ ሳይሆን እንዲበላ ያደርገዋል፡፡ ከሆድ ጠብ እንዲል፣ አንጀት እንዲያላውስ፣ ቁጣን አቀዝቅዞ፣ ፈገግታ እንዲጨምር፣ ኀዘንን አስረስቶ ደስታን እንዲያስከትል ያስችለዋል፡፡ 
 
ያቺ በመስኮቱ ጥግ የነበረችው ሴት እንዲህ ብላ ነበር ለጓደኛዋ ምሳሌ የሰጠቻት፡፡
ዛሬ ጠዋት የተነጋገርነውን ነገር ልንገርሽ፡፡
ደወለና ‹ልጆቹን ዛሬ ማነው ከትምህርት ቤት የሚያወጣቸው?›
‹አንተ አትችልም እንዴ?›
‹አልችልም›
‹ምን ይሻላል?›
‹እንትና ያውጣቸው ንገሪው›
‹አንተ ብትደውልለት አይሻልም?›
‹አንቺ ደውዪ›
‹ስልኩን ትሰጠኝ?›
‹ቴክስት አደርጋለሁ›
‹ኦኬ›
‹ቻዎ›
አሁን እዚህ ውስጥ ፍቅር፣ ናፍቆት፣ ደግነት፣ ቤተሰባዊነት፣ ኀዘኔታ፣ አክብሮት፣ ባልነት፣ ሚስትነት አሉ? አሁን ይኼ ንግግር በሁለት አማርኛ በሚችሉ ሰዎች መካከል የተደረገ መሆኑን እንጂ በሚዋደዱ ባልና ሚስት መካከል የተደረገ መሆኑን የሚያሳይ አንዳች ነገር ልታሳዪኝ ትችያለሽ፡፡ እንዲህ ነውኮ ሁሌም የምናወራው፡፡ ቃላት መለዋወጥ ብቻ፡፡ ዜማ የለው፣ ፍቅር የለው፣ አክብሮት የለው፣ ትኅትና የለው፣ ናፍቆት የለው፡፡ ባዶ ቃላት ብቻ፡፡ የተሰበሰበ ድንች፡፡
 
‹የተሰበሰበ ድንች› ነበር ያልኩት ለራሴ፡፡ ‹እምቦቲቶ› ሲበላ እንኳን በሚንተከተክ ብረት ድስት ተቀቅሎ፣ በሚጥሚጣ፣ በቁንዶ በርበሬ፣ በጨው ጣፍጦ ነው፡፡ ‹የተሰበሰበ ድንች› አለች፡፡ አንድ የቢሮ ጓደኛዬ ምን እንዳለችኝ ልንገርሽ.. ስትል የመውረጃ ቦታችን ደረስን፡፡ – ካዛንቺስ፡፡ ወረድን፡፡ ወደ ኡራኤል አቅጣጫ እየወረዱ ተረከችላት፡፡
(ይቀጥላል)
    


ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
እነሆ በድጋሚ ወደ ተረት ዓለም ልወስዳችሁ ነው፡፡ ድሮ የሰማሁት አንድ ተረት ከሰው ልጅ ደካማ ባህሪያት መካከል የሚቆጠረውን “ጥጋብ”ን በተዋበ መንገድ እንዴት እንደሚሄሰው እዩት፡፡
—–
በአንዲት መንደር የሚኖር አንድ ደሃ ሰው የሚበላውን እያጣ ይቸገር ነበር፡፡ ሰውዬው ብዙ ዘመን በችግር ካሳለፈ በኋላ “በተወለድኩበት ምድር በረሃብ ከምሞት ወደ ሌላ ሀገር ልሂድና ሲሳዬን ልፈልግ” በማለት ተሰደደ፡፡ ብዙ ከሄደ በኋላ ድካም ሲጀምረው ከአንድ ዛፍ ስር አረፍ አለ፡፡ ልክ እንደተቀመጠም ከዛፉ ላይ የነበረችው አንዲት በቀቀን “ጥጋብ አይቻልም” እያለች መዘመር ጀመረች፡፡ ሰውዬውም ወደላይ እያንጋጠጠ “እንዲህ ስትይ አታፍሪም እንዴ?! ረሃብ ነው የማይቻለው እንጂ ጥጋብማ በደንብ ነው የሚቻለው” በማለት አጸፋውን መለሰላት፡፡
  ሰውዬው የሚበቃውን ያህል ካረፈ በኋላ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ብዙ ከተጓዘ በኋላም ወደ አንዲት ትንሽ ከተማ ገባ፡፡ እዚያም ልመናውን ጀመረ፡፡ ብዙ ቤቶችን አዳረሰ፡፡ የከተማዋ ሰዎችም ያላቸውን ሰጡት፡፡ ሰውዬው ምሽቱን ከአንድ በረንዳ ስር አሳለፈ፡፡ በማግስቱም ልመናውን በመቀጠል ከአንድ ሰፊ ግቢ ደረሰ፡፡ እዚያም “ስለ አላህ! ያላችሁን ስጡኝ! ተዘከሩኝ” በማለት ልመናውን ተያያዘው፡፡ የቤቱ ባለቤት የግቢውን በር ከፈተችና ለማኙን አየችው፡፡ ሰውዬው ከመጎሳቆሉ በስተቀር መልከ መልካም ነው፡፡ አንድም የአካል ጉዳት የለበትም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሰው መለመኑ ስላስገረማት “አንተ ሰው! እንደዚህ ጤነኛ ሆነህ ነው እንዴ የምትለምነው?” አለችው፡፡ “ምን ላድርግ እመቤቴ ተቸግሬ ነው እኮ!” በማለት መለሰላት፡፡
“ለምን ሰርተህ አትበላም?”
“ስራ የለኝም፤ ትናንት ነው ከሌላ ሀገር የመጣሁት”
“እና ልትለምን ነው የመጣኸው?”
“አዎና እመቤቴ! ስራ የለኝም እኮ”
“ስራ ቢሰጥህ ትሰራለህ?”
“አዎን እሰራለሁ”
ሴትዮዋ የሀብታም ሰው ሚስት ነበረች፡፡ ባሏ በድንገት ሲሞትባት ከባሏ በወረሰችው ገንዘብ እየነገደችና እያስነገደች ትኖር ነበር፡፡ በመሆኑም ለማኙን ሰውዬ ከሌሎች ተቀጣሪዎቿ ጋር እንዲሰራ ፈቀደችና ወደ ግቢዋ አስገባችው፡፡ ከዚያም የለበሰውን ቡትቶ እንዲያወልቅ በመንገር አዲስ ልብስ እንዲሰጠው አደረገች፡፡ የሚኖርበትም ቤት ተሰጠው፡፡ ቀለብም ተቆረጠለት፡፡ ሰውዬወም በሴትዮዋ ለጋስነት እየተገረመና ምስጋና እያቀረበ የተመደበለትን የሱቅ አሻሻጭነት ስራ መስራት ጀመረ፡፡
 ሰውዬው ከስራው ጋር በጥቂት ጊዜ ውስጥ ተለማመደ፡፡ በስራው ውስጥ ከሁሉም ሰራተኞች በላጭ ሆኖ ተገኘ፡፡ በታማኝነቱም የተመሰገነ ሆነ፡፡ ሴትዮዋ በሰውዬው ባተሌነትና በታማኝነቱ ልቧ ተነካ፡፡ እያደርም በፍቅሩ ተነደፈች፡፡ ብዙ አውጥታ ካወረደች በኋላም ልታገባው ወሰነች፡፡ እናም ለሰውዬው ይህንኑ ነገረችው፡፡
   ይሁንና ሰውዬው በሴትዮዋ አባባል አኮረፈ፡፡ “እኔ ከትቢያ ላይ የተነሳሁ አንድ ድሃ ሰው ነበርኩ፤ እንዴት ካንቺ ጋር በጋብቻ መተሳሰር እችላለሁ?” አላት፡፡ ሴትዮዋ ምክንያቱን ነገረችው፡፡ ከብዙ ክርክር በኋላ ሰውዬው ሊያገባት ወሰነ፡፡ በመሆኑም ድል ያለ ድግስ ተደግሶ ያ የጥንት ለማኝ የቤቱ አባወራ ለመሆን በቃ፡፡
ሰውዬው አባወራ ከሆነ በኋላም ኃላፊነቱን በትጋት መወጣቱን ቀጠለ፡፡ ሴትዮዋም ይበልጥ እያፈቀረችው ሄደች፡፡ “ይሄ ሰውዬ ለምንጊዜውም የሚከዳኝ አይመስለኝም፤ ስለዚህ የስራውን ኃላፊነት በሙሉ ለርሱ ልስጠው፤ ትንሽ ቆይቼ ደግሞ ድርጅቱን በርሱ ስም አዛውራለሁ” በማለት ወሰነች፡፡ ከዚያም ሰውዬውን ጠራችና እንዲህ አለችው፡፡
“እስከዛሬ ድረስ እንደ ሰራተኛም እንደ ባልም ሆነህ ጥሩ ጊዜ ከኔ ጋር አሳልፈሃል፤ ባሳየኸኝ ታማኝትና በሰጠኸኝ ፍቅር ሙሉ ደስተኛ ነኝ፡፡ ስለዚህ ከዛሬ ጀምሮ የድርጅቱ ሃላፊም ሆነ ተቆጣጣሪ አንተ ነህ፤ ካንተ በላይ ማንም የለም፤ እኔ ራሴ በአንተ ስር ነኝ” አለችው፡፡ይህንን ካለችው በኋላ የድርጅቱን አስፈላጊ ሰነዶች አስረከበችው፡፡ በቤቷ የሚገኙ የካዝና ቁልፎችንም ስታስረክበው እንዲህ አለችው፡፡
  “እኝሁልህ የካዝናዎቻችን መቆለፊያዎች! ከዛሬ ጀምሮ ባንተ ኃላፊነት ስር ሆነዋል፤ ወርቁም ሆነ አልማዙ በብዛት አለልህ፤ ነገር ግን የአንዱን ካዝና ቁልፍ አልሰጥህም፤ በዚያ ውስጥ ምን እንዳለ እንድትጠይቀኝም አልፈቅድልህም፤ እርሱን የጠየቅከኝ እለት መቆራረጣችንን እወቅ”፡፡ ሰውዬውም ስለጉዳዩ ምንም ነገር ላይጠይቃት ቃሉን ሰጣት፡፡ በመሃላ ጭምር አረጋገጠላት፡፡
    ባልና ሚስቱ እንዲህ ከተግባቡ በኋላ ኑሮአቸው ደራ፡፡ ትዳራቸው ይበልጥ ተሟሟቀ፡፡ ድርጅታቸው በትርፍ ላይ ትርፍ መዛቁን ቀጠለ፡፡ ሰውዬውም ምንም ተቆጣጣሪ ሳይኖረው ገንዘቡን እንዳሻው ያወጣ ጀመር፡፡ እያደር ግን የሰውዬው ልብ መቀየር ጀመረች፡፡ በአንድ ካዝና እና በውስጠ ሚስጥሩ ላይ ጥያቄ እንዳያቀርብ የተጣለበትን እግድ ሲያስታውስ ገና የሀብት ጣሪያ ላይ ያልደረሰ ሆኖ ተሰማው፡፡ ያንን ካዝና ከፍቶ አለማየቱም ያንገበግበው ጀመር፡፡ ሴትዮዋ አንዱን ካዝና ነጥላ በማስቀመጧም “እወድሃለሁ የምትለው ከልቧ አይደለም” በማለት ወቀሳት፡፡ በመሆኑም ካዝናውን ከፍቶ ለማየት ተመኘ፡፡ ወደሴትዮዋ ሄዶም ጥያቄውን አቀረበ፡፡
   
  ሴትዮዋ በጥያቄው ተደናገጠች፡፡ ተገረመችም፡፡ ቃሌን ያከብራል ብላ የገመተችው ሰው ቃል አባይ ሆኖ በመገኘቱ ተናደደችበት፡፡ ነገር ግን ከሰውዬው ፍቅር ስለያዛት የመጨረሻ እድል ልትሰጠውና ከመንገዱ ልትመልሰው ወሰነች፡፡ እንዲህም አለችው፡፡
   “አረ አንተ ሰው የፈጠረህን ፍራ! ስለዚህ ካዝና ጉዳይ አንድም ጥያቄ ላትጠይቀኝ ቃል ኪዳን ሰጥተህኛል እኮ፤ እባክህ ይህንን ጥያቄህን ተውና በሰላም አብረን እንኑር”
“አንቺ ራስሽ እወድሃለሁ የምትይው ከልብሽ አይደለም፤ ያንን ካዝና ከፍተሸ ከውስጡ ያለውን ነገር ካላሳየሽኝ አትወጂኝም ማለት ነው”
“አረ አንተ ሰው መሀላ አታፍርስ! እረፍልኝ ብዬሃለሁ”
“የካዝናውን ቁልፍ እንድትሰጭኝ እፈልጋለሁ”
ሴትዮዋ ተናደደች፤ ነገር ግን ሰውዬውን ስለምትወደው በሽማግሌ ልታመስክረው ሞከረች፡፡ ሽማግሌዎችም “መሃላህን አትብላ! የፈጣሪ ቁጣ ይወርድብሃል፤ እንደ ድሮው በሰላም ብትኖሩ ይሻላል” አሉት፡፡ ሰውዬው ግን “ካዝናው ካልተከፈተ ሞቼ እገኛለሁ” በማለት ሙግቱን አፋፍሞ ቀጠለ፡፡ ሴትዮዋም በነገሩ ተስፋ ቆረጠች፡፡ ሰውዬው ወደ ኋላ የማይመለስ መሆኑን ካረጋገጠች በኋላ የከተማዋ ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አደረገች፡፡ ከዚያም ካዝናውን ከፈተችውና ከውስጡ ያለውን እቃ አወጣች፡፡ በሀይለ ቃልና በቁጭት በሰውዬው ፊት ላይ ወረወረችው፡፡
———-
ከካዝናው ውስጥ የተገኘው እቃ ሰውዬው ከሀገሩ የመጣበት ቡትቶ ልብስ እንጂ እንቁ ወይንም ሌላ የከበረ ጌጣጌጥ አልነበረም፡፡ ሴትዮዋ ለክፉ ቀን መጠባበቂያ እንዲሆናት ነው ከካዝና ውስጥ የቆለፈችበት፡፡ እውነተኛው ቀን ሲደርስ ልብሱን እዚያ ማስቀመጧ ትክክል እንደሆነ ተረዳች፡፡ ልብሱን በሰውዬው ፊት ላይ ከወረወረችለት በኋላም እንዲህ አለችው፡፡
“አንተ ውለታ ቢስ! ቶሎ ብለህ የኔን ልብስ አውልቅ! አንተ ያመጣኸውን ልብስ ልበስና ከዚህ ቤት ጥርግ ብለህ ጥፋልኝ”
ሰውዬው በድንጋጤ ክው ብሎ ቀረ፡፡ ከትቢያ ተነስቶ በተከበረበት ከተማ መዋረዱ ከፍተኛ እፍረት ውስጥ ጣለው፡፡ በመሆኑም ከከተማዋ በደረቅ ሌሊት ጠፋ፡፡ ወደ ሀገሩ ሊመለስም ጉዞውን ተያያዘው፡፡ ረጅም ርቀት ከተጓዘ በኋላ በቀቀኗን ካገኘበት ቦታ አረፈ፡፡
  ታዲያ በቀቀኗ “ጥጋብ አይቻልም” እያለች የድሮውን መዝሙር መዘመሯን እንደቀጠለች ነው፡፡ ሰውዬውም “እውነትሽን ነው! ጥጋብን ከእግር እስከ ራሱ አይቼው የማልችለው ዐይነት ሲሆንብኝ ወደ ድሮው የድህነት ህይወቴ እየተመለስኩ ነው” አላትና የመዝሙሩን ሐቀኛነት አረጋገጠላት፡፡
———–
አይጣል ነው መቼስ! በርግጥም ጥጋብ አይቻልም፡፡ በእውነታው ዓለም የተከሰቱ በርካታ ታሪኮችን ከዚህ ጋር ማነጻጻር ይቻላል፡፡ ሀብትን ስናገኝ  አዕምሮአችን ከርሱ ጋር ካላደገ የሰራነው ሁሉ ወደ ዜሮ ሊመልስብን ይችላል፡፡ ለሁሉም ግን ፈጣሪያችን ከእንዲህ ዓይነቱ ክፉ እጣ ይሰውረን!
አሚን!
——
መጋቢት 19/ 2006
አፈንዲ ሙተቂ
(ተረቱን ያጫወቱኝ የገለምሶ ትልቁ መስጊድ ኢማም የሆኑት ሼኽ ሙኽታር አሊይ ናቸው፤ ዘመኑም እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር 1988 ነበር፤ ሼኽ ሙኽታር በአሁኑ ጊዜ የ85 ዓመት አዛውንት ናቸው፤ አላህ ጤናውንና ብርታቱን ይጨምርላቸው)፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት “ኢሕገ-መንግስታዊ” ያለውን ድርጊት ፈጽሟል፤ ሲል ለወነጀለው ተቃዋሚው የሰማያዊ ፓርቲን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ጽፏል።

ሰማያዊ ፓርቲና አጋሮቹ በበኩላቸው ማስፈራራትና አፈና የዴሞክራሲ ጥያቄዎችንና ሰላማዊ ሕዝባዊ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን አይቀለብሱም፤ ሲሉ የተቃውሞ መግለጫ አውጥተዋል።

የዘገባውን ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ፤

 

 

የምሥራቅ አፍሪቃ አገሮች በስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ላይ የጋራ ራእይና እቅድ እንዲኖራቸው ለማስቻል የታለመ የሁለት ቀናት ውይይት አዲስ አበባ ላይ ተጀምሯል።

የስደተኞች አንዷ መዳረሻ በሆነችው የወቅቱ የአውሮፓ ሕብረት ፕሬዝዳንት ጣልያን አነሳሽነት የሚካሄደው ይህ ውይይት በአጭርና ረዥም ጊዜ የሚተገበሩ ግቦች ያመነጫል፤ ተብሎ ተጠብቋል።

በሌላ በኩል የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳሳት አቡነ ፍራንሲስ ትላንት ስትራስበርግ ፈረንሳይ ለሚገኙት የአዉሮፓ ፓርላማና ምክር ቤት ንግግር ስለ ስደተኞች ሰብአዊ መብትና መከበር ንግግር አድርገዋል።

ርእስ ሊቃነ-ጳጳሱ በሁለቱም ስፍራዎች ባደረጉት ንግግር አዉሮፓ የቆመችለትን ሰብአዊ መብትን የማክበር መርህና ዴሞክራዊ እንድታከብር ጥሪ አድርገዋል።

የሮማው ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳስ በ25 ዓመታት ውስጥ…

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር መግቢያ ላይ ማይክል ብራውን የተባለው አንዳች የመከላከያ መሣሪያ ያልያዘ የ 18 ዓመት ወጣት ፣ዳረን ዊልሰን የተሰኘው ነጭ ፖሊስ በተደጋጋሚ ጥይት ተኩሶ መግደሉ ብዙ የተባለለት ጉዳይ ነው።

አውሮጳ ለዜጎቿ ዋስትና ልትሰጥ ብሎም ዕድል ልታመቻች ይገባል፥ ለእዚያም አዲስ አንቀሳቃሽ ኃይል ያሻታል ሲሉ የካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን ርእሰ-ሊቃነ-ጳጳሳት ፍራንሲስ በአውሮጳ ምክር ቤት ተናግረዋል። የፍራንሲስን ንግግር የምክር ቤቱ አባላት ያጤኑት ይኾን?

ምግብ ማግኘት ፍጹም መሠረታዊ ሰብአዊ መብት ነው፤ መብቱን የሚገነዘብለት ፣ መብቱን የሚያከብርለት –ኖረም -አልኖረ! የገንዘብ አቅም ላለው ደግሞ፣ በኢንተርኔት አገልግሎት መሥመር መጠቀምም መሠረታዊ ሰብአዊ መብት ነው። ይህ አገልግሎት ፍጹም

በሊቢያ የባህር ዳርቻ ከተማ ዴርና በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ራሱን « እስላማዊ መንግሥት» አይሲስ ብሎ የሚጠራውን የሙስሊም አክራሪ ቡድን መቀላቀላቸው ተሰምቷል። ተንታኞች ቡድኑ ሊቢያ ውስጥም ተዋጊዎችን ሊመለምል ይችላል የሚል ስጋት አላቸው።

ኀዳር ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ትብብሩ ባወጣው መግለጫ ህዳር 21 ለሚደረገው ስብሰባ ለመስተዳድሩ የሰለማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ደብዳቤ ቢላክለትም ለመቀበል ፈቃደኛ ካለመሆኑም በተጨማሪ፣ ስብሰባውን የሚያስተባብሩት የመኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ ገንዘብ ያዥ የሆኑት አቶ ኑሪ ሙደሲር ላይ የድብደባ ወንጀል እንደተፈጸመባቸው ገልጿል።‹‹ነጻነታችን በእጃችን›› ነው የሚለው ትብብሩ፣  በኢህገመንግሥታዊና ኢዲሞክራሲያዊ እርምጃዎች ወደኋላ እቅዱን በህጋዊ መንገድ …

ኀዳር ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስት የጀመራቸውን የሃይል፣ የመንገድ፣ የባቡርና የስኳር ፋብሪካዎችን ለመጨረስ የሚያስችለውን ገንዘብ ከአለማቀፍ አበዳሪ ድርጅቶች ለመበደር የሚያስችለውን ድርድር ከሁለት የአውሮፓ እና ከአንድ የአሜሪካ ባንክ ጋር ጀምሯል። መንግስት ገንዘቡን ለመበደር የሚያስችለውን ቦንድ ለገበያ የሚያቀርብ ሲሆን፣ አለማቀፍ አበዳሪ ተቋማትም የመንግስትን የመክፈል አቅም በማየት ብድሩን ይፈቅዳሉ። መንግስት ከአለማቀፍ የግል አበዳሪ ድርጅቶች …

ኀዳር ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዲስ አበባ የኢህአዴግ ጽ/ቤት ለከተማ አስተዳደሩ ከላከው ቅጽ ለመረዳት እንደሚቻለው ፓርቲው በአዲስ አበባና ኦሮምያ የተቀናጀ የከተማ እቅድ ዙሪያ በመንግስት ሰራተኛው ውስጥ ያለውን የአመለካከት ክፍተት ለመሙላት ስልጠና ይዘጋጃል። ፓርቲው የተለያዩ ቅጾችን ለሰራተኛው በመበተን ሰራተኛው እስካሁን ስለነበሩት ክንውኖችና ድክመቶች አስተያየቱን እንዲጽፍ ተጠይቋል። እጅግ አወዛጋቢ ሆኖ ተቃውሞ ያስነሳውንና በርካታ …

ኀዳር ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስአበባ ከተማ የተጋነነ የትምህርት ቤት ክፍያ ዋጋ በመጨመር ህብረተሰቡን ለአላስፈላጊ ወጪ ዳርገዋል በተባሉ 130 የግል ትምህርት ቤቶች ላይ ክስ መመስረቱን የአዲስአበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን እና የግል ትምህርት ቤቶች ማህበር በጋራ ያጠኑትና በሐምሌ ወር 2006 ዓ.ም ይፋ የተደረገ አንድ ጥናት እንደሚያሳየው በአዲስአበባ …

ኀዳር ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የክልሉ ካቢኔ የከተማዋ ነዋሪዎች ጭማሪው እንዲከፍሉ የወሰነው ለከተማው ውሃ ለመዘርጋት ከፍተኛ ገንዘብ ማውጣቱን በመግለጽ ነው። የክልሉ የውሃ ሀብት ም/ል ሃላፊ ለክልሉ ካቢኔ እንደገለጹት ለከተማዋ የውሃ መስመር ዝርግታ 6 ሚሊዮን 300 መቶ ሺ ብር ለማስፋፊያ ስራ ደግሞ 60 ሚሊዮን ብር በመውጣቱ፣ አጠቃላይ ወጪውን ለማስመለስ ተጠቃሚው ህብረተሰብና የንግድ …

ኀዳር ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዊ ዞን አንከሻ ወረዳ ውስጥ የሚማሩ የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች የኢህአዴግን የአባልነት መሙያ ፎርም ወስደው እንዲመዘገቡ በርእሰ መምህራቸው አማካኝነት ቢጠየቁም፣ ከ700 ያላነሱ ተማሪዎች ድርጊቱን ተቃውመዋል። ተማሪዎቹ የአባልነት ቅጹን በሁለት ቀናት ውስጥ የማይሞሉ ከሆነ ከትምህርት ቤት እንደሚባረሩና ለፈተናም እንደማይቀርቡ ተነግሯቸዋል። “ከእንግዲህ ኢህአዴግ የሚባል ነገር ማየት አንፈልግም” ያሉት ተማሪዎች …

ኀዳር ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል የደቡብ ወሎና የሰሜን ሸዋ ዞን ወረዳዎችና አብያተክርስቲያናት ተገቢ ጥበቃ ባለማግኘታቸው የተለያዩ ቅርሶች የተዘረፉና የጠፉ መሆኑን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ በአመት አንድ ጊዜ በሚዘጋጀው የቅርስ ጉባኤ ላይ ገለጸ፡፡ በሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ በተለያዩ ወረዳዎች 37 ቅርሶች መሰረቃቸውን ይፋ ያደረጉት የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ አቶ አለበል …

ኀዳር ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በእየአመቱ ህዳር 29 ቀን የሚከበረው የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ለማክበር መንግስት እስከ 300 ሚሊዮን ብር እንደሚያወጣ መረጃዎች አመለከቱ። ለኢሳት የደረሱ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ዝግጅቱን ከማቀድ ጀምሮ የተለያዩ ስራዎችን የሚፈጽሙት ከህወሃት ባለስልጣናት ጋር ግንኙነት ያላቸው ድርጅቶች ናቸው። በኢትዮጵያ የሚከበሩ በአላትን እነዚህ ተቋማት ያለተቀናቃኝ በመውሰድ እየበለጸጉበት መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ። ኢህአዴግ ካወጣው …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

መቀመጫውን ጀርመን ያደረገው የ«አልፋ-ቤትኢትዮጵያ»ማሕበርበተለይ በኢትዮጵያ በጉራጌ ዞን ያንበሊ አካባቢ ታዳሽ የሀይል ምንጭ ለአካባቢው ነዋሪዎች በማቅረብ ይንቀሳቀሳል። ይኼው ማህበር ከሁለት ሳምንታት በፊት ባዘጋጀው ስብሰባ የንጹህ ውሀ አቅርቦት እና የዕውቀት ሽግግር ቀጣዩ አላማው እንደሆነ አስታውቋል።

አልሸባብ በማንዴራ ከተማ 28 ሰዎችን ከገደለ በኋላ የኬንያ መንግስት የወሰደው የበቀል እርምጃ ለትችትና ወቀሳ አግልጦታል።የኬንያ መንግስት ችግሩን ለማስወገድ የጸጥታ ተቋማትን እንዲያጠናክርም የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እያሳሰቡ ነዉ።

ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ የፍርድ ሸንጎ ያልታጠቀ ጥቁር ታዳጊ ወጣትን በመግደል የተጠረጠረዉን ነጭ ፖሊስ ከመከሰስ ነፃ ማድረጉ በፈርጉሰን ሚዙሪ ግዛት የከፋ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ እንዲያገረሽ ማድረጉ ተነገረ።

ሌተና ኮሎኔል ያኩባ ኢሳክ ዚዳ የወታደር የደንብ ልብሳቸውን አውልቀዋል። ትናንት በተካሄደው የቡርኪና ፋሶ የሽግግር መንግሥት የመጀመርያዉን የካቢኔ ስብሰባ በጠቅላይ ሚኒስትርነት መርተዋል። ስብሰባው ከተከፈተ ከአንድ ሰዓት በኋላም ዚዳ « በርካታ ለውጦችን» ለሀገራቸው አውጀዋል።

“የአክሰስ ሪል ኢስቴት” ቤት ገዢዎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ቤታቸዉን ወይም ገንዘባቸውን የሚያገኙበትን እቅድ ማዉጣቱን የኢትዮጵያ መንግስት ያቋቋመው አንድ ኮሚቴ አስታወቀ።

ከ2005 ዓም አንስቶ ቤታቸዉን መረከብ የነረባቸውና ይህ ባለመሆኑ ቅሬታ ሲያቀርቡ የነበሩ ወደ 2000 የሚጠጉ ቤት ገዢዎች ጥያቄ በዚህ እቅድ ምላሽ ያገኛል፤ የሚል ተስፋ ተሰጥቷል።

“የአክሰስ ሪል ኢስቴት” በሚል መጠሪያ በሚታወቀው በዚህ የቤቶች ሻጭ ድርጅት የተከሰተውን ይህን ሁኔታ መነሻ በማድረግ መንግስት በአጠቃላይ በዘርፉ “አለ” ያለዉን ችግር ለመፍታት እንደሚሰራ የንግድ ሚኒስቴር አማካሪና መንግስት ያቋቋመው የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ አስታውቀዋል።

በቅርቡ በወጣት ሃና ላላንጎ ላይ የተፈጠረዉ አሰቃቂ በቡድን የመድፈር ወንጀል ኢትዮጵያውያንን በእጅጉ ያሳዘነና ከፍተኛ ድንጋጤ መፍጠሩ፤ የሴቶችና የህጻናት ደህንነትንም የበረታ ስጋት ማሳደሩ ተገለጸ።

በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን ለመከላከል የሚሠራ ልዩ ግብረ ሃይል በጠቅላይ ሚንስትሩ ጽህፈት ቤት ስር እንዲደራጅ መጠየቁ ተዘግቧል።

የዘገባውን ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ፤

 

 

የ United States ፕረዚዳንት ባራክ ኦባማ ባለፈው ሐሙስ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ የመኖርያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገር ተወላጆችን ህይወት ሊለውጥ የሚችል የ United States ን የኢሚግሬሽን ፖሊሲን የሚቀይር ውሳኔ እንደሚወስዱ ማስታወቃቸው ይታወሳል። አቶ ተመስገን ተካ የኢሞግረሽን ህግ ባለሙያ ያብራራስሉ።