የዩክሬን ፤የምሥራቅ ምዕራቦች መሻኮቻ ሐገር
ባለፉት አስምስት ወራት ብቻ ከሁለት ሺሕ በላይ ሰዉ ሞቷል።በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ተሰዷል።በስንዴ ምርቱ ከዓለም የታወቀዉ ግዛት፤በነፋሻ አየሩ የሚወደደዉ ያ ግዛት እየጠፋ ነዉ።
ባለፉት አስምስት ወራት ብቻ ከሁለት ሺሕ በላይ ሰዉ ሞቷል።በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ተሰዷል።በስንዴ ምርቱ ከዓለም የታወቀዉ ግዛት፤በነፋሻ አየሩ የሚወደደዉ ያ ግዛት እየጠፋ ነዉ።
ኢራቅ ዉስጥ ለሚገኙ የኩርድ ተወላጆች የጦር መሣሪያ እናቅርብ የሚለዉ ሃሳብ ባለፉት ሳምንታት እዚህ ጀርመን ሲነሳ ሁለት የተለያዩና የሚፃረሩ አስተያየቶች ባለፉት ቀናት ተሰምተዋል። በእነዚህ ነጥቦች ላይም ሰሞኑን ፖለቲከኞቹ ሲከራከሩበት ሰንብተዋል።
ጥያቄው የለውጥና የነጻነት ነው ። ለለውጥ እንትጋ !!! ነፃነታችን በጃችን ላይ ነው፡፤ !!!
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
አዎ የኛ የኢትዮጵያውያን ጥያቄ የግለሰቦች በስልጣን ወንበር ላይ መፈራረቅ ሳይሆን ጥያቂያችን የለውጥ ጥያቄ ነው። የፖለቲካ አስተዳደር ለውጥ የኑሮ ውድነት የሚያላቅቅ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለውጥ በጋራ ህብረተሰባዊነት ላይ የተመሰረት የማህበራዊ ፍትህ እኩልነት ለውጥ የነጻነት እና የመብት ማግኘት ጥያቄ በሃገራችን ተዘዋውረን በፈለግነው ቦታ የመስራት እና የመኖር ጥያቄ የመሳሰሉት ለውጦች በሃገራችን ላይ የሃገራችን ባለቤቶች ስንሆን የ ሚገኘው ብልጽግና እና እድገት ባለቤት መሆናችንን የሚያረጋግጥልን ለውጥ እንፈልጋለን፡፡
የጉልቻ መለዋወጥ ከሆነ እንደ ለውጥ የሚታየው በኢትዮጵያውያን የ እለት ከእለት የሕይወት ሂደት ውስጥ ድህነት እና ነጻነት ማጣት እንጂ ምንም አይነት የፈየደው ነገር አለመኖሩን ከሃይለስላሴ ጀምሮ ያየነው ነው፤ መንግስቱ ሓ/ማርያም መጣ ሄደ መለስ ዜናዊ መጣ ሄደ አሁንም ጠቅላይ ተብሎ ተሾመልን ይህም ጉልቻውን ለፖለቲካ ማጣፈጫ ሆነ እንጂ እንኳን ሊያስተዳድረን ይቅር እና የገዛ አንገቱን እንኳን ማዘዝ አልቻለም፤ ታዲአ የዜጎችን የለውጥ ጥያቄ ጉልቻ በመለዋወጥ መመለስ እንደማይቻል በይፋ እያየነው ነው፡፡
የኛ የለውጥ ጥያቄ የህዝቦችን የዜግነት መብቶች የሚያረጋግጥ እንጂ በውጭው አለም እና በሃገር ውስጥ ብሄራዊ ውርደት የሚያከናንብ አስተዳደር አይደለም፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ በተስኪያናችንን እና መስኪዳችን እንዲሁም ታሪኮቻችንን የሚያረክስ የፖሊስ እና የጦር ሰራዊት ለውጥ ሳይሆን የነጻነት እና የመብት ጥያቂያችንን በህገመንግስት መሰረት የሚያስከብርልን አስተዳድር ነው፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ በኑሮ ውድነት አደባይቶን በሙስና ጥቂት ሃብታም ብዙ ደሃ የሚፈጥር ዋሾ አስተዳደር አይደለም፡፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ ህዝባዊ መሰረት ያለው ሚዲያ እንጂ በግምት የሚደሰኩር ውሸታም ሚዲያ አይደለም፡፤በአጠቃላይ የለውጥ ጥያቄያችን የባሰ እና የበሰበሰ መንግስት እንዲያስተዳድረን ሳይሆን እንደ ሃገር ባለቤትነታችን መብታችንን አስከብሮ በነጻነታችን እያኖረ ሃገራዊ ሃላፊነት እና ግዴታ እንዲሰማን የሚያደርግ መንግስት እንጂ የጉልቻ ተፈራራቂ አምባገነን ንግስና አይደለም፡፡
ኢትዮጵያውያን ለውጥ እንፈልጋለን ስንል የለውጥ ጥያቂያችንን መከለያ አድርጎ የስልጣን ጥሙን የሚያረካ የፖለቲካ ድርጅት እና የፖለቲካ ወያላ አንፈልግም፡፤ የኛን የለውጥ ጥያቄ ለፖለቲካ አጀንዳቸው ተጠቅመው ነጻነታችንን የሚያስነጥቁን የፖለቲካ ድርጅቶችን አንናፍቅም፡፤እኛ በፈረንጅ ቋንቋ የተገነባ የዲሞክራሲ ንግድ በነጻነታችን ላይ እንዲሰራፋ አንፈልግም። ኢትዮጵያውያን ነጻነታችን ያለው በፈረንጆች ሳይሆን በ እጃችን ላይ ስለሆነ እያንዳንዳችን ነጻነታችንን ለማስመለስ መረባረብ ግድ ይለናል። ጥያቂያችን የምእራብ ዲሞክራሲ ሳይሆን በነጻነት የመኖር ትያቄ ነው፡፤ ለለውጥ አሁንም እንጮሃለን። ፈረንጅ ለራሱ አጽድቆ ያራባውን ዲሞክራሲ ከነጻነት በኋላ እንደርስበታለን።
የዲሞክራሲ ትርጉም ቢገባንም ገዢዎቻችን ግን ለለበታ ስለሚጠቀሙበት በቋንቋችን ነጻነት ለውጥ እያልን እንዘምራለን፡፤ለለውጥ በጋራ በመነሳት ነጻነታችንን በትግላችን መቀናጀት ግድ ይለናል። በሃገራችን እና በነጻንትችን ላይ ባለቤቶች እንደሆንን ሃላፊነት ሊሰማን ስለሚገባ ነጻነታችንን ራሳችን ማረጋገጥ አለብን እንጂ የማንም ችሮታ እንዳልሆነ ተገንዝበን በጋራ ለለውጥ መነሳት ግዲታችን ነው። ነጻነታችን በ እጃችን ስለሆነ ዛሪውኑ ለማስመለስ እንትጋ።
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ተሰደደ።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በተለያዩ ጋዜጦች፣ መፅሔቶች የራሱ “አዲስሚዲያ” ብሎግን ጨምሮ በተለያዩ ድህረ-ገፆች አዘጋጅ እና ፀሐፊ ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤል መሰደዱ ታወቀ፡፡ ጋዜጠኛው ቀደም ሲል የፍኖተ-ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጅ፣የኢቦኒ መፅሔት ዋና አዘጋጅ፣ በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው ኢሳው መፅሔት ባልደረባና አምደኛ፤ በኢትዮ-ምህዳር ጋዜጣና በቅርቡ ወደህትመት የገባው ቀዳሚ ገፅ ጋዜጣ ላይም የተለያዩ የፖለቲካ፣ ሰብዓዊ መብት ጥሰትና ማኀበራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ በራሱና በብዕር ስም እንደሚፅፍ ይወቃል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተመሰረተውና በመንግስት ከፍተኛ ቁጥጥርና ጫና ላይ የወደቀው የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) መስራች አባል፤ በኋላም የማኀበሩ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ በመሆን እያገለገለ እንደነበር ይታወቃል፡፡
ጋዜጠኛው ከዚህ በፊትም በመንግስት ደህንነት ኃይሎች በምሽት እገታ እንደገጠመው፣ ከስልክ ጠለፋ እስከ ዛቻና ማስፈራራት ይደርስበት እንደነበር ከዚህ ቀደም የወጡ መረጃዎች ቢያመለክቱም፤በተለይ ከጥቅምት 2006 ዓ.ም. ከአዲሱ ጋዜጠኞች ማኀበር መመስረት ሂደት ጀምሮ እና በሚያዚያ ወር 2006 ዓ.ም. 3 ጋዜጠኞችን እና 6 የዞን 9 ብሎገሮች በመንግስት ከታሰሩ በኋላ የመንግስት ደህንነቶች ክትትል ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉንና ቀጣዩ እስር እሱ ላይም ሊፈፀም እንደሚችል በመረዳት ለቅርብ ጓደኞቹ አሳውቆ ነበር፡፡
ብስራት ባለፈው ነሐሴ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. አርብ ጠዋት አዲስ ባወጣው የስልክ መስመር የማዕከላዊ ስልክ ጥሪ ካስተናገደ በኋላ ለጊዜው ከአዲስ አበባ ውጭ መሆኑን በማሳወቅ ለሰኞ እንደሚቀርብ ምላሽ ከሰጠ በኋላ ባለፈው እሁድ ድንገት ሀገር ጥሎ መሰደዱ ታውቋል፡፡
በቅርቡ ከታሰሩት ጋዜጠኞችና ብሎገሮች የእስር ስም ዝርዝር ውስጥ የማኀበሩ አመራሮች መኖራቸውና በቀጣይም መንግስት በአመራሮቹ ዙሪያ መረጃ እየሰበሰበ መሆኑ ምንጮች አረጋግጠው እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ቀደም ሲል የማኀበሩ ፕሬዘዳንት ጋዜጠኛ በትረ ያዕቆብ፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ጋዜጠኛ ዘሪሁን ሙሉጌታ፣ ገንዘብ ያዥ ጋዜጠኛ ሃብታሙ ስዩም እና መስራች አባል ጋዜጠኛ ተሰማ ደሳለኝ መሰደዳቸው አይዘነጋም፡፡ በአጠቃላይ ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤልን ጨምሮ በ2006 ዓ.ም. ብቻ 25 የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ሲሰደዱ፤3 የውጭ ዜጎች ጋዜጠኞችን ጨምሮ 20 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች ደግሞ በእስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡
ኦሕዴድ ከኢህአዴግ ተለይቶ ራሱን የቻለ ፓርቲ እንዲሆን የሚፈልግ ቡድን ተነስቷል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በዚህ በያዝነው ነሃሴ ወር ውስጥ ብቻ የሕወሓት/ብአዴን ከፍተኛ አመራሮች እና አንጋፋ ታጋዮች የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እና የደቡብ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትን ባገለል እና ባላሳተፈ በተከታታይ የተደረጉ ተደራራቢ ስብሰባዎች በኦሕዴድ አመራሮች ዘንድ ጥያቄን ያጫረ ሲሆን በደሕዴግ አመራርች ዘድ ደሞ የዝምታ ድባብ እንዲያጠላ በማድረጉ በኢሕአዴግ ድርጅቶች መካከል በአዲስ መልኩ የውስጥ ፍጥጫ ማየሉን የድርጅቱ መረጃዎች ጠቁመዋል።
የኦሕዴድ አመራሮች በኢሕአዴግ ውስጥ የሚደረጉ ስብሰባዎች ለምንድነው የድርጅታችንን ሰዎች የሚያገሉት የሚሉ ጥያቄዎች ስእሞኑን ለሙክታር ከድር እና ለአባዱላ ገመዳ የቀረቡ ሲሆን እስከመቼ በሕዝብ ተተፍተን በሃይል ብቻ ለመኖር እንችላለን ኦሕዴድ ከኢህአዴግ ተለይቶ ራሱን የቻለ ፓርቲ በመሆን ተሃድሶ እንዲያደርግ ካልሆነ ድርጅቱ ከአንድ አካል የበላይነት የሚላቀቅበት መፍትሄ እንዲፈለግ ሲሉ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።
በዚህ ወር ወስጥ ኢሕአዴግን ለማዳን በሚል የተለያዩ ስብሰባዎች በቀድሞ አንጋፋ ታጋዮች በሆኑት እና በሲቪል እና ውታደራዊ ስልጣን ላይ ባሉት የሕወሓት እና የብአዴን አመራሮች ተከታታይ ስብሰባዎች እየተደረጉ ሲሆ የወያኔው ጁንታ ዜጎች እየሰበሰበ በማሰር እና በሕዝቡ ዘንድ በሃሰት ፕሮፓጋንዳ እንድሁም ስም በማጥፋትና በተለያዩ እኩይ ተግባሮቹ በውጪም በውስጥም በደረሰበት የፖለቲካ ኪሳራ ለመጪው አመታት ሕዝቡን እንዴት አታሎ እና አጭበርብሮ መግዛት እንዳለበት እቅድ እያወጣ ሲሆን ለአዲስ አመት መጀመሪያም የኢሕአዴግ አመራሮችን ሰብስቦ መመሪያ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ወያኔ ሲፍረከረክ አጋጣሚዎችን መጠቀም እስካሁን ያልቻሉት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አሁንም በወያኔ ላይ የደረሰውን ኪሳራ ትጠቅመው አፋጣኝ የፖለቲካ ድሎችን በማስመዝገብ የበሰበሰውን ስርአት ወደ መቃብር እንዲወርድ ያላሰለስ ትግል ማድረግ አለባቸው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራል።
‹‹ጠበቆቻቸው በእየዕለቱ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመጣስ በሰፊ የፖለቲካ ዘመቻ የተጠመዱ ናቸው፡፡›› ገጽ 46
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
ባለፈው ሳምንት ለተማሪዎች በሚሰጠው ስልጠና ቴዲ አፍሮና ሰማያዊ አጀንዳ መሆናቸውን መግለጻችን ይታወሳል፡፡ በአሁኑ ወቅት ስልጠናው ወደ ሙስሊሙ እንቅስቃሴና የኮሚቴው ጠበቃዎች መዞሩን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሚሰጠው በዚህ ስልጠና የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊና መንግስት የሙስሊሙ ጉዳይ እልባት እንዲሰጥ የጠየቁ አካላት በአክራሪነት ፈርጇቸዋል፡፡ ‹‹የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ፈተናዎች›› በሚለው ሰነድ የሙስሊሙ ማህረሰብ እንቅስቃሴ ደም ለማፍሳሰስ እየጣረ እንደሚገኝ ይገልጻል፡፡
ከዚህም ባሻገር የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠበቆች ከጥብቅና ይልቅ የፖለቲካ ስራ እንደሚሰሩ በሰነዱ ላይ ተጠቅሷል፡፡ በሰነዱ ገጽ 46 ላይ ‹‹ጠበቆቻቸው በእየ ዕለቱ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመጣስ በሰፊ የፖለቲካ ዘመቻ የተጠመዱ ናቸው፡፡›› ሲል ያትታል፡፡
ሰነዱ ለስርዓት ግንባታ እንቅፋት ናቸው የሚላቸው የሁለቱንም እምነት ተከታዮች ሲሆን ‹‹በክርስትናም ሆነ በእስልምና ሽፋን አገራዊ አጀንዳዎችን አስቀድመው ከሚፈታተኑን ኃይሎች ባልተናነሰ ደረጃ ደግሞ በሚያገኙት የገንዘብ ጥቅማጥቅም ተደልለው አገራችን የጀመረችውን የእኩልነት ጉዞ የሚያጥላሉ፣ ህገ መንግስታዊ ስርዓታችንን ጥላሸት የሚቀቡ ኃይሎች አሉ፡፡›› ሲል የሁለቱን እምነት ተከታዮች ይወቅሳል፡፡
ሰልጣኞቹ የላኩልንን የሰነዱ ክፍል እንደሚከተለው አያይዘነዋል፡፡
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ሰሞኑን ፕሮፌሠር መሥፍን ወልደማርያም «ሸገር» ከተሰኘ በኤፍ.ኤም. 102.1 (FM 102.1) ከአዲስ አበባ መርኃግብሩን ከሚያሠራጭ የሬድዮ ጣቢያ ጋዜጠኛ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ «ዐማራ» የሚባል ነገድ በኢትዮጵያ አለመኖሩን ልባቸውን ነፍተው ሲናገሩ ተደምጠዋል። ፕሮፌሠር መሥፍን በዚህ ቃላቸው፣ በ፲፱፹፫(1983)ዓ.ም. ከሟቹ የትግሬ-ወያኔዎች መሪ መለስ ዜናዊ ጋር በቴሌቪዥን ቀርበው ስለ ዐማራው ነገድ ያለመኖር ያንጸባrmቁትን አቋም አፅንዖት በመስጠት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ዐማራ የሚባል ነገድ በኢትዮጵያ ውስጥ «አለ» ወይስ «የለም» ብሎ፣ በላ! ልበልሃ! ወደሚል እጅግ የወረደ ክርክር የሚገባ ጤነኛ አዕምሮ ያለው ሰው የለም። እንዲህ ዓይነት ክርክር ውስጥ የሚገባ ሰው፣ ኃሣቡ ተቀባይነትን እንዲያገኝ ተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ የማይችል የፕሮፌሠር መሥፍን ዓይነቱ ሰው ብቻ ነው። ለነገሩ በዚህ የቀን ቅዠት አቋም የሚፀና ካለ ከፕሮፌሠር መሥፍን ሌላ ጤነኛ አዕምሮ ያለው ሰው ይገኛል ተብሎ አይታሰብም። የፕሮፌሠር መሥፍንም ክርክር ጭፍን ክህደት ወይም መሣት (መጃጀት) አልያም ቀቢፀ-ተስፋ የተሞላው ቁጭት ከመሆን አያልፍም። የፕሮፌሠር መሥፍን አቋም የክህደት ከሆነ፣ ወላጅ አባታቸውን ዕውቁን ሊቅ አለቃ አስረስ የኔሰውን ክደዋልና የዐማራ ነገድን ኅልውና ከመካድ የሚያግዳቸው የኅሊና ልጓም ይኖራል ተብሎ አይታሰብም። ከመሣት(መጃጀት) የመነጨ ከሆነ ግን አያድርስ! እንዲህ እስኪሆንስ ፈጣሪን «አታቆዬን» ከማለት ሌላ ምን ይባላል። ከቁጭት ከሆነ ነገሩ ሌላ ነው። በቁጭት የአንድን ታላቅ ሕዝብ መኖር ኅልውና ክዶ ስለዚያ ሕዝብ መከራከር እና መጮህ አይቻልም። የቁጭት ተገቢ መገለጫው «አሻፈረኝ! በቃኝ! ተነስ! ዱሩ ቤቴ በል!» በማለት እንጂ «የለህም! የሚያጠፉህ ሳትኖር ነው!» በማለት አይደለም። የሌለ፣ ኅልው ያልሆነ፣ ሊያደርገው የሚችለው ምንም ነገር የለምና!
ፕሮፌሰር መሥፍን «ዐማራ የሚባል ነገድ የለም» ከሚል መደምደሚያ የደረሱት፣ ከፍ ሲል ከተጠቀሱት ከሦሥቱ በአንዱ ወይም በሁሉም ተያያዥነት እንደሆነ ቀደም ካሉት ድርጊቶቻቸው መገንዘብ ይቻላል። የመጀመሪያው በ፲፱፹፫(1983) ዓ.ም. ከሟቹ መለስ ዜናዊ ጋር በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ባደረጉት ውይይት ዐማራን እና ክርስቲያንን የአንድ ሣንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን በመዘንጋት፣ ወይም ሆን ብለው «ክርስቲያን እንጂ፣ ዐማራ የሚባል የለም» ብለው ተከራክረው ስለነበር ያ አቋማቸው ያልተለወጠ መሆኑን እና ዛሬም «በዚያው አቋማቸው የጸኑ ናቸው» ለመባል ከማሰብ የመነጨ፣ ከስህተት ወደ ስህተት የመጓዝ አስተሳሰብ ነው። ሁለተኛው ፕሮፌሠር መሥፍን ክህደት የመታወቂያ ባሕሪያቸው ስለሆነ ትናንት የካዱትን ከ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት በኋላም በክህደቱ የቀጠሉ መሆኑ የሚያመለክት ነው። ይህም ሌላው ግትርና «ያለ እኔ ዐዋቂ የለም» የሚለው የገነገነ አስተሳሰባቸው መገለጫ ነው። ሦስተኛው ከክህደት ባሕሪይ በተጨማሪ በዕድሜ መግፋት ምክንያት የመጣ፣ የኋላን ያለማዬት እና የመሣት አባዜ የገጠማቸው መሆኑን የሚያመለክት ነው። አራተኛው በዘመነ የትግሬ-ወያኔ ዘረኛ አገዛዝ በዐማራው ላይ በተከታታይ እየተፈጸመበት ያለው መገደል፣ መታሠር፣ ከሥራ መፈናቀል፣ ከአገር መባረር፣ መዋረድ እና መጎሳቆል እጅግ በዝቶ የግፉ ጽዋ ሞልቶ የሚፈስበት ደረጃ ላይ ደርሷል። ሆኖም ዐማራው «አሻፈረኝ» ብሎ ወያኔን ግብግብ ከመግጠም ይልቅ የሚሣየውን ሆደ ሠፊነት ከኢዮብ ትዕግሥት በላይ ሆኖ ስላገኙት፥ «ዐማራ የሚባል ነገድ ቢኖር ኖሮ ይህ ሁሉ ጥቃት እና ውርደት ሲፈጸምበት ዝም ብሎ አይመለከትም ነበር! ሌሎቹ እንደሚያደርጉት ኃይሉን አስተባብሮ ጥቃቱን ይቋቋም ነበር! ባለመኖሩ ነው ይኸ ሁሉ ጥፋት የሚፈጸምበት» ከሚል ቁጭት የደረሱበት ድምዳሜ ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል።
ይህ ግን ከዐማራው ባህል፣ ዕምነት፣ አኗኗር፤ ማኅበራዊ ግንኙነት እና የኢትዮጵያዊነት ስሜት ጋር አጣምሮ ለሚያይ ሰው፣ ዐማራው በወያኔ የደረሰበትን ሁለንተናዊ ግፍ እና በደል በአርምሞ በመመልከት ላይ ያለው፣ በደሉ ሳይሰማው ቀርቶ አይደለም። እንዲያውም «የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች» እንዳይሆንበት የትግሬ-ወያኔዎችን ግፍ ለመበቀል ሲል በደልን በበደል መመለስ፣ የትልቂቱን አገሩን የኢትዮጵያን ኅልውና እንዳያፈርስ ኅሊናውን ገዝቶት፣ በሆደ ሠፊነት እና በትዕግሥት ማየቱ፥ ብልኅነቱን፣ አስተዋይነቱን፣ «አድሮ እንየው» ማለቱን፣ ውሽንፍርን እና ጥምዝምዝን አጎንብሶ ማሳለፍ ባህሉ መሆኑን፣ እንጂ፤ ጥቃትን እስከ ዝንተ ዓለሙ የሚቀበል አለመሆኑ ታሪኩ ያስረዳል። «ዐማራ ሰንበሌጥ ነው፤» የሚባለውም እኮ ለዚህ ነው። ማንም እንደሚያውቀው ሰንበሌጥ ኃይለኛ ወዠብ (ነፋስ) ሲመጣበት ለጥ ብሎ ያሳልፋል፣ ወዠቡ ሲያልፍ ይነሣል። ዐማራውም በተደጋጋሚ እና በተከታታይ ሊያጠፉት የተሰለፉትን ኃይሎች ሁሉ ተቋቁሞ እስካሁን የዘለቀው በዚህ መንገድ ነው። ጠላቶቹን የሚያሸንፋቸው በመበቀል ሣይሆን በይቅርታ እና በፍቅር መሆኑን ለአፍታም መዘንጋት አያስፈልግም። የኢትዮጵያዊነት ማገር፣ ዋልታ እና ጭምጭም ሆኖ ለዘመናት የዘለቀውም የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ስሜቱ የዳበረ በመሆኑ ነው። ይህም በመሆኑ ነው የዐማራው ሥነልቦና በድል ጊዜም ሆነ በጥቃት ላይ እያለ የበላይነቱን እንደጠበቀ እንዲዘልቅ ያደረገው።
ዛሬ ወያኔን እና መሠል ቡድኖችን ያስጨነቃቸው ይኸው የዐማራው የኢትዮጵያዊነት ሥነልቦና የበላይነት አልሰበር በማለቱ ነው። እኒህን ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች ሌት ተቀን የሚያባንናቸው ዐማራው ኢትዮጵያዊነትን ማተቡ፣ ዕምነቱ እና የእሱነቱ መገለጫ፤ ሠንደቅ ዓላማውንም ልብሱ፣ ትራሱ እና መጌጫው አድርጎ በዓለም አደባባይ ስለኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት የሚያሰማው ድምፅ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያስገመገመ በመጓዙ ነው።
ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ይህን መግለጫ ለማውጣት የወሰነው በሁለት መሠረታዊ ምክንያቶች ነው። አንደኛው ምክንያት ዛሬ በምንኖርበት የቴክኖሎጂ ዘመን አብዛኛው ሰው የሚያምነው የሚያየውን ብቻ ሣይሆን የሚሰማውንም ጭምር በመሆኑ ነው። እንዲያውም ሰው ከሚያየው ይልቅ የሚሰማውን ይበልጥ አምኖ ይቀበላል። ስለሆነም «ፕሮፌሠር መሥፍን እኮ ዐማራ የሚባል ነገድ የለም ብለዋል» ብሎ የሚቀበለው እና የሚያምነው ሰው ቁጥር ቀላል ስለማይሆን፣ ለዚህ ዓይነቱ አድማጭ ዕውነታውን ማሣወቅ አስፈላጊ ይሆናል። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ፥ ምንም እንኳን ጊዜ እየከዳቸው ያሉ ቢሆንም፣ እስትንፋሳቸው እስካለ ድረስ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሌሎች የክህደት ንግግሮችን ከመናገር ስለማይቆጠቡ፣ ፕሮፌሠር መሥፍን «ዐማራ የለም» ሲሉ የካዱትን ክህደት በተጨባጭ መረጃዎች በማሣዬት ለወደፊት አድማጫቸው እና አንባቢያቸው ከሃዲነታቸውን ከወዲሁ እንዲገነዘብ ለማድረግ ነው። ከዚህ አንፃር የዐማራን ነገድ ከኢትዮጵያ ምድር አልፎ በዓለም ዙሪያ ተሠራጭቶ የሚኖር መሆኑን የሚከተሉት መረጃዎች ያረጋግጣሉ። እነርሱም፦
፩ኛ አካላዊ (ነባራዊነት)፣
፪ኛ አማርኛ የተሰኘ ቋንቋ በኢትዮጵያ መኖር እና በስፋት መነገር፣ እንዲሁም
፫ኛ የጽሑፍ፣ የቃል (ድምፅ) እና የምሥል ማስረጃዎች ናቸው።
፩ኛ. አካላዊ (ነባራዊነት)
አካላዊ ወይም ነባራዊነት ስንል፥ በእጅ የሚዳሰስ፣ በዐይን የሚታይ፣ ግዙፍ፣ ራሱን «ዐማራ ነኝ» ብሎ የሚገልጽ ሰው የተሰኘ ፍጡር በኢትዮጵያ ምድር በስፋት ተሰራጭቶ የሚኖር ሕዝብ ማለታችን ነው። ይህ ሕዝብ ቀደም ሲል ክርስትና ወደ አገራችን ሲገባ ቀድሞ የተቀበለ በመሆኑ ከክርስትና ኃይማኖት ጋር አያይዞ የራሱን ማንነት የሚጠራ፤ ሌሎችም «ዐማራ» ሲሉ «ክርስቲያን የሆነ» ማለታቸው እንደሆነ አድርገው የሚገልጹት፣ በኋላም በጊዜ ሂደት ወደ አገራችን የገቡ ዕምነቶችን ሳይቃወም፣ መቻቻልን መርሑ አድርጎ የተቀበለ እና ከእርሱም ውስጥ የተወሰነው ክፍል የክርስትና ኃይማኖቱን በመተው ሌሎች ዕምነቶችን በመከተል የኖረ፣ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ነገዶች በቁጥር ከፍተኛውን መጠን የያዘ ማለታችን ነው።
ማንም በግልጽ ሊገነዘበው እንደሚችለው፣ ቋንቋ ከሰው በፊት አልተፈጠረም። ቋንቋ ከሰው ልጅ ኅልውና በኋላ የተከተለ የሰዎች የጋራ የመግባቢያ መሣሪያ ነው። ቋንቋ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ይዳብራል፣ ይሞታል የሚባለውም ከሰዎች መኖር ጋር በጥብቅ የተሳሰረ በመሆኑ ነው። በሌላም በኩል ቋንቋ ባህልም ነው። ከጥንት ጀምሮ የቁጥር መጠኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ የሄደ እና ራሣቸውን «ዐማራ ነኝ» በሚሉ ተወላጆች የጋራ ማንነት የተገነባ ነገድ አለ። እኒህ ሰዎች አፋቸውን በአማርኛ ቋንቋ የፈቱ፣ ካለ አማርኛ ቋንቋ ሌላ ቋንቋ መናገር የማይችሉ ኢትዮጵያውያን ናቸው። በመሠረቱም የአማርኛ ቋንቋን መግባቢያ እና መገልገያ ያደረገ ሕዝብ ሣይኖር የአማርኛ ቋንቋ ሊኖር አይችልም። በመሆኑም የኢትዮጵያ ሕዝብ ወይም ነገዶች እና ጎሣዎች አንድ ተብለው መቆጠር ሲጀምሩ በቅድሚያ በማንም ሰው አዕምሮ ውስጥ ድቅን የሚለው ዐማራ ነው። ስለዚህ በማንነቱ ከኢትዮጵያ ኅልውና ጋር በጥብቅ የተሣሰረ «ዐማራ» የሚባለውን የኢትዮጵያ ሕዝብ አካል ኅልውና መካድ ኢትዮጵያን ከመካድ ተለይቶ አይታይም።
ሌላው አካላዊ ማስረጃ «ዐማራ ሳይንት» የተባለው እና በላኮመልዛ(ወሎ) ክፍለሃገር የሚገኘው የአውራጃ ስም ነው። «ዐማራ» የሚባል ነገድ ሳይኖር፣ በዐማራ ስም የሚጠራ የቦታ ስም ሊኖር አይችልም። በሌላም በኩል ከጥንት ጀምሮ በጌምድርና ስሜን(ጎንደር)፣ ጎጃም፣ ሸዋ እና ላኮመልዛ(ወሎ) የተሰኙ የኢትዮጵያ መልከዐ-ምድር አካል የሆኑ ክፍለ-ሀገሮች አሉ። የነዚህ ክፍለ-ግዛቶች አብዛኛው ነዋሪ ሕዝብ ዐማራ በመሆኑ «ዐማራ የሚኖርባቸው» ተብለው የሚታወቁ ናቸው። ከዚህም አልፎ በዘመነ ትግሬ-ወያኔ «የዐማራ ክልል» በመባል የሚታወቀው የኢትዮጵያ ክፍል ኅልውናውን ካስቆጠረ ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት ሆኗል። ስለዚህ ይህን ሁሉ እንዴት መካድ ይቻላል? ለፕሮፌሠር መሥፍን የክህደት መንገዳቸው ማጠናከሪያ አድርገው የሚያቀርቡት «ስለ ዐማራ አጥንቻለሁ» የሚሉት ፈሊጥ ነው። ይህ አጥንቻለሁ የሚሉት ጥናት ዕውነት ከሆነ፥ ባለፉት ዘመናት «የዐማራ ገዥ መደብ፣ ጨቋኝ የዐማራ ብሔር፣ ነፍጠኛ ዐማራ፣ የኢትዮጵያ ብሔር/ብሔረሰቦች ደመኛ ጠላት፣ ወዘተርፈ» እየተባለ ሲወገዝና የመከራ ዓይነቶችን ሲቆጥር ለምን ዝም አሉ? ኢትዮጵያውያን ዐማሮች ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች፥ «አገራችሁ አይደለም እና ውጡ» ተብለው፣ ቤት ንብረታቸውን ተነጥቀው፤ ከደቡብ፣ ከሐረርጌ፣ ከአርሲ፣ ከባሌ፣ ከወለጋ፣ ከኢሉባቡር፣ ከሶማሌ፣ ከቤንሻንጉል-ጉምዝ እንዲሁም ከሌሎችም የኢትዮጵያ ክፍሎች ሲባረሩ፣ ፕሮፌሠር መሥፍን «እነዚህ እኮ ዐማራ አይደሉም፣ የሌላ ነገድ አባሎች ናቸው፤» አላሉም? «እንዲያውም ዐማራ የምትሉት ሰው በምድረ-ኢትዮጵያ የለም፤» ብለው ማስተባበል እንዴት ተሣናቸው? እኒህ ሰው የሌሎችን የኢትዮጵያ ነገዶች እና ጎሣዎች ኅልው መሆን ሲቀበሉ እንዴት የዐማራ ነገድን ኅልውና ሽምጥጥ አድርገው ለመካድ ዳዳቸው? ማንን ለማስደሰት ይሆን?
በደርግ የአገዛዝ ዘመን ስለኢትዮጵያ ነገዶች እና ጎሣዎች በኢትዮጵያ የብሔረሰቦች ጥናት ተቋም በተደረጉት የጥናት ውጤቶች መሠረት፣ የዐማራ ነገድ ከኢትዮጵያ ነገዶች አንጋፋው፣ በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች ተሠራጭቶ የሚኖር፣ እንዲሁም በቁጥርም ከፍተኛው እንደሆነ ያሣያሉ።
ሌላው የዐማራን ነገድ ኅልውና የሚያረጋግጠው ደረቅ ማስረጃ በኢትዮጵያ የተደረጉት የሕዝብ ቆጠራ ውጤቶች ናቸው። ለምሣሌም ያህል፦ በ፲፱፻፸፮ (1976) ዓ.ም. በተደረገው የሕዝብ ቆጠራ ውጤት የኢትዮጵያ ሕዝብ ብዛት ፵፪(አርባ ሁለት) ሚሊዮን ያህል እንደነበረ ይታወቃል። ከጠቅላላው የአገሪቱ ሕዝብ (42 616 876) ውስጥ የዐማራው ነገድ ተወላጆች ብዛት 12 055 250 (አሥራ ሁለት ሚሊዮን ሃምሣ አምሥት ሺህ ሁለት መቶ ሃምሣ) ነበር። ይህም ከአጠቃላይ የአሪቱ ሕዝብ 28.288 ከመቶ እንደነበረ ያሣያል። በሥርጭት ረገድም፥ በሸዋ 23.1 በመቶ፣ በአዲስ አበባ 47.86 በመቶ፣ በወሎ 79.86 በመቶ፣ በጎንደር 84.83 በመቶ፣ በጎጃም 87.58 በመቶ፣ የዐማራ ነገድ ተወላጆች ነበሩ፣ በግለሰብ ደረጃም ሰዎች ማንነታቸውን «ዐማራ ነን» ብለው ማረጋገጣቸው በውል ታይቷል። ዐማራው በሌሎች የአገሪቱ ክፍለ-ሀገሮችም በበቂ መጠን ተሰራጭቶ እንደሚገኝ የቆጠራው ውጤት አሣይቷል። በዚህም መሠረት በሐረርጌ፣ በሲዳሞ፣ በከፋ፣ በወለጋ፣ በጋሞጎፋ፣ በባሌ፣ በአርሲ እና በአሰብ የዐማራው ነገድ ተወላጆች ብዛት ከ1.2 ሚሊዮን በላይ እንደነበረ መረጃው ያስረዳል። በዚያ የሕዝብ ቆጠራ ውጤት የኦሮሞን ቁጥር ከፍ፣ የዐማራን ቁጥር ግን ዝቅ ለማድረግ ሆን ተብሎ የቁጥሮች ጨዋታ የተሠራ መሆኑ ቢታወቅም፣ ዐማራው በቁጥር በአገሪቱ ከሚገኙ ነገዶች እና ጎሣዎች በሁለተኛ ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ያረጋግጣል (ማዕከላዊ የስታትስቲክስ ባለሥልጣን፣ ታኅሣሥ ፲፱፻፹፫ (1983) ዓ.ም.)።
በሁለተኛ ደረጃ በ፲፱፻፹፯(1987) ዓ.ም. በተደረገ የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ አጠቃላዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ብዛት 53 499 248 መሆኑ ተገልጿል። ከዚህ ውስጥ 13 834 297 ያህሉ ዐማሮች መሆናቸውን ያሣያል። በንፅፅር ሲታይ በትግሬ-ወያኔ ዘመን በተደረገው የሕዝብ ቆጠራ ውጤት መሠረት በ፲(አሥር) ዓመታት ውስጥ የዐማራ ነገድ ተወላጆች ቁጥር የጨመረው በ1,779,047 ብቻ ነው። ይህም የቆጠራው ውጤት የወያኔን ዐማራን የማጥፋት የፖለቲካ ዓላማ በጉልህ የሚያሣይ ነው። ሆኖም የዐማራ ነገድ በቁጥሩ ብቻ ሣይሆን በሥርጭትም ጭምር በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች በብዛት የሚገኝ መሆኑን የቆጠራው ውጤት አላስተባበለም። በመሆኑም ወያኔ «የዐማራ ክልል» ብሎ በከለለው ውስጥ ከሚኖረው 13 834 297 ሕዝብ መካከል ዐማራው 81.5 ከመቶ መሆኑን፣ በ«ትግራይ ክልል» ከሚኖረው 3 136 267 ሕዝብ መካከል የዐማራው ነገድ 2.6 ከመቶ በመያዝ በክልሉ በሕዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ እንደሚገኝ ታውቋል። በ«ኦሮሚያ ክልል» ከሚኖረው 18 732 525 ሕዝብ መካከል 9.1 ከመቶ የሚሆነው የዐማራ ነገድ መሆኑን እና ይህም በ«ክልሉ» ከሚኖሩት ነገዶች መካከል ከኦሮሞው ቀጥሎ በቁጥር ከፍተኛው እንደሆነ ያሣያል። አርባ አምሥት(፵፭) ነገዶች እና ጎሣዎችን ባጠቃለለው የ«ደቡብ ክልል» ዐማራው በቁጥር በስምንተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በዚህ «ክልል» 10 377 028 ሕዝብ እንደሚኖር ቆጠራው አሳይቷል። ወያኔ «ሐረሪ» ብሎ የመንግሥትነት ዕውቂያ ከሰጣቸው ክልሎች አንዱ የሆነው የሕዝቡ ቁጥር 131 139 ነው። ከዚህ የ«ሐረሪ ክልል» ነዋሪ ሕዝብ መካከል 52.3 ከመቶው ኦሮሞ ሲሆን፣ 32.6 ከመቶው ዐማራ ነው። ሐረሪዎቹ 7.1 ከመቶ ብቻ ናቸው። እንግዲህ ለእነዚህ አናሣ ቁጥር ለያዙት ነው የአብዛኛውን የኦሮሞ እና የዐማራ ነገዶች ተወላጆች ዕጣ ፋንታ እንዲወስኑ ወያኔ የመንግሥትነት መብት የሰጣቸው። ይህንንም «ዲሞክራሲ ነው» እያሉን ነው። በሶማሌ ክልል 3 439 860 ሕዝብ እንደሚኖር በ፲፱፻፹፱(1989) ዓ.ም. የተደረገው የሕዝብ ቆጠራ ያመለክታል። ከዚህ መካከል በዚያ ክልል ዐማራው 0.69 ከመቶ በመያዝ በሦስተኛነት ደረጃ ላይ ይገኛል።
የ28ንቱ የአዉሮጳ ሃገራት መንግሥታትና ጠቅላይ ሚኒስትሮች፤ ትናንት ብራስል ላይ ልዩ ጉባኤ ካካሄዱ በኋላ ለኅብረቱ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሄርማን ቫን ሮምፑይ እና ለኅብረቱ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኃለፊ ካትሪን አሽተን ፤ ተተኪ መረጡ።
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
በጀልባ ወደ አውሮጳ የሚገቡ አፍሪቃውያን ስደተኞችን ችግር ለማቃለል የተመድ የስደተኞች ጉዳይ ተመልካች መስሪያ ቤት ለአውሮጳ ኅብረት ጥሪ አቅርቦዋል።
የደቡብ አፍሪቃ ግዛት በሆነችዉ ንዑሷ የሌሴቶ ግዛት ንጉሳዊ አስተዳደር ላይ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት መፈፀሙ ተዘገበ። መፈንቅለ-መንግሥቱን ተከትሎ የሌሶቶ ጠቅላይ ሚንስትር ለሕይወታቸው በመስጋት ሀገር ለቀዉ መዉጣታቸዉም ተጠቅሷል።
የደቡብ አፍሪቃ ግዛት በሆነችዉ ንዑሷ የሌሴቶ ግዛት ንጉሳዊ አስተዳደር ላይ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት መፈፀሙ ተዘገበ። መፈንቅለ-መንግሥቱን ተከትሎ የሌሶቶ ጠቅላይ ሚንስትር ለሕይወታቸው በመስጋት ሀገር ለቀዉ መዉጣታቸዉም ተጠቅሷል። ።
የደቡብ አፍሪቃ ግዛት በሆነችዉ ንዑሷ የሌሴቶ ግዛት ንጉሳዊ አስተዳደር ላይ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት መፈፀሙ ተዘገበ። መፈንቅለ-መንግሥቱን ተከትሎ የሌሶቶ ጠቅላይ ሚንስትር ለሕይወታቸው በመስጋት ሀገር ለቀዉ መዉጣታቸዉም ተዘግቦአል።
አንዱዓለም ተፈራ (የእስከመቼ አዘጋጅ)
ባለፈው ጽሑፌ ኢትዮጵያዊነት ማለት ምን ማለት እንደሆነ፤ ከልቤ ያማምንበትን በጥቅሉ አስፍሬ ነበር። በዚያ፤ ኢትዮጵያዊያንን መውደድ ማለት፤ ታሪካቸውን፣ ባህላቸውን፣ ቋንቋቸውን፣ መላ የኑሮ ሁኔታቸውን ጨምሮ ማለት ነው።
ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)
“እኛ ትክክለኛ እና ጠቃሚ የሆኑ በርካታ ነገሮችን አከናውነናል፣ ሆኖም ግን ከዚህ በተለዬ መልኩም ህዝብን አሰቃይተናል፣ ከእሴቶቻችን ጋር ተጻጻሪ የሆኑ ነገሮችን ፈጽመናል። ከፍ ወዳሉ የምርመራ ስልቶች ስንገባ ማለትም ማሰቃየትን ጨምሮ ማንም ሚዛናዊ የሆነ አስተሳሰብ ያለው ሰው እንደሚያስበው እና እንደሚያምነው የምናደርገው ድርጊት ማሰቃየት ሆኖ ሲገኝ መስመሩን አለፍን ማለት ነው። እናም ይህ ጉዳይ ግንዛቤ ሊወሰድበት እና ተቀባይነትንም ማግኘት አለበት“ በማለት ፕሬዚዳንት ኦባማ ከጥቂት ቀናት በፊት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ገልጸዋል።
ዘላለም ክብረት
የኔ ፅጌረዳ ሰላም ላንቺ ይሁን! እንዴት ነሽልኝ? ባለፈው የፃፍኩልሽን ቧልታይ የበዛበት ደብዳቤ አነበብሽው ይሆን? ዛሬ ደግሞ ስለክሴ፣ ስለከሳሼና ስለአጠቃላይ ሁኔታዎች ልጽፍልሽ አሰብኩ፡፡ እንግዲህ በዚህ ደብዳቤ ትንሽ ኮስተር ሳልል አልቀርምና ከወዲሁ ይቅርታን እለምናለሁ፡፡
ግርምቴ
ከታሰርኩበት ሚያዝያ 17/2006 ጀምሮ በጣም ሲገርመኝ የነበረው ነገር የፖሊስ/የመንግስትና የሕግ ታላቅ እኩያ ከተያዝኩበት ደቂቃ ጀምሮ አውቆ በሚመስል መልኩ የተለያዩ የፍትሕ አካላት እያንዳንዱን የሕግ አንቀፆች በተግባር ሊጥሷቸው ማየቴ ነበር፡፡
ለሕጎቹና ለሕግ አካላቱ ቅርብ በመሆኔ ምክንያት የመንግስት አካላቱ ይወስዷቸው የነበሩትን የተለያዩ ርምጃዎች በሕጉ አይን በማየቴ ሊሆን ይችላል የሕግ ጥሰቱ እጅግ ጎልቶ የታየኝ፡፡
የፍተሻ ፈቃድ (Search Warrant) ከእስር ማዘዣ (Arrest Warrant) ጋር በአንድ ወረቀት ላይ ተደባልቆ በመምጣቱ ገና ከመታሰሬ ነው የሕጉ ነገር ያሳሰበኝ የጀመረው፡፡ ሕግ ስንማር የፍተሻ ፈቃድ ከእስር ማዘዣ ተለይቶ እንደሚመጣ፣ በፍተሻ ፈቃዱ ላይ ሊፈተሽ የተፈለገው ነገር በግልፅ ሊቀመጥ እንደሚገባ፣ ፍተሻ ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት መከናወን እንዳለበት …ብንማርም ‹ፖሊስ› በታሰርኩበት ወቅት አንዱንም የሕግ አንቀፅ ላለማክበር ያሰበ በሚመስል መልኩ የፍተሻ ፈቃድን ከእስር ፈቃድ ሳይለይ፣ ፍተሻውን ከምሽቱ 12 ሰዓት በኋላ በመጀመር፣ በፍተሻው ምን ማግኘት እንደሚፈልግ የማይገልፅ የፍተሸ ፈቃድ በማሳየትና እኔ ስጠይቅም ለመናገር ፍቃደኛ ባለመሆን… ሕጉን‹ንዶ ንዶ› የኔን የግለሰቡን መብቶች በዜሮ በማባዛት ‹ወንጀልን የመከላከል እርምጃውን› ጀመረ፡፡ በፍተሻ ወቅት የሚፈለገው ነገር ምንነት አለመገለፁም ፖሊስ ‹ለጠረጠረኝ› ሕገ-መንግሥቱንና ሕገ-መንግሥታዊ ስርዓቱን በኃይል፣ በዛቻና በአድማ የመናድ ወንጀል እንደ ኤግዚቢት የያዛቸው ‹ማስረጃዎች› ምንነት ይገልጣቸዋል፡፡
በፍተሻ ወቅት ፖሊስ ከቤቴ በኤግዚቢትነት ከያዛቸው ‹እቃዎች› መካከል 90 በመቶው ገበያ ላይ ያሉ መጽሐፍት ሲሆኑ ከነዚሀም መካከል የPaulo Coelho “By the river paedra I set down and wept’ PV.I.Lenin ‘what is to be done’ የአፄ ሱስንዮስ ዜና መዋዕል፣ የፍቅረስላሴ ወግደረስ ‹እኛና አብዮቱ›… ጨምሮ ሌሎች መፅሀፍት የሚገኝበት ሲሆን፤ የተለያዩ የሙዚቃ ሲዲዎችም በኤግዚቢትነት ተይዘዋል፡፡
(የሚገርመው ፍተሻው ሕገወጥ መሆኑን ‹ለፖሊስ› በተደጋጋሚ ብናገርም ‹ብርበራ ከጀመርን በኋላ ልናቋርጥ አንችልም›፣ የሚያስፈልገንን ነገር አንተ ልትነግረን አትችልም… የሚሉ መልሶች በመስጠት ‹አዲዮስ ሕግ› የሚል አሰራር ከመከተላቸውም በላይ በቤቴ የተገኘ እንደ ‹አዲስ ራእይ› አይነት መፅሄቶችን የብርበራው መሪ የሆኑ ግለሰብ ለበታች መርማሪዎች ‹ተዉት እሱ የኛ ነው› የሚል አመራር እየሰጡ ግርምቴን አብዝተውት ነበር፡፡ ጉዳዩን አስቂኝ የሚያደርገው ደግሞ በፍተሸው ወቅት ቤቴ ውስጥ ከተያዙት ‹ኤግዚቢቶች› መካከል አንዱም እንኳን ለክስ ማስረጃ ሁነው አለመቅረባቸው ነው፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ለህግ ት/ቤት ‹search is not a fishing expedition in which the police grabs every thing › ተብለን የተማርነው፡፡)
የእስርና የምርመራ ጊዜ ደግሞ ፖሊስ ሕጉን ለመጣስ ሆን ብሎ የተጋ በሚያስመስለው መልኩ ሕጉ ግድ ሳየሰጠው የፈለገውን ሲያደርግ የከረመበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ወቅት ነው ‹እኛ የሚያሳስበን የአንተ የአንድ ግለሰብ መብት ሳይሆን፣የሰማንያ ሚሊዮን ሕዝብ ደህንነት ነው› የተባልኩት (ውዴ! Ayn Rand እንኳንም ይሔን ሳትሰማ ሞተች አላልሽም?)፡፡ በዚህ ወቅት ነው ‹የሽብር ሕጉን ጥርስ አውልቃችሁ አምጡ የሚለን ከሆነ ጥርስ ከማውለቅ ወደኋላ አንልም› ብሎ ፖሊስ ሕገ-መንግስቱንና የዜጎች መብትን በአንድ ላይ ሲቀብራቸው የተመለከትኩት፡፡ (‹ሕገ -መንግስቱ የሀገሩ ህጎች በሙሉ የበላይ ሕግ ነው› የሚለው የህገ መንግስቱ አንቀፅ በምድረ በጋ የተደነገገ እንደሆነ ግንዛቤ ለመጨበጥ ችያለሁ)፡፡ በዚህ ወቅት ነው፡ የፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እንዲፈፀምልኝ ለጠየኩት ጥያቄ ‹ሂድ ከዚህ!የማነው?! ፍርድ ቤት ማነው እኛን የሚያዘው? ከፈለገች ዳኛዋ ራሷ ትፈፅምልህ…› የሚል መልስ ‹ከህግ አስከባሪ ፖሊስ› የተሰጠኝ፡፡
‹‹ምን አይነት ዘመን ነው ፣ የተገላቢጦሽ፤
አህያ ወደ ቤት፣ ውሻ ወደግጦሽ፡፡
ይሏል እንዲህ ነው፡፡ በዚህ ወቅት ነው፤ ምንም አይነት ሕጋዊ መብቶቼ ሳይነገሩኝ ‹ለምርመራ የተቀመጥኩበትና ብሎግ ላይ የተፃፉ ፅሁፎች የእኔ ‹የእምነት ክህደት ›ቃል እንደሆኑ ተደርገው መፃፍ እንዳለባቸው ትእዛዝ የተሰዘጠኝና በእምነት ክህደት ቃሌ ውስጥ ወይ ‹ጥፋተኛ ነኝ› ማለት አለያም ባዶውን መተው እንጂ ‹ጥፋተኛ አይደለሁም› የሚል ነገር መስፈር እንደማይችል የተረዳሁትና ‹ለምን?› ብዬ ስጠይቅም ‹ከበላይ አካል የመጣ ትዕዛዝ› እንደሆነ የተነገረኝ፡፡ (ማሬ፣ ዕድለኛ ባልሆን ኖሮ እንደ ‹አንድ› አባሪዬ ‹ህገ መንግስቱ ተከብሮ እያለ፣ ሕገ-መንግስቱ ይከበር ‹በማለቴ ጥፋተኛ ነኝ› ብለህ ፈርም ተብዬ መከራዬን አይ ነበር፡፡)በዚህ ወቅት ነው፤ መንግስቴ በመጀመሪያ ‹በሽብር ወንጀል› ባይጠረጥረኝም የፀረ-ሽብር ሕጉ አንቀፅ 14 በሚያዘው መሰረት ስልኬን ከግንቦት 2005 ዓ.ም ጀምሮ በመጥለፍ ንግግሬን ሁሉ ሊያደምጥ እንደነበር የተረዳሁትና ‹‹እንዴ ‹የሽብር ተግባራትን ለመፈፀም የማሴር ወንጀል› የተጠረጠርኩት ከታሰርኩ ከ23 ቀናት በኋላ ነው፤ ይሄም ፖሊስ እስከታሰርኩበት 23ኛ ቀን ድረስ በሽብር ጉዳይ ምንም አይነት ጥርጣሬ ያልነበረው ሲሆን ታዲያ ስልኬን አንድ አመት ለሚሆን ጊዜ እንዴት የፀረ ሽብር-ሕጉን ጠቅሶ ሊጠልፍ ቻለ?›› ብዬ ለጠየኩት ጥያቄ መልሱ ዝምታ እንደሆነ የተረዳሁት፡፡ (በነገራችን ላይ ስልኬ ለረጅም ጊዜ ቢጠለፍም ለማስረጃነት የቀረበብኝ ከአባሪዎቼ ጋር ‹ሻይ-ቡና እንበል እስኪ ብለን ያወራናቸው ወሬዎች ሲሆኑ፤ካንቺ ጋር ያውራናቸው ወሬዎች በማስረጃነት ባለመምጣታቸው ቅር መሰኘቴን በዚህ አጋጣሚ እገልፃለሁ፡፡)
ግርምቴ ብዙ ቢሆንም እንዳይሰለችሽ በማሰብ አንድ የመጨረሻ ግርምቴን ልንገርሽና ሌላ ጉዳይ ላይ እናልፋለን፡፡ የእስር፣ የምርመራ፣ የብርበራ … ሁሉ ዓላማ ተጠርጥረው የተጠረጠረበትን ወንጀል የሚያረጋግጥ መረጃ ለማግኘት ቢሆንም ከሁለት ወራት ለሚበልጥ ጊዜ፣ እጅግ የተራዘመ ምርመራ ተደርጎብኝ የቀረበብኝን ክስ ስመለከት ብዙ ነገሮች አስገረሙኝ፡፡ ቀዳሚው ጉዳይ የተከሰስኩበትን ‹የሽብር ተግባር ለመፈፀም የማሴር ወንጀል› በሚመለከት በምርመራ ወቅት አንድም ጥያቄ ያልቀረበልኝ ሲሆን፤ ይሄም ነገር ታዲያ የምርመራው አላማ ምን ነበር? እንድል አድርጎኛል፡፡ ሌላው ገራሚው ጉዳይ የሀገሪቱ ከፍተኛ የምርመራ ሂደት እንዲህ ቧልትና እያንዳንዱን እንቅስቃሴውን ከሕጉ ጋር በመላተም እንደሚያከናውን መገንዘቤ ነው፡፡ ታዲያ ‹ፖሊስ› ህግን ለመጣስ ካለው ትጋት የበለጠ ምን አስገራሚ ነገር አለ ውዴ?!
The Fridgegate Scandal እና ሌሎችም …
እኔ አሁን ደግሞ ወደ ክሴ ልውሰድሽ እስኪ ክሴን ባጭሩ ለማስረዳት ያክል (ምንም እንኳን ክሱ ግልፅ ባይሆንም፣ እኔ እንደመሰለኝ)፤ ‹የሽብር ቡድን በማቋቋም (ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት ለማድረግ የሚልም ‹ይመስላል›)በሀገር ውስጥ የተለያዩ የሽብር ድርጅቶችን (ሰውን ለመግደል የሕብረተሰቡን ጤና ለከፍተኛ አደጋ ለማጋለጥ፣ እገታ ወይም ጠለፋ ለመፈፀም፣ ንብረት ለማውደም፣ በተፈጥሮ፣ በታሪካዊና በባሕላዊ ቅርሶች ላይ ጉዳት ለማድረስ፣ የህዝብ አገልግሎቶችን ለአደጋ ለማጋለጥ ወይም በቁጥጥር ስር ለማዋልና ለማበላሸት) በመዘጋጀት፣ በማሴር፣ በማነሳሳትና በመሞከር የሚለው የመጀመሪያውና ዋነኛው ክሴ ሲሆን፤ሁለተኛው ክሴ ደግሞ ያች የፈረደባት ‹ሕገ-መንግስትንና ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን የመናድ ወንጀል ነው፡፡
ሁለቱም ክሶቼ የቅጣት ጣሪያቸው እስከ ሞት ድረስ መሆኑን መግለፄም አያስከፋሽም ብዬ አስባለሁ፡፡ (ዘጠኝ ሞት መጥቶ ከደጅ ቁሟል ቢለው፣ ስምንቱን ተውና አንዱን ግባ በለው› አለ የሞት ዳኛ፡፡ እንደዳኛው ‹አንዱን ሞት ግባ› ብዬ ከመጋበዜ በፊት ብዙ የማጫውትሽ ጉዳይ አለኝና አስኪ ተከተይኝ ውቤ)
ከሳሼ ‹የሽብር ተግባራትን› ልፈፅም እንደተዘጋሁና እንዳሴርኩ እንዲሁም ‹ሕገ-መንግስቱንና ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል ለመናድ› እንደሞከርኩ ለማስረዳት ያቀረቡልኝ የማስረጃ ዝርዝርን ስመለከት ግን የአሳሪዎችን ፍላጎት ‹ወዲህ› መሆኑን የተረዳሁት፡፡
በምርመራ ወቅት አንድም ጥያቄ ያልቀረበልኝ ‹የሽብር ድርጊት› ዋና ‹ወንጀሌ› ሁኖ ሲመጣ አሳሪዬ ጋር ያለው ፍላጎት ሙሉ ለሙሉ የወንጀል እንዳልሆነ ያስረዳኝ ሲሆን፤ በሰነድ ማስረጃነት ከቀረቡብን ብዙ ገራሚና አስቂኝ ‹ማስረጃዎች› መካከል ‹የሽብር ተግባራትን ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር በመሆን ለመፈፀም እንዳሴርን› ያስረዳል ተብሎ የቀረበው ዋነኛና ብቸኛ ማስረጃም ከጓደኛዬና አባሪዬ አንደኛ ተከሳሽ፣ ሶልያና ሽመልስ (ክሷ In Abesntia) እየታየ ያለችና በአንድ ቀጠሯችን ፖሊስ ከ Interpol ጋር በመሆን ለመያዝ ጥረት እያደረገ እንደሆነ የገለፁት በጥብቅ የምትፈለግ ‹አሸባሪ› ቤት በሌለችበት ፖሊስ ላደረገው ብርበራ ማቀዝቀዣ Fridge ዙሪያ ‹አገኘሁት› ያለው ግንቦት ሰባት የተባለ ፓርቲ በታህሳስ 2005 የወጣ የአባላት የውስጥ Newsletterና ቀኑ በሰነዱ ላይ ያልተመለከተ ሌላ የዚሁ ፓርቲ ሰነድ ነው፡፡
ውዴ ለመረጃ አንች ከእኔ ትቀርቢያለሽና ከላይ ስለጠቀስኩት ‹ሰነድ› ጉዳይ ብዙ ሰምተሻል የሚል ግምት አለኝ፡፡ እኔ ያለኝን መረጃ እና የዚህ ሰነድ ስለክስ ሒደቱ ሊኖረው ስለሚችለው አመላካችነት አንዳንድ ወሬዎችን እያመጣን እንተክዝ እስኪ፡፡
መቼም አሜሪካ ግሩም ሀገር ነው፡፡ ብዙ ነገሮች እንደቅሌት (Scandal) እየሆኑ ሲወጡ የምናይበት የቅሌቶች ሁሉ ቅሌት ድሞ የRichard Nixon ነው ‘The Watergatge scandal’ ይሉታል፤ ኒክሰን በ1972 ለተደረገው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ መረጃ ለማግኘት በማሰብ በ Washington DC የሚገኘውን የዲሞክራቲክ ፓርቲ ICT ዋና መሥሪያ ቤት Watergate የተባለው ሕንፃ ውስጥ) እንዲበዘበዝ በማስደረጋቸውና ይሄም ድርጊታቸው በፕሬሱ ይፋ በመሆኑ ኒክሰን ከስልጠናቸው ተዋርደው እንዲለቁ ሆነ፡፡
የWatergate ብዝበዛን ተከትሎ ብዙ ሐረጎች ለብዙ ሁነቶች መግለጫ በመሆን ይቀርቡም ጀመር ለምሳሌ ‘The Watergate Burglars’ ‘The Saturday Night Massacre:- ‘United States Vs Nixon’…. (የእያንዳንዷን ዝርዝር Google እያደረግሽ እንደምታይው ተስፋ አለኝ አበባዬ)፡፡ ከዛም በኋላ የተለያዩ ቅሌቶችን ከWatergate ጋር እያያያዙ መጥራት የተለመደ ነው፡፡ አሁንም ሌላ ምሳሌ ‘The Monicagate’ የፕሬዚዳንት ክሊንተንን የወሲብ ቅሌት ለመግለጽ)፣( ‘The Nipplegate’ (በ2003 ዓ.ም ጃኒት ጃክሰን በLive የቴሌቪዥን የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ባልታሰበ ሁኔታ ያጋጠማትን የጡት ጫፍ (Nipple) መራቆትና በቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ታሪክን የቀየረ ሁነት ለመግለፅ)፤
ይሔን ሁሉ ማለቴ ወዴት ለመሔድ አስቤ እንደሆነ ሳትረጂው አትቀሪም ፍቅር፡፡ ከላይ ወደጠቀስኩልሽ ግንቦት 7 የተባለ ፓርቲ ሰነድ ጓደኛችን ቤት ተገኝ ስለመባሉ ጉዳይ ላስረዳሽ አስቤ ነው፡፡ ተገኘ የተባለው ሰነድ ላይ ጓደኛችን ወክለው ቤቷን ሲያስፈትሹ የነበሩት እናቷ ‹ይህ ሰነድ ፖሊስ ከፋይሉ ጋር ይዞት የመጣው ሰነድ ነው፡፡ እዚህ ቤት የተገኘ አይደለምና እዚህ ቤት ተገኘ ብዬ ልፈርም አልችልም› ማለታቸው በሰነዱ ላይ በግልጽ የተመለከተ ሲሆን፤ ሰነዱ ተገኘ የተባለበት ቦታ ደግሞ የጉዳዩን አስገራሚነት ያንረዋል- ማቀዝቀዣ (Fridge)! (በነገራችን ላይ ፖሊስ የወንጀል ‹ማስረጃ› ከውጪ ይዞ ቤት ውስጥ በመጣል ‘Eureka’ ‹ማስረጃ› አገኘሁ የሚልበት ልማድ አዲስ አይደለም፤ በኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ጉዳይ የተከሰሱ ብዙ ሰዎች የዚህ ዓይነት ‹ፖሊስ አመጣሽ› ማስረጃዎች ሰለባ መሆናቸውን እያነበብን/እየሰማን ነው የጎለመስነው፡፡ ፖሊስን ወደቤታቸው ፈትሸው ከማስገባት ጀምሮ የተለያዩ ፖሊስን የመጠበቅ አስቂኝ ተግባራትን በቤት ብርበራ ወቅት እንደሚያከናውኑ ስንለውም ኖረናል፡፡ አስቢው እስኪ ውዴ፤ ሕዝብ ፖሊስን ሲጠብቀው የሚኖርበት ሀገር!)
ለማንኛውም ይህ ‹ Fridge ማስረጃ› ‹አገኘሁ› የሚለው የፖሊስ ተግባር ነው… ‘The Fridgegate Scandal’ እንድል ያደረገኝ፡፡ እስርም፣ ክስም፣ ‹ማስረጃም›…. ከአሳሪዬ በኩል መምጣቱ ‹ፍርድም› ከአሳሪዬ በኩል ሊመጣ ይችላል የሚል ስጋት ውስጥ ቢከተኝም ተስፋ አልቆርጥም! ወዳጄ ‘The Fridgegate scandalን’ እንደ አንድ የክስ ሒደቱ ማሳያ ማቅረቤ ‘The Fridgegate Burgalrs’ ለፍትሕ ይቀርባሉ ብዬ በማሰብ አይደለም ወይም በባለስልጣኖቻችን መካከል ‘The Renaissance Massacre’ ተከስቶ ስልጣን ይለቃሉ የሚል ቅዠትም የለኝም፤ይልቁንም (በክርክሩ ሒደት የምናየው ቢሆንም) የቀረቡብን የሰነድ ማስረጃዎች አስቂኝነትና ምን እንደሚያስረዱ ካለመታወቃቸው አልፎ እንዲህ የአሳሪዎቻችን የቅሌት ተግባራት ውጤት መሆናቸውን ከ Alexander Hamilton የFederaliot Paper Number 78:
“The Judiciary is ‘beyond comparison the weakest of the three department of power”
ቃል ጋር አንድ ላይ ስመለከተው ‹ማስረጃ› ፈጣሪው› እና ጠንካራው አሳሪያችን ‹ደካማውን› ፍርድ ቤት እንዳይጫነው ብሰጋ ነው፡፡ ቢሆንም ግን ሁሌም ተስፈኛ ነኝ፡፡ ማሬ በሕግ ቋንቋ (በልሳን) ትንሽ አውርተን ወደ ሌላ ጉዳያችን እንሂድ፡፡ ያን ረጅም የምርመራ ሂደት አልፈንና ሕግ-አስፈፃሚው ሂደቱን እንዲያስጠብቁ በሕግ-አውጭው የወጡትን የስነ-ስርዓትና መሰረታዊ የመብት መጠበቂያ (Procedual and substantive) ሕጎችን አንድ በአንድ እየሰባበረ ለሕግ ተርጓሚው አካል ያቀረባቸውን ‹የወንጀል ድርጊት ማሳያ ማስረጃዎችን› በሕግ ትምህርት ቤት ‘The Fruits of Poisonous free’ የተባሉት ሲሆኑ፤ ተስፋዬም ከሶስቱ የመንግሥት አካላት ደካማ የተባው ሕግ ተርጓሚው አካል የቀረበለት ነገር በትክክል ‹ፍሬ› እንዳልሆነ ይገነዘባል የሚል ሲሆን፤ ያ ካልሆነም ‹ፍሬው› ከተመረዘ ዛፉ ለሕግ ተርጓሚው አካል በግድ ካልገመጥ አይለውም አይባልም፤ ዛፉን ለመመረዝ አካል ፍሬውን ለማስገመጥ አይሰንፉምና፡፡ ፍቅር! ለማንኛውም ተስፋ ጥሩ ነው፡፡
መንግስቱ ኃይለማርያም ደሳለኝን (MHD) አየኋችሁ
የኔ እመቤት! እውነት እውነት እልሻለሁ እንደ መታሰር ያለ አስተውሎትን የሚያሳድግ ነገር የለም፡፡ ምክንያቴን ከነማስረጃዬ አቀርባለሁ፡፡ ያኔ በዞን ዘጠኝ እያለሁ (ከመታሰሬ በፊት) ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝን አጠር አድርገን ‘HMD’ በሚል አፅርሆት እንጠራቸው ነበር፡፡ መታሰሬ ግን ዓይኔን አበራልኝና የእስከዛሬው አጠራራችን የፊደል መፋለስ እንዳለበት ለመረዳት ችያለሁ፡፡ እንዴት?
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለሽብር፣ ስለእስርና ስለመንግስታቸው አቋም በቅርቡ ተጠይቀው የሰጡትን ምላሽ በኢቲቪ ተመለከትኩ፡፡ ‹‹እነዚህ አሸባሪዎች ከአስመራ እስከ ሞቃዲሾ የተዘረጋው የሽብር ሰንሰለት አካላት ናቸው (በነገራችን ላይ በቅርቡ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ከደቡብ ሱዳን ጁባ ተይዘው መምጣታቸውን ተከትሎ የሽብር ሰንሰለቱ ከአስመራ-ሞቃዲሾ-ጁባ ተለጥጦ ሶስት ማዕዘን መስራቱን መንግስት እየገለፀ ነው) ጋዜጠኛ ነኝ፣ ብሎገር ነኝ እያሉ የሽብር ዓላማን ማንገብ አይቻልም፡፡ እናንት ጋዜጠኞችም ተጠንቀቁ….›› አይነት ዱላ ቀረሽ ዛቻ ሲያሰሙ ተመልክቼ እንደሰውየው ‹ ኃይለማርያም አሁንስ መንግስቱን መንግስቱን መሰልከኝ ማለቴ አልቀረም፡፡ ለዛም ነው ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ መንግስቱ ኃይለማርያም ደሳለኝን (MHD) የሚለውን ስያሜ አፌ ላይ አልጠፋ ያለው፡፡
እንደዱሮው ‹ይሄ በፍርድ ቤት የተያዘ ጉዳይ ስለሆነ አስተያየት መስጠት አልፈልግም› ማለት ቀረና እንደዳኛ ግራና ቀኝ የተቀመጡትን ጋዜጠኞች እየገላመጡ ቢሯቸው ውስጥ ፍርድ ስጡኝ፡፡ ሌላው ሁሉ ይቅር በሕግ ፊት ነፃ ሆኖ የመገመት ሕገመንግስታዊ መብቴን ያክብሩ አላልኩም፡፡ ባይሆን የቀረበብኝን ‹ማስረጃ› ተመልክተው ፍርድዎችን ይስጡም አልልም፡፡ ግን ግን ‹ለባንዲራ ፕሮጀክታችን› (የሕዳሴው ግድብ) ማሰሪያ ይሆን ዘንድ የሁለት ወር ደመወዜን ለቦንድ መግዣ (ምንም እንኳን ለቦንድ ግዢ ጠቅላላ ክፍያ ሳልጨርስ ከስራ በመሰናበቴ ምክንያት ደመወዜ ቢቋረጥም) መስጠቴን እንደውለታ ቆጥረው በቤተ-መንግስት የዘረጉት ‹የፍርድ ችሎት› ላይ ምህረት ቢያደርጉልኝ ምን አለ? ‹ወርቅ ላበደረ ጠጠር፣ እህል ላበደረ አፈር› ይሰጡታልን?
ውቤ! ለማንኛውም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተበየነብንን የሽብርተኝነት ካባ በፍርድ ቤት እንደማይፀናብን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
‹የነሲቡ ችሎት›
አፈ ንጉስ ነሲቡ መስቀሉ ከ1874 ዓ.ም ጀምሮ ወደ 30 ዓመት ለሚሆን ጊዜ በዳኝነት የተለያዩ የኢትዮጵያን ነገስታት ያገለገሉ ሲሆን ፍርዳቸው እጅግ ከባድና ጠንካራ ስለነበር በዘመኑ ‹እባክህ ከነሲቡ ፊት አታቁመኝ› እየተባለ ይለመን እንደነበር መርስኤ ሀዘን ወልደቂርቆስ በዓይን ያዩትን፤ በጆሮ የሰሙትን፤ ከትበው ይነግሩናል፡፡ በተመሳሳይ ጉዳይ በንጉሱ ዘመን አርሲ፣ አሰላ ላይ እጅግ ጨካኝ ደኛ ተሹመው ፍርዳቸው ከባድ ከመሆኑ የተነሳ ‹አቤት አቤት፤ የአሰላው ፍርድ ቤት› እስከመባል ደርሶ እንደነበር አሁንም ማስረጃችን ታሪክ ነው፡፡
ውዴ! ይሔን የምፅፍልሽ የእኛው ዘመንን ‹የነሲቡ ችሎት› አስመለክቶ ትንሽ ነገር ብዬሽ ደብዳቤዬን ልቋጭልሽ በማሰብ ነው፡፡ አዋጅ ቁጥር 652/2001 (የፀረ-ሽብር አዋጅ) ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ በሽብር ጉዳዮች ላይ ስልጣን (Juridiction) ያለው የፌዴራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት እንደሆነ በመደንገጉ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ተኛ ወንጀል ችሎት የተለያዩ በፀረ-ሽብር ሕጉ የተከሰሱ ግለሰቦችንና ቡድኖችን ጉዳይ እያየ የቆየ ሲሆን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ‹የፀረ-ሽብር ሕጉ ሰለባዎች› እየተበራከቱ በመሔዳቸው ምክንያት 4ተኛውን ወንጀል ችሎ ለማገዝ በማሰብ 19ኛ ወንጀል ችሎ የሽብር ጉዳዮችን በማዬት ላይ ይገኛል፡፡
በፀረ ሽብር ሕጉ ተከሰውኖ 4ተኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ነፃ የወጡ (Acquit) ሰዎች ብዛት ለጊዜው ለማወቅ ባልችልም እጅግ በጣም ትንሽ እንደሆኑ ግን እርግጠኛ ነኝ፡፡ ይህ የሆነው ችሎቱ ከሌሎች ችሎቶች የተለየ በመሆኑ እንዳልሆነም አስባለሁ፡፡ ይልቁንም ችሎቱ የሚይዛቸው ጉዳዮች በፀረ-ሽብር ሕጉ አግባብ ለማየት ስለሚገደድ ነው፡፡ መቼም የፀረ-ሽብር ሕጉን አሳፋሪነትና ጅምላ ጨራሽነት ላንች እንዳዲስ በመንገር ጊዜሽን አላባክንብሽም፡፡ ለዛም ነው በዚህ ዘመን ‹እባክህ ከ4ተኛ ወንጀል ችሎት ፊት አታቁመኝ› ወይም ‹አቤት አቤት፣ 4ተኛው ወንጀል ችሎት› ብንል ብዙም የማያስገርመው፡፡ የፀረ-ሽብር ሕጉ ከሚሰጠው ሰፊና ጠቅላይ የሆነ የወንጀል ትርጉም አንፃር ከልብ ወለዳዊው ‘Moratorium on the Brain’ አዋጅ ጋር በተነፃፃሪ መቆም የሚችል ከመሆኑም በላይ በሽብር ጉዳይ የተሰየወን ችሎትም እጅግ አሳፋሪ ያደርገዋል፡፡
እንግዲህ የእኛም ጉዳይ የ4ተኛ ወንጀል ችሎት እህት ከሆነው 19ነኛ ወንጀል ችሎት እየታዬ የሚገኝ ሲሆን የፀረ-ሽብር ሕጉም ‹ሰለባ› ፍለጋ በችሎታችን ተገኝቷል፡፡ እንግዲህ አበባዬ ጉዳያችን በፀረ-ሽብር ሕጉ ከመታየቱ ጋር ተያይዞ ስራ አስፈፃሚው አካል ‹ማስረጃ› ፈጥሮ የከሰስን መሆኑ ነው ችሎቱን ‹የነሲቡ ችሎት› ያደረገው፡፡ ለማንኛውም ግን ይሄን ስታነቢ ታዲያ ‹ከአንበሳ መንጋጋ፣ ማን ያወጣል ስጋ› ብለሽ ተስፋ እንደማትቆርጪ አምናለሁ፡፡ እኔና አንች እኮ ተሸንፈን አናውቅም ውዴ፡፡ ሁሌም ማሸነፍ፣ ሁሌም ሌላ ተስፋ ማድረግ፣ ሁሌም ደስተኛ መሆን፣ ሁሌም መዋደድ የሕይወት ግባችን አይደለምን ? ታዲያ ይችን ክስ በድል እንዳንወጣት ማን ያግደናል? ምን አልባት አሳሪያችን፡፡ Hamilton በድጋሚ ጠቅሼልሽ ተስፋችንን አለምልመን እንለያይ፡
‘The Judiciary (…) has no influence over either the sword or the purse (…) It may truly be said to have neither force nor will, but merely judgement’
Amen!
ያንችው ዘላለም
ከብዙ ፍቅር ጋር!
ባለፈው ጽሑፌ ኢትዮጵያዊነት ማለት ምን ማለት እንደሆነ፤ ከልቤ ያማምንበትን በጥቅሉ አስፍሬ ነበር። በዚያ፤ ኢትዮጵያዊያንን መውደድ ማለት፤ ታሪካቸውን፣ ባህላቸውን፣ ቋንቋቸውን፣ መላ የኑሮ ሁኔታቸውን ጨምሮ ማለት ነው። ሀገራችንን ኢትዮጵያን ማፍቀር ደግሞ፤ ዳር ደንበሯ፣ የተፈጥሮ ሀብቷ፣ ወንዞችና ተራሮቿ፣ ደጋ፣ ወይነደጋና ቆላ ምድሯ፣ አራዊቷ፣ የሚለዋወጡ አራቱ የሀገራችን አየር ጠባይ ወቅቶችን ማለት ነው። ሀገር ያለ መንግሥት ችግር ነው። መንግሥት ደግሞ […]
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ነሃሴ ፳፫(ሃያሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ አገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ነጋዴዎች ለኢሳት እንደገለጹት መንግስት በሰበብ አስባቡ ከገበያ እያስወጣቸው ነው።አንዳንድ ነጋዴዎች አድሎአዊ በሆነ ሁኔታ ከሚጣለው ግብር በተጨማሪ ፣ በአስተዳደራዊ በደሎች እየተማረሩ ነው። በአዋሳ ነዋሪ የሆኑ አንድ ነጋዴ እንደተናገሩት፣ ኢፍትሃዊ በሆነ መንገድ በተጣለባቸው ግብር ድርጅታቸውን ሸጠው ስደት ለመምረጥ እየተገደዱ ነው በሚዛን ተፈሪ ነዋሪ የሆኑ ሌላ አስተያየት ሰጪ …
ነሃሴ ፳፫(ሃያ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በለንደን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ፊት ለፊት በየሳምንቱ የሚካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬም በጠነከረ ሁኔታ ተካሂዷል። የተቃውሞ ሰልፉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱን በስፍራው የምትገኘው መታሰቢያ ቀጸላ ገልጻለች። አቶ አንዳርጋቸው ባለቤት ወ/ሮ የምስራች ሃ/ማርያምም በተቃውሞ ሰልፉ እና በእንግሊዞች አቋም ዙሪያ ተናግረዋል።
ነሃሴ ፳፫(ሃያሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ከተማ በኢንቨስትምንት ስራ ላይ ከተሰማሩት በውጪ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጽያዊን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ወይንም የዲያስፖራ አባላት መካከል በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩት 7 በመቶ ብቻ መሆናቸው አሳሳቢመሆኑን አንድጥናትአመለከተ፡፡ የዲያስፖራው አባላት 93 በመቶ ያህል የተሰማሩባቸው ሥራዎች የአገልግሎት ዘርፎች ማለትም በሆቴል እና በተለያዩ የንግድ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ መሆናቸውን ያመለከተው ጥናቱ አባላቱ በቴክኖሎጂ …
ነሃሴ ፳፫(ሃያሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኮሌጁ የሚማሩ ከ1 ሺ በላይ የክረምት ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠው ለመውጣት የተገደዱት የትምህርቱ ጊዜ በመራዘሙ ነው። የኮሌጁ አስተዳደር ቀደም ብሎ ለ4 አመት ይሰጥ የነበረው ትምህርት ወደ 6 አመት እንደሚራዘም የገለጸላቸው ሲሆን፣ ተማሪዎቹ የኮሌጁን ውሳኔ ተቃውመዋል። “ብትፈልጉ ተማሩ ወይም ግቢውን ልቀቁ መባላቸውን” የገለጹት ተማሪዎች፣ በዚህም የተነሳ ግቢውን ለቀው ወደ መጡበት መመለሳቸውና …
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
በደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች መካከል በምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ኢጋድ አደራዳሪነት የተኩስ አቁም ብቻ ሳይሆን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በየሚካሄደዉ ንግግር ሰሞኑን አንድ ሰነድ ተፈራርመዋል።
ሰሞንን የወጣ አንድ ጥናት እንደሚያመላክተው አውሮፓ ውስጥ የወጣት ሥራ አጡ ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃጸር በ30 000 ከፍ ብሎ 7,5 ሚሊዮን ደርሷል።
ሰሞንን የወጣ አንድ ጥናት እንደሚያመላክተው አውሮፓ ውስጥ የወጣት ሥራ አጡ ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃጸር በ30 000 ከፍ ብሎ 7,5 ሚሊዮን ደርሷል።
አህምት ዳቩቶግሉ ቱርክን የሚያሥተዳድረዉ የፍትሕ እና የልማት ፓርቲ በቱርክኛ አፅሮቱ የ «AKP» ዋና ሊቀመንበር ሆነዉ ተሾሙ። እስከ ዛሬ የቱርክ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነዉ ያገለገሉት አህሜት ዳቩቱግሉ በተጨማሪ፤ የሃገሪቱ ፕሬዚደንት በመሆን በአዲስ የተመረጡትን የሬሴፕ ተይፕ ኤርዶኻንን የጠቅላይ ሚኒስቴርነት ስልጣንንም ተረክበዋል።
አህምት ዳቩቶግሉ ቱርክን የሚያሥተዳድረዉ የፍትሕ እና የልማት ፓርቲ በቱርክኛ አፅሮቱ የ «AKP» ዋና ሊቀመንበር ሆነዉ ተሾሙ። እስከ ዛሬ የቱርክ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነዉ ያገለገሉት አህሜት ዳቩቱግሉ በተጨማሪ፤ የሃገሪቱ ፕሬዚደንት በመሆን በአዲስ የተመረጡትን የሬሴፕ ተይፕ ኤርዶኻንን የጠቅላይ ሚኒስቴርነት ስልጣንንም ተረክበዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በመስተዳድር 3 ሰሜናዊ ጫፍ ዋግ ሃምራ አካባቢ በሚገኙ አንዳንድ ቀበሌዎች የዝናም እጥረት ባስከተለው ድርቅ ሳቢያ፣ አንዳንድ የአካባቢው አርሶ አደሮች ለረሃብ መጋለጣቸውን ለአዲስ አበባው ዘጋቢአችን ለዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ገልጸውለታል።
ነሃሴ ፳፪(ሃያሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምርጫ 97 ለተገደሉት እና ለቆሰሉት ፍትህ ለመጠየቅ የተቋቋመው ግብረሃይል ስራውን አጠናቆ ዛሬ የ13 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትንና የመከላከያ ሰራዊት አዛዦችን ስም ዝርዝር የያዘ የክስ ማመልከቻ ለስዊድን አለማቀፍ የጦር ወንጀል መርማሪ ፖሊስ አስረክቧል። አርከበ እቁባይ፣ በረከት ስምኦን፣ አባ ዱላ ገመዳ፣ ሳሞራ የኑስ፣ አባይ ጸሃየ፣ ጌታቸው አሰፋ፣ ሌ/ጄ ታደሰ ወረደ፣ ሃሰን ሺፋ፣ …
ነሃሴ ፳፪(ሃያሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ መንግስት በፋክት፣ አዲስ ጉዳይ፣ ሎሚ፣ እንቁ፣ ጃኖ መጽሄቶችና አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ ላይ ፍትህ ሚኒስትር ክስ መመስረቱን ተከትሎ ሚዲያዎቹ ከህትመት በመውጣታቸው ምክንያት ስራ ሊያቆሙ መሆኑን የጋዜጣ አዙዋሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በአራት ኪሎ፣ ፒያሳ፣ መርካቶ፣ ሳሪስ፣ ቦሌና ካሳንቺስ የሚገኙ የጋዜጣ አዙዋሪዎች በርካታ አንባቢ የነበራቸው መጽሄቶችና ጋዜጦች ከገበያ በመውጣታቸው፣ ሌሎቹን ጋዜጦችና …
ነሃሴ ፳፪(ሃያሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግብጽ ጋዜጦች እንደዘገቡት ኢትዮጵያ ለወራት ውድቅ ስታደርገው የነበረውን ስምምነት ከግብጽ ጋር ተፈራርማለች። አዲሱ ስምምነት የአባይ ግድብ ግንባታ በውጭ አገር ገለልተኛ አጥኚዎች እንዲጠናና ኢትዮጵያም የጥናቱን ውጤት እንድታከብር የሚያስገድድ ነው። በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ሲደራደሩ የቆዩት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ ከወራት በፊት ሱዳን ላይ ተካሂዶ በነበረው የሰላም ስምምነት ላይ ግብጽ …
ነሃሴ ፳፪(ሃያሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደሚሉት በመቀሌ፣ ባህር ዳርና በተለያዩ የጤና ተቋማት የሚሰሩ ሙያተኞች መንግስት በቅርቡ ያደረገው የደሞዝ ጭማሪ ሙያችንን ግምት ውስጥ ያስገባ አይደለም በማለት ስራቸውን እየሰሩ ቀይ ሪባን በመልበስ ተቃውሞ እንደሚጀምሩ ታውቋል።ዲፕሎማ እንዳላቸው የሚገልጹት ሰራተኞች መንግስት የስራ ዝርዝራቸውን ለይቶ እንዲያስቀምጥላቸውም ይጠይቃሉ። በሀረር ከተማ ደግሞ ከ400 ያላነሱ በጽዳት ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች …
ነሃሴ ፳፪(ሃያሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮ- ቴሌኮም በአዲስ አበባ የኢንተርኔት አገልግሎትን በማሳደግ የ4ጂ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትደረጃደርሻለሁቢልምየአገልግሎቱጥራት በከፍተኛደረጃእየወደቀመምጣቱተጠቃሚዎችበከፍተኛደረጃምሬትውስጥእየከተተነው፡፡ በ1 ነጥብ 6 ቢሊየንዶላርወጪየቻይናዎቹሁዋዌእናዜድቲኢየሚባሉኩባንያዎችየማስፋፋፊያውንፕሮጀክትለመስራትከኢትዮቴሎኮምጋር በዚህዓመትመጀመሪያየተፈራረሙሲሆንየአዲስአበባውፕሮጀክትእስከሰኔወር 2006 ዓ.ምመጨረሻተጠናቆየተሻለአገልግሎትመስጠት ይጀምራልተብሎነበር፡፡ ኢትዮቴሌኮምየማስፋፊያፕሮጀክቱበስኬትተጠናቋልበሚልተደጋጋሚመግለጫየሰጠሲሆንነገርግንበአሁኑወቅትየሞባይልሒሳብለመሙላትና ቀሪሒሳብለመጠየቅአለመቻል፣የፈለጉትንሰውበቀላሉደውሎማግኘትአለመቻል፣ያልደወሉበትሒሳብ መቆረጥ፣የሞባይልኢንተርኔትበተለይፈጣንነውየተባለውን 3ጂጨምሮደካማመሆን፣ የፌስቡክአካውንትአለመከፈት፣የገመድአልባኢንተርኔትና ብሮድባንድኢንተርኔትአገልግሎትመቆራረጥናደካማመሆንበስፋትእየታየነው፡፡ ያነጋገርናቸውተጠቃሚዎችየአፍሪካህብረትናየሌሎችዓለምአቀፍተቋማትየሆነችውአዲስአበባጥራትያለውየሞባይልናኢንተርኔትአገልግሎት ብርቋመሆኑእንደሚያሳዝናቸውተናግረዋል፡፡አንድአስተያየትሰጪእንዳሉትኢትዮቴሌኮምየተሻለማስፋፊያአድርጌለሁእያለበተግባርይህ አለመታየቱምናልባትምመንግሥትበተለይበማህበራዊ ድረገጾችእየተሰነዘረበትያለውንጠንካራተቃውሞናትችትለማፈንየተጠቀመበትአዲስዘዴሊሆንይችላልየሚልጥርጣሬእንደገባውተናግሮአል፡፡ የኢንተርኔትኔትወርክእንደመብራትብልጭድርግምእያለብዙዎችበመበሳጨት አገልግሎቱንእየተውነውያለውአስተያየትሰጪያችንመንግሥት በዚህሒደትከሚያጣውገንዘብይልቅተቃዋሚዎቹን ለማፈንትልቅግምትሳይሰጠውእንዳልቀረአስረድቷል፡፡
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
የዓለም አቀፉ የ «ጋዝፕሮም » ኩባንያ ባንክ (GPB Global)በሰሜን ምሥራቅ ኢትዮጵያ በአፋር መስተዳድር፤ ነዳጅ ዘይ ት ለመፈለግ ከአንድ ወር ገደማ በፊት ውል መፈራረሙ ተመልክቷል።በኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝና ነዳጅ ዘይት አሳሽ ኩባንያዎች፣ እስካሁን
ሚንስትሩ ግብፅ ኮሚቴዉ እንዲስየም ተስማማች ማለት «የግድቡን ግንባታ በይፋ ተቀበለች ማለት አይደለም» በማለት አጠቃላይ ዉዝግቡን ለማስወገድ ሰወስቱ ሀገራት አሁንም ብዙ መራቃቸዉን አልሸሸጉም።
ካለፈው ግንቦት ወር ጀምሮ በዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ማኅበር አዘጋጅነት በተለያዩ ከተሞች በመካሄድ ላይ ያለው የዳይመንድስ ሊግ ዛሬ ምሽት በስዊትዘርላንድ የዙሪኽ ከተማ በሚደረጉ ውድድሮች ይፈፀማል።
የሩዋንዳ ከፍተኛ ባለስልጣናት በያዝነዉ ሳምንት መጀመርያ ለእስር ተዳርገዋል፤ በርካታ ሰዎችም ያሉበት ቦታ አይታወቅም። የደረሱበት እስካሁን ያልታወቁት ዜጎች ከመንግሥት ተቃዋሚ ወገን ብቻ ሳይሆን፤ ከደጋፊዎችም በኩል መሆኑ ተመልክቶአል። በዚህም ምክንያት የፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ የአገዛዛዊ መንግሥት ሃገሪቱን ሥጋት ላይ መጣሉ እየተነገረ ነዉ።
መንግሥት በአንዳንድ የግል ጋዜጦች ላይ ክስ ከመሠረተ እና ባለፈው ግንቦትም ዘጠኝ ጋዜጠኞች እና የድረ ገፅ አምደኞች ከታሰሩ ወዲህ ቁጥራቸው ትንሽ የማይባል ጋዜጠኞች ኢትዮጵያን ለቀው ወጥተዋል።
ቡሄን አስታከን ሆያ ሆዬን ይዘን ብቅ ያልነዉ ዘግየት ብለን ቢሆንም፤ እንደ ባህላችን አዲስ ዓመት ጠብቶ መስቀል በዓል እስኪከበር ሆያሆዬን መጨፈራችን የታወቀ ነዉና፤ ዛሬም ጀርመናዉያኑ ሆያ ሆዬ ባስጨፈሩበት የኢትዮጵያ ባህላዊ የቡሄ ዜማ የዕለቱን ዝግጅት ለመጀመር ወሰን። ሆያሆዬ ያስጨፈሩት ጀርመናዉያኑ የሙዚቃ ባንድ ካሪቡኒ አዲስ ይባላል።
የጀርመን መንግሥት ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ስደተኞች የምግብ ርዳታ አቅርቦት የሚውል 750,000 ዩሮ ርዳታ ሰጠ። በአፍሪቃ ስደተኞችን በማስተናገድ ረገድ በወቅቱ የአንደኛውን ደረጃ የያዘችው ኢትዮጵያ ገንዘቡ ለሚቀጥሉት አራት ወራት የሚያስፈልገውን ምግብ ለማቅረቢያ እንደምታውለው የጀርመን ኤምባሲ አስታውቋል።