በብሄራዊ በዓላት ቀን በአብዛኛው ከወደ እስር ቤት የሚሰማው ዜና አስደሳች ነበር፡፡ይህንን አጼዎቹ ፣ሰው በላው የደርግ ስርዓትና ብሶት ወለደኝ ያለን ኢህአዴግ ሲያደርጉት ቆይተዋል፡፡በዘንድሮው አዲስ አመትም የመንግስትን ይቅርታ በማግኘት ከወዳጅ ዘመዶቻቸው የተቀላቀሉ ስለመኖራቸው ተሰምቷል፡፡በአዲሱ ዓመት ይቅርታ ከተቸራቸው እስረኞች መካከል ታዋቂ ፖለቲከኞች፣አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች አለመኖራቸው ተፈቺዎቹ በደረቅ ወንጀል ታስረው የነበሩ መሆናቸውን ለመናገር ብዙ መድከም አይጠይቅም፡፡ መንገስት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ሂሩት […]

የዶይቸ ቬለ የእጅ ስልክ አገልግሎት
http://m.dw.de/amharic የሚለውን የድረ ገፅ አድራሻ በመጻፍ የዶይቸ ቬለን ዜና፣ የዜና ትንታኔ እና ሳምንታዊ ዝግጅቶችን በጽሑፍ እና በድምፅ በእጅ ስልክዎ በየትኛውም ቦታ ለማግኘት ይችላሉ። ?maca=amh-standard_feed-amh-11646-xml

ኢትዮጵያ ሪቪው በቅርቡ ባወጣው ረፖርት፣ በአቶ አንዳርጋቸው መታሰር ዙሪያ የሻእቢያ እጁ እንዳለበት መዘገቡ ይታወቃል። በጉዳዩ ላይ ለኢትዮሜዲያ አስተያየት የሰጡት፣ የድርጅቱ አመራር አባል አቶ ነዓምን ዘለቀ፣ ሪፖርቱን ልብ ወለድና የፈጠራ ወሬ ብለዉታል። የኢትዮጵያ ሪቪው ዋና ኤዲተር የሆኑት አቶ ኤሊያስ ክፍሌ ፣ ሪፖርቱን ከማውጣታቸው በፊት አስቀድመው እርሳቸዉን ሆነ ሌሎች የግንቦት ሰባት አመራር አባላትን ቢያነጋገሩ ኖሮ ጥሩ ይሆን […]

ጳጉሜን ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ ኦሞድ ኦባንግ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ 400 ሰዎች የተገደሉበት የጋምቤላወኢ ጭፍጨፋ እንዴት እንደተከናወነ በዝርዝር አስረድተዋል። የህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ አባይ ጸሃየ ግድያውን በተመለከተ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። በክልሉ ስለሚፈጸመው ሙስናና የመሬት ወረራ የቀድሞው ባለስልጣን በዝርዝር ገልጸዋል። አቶ አዲሱ ለገሰ በቅርቡ ባወጡት ጽሁፍ በጋምቤላ ለኢህአዴግ ታማኝ የሆነ ሰው ለማግኘት …

ጳጉሜን ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ የኢህአዴግን ፖሊሲዎች ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ ለዳኞችና አቃቢያን ህጎች፣ ለፖሊሶች እንዲሁም ለኢህአዴግ የተለያዩ ፎረም አባላት ሲሰጥ የቆየውን ስልጠና ለመንግስት ሰራተኛው በሙሉ ለመስጠት ማቀዱ ታውቋል። እስካሁን ድረስ በተካሄዱት ስልጠናዎች ኢህአዴግ ከአባላቱ ጭምር ሳይቀር ከፍተኛ የጥያቄ ናዳዎችን ሲያስተናግድ የቆየ ቢሆንም፣ ውይይቱን ከማቋረጥ ይልቅ ወደ መንግስት ሰራተኛው በማውረድ አስፋፍቶ ለመስጠት ማቀዱን …

ጳጉሜን ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመከላከያ ሰራዊት የከዱ 10 የሚደርሱ ወታደሮች ከሆሳእና ከተማ ባለስልጣናት ጋር የፈጠሩትን ውዝግብ ተከትሎ፣   አንድ የከተማው የምክር ቤት አባል በደረሰበት ድብደባ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን፣ ይህን ተከትሎ  አንደኛው ወታደር ሲያዝ ቀሪዎቹ አምልጠዋል። ይሁን እንጅ  ወታደሩ ነሃሴ 30 ቀን 2006 ዓም ታይዞ መታሰሩን የገለጹት ምንጮች፣ ያልተያዙት ወታደሮች በምሽት እስር ቤቱን በመስበር …

ጳጉሜን ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቢቢሲ፦ሂዩማን ራይትስ ዎችን በመጥቀስእንደሰገበውውሃእናህክምናፍለጋቀያቸውንለቀው  ወደሞቃዲሾየሰላምአስከባሪሀይሉወደሰፈረበትካምፕየሄዱየሶማሊያ ልጃገረዶችናሴቶችበህብረቱየሰላምአስከባሪሀይላትበሀይልተደፍረዋል። አንዲትየ 15 ዓመትሙስሊምወጣትልጅ  ከአንገቱዋበላይየተሸፋፈነች በትንልብስበሀይልእንድታወጣናእንድት ገላለጥከተደረገችበሁዋላ  መደፈሩዋንየሰብዓዊመብትተቁዋሙጠቅሱዋል። በሶማሊያ  አልሸባብንናአክራሪእስላሚስቶችንለመዋጋትወደ 22 ሺህጦርያሰፈረውየአፍሪካህብረትየሰብዓዊመብትተቁዋሙየመሰረተውን ክስአስመልክቶ  ማጣራትእንደሚያደርግአስታውቁዋል። የመንግስታቱድርጅትየስደተኞችጉዳይከፍተኛኮሚሽንሪፖርትእንደሚያመለክተው በ2012 ብቻ  ከቀያቸውበተፈናቀሉ 1700 የሶማሊያሴቶችላይየአስገድዶመድፈርወንጀልመፈጸሙተመስግቡዋል። ባለፈውዓመት  አንዲትየሶማሊያሴትበህብረቱሰላምአስከባሪናበሶማሊያ ጦርአባላትበጋራመደፈሩዋንተከትሎከፍተኛውስግብተነስቶእንደነበር ቢቢሲአስታውሱዋል። የመደፈርአደጋእያጋጠማቸውያሉትአብሳኞቹሴቶችበተለይከ2011 ጀምሮ እያየለበመጣውየእርስበርስግጭትና  በድርቅምክንያትከቀያቸውተፈናቅለው ወደተለያዩመጠለያካምፖች  የገቡናቸው። የአፍሪካህብረትየሶማሊያሰላምአስከባሪልኡክከእንግዲህእንዲህያለውንነገር አላየኹምብሎዓይኑንሊጨፍንአይችልም፤ይህንድርጊትማድበስበስ  በአካባቢው  በዋነኝነትየተሰለፈበትንሰላምየማስከበርአላማን  ዋጋያሳጣዋል” ብለዋል- የሂዩማንራይትስዎችየሴቶችጉዳይዳሬክተርሊየስልጌርንቶልትስ። ከ 12 ዓመትጀምሮያሉ 21 ሴቶችበተደረገላቸውቃለ-ምልልስአብሳኞቹበኡጋንዳናበብሩንዲወታደሮችእንደተደፈሩመናገራቸውን የቢቢሲሰገባያመለክታል።

በመጪው አመት 2007 ወያኔን ለመቅበር ልዩነትን በማቻቻል በጋራ መታገል ችላ የማይባል ጉዳይ ነው። ላለፉት 23 አመታት በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተቀምጠውን ዘራፊውን እና ጨቋኙን የወያኔ ጁንታ በመጪው አመት ለመቅበር የአንድነት እና የለውጥ ሃይሎች ልዩነቶችን በማቻቻል በጋራ ልንታገል የሚገባና ለውጥ ልናመጣ የሚገባ ችላ የማይባል ጉዳይ ነው።ባሳለፍነው የትግል አመታት ውስጥ የተቃዋሚዎች እርስ በ እርስ መፈራረጅ መወነጃጀል ለስልጣን […]

ኢትዮጵያውያን በያዝነው አምባገነንነትን የማውደም ትግል ውስጥ እያንዳንዱ ዜጋ የራሱ ድርሻ እንዳለው የማይካድ ሃቅ ነው ። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በእኛ ሰዎች ዘንድ አንድ ችግር አለ ፡ አንድ ሰው በራሱ አስተሳሰብ የሚሄድ ከሆነ እውነታን ይዞ አንገቱን ሰብሮ የሚታገል ከሆነ አንዱ ለአንዱ ለምን አላጎበደደም እንደኛ ለምን አላሰበም ለምን አስተሳሰቡን ጻፈ በሚል በከፍተኛ ፍጥነት ጥላቻ ይንጸባረቅበታል ይፈረጃል። እያንዳንዳችን ሰዎች […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

እ ጎ አ በ 1884 የአውሮፓ መንግሥታት ፣ በርሊን ፣ ጀርመን ውስጥ ተሰብስበው የአፍሪቃውን ክፍለ ዓለም ተቀራምተው ቅኝ ግዛታቸው ካደረጉ ወዲህ፣ የክፍለ ዓለሙን ነባር ተወላጆች ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ አውሮፓ

ኢትዮጵያ ትምህርት አገልግሎትን በማስፋፋትና መምህራንን በመቅጠር የተሻለ እድገት ካሳዩ ሃገሮች ተርታ ተመድባለች። እንደ ማኖስ አንቶኒኒስ ከሆነ ከኢትዮጵያ የአንደኛ ደረጃ መምህራን መካከል በቂ የሙያ ስልጠና ያገኙት 20 በመቶው ብቻ ናቸው

«ለቅዱስ ጦርነት» እየተባለ በምዕራብ ሀገራት የሚገኙ ወጣት ሙስሊሞች እየተሰበኩ መሰደዳቸውን ቀጥለዋል። ለዚህም ለቅዱስ ጦርነት የሚሰብኩ እና የሚመለምሉ ጀርመን ሀገርም አልጠፉም። በሶርያ ብቻ ከ 74 ሀገራት የተመለመሉ 12 000 የሚደርሱ የውጭ ሀገር ዜጎች እንዳሉ ይገመታል።

የዩክሬይን መንግሥት እና መፍቀሬ ሩስያ የሚባሉት የምሥራቅ ዩክሬይን ዓማፅያን ባለፈው ዓርብ በሚንስክ ቤላሩስ የደረሱት የተኩስ አቁም ስምምነት ከሞላ ጎደል መፅናቱን ተሰማ። ይሁንና፣ የአውሮጳ ፀጥታ እና ትብብር ድርጅት

ይህ አመት አንደተለመደው አይነት አመት ቢሆን ኖሮ በዚህ ወቅት የዞን9 ጦማርያን በጦማሪት ማህሌት አስተባባሪነት ፣ በአጥናፍ ብርሃኔ እና በጆማኔክስ ካሳዬ ትብብር የአመቱን ታላላቅ ክስተቶች አሰባስበው ከመታተሙ በፊት ለቡድኑ ክለሳ የሚያቀርቡበትና የተረሱ እና ለክስተትነት የማይበቁ የምንላቸውን ሁነቶች የምንለይበትና የአመቱን የጊዜ መስመር የምናወጣበት ወቅት ነበር፡፡ ዘንድሮ ግን ያንን ከማድረግ ይልቅ የዞን9 የጦማርያን ቡድን የጊዜ መስመርን በመስራት ያለፈው አንድ አመት አሁን በስደት እና በእስር የሚገኙት ወዳጆች አንዴት አሳለፉት የሚለውን ለመግለጽ ወደድን፡፡  ይህ የጊዜ መስመር የመጨረሻው የዞን9 ኢትዮጲያዊ ህልም ዘመቻ ከተካሄደ በሁዋላ ባለው የ2006 ዓ/ም በዞን9 ዙሪያ የነበሩ ነገር ግን ለአደባባይ ያልበቁ ክስተቶቸን ይዘግባል፡፡ አላማውም አመቱ አንደቀልድ አለማለፉን እና በአደባባይ ያልተባሉት ጉዳዪች ምን እነደነበሩ ለዞን9 ነዋሪያን ግንዛቤ ያህል ከብዙ በጥቂቱ የቀረበ ነው ፡፡
መስከረም 2006 –አራት የዞን9 ጦማርያን የተሳተፉበት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በኢትዮጲያ ምን ይመስላል የሚል ሪፓርት ዝግጅት ተጠናቀቀ፡፡ በሪፓርቱም ላይ ሃሳብን የነጸነት የመግለጽ መብት ምን ይመስላል የሚለውን ሪፓርት ለተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ በሚያዝያ ኢትዪጵያ መንግሰት ላይ ለሚያደርገው ዩንቨርሳል ፔሪዲክ ሪቪው (UPR)- የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ በሰባአዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ የሀገራት የእርስ በርስ መገማገሚያ ስነ ስርአት  የሚቀርብ  (ለሚዲያ የማይቀርብ ለተባበሩት መንግሰትት ብቻ የሚገባ) ሪፓርት ነበር፡፡
በሪፓርቱ ከተሰራ በሁዋላ ጦማርያን ጓደኞቻቸውን እና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ ጠንካራ አቋም አላቸው የሚሏቸውን የገዢውን ፓርቲ ደጋፌዎች በመጨመር የሪፓርቱን ውጤት አሳይተው ግብረ መልስ ተቀበሉ፡፡ በወሩ መጨረሻም ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስረከቡ፡፡ (በዚህ ሂደት በሁዋላ ለደህንነት አካላት የወዳጆቸን እንቅስቃሴ በመንገር አየር መንገድ ላይ ሲወጡ አንዲጠየቁ ያደረገው የሪፓርተሩ ጋዜጠኛ የማነ ናግሽ የዚህ ሪፓርት ዝግጅትም ንቁ ተሳታፌ ነበር፡፡ )
 በዚሁ ወር የዞን9 ጦማርያን ወዳጅ የሆኑ የተለያዩ አጋር አካላት መንግሰት ጦማርያኑን ከግንቦት ሰባት ጋር በማያያዝ ስማቸውን እያነሳ ነው በሚል ለጦማርያኑ ጉዳዩን ግልጽ አንዲያደርጉላቸው ጠየቁ፡፡ በማስከተልም   የዞን9 ጦማሪ እንዳልካቸው ሃይለሚካኤልን ለትምህርት ከአገር መሄድ አስመልክቶ በተደረገ የምሳ ግብዣ ላይ የቡድን የደህንነት ጉዳይ የውይይት ርእስ ሆኖ ተነሳ ፡፡ በወቅቱ ብዙ የዞን9 ጦማርያን መንግስት አንደ አደጋ አይቆጥረንም የሰራነውም ወንጀል የለም፣ ያለን እንቅስቃሴም ኢንተርኔት ላይ የተገደበ በመሆኑ የደህንነት( እስርም ሆነ የስደት ) ስጋት የለብንም በሚል ተከራከሩ፡፡ በተቃራኒው ቢሆንም አንዲህ አይነት የመንግስት አረዳድ ላይ ችግር ካለ ለጊዜው ለሚቀጥሉት ወራት አንቅስቃሴያችንን በማቀዝቀዝ የመንግሰት ጥርጣሬ አግባብ አለመሆኑን ለማሳየት እንሞክር የሚል ሌላ ክርክር በመምጣቱ ሃሳቡ ተቀባይነት አግኝቶ ውሳኔ ላይ ተደረሰ፡፡ በመሆኑም የበይነ መረብ ዘመቻዎች ለተወሰነ ጊዜ አንዲቆሙ ፣ ወደአፍሪካ ኮሚሽንም ሆነ ወደተባበሩት መንግስታት አንዲሁም የኢንተርኔት አራማጅነትን አስመልክቶ ልምድ ለማካፈል የሚደረጉ ማንኛውም አይነት አለም አቀፍ ጉዞዎች ( በጣም አስፈላጊ እና ቀድመው የታቀዱ ካልሆኑ በስተቀር) አንዲተላለፉ ተወሰነ
በዚሁ ወር አጋማሽ ጦማሪ እነዳልካቸውለፒኤች ዲ ትምህርት ወደአሜሪካን አገር ኦሪጎን ዪንቨርሲቲ አቀና፡፡
በዚሁ ወር መጨረሻ ሁለት የዞን9 ወዳጆች እና አጋሮች ከአዲስ አበባ ኤርፓርት ለመውጣት ሲሞክሩ ኢሜግሬሽን ላይ ካገር አንዳይወጡ ለተወሰነ ሰአት ተይዘው የተለያዩ ጥያቄዎች ቀረበላቸው ፡፡ ሁለቱም ወዳጆች ላይ በተደረገው ድንገተኛ ምርመራ ከዞን9 ጦማርያን ጋር ያላቸውን ግንኙነት አንዲያስረዱ ተጠየቁ ፡፡
ጥቅምት/ ህዳር 2006 – ጦማርያኑ በዞን9 በኩል የሚጻፉ ጽሁፎችን አቀዝቅዘው በግል የማህበረሰብ ሚዲያው ላይ ወጣ ገባ ሲሉ ቆዩ፡። በዝምታው ቆይታ በጦማርያኑ የታየ ይህ ነው የሚባል የአደባባይ ስራ ቢኖር አሜሪካን አገር ለሚገኘው የኤንፒአር ኮጆ ሾው ኢትዮጲያ ውስጥ በትችት ድምጽ መጦመር ምን ይመስላል የሚለውና የሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በኢትዮጵያ የሚለው አርቲክል 19 በተባለው መንግስታዊ ያልሆነ የሰብአዊ መብት ድርጅት የተሰራው ዶክመንተሪ ፊልም ላይ ተሳትፎ ማድረግ ብቻ ነበር፡፡
ታህሳስ 2006  – በዚህ ወር በተደረገ ስብሰባ የታየ በቂ ደህንነት ችግር ስለሌለ ስጋታችን የተጋነነ ነውና ወደተለመደው አንቅስቀሴያችን መመለስ አለብን የሚል ውይይት ተካሄደ፡፡ ወደ ሥራ ለመመለስ የጋራ እቅድ ለማውጣት እና የተለመዱ የዞን9 ስራዎችን ይዞ መመለስ ይገባል የሚል ሃሳብ ተነስቶ ለመመለስ የሚያስፈልጉ ዘመቻዎች እቅዶች እና አዳዲስ ጉዳዮቸን የማስተዋወቅ እቅድ አንዲወጣ የስራ ክፍፍል ተደረገ፡፡  ተያይዞም ኢንተርኔት ላይ የዞን9 ህጋዊ ምዝገባን ለማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ ባለመኖሩ በተለያየ መልክ በመመዝገብ ይበልጥ ወደ ማህበረሰባዊ ስራ መጠጋትና ተቋማዊ ማድረግ ይገባል ተብሎ ተወሰነ፡፡ በ6 ወር ጊዜ ገደብ ውስጥም ወደሚዲያ/ሲቪል ሶሳይቲ ለማሳደግ ያሉትን እድሎች የማየት እቅድም አብሮ ተያዘ፡፡  በተመሳሳይ ወር አቶ አቤል አባተ አቀናባሪነት በመንግሰት ደህንነትና በኢትዮጲያ ቴሌቪዥን ድጋፍ የዞን9 ጦማርያን ላይ የተነጣጠረ የቀለም አብዩት የተሰኘው አሳፋሪ ሃሳብን የሚያቀርበው የቴሌቪዥን ዶክምንተሪ ታየ፡፡ (በወቅቱ በጦማርያኑ መካከል በተደረገ ውይይት ከዶክንተሪው በፌት ዞን9ን ይመለከታል የሚል ግምት መጀመሪያም አሳድሮ ነበር፡፡ )  
ጥር 2006 – ጦማሪ ናትናኤል ከአንድ ራሱን ከብሄራዊ ደህንነት አንደመጣ ባስተዋወቀ ሰው በመኖርያ ወረዳው አስተዳደር አማካኝነት ጥያቄ ቀረበለት፡፡ በወቅቱ ጥያቄው ስለጦማሪ ናትናኤል የፓለቲካ ተሳትፎ ስለዞን9 ምስረታ፣ አላማ ፣ እና አባላት የመሳሰሉት ሲሆኑ የደህንነት አባሉ የዞን9 አባላት 10፣000 ናቸው አላማችሁ ምንድነው? የአገር ደህንነትን የሚነካ ነገር እየሰራችሁ እንዳልሆነ በምን እናውቃለን የመሳሰሉ ጥያቄዎችን ያካተተ ነበር፡፡ ናትናኤል የዞን9 አላማ እና የሚሰራቸውን ስራዎች በዝርዝር አስረድቶ አባላቱ 9 አንደሆኑ 10.000 የተባሉት የዞን9 የፌስ ቡክ ገጽ ላይክ ያደረጉት ናቸው በማለት አብራራለት፡፡ የደህንነት አባሉ የቡድን አደረጃጀት ምን ይመስላል? ድጋፍ ታገኛላችሁ ወይ የመሳሰሉትን ጥያቄዎች በመጠየቅ ናትናኤልን አብረኸን እንድትሰራ አንፈልጋለን የሚል ጥያቄ አቀረበለት፡፡ ናትናኤል በወቅቱ ከደህንነት ጋር የሚያሰራ ምንም ችሎታ አንደሌለው ሌላ ጊዜ ቢጠየቅም ተመሳሳይ መልስ አንደሚመልስለት[JK4]  በማሳወቁ ደህንነቱ ወደፌት እናወራለን በማለት ተለየው፡፡ በዚህም የተነሳ በዚሁ ወር የታቀደው ጽሁፎችን እና ዘመቻዎችን ይዞ የመመለስ ውሳኔ ጉዳይ በድጋሚ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ፡፡ በተመሳሳይ ወር ከታሳሪዎች አንዳቸው ከናትናኤል ጋር ተመሳሳይ የሆነ የደህንነት ጥየቃ አስተናገዱ ፡፡ በወቅቱ ከአሁን ታሳሪዎችን አንዱን ያናገረው ሌላ የደህንነት አባል  የሚሰሩትን ነገር ሪፓርት አድርጉልን እየተከታተላችሁ በመናገር አብራችሁን ስሩ የሚል ጥያቄ አቅርቦ ነበር፡፡
የካቲት 2006 – በዚሁ ወር መጨረሻ ጦማሪት ሶልያና ሽመልስ ሰብአዊ መብት አማካሪ ፌሎ በመሆን በቀጣዩ የኢትዮጲያ ሰብአዊ መብት ግምገማ ጋር ተያያዥ የሆኑ ስራዎቸን ለመስራት ለመስራት ተጓዘች፡፡ በጦማሪያኑ በተደጋጋሚ የሚገናኙባቸው ቦታዎች ላይ በግልጽ እና በሚታይ መልኩ የደህንነት ሰዎች አዘውትረው መታየት ጀመሩ፡፡ በተመሳሳይ  ወር ጦማሪ ሶልያና ቀድማ የምትሰራበት መስሪያ ቤቶች ሃላፌዎች ጋር የደህነት ሰዎች የተለያዩ ጥያቄዎችን አቀረቡ፡፡ በዚሁ ወር በተመሳሳይ ናትናኤል እና በሌላ አሁን ታሳሪ ላይ ላይ የሚደርሰው ወከባ (በአካልም በስልክም) በረታ ከሚጠየቁት ጥያቄዎችም መካከል አላማችሁ ምንድነው ? ከነማን ጋር ነው የምትሰሩት? በፓርላማ ከታገዱ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላችሁ ወይ ? ባለፉት ወራት ዝም ያላችሁት ለምንድነው ? እየሰራችሁ ያላችሁት ሌላ ስራ አለ ወይ? የሚሉ ነበሩ፡፡ በወቅቱ የተነሱት ጥያቄዎች አላማችሁ ምንድነው? አባላታችሁ አደጃጀት አላችሁ ወይ የሚሉ ተደጋጋሚ እና አሰልቺ ሲሆኑ ጥያቄ ፣ የደህንነት አባላቶቹ ስለ ኢንተርኔትም ሆነ ስለማህበረሰብ ሚዲያ ያላቸው እውቀት በጣም አነስተኛ በመሆኑ ግማሹ ጊዜ መሰረታዊ የማህበረሰብ ሚዲያን አሰራር በማስረዳት የሚያልቅ ሲሆን በአንድ ወቅት አንዱ የደህንነት አባል ፍሪደም ኦፍ ኤክስፐረሽን ትሰራላችሁ የሚል ክስ በማቅረቡ በተመጣጣኝ ደረጃ መነጋገር አስቸጋሪ እየሆነ ነበር፡፡
መጋቢት 2006-  ከአሁን ታሳሪዎች አንዱ ላይ  አሁን ዝም ያሉት ለምንድነው?  የሚሰሩት ሌላ ነገር ስላለ ነው የሚሉ ጥያቄዎቸን በተደጋጋሚ አስተናገዱ፡፡ ፣ በዚሁ ወር ነገሮች መክፋታቸውን ተከትሎ ለዞን9 ጦማርን ለሌሎች ልምድ እንዲያካፍሉ በተጋበዙበት በታንዛንያ በተደረገው ስብሰባ ውጪ ያሉ የዞን9 ጦማርያን በስካይፕ የተሳተፉበት ሰፋ ያለ ውይይት ተካሄደ፡፡ በዚህ ውይይት ላይም የምንሰራው ወንጀል የለምና ምንም ሊያሰጋን የሚገባ ነገር የለም የሚለው ክርክር አንዳለ ቢሆንም እየበረታ ካለው የደህንነቶች ወከባ አንጻር ተረጋግተው አንዲመለሱ ማድረግ የሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ውሳኔ ተሰጠ፡፡ ፡፡ በዚህም መሰረት ጦማሪ ናትናኤል ደህንነት አባሉ በሚያናግረው ወቅት ስራችንን አንዲያስረዳው (  ደህንንቱ ትዊተር ፌስ ቡክ አጠቃቀም አንዲያሳየው ፣ የተጠረዘውን የዞን9 ስራዎች ስብስብ አንዲሰጠው እና ክትትላቸውም አግባብ አንዳልሆነ እንዲገልጽለት) ተወሰነ፡፡ መንግሰት አዲሱ ስጋት ከ ለምን ተናገራችሁ? ወደ ለምን ዝም አላችሁ? የተቀየረ በመሆኑ ዝምታችን ማቆምና የመመለስ ዝግጅት ማድረግ አንደሚገባ፣ እንዲሁም በደህንነቶች በከፍተኛ ሁኔታ ስማቸው የሚነሳ የቡድኑ አባላት ከፍተኛ የደህንነት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አንዲመች የደህንነት ስጋት ቅደም ተከተል በማውጣት ጦማሪት ሶልያና እና ጦማሪ በፍቃዱ በአንደኛ ደረጃ በመንግሰት ደህንነቶች አይን በመታየት ጦማሪ አጥናፍ እና ናትናኤል (ናትናኤል በቀጥታ እያናገሩት በመሆኑ እና አጥናፍ ቀድሞ የሚሰራበት መስሪያ ቤት በመሄድም ጭምር የክትትል ሂደቱ ስለጠነከረበት ) በሁለተኛ ደረጃ  በከፍተኛ የደህንነት ግንኙነት መረብ ውስጥ በመሆን  እነዚህ ጦማርያን አስፈላጊውን ጥንቃቄ አንዲያደርጉ እና ወደፊትም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ደህንነታቸውን ለማረጋገጥ የተለያዩ እርምጃዎችን መውሰድ አንደሚያስፈልግ  ለጊዜው ግን ወደ ተለመደው ኢንተርኔት በመመለስ ምንም እየሰራን አንዳልሆነ ማሳየት አለብን የሚል ውሳኔ ተደረሰ፡፡ ( በወቅቱ ሌሎች ጦማርያን ላይ ያለው ስጋት ተመሳሳይ ደረጃ ላይ ነው የሚል ድምዳሜ ነበር)
በዚሁ ወር መጨረሻ ጦማሪ አቤል ዋበላ ላይ ከምሽቱ 2 ሰአት 22 አካባቢ በፌዴራል ከሚጠበቅ የመንግስት መስሪያ ቤት አጠገብ ከፍተኛ የአካል ድብደባ ደረሰበት በድብደባው ራሱን የሳተ ሲሆን ሲነቃ ከላፕቶፑና ከስማርት ስልኩ ውጨ የተወሰደ ምንም ንብረት አለመኖሩም ሌላ ከፍተኛ ጥርጣሬን አስነሳ፡፡
በዚያው ወር መጨረሻ ጦማሪ ናትናኤል ለደህንነት አባሉ የዞን9 ስራዎችን የሚያሳይ ጥራዝ በመስጠት የአባላቱን የፌስ ቡክ እና የትዊተር አንቅስቃሴ አንዴት መከታተል አንደሚችል በተወሰነው መሰረት አስረዳው፡፡ ከሚታየው ውጪ የምንሰራው ነገር የለም የዝምታችን ምንጭም የደህንነቶች ወከባ መሆኑን ተናገረ ፡፡ በተደጋጋሚ ህጋዊ መታወቂያ ቢጠይቀውም የደህንነት አባሉ መታወቂያ ለማሳየት ፍቃደኛ አልነበረም፡፡ በዚሁ ወር ከቀድሞው በተጨማሪ ከአሁን ታሳሪዎች በአንደኛው ላይ ከደህንነቶች ጋር አብሮ የመስራት ጥያቄው ጠነከረ፡፡ አብሮ ካልሰራ የመታሰር አደጋ አንዳለውም ደጋግመው አስጠነቀቁት፡፡ ነገር ግን ማስፈራሪያውን ተከትሎ የሰሩትን ህገ ወጥ ስራ ስለማላውቅ ልተባበር አልችልም ብሎ በአቋም ጸና፡፡
ሚያዝያ 2006  -የቡድኑ የወቅቱ አስተባባሪ ናትናኤል ፈለቀ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቶች ጋዜጠኞች እና ጦማርያን የሚያደርጉበት አመታዊ የልምድ ልውውጥ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስዊድን ተጉዞ ተመለሰ፡፡ በዚሁ ወር መጀመሪያ ከዞን9 ጦማርያን ጋር ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ጋር ተያያዥ ስራዎችን በመስራት አጋር ድርጅት የሆነው የአርቲክል 19 ሰራተኛ አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ላይ ለ36 ሰአታት ተይዞ ከአገር አንዲወጣ ተደረገ፡፡ በወቅቱም መንግሰት ድርጅቱ የሚሰራውን ስራ አንወደውም ከማለት ውጪ ለማባረሩ የሰጠው ሌላ ምክንያት አልነበረም (ይህ ድርጅት ከዚህ ቀደም አቶ ሽመልስ ከማልን ጨምሮ ለሌሎች ባለስልጣናት ስልጠና የሰጠ ሲሆን የሚዲያ ሕጉ በሚወጣበት ወቅት ከመንግስት ጋር አብሮ ይሰራ የነበረ መሆኑ ይታወሳል )
በዚሁ ወር በነበረው በጄኔቫ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሚካሄደው የኢትዮጲያ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ በሰባአዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ የሀገራት የእርስ በርስ መገማገሚያ ስነ ስረአት ቅድመ ግምገማ (Pre UPR) ሊሳተፉ ተጋብዘው የነበሩ ሁለት ጦማርያን የመንግስትን ክትትል ለማረጋጋት በማሰብ ጉዞአቸውን ሰረዙ ፡፡
በመጀመሪያው ሳምንት በጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ፣ በጦማሪ አጥናፍ ላይ የነበረው ክትትል በመጨመሩ እና በጦማሪ አቤል ላይ የደረሰው ድብደባ አጠራጣሪነቱ ከመጨመሩም በተጨማሪ ሌሎች የዞን9 ወዳጆች ከደህንነቶች በተደረገ ተከታታይ የስልክ ጥሪ ጆማኔክስ እና ማሂፋንትሽ የሚባሉ ጦማርያንን አድራሻ አንደሚያውቁና አንዲናገሩ መጠየቃቸውን ተናገሩ፡፡  
በተመሳሳይ ቀን ከደህንነት ቢሮ ጦማሪ ናትናኤል ጋር ተደውሎ የዘጠኙንም አባላት ሙሉ ስም የስልክ አድራሻ እና የሚሰሩበትን መስሪያ ቤት አንዲገልጽ ተጠየቀ፡፡ ( ናትናኤል በወቅቱ ስራቸውን ለመስራት የተሻለ ስልት መጠቀም አንደሚገባቸው በማሳሰብ የማንንም አድራሻ ለመናገር ፍቃደኛ አንዳልሆነ መለሰ)
በእለቱ  ምሽት በጣም አስጊ የሆኑትን ጉዳዪች አስመልክቶ ከፍተኛ ውጥረት የነገሰበት ውይይት ተካሄደ፡፡ በመሆኑም ዝም በማለት የመንግስት ደህንነቱን ለማረጋጋት የተደረገው ሙከራ አለመሳካቱ አንደውም ለምን ዝም አሉ ወደሚለው መንገድ ማምራቱን ተከትሎ መናገርም ዝም ማለትም ያልተፈቀደልን የቡድኑ አባላት የተለያዩ ምን ማድረግ ይገባል የሚሉ ተከታተይ ውይይቶችን በየቀኑ ማካሄድ ተጀመረ፡፡[በወቅቱ የስጋቱን ከፍተኛ ደረጃ መድረስ ተከትሎ አውሮፓ ቪዛ ያለው ጦማሪ በፍቃዱ ለጊዜው ከአገር ወጥቶ ዞር አንዲል  የቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ አደረገው፡፡ ( በወቅቱ በነበረው መረዳት ከፍተኛ አደጋ ላይ አለ ተብሎ የታሰበው በፍቃዱ ነበር)
 ተከታታይ ውይይቶቹ ሲጠናቀቁ ሁለት ሃሳቦች ለውሳኔ ቀረቡ – አንደኛው እየተጠናከረ የመጣውን ጫና በይፋ በመግለጽ ዞን9ን በመበተን ቡድኑ በይፋ እንዲዘጋ ማድረግ ሲሆን ሁለተኛው ደሞ ወደተለመደው የኢንተርኔት  እንቅስቃሴ በመመለስ እስካሁን ቡድኑ የጠፋበትን ምክንያት መግለጽና ተመሳሳይ የሆኑ ክትትሎችን በተከታታይ ለአአደባባይ ማዋል  በሚል ውይይት ተደረገ፡፡ በዚህ ቀናትን በፈጀ ውይይት ለመጀመሪያም ( ምናልባትም ለመጨረሻ ጊዜም) ውሳኔ ለመስጠት ድምጽ ብልጫ ይደረግ በተባለው መሰረት  በአንድ ተቃውሞ በሁለት አብላጫው በወሰነው እስማማለሁ እና በስድስት ድጋፍ ወደእንቅስቃሴ ለመመለስ ተወሰነ፡፡ ተያይዞም ከደህነት የሚመጡ ጥያቄዎቸን ከዚህ በሁዋላ ማስተናገድ አንደማይገባ ተወሰነ፡፡  
( በዚህ ውሳኔ ወቅት ሁሉም ጦማርያን መንግስት በፍጥነት የእስር እርምጃ ይወስዳል የሚል ግምት ያልነበረን ሲሆን ወደስራ ተመልሰን “ተጽእኖ” እስክንፈጥር ወይም የስራችንን ይዘት አይተው እርምጃ ይወስዳሉ በሚል ግምት ከጥቂት ጊዜያት በሁዋላ ሊመጣ የሚችለውን ነገር አና መደረግ የሚገባቸውን ስራዎች ማዘጋጀት ላይ ከማቀድ ውጨ ያደረግነው ዝግጅት አልነበረም፡፡) 
ሚያዝያ 15 – የዞን9 አባላት ሁሉም በተለመደው ሁኔታ የኢንተርኔት እንቅስቃሴያቸን መመለሳቸውን የሚገልጽ መግለጫ ወጣ፡፡ በወቅቱም ለጊዜው የእስረኞች አያያዝን፣ እየተነቃቃ መጣውን የኦሮሞ ብሄርተኝነት ተከትሎ ታዋቂ የኦሮሞ ፓርቲዎች ፕሮግራምን ማስተዋወቅን( ልዩነቶቻቸው እና አንድነቶቻቸውን)  እና ለመጪው ምርጫ የሚሰሩ ዘመቻዎችን ማዘጋጀት ላይ ማተኮር የመመለሻ ስራዎች አቅጣጫ አንዲሆን ተወሰነ፡፡  ተወሰነ፡፡ በተጨማሪም በመጪው ሳምንት የሚካሄደውን የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ በሰባአዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ የሀገራት የእርስ በርስ መገማገሚያ ስነ ስረአት አስመልክቶ መረጃዎችን መስጠት ላይ አንድናተኩር እና ቀድመው ታቅደው ነበሩ የዞን9 ስራዎችን መከለስ የመሳሰሉ የስራ ክፍፍሎች ተሰጡ፡፡ 
ሚያዝያ 17 – ሚያዝያ 17 ማምሻውን በተመሳሳይ ሰአት የዞን9 ጦማርን በያሉበት እየተያዙ እነደሆነ መረጃዎች ተሰሙ፡፡ያንን ተከትሎ  እስሩ እየተከናወነ ያለው በተመሳሳይ ሰአት  በመሆኑ መረጃዎች እነደተሰሙ ለሁሉም ጦማርያን ለማስተላለፍ የተደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀረ፡፡ በእለቱ 6 ጦማርያን መያዝ ሲረጋገጥ እስሩ እየተከናወነ እያለ ከመታሰሩ ቀድሞ መረጃ ማድረስ የተቻለው ለጦማሪ ጆማኔከስ በመሆኑ ማምሻውን በአስቸኳይ ነበረበትን ከተማ ቀየረ፡፡
ሚያዝያ 18 – ጦማሪ ጆማኔክስ ካሳየ በተጣደፈ በጣም አጭር የቡድን ውሳኔ ከአገር በፍጥነት ወጣ፡፡ ( ከአገር የወጣው የመጨረሻው ጦማሪ በመሆን ከመንግሰት የተቀናጀ አፈና የተረፈው ብቸኛው የዞኑ ጦማሪ በመሆን ስደትን ተቀላቀለ) በተጨማሪም የዞን 9 ወዳጅ የነበሩ ጋዜጠኞች በተመሳሳይ ክስ መአከላዊ ምርመራ ለእስር አንደተወሰዱ ተሰማ።
 ሚያዝያ 19 – የህግ አማካሪ እና ቤተሰብ ባልተገኘበት እሁድ ቀን አራዳ ፍርድ ቤት ጦማርያኑ ከእስረኛ ጋዜጠኞች ጋር ቀረቡ በወቅቱም ፓሊስ ራሱን የሰብአዊ መብት ተቋም በሚል ከሚጠራ ድርጅት ጋር በመተባበር ህገ መንግሰታዊ ስርአቱን በሃይል ለመናድ በማህበረሰብ ሚዲያ አመጽ የመቀስቀስ ዝግጅት በማድረግ ወንጀል መጠርጠራቸውን መግለጹን ከፍርድ ቤት ፋይሉ መረዳት ተቻለ፡፡
የተባበሩት መንግስታት ክሱን ተከትሎ ከሰብአዊ መብት ተቋማት ጋር መስራትን ወንጀል ማድረግ አደገኛ እና ከአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎች ጋር የሚጋጭ መሆኑን በማሳወቅ አስቸኳይ መግለጫ አወጣ፡፡ ይህንንም ተከትሎ በመቶዎች የሚጠጉ የሰብአዊ መብት ተቋማት እስሩን የሚያወግዙ መግለጫዎችን አወጡ፡። በተመሳሳይ ወር ግሎባል ቮይስስ የመጀመሪያውን አለም አቀፍ የጦማርያኑ እና የጋዜጠኞቹ እስርን የሚቃወም ዘመቻ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን በሺዎች  የሚቆጠሩ በመላው አለም ያሉ የሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ተሟጋቾች አጋርነታቸውን አሳዩ፡፡ በማህበረሰብ ሚዲያዎችም አበረታች የአጋርነት ድጋፎች  ታዩ፡፡
ሚያዝያ 23 እና 24 – ጦማሪ ጆማኔክስ ካሳየ መኖሪያ እና የስራ ቦታ ከፍተኛ ወከባ እና ተያያዥ ጥያቄዎች ለተለያዪ ሰዎች ቀረቡ፡፡ መንግሰት ደህንነት ሰዎች ባደረጉት በዚህ ከበባ የጦማሪውን አገር ውስጥ አለመኖር ተረዱ፡፡
ሚያዝያ 29 እና 30 – የዞን9 ጦማርን እና ጋዜጠኞች ፍርድ ቤት በሚቀርቡበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ በቤተሰብ አና በጓደኞቻቸው መታየት ቻሉ፡፡ ሁለት ጦማርያንም ድበደባ እና ኢሰብዓዊ  የሆነ እንግልት እንደደረሰባቸው ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቀረቡ፡፡ በተመሳሳይ ወር በሁሉም እስረኞች ላይ ከድብደባ ከኢሰብአዊ አያያዝ  የአንቅልፍና የምግብ መክከል አንዲሁም ሌሎች ለአደባባይ የማይገለጹ መንገላታቶች ደረሱባቸው፡፡
 ግንቦት 2006 – በዚህ ወር በአራት የተለያዩ ቀናት በተለያዪ ቡድኖች ወደ ፍርድ ቤት የቀረቡት ጦማርያን እና ጋዜጠኞቹ ክስ ከሰብአዊ መብት ተቋማት ጋር በመስራት አመጽ ማነሳሳት ከሚለው ወደ ሽብተኛነት ጥርጣሬ ተቀየረ፡፡ አዲስ ወንጀል ለመቀየሩ ማእከላዊ ምርመራ ያሳየው ምንም አይነት ማስረጃ ባይኖርም የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮን እንደፈለገ ማግኘት ቻለ፡፡ በዚሁ ወር በነበረው የመጀመሪያ ቀጠሮ ባለፈው አቤቱታ ካቀረቡት በተጨማሪ ጦማሪ አጥናፍ ብርሃኔ በሌሊት እየተጠራ ምርመራ እንደሚደረግበት እና ድብደባ አንደተፈጸመበት ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቀረበ፡፡
በዚሁ ወር ጦማርኑ ከታሰሩ ከአራት ሳምንት በሁዋላ “የሽብር ወንጀል ተጠርጣሪ” በሆነችው በጦማሪ ሶልያና ሽመልስ ቤት በሌለችበት  በሁለት ዙር የተከፈለ ብርበራ ተካሄደ፡፡ በመጀመያው ዙር ምርመራውን ጨርሶ የሄደው ፓ

ኢትዮጵያውንና ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን በዛሬው እለት ከዋሽንግተን ዲሲው የአሜሪካ ድምጽ ዋና መሥሪያ ቤት ደጃፍ የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ።

”የተዛቡ ዘገባዎችን በማሰራጨት” የከሰሱትን የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ የአማርኛው አገልግሎት፤ የገዛ መመሪያውን ያክብር፤ ያሉት የተቃውሞ ሰልፈኞች፤ “የተዛባ አዘጋገቡንም ያቁም፤” ሲሉ፥ ጠይቀዋል።

የአሜሪካ ድምጽ በበኩሉ በቅርቡ በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ሰልፈኞቹ ያሰሙትን ጥሪና ቅሬታ ጠቅሶ፤ አስተዳደሩ የአሜሪካ ድምጽንና ሌሎች የዩናይትድ ስቴትስ የዜና አገልግሎቶች በሚያስተዳድረው Broadcasting Board of Governers ውስጥ የሚገኘውን ገለልተኛ ጽ/ቤት ጉዳዩን እንዲመርምር ማድረጉን አስረድቷል። የአሜሪካ ድምጽ አክሎም ጽ/ቤቱ የደረሰባቸውን ሦሥት ድምዳሜዎች ዘርዝሯል።

በሳሞራ የኑስ እና በጌታቸው አሰፋ የሚመራ ልዩ የኮማንዶ እና የደህንነት ሃይል አዲስ አበባ ባህር ዳር እና ድሬዳዋን መቆጣጠር የሚችልበትን ስልት እየነደፈ ነው። 2007 ለለውጥ ! – በሳሞራ የኑስ የሚመራው የኮማንዶ ጦር ህገመንግስታዊ ጥያቄ ማንሳቱ ታማኝነቱ ጥርጣሪ ውስጥ ገብቷል – መጪው ጊዜ በመላው ኢትዮጵያ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ሃይሎች ገነው ይወጣሉ። – ዲያስፖራው ከምንም ጊዜ በበለጠ ለወያኔ […]

አቶ አንዳጋቸውን አሳልፎ የሰጠው የኤርትራ ደህንነት ጽ/ቤት እንደሆነ ኢትዮጵያ ሪቪዉ ዘገባ። ለሁለት ወራት አደረኩት ባለው ምርመራ ፣ በግንቦት ሰባቱ ዋና ጸሃፊና በኤርትራ መንግስት መካከል የነበሩ አንዳንድ ልዩነቶችን ኢትዮጵያ ሪቪው ዘርዝሯል። አቶ አንዳርጋቸው በሻእቢያ ተስፋ ቆርጠው እርዳታ ከግብጽ ለማግኘት ወደ ካይሮ አመርተው እንደነበረ የዘገበው ኢትዮጵያ ሪቪው፣ የአቶ አንዳርጋቸው የካይሮ ጉዞ ሻእቢያን እንዳበሳጨም ገልጿል። የሻእቢያ ሰለባ ሲሆኑ […]

 

 

የዓለምአቀፍ ቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ማኅበራት ፌዴሬሽን አዲሱ ዋና ፀሐፊ ሀገሮች የኢቦላ ወረርሽኝን ለመከላከል በሚያደርጉት ጥረት ድንበራቸውን ከመዝጋት እንዲቆጠቡ ጠይቀዋል።

በምሥራቅ አፍሪካ ረሃብ እንደገና እያንዣበበ እንደሆነም ተገልጿል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ።

ጳጉሜን ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአለፈው አንድ አመት ውስጥ ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ለፓርቲው የፖለቲካ ስራ የሚጠቅም ከመንግስት ባጀት ከ900 ሚሊዮን ብር ያላነሰ ገንዘብ ማውጣቱን ምንጮች ገለጹ። ለብሄር ብሄረሰቦች ቀን፣ ለባንዲራ ቀን፣ ለመከላከያ ቀን፣ ለተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የፖለቲካ ስልጠና፣ ከ100 ሺ በላይ ለሚሆኑ የኢህአዴግ አባላት ስልጠና፣ ለፖሊስ ሰራዊት የተሰጠው ስልጠና፣ እንዲሁም በተለያዩ ታሃድሶ የሚል …

ጳጉሜን ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት በመግለጫ የከሰሳቸው ጋዜጠኞች አግር ጥለው ከወጡ በሁዋላ ጉዳያቸው በሌሉበት እየታየ ነው። ከሳምንት በፊት ጥሪ ተደርጎላቸው እኢነዲቀርቡ የታዘዙት የፋክት፣ አዲስ ጉዳይ እና ሎሚ መጽሄት አዘጋጆችና ባለቤቶች  ፍርድ ቤት ለመቅረብ ባለመቻላቸው 17ኛው ወንጀል ችሎት  ጉዳያቸውን በሌሉበት ለማየት ተጨማሪ ቀጠሮ ሰጥቷል። ተከሳሾቹ ህመንግስታዊ ስርዓቱን በአመጽ ለማፍረስ አስበዋል የሚል ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን፣ …

ጳጉሜን ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሊጠናቀቅአንድዓመትበቀረውየመንግሥትየአምስትዓመቱመርሃግብርመሠረት የሆልቲካቸርእናሰፋፊእርሻ ኢንቨስትመንትዕቅዶችየተለጠጡስለነበሩየተሳካአፈጻጸምእንዳልተመዘገበባቸውየግብርናሚኒስትሩ አቶተፈራደርበውለመጀመሪያጊዜአምነዋል፡፡ ሚኒስትሩከመንግስታዊውአዲስዘመንጋዜጣጋር  ባደረጉትቃለምልልስእንደተናገሩት በመርሃግብሩዘመንየሆልቲካልቸርበተለይምየአትክልትናፍራፍሬኢንቨስትመንትበማስፋፋትለሀገሪቱ ከአንድቢሊየንበላይየሚደርስ የውጭምንዛሪለማስገባትታቅዶእንደነበርአስታውሰውነገርግንዕቅዱከመነሻውየተለጠጠናየተለያዩችግሮችአጋጥመውስለነበር ያስብነውንያህልከዘርፉውጤትማግኘትአልቻልንምብለዋል፡፡ በዘርፉታይተዋልካሉዋቸውችግሮችመካከልየዕዝሰንሰለቱንየተከተለአሰራርአለመኖር፣ለአየርትራንስፖርትየቀረበመሬትአቅርቦት ችግር፣የሎጀስቲክአቅርቦትማነስተጠቅሰዋል፡፡ የሰፋፊእርሻኢንቨስትመንትንለማስፋፋትየተደረገውጥረትመሬትተረክበውበፍጥነት ወደሥራያለመግባትችግሮች ማጋጠማቸውንጠቁመውይህንችግርለመፍታትጥረቶችመደረጋቸውንጠቅሰዋል፡፡በአሁኑወቅት በዘርፉየቱርክ ባለሃብቶችበጥሩሁኔታእየተንቀሳቀሱመሆኑንሌሎችምከእነሱተሞክሮሊወስዱይገባልሲሉተናግረዋል፡፡ ሚኒስትሩእንደእነካራቱሪያሉየህንድባለሃብቶችየተረከቡትንመሬትተፈጥሮሃብትበማውደም፣ፈቃድያወጡበትን ኢንቨስትመንትስራባለመስራትእንዲሁምየባንክብድርበመውሰድስላደረሱትጥፋትናኪሳራምንምያሉትነገርየለም፡፡

ጳጉሜን ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ አበባ ውስጥ በየ ቤቱ እየዞሩ ዲሽ የሚገጥሙ ወጣቶች ‹‹ኢሳትን እየቀጠላችሁ ነው›› በሚል ወከባ እንደሚደርስባቸው መናገራቸውን ነገረ-ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡ጋዜጣው እንዳለው ወጣቶቹ ከኢሳት ውጭ ያሉ ጣቢያዎች የሚተላለፉበት ዲሽ  ጭምር በሚገጥሙበት ወቅትም ‹‹ኢሳትን እየቀጠላችሁ ነው፡፡ ህዝቡ ኢሳትን እንዲያይ ታደርጋላችሁ›› በሚል በደህንነቶች ወከባ እንደሚደርስባቸው ለጋዜጣው ዝግጅት ክፍል ተናግረዋል፡፡ ከወራት በፊት መርካቶ አካባቢ ዲሽ …

ጳጉሜን ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአሉ ቅዳሜ መስከረም 6 ቀን 2014 ዓ.ም የድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች በተገኙበት በድምቀት መከበሩን ከስፍራው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል። የዕለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት አቶ አበረ አዳሙ የግንቦት ሰባት ምክር ቤት አባል ስለ ወቅቱ ተጨባጭ ሁኔታና የግንቦት ሰባት የሥራ እንቅስቃሴ ሰፊ ንግግር አድርገዋል። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የሕይወት ታሪክ ላይ የተዘጋጀ ዶክመንታሪ ቪድዮ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ አዲስ አበባ ስታዲየም ውስጥ በአልጄሪያ 2 ለ1 ተሸንፏል። በአውሮጳ የእግር ኳስ ማኅበራት ኅብረት ጨዋታ ፖርቹጋል ባልተጠበቀ ሁናቴ በሜዳዋ በአልባኒያ ስትረታ፤ ማኅበሩን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀላቀለችው አዲሲቷ አባል ጂብራልተር በፖላንድ የግብ ጎተራ ሆናለች። ጀርመን ስኮትላንድን ረትታለች።

የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ አዲስ አበባ ስታዲየም ውስጥ በአልጄሪያ 2 ለ1 ተሸንፏል። በአውሮጳ የእግር ኳስ ማኅበራት ኅብረት ጨዋታ ፖርቹጋል ባልተጠበቀ ሁናቴ በሜዳዋ በአልባኒያ ስትረታ፤ ማኅበሩን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀላቀለችው አዲሲቷ አባል ጂብራልተር በፖላንድ የግብ ጎተራ ሆናለች። ጀርመን ስኮትላንድን ረትታለች።

በመሐሉ ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለማርያም ከመስከረም በፊት፤መስከረምና ከዚያ በሕዋላ እሳቸዉም ሹማምንቶቻቸዉም ያሉትን ኢሕአዴግ ሥልጣን የያዘበት ሃያ-ሰወስተኛ ዓመት ሲከበር ደገሙት።ግንቦት ሃያ።ተደጋጋሚዉ ዛቻ፤ እገታ የዚያን ቀን ሰነዓ ላይ ከተፈፀመዉ ያደርሳል ብሎ የጠረጠረ የሩቅ ታዛቢ አልነበረም።ሰኔ አስራ-ስድስት።

]በአሉ ግርማና አስፋው ዳምጤ

[email protected]

ባለፉት ወራት የአገር ቤቶቹንም ሆነ ውጪ ያሉትን የሚዲያ አውታሮች በተለያየ መልክ ያነጋገረው የበአሉ ግርማ አሟሟት ላለፉት 30 አመታት ሲያነታርክ ቆይቶአል ። እስከደርግ መጨረሻ ድረስ በድብቅ ፤ ከዚያ በኋላ ደግሞ በግልፅ አነታርኳል ። ይህም የሆነው በሁለት ምክንያቶች ነው ። አንደኛው ምክንያት በአሉ ግርማ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ስነ-ፅሁፍ አቻ የማይገኝለት ደራሲ በመሆኑና በብዙ አንባቢዎቹ ልብ ውስጥ ልዩ ቦታ ያለው መሆኑ ሲሆን ፣ ሁለተኛው ደግሞ ፍትህንና እውነትን ፈላጊ ተስፋ የማይቆርጥ ቤተሰብ ስላለው ነው ። በተለይ ደግሞ ባለቤቱ ወ/ሮ አልማዝ አበራ ። ለፍትህ እታገላለሁ የሚል ወገን ሁሉ ለበአሉ ግርማ ቤተሰብ ፍትህ ማግኘት የበኩሉን አስተዋፅኦ ሊያደርግ ይገባዋል የሚል እምነት አለኝ ። ይህን ያልኩበት ምክንያት በውጪም ሆነ በአገርቤት “በቃ በአሉ ግርማን ደርግ ገድሎታል ሁላችንም የምናውቀው ነውና እንተወው ፦ የሚሉ ወገኖች ስላሉ ፤ በተለይ የእያንዳንዱ ግለሰብ የግል ነጻነት ተከብሮ በሚኖርበት አውሮጳና አሜሪካ እየተኖረ ይህን የመሰለ ድፍን ያለ ድምዳሜ ላይ መድረስ በስደት ከየምንኖርበት አገር የፍትህ ስርአት የተማርነው እንደሌለና ሆዳችንን ከመሙላት በቀር ምንም ትርፍ እንዳላመጣን ማሳያ ይሆናልና ነው ።

ይህን ካልኩ በኋላ ለዛሬ አብይ ነው ብዬ ወደተነሳሁበት ጉዳይ ልምጣ ።

አቶ አስፋው ዳምጤ “በበአሉ ግርማ ጉዳይ ላይ ከህሊና እዳ ነፃ ነኝ” በሚል ርዕስ ስለ በአሉ ግርማ መሰወር ጉዳይ የሰጡትን ቃለ- መጠይቅ ፍቱን ከምትባል መፅሄት ላይ ተወስዶ በአንድ ዌብ ሳይት ላይ ተለጥፎ አግኝቼ አነበብኩትና ከቃለ መጠይቁ የተረዳሁትን ለአንባቢ ለማሳወቅ ፈልጌ ነው ።
አቶ አስፋው ፤ በመጀመሪያ በራስዎ ስም መልስ ለመስጠት በመሞከርዎ ላድንቅዎ እፈልጋለሁ ።የሰጡት መልስ አሳማኝም ይሁን አይሁን ዋናው ለቀረበብዎት ጥያቄ በቃለ-መጠይቅ መልክ መልስ ለመስጠት ሞክረዋል ። ያስመሰግንዎታል ። ከቃለ መጠይቅ ይልቅ በራስዎ ፅሁፍ የነበረውን ሁኔታ ቢገልፁልን ኖሮ ደግሞ ተመራጭ ይሆን ነበር ። አዲስ አበባ ተወልደው ስላደጉም ይሆናል በወዳጅ በዘመድ አፅፈው በጎን ለማለፍ አለመፈለግዎ ፤ ትልቅ ነገር ነው ።(በጋዜጠኛው አቀራረብ ላይ ጥያቄ ቢኖረኝም)።
ያነጋገርዎ ጋዜጠኛ እንደነገረን የመጀመሪያ ዲግሪዎን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛውን ደግሞ ከካምብሪጅ አግኝተዋል ። ከዚያም ለረጂም ዘመናት በገንዘብ ሚኒስቴር ሰርተዋል ። ከዚህ በመነሳት ትምህርትዎ የጋዜጠኝነት ወይም የስነ-ፅሁፍ እንዳልሆነና economics ሊሆን እንደሚችል ጠርጥሬአለሁ ። ተሳስቼ እንደሆን ለመታረም ዝግጁ ነኝ ። ከዚያም በመፅሃፍ ድርጅትና በኩራዝ አሳታሚ ሰርተዋል ።
ይህን ካልኩ በኋላ በቀጥታ ወደርስዎ ቃለ-ምልልስ ልምጣ ።
የደራሲ በዓሉ ግርማ ባለቤት፣ ወ/ሮ አልማዝ አበራ፣
‹‹…የካቲት 24 ቀን 1976 ዓ.ም. ቀን ላይ አስፋው ዳምጤ እቤት ስልክ ደወለ :: በዓሉ ቤት አልነበረምና፣ ስልኩን አንሥቼ ያነጋገርኩት እኔ ነበርኩ :: የእግዜር ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ፣ ‹… በዓሉ እንደመጣ እዚያ እቀጠሯችን ቦታ ባስቸኳይ እንድትመጣ ብሎሃል በዪልኝ …› ብሎ ስልኩን ዘጋ ::››
አቶ አስፋው ፡ የዚህ አጭር መልሱ “ሃሰት” ነው ። ብለዋል ።
አበራ ለማ ከበአሉ ባለቤት ከወይዘሮ አልማዝ አገኘሁት ብሎ ካቀረበው ፅሁፍ ላይ ለእርስዎ ቃለ መጠይቅ መንደርደሪያ ሃሳብ ሆኖ የቀረበው ከፊሉ ብቻ ነው ። የአበራ ለማ ሙሉውን ምእራፍ ስናነብ ነው ፈታ ያለ ግንዛቤ የሚኖረን ። እንዲህ ይነበባል ፤ እጠቅሳለሁ፦
“….የካቲት 24 ቀን 1976 ዓ.ም. ቀን ላይ አስፋው ዳምጤ እቤት ስልክ ደወለ፡፡ በዓሉ ቤት አልነበረምና ስልኩን አነስቼ ያነጋገርኩት እኔ ነበርኩ፡፡ የእግዜር ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ’… በዓሉ እንደመጣ እዚያ እቀጠሯችን ቦታ ባስቸኳይ እንድትመጣ ብሎሃል በዪልኝ…’ ብሎ ስልኩን ዘጋ፡፡ በዓሉ ወደ አሥራ አንድ ሰዓት ገደማ ወደ ቤት ሲመጣ መልእክቱን ነገርኩት፡፡ ወዲያው ሻወር ወስዶ ወጣና ለመሄድ ሲጣደፍ፣ ’እደጅ ውለህ መምጣትህ ነውና እባክህ ትንሽ እህል ብጤ ቀምሰህ ውጣ’ ብለው፤ ’አልችልም… ብርቱ ቀጠሮ አለንና ወደዚያው መፍጥን አለብኝ’ ብሎኝ ፈጥኖ ከቤት ወጣ::” የጥቅሱ መጨረሻ ።
መርምሮ ለሚያነብ ሰው የነገሩ ጭብጥ ያለው ወ/ሮ አልማዝ ከጠየቁትና አበራ ለማ ካቀረበው ከላይኛው ጥቅስ ጋር የተያያዘ ነው ። ወ/ሮ አልማዝ በስልክ መልእክት ከአቶ አስፋው ተቀብዬ ለባለቤቴ ነገርኩትና በመልእክቱ መሰረት ወደ ጓደኛው ወደ አቶ አስፋው ሄደ ነው የሚሉት ።
አቶ አስፋው የሚሉት ደግሞ የለም ስልክ አልደወልኩም ፤ ቀጠሮም አላደረኩም ፤ ሆኖም ግን ያለቀጠሮ በዚያች የመጨረሻዋ ምሽት በአሉን አግኝቼዋለሁ ነው ። እዚህ ላይ አንድ መሰረታዊ ጥያቄ ይነሳል ። ይኸውም ወይዘሮ አልማዝ ከአቶ አስፋው ጋር ጠብም ወዳጅነትም ቅርርብም የላቸውም አቶ አስፋው ዳምጤ እንደነገሩን ። ይህ ከሆነ ደግሞ ለምን ወይዘሮ አልማዝ እስካሁን ድረስ የምታውቀው ነገር አለና ንገረኝ ብለው አቶ አስፋውን ያስጨንቃሉ ፤ ለምን ሌሎቹን የበአሉ ጓደኞች አንደ አቶ አስፋው ሁሉ ጠይቀው አያውቁም ? ሌላው ደግሞ በመጨረሻዋ በአሉ በተሰወረባት ምሽት ፤ በአሉ ወደቤቱ ስላልተመለሰ ለወይዘሮ አልማዝ ከአስፋው ጋር አመሸሁ ብሎ አልነገራቸው ፤ ከእርስዎ ጋር ማምሸቱንስ ወ/ሮ አልማዝ እንዴት አወቁና ነው ወደቤትዎ የደወሉት ፤ ቀድመው ወደቤት ደውለው በወይዘሮ አልማዝ በኩል ለበአሉ ቀጠሮ ካልሰጡ ? አቶ አስፋው ወ/ሮ አልማዝ ወደቤቴ አልደወለችም ብለው ቢያስተባብሉም ጠዋት ላይ ወደስራዎ ደውለው እንደተነጋገሩ ደግሞ አልካዱም ። ወይዘሮ አልማዝ ባለቤቴ በአሉ ግርማ ማታ አልገባምና የምታውቀውን ንገረኝ ብለው ሲጠዩቅዎ “ አይቼዋለሁ ግን” ብየ የምለው ጠፋኝና ፤ የምለው ጠፋኝና ነው ያሉት ! ለምን የሚሉት ጠፋዎት ? አሁን የሚነግሩንን መገናኛችሁ አጠገብ ቆመን አንድ አንድ ብለን ተለያየን ብለው ለምን አልነገሯቸውም ለወ/ሮ አልማዝ ። ይህን ብለዋቸው እስቲ ደግሞ ከሌሎች ሰዎች ላጣራ ብለው ቢሆን ኖሮ የተናገሩት እውነት ይመስል ነበር ። አንድ ሰው የሚለው የሚጠፋው አንድ የሚያውቀው ነገር ሲኖርና ለዚያ መልስ ሳይዘጋጅ ድንገት ጥያቄ ሲቀርብበት ነው ። ወዲያው የሚያስገድደው ሁኔታ እስካልተፈጠረ ድረስ የመዘጋጃ ጊዜ ለመግዛት ዘዴ ይቀይሳል ። አቶ አስፋው ለርስዎ ጊዜ መግዣ አድርገው የተጠቀሙበት “ አሁን አንድ ትልቅ ባለስልጣን ዘንድ ስለምሄድ እሱን ጠይቄ እነግርሻለሁ ብለው ዛሬ በህይወት የሌሉትን ሰው ለማ ጉተማን ምስክርነት መጥራት ነው ። እስቲ ቆም ብለው ያስቡት ለራስዎም አልገረመዎትም ?
ሌላው ወ/ አልማዝ የተናገሩትን ለማስተባበል ማስረጃ አድርገው የተጠቀሙበት የሬይደልፍ ኬ ሞልቬርን Reidulf K. Molvaerን ብላክ ላዮንስ Black Lions የተባለው መፅሃፍ ላይ ደራሲው በአሉ ግርማ በጠፋባት በዚያች ምሽት ያቀረበውን ትንተና ነው ። በአጭሩ መፅሃፉ ላይ እርስዎ በአሉን መጥተው ከቤቱ ወሰዱት አይነት አቀራረብ ስለሆነ አንዴ ስልክ ደውሎ ቀጠሮ ሰጠው ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ከቤቱ መጥቶ ወሰደው ተብሏልና አንዱን ይምረጡ ነው አባባልዎ ። መፅሃፉ ላይ እኮ ወ/ሮ አልማዝ እንደነገሩኝ ብሎ አልፃፈም ሞልቬር ፤ ስለዚህ ሞልቬር ይህን ነጥብ ከየትም ሊያገኘው ይችላል ። ሞልቤር ስህተት ፈፅሞ ከሆነ እንኳን ወ/ሮ አልማዝን ምርጪ አትምረጪ ሊያሰኛቸው አይችልም ። መፅሃፉ ላይ ለወጣው ፅሁፍ ተጠያቂ መሆን ያለበት ሞልቬር ብቻ ነው ። ታዲያ እኮ ሞልቬር እዚያው ገፅ ላይና እዛው ፓራግራፍ ላይ የጠቀሳቸው ነጥቦች ነበሩ ፤ እርስዎ ሳያዩአቸው አልፈዋል ወይም ሆን ብለው ዘለዋቸዋል ። ሞልቬር እንዲህ ይላል እዚያ ላይ ፤ እርስዎ አቶ አስፋው በአሉ ከተሰወረባት ከመጨረሻዋ ቀን አስራ አምስት ቀን በፊት ነው በአሉን ያየሁት ብለው ለሌሎች ሰዎች ተናግረዋል ብሏል ። ይህም ወ/ሮ አልማዝ ከተናገሩትና ከሚሉት ጋር ባለመግጠሙ ሰዎች ደንቆቸዋል ሲል ፅፏል ፤ ይህን ነጥብ ይያዙ ። ቀጥሎም እንዲህ ይላል ሞልቬር (ስም ባይጠቅስም) ምንልባትም ይህ ጓደኛው ፤ ላደረገው አብዮታዊ አስተዋፅኦ መንግስታዊ ለሆነው ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት በዚያኑ ሰሞን ስልጣን ተሰጠው ፤ ብሏል ። ሞልቬር ብላክ ላዮንስ በሚለው መጽሃፉ ላይ ያስቀመጠው እንዲህ ይነበባል ገፅ 348 ፦ To other people he ( the friend ) said that he had not seen Be’alu for two weeks before he disappeared, and they were surprised to hear another story from Be’alu’s wife . Soon after the friend got ( perhaps as areward for his contribution to the revolutinary cause ) a high position with Kurraz , the government publishers.
እዚህ ላይ አንድ ነገር ትዝ አለኝ ። አበራ ለማ የሰዎች ስም አጠፋ የርስዎን የአቶ አስፋው ዳምጤን ጨምሮ እየተባለ ሲጠቀስ በየመጣጥፉ ላይ አንብቤ ነበር ። የእርስዎም ብሶት አበራ ለማ ስሜን አጥፍቷል ነው ። ከዛሬ 17 አመታት በፊት በ1997 እ.አ.ኤ ሞልቬር ይህንኑ ፅፎት የለም እንዴ ያውም ዘላለማዊ ሆኖ በሚቀር መፅሃፍ ላይ ! ምነው አበራ ለማ እንዚህን መረጃዎች ሰብስቦ ሲፅፍ ድንቅ ሆነ ?
አቶ አስፋው ሌላው ያሳዘነኝን ሳልገልፅልዎ ማለፍ አልፈልግም ። ጋዜጠኛው ከአበራ ለማ ጋር ቅራኔ ነበራችሁ ? ብሎ ይጠይቅዎታል ። መሆን የነበረበት ከቮልቴር ጋር ቅራኔ ነበራችሁ ? ነው ። እርስዎም ሲመልሱ “ እኔ ከእርሱ ጋር ቅራኔ ውስጥ ገብቻለሁ ብየ አስቤ አላውቅም ብለው ነበር ። ይህ የጨዋ መልስ በቂ ነበር ። በተረፈ ከዚያ አልፎ ከዛሬ 37 አመታት በፊት የተደረገን ስነፅሁፋዊ ክርክር ቂም በቀል አድርጎ ለማቅረብ መሞከርና በዚያ አስታኮ ስሙ ያልተጠቀሰ አስተማሪው እንዲህ ብሎ አለው ብሎ በማለት ሰውን በሾርኒ ለመስደብ መሞከር ትንሽነትን የሚያስይ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ። በስነፅሁፍ ቅስሙ ቢሰበር ኖሮማ አበራ ለማ አሁን ይህን የመሰለ ኢንቬስቲጌቲቭ ስራ ባላቀረበልን ነበር ። በነገራችን ላይ አበራ ለማን ከፅሁፉ በስተቀር ጥቁር ይሁን ቀይ ሰልካካ ይሁን ኩርፋድ አላቀውም ። አስተያየቴ በሙሉ በአሉ ግርማን አስመልክቶ ከፃፈው ጋር የየያያዘ ነው ። በርግጥ ሌሎች የግጥም ስራዎቹንም አውቃለሁ ቅስሙ አልተሰበረም ህያው ነው ለማለት ነው ። እውነቱን ለመናገር እርስዎን ቃለ-መጠይቅ ካደረገልዎ ጋዜጠኛ ነው የድርሰት ስራዎች እንዳሉዎትም የሰማሁት ። ልጅ ሆኜ የአንደኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁ ነው መፅሕፍትን የማንበብ ልምድ የተጥናወተኝ ። ካነበብኳቸው ውስጥ አንዱ ርዕሱ “ከልታማዋ እህቴ” ይላል አሁን የዚህን መፅሃፍ ደራሲ ማን እንደ ደራሲ ቆጥሮ ያስታውሰዋል !
ወደ ወ/ሮ አልማዝ አበራ ልመለስ ። እኔ እንደገባኝ ከሆነ የወ/ሮ አልማዝ ጥያቄ አቶ አስፋው ባለቤቴን በአሉን ገድለዋል ፤ ወይም በግድያው ላይ እጃቸው አለበት አይደለም ። በኦሮማይ ምክንያት ህይወቱ እንዳለፈም ያውቃሉ ። የሳቸው ጥያቄ ግን አንድና አንድ ብቻ ነው ። የሟች ባለቤቴን የሞት መንገድ ፍለጋ ላይ ነኝ መዳረሻውን ላለፉት 30 አመታት እየፈለኩ ነው ። የዚያች መንገድ መግቢያ ቁልፍ አቶ አስፋው እርስዎ እጅ ላይ ይገኛልና ለፍትህ ብሎም ለህሊናዎ ሲሉ ይጠቁሙኝ ነው ። አቶ አስፋው ወ/ ሮ አልማዝ ልብ ውስጥ እንደማንኛውም ሰው ሊመላለስ የሚችለውን ስሜት ሊረዱት ይገባል ። የውድ ባለቤታቸውን ደብዛ እየፈለጉ ያሉ ናቸውና ። ቀያፋ ላዘዛቸው ሮማውያን ወታደሮች ጲላጦስ እየሱስን በግላጭ ጉንጩን ስሞ አሳልፎ ሰጥቶታል ብለው ቢያስቡስ ወ/ሮ አልማዝ ላይ ይፈረዳል ?
አቶ አስፋው ሌላው ያሳዘነኝን ሳልገልፅልዎ ማለፍ አልፈልግም ። ወ/ሮ አልማዝ ላይ ለምን ጠየቀችኝ ከሚል ቅሬታ ተሰምቶዎታል ስለዚህም አቂመውባቸዋል ። ወ/ሮ አልማዝ ጋር በስራ ምክንያት የሚያገናኛችሁና በዚህ ተቀይማኛለች በማለት ሊያቀርቡት የሚችሉት ምክንያት ሊኖር አልቻለም ። እና የሞተውን ባላቸውን በአሉን ሌላ ውሽማ ነበረችው በማለት የሴትነት ብቃታቸውን ለማዋርድ ሞከሩ ። ባልሻረ ቁስላቸው ላይ ጨው ነሰነሱበት ። ምን አይነት ጭካኔ ነው ! አዝናለሁ እንዲህ በማለቴ ፤ እንዲያውም ወራዳነት ነው ። የገባበትና አፅሙ እንኳ የት እንደወደቀ ያልታወቀ ሙት ወዳጁን አጽም ፤ ሰው እንዴት ይግጣል ። ቤተሰቡን ለማስቀየምስ ለምን ይቸኩላል ። ከራስዎ ጥያቄና መልስ ልነሳና ይህን ራስዎ የፈጠሩት መሆኑን ደግሞ ላስረዳዎ አቶ አስፋው ።
ጠያቂው ጋዜጠኛ ቀድሞ የተዘጋጀበት በሚመስል መልኩ ከመሬት ተነስቶ አንድ ጥያቄ ያቀርብልዎታል ። በአሉ እርስዎጋ ከመድረሱ በፊት ይት ቆየ ብለው ነው የገመቱት ? ይልዎታል ። ከዚያ አስቀድመው እርስዎ ካላዘጋጁት በቀር የበአሉን መቆያ ቦታ ሐሳብ ከዬተ አመጣው ? የቃለ- መጠይቁን ቁራሽ እነሆ
ፍቱን ፦ በአሉ እርሶ ጋ ከመድረሱ በፊት የት ቆየ ብለው ነበር የገመቱት ?
አቶ አስፋው፦ጥቂት ቀደምብሎ እዚያው አካባቢ ወዳጅ እንደነበረው ተገንዝቤ ነበር ።
ፍቱን፦ የማን ቤት ነው?
አቶ አስፋው ፦ እሱን አልውቅም ።
ፍቱን፦ወንድ ሴት?
አቶ አስፋው ሴት ።
ፍቱን፦ በዚያች እለት ምሽት እዚያ ቆይቶ ከተመለሰ በኋላ ነበር ከእርሶ ጋር የተገናኛችሁት ?
አቶ አስፋው፦ እንደዚያ ነበር አመጣጡን ሳይ የገመትኩት ።
ወዳጅ እንደነበረው ተገንዝቤ ነበር ። ተገንዝቤ ነበር የሚለውን ቃል መጠቀም የሚቻለው ለትምርት ለእውቀት ሲሆን ነው ። ውሽማ ነበረችው ለማለት ግንዛቤ አያሻውም አውቅ ነበር ነው የሚባለው ፤ ፈጠራዎን ግዝፈት ለመስጠት ግዙፍ ቃል ተጠቀሙ ። ይህ የሚያሳየው ደግሞ ራስዎም የተናገሩትን እንዳላመኑበት ነው ። እዚያው ላይ ዝቅ እንበልና የማን ቤት ነው ? ሲል ይጠይቃል ጋዜጠኛው ። አቶ አስፋው እሱን አላውቅም ሲሉ ይመልሳሉ ። ወንድ ሴት ይልዎታል ጋዜጠኛው ። የእርስዎ መልስ ደግሞ ሴት ይላል ። የማን ቤት መሆኑን ከላይ ሲጠቅሱ አልውቅም ካሉ በኋላ ፤እንዴት የሴት ቤት መሆኑን አወቁ ? እርስዎ ጋር ከመገናኘቱ በፊት ደግሞ ውሽማውጋ ቆይቶ ነው የመጣው ? ሲልዎ ጋዜጠኛው ፣ እንደዚያ ነበር አመጣጡን ሳይ የገመትኩት ይላሉ እርስዎ ። ለካ ግምት ነው የተረጋገጠ ማስረጃ የለዎትም ! ታዲያ በስድስት አረፍተ ነገሮች ወስጥ ሶስት የተለያዩ የተምታቱ ነገሮችን ማቅረብ ወ/ሮ አልማዝን ለመስደብ የተፈጠረ ቅጥፈት መሆኑን አያሳይም ?
አንዳንድ ነጥቦችን ላንሳ ፤
1)በአሉ ግርማ ከወደአንዲት ሴት ቤት መምጣቱን ገመትኩ አሉ፡
2) ኮማንደር ለማ ጉተማን ምስክርነት ጠሩ ፤በህይወት የሌለ ሰው ፡
3)ስሙን ያልጠቀሱትን የአበራ ለማን መምህር ፤ እንዲህ ብሎ አለው አሉ ፡
4)ወ/ሮ አልማዝ መስሪያ ቤትዎ ደውለው ሲያነጋግሩዎ የሚሉት ጠፋብዎ ፡
5)አበራ ለማ በግጥሙ ምክንያት አደረገ ላሉት ክርክር ምስክር አድርገው አሁንም ያቀረቡት በህይወት የሌለውን ስብሃት ገ/እግዚአብሄርን ነው ።
ከተደረገልዎ ቃለ-መጠይቅ ላይ ከሰጧቸው መልሶች የቱን ተቀብለን የቱን እንተው ፤ የትኛው እውነት የትኛው ሃሰት እንደሆነስ በምን እናረጋግጥ ?
እስቲ እኔም እንደርስዎ ልገምት speculate ላድርግ በአሉ ግርማ ከሌላ ሴት ቤት መጣ ብየ ገመትኩ እንዳሉት ማለት ነው ። ከዚያ በፊት በደህናው ጊዜ በአሉ ከደሞዙ ሌላ በድርሰት ስራዎቹ የሚያገኘው ጠቀም ያለ ገንዘብ ነበረው ። እርስዎም ተቸግረው ከበአሉ ገንዘብ ተበድረው ነበር ። ያን ገንዘብ ሊከፍሉት አልቻሉም ወይም አልፈለጉም ። በመጨረሻዋ እለት ላለፉት 6 ወራት ስራ ስላልነበረው የተበደረውን ገንዘብ ሊከፍለኝ ነው ብሎ ይሆን እንዴ ለወይዘሮ አልማዝ በሰጧቸው ቀጠሮ አማካይነት ከቀጠሮው ስፍራ የደረሰው ። በቃለ- መጠይቅዎም ላይ እኔና እሱን ብቻ የምትመለከት የግል ጉዳይ ነበረችን ብለዋል ከገንዘብ ብድር ጋር የተያያዘች ትሆን ? በአሉን ሰዋራ ስፍራ ድረስ በመውሰድ ለደርግ ሰዎች ማስረከብ እርስዎን ከገንዘብ እዳ ነጻ ሲያደርግዎ ፤ ደርግ ተረጋጋሁ ባለበት በዚያ ዘመን በኦሮማይ እርቃኑን ያስቀረውን የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣኑን በአሉን ያለግርግር እርስዎ ከወሰዱበት ስፍራ በቀላሉ ማፈን ችሏል ማለት ይሆን ?
አቶ አስፋው ፤ አንድ ነገር እንዲያስቡ እፈልጋለሁ ። ላለፉት 30 አመታት የውድ ባለቤቴን መውደቂያ እፈልጋለሁ ብላ ያለድካም የምትተጋ አንድ ወይዘሮ በቤቷ ውስጥ ምን ያህል ፍቅር እንዳለ ማሳያ ናት ። ለባለቤቷም ሆነ ለራሷ የፍቅር ተምሳሌት ናት ። እንዲህ አይነት ሴት ደግሞ ለማይነጥፍ የቤት ውስጥ ፍቅር ምንጭ ናት ። እንደማናቸውም ድንቅ ደራስያን ሁሉ በአሉ ግርማም ከቤቱ ያገኘው የነበረው ፍቅር ለድርሰት ስራዎቹ ሁሉ ፅኑ መሰረት ሆኖት ለኛም ለአንባቢዎቹና ለአድናቂዎቹ የድርሰቶቹ ትሩፋት ደርሰውናል ።
ለዛሬው በዚሁ ላብቃ ።

ከአንበሳው ይብራ !

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የኢትዮጵያ መንግሥት በመላይቱ ሀገር ከ350 ሺህ ለሚበልጡ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች 15 ቀን የዘለቀ ስልጠና ሰጥቶዋል።በዕረፍት ላይ ያሉት ተማሪዎች ስልጠናውን በሚገኙበት አካባቢ ባሉ የትምህርት ተቋማት ውስጥ እንዲከታተሉ መደረጉም ተሰምቶዋል። የስልጠናውን ይዘት እና ዓላማ የመወያያ ርዕስ አድርገነዋል።

ዩኤስ አሜሪካ ኢራቅ ሃዲታህ የተሰኘ ግድብ አካባቢ ራሱን እስላማዊ መንግሥት «IS» ብሎ በሚጠራዉ ቡድን ላይ የአየር ድብደባ ማካሄድዋን ገለፀች።በሌላ በኩል ሊባኖስ ዉስጥ IS በመባል የሚታወቀዉ አክራሪዉ እስላማዊ ቡድን አፍኖ የወሰደዉን ሊባኖሳዊ ወታደር አንገት መቀላቱን የሚያሳይ ቪዲዮ መሰራጨቱ ተዘገበ።

ዩኤስ አሜሪካ ኢራቅ ሃዲታህ የተሰኘ ግድብ አካባቢ ራሱን እስላማዊ መንግሥት «IS» ብሎ በሚጠራዉ ቡድን ላይ የአየር ድብደባ ማካሄድዋን ገለፀች።በሌላ በኩል ሊባኖስ ዉስጥ IS በመባል የሚታወቀዉ አክራሪዉ እስላማዊ ቡድን አፍኖ የወሰደዉን ሊባኖሳዊ ወታደር አንገት መቀላቱን የሚያሳይ ቪዲዮ መሰራጨቱ ተዘገበ።

በሰሜን አሜሪካው የኢትዮጵያዊያን ስፖርትና ባህል ፈዴሬሽን የቦርድ አባላት መካከል አለ የተባለውን አለመግባባት መነሻ በማድረግ ለመፍትሔ ፍለጋ ይረዳ ዘንድ በአሜሪካ ድምፅ የአማርኛው አገልግሎት፣ የራድዮ መፅሔት ዝግጅት፣ ቀጣዩን ተከታታይ ውይይት አዘጋጅቷል።