ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በአፍሪቃ ሀገራት የመሠረት ልማት ፕሮዤ ለማነቃቃት በሚታሰብበት ጊዜ ሁሉም የሚያስበው ስለ ቻይና ነው። ቻይና እአአ በ1960 ኛዎቹ ዓመታት በሶሻሊስታዊው ፕሮዤ አማካኝነት ከዛምቢያ እስከ ታንዛንያ የሚዘልቅ የባቡር ሀዲድ ግንባታን በገንዘቧ መርዳቷ ይታወሳል።

ዘላለማችንን የፖለቲካ የበታችነት የተጠናወተን ጥገኞች ሆነናል:: በባህር ዳር ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እየተካሄደ ያለው የብአዴን ካድሬዎች እና የለውጥ ሃዋርያ ብሎ ራሱን የሚጠራው የወጣት አባላት ቡድን በድርጅቱ ውስጥ ያገረሸውን የለውጥ ጥያቄ ተከትሎ በብኣዴን ውስጥ እየተነሳ ስላለው የፖለቲካ መብት ጥያቄ በሰፊው ውይይት የተደረገበት ሲሆን ብአዴን የኢሕኣዴግን መርሆ እንደጠበቀ ከሌሎች ድርጅቶች የበላይነት እና ጥገኝነት መላቀቅ አለበት በሚሉ እና ወደ […]

ብሔራዊ እርቅ (National Reconciliation) በተለይ በእርስ በእርስ ግጭት ደም የተቃባንና የከፋ አደጋ የተጋረጠበትን ኅብረተሰብ ወይም የመበታተን አደጋ የተጋረጠባትን ሀገር በይቅር ለእግዚአብሔር ይቅር አባብሎ ሰላም ለማውረድና የቂም በቀልን ዶሴ ዘግቶ በአዲስ መንፈስ ብሔራዊ መግባባትን (National Consensus) ፈጥሮ የአንዲት ሀገርን ሕዝብ በአንድነት አስተባብሮ ለማንቀሳቀስና ህልውናውን ከመረጋጋቱ ጋራ ለማስቀጠል ዓይነተኛ መንገድ ነው፡፡ በሕወሀት ኢሕአዴግ የአገዛዝ ዘመን የዚህ የብሔራዊ […]

ከክፍል አንድ የቀጠለ እሁድ (ሐምሌ 1 ቀን 2004 ዓ.ም) በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ጽ/ቤት ውስጥ የ“አዲሱ ትውልድ ተልዕኮ” በሚል ርዕስ ወጣት ሀብታሙ አያሌውን ገብዘዉት ነበር፡፡ ሀብታሙን በአካል ያየሁት ያኔ ነበር፡፡ ከሀብታሙ ጋር በደንብ የተዋወቅነው ከዚህ ዘገባ በኀላ ነበር፡፡ ሀብታሙን ስሞኑን ሳስታውስው፣ ያኔ በስንደቅ ጋዜጣ ላይ የዘገብኩትን መለስ ብየ አየሁ። እስቲ በጋራ እናነብው ፡፡ ክፍል […]

እሁድ (ሐምሌ 1 ቀን 2004 ዓ.ም) በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ጽ/ቤት ውስጥ የ“አዲሱ ትውልድ ተልዕኮ” በሚል ርዕስ ወጣት ሀብታሙ አያሌውን ገብዘዉት ነበር፡፡ ሀብታሙን በአካል ያየሁት ያኔ ነበር፡፡ ከሀብታሙ ጋር በደንብ የተዋወቅነው ከዚህ ዘገባ በኀላ ነበር፡፡ ሀብታሙን ስሞኑን ሳስታውስው፣ ያኔ በስንደቅ ጋዜጣ ላይ የዘገብኩትን መለስ ብየ አየሁ። እስቲ በጋራ እናነብው ፡፡ ክፍል 1 – የዛሬው […]

‹‹ከታሰርኩ ጀምሮ ከጠበቃዬ ጋር የተገናኘሁት አንድ ቀን ብቻ ነው›› አብርሃ ደስታ ‹‹ሕገ-ወጥ ሕጎች እየበዙ ነው፣ ማብቃት አለባቸው!›› ‹‹አንዱ በሀገርህ ላይ የመኖርህ መገለጫ ሳትሰጋህ መኖር ነው፤ ሌላ ሀገር ያለ ይመስል አልሰጋም›› ጠበቃ ተማም አባቡልጉ *****አብርሃ ደስታን በተመለከተ፣ ከጠበቃ ተማም አባቡልጉ ጋር ያደረኩት ቃለ-ምልልስ**** በዛሬው ዕለት አብርሃ ደስታ ጊዮርጊስ በሚገኘው የአራዳ ፍርድ ቤት ቀርቦ የ28 ቀናት የጊዜ […]

እንደሰማሁት ከሆነ ጥቁር ሳምንት በሚል የተጀመረው ዘመቻ ጥሩ ዘመቻ ነው፡፡ በማህራዊ ሚዲያው ሲንቀሳቀሱ የነበሩትም ሆነ ጋዜጠኞች በመታሰራቸው እንቅስቃሴው አለመዳከሙ ያስደስታል፡፡ መጭው ዘመን የነጻነት ይሆን ዘንድ ኢትዮጵያውያን ይህን የመሰሉ እንቅስቃሴዎችን መደገፍ፣ ማበረታታትና መቀላቀል አለባቸው፡፡ በተለይ በአሁኑ ዘመን ማህበራዊ ሚዲያው ትልቅ ለውጥ እያመጣ ነው፡፡ በግብጽና ቱኒዚያ ማህበራዊ ሚዲያው ቀላል የማይባል ለውጥ አምጥቷል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጋዜጠኛ አንተነህ መርዕድ

ህወሃት በሻዕብያ ታዝሎ* ምኒልክ ቤተመንግስት ከገባና ኦነግንም ሆነ ሌሎቹን ጠፍጥፎ የሰራቸውን መናኛ ድርጅቶች እንኳ ሳያስቀርብ በብቻው የተያያዘው ዘረፋ፣ ሁሉን ለእኔ ብቻ ያለ ሂደቱ ያላስደነገጠው ኢትዮጵያዊ አልነበረም። ያለፉትን ስርዓቶች የተሻገሩ ሁለት አንጋፋ ጓደኛም ጋዜጠኞች ሲጨዋወቱ በቦታው ነበርሁ። አንደኛው ወያኔ ነፃ አወጣዋለሁ ከሚለው ከኩሩው ኢትዮጵያዊ ከትግራይ ህዝብ አብራክ የተገኘ ነበርና “ወንድሜ ይሉኝታ በትግርኛ ምንድን ነው የሚባለው?” ሲል ጠየቀው። “ይሉኝታ..ይሉኝታ…” እያለ ቃሉን ማፈላለግ ሲጀምርና ፈጥኖም ቃሉን ማግኘት ሲሳነው “ተወው ወንድሜ የሌለውን ነው የጠየቅሁህ ቃሉ ከሌለ ወያኔዎች ከየት ይማሩታል ብዬ ልጠብቅ” በማለት ሁላችንንም አሳቀን።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

‹‹እኛታስረንም፣በኢትዮጵያጋዜጠኝነትእናጋዜጠኞችላይየሆነውነገርእጅግቅስምይሰብራል ( It’s really heart breaking!)››
ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ
‹‹እስርደግምነገርነው›› ጋዜጠኛ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ
‹‹የነጻነትትግልላይእንዳለሁያወኩትእስርቤትነው›› ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ
‹‹መጽሔቶችመታተምመቆማቸውያሳዝናል፡፡አማራጩምንይሆን?››
አህመዲን ጀበል (የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል) 

ከትናንት በስትያ፣ ሰኞ ነሐሴ 26 ቀን 2006 ዓ.ም በጣም የናፈቁኝን ታሳሪ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን ለመጠየቅ በማቀድ፣ ረፋድ ላይ ወደቂሊንጦ እስር ቤት አመራሁ። በቃሊቲ ወህኒ ቤት ዋና በር ጋር በታክሲ ሳልፍ፣ ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ እና ኤዶምን ካሳዬ፣ ጦማሪ ማህሌት ፋንታሁንን፣ አቶ አንዷለም አራጌን፣ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና ሌሎች የማውቃቸውን እስረኞች በሀሳቤ መጥተው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመላው አውሮፓ የተሰባሰቡ ኢትዮጵያውያን የተገኙበት ይህ የተቃውሞ ሰልፍ እጅግ ደማቅ መሆኑን ወንድማገኝ ጋሹ በስልክ ገልጿል። የግንቦት7 ዋና ጸሃፊ  በየመን የጸጥታ ሃይሎች ተይዘው  ተላልፈው ከተሰጡበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት ሰብአዊ መብታቸውን በመግፈፍ በኢትዮጵያውያን እንዳይጎበኙ ከልክሏል። አብዛኛውን ስራቸውን እንዳጠናቀቁ በተደጋጋሚ ሲናገሩ የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ወደተለያዩ ቦታዎች በሌሊት እየተዘዋወሩ ምርምራ እየተደረገባቸው መሆኑን …

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ በተለያዩ ሊጎች ወይም ፎረሞች ለሰበሰባቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚሰጠው የፖለቲካ ስልጠና ባልጠበቀው አቅጣጫ እየሄደበት መሆኑን ተከትሎ ሰዎችን ከመከፋፈል ጀምሮ እስከ ማባረር መድረሱን ምንጮች ገልጹ። በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የመሰብሰቢያ ቦታዎች በሚደረጉት ስልጠናዎች ላይ ለገዢው ፓርቲ ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን የሚያቀርቡ ወጣቶች እና የፖለቲካ ንቃት አላቸው የሚባሉ ነዋሪዎች ፣ ከቀሪ …

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለገጣፎ ውስጥ በሶስት ጎጦች የሚኖሩ ዜጎች በ10 ቀን ውስጥ ቤታቸውን እንዲያፈርሱ መታዘዛቸውን ጋዜጣው የትእዛዝ ወረቀቱን በማያያዝ ያሰፈረው ዜና ያማለክታል፡፡ጎራጎጭ፣ዳሌናድሬበተባሉትሶስትጎጦችእስከ 23 ሺህህዝብእንደሚኖርባቸው ነዋሪዎቹ ለጋዜጣው ዘጋቢ ተናግረዋል። “የሰንዳፋወረዳሰራተኛናማህበራዊጉዳይጽ/ቤት ማህተም አስቀርጾ የመረዳጃ እድር ማቋቋሙን፣ ለመብራትኃይልአንድሚሊዮንያህልገንዘብከፍለውትራንስፎርመርለማስተከልእየተጠባበቁመሆናቸውንና፣የውሃናሌሎችተቋማት ህጋዊለሆነአካልየሚሰጡትንአገልግሎትከፍለውእያገኙእንደቆዩበመግለጽየሚኖሩበትአካባቢህገወጥአለመሆኑንበመግለጽ እየተከራከሩ ቆይተዋል። እንደጋዜጣው ዘገባ  ነሃሴ 26 ተጻፈየተባለናከፊንፊኔልዩዙሪያ  በረህወረዳ   የመሬትአስተዳደርጽ/ቤትእንደሆነ የሚገልጽፊርማየሌለውደብዳቤ  ማምነታቸው በውል ያልተለየ ሰዎች ነሃሴ 30 …

የኤቦላ ተሕዋሲ ሥርጭትን ለመግታትም ሆነ ለበሽታ የተጋለጡ ሠዎችን ለመርዳት መንግሥታት ተገቢዉን ጥረት አለማድረጋቸዉን ግብረ-ሠናይ ድርጅቶች አጋለጡ።ድንበር የለሽ ሐኪሞች፤ የአለም ጤና ድርጅትና ሌሎች ድርጅቶች በየፊናቸዉ እንዳሉት የኤቦላን «አደጋ» ለማስወገድ ከተገባዉ ቃል አብዛኛዉ ገቢር አልሆነም።

በልጅነት ወቅት ሳድግ ሀኪም፣ የአይሮፕላን አብራሪ፣ ጠበቃ፣ ሌላም ሌላም እሆናለሁ እያሉ የተለያዩ የሙያ መስኮችን መጥራት የተለመደ ነው። ታድያ የወጣትነት ጊዜ ሲደርስ ለዚህ መሰረት የሆነውን የትምህርት ዘርፍ ለመከታተል ወይም ጨርሶ በሌላ መስክ ለመሰማራት እንወስናለን።

የናኘዉን ፅንፈኛ ቡድንን የእሥልምና ሐይማኖት መሪዎች ሲቃወሙ፤ እርምጃዎቹን ሲያወግዙ የብሪታኒያ ሙስሊም መሪዎች የመጀመሪያዎቹ አይደሉም።የግብፁ ዓል-አዝሐር ዩኒቨኒርስቲ መሪዎች ISISን አዉግዘዉ ነበር።ከግብፆች በፊት የሳዑዲ አረቢያ የሐያማኖት አባቶችም ቡድኑን አዉግዘዉት ነበር።

ኢትዮጵያና ጀርመን የሁለትዮሽ ትብብር ዉል ተፈራረሙ። ትናንት የገንዘብ እና የኤኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴታ አቶ አህመድ ሽዴ እና የፌደራል ሪፑብሊክ ጀርመን የኤኮኖሚና ልማት ምክትል ሚኒስትር ቶማስ ዚልበርሆርን ለሁለቱ ሃገራት የተፈራረሙት የትብብር ዉል ከጎርጎሪዮሳዊዉ 2015 እስከ 2018ዓ,ም የሚዘልቅ ነዉ።

ኢትዮጵያዊዉ የአፈር ሳይንስ ባለሙያና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ተካልኝ ማሞ የኖርዌይን ዓለም ዓቀፍ ሽልማት ተቀበሉ። ሽልማት ሰጪዉ ተቋም በድረገፁ ላይ ባሰፈረዉ መረጃ መሠረት ተሸላሚዉ ፕሮፌሰር ተካልኝ የተማሩትን ትምህርት ከአካዳሚ ሚናዉ ባለፈ ለኅብረተሰብ ትልቅ ጥቅም ለሚያስገኝ ዉጤት ማዋሉ ተሳክቶላቸዋል።

ካለፈው ሰኞ አንስቶ በአልጀሪያ መዲና በአልጀርስ፤ በማሊ መንግሥትና በሰሜናዊው የአገሪቱ ክፍል በሚንቀሳቀሰው የቱዓሬጎች አማጺ ኃይል ለውዝግቡ መላ ለመሻት ሲካሄድ የሰነበተው ድርድር ሳንክ አጋጥሞታል። ድርድሩ 8 ሳምንታት እንደሚወስድ አስቀድሞ

አገር ውስጥ በሰላም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች አመራር አባላት ናቸው። አብርሃ ደስታ ከአረና፣ ዳንኤል ሺበሺና ሃብታሙ አያሌው ከአንድነት፣ የሺዋስ አሰፋ ከሰማያዊ። ሐምሌ 1 ቀን 2006 ሽብርተኞች ናችሁ ተብለው ተያዙ። ጠበቃዎቻቸው በሌሉበት በድብቅ ፍርድ ቤት ቀረቡ ተባለ። ፖሊስ ዜጎችን ከመያዙ በፊት በእጁ መረጃ ሊኖረው ሲገባ፣ መረጃ ለማሰባሰብ ጊዜ ያስፈልገኛል ብሎ ለ28 ቀናት ቀጠሮ ይጠይቃል። ፍርድ ቤቱ፣ ያለምንም ማቅማማት፣ […]

የመግቢያ ማስታወሻ

በጽሑፉ ውስጥ በግእዝ ቁጥሮች በቅንፍ ውስጥ የተጻፉት ሐሳቡን እንዲወክሉ ብቻ ነው፡፡ በኋላ (ቁጥር ፭ ተመልከት ቢል ያንን ሐሳብ መልሶ ለማየት እንዲረዳ ነው፡፡

የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ ጳጉሜ የምትባል አሥራ ሦስተኛ ወር ስላለችን ነው፡፡ የቤት ኪራይና የወር ደመወዝ የማንከፍልባትና የማንቀበልባት፤ መብራትና ውኃ ግን ከነሐሴ ወር ጋር ጨምረው የሚያስከፍሉባት፤ ሲሻት አምስት፣ ሲያስፈልጋት ስድስት፣ ስትፈልግ ደግሞ ሰባት የምትሆን ወር ናት፡፡ እንዲያውም ከአሥራ ሁለቱ የኢትዮጵያ ወሮች ጳጉሜ በብዙ መንገድ የተለየች ናት፡፡

በአንድ በኩል በጣም ትንሿ ወር ናት፡፡ ሲቀጥልም ወርኃዊ በዓላት የማይውሉባት ወር ናት፡፡ እንዲያም ሲል ደግሞ ከሌሎች ወሮች በተለየ የቀኖቿ መጠን የሚቀያየሩ ብቸኛ ወር ናት፡፡ ከሌሎች የኢትዮጵያ ወሮች በተለየም ስሟ ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ወር ናት፡፡ በሁለት ዘመናት መካከልም እንደ መሸጋገሪያ የምትታይ ወርም ናት፡፡  

ጳጉሜ ማለት በግሪክ ‹ጭማሪ› ማለት ሲሆን ዓመቱን በሠላሳ ቀናት ስንከፍለው የሚተርፉትን ዕለታት ሰብስበው የሰየሟት ተጨማሪ ወር ናት፡፡ ወይም በየዕለቱ በፀሐይና በጨረቃ አቆጣጠር መካከል የሚፈጠረውን ልዩነት ሰብስበው ያከማቹባት ወር ትባላለች፡፡ ዓመቱ በዐውደ ፀሐይ ሲለካ 365 ቀናት ከ15 ኬክሮስ 6 ካልዒት ሲሆን በጨረቃ ሲለካ ደግሞ 354 ቀናት ከ22 ኬክሮስ፣ 1 ካልዒት፣ 36 ሣልሲት፣ 52 ራብዒት፣ 48 ኀምሲት ነው፡፡ (60 ኬክሮስ አንድ ቀን ነው)በሁለቱ መካከል(በፀሐይና በጨረቃ) በዓመት ውስጥ ያለው ልዩነት 11 ቀናት ከ7 ኬክሮስ ይሆናል፡፡ [በነገራችን ላይ በዘመን አቆጣጠራችን ውስጥ ከዕለት በታች የምንቆጥርባቸው ስድስት መለኪያዎች አሉ፡፡ ኬክሮስ፣ ካልዒት፣ ሣልሲት፣ ራብዒት፣ ኀምሲትና ሳድሲት፡፡ 60 ሳድሲት አንድ ኀምሲት፣ 60 ኀምሲት አንድ ራብዒት፣ 60 ራብዒት አንድ ሣልሲት፣ 60 ሳልሲት አንድ ካልዒት፣ 60 ካልዒት ደግሞ 1 ኬክሮስ ይሆናል፡፡ 60 ኬክሮስ ደግሞ 1 ዕለት፡፡ 1 ኬክሮስ 24 ደቂቃ ነው]

ጳጉሜን ለማግኘት የሚጠቅመን የየዕለቱን ልዩነታቸውን መመልከቱ ነው፡፡ በየዕለቱ በጨረቃና በፀሐይ መካከል 1 ኬክሮስ 52 ካልዒት(60 ካልዒት አንድ ኬክሮስ ነው)፣ ከ 31 ሣልሲት(60 ሣልሲት አንድ ካልዒት ነው) ይሆናል፡፡[ይህም ማለት 5 ሰዓት ከ48 ደቂቃ ከ46 ካልዒት(ሴኮንድ?)] ይህ ልዩነት በአንድ ወር ምን እንደሚደርስ ለማወቅ በ30 እናባዛው፡፡ 30 ኬክሮስ፣ 1560 ካልዒት፣ ከ930 ሣልሲት ይሆናል፡፡ የዓመቱን ለማግኘት ደግሞ በ12 እናባዛው፡፡ 360 ኬክሮስ(፩)፣ 18720 ካልዒት(፪)፣ 11160 ሣልሲት(፫) ይመጣል፡፡

ቀደም ብለን 60 ኬክሮስ አንድ ዕለት ይሆናል ባልነው መሠረት 360 ኬክሮስ ለ60 ሲካፈል 6 ዕለታትን ይሰጠናል(፩)፡፡ 18720 ካልዒትን(፪) በስድሳ በማካፈል 312 ኬክሮስን እናገኛለን፡፡ ያም ማለት ትርፉን 12 ኬክሮስ ትተን 300ውን ኬክሮስ ለ60 በማካፈል 5 ዕለት እናገኛለን፡፡ ይኼም ማለት 5 ዕለት ከ12 ኬክሮስ(፬) ይሆናል፡፡ 11160 ሣልሲትን(፫)ለ60 ብናካፍለው 186 ካልዒት ወይም ደግሞ 3 ኬክሮስና 6 ካልዒት(፭) ይሆናል ማለት ነው፡፡

ከላይ ኬክሮስን በዓመቱ ቀናት አባዝተን ያገኘነው(፩) 6 ዕለት አለ፡፡ ይኼ ዕለት ሕጸጽ ይባላል፡፡ ፀሐይና ጨረቃን እኩል መስከረም አንድ ላይ ዓመቱን ብናስጀምራቸው ፀሐይ የወሯ መጠን ምንጊዜም ሠላሳ ሲሆን ጨረቃ ግን በአንደኛው ወር 29 በሌላኛው ወር ግን 30 ስለምትሆን ዓመቱ እኩል አያልቅም የጨረቃ ዓመት ነሐሴ 24 ቀን ያልቃል፡፡ ይህም ማለት ጨረቃ በሁለት ወር አንድ ጉድለት ታመጣለች፡፡ ያንን ነው ሊቃውንቱ ሕጸጽ(ጉድለት) ያሉት፡፡ በዚህም መሠረት ከላይ ኬክሮሱን(፩) በዓመቱ ቀናት አባዝተን ያገኘነውን 6 ዕለት ለጨረቃ ሕጸጽ ስንሰጠው የመስከረም/ ጥቅምት (1)፣ የጥቅምት/ ኅዳር(2)፣ የጥር/ የካቲት(3)፣ የመጋቢት/ ሚያዝያ(4)፣ የግንቦት/ ሰኔ (5)፣ የሐምሌ ነሐሴ (6) ሆነው ተካፍለው ያልቃሉ፡፡

በሌላም በኩል ደግሞ በጨረቃና በፀሐይ ዑደት መካከል በዓመት ያለው ልዩነት 11 ቀናት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት) ይሆናል፡፡ ስድስቱን ዕለታት ጨረቃ ለምታጎልበት (ሕጸጽ) ብንሰጠው ቀሪ 5 ዕለት ይኖረናል፡፡ ጳጉሜ ማለት እነዚህ 5 ቀናት ናቸው፡፡ አሁን የአሥራ አንዱን ዕለታት ከፈጸምን ሽርፍራፊዎቹን (15 ኬክሮስና 6 ካልዒት) እንይ፡፡

ከላይ እንዳየነው በፀሐይና ጨረቃ ዓመታት መካከል የተፈጠሩትን 11 ቀናት ስድስቱ ለሕጸጽ ማሟያ ሲገቡ የቀሩት 5 ዕለታት ናቸው ጳጉሜ የምትባለውን ወር በመሠረታዊነት የፈጠሯት፡፡ በጎርጎርዮሳውያኑ አቆጣጠር እነዚህ 5 ተጨማሪ ዕለታት በጃንዋሪ፣ ማርች፣ ሜይ፣ ጁላይና ኦገስት ላይ ስለተጨመሩ እነዚህ ወራት 31 ለመሆን ተገድደዋል፡፡ (ይህንን የከፈለው በ46 ቅልክ የነበረው ዩልየስ ቄሣር ነው፡፡ ለአራቱ ወሮች 30 ቀን፣ ለአንዱ 28/29 (በየአራት ዓመቱ)፣ ለቀሩት ሰባት ወሮች ደግሞ 31 ሰጥቷቸዋል፤ ለአምስቱ ወሮች 31 ያደረጋቸው ከጳጉሜ ወስዶ ሲሆን ለሁለቱ ወሮች አንዳንድ ቀን የጨመረላቸው ከፌቡርዋሪ 2 ቀናት ወስዶና ወሩን 28 አድርጎ ነው)፡፡

ከእንግዲህ የሚቀሩን ከላይ የየዕለቱን ልዩነት ለዓመት ስናባዛ (ቁጥር ፪ና ፫ ተመልከት) የቀሩን 15 ኬክሮስና 6 ካልዒት ናቸው፡፡ ሁለቱን  ከላይ ያየናቸውን (፬ና፭) ስንደምራቸው (12 ኬክሮስ + 3 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት) 15 ኬክሮስ ከ 6 ካልዒት ይመጣሉ፡፡

ቀደም ብለን አንድ ዕለት 60 ኬክሮስ ነው ብለናል፡፡ ስለዚህም አንድ ዕለት (60 ኬክሮስ) ለማግኘት ከላይ ያገኘነውን 15 ኬክሮስ በ 4 ማባዛት አለብን፡፡ በአራት ዓመት አንዴ ጳጉሜ 6 የምትሆነው እነዚህ በየዓመቱ የተጠራቀሙት 15 ኬክሮሶች አንድ ላይ መጥተው በአራት ዓመት አንድ ጊዜ አንድ ዕለት ስለሚሆኑ ነው፡፡ እርሷም ሠግር(leap year) ትባላለች፡፡ ጎርጎርዮሳውያኑ ይህቺን ሠግር በፌቡርዋሪ ወር ላይ ጨምረው ወሩን በየአራት ዓመቱ አንድ ጊዜ 29 ቀን ያደርጉታል፡፡

15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ተደምረው አንድ ዕለት መጡና በአራት ዓመት አንዴ ጳጉሜን ስድስት አደረጓት፡፡ የቀረችው 6 ካልዒትስ (ቁጥር ፭) የት ትግባ?

ካልዒት አንዲት ዕለት ትሆን ዘንድ 3600 ካልዒት ያስፈልጋሉ፡፡ ይህንን ያህል ካልዒት ለማግኘት 600 ዓመታት ያስፈልጉናል፡፡ ለዚህ ነው ጳጉሜ በየስድስት መቶ ዓመታት ሰባት የምትሆነው፡፡ እስካን የጠየቅኳቸው የባሕረ ሐሳብና የታሪክ ሊቃውንት በታሪካችን ውስጥ ጳጉሜን 7 የሆነችበትን ዘመን እንደማያውቁ ነግረውኛል፡፡ ሒሳቡ ሲሰላ በየ 600 ዓመቱ ሰባት ትሆናለች ቢባልም አስቦ በስድስት መቶኛው ዓመት ሰባት የሚያደርጋት እንደሌለ ይናገራሉ፡፡ በፈረንጆቹ ብሂል ‹ፌብሩዋሪ 30› ማለት የመሆን ዕድል ያለው ነገር ግን ሆኖሞ የማያውቅ ሊሆንም የማይችል(possible but never happen)› ተደርጎ እንደተወሰደው ሁሉ ምናልባት በኛም ጳጉሜን 7 ማለት እንደዚያው ይሆን ይሆናል፡፡

በነገራችን ላይ ጳጉሜን 5 ቀን በቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ዘንድ ‹ዕለተ ምሪያ› ወይም የተመረጠች ቀን ትባላለች፡፡ የጌታችን ልደት ለመጠበቅ ሊቃውንቱ ሲያሰሉባት የቆየችው ዕለት በመሆኗ ነው ይህንን ስያሜ ያገኘችው፡፡ የጌታችንን ልደት ቀን የምትወስነው ጳጉሜ 5 ቀን ናት፡፡ ልደት የሚውለው ጳጉሜ 5 በዋለበት ቀን ነው፡፡ ለምሳሌ ዘንድሮ ጳጉሜን 5 ቀን ረቡዕ ነው የምትውለው፤ ስለዚህም በ2007 ዓም ልደት የሚውለው ረቡዕ ነው፡፡ በየአራት ዓመቱ አንድ ጊዜ ጳጉሜን 6 ስትሆን ልደት በ28 የሚከበረው ዕለተ ምሪያን ስለማይለቅ ነው፡፡ ስድስተኛዋ ቀን ልደትን በአንድ ቀን ስታዘልለው እኛ በ28 እናከብረዋለን፡፡ ልደት ጳጉሜ 5 ቀንን(ዕለተ ምሪያን) ስለማይለቅ፡፡ ታድያ ምነው እነ ጥምቀትና ግዝረት አይለወጡም? ቢሉ፡፡ ሊቃውንቱ የሚሰጡት መልስ ‹ትውልድ ሱባኤ እየቆጠረ በተስፋ የጠበቃት ዕለተ ልደትን ስለሆነ ነው፤ ሌሎቹ የመጡት በልደቱ ምክንያት ነው›› የሚል ነው፡፡

በጎርጎርዮሳውያንም ቢሆን በአራት ዓመት አንዴ ልደት ዝቅ ትላለች፡፡ የእነርሱ የማይታወቀን ጭማሪዋ ፌብርዋሪ ላይ ስለሆነች ነው፡፡ ያ ደግሞ አዲሱን ዓመት ካከበሩ በኋላ ስለሚመጣ ነው፡፡ የእኛ ግን የምትወድቀው ጳጉሜን መጨረሻ ላይ በመሆኗ ከአዲስ ዓመት በፊት ስለምትጨመር ጎልቶ ይታወቃል፡፡

እንግዲህ ጳጉሜ የምትባለው አስገራሚ ትንሷ ወራችን እንዲህ በስሌት የተሞላች፣ አምስት ሆና ቆይታ በየአራት ዓመቱ አንዴ ስድስት፣ በየስድስት መቶ ዓመቱ ደግሞ ሰባት የምትሆን ናት፡፡ ታላላቆቹ ወሮች ምንም ሳይፈጥሩ የልደትን ቀን የምትወስን፣ የዓመቱን ሠግር የምታመጣ፣ ታሪከኛ ወር ናት፡፡ ትንሽ ትልቅ ማለት እንዲህ ነው፡፡

 

 

 

ከኅዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ አዲስ አበባ የገቡት የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እና ከኢትዮጵያ አቻቸው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ጋር ተገናኝተዋል፡፡

የሁለቱ ሃገሮች መሪዎች ከወራት በፊት ኢኳቶሪያል ጊኒ ዋና ከተማ ማላቦ ላይ ያደረጉት ውይይት ለተሻለ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በጋራ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡

ለዝርዝሩ በመግለጫው ላይ የተገኘውን እስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

ለተጨማሪ መረጃና ማብራሪያዎች ከታች ያሉትን ማገናኛዎች እየተጫኑ…

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በኢትዮጵያ ፍትሕ ሚኒስቴር መከሰሳቸውን ተከትሎ ሀገር ጥለው የተሰደዱ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች የደኅንነት ስጋት ገጥሞናል ይላሉ። የጋዜጠኞቹ የደኅንነት ስጋት ተዓማኒ ከሆነ ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ድርጅት የኬንያ ፅ/ቤት ተናግሯል።

አንድ የጀርመን ፍርድ ቤት በእስር ላይ ሳለ በእሳት ቃጠሎ ሕይወቱን ባጣ የዉጭ ዜጋ ጉዳይ በፖሊስ ላይ ያሳለፈዉን ፍርድ አጸና። ካልስሬኸ ከተማ የሚገኘዉ የፌደራሉ መንግሥት ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሴራሊዮናዊዉ እስረኛ በንዝህላልነት ሕይወቱ ጠፍቷል በሚል ከዚህ ቀደም በፖሊስ ላይ የተጣለዉን የገንዘብ ቅጣት ዛሬም በድጋሚ አፅንቶታል።

ለኢትዮጵያ አስተዳደር አማራጭ የፖለቲካ መርሕ ከቀየሱት በሰላማዊ መንገድ ከሚንቀሳቀሱት የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ ፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ፍትሕ ፓርቲ ፤ በመጪው 2007 አዲስ ዓመት ፣ ሀገራዊ ኀላፊነትን መሸከም በሚያስችል መርኀ ግብር ለመሥራት

ናይጀሪያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሰዉ እስላማዊ ፅንፈኛ ታጣቂ ቡድን የሚፈጽማቸዉን የኃይል ርምጃዎች እያጠናከረ በመሄድ ላይ ነዉ። በሰሜን የሀገሪቱ ክፍል በያዝነዉ ሳምንት መጀመሪያ አንዳንድ ከተሞችን መቆጣጠሩ የሚነገርለት ይኸዉ ቡድን ቀጥሎ የቦርኖ ግዛት ዋና ከተማ ማይዱጉሪን ሊይዝ ይችላል የሚል ስጋትም ይሰማል።

የአዲስ አበባ የትያትር ጥበባት ተማሪዎች «ልዑል አለማየሁ» በሚል ርዕስ አዲሱን 2007 ዓመት አስታከዉ በብሔራዊ ትያትር ሙዚቃዊ ተዉኔት ለማቅረብ ዝግጅት ላይ ይገኛሉ። ታሪካቸዉ እጅግም ብዙ እንዳልተፃፈበት እና ትያትርም ሆነ ሙዚቃ እንዳልተሰራለት ስለተነገረዉ ስለ አፄ ቴዎድሮስ ልጅ ስለ ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ፤

ነሃሴ ፳፱(ሃያዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ1997 ምርጫ ወቅት ለ200 ሰዎች ሞት እና በመቶዎች ለሚቀጠሩት ቁስለኞች ተጠያቂ በሆኑ 13 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ወታደራዊ  አዛዦች ላይ ለፖሊስ የክስ አቤቱታ አስገቡት በስዊድን ታዋቂ የሆኑት ጠበቃ ስቴላ ጋርደ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፣ በቅርቡ ለፖሊስ ከገባው አቤቱታ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በግፍ ለተገደሉት፣ ለቆሰሉት ፣ ለታሰሩት፣ ከስራ ለተፈናቀሉት አስፈላጊውን …

ነሃሴ ፳፱(ሃያዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች በመካሄድ ላይ ባለው የኢህአዴግ አባላት ስብሰባ ፣ አባላቱ ዛሬም በርካታ ጥያቄዎችን ሲጠይቁ መዋላቸውን ከውስጥ ምንጮች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ዛሬ ከሰዓት በኋላ በአባላቱ ከተነሱት ጥያቄዎች  መካከል፡- ” የኢትዮጵና የኤርትራ ህዝቦች የማይነጣጠሉ የአንድ ሃገር ዜጎች ሆነው ሳለ በመሪዎች አለመግባባትና ሽኩቻ በመለያየታቸው እስከዛሬ ድረስ እየተላቀሱ ይገኛሉ፤ ይህም የሆነው …

ነሃሴ ፳፱(ሃያዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው  ነሃሴ 29/2006 ዓ.ምበአራዳችሎትየቀረበው የአረና ፓርቲ የአመራር አባልና ታዋቂ ጸሃፊ መምህር አብርሃደስታ ፣ ፖሊስ ‹‹ተጨማሪሰነድለማሰባሰብናምስክሮችለማቅረብ” የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው በመጠየቁ ፣ ፍርድ ቤቱ ለመስከረም 22 ቀጠሮ ሰጥቷል። የኢምባሲናሌሎችተወካዮችንጨምሮበርከትያለህዝብየተገኘሲሆንአብርሃደስታከማዕከላዊወደችሎቱበሚመጣበት ጊዜህዝቡደመቅባለ ጭበጭባእንደተቀበለው ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡ህዝቡለአብርሃያደረገውንጭብጨባተከትሎምፖሊስህዝቡከግቢውእንዲወጣቢያስገድድምህዝቡ ሳይወጣ መቅረቱንም አክሎ ዘግባል። የአብርሃደስታጠበቃ  የሆኑት አቶ ተማምአባቡልጉከደንበኛቸውጋርበ28 ቀናትውስጥአንድቀንብቻ እንዳገኙት የነገረ ኢትዮጵያ ዘገባ ያመለክታል። ሀብታሙ አያሌው፣ …

የ «ጌታቸውን » የአቶ መለስን ራእይ፣ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በትጋት እየፈጸሙት እንደሆነ በስፋት እያየን ነው። የአቶ መለስ ራእይ ጭቆና፣ አምባገነንነት፣ ሰላማዊ ዜጎችን ማሰር፣ ሜዲያዉን መጨፍለቅ ነው። የአቶ መለስ ራእይ በእርቅና በፍቅር አገርን ማሳደግ ሳይሆን፣ ማክረር በዜጎችን ላይ መጨከን ነው። የፍቅርና የሰላም መጽሀፍን (መጽሐፍ ቅዱስን) በየቀኑ አነባለሁ በሚሉት በአቶ ኃይለማሪያም አገዛዝ ግን፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ በመለስ ጊዜ ከነበረው […]

ትላንት ከጠዋቱ 3፡00 በአራዳ ምድብ ችሎት ሐብታሙ አያሌው ዳንኤል ሺበሺና የሺዋስ አሰፋ እንደሚቀርቡ በመነገሩ የአንድነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና የየፓርቲዎቹ አባላትና ጋዜጠኞች ተገኝተው ነበር፡፡ ፖሊስ በፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የቀጠሮ ሰዓት አክብሮ እስረኞቹን ማቅረብ አለመቅረባቸው ላይ ብዙዎች ስጋት የነበራቸው ፡፡ የታሳሪዎቹ ጠበቆች አቶ ተማም አባቡልጉና አቶ ገበየሁ ይርዳው በግምት 4፡30 ተጠርተው ዳኛ ስለሌለ ከሰዓት በኋላ በ8፡00 ሰዓት […]